en
Feedback
Addis Ababa Design And Construction Works Bureau

Addis Ababa Design And Construction Works Bureau

Open in Telegram

Government Organization

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Addis Ababa Design And Construction Works Bureau

Channel Addis Ababa Design And Construction Works Bureau (@addiscitycon) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 20 673 subscribers, ranking 2 849 in the Politics category and 1 629 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 20 673 subscribers.

According to the latest data from 09 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 269 over the last 30 days and by 7 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 12.56%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.77% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 2 595 views. Within the first day, a publication typically gains 1 812 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 16.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Government Organization

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 10 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Politics category.

20 673
Subscribers
+724 hours
+257 days
+26930 days
Posts Archive
ዛሬ በምርጫ ሥራዎቻችን አፈጻፀምና የድህረ ምርጫ ሥራዎቻችን በውጤታማነት በመከወን የያዝናቸውን ግቦች በተሟላ መልኩ ከማሳካት አንፃር የተገኙ ዉጤቶችን ከመላው የከተማችን አመራሮች ጋር ገምግመናል ።
+8
ዛሬ በምርጫ ሥራዎቻችን አፈጻፀምና የድህረ ምርጫ ሥራዎቻችን በውጤታማነት በመከወን የያዝናቸውን ግቦች በተሟላ መልኩ ከማሳካት አንፃር የተገኙ ዉጤቶችን ከመላው የከተማችን አመራሮች ጋር ገምግመናል ። 7ኛውን ጠቅላላ ሃገራዊ ምርጫ በስኬት እንዳይጠናቀቅ ለማደናቀፍ በውጭም በውስጥም በጋራ በማበር በሚደያ ዘመቻዎች እና በተለያዩ ቅስቀሳዎች ሰላም የማደፍረስ ዝግጅቶችና ትንኮሳዎች ተደርገው ሳይሳካላቸው በኢትዮዽያ ታሪክ ትልቅ እድገት የታየበት ዴሞክራስያዊ፥ ሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ በማካሄድ ኢትዮዽያዊን በፅናት አዲስ ታሪክ ፅፈዉ ኢትዮጲያ መርጣለች፥ ኢትዮጵያ አሸንፋለች። እንደሃገር ያሳካነው እጅግ ውጤታማ እና ታሪካዊ ምርጫ የህዝባችን ፣የአመራራችን፣ የአባሎቻችን ፣የደጋፊዎቻችን፣የሲቭክ ማህበራት ፣ የሚድያዎቻችን፣ ተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲዎች እንዲሁም በገለልተኝነትና በከፍተኛ ዲሲፕሊን ትልቅ ሃገራዊ ሃላፊነታቸዉን የተወጡት የፀጥታ አካላትና የምርጫ ቦርድ በጥቅሉ ሁሉም ባለድርሻ አካል እንደ ሀገር ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላንን ቁርጠኝነትና በጋራ ያሳካነው ግብ መሆኑን ተግባብተናል ። ለዚህም ሁሉንም ባለድርሻ አካላት እናመሰግናለን። የድህረ ምርጫ ስራዎቻችን በውጤታማነት በመፈፀም ይህንን ፅኑ ህዝብ ለመካስ ያስቀመጥናቸዉን ግቦች በተሟላ መልኩ ለማሳካት ከመላው አመራራችን ጋር ተግባብተናል። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የ5ቱ ዓመታት ገፆች፡ በመደመር ትውልድ ያበበችውና ነዋሪዎቿን ያከበረችው አዲሲቱ ከተማ የከተሜነት እውነተኛ ትርጉም በሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች መደርደር ወይም በኮንክሪት ክምችት ብቻ ሳይሆን፣ ነዋሪዎች በክብር፣ በምቾትና በደህንነት በሚኖሩበት ዘመናዊ ሥርዓት ይለካል። ካለፈው 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ እስከ 7ኛው ምርጫ ዋዜማ በተዘረጉት አምስት ዓመታት፣ የመደመር ትውልድ የከተሞቻችንን የትላንት ገፅታ በመቀየር፣ ከተሞችን ከድህነትና ከጥግግት አውጥቶ ለነዋሪዎቻቸው የተመቹ የብልፅግና ማዕከላት እንዲሆኑ አስደናቂ ስራዎችን በመንግሥት መሪነት አከናውኗል። በእነዚህ የ5ቱ ዓመታት ገፆች ጎልቶ ከሚታየው ስኬት አንዱ የቤት ልማት አብዮት ነው። ቀደም ሲል ዘላቂና ውጤታማ ያልነበረውን የቤት ልማት ፕሮግራም በአዲስ መልክ በመቃኘት ታላቅ የቤት አቅርቦት ንቅናቄ ተደርጓል። መንግሥት በዋነኝነት ሲያከናውነው የነበረውን ልማት ከግል ዘርፉ እንዲሁም ከመንግሥትና የግል አጋርነት (PPP) ጋር በማስተሳሰር የቤቶች ልማት በከፍተኛ ፍጥነት እንዲከናወን ተደርጓል። በዚህም ከ2013 እስከ 2017 በጀት ዓመት ባሉት ጊዜያት ብቻ ከመንግሥት፣ ከሪል ስቴት አልሚዎችና ከግል ቤት ሠሪዎች አቅም ጋር ተደምሮ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ቤቶች ተገንብተዋል። ከዚህ ጎን ለጎንም፣ ዐቅማቸው ዝቅተኛ ለሆኑ ቤት ፈላጊዎች በመንግሥት በኩል የሚከናወኑ የቤት ልማት ፕሮግራሞች ሳይቋረጡ ቀጥለዋል። የመደመር ከተሜነት ሰውን ማዕከል ያደረገ በመሆኑ፣ ማኅበረሰብን በማስተባበር ዐቅመ ደካማ ለሆኑ ወገኖች 166,207 ደረጃቸውን የጠበቁ ቤቶች ተገንብተው ተላልፈዋል። ከተሞችን ከእርጅናና ከድህነት ገፅታ ለማላቀቅ፣ በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ ቤቶችን ደረጃ የማሳደግ ሥራ በስፋት ተከናውኗል። በ2013 ዓ.ም ከ75 በመቶ በላይ የነበረውን ከደረጃ በታች የሆኑ (substandard) ቤቶች ድርሻ፣ በ2017 ዓ.ም ወደ 52 በመቶ ዝቅ ማድረግ ተችሏል። ይህ ዜጎችን ከማይመችና ኋላቀር አኗኗር ወደ ዘመናዊ የኑሮ ሁኔታ በፈቃደኝነት ያሸጋገረ የክብር ጉዞ ነው። ይህ ታላቅ የከተማ ትራንስፎርሜሽን የሲቪል ሰርቪሱንና የከተሞችን አገልግሎት ከማዘመን ጋር ተጣምሮ የተጓዘ ነው። ከተሞች ዘመኑን የዋጀ አደረጃጀትና የአስተዳደር ሥርዓት እንዲኖራቸው በማድረግ፣ የማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች ለዜጎች በተሻለ ቅልጥፍና እንዲቀርቡ ተደርጓል። ይሁን እንጂ፣ መንግሥት ከተሞችን በተቀናጀ አግባብ ሲያለማ፣ አንዳንድ ኃይሎች ይህንን የልማት አቅጣጫ ባለመረዳት የተዛባ አመለካከት ሲያራምዱ ቆይተዋል። ዜጎችን ወደ ተሻለ የኑሮ ሁኔታ ለማሸጋገር የሚሰሩትን የመልሶ ማልማት ስራዎች "ማፈናቀልና ማህበራዊ ኢንጂነሪንግ" ብለው ሲስሉ፣ የከተማን ይዞታ ስርዓት ለማስያዝና አረንጓዴ ቦታዎችን ለመጠበቅ የሚወሰዱ ህጋዊ እርምጃዎችን በሌላ ስም ለማጠልሸት ሞክረዋል። አልፎ ተርፎም ከተሞቻችን ባህላችንንና ታሪካችንን እንዲያንፀባርቁ ለማድረግ የተሰሩትን የውበት ሥራዎች "ታሪክን እንደ ማውደም" አድርገው አቅርበዋል። ሆኖም እውነታው በተግባር ሊደበቅ አይችልም። ዜጎቻችን የስራዎቹን ፋይዳ አውቀው ምስክርነታቸውን ሲሰጡ፣ የውጭ ሀገራት ሚዲያዎችና ዜጎች ሳይቀሩ በከተሞቻችን ላይ የተመዘገቡትን አስደናቂ ለውጦች እያደነቁ ይገኛሉ። የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና የሲቪል ሰርቪሱን ውጤታማ ለማድረግ የሚከናወኑ ሪፎርሞችንም አሉታዊ ስም በመስጠት ለውጡን ለማደናቀፍ የተሞከሩ ሙከራዎች ከሽፈዋል። በአጠቃላይ እነዚህ የ5ቱ ዓመታት ገፆች፣ መንግሥት ከተሞችን የነገው ዘመን የሥልጣኔ ማዕከላት ለማድረግ ያለውን ግልጽ አቋምና የማድረግ አቅም በተግባር ያረጋገጡ፣ እንዲሁም ለነዋሪዎቻቸው ምቹና ዘመናዊ ከተሞችን የፈጠሩ ደማቅ ታሪካዊ ምዕራፎች ናቸው።

The New Face of Addis

ከሀገር በቀል ጥበብ እስከ መዲናዋ ውበት አዲስ አበባን ከተፈጥሮ ጋር ያስታረቀው አረንጓዴ ልማት አዲስ አበባ የተመሰረተችው ከተራራ እና ከውኃ ጋር በተያያዘ የሕይወት ዑደት ውስጥ ነው። እንጦጦ ለአዲስ አበባ የተፈጥሮ ውበቷና ከነፋስ መከላከያ መከታዋ ሲሆን፤ ቀጨኔ፣ ቀበና፣ ግንፍሌ፣ ቡልቡላ እና ሌሎችም ወንዞች ደግሞ የከተማዋ ዋነኛ የሕይወት መስመሮች ነበሩ። ይህንን የቆየና የልማት አቅጣጫ በአዲስ እሳቤ ለመቀየር፣ አዲስ አበባ አረንጓዴ እና ተፈጥሮን ማዕከል ያደረገ መንገድ መያዝ ግድ ስላላት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት ይፋ የሆነውን ከተማዋን የማስዋብ ፕሮጀክት በመቅረጽ በ2011 ዓ.ም ወደ ተግባራዊ ስራ ተገብቷል። በዚህ አዲስ መዋቅር ከተሰሩ በርካታ ስኬታማ ተግባራት መካከል የሚጠቀሰው የእንጦጦ-ቀጨኔ መድኃኔዓለም የወንዝ ዳርቻ ልማት፤ የተራራ፣ የሸለቆ፣ የባህል፣ የሥራ ፈጠራ እና የአካባቢ ጥበቃ ታላቅ ድምር ውጤት ሆኗል። ይህ ልማት ሀገር በቀል ማንነትንና እውቀትን ያከበረ መሆኑን ያሳየበት፣ የኮንሶዎችን የዘመናት ጎርፍ የመከላከል ጥበብ የእርከን ሥራ በተግባር የተገበረበት ነው፡ አረንጓዴ ልማት ውበት ብቻ ሳይሆን የጠንካራ ኢኮኖሚ መሰረትም ጭምር ነው። በእንጦጦ-ቀጨኔ እና በመላው አዲስ አበባ የሚገኙ የወንዝ ዳርቻ የልማት ሥፍራዎች አሁን ላይ ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድልን መፍጠር ችለዋል። ካፌዎች፣ የብስክሌት ሽያጭና ኪራዮች፣ እንዲሁም የቱሪስት አገልግሎቶች ለነዋሪው አዲስ የገቢ ምንጭ የፈጠሩ ሲሆን፤ በሌላ በኩል የሚፈጠሩት የባህል እና የገበያ ትስስሮች ለአካባቢው ልዩ ድባብ መፈጠሪያ እና ለማኅበረሰቡ ማንነትን መግለጫ መንገድ ሆነዋል። በተለይም ቀጨኔን በሸክላ ሥራዋ፣ ሽሮሜዳን ደግሞ በሸማ ጥበቧ የምናውቃቸውን የእጅ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ምርቶቻቸውን ደህንነቱ በተጠበቀ፣ ለጎብኚዎች በቀላሉ በሚደርስ እና ንጽህናው በተጠበቀ የሕዝብ ገበያ ለማቅረብ ሰፊ ዕድል አግኝተዋል። ፅዱ ከተማ ማለት ውብ መንገድ ብቻ ሳይሆን ጤናማ ነዋሪ፣ የተጠበቀ ተፈጥሮ፣ የተነቃቃ ኢኮኖሚ እና ለትውልድ የሚተርፍ ማለት ነው።

በኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት በየወሩ እየተዘጋጀ ለንባብ የሚበቃው ዜና መፅሔት ቅፅ 04 ቁጥር 38 (የወርሀ ግንቦት 2018 ) ዕትም እንሆ የቢሮውን ይፋዊ የማሕበራዊ ገፆች ይከታተሉ ፌስቡክ https://www.facebook.com/AddisConstruction/ ቴሌግራም https://t.me/AddisCityCon ትዊተር https://twitter.com/AddisCity ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCwuES6TQUZmVlUT8tazLHmg ቲክቶክ https://tiktok.com/@design_and_construction1 ዋትሳፕ https://whatsapp.com/channel/0029Vani9gI0lwgzDJ1eFH1x ዌብሳይት www.addisconstructionwork.gov.et ነፃ የስልክ መስመር 9426

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን በመጠቀም የተገነቡ ቤቶችን የሚያሳይ የግንባታ ሳይት ጎብኝተዋል

ዛሬ ማለዳ በሶስተኛው ዙር የጀመርናቸውን 13.4 ኪሜ የሚሸፍነውን የኮሪደር ልማት ስራዎችን አፈፃፀም ገምግመናል። የኮሪደሮቹ ልማት በአምስት የኮሪደር መስመሮች ተከፋፍለዉ እየተሰሩ ሲሆን እነርሱም:-
+9
ዛሬ ማለዳ በሶስተኛው ዙር የጀመርናቸውን 13.4 ኪሜ የሚሸፍነውን የኮሪደር ልማት ስራዎችን አፈፃፀም ገምግመናል። የኮሪደሮቹ ልማት በአምስት የኮሪደር መስመሮች ተከፋፍለዉ እየተሰሩ ሲሆን እነርሱም:- 1- ከቦሌ መድሃኔዓለም እስከ ጎላጎል ( የቦሌ አትላስን መንገድ ከመስቀል አደባባ መገናኛ መንገድ ጋር የሚገናኝ) ፣ 2- ከጎላጎል እስከ እንግሊዝ ኤምባሲ ( የቀበና መገናኛ መንገድን ከመስቀል አደባባ መገናኛ መንገድ ጋር የሚገናኝ) ፣ 3- ከቦሌ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በሞኤኮ እስከ ቦሌ መገናኛ መንገድ ( የቦሌ አትላስን መንገድ ከቦሌ መገናኛ መንገድ ጋር የሚገናኝ)፣ 4- ከኢምፔሪያል በአደይ አበባ ስቴድዮም እስከ ሻላ መናፈሻ ፣ 5-ከውሃ ልማት በአትላስ ያለውን እና ከአትላስ እስከ ቦሌ ሩዋንዳ ( የቦሌ አትላስ መንገድን ከመስቀል አደባባ መገናኛ መንገድ ጋር የሚገናኝ) በከፍተኛ ደረጃ የመንገድ ኔትወርኩን የሚያሰፋ፣ የንግድ ተቋማን፣ ሰፋፊ የእግረኛ መንገድ፣ የሳይክል መንገድ እና ለትራንስፖርት አገልግሎት ምቹ እንዲሆኑ ተደርገው እየተገነቡም ናቸው። በተጨማሪም በርካታ የህዝብ አገልግሎት መስጫ ግንባታዎችን የያዘ ሲሆን የግንባታውም ሂደትም በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል። በአደይ አበባ ስታዲየም ዙሪያ አስቀድመው የተጀመሩ የኮሪደርና ሌሎች መሠረተ ልማት ግንባታዎች በፍጥነትና በጥራት እንዲከናወኑ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ከኮሪደሩ በተጨማሪም ለብዙ ዘመናት ተረስቶ የኖረ፣ ከሕዝብ ተወስዶ በግለሰቦች ያለአግባብ ተወሮ ለብዙ ብልሽት ተዳርጎ የኖረውን ቦታ ለህዝብ አገልግሎት እንዲውል ተደርጎ በመሰራት ላይ ይገኛል። ፕሮጀክቶቹን እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ለማዋል በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ ከንቲባ አዳነች አቤቤ

“ከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች አካታች፣ ተደራሽና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት አየሰራ ነው!” በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላ
+8
“ከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች አካታች፣ ተደራሽና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት አየሰራ ነው!” በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ጀማሉ ጀምበር (ዶ/ር) ከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች አካታች፣ ተደራሽና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት አየተሰራ ነው ሲሉ ዶር ጀማሉ ጀንበር ገለፁ። አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አላስፈላጊ የቢሮክራሲ አሰራርን ያስቀረና ተጠያቂነትን ያሰፈነ ነውም ብለዋል። በዛሬው ዕለት ለአገልግሎት የበቃው የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል የመንግስት አገልግሎት የየካ ማዕከል 96 ተገልጋዮችን በአንድ ጊዜ ማስተናገድ የሚያስችል መስኮትና ሌሎች መሰረተ ልማቶች የተሟሉለት መሆኑን አስረድተዋል። ማዕከሉ የ22 ተቋማትን 114 አገልግሎት መስጠት ያስችላል። በቀጣይ ተጨማሪ አገልግሎቶች እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል።

ቃል በተግባር በከተማችን ተጠናክሮ ቀጥሏል--- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል የመንግስት አገልግ
+9
ቃል በተግባር በከተማችን ተጠናክሮ ቀጥሏል--- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል የመንግስት አገልግሎት የካ ማዕከልን መርቀው አስጀመሩ። በም/ከንቲባው የተመረቀው የየካ ማዕከል በከተማችን 9ኛው መሶብ ዲጅታል የመንግስት አገልግሎት ነው። መሶብ በከተማ አስተዳደሩ የአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ያሉ የህዝቡን ቅሬታዎችን እየፈታ መሆኑንም አቶ ጃንጥራር አባይ ተናግረዋል። በዚህ ዓመት ቀደም ሲልና አሁን ላይ ወደ ስራ በገቡ የመሶብ ማዕከላት የተገልጋዮች እርካታን 99 በመቶ ማድረስ ተችሏል። ይህን የነዋሪዎችን የአገልግሎት እንግልት ለማስቀረት ከምርጫ ማግስትም አዳዲስ የመሶብ ዲጅታል ማዕከላትን ወደ ስራ የማስገባት ጥረታችንን አጠናክረን በመቀጠል 9ኛው የየካ ማዕከል ላይ ደርሰናል። በቀጣይ ጥቂት ቀናት ደግሞ ግንባታቸው የተጠናቀቁትን የአቃቂና የለሚ ኩራ ማዕከላትን ወደ ስራ የምናስገባ ይሆናል። ተጨማሪ ስራ በመስራት የህዝባችንን እርካታ እንዲጨምር እናደርጋለን ሲሉም አቶ ጃንጥራር ተናግረዋል።

ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር መፈፀም መለያችን ነው!! ዛሬ 9ኛውን መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በየካ ክፍለ ከተማ አስጀምረናል። የመንግስት አገልግሎት አሰጣጣችንን ቀልጣፋ
+9
ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር መፈፀም መለያችን ነው!! ዛሬ 9ኛውን መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በየካ ክፍለ ከተማ አስጀምረናል። የመንግስት አገልግሎት አሰጣጣችንን ቀልጣፋ፣ ፈጣን፣ ግልፅ እና ተደራሽ ለማድረግ በሁሉም ክፍለ ከተሞች መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ስራ በ2018 በሁሉም ክፍለ ከተሞች ስራ ለማስጀመር አቅደን ለህዝቡ ቃል በገባነው መሰረት እነሆ የዛሬውን ጨምሮ 9 ማዕከላትን ወደ ስራ አስገብተናል። የአገልግሎት እንግልትን፣ እዚህም እዝያም ጉቦ የመጠየቅ ችግርን ለመቅርፍ፣ ተጠያቂነትን እና የህዝባችንን በክብር የመገልገል መብት ለማረጋገጥ፣ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜውንና ገንዘቡን ሳያባክን ያለውን ሃብት ለልማት እንዲያውለው ለማድረግ ያቀድነውን ግብ በማሳካት የጀመርነውን የብልፅግና ጉዞ አጠናክረን እንቀጥላለን ። የየካ ክፍለ ከተማ ባለ 7 ወለል ህንፃ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በፍጥነት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ የሰራችሁትን ሁሉ አመሰግናለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ውድድር አሸናፊ ሆነች በ19ኛው የኢትዮጵያ የግማሽ ማራቶን ውድድር በሴቶች የአዲስ አበባ ፖሊሷ መሰለች አለማየሁ አሸንፋለች። ዝማም ማራኪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለተኛ ወጥታለች። መነሻ እና መድረሻ
+3
ውድድር አሸናፊ ሆነች በ19ኛው የኢትዮጵያ የግማሽ ማራቶን ውድድር በሴቶች የአዲስ አበባ ፖሊሷ መሰለች አለማየሁ አሸንፋለች። ዝማም ማራኪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለተኛ ወጥታለች። መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ አድርጎ በተከናወነው ውድድር በወንዶች 455 እና በሴቶች 183 በድምሩ 638 አትሌቶች ተሳትፈውበታል፡፡

የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ሩጫ እየተካሄደ ነው 19ኛው የኢትዮጵያ የግማሽ ማራቶን ውድድር በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው ውድድሩ በወንዶች 455
+3
የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ሩጫ እየተካሄደ ነው 19ኛው የኢትዮጵያ የግማሽ ማራቶን ውድድር በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው ውድድሩ በወንዶች 455 እና በሴቶች 183 በድምሩ 638 አትሌቶች እየተሳተፉበት እንደሚገኝ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል። በዴንማርክ ኮፐንሀገን ለሚካሄደው የግማሽ ማራቶን ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች በውድድሩ እንደሚመረጡ ተገልጿል።

የቀድሞ የአርሰናል ተጫዋች ኢማኑኤል ኢቦዬን ጨምሮ የክለቡ ደጋፊዎች እና የAFTV ሚድያ በአዲስ አበባ ያደረጉት ጉብኝት በምስል!
+9
የቀድሞ የአርሰናል ተጫዋች ኢማኑኤል ኢቦዬን ጨምሮ የክለቡ ደጋፊዎች እና የAFTV ሚድያ በአዲስ አበባ ያደረጉት ጉብኝት በምስል!

አዲስ አበባ፥ የስፖርት ቱሪዝም ማዕከል! የአርሰናል ክለብ ደጋፊዎች እና የቀድሞው የክለቡ ተጫዋች አዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችና የተለያዩ ታሪካዊ መስህቦችን ጎበኙ። መንግስት የስፖ
+7
አዲስ አበባ፥ የስፖርት ቱሪዝም ማዕከል! የአርሰናል ክለብ ደጋፊዎች እና የቀድሞው የክለቡ ተጫዋች አዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችና የተለያዩ ታሪካዊ መስህቦችን ጎበኙ። መንግስት የስፖርት ቱሪዝም ለማሳደግ፣ የተለያዩ የስፖርት ማዕከላትን ከመገንባት ባሻገር፥ ሀገራዊ፣ ዓለማቀፉዊና አህጉራዊ ስፖርታዊ ፌስቲቫሎችን እንዲዘጋጁ በማድረግ ህብረተሰቡ እየተዝናና ጤናውን እንዲጠብቅ ምቹ ሁኔታን ተፈጥሯል። የቀድሞው የአርሰናል ተጫዋች ኢማኑኤል ኢቦዬን ጨምሮ የክለቡ ደጋፊዎች እና የAFTV ሚድያ በከተማችን የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችና የስፖርት ማዕከላትን በዛሬው ዕለት ጎብኝተዋል።

ምርጫውን ለማደናቀፍ የተደረገው ጥረት በሕዝብ እና በጸጥታ አካላት ቅንጅት ከሽፏል፡- የሰላም ሚኒስቴር በኢትዮጵያ የተካሄደውን ሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ ለማደናቀፍና የሕዝብን ሰላም ለማደፍረስ ጽንፈኛ ኃይሎችና የውጭ ጠላቶች የከፈቱት ሁለንተናዊ ጥቃት መክሸፉን የሰላም ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ በሰጠው መግለጫ ሀገራዊ ለውጡን የማይቀበሉ አካላት በመሬት ላይ የሽብር ጥቃቶችን ከመፈጸም ጀምሮ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የፕሮፓጋንዳና የሥነ-ልቦና ጦርነት ሲያካሂዱ ቆይተዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት ምርጫውን የህልውና እና የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማረጋገጫ አድርጎ በመውሰድ በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን የገለጸው ሚኒስቴሩ፤ በአንጻሩ የስልጣን ሽግግርን በድምጽ መስጫ ኮሮጆ ሳይሆን በኃይል ለመጠቅለል የሚሹ የውስጥ ቅጥረኞችና የኢትዮጵያን እድገት የማይፈልጉ የውጭ ኃይሎች ሂደቱን ለማስቆም ከምርጫው በፊት፣ ወቅትና በኋላ ከፍተኛ ሴራዎችን መሸረባቸውን ይፋ አድርጓል። አፍራሽ ኃይሎቹ የመንግሥትን ሕጋዊ ቅቡልነት ለማሳጣትና ኢትዮጵያን ወደ ሥርዓት አልበኝነት ለመክተት ሕዝቡ የምርጫ ካርድ እንዳይወስድ፣ በፖለቲካ ድጋፍ ሰልፎች ላይ እንዳይገኝ እና በምርጫው ቀን ድምጽ እንዳይሰጥ ቅስቀሳ ሲያደርጉ እንደነበር ተጠቅሷል። ሆኖም የኢትዮጵያ ህሕብ ለጥሪዎቻቸው እውቅና ባለመስጠትና የጽንፈኝነትን አጀንዳ ውድቅ በማድረግ፥ ከፍተኛ ቁጥር ባለው ተሳትፎ የምርጫ ካርድ በመውሰድ፣ በሰልፎች ላይ በነጻነት በመገኘትና በምርጫው ቀን በነቂስ ወጥቶ ድምጽ በመስጠት አፍራሽ ኃይሎቹን ማሸነፉን ሚኒስቴሩ ገልጿል። ይህ የዲሞክራሲ ስኬት ያለመስዋዕትነት እንዳልመጣ የጠቀሰው የሰላም ሚኒስቴር፤ የጸጥታ ተቋማት ባደረጉት ወቅቱን የጠበቀና የተቀናጀ አጸፋዊ እርምጃ የሽብር ዕቅዶቹ ሊከሽፉ መቻላቸውን አስታውቋል። ሆኖም የሕዝቡን አብሮነት ለመስበር የተሞከሩ የሽብር ጥቃቶች እንደነበሩ ጠቅሶ፤ ህዝቡ የከፈለው መስዋዕትነት ጽንፈኝነትን በመቃወም ሀገርን የሚያስቀጥል ሕጋዊ መንግስት ለመመስረት ያለውን ጽኑ ፍላጎት ያሳየበት መሆኑም ተመልክቷል። AMN

ከአክሞ ማዳን በፊት መከላከል ትኩረት ማድረግ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ አህጉራዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው በአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራን በተግባራዊ ፖሊሲዎች ለመደገፍ ያለመ አህጉራዊ ጉባኤ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰኔ 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) ያዘጋጀው ይህ ጉባኤ በአካዳሚክ ምርምሮች እና በፖሊሲ አፈጻጸሞች መካከል ያለውን ክፍተት መሙላትን ታሳቢ ያደረገ ነው። የአፍሪካ ልማትና የተግባራዊ መፍትሄዎች መድረክ (ADIF 2026) የሚል ስያሜ ያለው ጉባኤ “በአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳደግ የሚረዱ ምርጥ ተሞክሮዎችና የፈጠራ መፍትሔዎች” በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ ነው። ጉባኤው በአፍሪካ በፍጥነት እያደገ የሚገኘውን የወጣት ማኅበረሰብ፣ በዓመት ከ15 ሚሊዮን በላይ የሥራ ዕድል በመፍጠር አህጉራዊው ፍላጎትን ለመመለስ ከተያዘው ውጥን ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነው። ይህ አዲስ መድረክ ከተለመዱ አህጉራዊ ስብሰባዎች በተለየ፤ የፖሊሲ አፈጻጸምን በማፋጠን በዘርፉ ያለውን የፖሊሲ እና የአሰራር ሂደት ለማቀለጣፈ ያለመ መሆኑን ኢዜአ ከኢሲኤ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በዚህም መሠረት የኢኮኖሚክ ኮሚሽኑ በገንዘብ እጥረት ምክንያት መሬት ያልወረዱ ጥናታዊ ምርምሮችን ወደ ተግባር ለመለወጥ፣ በጥቂት አካባቢዎች ተሞክረው ስኬታማ የሆኑ አነስተኛ የሙከራ ፕሮጀክቶችን ለማስፋት እንዲሁም አህጉር በቀል ምርጥ ተሞክሮዎችን በአገራት አጠቃላይ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች ውስጥ በቀጥታ ለማካተት አቅዷል። አሠራሩ በልማት ላይ የሚፈሱ የአህጉሪቱ ኢንቨስትመንቶች አስተማማኝና ዘላቂ ውጤት እንዲያመጡ ለማድረግ ትልቅ እገዛ ይኖረዋል ተብሏል። የፎረሙን ውጤታማነትና ተጠያቂነት በተረጋገጠ መልኩ ለመከታተልም፣ ከጉባኤው በፊት፣ በጉባኤው ወቅትና ከጉባኤው በኋላ የሚተገበር የአሠራር ሥርዓት ተዘርግቷል። የመድረኩን ቀጣይነትና ትስስር አስተማማኝ ለማድረግ፣ የየዓመቱ መሪ ሀሳቦችን አንዱ ከሌላው ጋር በማስተሳሰር እና ተመጋጋቢ በማድረግ እንደሚዘጋጁ ኮሚሽኑ አስታውቋል። በቀጣይ የሚካሄዱት ፎረሞች፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና (AfCFTA) ትግበራን ከአህጉራዊ የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂዎች ጋር ማስተሳሰር ጨምሮ ሌሎች የልማት የትኩረት መስኮችን ታሳቢ በማድረግ እንደሚካሄድ መገለጹን ኢዜአ ዘግቧል።