uk
Feedback
Addis Ababa Design And Construction Works Bureau

Addis Ababa Design And Construction Works Bureau

Відкрити в Telegram

Government Organization

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Addis Ababa Design And Construction Works Bureau

Канал Addis Ababa Design And Construction Works Bureau (@addiscitycon) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 21 107 підписників, посідаючи 2 761 місце в категорії Політика та 1 603 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 21 107 підписників.

За останніми даними від 28 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 254, а за останні 24 години на 3, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 7.93%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 8.45% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 1 673 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 783 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 10.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
Government Organization

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 29 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Політика.

21 107
Підписники
+324 години
+357 днів
+25430 день
Архів дописів
ዓንዲ ሑቐ ህንፀት ከተማ

ዛሬ ማምሻዉን ከመላ አመራራችን ጋር በክረምት ወቅት የምንስራቸው የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች፥ የቤት ግንባታ፣የጎርፍ አደጋን መከላከል ፥ የፅዳት ስራዎች፥ የአረጓዴ አሻራ፥ ማዕድ ማጋራት፥ የክረምት
+9
ዛሬ ማምሻዉን ከመላ አመራራችን ጋር በክረምት ወቅት የምንስራቸው የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች፥ የቤት ግንባታ፣የጎርፍ አደጋን መከላከል ፥ የፅዳት ስራዎች፥ የአረጓዴ አሻራ፥ ማዕድ ማጋራት፥ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ፥ ደም ልገሳ፥ ተረጅነትና ድህነት ቅነሳ ወዘተ ስራዎች አፈፃፀምን ገምግመናል። በሁሉም መስክ ውጤታማ ተግባራት እየተፈፀሙ መሆኑን አረጋግጠናል።ሆኖም በክፍለ ከተሞች እና በተቋማት መካከል የአፈፃፀም ልዩነቶች ይታያሉ። በቀጣይም ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በቅንጅት መመራት የሚገባቸው፡- 👉የጀመርናቸዉን የቤቶች ግንባታን ማፉጠን፣ 👉ዲቾችን ማፅዳት እንዲሁም አዳዲስ ዲቾችን መገንባት 👉ከፍተኛ ሀብት ፈሶባቸው የለሙ ቦታዎች መንከባከብ ፅዳታቸውን መጠበቅ 👉አጠቃላይ የከተማ ፅዳት ባህል እንዲሆን መስራት 👉 በግንባታ ምክንያት በተረፈ ምርቶች መንገዶችን የሚያበላሹ፥ ዲቾችን የሚዘጉ አካላት በአፋጣኝ ችግሩን እንዲያርሙ ተጠያቂም እንዲሆኑ ማድረግ 👉 በአረንጋዴ አሻራ የጀመርነው ውጤታማ ስራ ለጥራቱም ትኩረት መስጠት እንዲሁም የችግኝ ተከላ ስራ በአጠረ ጊዜ እና ከእቅድ በላይ ማሳካት 👉 የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ሁሉም ዜጋ ባህል እንዲያደርገዉ የማስቻል ስራ መስራት 👉 ተማሪዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት በልዩ ትኩረት መስራት 👉 የጎልማሶች ትምህርት ማጠናከር 👉 ከተረጅነት ለመሸጋገር የተጀመሩ የሰብዓዊ ስራዎች ለመተግበር መጋዘኖች በጥራት የተገነቡ ቢሆንም ቀጣይ ስራ የሚሆነው በቂ የሰብዓዊ ድጋፍ ቁሶች እንዲኖራቸው ማድረግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ሁሉም አመራር በጥብቅ የሚፈፅማቸው ናቸው። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!

“ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለጉባዔው ተሳታፊዎች የሎጂስቲክስ እገዛ አድርገውልናል” መሥፍን አርዓያ (ፕ/ር) የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ተሳታፊዎች የሎጂ
+2
“ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለጉባዔው ተሳታፊዎች የሎጂስቲክስ እገዛ አድርገውልናል” መሥፍን አርዓያ (ፕ/ር) የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ተሳታፊዎች የሎጂስቲክስ ድጋፍ ማድረጋቸውን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መሥፍን አርዓያ (ፕ/ር) ተናገሩ፡፡ የምክክር ጉባዔውን ሂደት አስመልክቶ ዋና ኮሚሽነሩ በሰጡት መግለጫ፤ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በጉባዔው እየተሳተፉ ለሚገኙ አካል ጉዳተኞች ምክክር በሚደረግበት አቅራቢያ የማረፊያ ስፍራ ሰጥተውልናል ብለዋል፡፡ ለአዲስ አበባ ተሳታፊዎችም ክረምት እንደመሆኑ መጠን በተለይም ከሩቅ ለሚመጡት እገዛ እንዲያደርጉልን ጠይቀን እያገዙን ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል ኮሚሽኑ ለተመካካሪዎች ትራንስፖርትን ጨምሮ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ተሳታፊዎች የሚጠበቅበትን ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል፡፡

የፖሊሲ ጉዳይ ቅኝት - ሐምሌ 18፣ 2018 ዓ.ም #PMOEthiopia #RainySeasonVolunteering #PMInitiatives
የፖሊሲ ጉዳይ ቅኝት - ሐምሌ 18፣ 2018 ዓ.ም #PMOEthiopia #RainySeasonVolunteering #PMInitiatives

"የከተማዋን ገጽታ የሚመጥኑ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን ለማከናወን ሌት ተቀን ጥረት እየተደረገ ነው" አቶ ጃንጥራር አባይ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ መዲናችን አዲስ አበባን ለአካባቢ ጥበቃና ለዜጎች ጤና ተስማሚ፣ ምቹና ተመራጭ የከተማ ማዕከል ለማድረግ ያለመ "ጽዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ" የተሰኘ የሦስት ወር ከተማ አቀፍ ንቅናቄ በይፋ ተከፍቷል። በመክፈቻ ፕሮግራሙ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ በዚህ የሶስት ወራት የንቅናቄ መርሃ ግብር፤ የከተማ አስተዳደሩ በአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አማካኝነት ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ የአካባቢ ብክለትን በመከላከልና ህግ በማስከበር ረገድ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫና የተግባር ስራዎችን እንደሚያከናውን ገልጸዋል። አዲስ አበባ የአፍሪካ መዲና፣ የፌደራል መንግስቱ መቀመጫና በዓለም አቀፍ ደረጃ ሦስተኛዋ የዲፕሎማቲክ ማዕከል መሆኗን የገለጹትት ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ ፤ ይህንን ድርብርብ ኃላፊነት ለመወጣትና የከተማዋን ገጽታ የሚመጥኑ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን ለማከናወን ሌት ተቀን ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ምክትል ከንቲባው አክለውም በጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አብይ አህመድ ሃሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ልማት፣ የኮሪደር ልማት፣ የወንዝ ዳርቻዎችና የፓርኮች ግንባታ ለአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮቶችን ለመቋቋም እና ብክለትን ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አብራርተዋል። ሆኖም ከከተማዋ ፈጣን እድገት ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የፕላስቲክ፣ የአደገኛ ቆሻሻ እና የድምፅ ብክለቶች የዜጎችን በንጹህ አካባቢ የመኖር መብት የሚፃረሩ በመሆናቸው ጠንካራ ቁጥጥርና የጋራ ርብርብ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። ለቀጣዮቹ ሦስት ወራት የሚተገበረው የ"ጽዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ" ንቅናቄ በዋናነት በፕላስቲክ ብክለት መከላከል፣በአደገኛ ቆሻሻ ብክለት ቁጥጥር እና በድምፅ ብክለት መቀነስ ሦስት ዓበይት የብክለት ዓይነቶች ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ አቶ ጃንጥራር ገልጸዋል። ይህ ንቅናቄ ስኬታማ ይሆን ዘንድ መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ በጎ ፈቃደኞች፣ ሲቪክ ማህበራት፣ ምሁራንና የትምህርት ተቋማት እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን የተጣለባቸውን ታሪካዊና የዜግነት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ምክትል ከንቲባው አቶ ጃንጥራር አሳስበዋል።

በአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ የስራ እንቅስቃሴ ዙሪያ ዳሰሳ ያደረገውን መሰናዶ ማክሰኛ 10:00 በ AMN PLUS Tigrigna ይጠብቁ። መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ይፋዊ ገፆች ይወዳጁ ፌስቡክ https://www.facebook.com/AddisConstruction/ ቴሌግራም https://t.me/AddisCityCon ትዊተር https://twitter.com/AddisCity ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCwuES6TQUZmVlUT8tazLHmg ቲክቶክ https://tiktok.com/@design_and_construction1 ዋትሳፕ https://whatsapp.com/channel/0029Vani9gI0lwgzDJ1eFH1x ዌብሳይት www.addisconstructionwork.gov.et ነፃ የስልክ መስመር 9426

ጥራት ያለው፣ ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪና በክህሎት የበለጸገ የሰው ሃይል የማፍራት ተቋማዊ ራዕያችንን የምናሳድግበት ታላቅ ምዕራፍ ላይ እንገኛለን - አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ የአዲስ አበባ ከተማ የስራና ክህሎት ቢሮ የከተማዋ ወጣቶች በሙያና በክህሎት የታነጹ፣ በራሳቸው የሚተማመኑ እና የስራ ፈጠራ ክህሎት ያላቸው አምራች ዜጎች እንዲሆኑ ለማስቻል ከባለድርሻዎች ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የቢሮው ሃላፊ አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ የአዲስ አበባ ስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ላይ ገልጸዋል። ቢሮው በስሩ ባሉ 14 ነባር የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች በተለያዩ የሙያና የአገልግሎት ዘርፎች በየዓመቱ በአስር ሺዎች መካከለኛ ባለሙያዎችን እያፈራ እንደሚገኝ የጠቆሙት ሃላፊው ነባሮቹን ከጊዜው ጋር ከማዘመንና ከማሳደግ ባሻገር አዳዲስ ኮሌጆችን መገንባት አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። ዛሬ ግንባታው የተጀመረው አዲስ ስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሲጠናቀቅ የማሰልጠን አቅምን በከፍተኛ ሁኔታ የሚያሳድግ፣ የሰልጣኞችን ቁጥር የሚጨምር እና የስልጠና ጥራትን ወደ ላቀ ቴክኖሎጂ ደረጃ የሚያሸጋግር ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን አቶ ሚሊዮን የገለጹ ሲሆን ይህም ቢሯቸው የያዘውን ጥራት ያለውንና ተወዳዳሪ የሰው ሃይል የማፍራት ራዕይ በብቃት ለመወጣት የሚያስችለውን ተጨማሪ የትምህርትና የስልጠና ጉልበት ይፈጥርለታል። ስማርት ኮሌጁ ከ800 በላይ ወጣቶችን በዓመት ተቀብሎ በተለያዩ ዘርፎች ከማሰልጠን በዘለለ በውስጡ በሚቋቋመው የፈጠራ ማበቢያ (incubation center) አማካኝነት ወጣቶች በስልጠና ወቅት የሚያመጧቸውን አዳዲስ የቴክኖሎጂ ሃሳቦችንና የምርምር ውጤቶችን ወደ ተግባራዊ ቢዝነስ የሚቀይሩበት፣ የራሳቸውን ኢንተርፕራይዞች የሚመሰርቱበትና ለሌሎች ወጣቶችም የስራ እድል የሚፈጥሩበት ማዕከል እንደሚሆን ተነግሯል።

ዛሬ ከሰዎች ለሰዎች ድርጅት ጋር በመተባበር በሀገራችን በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታ አስጀምረናል። ይህ ስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታው ሲጠናቀቅ ወጣቶችን በ
+9
ዛሬ ከሰዎች ለሰዎች ድርጅት ጋር በመተባበር በሀገራችን በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታ አስጀምረናል። ይህ ስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታው ሲጠናቀቅ ወጣቶችን በማኑፋክቸሪንግ፣ በአውቶሞቲቭ፣ በኤሌክትሪክና ኤሌክትሮኒክስ፣ በኮሚዩኒኬሽንስ፣ በቴክስታይል እና የሲኤንሲ (CNC) ቴክኖሎጂዎች ላይ ተግባር ላይ ያተኮረ እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን የሚጠቀም ስልጠና ይሰጣል። ሀገርን ማልማት እና ከድህነት መላቀቅ በንድፈ ሃሳብ ብቻ በተገደቡ ትምህርቶች ማሳካት ስለማይቻል፣ ሃሳብን የሚያፈልቁ አዕምሮዎችን እና የሚሰሩ እጆችን ያጣመረ ክህሎት መር የሰው ሀይል እጅግ አስፈላጊ ናቸው። ዛሬ ያስጀመርነው ፕሮጀክት በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ወጣቶቻችንን ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት፣ ከንድፈ ሃሳብ ወደ ተግባር የሚያሸጋግር፣ አዲስ የሥራ እድል የሚፈጥር የክህሎት ድልድይ የሚሆን ነው። የዚህ ኮሌጅ ግንባታ በጥራትና በተቀመጠለት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ በልዩ ትኩረት የምንከታተለው ሲሆን፣ ፕሮጀክቱን በትብብር የሚገነባው የረጅም ጊዜ የልማት አጋር የሆነው ሰዎች ለሰዎች ድርጅት እና የሚሰራው ለትውልድ የሚሻገር አሻራ ነው ብላችሁ መሬታችሁን ለፕሮጀክቱ የለቀቃችሁ አርሶ አደሮችን በራሴና በተጠቃሚ ወጣቶች ስም ምስጋናዬን አቀርባለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ቢሮው በጉለሌ ክፍለከተማ ያስገነባቸውን የዓቅመ-ደካማ ቤቶች በይፋ አስተላለፈ፡፡ የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ባሳለፍነው በጀት ዓመት በጎ ፍቃደኛ ባለሀብቶችን በማስተባበር ካከናወናቸው
+9
ቢሮው በጉለሌ ክፍለከተማ ያስገነባቸውን የዓቅመ-ደካማ ቤቶች በይፋ አስተላለፈ፡፡ የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ባሳለፍነው በጀት ዓመት በጎ ፍቃደኛ ባለሀብቶችን በማስተባበር ካከናወናቸው የዓቅመ-ደካሞች ቤት ግንባታዎች ውስጥ የሁለተኛውን ዙር ቤቶች በዛሬው ዕለት በይፋ አስተላልፏል፡፡ በጉለሌ ክፍለከተማ ወረዳ 08 የተገነቡትንና በ6 አባወራዎች ስር የሚጠለሉ 13 ቤተሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርጉትን የእነዚህን ቤቶች ቁልፍ ለነዋሪዎቹ ያስረከቡት የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኃላፊ ኢ/ር አያልነሽ ሐብተማርያም በዚሁ ስነ-ስርዓት ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ቢሮው በ2018 ሰው ተኮር ፕሮግራሙ የዛሬዎቹን ጨምሮ 24 የዓቅመ ደካሞች መኖሪያዎችን ማስገንባት እንደቻለ አስታውሰው በዘርፈ ብዙ ሰው ተኮር ፕሮግራሙም ከዚህ ቀደም በመስሪያ ዕድሜያቸው ሀገርን አገልግለው በእድሜ እና በሌሎች ገፊ ምክንያቶች ለማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች የተጋለጡ ወገኖች በስፋት ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኝም ያነሱ ሲሆን በተስፋ ብርሀን የምገባ ማዕከል እና በሌሎች ስፍራዎች የሚደረጉ የማዕድ ማጋራትና ተያያዥ ድጋፍፎችን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡ በመጨረሻም ቢሮው ለመልካም ተግባር ያቀረበላቸውን ግብዣ በመቀበል ሰርተው ካገኙት ጥሪት ላይ ለወገኖቻቸው የተረፈ በጎ ተግባር ላደረጉት መስ ኤፍ ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ እንዲሁም አቻ ሁለገብ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማሕበርን በቢሮው እና በተጠቃሚ ወገኖች ስም አመስግነዋል፡፡ ሐምሌ 15/2018 ዓ/ም የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

በአዲስ አበባ እየተከናወኑ ያሉ ዘመን ተሻጋሪ የልማት ስራዎች መዲናዋን የዓለም አቀፍ ትኩረት ማዕከል አድርገዋታል! አዲስ አበባ ልክ እንደ ስሟ አዲስ እና ማራኪ ሆና በድጋሚ እየተወለደች ባለችበት በ
+6
በአዲስ አበባ እየተከናወኑ ያሉ ዘመን ተሻጋሪ የልማት ስራዎች መዲናዋን የዓለም አቀፍ ትኩረት ማዕከል አድርገዋታል! አዲስ አበባ ልክ እንደ ስሟ አዲስ እና ማራኪ ሆና በድጋሚ እየተወለደች ባለችበት በዚህ ወቅት፣ በመዲናዋ እየተከናወኑ ያሉ ዘመን ተሻጋሪ የኮሪደር፣ መልሶ ማልማት እና የወንዞች ዳርቻ ልማቶች የከተማዋን ገጽታ ሙሉ በሙሉ እየቀየሩት ነው። ከጫፍ እስከ ጫፍ የተዘረጉ ዘመናዊ መንገዶች፣ ለእግረኞች እና ለብስክሌተኞች የተሰናዱ ምቹና ደህንነታቸው የተጠበቁ መንገዶች፣ እንዲሁም ለዓይን ማራኪ አረንጓዴ ስፍራዎችና መናፈሻዎች ከተማዋን ለነዋሪዎቿ እጅግ ምቹ እና ስሉጥ የኑሮ ከባቢ እንዲኖራት አድርገውታል። የዚህ ታላቅ ለውጥ ሌላው አስደናቂ ገጽታ ፍትሃዊ የልማት ተደራሽነት መረጋገጡ መሆኑ ሲሆን፣ በአንድ አካባቢ ብቻ ሳይወሰን በሁሉም ክፍለ ከተሞችና ሰፈሮች ውስጥ በእኩል ደረጃ እየተዳረሰ ይገኛል። ዛሬ አዲስ አበባ የአፍሪካ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በድምቀት አስጠብቃ፣ ዓለም አቀፋዊ ደረጃዎችን የሚያሟሉ መሠረተ ልማቶችን በማሟላት የኮንፈረንስ ቱሪዝም ዋና መዲና መሆን ችላለች። ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚመጡ ታላላቅ እንግዶች የሚጎርፉባት፣ በንግድ፣ በባህልና በዕውቀት ልውውጥ ደምቃ የምትታይ፣ ቀንና ሌሊት እግር የሚበዛባት ሕያው ከተማ ሆና የምትቀጥለው መዲናችንን በሁሉ አቅጣጫ አብባና አምራ ማየት የጋራ ኩራት ነው። ይህቺን ታላቅ መዲና በጋራ ጠብቆና ከፍ አድርጎ ማስቀጠል ደግሞ የሁላችንም ታሪካዊ ኃላፊነት ነው።

አዲስ አበባ ከተማ የማያቋርጥ ዕድገት ማሳያ ናት- አቶ አደም ፋራህ! በአቶ አደም ፋራህ የተመራ የፓርቲው የዋናው ጽህፈት ቤት እና የክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች አመራሮች በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወነ ያለውን የተቋማት ግንባታ ስራዎችን ተመልክቷል። በዚህ ወቅት የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ አዲስ አበባ የማያቋርጥ ዕድገት ማሳያ ናት ሲሉ ገልጸዋል። አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለሌሎች የሀገራችን ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ትምህርት የሚወስድበት ስራዎችን እያከናወነች ነው፣ በፓርቲ ስራዎችም በተመሳሳይ ምሳሌ የሚሆን ተግባራት እያከናወነ እንደሆነ አንስተዋል። አዲስ አበባ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ እሳቤዎችን እና ኢኒሼቲቮችን በተሟላ መልኩ እየፈጸመች መሆኑን ብዙ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ማሳያዎች አሉ ብለዋል። ሕዝቡን አስተባብሮ በላቀ ትጋት እና ቁርጠኝነት መስራት በመቻሉ ባለፉት አምስት ዓመታት ስኬት ተግኝቷል። አዲስ አበባ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር የሚያሸጋግሩ ስራዎችን በመስራት ረገድ የድርሻውን እየተወጣች ነው ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ አቶ አደም ለዚህም አመራሩ እና ሕዝቡ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል። በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ በበኩላቸው፣ ሕዝብ በምርጫ የሰጠንን አደራ ለመወጣት፣ የሕዝቡን አዳዲስ የዕድገት ፍላጎት ማዕከል ያደረጉ ስራዎችን መስራት እንደሚገባ አንስተዋል። የተቋም ግንባታ ለሀገረ መንግስት ከፍተኛ አበርክቶ ያለው በመሆኑ በትኩረት እየሰራን ነውም ብለዋል። የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎችን በመለየት ሪፎርም ለማድረግ ከያዝናቸው ተግባራት መካከል አንዱ የፓርቲ የተቋም ግንባታ ነው ያሉት አቶ ሞገስ፣ ይህንንም በተሟሏ መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ስራዎች እየተከናወኑ ነው ሲሉ ጠቅሰዋል። በከተማዋ ምልከታ ባደረጉባቸው የፓርቲው ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል። ከነገ ጀምሮ የ2018 በጀት ዓመት የብልጽግና ፓርቲ እቅድ አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል።

"ወንዞቻችንን ከበሽታና ብክለት ምንጭነት ወደ ውበትና ጤናማነት" ከንቲባ አዳነች አቤቤ

"ለውጥ ሂደት ነው" ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ

"በመርህ እና በእውቀት የተገነባ ተቋም ፤ በውጤት የደመቀ ተግባራዊ አፈፃፀም"
"በመርህ እና በእውቀት የተገነባ ተቋም ፤ በውጤት የደመቀ ተግባራዊ አፈፃፀም"