fa
Feedback
Addis Ababa Design And Construction Works Bureau

Addis Ababa Design And Construction Works Bureau

رفتن به کانال در Telegram

Government Organization

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Addis Ababa Design And Construction Works Bureau

کانال Addis Ababa Design And Construction Works Bureau (@addiscitycon) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 20 880 مشترک است و جایگاه 2 809 را در دسته سیاست و رتبه 1 621 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 20 880 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 30 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 228 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 16 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 13.78% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 8.89% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 2 878 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 856 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 12 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Government Organization

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 01 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته سیاست تبدیل کرده‌اند.

20 880
مشترکین
+1624 ساعت
+927 روز
+22830 روز
آرشیو پست ها
በቢሮው የተካሄደው የስታንዳርዳይዜሽንና የአፈጻጸም ምዘና ተጠናቀቀ፡፡ የአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ በዛሬው ዕለት በከተማው ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ በመገኘት የስታን
+9
በቢሮው የተካሄደው የስታንዳርዳይዜሽንና የአፈጻጸም ምዘና ተጠናቀቀ፡፡ የአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ በዛሬው ዕለት በከተማው ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ በመገኘት የስታንዳርዳይዜሽን እና የአፈጻጸም ምዘና አካሄደ። ምዘናው ተቋሙ ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥ ከማስፈንና ምቹ የስራ ከባቢ ከመፍጠር አንፃር እያከናወናቸው ያሉትን ተግባራት ውጤታማነት ለመገምገም ያለመ እንደሆነ በመድረኩ ተጠቅሷል። በዚሁ ተቋማዊ ምዘና ቢሮው የከተማዋን ነዋሪዎች ፍላጎት መሰረት ያደረጉ ዲጂታላይዝድ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን እና የህዝብ እርካታን ለማሳደግ የወሰዳቸው እርምጃዎች እና የሄደበት ርቀት ተፈትሿል። በተለይም ተገልጋዮች እንግልት ሳይገጥማቸው ቀልጣፋ ምላሽ የሚያገኙባቸውን የቴክኖሎጂ አማራጮች መዘርጋቱ ፤ ለአገልግሎት ሰጪውና ተቀባዩ ምቹ እና ሳቢ የቢሮ አደረጃጀቶች መፍጠሩ እንዲሁም ደጋፊ መሰረተ-ልማቶች ዕውን ማድረጉ በምዘናው ወቅት ትኩረት ተሰጥቶባቸዋል። የዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኃላፊ ኢ/ር አያልነሽ ሐብተማሪያም የድጋፍና ክትትል ቡድኑን በተቀበሉበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ተቋማዊ ለውጥን ዕውን ለማድረግና ተልዕኮን በተሳካ ሁኔታ ለመፈፀም ስታንዳርዳይዜሽንን በተቋም ደረጃ መተግበር ትልቅ ድርሻ እንዳለው ጠቅሰው ቢሮው ይህን የሚደግፉ የዲጂታላይዜሽን አሰራር ስርዓቶችን በስፋት ስራ ላይ በማዋል ተጨባጭ ውጤት ማየቱን አመላክተው ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል። የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ሰኔ 22/2018 ዓ.ም

ፅዱና ውብ ቀበና ለትውልድ ስጦታ !

87.6 ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን እና 10.5 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውን የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን ዛሬ በይፋ መርቀናል። ይህ ሰፊ መሰረተ ልማት የወንዝ መከላከያ ግንቦችን፣ ዘመናዊ ድልድዮችን እና ሰፊ አረንጓዴ ስፍራዎችን በጋራ የያዘ ነው። ፕሮጀክቱ የግንባታ ስኬት ብቻ ሳይሆን፣ መዲናችንን የአየር ንብረት ለውጥን የምትቋቋምና ለነዋሪዎቿ ምቹ የሆነች፣ ዓለም አቀፍ የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ ማዕከል ለማድረግ የጀመርነውን ስልታዊ ሽግግር የሚያፋጥን ታላቅ አጋጣሚ ነው። ‎ ‎የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን! #EthiopiaDelivers ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ

እንጦጦ እስከ ቀበና የወንዝ ዳርቻ ሲገለጥ Entoto to Kebena Riverside Unveiled #EthiopiaUnveiled ጠቅላይ ሚኒስት ዶ/ር አብይ አህመድ
+9
እንጦጦ እስከ ቀበና የወንዝ ዳርቻ ሲገለጥ Entoto to Kebena Riverside Unveiled #EthiopiaUnveiled ጠቅላይ ሚኒስት ዶ/ር አብይ አህመድ

የሙያ ስነ-ምግባርን ያከበረ አገልጋይ መፍጠር ለተቋማት ተልዕኮ ስኬት እና ለህዝብ እርካታ መጎልበት የማይናቅ ድርሻ እንዳለው ተገለጸ፡፡ በአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ቢሮ የስነ-ምግባርና ፀ
+9
የሙያ ስነ-ምግባርን ያከበረ አገልጋይ መፍጠር ለተቋማት ተልዕኮ ስኬት እና ለህዝብ እርካታ መጎልበት የማይናቅ ድርሻ እንዳለው ተገለጸ፡፡ በአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ቢሮ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት "የሙያ ስነ-ምግባር በመገንባት ሙስና ስጋት የማይሆንባት አዲስ አበባን እንፈጥራለን" በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጀውን ስልጠና በዛሬው ዕለት መስጠት ጀምሯል፡፡ የቢሮው የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ወንድምአገኝ አበራ ስልጠናውን ሲከፍቱ ባደረጉት ንግግር በማንኛውም የስራ መስክ ላይ የሚገኙ ባለሙያዎች የሙያ ስነ-ምግባርን አክብረው መስራታቸው ለተቋማዊ ስኬት እና ለህዝብ ተጠቃሚነት ዋነኛ መሰረት እንደሆነ አንስተዋል። የሙያ ስነ-ምግባር አንድ ባለሙያ በስራ ዓለም በሚያደርጋቸው ዕለታዊ እንቅስቃሴውዎች ውስጥ ሊከተላቸው የሚገቡ የሞራል መርሆዎች እና እሴቶች ስብስብ እንደሆነም በዚሁ ስልጠና ላይ የተመላከተ ሲሆን አገልጋዩም በፍፁም በኃላፊነት እና በፍትሃዊነት ስራቸውን እንዲከውኑ የሚያግዙ መሰረታዊያን እንደሆኑ ተጠቅሷል። ተያይዞም የሙያ ስነ-ምግባርን በተገቢው መንገድ መገንባትና መተግበር የሙያውን ክብር እና ታማኝነት ለመጠበቅ ፣ የህዝብን እምነት ለማግኘት እንዲሁም ለደንበኞች ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት ተኪ የሌለው ሚና እንዳለውም ተያይዞ ተጠቁሟል። በመጨረሻም በተቋማት ውስጥ ጥራትንና ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የባለሙያዎችን ሙያዊ ስነ-ምግባር አቅም መገንባትና መርሆዎቹ እንዲከበሩ መደገፍ ብሎም የተጠያቂነት ስርዓት መዘርጋት የተቋማት ቀዳሚ ተግባር ሊሆን እንደሚገባም ተመልክቷል። ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ሰኔ 18/2018 ዓ.ም

ኢትዮጵያ ታከናውናለች፡ የአዲስ አበባ የአዲሱ ትውልድ አሻራ ከእንጦጦ እስከ ፒኮክ ባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወነው የወንዞች ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ከተማዋን ውበት ከማልበስ ባለፈ የነዋሪዎቿን የደኅንነት፣ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ሕይወት ምሕዋር ሙሉ በሙሉ የቀየረ ሥር ነቀል የትራንስፎርሜሽን ማሳያ ሆኗል። ይህ ግዙፍ መሠረተ ልማት ከእንጦጦ እስከ ፒኮክ ፓርክ እንዲሁም ከእንጦጦ እስከ ቀበና ከ22 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያለውን መስመር በመሸፈን የከተማዋን መልክ በከፍተኛ ደረጃ ቀይሮታል። ፕሮጀክቱ ከመልክዓ-ምድር ውበት እና ከወንዝ ዳርቻ ማስዋብ ባለፈ፣ ልማት ከአካባቢ ጥበቃ ጋር በተናበበ መልኩ በጥናትና በጋራ ግብ እንዴት ሊከወን እንደሚችል በተግባር ያሳየ ዘመናዊና ውጤታማ የፈጠራ አውድ ነው። የዚህ አምስት ዓመት የልማት ጉዞ እጅግ የጎላው ስኬት የተመዘገበው በአካባቢ ጥበቃ ሽግግር እና በሕዝብ ደኅንነት ረገድ ነው። ቀደም ሲል መርዛማ ኬሚካሎችና ቆሻሻዎች ይጣሉባቸው የነበሩ እንዲሁም ለከፍተኛ የጎርፍ አደጋ ተጋላጭ የነበሩ የከተማዋ ክፍሎች ዛሬ ላይ ወደ ንጹሕ፣ ጤናማ እና እፎይታን ወደሚሰጡ አረንጓዴ ስፍራዎች ተለውጠዋል። ይህ የተቀናጀ የልማት ሥራ የፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦዎችን ችግር በመፍታት እና የጎርፍ ሥጋትን በከፍተኛ ደረጃ በመቀነስ የወንዝ ዳርቻዎችን ተገን አድርገው በአስጊ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ በርካታ ነዋሪዎችን ሕይወት ታድጓል። የተፈጥሮ ወንዞችን ከቆሻሻ መጣያነት አላቅቆ ወደ ቀደመ ተፈጥሯቸው በመመለስ የተረጋገጠው የወንዞች ትንሣኤም የነዋሪዎችን አስተሳሰብ እና የቦታ አጠቃቀም ወደ ሀብት የቀየረ ታላቅ ድል ነው። በሌላ በኩል የፕሮጀክቱ ሰውን ማዕከል ያደረገ ስትራቴጂ የከተማዋን ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር በአዲስ መልክ አዋቅሮታል። ሰፊ የሕዝብ መሰብሰቢያዎችን፣ የእግር ጉዞ መንገዶችን፣ የመዝናኛ ማዕከላትን እና የንግድ ቦታዎችን በማቀናጀት አዲስ አበባን በሰው ልጅ እንቅስቃሴና ምቾት ላይ የተመሠረተች ንቁ የቱሪስት መዳረሻ ማድረግ ተችሏል። ከዚህም ባሻገር በግንባታ፣ በምሕንድስና፣ በመልክዓ-ምድር ውበት እና በሎጂስቲክስ ዘርፎች ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል። አብዛኛው የመሠረተ ልማት ሥራ በሀገር ውስጥ ተቋራጮች እና በኢትዮጵያውያን መሐንዲሶች መከናወኑ የሀገር ውስጥ ባለሙያዎችን አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ያሳደገ ነው። በስፍራው የቆሙት የተለያዩ ሐውልቶች እና ምልክቶችም ከውበት ባለፈ የኢትዮጵያን ታሪክ እና ምድረ ቀደምትነት የሚገልጹ መታሰቢያዎች ሆነው አገልግለዋል። ከዚህ ስኬት በስተጀርባ ያለው ጥልቅ ትርጓሜ ሲፈተሽ፣ ፕሮጀክቱ በከተማዋ የሥነ-ልቦና እና የማኅበረሰብ ግንባታ ላይ ያመጣው ለውጥ እጅግ የጎላ ሆኖ እናገኘዋለን። ቀደም ሲል የነበረውን "የለንም" የሚል የተስፋ መቁረጥ ስሜት እና ራስን የማሳነስ ልማድ በመስበር፣ የከተማዋን የተፈጥሮ ሀብቶች ወደ ታላቅ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ እሴት መቀየር እንደሚቻል በተግባር ተረጋግጧል። በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል ዓለም አቀፍ አርዓያነትን ካስመዘገበው የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ስትራቴጂ ጋር የተናበበው ይህ ልማት፣ አዲስ አበባን ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ የአፍሪካ መዲናዎች ተርታ እንድትሰለፍ አድርጓታል። በአጠቃላይ ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡት እነዚህ ሁለንተናዊ ድሎች ከተማዋን ሰውን ማዕከል ባደረገ፣ ዘመናዊ፣ አረንጓዴና በኢኮኖሚ በጠነከረ መሠረት ላይ የገነቡ የትውልድ ታላቅ አሻራ ሆነው በታሪክ ይዘከራሉ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያለፉ ዓመታት የፋይናንስ ጉዞ፣ ከገቢ ማሳደግ እስከ ልማት ተኮር የበጀት ሽግግር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከ2010 እስከ 2019 በጀት ዓመት ያሳየው የፋይናንስ መረጃ፣ ከተማዋ በታሪኳ አይታው የማታውቀውን የኢኮኖሚ ዕድገትና መዋቅራዊ ሽግግር እያደረገች መሆኑን በግልጽ ያሳያል። ይህ የ10 ዓመታት ጉዞ ጠንካራ የገቢ አሰባሰብ አቅምን ከመገንባት ባለፈ፣ በጀትን አስተዳደራዊ ወጪዎችን በመቀነስ ለዘላቂ ልማት (ካፒታል) የማዋል ጤናማ የፋይናንስ ፖሊሲን የተገበረበት ነው። በ2010 30 ቢሊዮን ብር ብቻ የነበረው የገቢ አሰባሰብ አፈጻጸም፣ በ1574.23 በመቶ (በ472.27 ቢሊዮን ብር) በማደግ በ2019 በጀቱን በሙሉ በራስ አቅም መሸፈን ወደሚያስችልበት ደረጃ ደርሷል። ይህ የገቢ ዕድገት እና የአጠቃላይ በጀት ዕድገት መመጣጠን፣ ከተማዋ የፋይናንስ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጧን እና በውስጥ አቅም ፕሮጀክቶችን የማስፈጸም ብቃቷ መጎልበቱን ያመላክታል። ከቁጥራዊ ዕድገት ባሻገር፣ የከተማዋን የልማት ራዕይ ይበልጥ የሚያጎላው የበጀት ድልድል ስብጥር (Capital vs. Regular Budget) ለውጥ ነው። በ2010 የነበረው የካፒታል በጀት ድርሻ 53.18 በመቶ (21.53 ቢሊዮን ብር) የነበረ ሲሆን፣ ለመደበኛ ወይም ለሥራ ማስኬጃ 46.82 በመቶ (18.96 ቢሊዮን ብር) ይውል ነበር። ነገር ግን በ2019 ይህ ምጣኔ መሠረታዊ ለውጥ አሳይቶ፣ የካፒታል በጀቱ ድርሻ ወደ 71 በመቶ (355.52 ቢሊዮን ብር) ሲያድግ፣ የመደበኛ በጀቱ ድርሻ ወደ 29 በመቶ (146.74 ቢሊዮን ብር) ዝቅ ብሏል። የአስተዳደራዊ ወጪዎችን (መደበኛ በጀት) በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነስ የገንዘቡን አብዛኛውን እጅ ለመሠረተ ልማት እና ለትልልቅ ፕሮጀክቶች (ካፒታል በጀት) መዋሉ፣ ከተማዋ ፊቷን ሙሉ በሙሉ ወደ እድገትና ብልፅግና ላይ ለሚታይ ትክክለኛ ልማት ማዞሯን የሚያረጋግጥ የፖሊሲ ስኬት ነው። በአጠቃላይ፣ እነዚህ መረጃዎች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሀብት አሰባሰብ አቅሙን እጅግ በላቀ ሁኔታ ከማስፋቱም በላይ፣ የተሰበሰበውን ሀብት በአግባቡ ቆጥቦ የነዋሪዎችን ኑሮ ለሚቀይሩ እና ከተማዋን ለሚያዘምኑ የካፒታል ፕሮጀክቶች ቅድሚያ በመስጠት ከፍተኛ የአመራር ብቃት እያሳየ መሆኑን በተጨባጭ የሚያስረዱ ናቸው።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያለፉ ዓመታት የፋይናንስ ጉዞ፣ ከገቢ ማሳደግ እስከ ልማት ተኮር የበጀት ሽግግር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከ2010 እስከ 2019 በጀት ዓመት ያሳየው የፋይናንስ መረጃ፣ ከተማዋ በታሪኳ አይታው የማታውቀውን የኢኮኖሚ ዕድገትና መዋቅራዊ ሽግግር እያደረገች መሆኑን በግልጽ ያሳያል። ይህ የ10 ዓመታት ጉዞ ጠንካራ የገቢ አሰባሰብ አቅምን ከመገንባት ባለፈ፣ በጀትን አስተዳደራዊ ወጪዎችን በመቀነስ ለዘላቂ ልማት (ካፒታል) የማዋል ጤናማ የፋይናንስ ፖሊሲን የተገበረበት ነው። መረጃዎቹ እንደሚያሳዩት፣ በ2010 በጀት ዓመት 40.5 ቢሊዮን ብር የነበረው የከተማዋ አጠቃላይ በጀት፣ በ2019 ወደ 502.27 ቢሊዮን ብር አድጓል። ይህ የ461.77 ቢሊዮን ብር (የ1140 በመቶ) አስደናቂ ዕድገት ሊመዘገብ የቻለው ከተማ አስተዳደሩ የገቢ አሰባሰብ አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደጉ ነው። በ2010 30 ቢሊዮን ብር ብቻ የነበረው የገቢ አሰባሰብ አፈጻጸም፣ በ1574.23 በመቶ (በ472.27 ቢሊዮን ብር) በማደግ በ2019 በጀቱን በሙሉ በራስ አቅም መሸፈን ወደሚያስችልበት ደረጃ ደርሷል። ይህ የገቢ ዕድገት እና የአጠቃላይ በጀት ዕድገት መመጣጠን፣ ከተማዋ የፋይናንስ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጧን እና በውስጥ አቅም ፕሮጀክቶችን የማስፈጸም ብቃቷ መጎልበቱን ያመላክታል። ከቁጥራዊ ዕድገት ባሻገር፣ የከተማዋን የልማት ራዕይ ይበልጥ የሚያጎላው የበጀት ድልድል ስብጥር (Capital vs. Regular Budget) ለውጥ ነው። በ2010 የነበረው የካፒታል በጀት ድርሻ 53.18 በመቶ (21.53 ቢሊዮን ብር) የነበረ ሲሆን፣ ለመደበኛ ወይም ለሥራ ማስኬጃ 46.82 በመቶ (18.96 ቢሊዮን ብር) ይውል ነበር። ነገር ግን በ2019 ይህ ምጣኔ መሠረታዊ ለውጥ አሳይቶ፣ የካፒታል በጀቱ ድርሻ ወደ 71 በመቶ (355.52 ቢሊዮን ብር) ሲያድግ፣ የመደበኛ በጀቱ ድርሻ ወደ 29 በመቶ (146.74 ቢሊዮን ብር) ዝቅ ብሏል። የአስተዳደራዊ ወጪዎችን (መደበኛ በጀት) በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነስ የገንዘቡን አብዛኛውን እጅ ለመሠረተ ልማት እና ለትልልቅ ፕሮጀክቶች (ካፒታል በጀት) መዋሉ፣ ከተማዋ ፊቷን ሙሉ በሙሉ ወደ እድገትና ብልፅግና ላይ ለሚታይ ትክክለኛ ልማት ማዞሯን የሚያረጋግጥ የፖሊሲ ስኬት ነው። በአጠቃላይ፣ እነዚህ መረጃዎች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሀብት አሰባሰብ አቅሙን እጅግ በላቀ ሁኔታ ከማስፋቱም በላይ፣ የተሰበሰበውን ሀብት በአግባቡ ቆጥቦ የነዋሪዎችን ኑሮ ለሚቀይሩ እና ከተማዋን ለሚያዘምኑ የካፒታል ፕሮጀክቶች ቅድሚያ በመስጠት ከፍተኛ የአመራር ብቃት እያሳየ መሆኑን በተጨባጭ የሚያስረዱ ናቸው።

በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎትን በሁሉም ክፍለ ከተሞች 11 (አስራ አንድ) ማዕከላትን እውን በማድረግ ቃላችንን በተግባር አሳይተናል ! ውድ የከተማችን ነዋሪዎች ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ ወጪ ቆጣቢ፣ ግልፅ፣ ከአድሎና ጉቦ የፀዳ ፍትሃዊ አገልግሎት በሁሉም አካባቢ ማግኘት የሚያስችላችሁን ማዕከላት በማግኘታችሁ እንኳን ደስ አላችሁ! ዛሬ በአቃቂ ቃሊቲ እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተሞች ሁለት አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ከፍተን በከተማችን በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ በ11 (አስራ አንዱም ክፍለ ከተሞች) ማዕከላትን እውን አድርገናል። በእነዚህ ማዕከላት ለህብረተሰቡ 50 በመቶ ያህል የመንግስት አገልግሎቶች እጅግ ቀልጣፋ በሆነ መልኩ እየተሰጠ ይገኛል። ቀጣዩ ስራችን ደግሞ ቀሪዎቹን 50 በመቶ አገልግሎቶች ወደ እነዚህ ማዕከላት እንዲገቡ በማድረግ በአገልግሎት አሰጣጥ ሙሉ በሙሉ በማዘመን ለነዋሪዎቻችን እርካታና እፎይታን መፍጠር ይሆናል። ለረጅም ዘመን የተተበተበ ቢሮክራሲ፣ በብልሹ አሰራር ውስጥ የነበረውንና ለመለወጥ ጥረቶች ቢደረጉም ባለመለወጡ የሪፎርም ዝለትና ሊለወጥ አይችልም ወደሚል ተስፋ መቁረጥ ደረጃ ላይ የደረሰውን የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ተግተን በመስራት ትልቅ ሽግግር ያደረግንበት፣ ህዝባችን ጊዜውንና ገንዘቡን ለልማት እንዲያውል በሚያደርግ ማዕከል መተካት ችለናል። በሀገራችን ሙያተኞች የገነባናቸው እነዚህ ተቋማት የሀገራዊ ህልሞቻችን በለውጥ መገስገስ እንደምንችል ማረጋገጫዎች ናቸው ።የዛሬዎቹን ጨምሮ በአጭር ጊዜ በጥራት በመገንባት፣ በማማከር እንዲሁም ተቋሞቹን በቴክኖሎጂ እንዲሟሉ የበኩላችሁን አስተዋፅኦ ላደረጋችሁ ሁሉ በከተማችን ነዋሪዎች፣ በከተማ አስተዳደሩና በራሴ ስም ከልብ አመሰግናለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ “የብሪዝ ሲቲ ( Breathe Cities)” ከተሞችን ተቀላቀለች! “ብሉምበርግ” የተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት፣ የአየር ጥራትን ለማሻሻል 45 ሚሊዮን ዶላር በመመደብ በዓለም ላይ ከተመረጡ ከተሞች ጋር በቀጣይ ለመስራት ባስታወቀበት ወቅት ነው። አዲስ አበባ “የብሪዝ ሲቲ” ፕሮግራም ስትቀላቀል፣ በከተማዋ የአየር ጥራትን ለማሻሻል የሚደረገውን ስራ የበለጠ ይደግፋል። ዛሬ በለንደን የአየር ንብረት ለውጥ ትግበራ ሳምንት ፕሮግራም ላይ በተገለፀው፣ አዲስ አበባ የብሪዝ ሲቲ ከተሞች አባል መሆን የተረጋገጠ ሲሆን፣ ፕሮግራም በብሉምበርግ ግብረ ሠና የድርጅት፣ “በክሊን ኤር ፈንድ” እና “በሲ40 ሲቲስ” አማካኝነት የሚደረግ ድጋፍ ሲሆን፣ አላማውም የከተማችንን የአየር ጥራት ለማሻሻልና ከአየር ጥራት ጋር ተያይዞ የሚመጣው የጤና ጉዳት ለመቀነስ ያለመ ነው። ይኽም አዲስ አበባን ጨምሮ በ16 ዓለማቀፍ ከተሞች የሚተገበር ይሆናል። የፕሮግራሙ መገለፅ ተከትሎ፥ ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተወካያቸው “አዲስ አበባ የብሪዝ ሲቲ አባል መሆኗ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸው፣ በከተሞቻችን የኮሪደር ስራ እያሳየን ያለውን ሁለንተናዊ የላቀ የከተማ ትራንስፎርሜሽን፥ ፅዱ፣ ውብ፣ አረንጓዴ እና ለመኖር ምቹ ከባቢን ከመፍጠር ስራችን ጎን-ለጎን የአረንጓዴ አሻራ፣ የብስክሌት መንገድ እና የአየር ጥራት መቆጣጠርያ መሣርያዎችን የበለጠ አስፋፍተን እና አጠናክረን ለመስራት ያግዛል ብለዋል። ጨምረውም “በማይክል ብሉንበርግ እንዲሁም በሚመሩት የግብረሰናይ ድርጅት እየተደረገልን ያለው እገዛም ይህንን አጠናክረን ለመስራት ያስችለናል። እንዲሁም አዲስ አበባ የኮፕ 32ን ስታዘጋጀት በአየር ጥራት ቁጥጥር እና የአየር ጥራትን ማሻሻል የሚያስችሉ ተሞክሮዎችን ለሌሎችየአፍሪካ ከተሞች ብሎም ለአለም አቀፍ ከተሞች ተሞክሮ ለማሳየት ያግዘናል” ብለዋል ። የተባበሩት መንግታት በአየር ንብረት ለውጥ ልዩ መልዕክተኛ እና የብሉክ ብሉምበርግ ግብረሰናይ ድርጅት ዋና መስራች ማይክል ብሉንበርግ በበኩላቸው፣ “በብሪዝ ሲቲስ አማካኝነት የከተማ ከንቲባዎች እንዲሁም መሪዎች የአየር ጥራትን ከማሻሻል አንጻር ግንባር ቀደም ሆነው መስራታቸውን ቀጥለዋል ሲሉ ገልፀዋል። እያንዳንዱ ከተማ ወደፊት አየር ጥራትን ከማሻሻል አንጻር የሚወስደው እርምጃ ሕይወትን ለማዳን፣ የሕዝብ ጤናን ለማሻሻል እና የብክለትን ልቀትን ለመቀነስ ይረዳል - ይህም ከተሞች ለመኖርና ለመሥራት የተሻሉ ቦታዎችን ያደርጋል። ይህ አዲስ ኢንቨስትመንት ወይም ድጋፍ ከንቲባዎች እያደረጉ ባለው ስራ ተጨማሪ እገዛ ያደርጋል - ከነዚህ ስራዎች የሚገኙ ተሞክሮዎችንም ደግሞ ወደ ተጨማሪ ከተሞች ለማዳረስ ይረዳል”ብለዋል። አሁን ከተቀላቀሉት አዲስ አበባ እና ማድሪድ ከተሞች በተጨማሪ፥ አክራ፣ ባንኮክ፣ ቦጎታ፣ ብራስልስ፣ ጃካርታ፣ ጆሃንስበርግ፣ ለንደን፣ ሜክሲኮ ሲቲ፣ ሚላን፣ ናይሮቢ፣ ፓሪስ፣ ሪዮ ዴ ጄኔሮ፣ ሶፊያ፣ እና ዋርሶ ይገኙበታል። ይህም ብክለትን ለመቀነስ እና የህዝብ ጤናን ለማሻሻል የሚሰሩ የከንቲባዎች አውታረ መረብ ይፈጥራል።

ነዋሪዎቻችንን ከአደጋ መከላከል ቀዳሚ ስራችን ነው - ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ ዛሬ ከተማ አቀፍ የጎርፍ መከላከልና የአደጋ ዝግጁነት ንቅናቄ በአቃቂ ክፍለ ከተማ ተጀምሯል። በቦታው ተገኝተው ንቅናቄውን ያስጀመሩት የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ ንቅናቄውን በአቃቂ ቃሊቲ ጀምረን በሁሉም ለጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ዘላቂ ልማት እንዲኖር በማድረግ ነዋሪዎቻችንን ከአደጋ መከላከል የከተማ አስተዳደሩ ቀዳሚ ስራ ነው ብለዋል። ከጥቂት ዓመታት በፊት በጎርፍ ምክንያት ይከሰት የነበረው አደጋ አሳዛኝ እንደነበር እና እንደዚህ ዓይነቱን አደጋ ቀድሞ መከላከል ተገቢ መሆኑን የገለፁት ምክትል ከንቲባው አዲስ አበባ የልማት አብዮት ውስጥ የገባች እንዲሁም ብዙ ስራዎችን እያሳካች የምትገኝ ከተማ መሆኗን ገልፀዋል። በመሆኑም ከዚህ ቀደም ያጋጥሙ ለነበሩ ችግሮች መፍትሔ በመስጠት ከችግር ነፃ የሆነ አከባቢ መፍጠር የአስተዳደሩ አጀንዳ መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት ከሚያደርገው ጥረት በተጨማሪ ነዋሪዎች ከተማቸውን የማልማት፣ ወንዞችን የመንከባከብና በአከባቢያቸው ያሉ የወንዝ መፍሰሻ ቦይዎችን በማጽዳት በቆሻሻ እንዳይዘጉ የማድረግ ሃላፊነት እንዳለባቸው ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አሳስበዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ የከተማ አስተዳደሩ የአደጋ ተጋላጭነት ሁኔታን በአግባቡ አጥንቶ ዘላቂ ምላሽ መስጠት የሚያስችል ስራዎችን በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልጸው የወንዝ ዳርቻ አከባቢዎቻችን ውበት ሆነው ሰዎች የሚዝናኑባቸው እንጂ የአደጋ ስፍራዎች መሆን የለባቸውም በሚል የተጀመረው ስራ ውጤት እያመጣ ነው ብለዋል። ሥራ አስኪያጁ በዚህ ክረምት በሚሰሩ ስራዎችም የአደጋ ተጋላጭነትን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ መታቀዱን ተናግረዋል። አደጋ ቢያጋጥምም እንኳን በራስ አቅም ተጎጂዎችን ማቋቋምና ሰብዓዊ ድጋፍ ማድረግ የሚያስችል ስራ በሁሉም ክፍለ ከተሞች የአደጋ ስጋት የክምችት መጋዘኖችን የመገንባት ስራ መጠናቀቁን ኢንጂነር ወንድሙ ገልጸዋል።

ነዋሪዎቻችንን ከአደጋ መከላከል ቀዳሚ ስራችን ነው - ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ ዛሬ ከተማ አቀፍ የጎርፍ መከላከልና የአደጋ ዝግጁነት ንቅናቄ በአቃቂ ክፍለ ከተማ ተጀምሯል። በቦታው ተገኝተው ንቅናቄውን ያስጀመሩት የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ ንቅናቄውን በአቃቂ ቃሊቲ ጀምረን በሁሉም ለጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ዘላቂ ልማት እንዲኖር በማድረግ ነዋሪዎቻችንን ከአደጋ መከላከል የከተማ አስተዳደሩ ቀዳሚ ስራ ነው ብለዋል። ከጥቂት ዓመታት በፊት በጎርፍ ምክንያት ይከሰት የነበረው አደጋ አሳዛኝ እንደነበር እና እንደዚህ ዓይነቱን አደጋ ቀድሞ መከላከል ተገቢ መሆኑን የገለፁት ምክትል ከንቲባው አዲስ አበባ የልማት አብዮት ውስጥ የገባች እንዲሁም ብዙ ስራዎችን እያሳካች የምትገኝ ከተማ መሆኗን ገልፀዋል። በመሆኑም ከዚህ ቀደም ያጋጥሙ ለነበሩ ችግሮች መፍትሔ በመስጠት ከችግር ነፃ የሆነ አከባቢ መፍጠር የአስተዳደሩ አጀንዳ መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት ከሚያደርገው ጥረት በተጨማሪ ነዋሪዎች ከተማቸውን የማልማት፣ ወንዞችን የመንከባከብና በአከባቢያቸው ያሉ የወንዝ መፍሰሻ ቦይዎችን በማጽዳት በቆሻሻ እንዳይዘጉ የማድረግ ሃላፊነት እንዳለባቸው ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አሳስበዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ የከተማ አስተዳደሩ የአደጋ ተጋላጭነት ሁኔታን በአግባቡ አጥንቶ ዘላቂ ምላሽ መስጠት የሚያስችል ስራዎችን በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልጸው የወንዝ ዳርቻ አከባቢዎቻችን ውበት ሆነው ሰዎች የሚዝናኑባቸው እንጂ የአደጋ ስፍራዎች መሆን የለባቸውም በሚል የተጀመረው ስራ ውጤት እያመጣ ነው ብለዋል። ሥራ አስኪያጁ በዚህ ክረምት በሚሰሩ ስራዎችም የአደጋ ተጋላጭነትን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ መታቀዱን ተናግረዋል። አደጋ ቢያጋጥምም እንኳን በራስ አቅም ተጎጂዎችን ማቋቋምና ሰብዓዊ ድጋፍ ማድረግ የሚያስችል ስራ በሁሉም ክፍለ ከተሞች የአደጋ ስጋት የክምችት መጋዘኖችን የመገንባት ስራ መጠናቀቁን ኢንጂነር ወንድሙ ገልጸዋል።

የመረጠንን ህዝብ የምናመሰግነው በቃላት ብቻ ሳይሆን ችግሩን የሚፈቱ ተጨባጭ ተግባራዊ ምላሽ በመስጠት ነው። በተጣለብን በህዝብ እምነት ዳግም ኢትዮጵያን ለመምራት ተጨማሪ አምስት ዓመት ለፓርቲያችን ብልፅግና በተሰጠበት ማግስት በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት እጅግ የተጎሳቀለውን፥ ለኑሮ ምቹ ያልሆኑ መኖሪያ ቤቶችንና አካባቢውን  ወደ ንፁህ ፥ውብ መንደር ለመቀየር ከከንቲባ ፅ/ቤት ጀርባ ላይ “ አራዳ የበጎነት መንደር “ግንባታን ጀምረናል። በክረምት በጐ ፍቃድ 2500 ቤቶችን ለመገንባት ያቀድን ሲሆን ፣ዛሬ ባስጀመርነዉ የአራዳ የበጎነት መንደር ባለ 9 ወለል 8 ህንፃዎች  እና ሁለት በላ 4 ወለል የገበያ ማዕከል ያሉት ሲሆን ፥ የተጎሳቆሉ ቤቶችን እና አካባቢውን በመቀየር ለኑሮ ምቹ የሆኑ ፣ ንጽሕናቸውን የጠበቁ የመኖሪያ ቤቶችና አካባቢዎች፣ የጋራ መገልገያዎችን እና አረንጓዴ ሥፍራዎችን እንዲሁም ህፃናት ቦርቀው የሚጫወቱባቸው የስፓርት ሜዳዎች በጥቅሉ ለሰው ልጆች ምቹና ክብር የሚመጥን ዘመናዊ አኗኗርን የሚፈጥር የከተማዋን ውበት የሚቀይር መንደር ነው። በክረምት በጎ ፍቃድ የምንገነባው ቤት ብቻ ሳሆን አካባቢን እናፀዳለን፥  የጐርፍ መከላከያዎች እንገነባለን፣ ምንም ገቢ ለሌላቸው  ማዕድ እናጋራለን፥ ደም ልገሳ እናካሄዳለን፥    የጀመርነው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ እንተክላለን፣ የማጠናከርያ ትምህርት እንሰጣለን፣ የነፃ ህክምና አገልግሎት ፣ የመንገድ ትራፊክ ማሳለጥ እንዲሁም ከተማችን ውብ ፥ ለኑሮ ምቹ ከተማ የማድረግ ስራችን እጠናክረን እንሰራለን። የምንገነባው መተማመንን፣ ፅናትን፣ አብሮነትን፣ ወንድማማችነትን/ እህትማማችነትን፣ ክብራችንን በጥቅሉ የኢትዮዽያን የብልፅግና መንገድ  ነው። የከተማችን ባለሃብቶች  የህዝባችን አኗኗር ለመቀየር በምንሰራቸው ልማቶች ሁሉ  ስንጠራችሁ  ቀና እና ፈጣን ምላሽ ስለምትሰጡን እጅግ አድርገን እያመሰገንን፤  ዛሬም ግንባታውን የጀመርነው የአራዳ የበጎነት መንደር አብራችሁ ለመገንባት ቃል የገባችሁ ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ፥ የኢትዮዽያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣በላይነህ ክንዴ ፥ ያደታ ጁነዲን እያንዳንዳቸው አንድ ባለ 9 ወለል ህንፃ የሚገነቡ ሲሆን እንዲሁም ቲኤንቲ ኮንስትራክሽን፣ ግራንድ ሌጋሲ ሃውስ፥ ኢቲ ኦንላይን ኮሌጅ፣ አብይ ማስረሻ፥ ዴማ ሪልስቴት ፥ ቴምር ሪልስቴት፥ ስናፕ ትሬዲንግ፥ ጊፍት ሪልስቴት፥ መሃመድ አድናን ፥ አሚር በድሩ በጋራ ለመገንባት አብራችሁን ስለሆናችሁ በነዋሪዎች እና በራሴ ስም ከልብ አመሰግናለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ ከንቲባ አዳነች አቤቤ