Addis Ababa Design And Construction Works Bureau
📈 Telegram kanali Addis Ababa Design And Construction Works Bureau analitikasi
Addis Ababa Design And Construction Works Bureau (@addiscitycon) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 20 684 obunachidan iborat bo'lib, Siyosat toifasida 2 844-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 1 626-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 20 684 obunachiga ega bo‘ldi.
13 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 96 ga, so‘nggi 24 soatda esa 8 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 11.99% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 8.85% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 2 480 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 832 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 15 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“Government Organization”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 14 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Siyosat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 14 Iyun | 0 | |||
| 13 Iyun | +8 | |||
| 12 Iyun | 0 | |||
| 11 Iyun | +9 | |||
| 10 Iyun | +13 | |||
| 09 Iyun | +7 | |||
| 08 Iyun | +7 | |||
| 07 Iyun | 0 | |||
| 06 Iyun | +4 | |||
| 05 Iyun | +5 | |||
| 04 Iyun | +16 | |||
| 03 Iyun | 0 | |||
| 02 Iyun | +7 | |||
| 01 Iyun | +2 |
| 2 | ለስፖርት መሠረተ-ልማት ልዩ ትኩረት በመስጠት የትውልድ የዘመናት ጥያቄን የመለሰችው አዲስ አበባ!
ከዚህ ቀደም የአዲስ አበባ ጎዳናዎች ለህፃናት፣ ለአዋቂዎችና ለወጣቶች ምቹ ያልነበሩ ተሽከርካሪ እና እግረኛ እኩል የሚጋፋባቸው ለአደጋ የተጋለጡ በተለይም በየመንደሩ የሚኖሩ ታዳጊዎች ኳስ ለመጫወት የተመቸ ቦታ ባለማግኝታቸው እራሳቸውን ለአደጋ አጋልጠው የተሽከርካሪን መንገድ ዘግተው ሲጫወቱ ማየት የተለመደ ነበር። ዛሬ ይህ ታሪክ ሆኖ አልፏል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚሰራቸው ስራዎች ሁሉ ለታዳጊዎች ፣ ለወጣቶች እና ለህፃናት ምቹ ከተማን በመገንባት የከተማዋ ጎዳናዎች ለሁሉም ተስማሚ እንዲሆኑ ዘመን ተሻጋሪ ስራዎች አከናውኗል፡፡ በተለይም ለስፖርቱ ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመሰጠቱ በማዘመንና ተደራሽነቱን በማስፋፋት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ 1,547 ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በመገንባት ለአገልግሎት አብቅቷል፡፡
እነዚህ መሠረተ ልማቶች፣ ነዋሪው በቅርበት ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን እንዲያከናውን በማስቻል የከተማዋን የስፖርት ገጽታ በከፍተኛ ደረጃ ቀይረውታል።
በተጨማሪም የአካል ብቃት እንቅስቃሴን የህይወት ዘይቤና ባህል በማድረግ ህብረተሰቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበት እና በሚሰራበት አካባቢ የአካል ብቃት እንቅስቃሴን በማዘውተር ጤናማና አምራች ዜጋ እንዲሆን እንዲሁም የጋራ ትውስታ (Shared Memories) እንዲኖረው አስችለውታል ። | 1 454 |
| 3 | በሽታን ከመከላከል ኣክሞ እስከማዳን ዓቅም የገነባች፣ የጤና ቱሪዝም ማዕከል ውቢቷ መዲናችን አዲስ አበባ!
ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተገነቡ፣ የታደሱ የጤና ተቋማት የአዲስ አበባን በጤና መሠረተ-ልማት ልዕልና ማሳየት የቻሉ ከመሆናቸው በተጨማሪ፣ የጤና ቱሪዝምን በማሳደግ የዘርፉን የአገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ያላቁ ዘመን ተሸጋሪ፣ ትውልድ አኩሪ ስኬታማ ሥራዎች ናቸው፡፡
በመዲናችን አዲስ አበባ፣ ለዜጎች ጤና ቅድሚያ በመስጠት ከተማዋ ንፁህ፣ ምቹ እና ለመኖር ምቹ ከማድረግ ጎን-ለጎን ለእግር ጉዞ፣ ለብስክሌት እና መሰል ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች የተመቹ ስፍራዎች፣ ለጤና ጠንቅ የነበሩ የተበከሉ ወንዞች አክሞ ለአፍንጫም ለአይንም ውብ እንድትሆን በትኩረት በመስራት፣ በሽታን አስቀድሞ ለመከላከል እንዲያስችል ተደርጎ ተሰርቷል፡፡
ከመከላከል ባለፈ፣ የዜጎችን ጤና ለመታደግ፣ አክሞ ለማዳን የሚያስችሉ እንደነ ላፍቶ ሆስፒታል በምስራቅ አፍሪካ የመጀመርያ የሆኑ የህክምና ግብኣት የተሟላላቸው አዳዲስ ዘመናዊ ሆስፒታሎችና ጤና ጣቢያዎችን በመገንባት፣ እንዲሁም ነባሮቹን እንደነ ዘውዲቱ ሆስፒታል እና ሌሎች ከዘመሙበት ቀና አድርጎ ዳግም በማነፅ፣ በሰው ሃይል እና በዘመናዊ ቁሳቁስ በማደራጀት ቀን-ከሌሊት እየሰራ ይገኛል፡፡ ከዚሁም ባለፈ፣ ዜጎች የተሸለ ህክምና ለማግኝት ወደ ሌሎች ሀገራት የሚያደርጉት ጉዞ ማስቀረት አስችለዋል፡፡ በአንፃሩ በከባቢው የሚገኙ ሃገራት ለተሸለ ህክምና የሚመጡባት የጤና ቱሪዝም ማዕከል በመሆን ትገኛለች፡፡
አዲስ አበባ የሁለንተናዊ ዕድገት ካባ የተጎናፀፈች ከተማ! | 1 863 |
| 4 | ጎስቋላ ከባቢዋን የቀየረችው አዲስ አበባ!
መዲናችን አዲስ አበባ፣ ዕድሜ ጠገብ ባለታሪክ ከተማ ብትሆንም፣ ስምና ዕድሜዋን የሚመጥን ዕድሳት ሳይደረግላት በመቆየቱ፣ መንደሮቿና መንገዶቿ የፈራረሱ ለዓይን የማይጥሙ፣ አፍንጫ የሚሰነፍጡ ሆነው ቆይተዋል።
ይሁን እንጂ፥ ባለፈው ኣጭር ጊዜ በተሰራው ስኬታማ ስራ ከተማዋ ገፅታዋን እየለወጠች፣ የምትጀምራቸውን ፕሮጀክቶች በፍጥነትና በጥራት እያጠናቀቀች፣ ነዋሪዎቿን እያቀፈች፣ መስህቦቿን እያበዛች፣ የአፍሪካ የብልፅግና ፊት የመሆን ፅኑ መንገዷን ይዛ ትገኛለች፡፡
አዲስ አበባ፥ ውብ የቱሪስት መዳረሻዎችን በማስፋት ለዓለም አቀፍና አህጉር አቀፍ ኩነቶች የምትመረጥ፣ ንፁህ፣ አረንጓዴ ውብ ሥፍራን የተላበሰች፣ አሰራሯን ያዘመነች ህብረ ብሄራዊነቷን የጠበቀች ሰላም ያላት ውብ ከተማ መሆን ችላለች።
በተለይ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሰው ተኮር ልማቷ የብዙ ነዋሪዎቿን እንባ ያበሰች፣ መደገፊያ መጠጊያ የሆነች፣ ተስፋን የሰጠች የተጣሉትን ያስታወሰች ፣ የተራቡትን ያጎረሰች፣ የነገ ህፃናቶቿን የደገፈች፣ተማሪዎቿን ያስታወሰች፣ ማዕድ ያጋራች፣ የኑሮን ጫና ለማቃለል ሸክምን የተጋራች ፣ሌማት እንዲሞላ ያበረታታች እንደ አዲስ የተፈጠረች ከተማ ለመሆን በቅታች፡፡ | 2 520 |
| 5 | ውድ ኢትዮጵያውያን ለ5 ሚሊዮን ኮደሮች ምዕራፍ ስኬት እንኳን ደስ አላችሁ!
በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት የታቀደውን ግብ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማሳካት ተችሏል። የ«5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች» ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ፣ በመረጃ ትንተና፣ በአንድሮይድ ሶፍትዌር ልማት እና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ ትምህርቶች 5,005,146 ሰልጣኞች ተመዝግበው ከ3 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ስልጠናውን አጠናቀዋል። ይህ ስኬት የሕዝባችንን ቁርጠኝነት እና ወሰን የሌለው አቅም ማረጋገጫ ነው።
በዲጂታሉ ዓለም በልኩ ለመዘጋጀት የጀመርነው ታሪካዊ ምዕራፍ፤ የጉዟችን ማብቂያ ሳይሆን፥ ብሔራዊ ርዕያችንን ይበልጥ የምናፋጥንበት መነሻ ነው። እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም. ድረስ የሰልጣኞችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ የተሰነቀውን ግብ ለማሳካት፥ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የዚህ ብሔራዊ ተልዕኮ አካል እንዲሆን ጥሪዬን አቀርባለሁ።
ለወጣት ተማሪዎቻችን፤ መጭው የክረምት ወቅት ትልቅ ዕድላችሁ ነው። ጊዜያችሁን በዋዛ ከማሳለፍ ተቆጥባችሁ፤ በመመዝገብና በመማር ወደ ትምህርት ገበታችሁ ስትመለሱ ተማሪዎች ብቻ ሳትሆኑ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላችሁ የዲጂታል መሪዎች እንድትሆኑ አሳስባለሁ። ሥልጠናዎቹ ሙሉ በሙሉ በነጻ የሚሰጡ ሲሆን፥ የምስክር ወረቀቱም በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው ነው።
የምትገነቡት ነገ የሚጀምረው ዛሬ ነው!
ለመመዝገብ እዚህ ይጫኑ:
ethiocoders.et/ | 2 802 |
| 6 | ውድ ኢትዮጵያውያን ለ5 ሚሊዮን ኮደሮች ምዕራፍ ስኬት እንኳን ደስ አላችሁ!
በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት የታቀደውን ግብ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማሳካት ተችሏል። የ«5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች» ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ፣ በመረጃ ትንተና፣ በአንድሮይድ ሶፍትዌር ልማት እና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ ትምህርቶች 5,005,146 ሰልጣኞች ተመዝግበው ከ3 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ስልጠናውን አጠናቀዋል። ይህ ስኬት የሕዝባችንን ቁርጠኝነት እና ወሰን የሌለው አቅም ማረጋገጫ ነው።
በዲጂታሉ ዓለም በልኩ ለመዘጋጀት የጀመርነው ታሪካዊ ምዕራፍ፤ የጉዟችን ማብቂያ ሳይሆን፥ ብሔራዊ ርዕያችንን ይበልጥ የምናፋጥንበት መነሻ ነው። እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም. ድረስ የሰልጣኞችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ የተሰነቀውን ግብ ለማሳካት፥ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የዚህ ብሔራዊ ተልዕኮ አካል እንዲሆን ጥሪዬን አቀርባለሁ።
ለወጣት ተማሪዎቻችን፤ መጭው የክረምት ወቅት ትልቅ ዕድላችሁ ነው። ጊዜያችሁን በዋዛ ከማሳለፍ ተቆጥባችሁ፤ በመመዝገብና በመማር ወደ ትምህርት ገበታችሁ ስትመለሱ ተማሪዎች ብቻ ሳትሆኑ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላችሁ የዲጂታል መሪዎች እንድትሆኑ አሳስባለሁ። ሥልጠናዎቹ ሙሉ በሙሉ በነጻ የሚሰጡ ሲሆን፥ የምስክር ወረቀቱም በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው ነው።
የምትገነቡት ነገ የሚጀምረው ዛሬ ነው!
ለመመዝገብ እዚህ ይጫኑ:
ethiocoders.et/ | 1 |
| 7 | ዛሬ በምርጫ ሥራዎቻችን አፈጻፀምና የድህረ ምርጫ ሥራዎቻችን በውጤታማነት በመከወን የያዝናቸውን ግቦች በተሟላ መልኩ ከማሳካት አንፃር የተገኙ ዉጤቶችን ከመላው የከተማችን አመራሮች ጋር ገምግመናል ።
7ኛውን ጠቅላላ ሃገራዊ ምርጫ በስኬት እንዳይጠናቀቅ ለማደናቀፍ በውጭም በውስጥም በጋራ በማበር በሚደያ ዘመቻዎች እና በተለያዩ ቅስቀሳዎች ሰላም የማደፍረስ ዝግጅቶችና ትንኮሳዎች ተደርገው ሳይሳካላቸው በኢትዮዽያ ታሪክ ትልቅ እድገት የታየበት ዴሞክራስያዊ፥ ሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ በማካሄድ ኢትዮዽያዊን በፅናት አዲስ ታሪክ ፅፈዉ ኢትዮጲያ መርጣለች፥ ኢትዮጵያ አሸንፋለች።
እንደሃገር ያሳካነው እጅግ ውጤታማ እና ታሪካዊ ምርጫ የህዝባችን ፣የአመራራችን፣ የአባሎቻችን ፣የደጋፊዎቻችን፣የሲቭክ ማህበራት ፣ የሚድያዎቻችን፣ ተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲዎች እንዲሁም በገለልተኝነትና በከፍተኛ ዲሲፕሊን ትልቅ ሃገራዊ ሃላፊነታቸዉን የተወጡት የፀጥታ አካላትና የምርጫ ቦርድ በጥቅሉ ሁሉም ባለድርሻ አካል እንደ ሀገር ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላንን ቁርጠኝነትና በጋራ ያሳካነው ግብ መሆኑን ተግባብተናል ። ለዚህም ሁሉንም ባለድርሻ አካላት እናመሰግናለን።
የድህረ ምርጫ ስራዎቻችን በውጤታማነት በመፈፀም ይህንን ፅኑ ህዝብ ለመካስ ያስቀመጥናቸዉን ግቦች በተሟላ መልኩ ለማሳካት ከመላው አመራራችን ጋር ተግባብተናል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ | 2 862 |
| 8 | የ5ቱ ዓመታት ገፆች፡ በመደመር ትውልድ ያበበችውና ነዋሪዎቿን ያከበረችው አዲሲቱ ከተማ
የከተሜነት እውነተኛ ትርጉም በሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች መደርደር ወይም በኮንክሪት ክምችት ብቻ ሳይሆን፣ ነዋሪዎች በክብር፣ በምቾትና በደህንነት በሚኖሩበት ዘመናዊ ሥርዓት ይለካል።
ካለፈው 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ እስከ 7ኛው ምርጫ ዋዜማ በተዘረጉት አምስት ዓመታት፣ የመደመር ትውልድ የከተሞቻችንን የትላንት ገፅታ በመቀየር፣ ከተሞችን ከድህነትና ከጥግግት አውጥቶ ለነዋሪዎቻቸው የተመቹ የብልፅግና ማዕከላት እንዲሆኑ አስደናቂ ስራዎችን በመንግሥት መሪነት አከናውኗል።
በእነዚህ የ5ቱ ዓመታት ገፆች ጎልቶ ከሚታየው ስኬት አንዱ የቤት ልማት አብዮት ነው። ቀደም ሲል ዘላቂና ውጤታማ ያልነበረውን የቤት ልማት ፕሮግራም በአዲስ መልክ በመቃኘት ታላቅ የቤት አቅርቦት ንቅናቄ ተደርጓል።
መንግሥት በዋነኝነት ሲያከናውነው የነበረውን ልማት ከግል ዘርፉ እንዲሁም ከመንግሥትና የግል አጋርነት (PPP) ጋር በማስተሳሰር የቤቶች ልማት በከፍተኛ ፍጥነት እንዲከናወን ተደርጓል። በዚህም ከ2013 እስከ 2017 በጀት ዓመት ባሉት ጊዜያት ብቻ ከመንግሥት፣ ከሪል ስቴት አልሚዎችና ከግል ቤት ሠሪዎች አቅም ጋር ተደምሮ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ቤቶች ተገንብተዋል። ከዚህ ጎን ለጎንም፣ ዐቅማቸው ዝቅተኛ ለሆኑ ቤት ፈላጊዎች በመንግሥት በኩል የሚከናወኑ የቤት ልማት ፕሮግራሞች ሳይቋረጡ ቀጥለዋል።
የመደመር ከተሜነት ሰውን ማዕከል ያደረገ በመሆኑ፣ ማኅበረሰብን በማስተባበር ዐቅመ ደካማ ለሆኑ ወገኖች 166,207 ደረጃቸውን የጠበቁ ቤቶች ተገንብተው ተላልፈዋል። ከተሞችን ከእርጅናና ከድህነት ገፅታ ለማላቀቅ፣ በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ ቤቶችን ደረጃ የማሳደግ ሥራ በስፋት ተከናውኗል። በ2013 ዓ.ም ከ75 በመቶ በላይ የነበረውን ከደረጃ በታች የሆኑ (substandard) ቤቶች ድርሻ፣ በ2017 ዓ.ም ወደ 52 በመቶ ዝቅ ማድረግ ተችሏል። ይህ ዜጎችን ከማይመችና ኋላቀር አኗኗር ወደ ዘመናዊ የኑሮ ሁኔታ በፈቃደኝነት ያሸጋገረ የክብር ጉዞ ነው።
ይህ ታላቅ የከተማ ትራንስፎርሜሽን የሲቪል ሰርቪሱንና የከተሞችን አገልግሎት ከማዘመን ጋር ተጣምሮ የተጓዘ ነው። ከተሞች ዘመኑን የዋጀ አደረጃጀትና የአስተዳደር ሥርዓት እንዲኖራቸው በማድረግ፣ የማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች ለዜጎች በተሻለ ቅልጥፍና እንዲቀርቡ ተደርጓል።
ይሁን እንጂ፣ መንግሥት ከተሞችን በተቀናጀ አግባብ ሲያለማ፣ አንዳንድ ኃይሎች ይህንን የልማት አቅጣጫ ባለመረዳት የተዛባ አመለካከት ሲያራምዱ ቆይተዋል። ዜጎችን ወደ ተሻለ የኑሮ ሁኔታ ለማሸጋገር የሚሰሩትን የመልሶ ማልማት ስራዎች "ማፈናቀልና ማህበራዊ ኢንጂነሪንግ" ብለው ሲስሉ፣ የከተማን ይዞታ ስርዓት ለማስያዝና አረንጓዴ ቦታዎችን ለመጠበቅ የሚወሰዱ ህጋዊ እርምጃዎችን በሌላ ስም ለማጠልሸት ሞክረዋል። አልፎ ተርፎም ከተሞቻችን ባህላችንንና ታሪካችንን እንዲያንፀባርቁ ለማድረግ የተሰሩትን የውበት ሥራዎች "ታሪክን እንደ ማውደም" አድርገው አቅርበዋል።
ሆኖም እውነታው በተግባር ሊደበቅ አይችልም። ዜጎቻችን የስራዎቹን ፋይዳ አውቀው ምስክርነታቸውን ሲሰጡ፣ የውጭ ሀገራት ሚዲያዎችና ዜጎች ሳይቀሩ በከተሞቻችን ላይ የተመዘገቡትን አስደናቂ ለውጦች እያደነቁ ይገኛሉ። የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና የሲቪል ሰርቪሱን ውጤታማ ለማድረግ የሚከናወኑ ሪፎርሞችንም አሉታዊ ስም በመስጠት ለውጡን ለማደናቀፍ የተሞከሩ ሙከራዎች ከሽፈዋል። በአጠቃላይ እነዚህ የ5ቱ ዓመታት ገፆች፣ መንግሥት ከተሞችን የነገው ዘመን የሥልጣኔ ማዕከላት ለማድረግ ያለውን ግልጽ አቋምና የማድረግ አቅም በተግባር ያረጋገጡ፣ እንዲሁም ለነዋሪዎቻቸው ምቹና ዘመናዊ ከተሞችን የፈጠሩ ደማቅ ታሪካዊ ምዕራፎች ናቸው። | 2 337 |
| 9 | Matn yo'q... | 2 267 |
| 10 | The New Face of Addis | 2 611 |
| 11 | ከሀገር በቀል ጥበብ እስከ መዲናዋ ውበት
አዲስ አበባን ከተፈጥሮ ጋር ያስታረቀው አረንጓዴ ልማት
አዲስ አበባ የተመሰረተችው ከተራራ እና ከውኃ ጋር በተያያዘ የሕይወት ዑደት ውስጥ ነው። እንጦጦ ለአዲስ አበባ የተፈጥሮ ውበቷና ከነፋስ መከላከያ መከታዋ ሲሆን፤ ቀጨኔ፣ ቀበና፣ ግንፍሌ፣ ቡልቡላ እና ሌሎችም ወንዞች ደግሞ የከተማዋ ዋነኛ የሕይወት መስመሮች ነበሩ።
ይህንን የቆየና የልማት አቅጣጫ በአዲስ እሳቤ ለመቀየር፣ አዲስ አበባ አረንጓዴ እና ተፈጥሮን ማዕከል ያደረገ መንገድ መያዝ ግድ ስላላት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት ይፋ የሆነውን ከተማዋን የማስዋብ ፕሮጀክት በመቅረጽ በ2011 ዓ.ም ወደ ተግባራዊ ስራ ተገብቷል።
በዚህ አዲስ መዋቅር ከተሰሩ በርካታ ስኬታማ ተግባራት መካከል የሚጠቀሰው የእንጦጦ-ቀጨኔ መድኃኔዓለም የወንዝ ዳርቻ ልማት፤ የተራራ፣ የሸለቆ፣ የባህል፣ የሥራ ፈጠራ እና የአካባቢ ጥበቃ ታላቅ ድምር ውጤት ሆኗል።
ይህ ልማት ሀገር በቀል ማንነትንና እውቀትን ያከበረ መሆኑን ያሳየበት፣ የኮንሶዎችን የዘመናት ጎርፍ የመከላከል ጥበብ የእርከን ሥራ በተግባር የተገበረበት ነው፡
አረንጓዴ ልማት ውበት ብቻ ሳይሆን የጠንካራ ኢኮኖሚ መሰረትም ጭምር ነው። በእንጦጦ-ቀጨኔ እና በመላው አዲስ አበባ የሚገኙ የወንዝ ዳርቻ የልማት ሥፍራዎች አሁን ላይ ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድልን መፍጠር ችለዋል።
ካፌዎች፣ የብስክሌት ሽያጭና ኪራዮች፣ እንዲሁም የቱሪስት አገልግሎቶች ለነዋሪው አዲስ የገቢ ምንጭ የፈጠሩ ሲሆን፤ በሌላ በኩል የሚፈጠሩት የባህል እና የገበያ ትስስሮች ለአካባቢው ልዩ ድባብ መፈጠሪያ እና ለማኅበረሰቡ ማንነትን መግለጫ መንገድ ሆነዋል።
በተለይም ቀጨኔን በሸክላ ሥራዋ፣ ሽሮሜዳን ደግሞ በሸማ ጥበቧ የምናውቃቸውን የእጅ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ምርቶቻቸውን ደህንነቱ በተጠበቀ፣ ለጎብኚዎች በቀላሉ በሚደርስ እና ንጽህናው በተጠበቀ የሕዝብ ገበያ ለማቅረብ ሰፊ ዕድል አግኝተዋል።
ፅዱ ከተማ ማለት ውብ መንገድ ብቻ ሳይሆን ጤናማ ነዋሪ፣ የተጠበቀ ተፈጥሮ፣ የተነቃቃ ኢኮኖሚ እና ለትውልድ የሚተርፍ ማለት ነው። | 2 763 |
| 12 | Matn yo'q... | 2 804 |
| 13 | በኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት በየወሩ እየተዘጋጀ ለንባብ የሚበቃው ዜና መፅሔት ቅፅ 04 ቁጥር 38 (የወርሀ ግንቦት 2018 ) ዕትም እንሆ
የቢሮውን ይፋዊ የማሕበራዊ ገፆች ይከታተሉ
ፌስቡክ
https://www.facebook.com/AddisConstruction/
ቴሌግራም
https://t.me/AddisCityCon
ትዊተር
https://twitter.com/AddisCity
ዩቲዩብ
https://www.youtube.com/channel/UCwuES6TQUZmVlUT8tazLHmg
ቲክቶክ
https://tiktok.com/@design_and_construction1
ዋትሳፕ
https://whatsapp.com/channel/0029Vani9gI0lwgzDJ1eFH1x
ዌብሳይት
www.addisconstructionwork.gov.et
ነፃ የስልክ መስመር 9426 | 2 612 |
| 14 | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን በመጠቀም የተገነቡ ቤቶችን የሚያሳይ የግንባታ ሳይት ጎብኝተዋል | 3 168 |
| 15 | ዛሬ ማለዳ በሶስተኛው ዙር የጀመርናቸውን 13.4 ኪሜ የሚሸፍነውን የኮሪደር ልማት ስራዎችን አፈፃፀም ገምግመናል።
የኮሪደሮቹ ልማት በአምስት የኮሪደር መስመሮች ተከፋፍለዉ እየተሰሩ ሲሆን እነርሱም:-
1- ከቦሌ መድሃኔዓለም እስከ ጎላጎል ( የቦሌ አትላስን መንገድ ከመስቀል አደባባ መገናኛ መንገድ ጋር የሚገናኝ) ፣
2- ከጎላጎል እስከ እንግሊዝ ኤምባሲ ( የቀበና መገናኛ መንገድን ከመስቀል አደባባ መገናኛ መንገድ ጋር የሚገናኝ) ፣
3- ከቦሌ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በሞኤኮ እስከ ቦሌ መገናኛ መንገድ ( የቦሌ አትላስን መንገድ ከቦሌ መገናኛ መንገድ ጋር የሚገናኝ)፣
4- ከኢምፔሪያል በአደይ አበባ ስቴድዮም እስከ ሻላ መናፈሻ ፣
5-ከውሃ ልማት በአትላስ ያለውን እና ከአትላስ እስከ ቦሌ ሩዋንዳ ( የቦሌ አትላስ መንገድን ከመስቀል አደባባ መገናኛ መንገድ ጋር የሚገናኝ) በከፍተኛ ደረጃ የመንገድ ኔትወርኩን የሚያሰፋ፣ የንግድ ተቋማን፣ ሰፋፊ የእግረኛ መንገድ፣ የሳይክል መንገድ እና ለትራንስፖርት አገልግሎት ምቹ እንዲሆኑ ተደርገው እየተገነቡም ናቸው።
በተጨማሪም በርካታ የህዝብ አገልግሎት መስጫ ግንባታዎችን የያዘ ሲሆን የግንባታውም ሂደትም በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል።
በአደይ አበባ ስታዲየም ዙሪያ አስቀድመው የተጀመሩ የኮሪደርና ሌሎች መሠረተ ልማት ግንባታዎች
በፍጥነትና በጥራት እንዲከናወኑ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ከኮሪደሩ በተጨማሪም ለብዙ ዘመናት ተረስቶ የኖረ፣ ከሕዝብ ተወስዶ በግለሰቦች ያለአግባብ ተወሮ ለብዙ ብልሽት ተዳርጎ የኖረውን ቦታ ለህዝብ አገልግሎት እንዲውል ተደርጎ በመሰራት ላይ ይገኛል።
ፕሮጀክቶቹን እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ለማዋል በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ | 3 328 |
| 16 | “ከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች አካታች፣ ተደራሽና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት አየሰራ ነው!”
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ጀማሉ ጀምበር (ዶ/ር)
ከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች አካታች፣ ተደራሽና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት አየተሰራ ነው ሲሉ ዶር ጀማሉ ጀንበር ገለፁ።
አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አላስፈላጊ የቢሮክራሲ አሰራርን ያስቀረና ተጠያቂነትን ያሰፈነ ነውም ብለዋል።
በዛሬው ዕለት ለአገልግሎት የበቃው የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል የመንግስት አገልግሎት የየካ ማዕከል 96 ተገልጋዮችን በአንድ ጊዜ ማስተናገድ የሚያስችል መስኮትና ሌሎች መሰረተ ልማቶች የተሟሉለት መሆኑን አስረድተዋል።
ማዕከሉ የ22 ተቋማትን 114 አገልግሎት መስጠት ያስችላል። በቀጣይ ተጨማሪ አገልግሎቶች እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል። | 3 293 |
| 17 | ቃል በተግባር በከተማችን ተጠናክሮ ቀጥሏል---
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል የመንግስት አገልግሎት የካ ማዕከልን መርቀው አስጀመሩ።
በም/ከንቲባው የተመረቀው የየካ ማዕከል በከተማችን 9ኛው መሶብ ዲጅታል የመንግስት አገልግሎት ነው።
መሶብ በከተማ አስተዳደሩ የአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ያሉ የህዝቡን ቅሬታዎችን እየፈታ መሆኑንም አቶ ጃንጥራር አባይ ተናግረዋል።
በዚህ ዓመት ቀደም ሲልና አሁን ላይ ወደ ስራ በገቡ የመሶብ ማዕከላት የተገልጋዮች እርካታን 99 በመቶ ማድረስ ተችሏል።
ይህን የነዋሪዎችን የአገልግሎት እንግልት ለማስቀረት ከምርጫ ማግስትም አዳዲስ የመሶብ ዲጅታል ማዕከላትን ወደ ስራ የማስገባት ጥረታችንን አጠናክረን በመቀጠል 9ኛው የየካ ማዕከል ላይ ደርሰናል።
በቀጣይ ጥቂት ቀናት ደግሞ ግንባታቸው የተጠናቀቁትን የአቃቂና የለሚ ኩራ ማዕከላትን ወደ ስራ የምናስገባ ይሆናል።
ተጨማሪ ስራ በመስራት የህዝባችንን እርካታ እንዲጨምር እናደርጋለን ሲሉም አቶ ጃንጥራር ተናግረዋል። | 2 503 |
| 18 | ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር መፈፀም መለያችን ነው!!
ዛሬ 9ኛውን መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በየካ ክፍለ ከተማ አስጀምረናል።
የመንግስት አገልግሎት አሰጣጣችንን ቀልጣፋ፣ ፈጣን፣ ግልፅ እና ተደራሽ ለማድረግ በሁሉም ክፍለ ከተሞች መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ስራ በ2018 በሁሉም ክፍለ ከተሞች ስራ ለማስጀመር አቅደን ለህዝቡ ቃል በገባነው መሰረት እነሆ የዛሬውን ጨምሮ 9 ማዕከላትን ወደ ስራ አስገብተናል።
የአገልግሎት እንግልትን፣ እዚህም እዝያም ጉቦ የመጠየቅ ችግርን ለመቅርፍ፣ ተጠያቂነትን እና የህዝባችንን በክብር የመገልገል መብት ለማረጋገጥ፣ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜውንና ገንዘቡን ሳያባክን ያለውን ሃብት ለልማት እንዲያውለው ለማድረግ ያቀድነውን ግብ በማሳካት የጀመርነውን የብልፅግና ጉዞ አጠናክረን እንቀጥላለን ።
የየካ ክፍለ ከተማ ባለ 7 ወለል ህንፃ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በፍጥነት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ የሰራችሁትን ሁሉ አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ | 2 967 |
| 19 | ውድድር አሸናፊ ሆነች
በ19ኛው የኢትዮጵያ የግማሽ ማራቶን ውድድር በሴቶች የአዲስ አበባ ፖሊሷ መሰለች አለማየሁ አሸንፋለች።
ዝማም ማራኪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለተኛ ወጥታለች።
መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ አድርጎ በተከናወነው ውድድር በወንዶች 455 እና በሴቶች 183 በድምሩ 638 አትሌቶች ተሳትፈውበታል፡፡ | 3 353 |
| 20 | የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ሩጫ እየተካሄደ ነው
19ኛው የኢትዮጵያ የግማሽ ማራቶን ውድድር በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው ውድድሩ በወንዶች 455 እና በሴቶች 183 በድምሩ 638 አትሌቶች እየተሳተፉበት እንደሚገኝ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል።
በዴንማርክ ኮፐንሀገን ለሚካሄደው የግማሽ ማራቶን ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች በውድድሩ እንደሚመረጡ ተገልጿል። | 3 032 |
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
