ch
Feedback
Addis Ababa Design And Construction Works Bureau

Addis Ababa Design And Construction Works Bureau

前往频道在 Telegram

Government Organization

显示更多

📈 Telegram 频道 Addis Ababa Design And Construction Works Bureau 的分析概览

频道 Addis Ababa Design And Construction Works Bureau (@addiscitycon) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 20 649 名订阅者,在 政治 类别中位列第 2 855,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 629

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 20 649 名订阅者。

根据 07 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 265,过去 24 小时变化为 -5,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 13.40%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.70% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 766 次浏览,首日通常累积 1 796 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 18

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Government Organization

凭借高频更新(最新数据采集于 08 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 政治 类别中的关键影响点。

20 649
订阅者
-524 小时
-67
+26530
帖子存档
“ከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች አካታች፣ ተደራሽና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት አየሰራ ነው!” በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላ
+8
“ከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች አካታች፣ ተደራሽና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት አየሰራ ነው!” በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ጀማሉ ጀምበር (ዶ/ር) ከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች አካታች፣ ተደራሽና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት አየተሰራ ነው ሲሉ ዶር ጀማሉ ጀንበር ገለፁ። አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አላስፈላጊ የቢሮክራሲ አሰራርን ያስቀረና ተጠያቂነትን ያሰፈነ ነውም ብለዋል። በዛሬው ዕለት ለአገልግሎት የበቃው የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል የመንግስት አገልግሎት የየካ ማዕከል 96 ተገልጋዮችን በአንድ ጊዜ ማስተናገድ የሚያስችል መስኮትና ሌሎች መሰረተ ልማቶች የተሟሉለት መሆኑን አስረድተዋል። ማዕከሉ የ22 ተቋማትን 114 አገልግሎት መስጠት ያስችላል። በቀጣይ ተጨማሪ አገልግሎቶች እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል።

ቃል በተግባር በከተማችን ተጠናክሮ ቀጥሏል--- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል የመንግስት አገልግ
+9
ቃል በተግባር በከተማችን ተጠናክሮ ቀጥሏል--- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል የመንግስት አገልግሎት የካ ማዕከልን መርቀው አስጀመሩ። በም/ከንቲባው የተመረቀው የየካ ማዕከል በከተማችን 9ኛው መሶብ ዲጅታል የመንግስት አገልግሎት ነው። መሶብ በከተማ አስተዳደሩ የአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ያሉ የህዝቡን ቅሬታዎችን እየፈታ መሆኑንም አቶ ጃንጥራር አባይ ተናግረዋል። በዚህ ዓመት ቀደም ሲልና አሁን ላይ ወደ ስራ በገቡ የመሶብ ማዕከላት የተገልጋዮች እርካታን 99 በመቶ ማድረስ ተችሏል። ይህን የነዋሪዎችን የአገልግሎት እንግልት ለማስቀረት ከምርጫ ማግስትም አዳዲስ የመሶብ ዲጅታል ማዕከላትን ወደ ስራ የማስገባት ጥረታችንን አጠናክረን በመቀጠል 9ኛው የየካ ማዕከል ላይ ደርሰናል። በቀጣይ ጥቂት ቀናት ደግሞ ግንባታቸው የተጠናቀቁትን የአቃቂና የለሚ ኩራ ማዕከላትን ወደ ስራ የምናስገባ ይሆናል። ተጨማሪ ስራ በመስራት የህዝባችንን እርካታ እንዲጨምር እናደርጋለን ሲሉም አቶ ጃንጥራር ተናግረዋል።

ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር መፈፀም መለያችን ነው!! ዛሬ 9ኛውን መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በየካ ክፍለ ከተማ አስጀምረናል። የመንግስት አገልግሎት አሰጣጣችንን ቀልጣፋ
+9
ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር መፈፀም መለያችን ነው!! ዛሬ 9ኛውን መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በየካ ክፍለ ከተማ አስጀምረናል። የመንግስት አገልግሎት አሰጣጣችንን ቀልጣፋ፣ ፈጣን፣ ግልፅ እና ተደራሽ ለማድረግ በሁሉም ክፍለ ከተሞች መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ስራ በ2018 በሁሉም ክፍለ ከተሞች ስራ ለማስጀመር አቅደን ለህዝቡ ቃል በገባነው መሰረት እነሆ የዛሬውን ጨምሮ 9 ማዕከላትን ወደ ስራ አስገብተናል። የአገልግሎት እንግልትን፣ እዚህም እዝያም ጉቦ የመጠየቅ ችግርን ለመቅርፍ፣ ተጠያቂነትን እና የህዝባችንን በክብር የመገልገል መብት ለማረጋገጥ፣ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜውንና ገንዘቡን ሳያባክን ያለውን ሃብት ለልማት እንዲያውለው ለማድረግ ያቀድነውን ግብ በማሳካት የጀመርነውን የብልፅግና ጉዞ አጠናክረን እንቀጥላለን ። የየካ ክፍለ ከተማ ባለ 7 ወለል ህንፃ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በፍጥነት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ የሰራችሁትን ሁሉ አመሰግናለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ውድድር አሸናፊ ሆነች በ19ኛው የኢትዮጵያ የግማሽ ማራቶን ውድድር በሴቶች የአዲስ አበባ ፖሊሷ መሰለች አለማየሁ አሸንፋለች። ዝማም ማራኪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለተኛ ወጥታለች። መነሻ እና መድረሻ
+3
ውድድር አሸናፊ ሆነች በ19ኛው የኢትዮጵያ የግማሽ ማራቶን ውድድር በሴቶች የአዲስ አበባ ፖሊሷ መሰለች አለማየሁ አሸንፋለች። ዝማም ማራኪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለተኛ ወጥታለች። መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ አድርጎ በተከናወነው ውድድር በወንዶች 455 እና በሴቶች 183 በድምሩ 638 አትሌቶች ተሳትፈውበታል፡፡

የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ሩጫ እየተካሄደ ነው 19ኛው የኢትዮጵያ የግማሽ ማራቶን ውድድር በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው ውድድሩ በወንዶች 455
+3
የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ሩጫ እየተካሄደ ነው 19ኛው የኢትዮጵያ የግማሽ ማራቶን ውድድር በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው ውድድሩ በወንዶች 455 እና በሴቶች 183 በድምሩ 638 አትሌቶች እየተሳተፉበት እንደሚገኝ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል። በዴንማርክ ኮፐንሀገን ለሚካሄደው የግማሽ ማራቶን ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች በውድድሩ እንደሚመረጡ ተገልጿል።

የቀድሞ የአርሰናል ተጫዋች ኢማኑኤል ኢቦዬን ጨምሮ የክለቡ ደጋፊዎች እና የAFTV ሚድያ በአዲስ አበባ ያደረጉት ጉብኝት በምስል!
+9
የቀድሞ የአርሰናል ተጫዋች ኢማኑኤል ኢቦዬን ጨምሮ የክለቡ ደጋፊዎች እና የAFTV ሚድያ በአዲስ አበባ ያደረጉት ጉብኝት በምስል!

አዲስ አበባ፥ የስፖርት ቱሪዝም ማዕከል! የአርሰናል ክለብ ደጋፊዎች እና የቀድሞው የክለቡ ተጫዋች አዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችና የተለያዩ ታሪካዊ መስህቦችን ጎበኙ። መንግስት የስፖ
+7
አዲስ አበባ፥ የስፖርት ቱሪዝም ማዕከል! የአርሰናል ክለብ ደጋፊዎች እና የቀድሞው የክለቡ ተጫዋች አዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችና የተለያዩ ታሪካዊ መስህቦችን ጎበኙ። መንግስት የስፖርት ቱሪዝም ለማሳደግ፣ የተለያዩ የስፖርት ማዕከላትን ከመገንባት ባሻገር፥ ሀገራዊ፣ ዓለማቀፉዊና አህጉራዊ ስፖርታዊ ፌስቲቫሎችን እንዲዘጋጁ በማድረግ ህብረተሰቡ እየተዝናና ጤናውን እንዲጠብቅ ምቹ ሁኔታን ተፈጥሯል። የቀድሞው የአርሰናል ተጫዋች ኢማኑኤል ኢቦዬን ጨምሮ የክለቡ ደጋፊዎች እና የAFTV ሚድያ በከተማችን የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችና የስፖርት ማዕከላትን በዛሬው ዕለት ጎብኝተዋል።

ምርጫውን ለማደናቀፍ የተደረገው ጥረት በሕዝብ እና በጸጥታ አካላት ቅንጅት ከሽፏል፡- የሰላም ሚኒስቴር በኢትዮጵያ የተካሄደውን ሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ ለማደናቀፍና የሕዝብን ሰላም ለማደፍረስ ጽንፈኛ ኃይሎችና የውጭ ጠላቶች የከፈቱት ሁለንተናዊ ጥቃት መክሸፉን የሰላም ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ በሰጠው መግለጫ ሀገራዊ ለውጡን የማይቀበሉ አካላት በመሬት ላይ የሽብር ጥቃቶችን ከመፈጸም ጀምሮ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የፕሮፓጋንዳና የሥነ-ልቦና ጦርነት ሲያካሂዱ ቆይተዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት ምርጫውን የህልውና እና የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማረጋገጫ አድርጎ በመውሰድ በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን የገለጸው ሚኒስቴሩ፤ በአንጻሩ የስልጣን ሽግግርን በድምጽ መስጫ ኮሮጆ ሳይሆን በኃይል ለመጠቅለል የሚሹ የውስጥ ቅጥረኞችና የኢትዮጵያን እድገት የማይፈልጉ የውጭ ኃይሎች ሂደቱን ለማስቆም ከምርጫው በፊት፣ ወቅትና በኋላ ከፍተኛ ሴራዎችን መሸረባቸውን ይፋ አድርጓል። አፍራሽ ኃይሎቹ የመንግሥትን ሕጋዊ ቅቡልነት ለማሳጣትና ኢትዮጵያን ወደ ሥርዓት አልበኝነት ለመክተት ሕዝቡ የምርጫ ካርድ እንዳይወስድ፣ በፖለቲካ ድጋፍ ሰልፎች ላይ እንዳይገኝ እና በምርጫው ቀን ድምጽ እንዳይሰጥ ቅስቀሳ ሲያደርጉ እንደነበር ተጠቅሷል። ሆኖም የኢትዮጵያ ህሕብ ለጥሪዎቻቸው እውቅና ባለመስጠትና የጽንፈኝነትን አጀንዳ ውድቅ በማድረግ፥ ከፍተኛ ቁጥር ባለው ተሳትፎ የምርጫ ካርድ በመውሰድ፣ በሰልፎች ላይ በነጻነት በመገኘትና በምርጫው ቀን በነቂስ ወጥቶ ድምጽ በመስጠት አፍራሽ ኃይሎቹን ማሸነፉን ሚኒስቴሩ ገልጿል። ይህ የዲሞክራሲ ስኬት ያለመስዋዕትነት እንዳልመጣ የጠቀሰው የሰላም ሚኒስቴር፤ የጸጥታ ተቋማት ባደረጉት ወቅቱን የጠበቀና የተቀናጀ አጸፋዊ እርምጃ የሽብር ዕቅዶቹ ሊከሽፉ መቻላቸውን አስታውቋል። ሆኖም የሕዝቡን አብሮነት ለመስበር የተሞከሩ የሽብር ጥቃቶች እንደነበሩ ጠቅሶ፤ ህዝቡ የከፈለው መስዋዕትነት ጽንፈኝነትን በመቃወም ሀገርን የሚያስቀጥል ሕጋዊ መንግስት ለመመስረት ያለውን ጽኑ ፍላጎት ያሳየበት መሆኑም ተመልክቷል። AMN

ከአክሞ ማዳን በፊት መከላከል ትኩረት ማድረግ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ አህጉራዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው በአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራን በተግባራዊ ፖሊሲዎች ለመደገፍ ያለመ አህጉራዊ ጉባኤ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰኔ 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) ያዘጋጀው ይህ ጉባኤ በአካዳሚክ ምርምሮች እና በፖሊሲ አፈጻጸሞች መካከል ያለውን ክፍተት መሙላትን ታሳቢ ያደረገ ነው። የአፍሪካ ልማትና የተግባራዊ መፍትሄዎች መድረክ (ADIF 2026) የሚል ስያሜ ያለው ጉባኤ “በአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳደግ የሚረዱ ምርጥ ተሞክሮዎችና የፈጠራ መፍትሔዎች” በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ ነው። ጉባኤው በአፍሪካ በፍጥነት እያደገ የሚገኘውን የወጣት ማኅበረሰብ፣ በዓመት ከ15 ሚሊዮን በላይ የሥራ ዕድል በመፍጠር አህጉራዊው ፍላጎትን ለመመለስ ከተያዘው ውጥን ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነው። ይህ አዲስ መድረክ ከተለመዱ አህጉራዊ ስብሰባዎች በተለየ፤ የፖሊሲ አፈጻጸምን በማፋጠን በዘርፉ ያለውን የፖሊሲ እና የአሰራር ሂደት ለማቀለጣፈ ያለመ መሆኑን ኢዜአ ከኢሲኤ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በዚህም መሠረት የኢኮኖሚክ ኮሚሽኑ በገንዘብ እጥረት ምክንያት መሬት ያልወረዱ ጥናታዊ ምርምሮችን ወደ ተግባር ለመለወጥ፣ በጥቂት አካባቢዎች ተሞክረው ስኬታማ የሆኑ አነስተኛ የሙከራ ፕሮጀክቶችን ለማስፋት እንዲሁም አህጉር በቀል ምርጥ ተሞክሮዎችን በአገራት አጠቃላይ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች ውስጥ በቀጥታ ለማካተት አቅዷል። አሠራሩ በልማት ላይ የሚፈሱ የአህጉሪቱ ኢንቨስትመንቶች አስተማማኝና ዘላቂ ውጤት እንዲያመጡ ለማድረግ ትልቅ እገዛ ይኖረዋል ተብሏል። የፎረሙን ውጤታማነትና ተጠያቂነት በተረጋገጠ መልኩ ለመከታተልም፣ ከጉባኤው በፊት፣ በጉባኤው ወቅትና ከጉባኤው በኋላ የሚተገበር የአሠራር ሥርዓት ተዘርግቷል። የመድረኩን ቀጣይነትና ትስስር አስተማማኝ ለማድረግ፣ የየዓመቱ መሪ ሀሳቦችን አንዱ ከሌላው ጋር በማስተሳሰር እና ተመጋጋቢ በማድረግ እንደሚዘጋጁ ኮሚሽኑ አስታውቋል። በቀጣይ የሚካሄዱት ፎረሞች፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና (AfCFTA) ትግበራን ከአህጉራዊ የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂዎች ጋር ማስተሳሰር ጨምሮ ሌሎች የልማት የትኩረት መስኮችን ታሳቢ በማድረግ እንደሚካሄድ መገለጹን ኢዜአ ዘግቧል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 5ኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ስብሰባ በዛሬው ዕለት አካሄደ። ለካቢኔው በዛሬው በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አስተላልፏል፡፡ በዚህ መሰረት፡- 1ኛ. የ
+9
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 5ኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ስብሰባ በዛሬው ዕለት አካሄደ። ለካቢኔው በዛሬው በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አስተላልፏል፡፡ በዚህ መሰረት፡- 1ኛ. የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ አስተዳደር ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ተፈፃሚ እንዲሆን አፅድቋል። 2ኛ. የመሬት ይዞታ ማስለቀቅና ካሳ ጉዳዮች ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ እንደገና ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ አፅድቋል። 3ኛ. በግል ዘርፍ ለህክምና ተቋማት ግንባታ እና ማስፉፍያ የሚውል መሬት ለማስተላለፍ የቀረበ የዉሳኔ ሀሳብ ላይ ተወያይቶ፣ ተፈፃሚ እንዲሆን አድፅድቋል።

ዛሬ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነ፣ የሕዝባችንን የጤና አገልግሎት በአዲስ ከፍታ ላይ የሚያስቀምጥ አዲስ የዲኤንኤ(DNA)፣ የፎሬንሲክና ስነምረዛ ምርመራ የልህቀት ማዕከል መርቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል። ሀገራችን ብዙ የውጭ ምንዛሪ የምታጣበት እና የምርመራ ውጤት ለማግኘት በጣም ረጅም ጊዜ ይፈጅ የነበረውን ችግር የሚያስቀር የDNA መረጃ ማከማቻና ማነጻጸሪያ ሲስተም (CODIS)፣ በወንጀል የተጠረጠሩ፣ ወላጅነትን ለማረጋገጥና ተመሳሳይ ምርመራዎችን በዘር መለያ (DNA Profiling) ለመለየት፣ የቤተሰብ ግንኙነትን እስከ ዘር ሀረግ መለየትና ማረጋገጥ እንዲሁም አጠራጣሪ ማንነትን ለማወቅ የሚያስችል የልህቀት ማዕከል ነው። ይህ ማዕከል የሀገሪቱን የፍትሕ ሥርዓት ምርመራን ውጤታማ በማድረግና በማዘመን፣ በሳይንሳዊ ማስረጃ ላይ የተመሰረተ የወንጀል ምርመራ ለማካሄድ፣ የመብት ጥያቄዎችን ለመመለስና ለሕዝብ ጤና ጥበቃ ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ብሔራዊ የልህቀት ማዕከል ነው። ሁሌም ቃልን በተግባር ፈፅመን በቁርጠኝነትና በተሻሻለ የስራ ባህል እየሰራን ባለፉት 5 ዓመታት ለጤናው ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት 4 ዓለም አቀፍ ደረጃ የሚመጥኑ ሆስፒታሎች በመገንባትና ነባሮቹንም ሆስፒታሎች በማደስና በማስፋፋት ሰፊ ስራዎችን ሰርተን አዘምነናቸዋል፡፡ በከተማ አስተዳደራችን በጤናው ዘርፍ የኢትዮጵያን የዕድገት ተምሳሌትነት እና የከፍተኛ ቴክኖሎጂ ምዕራፍ እያበሰርን ነው! ተጠናክሮም ይቀጥላል። ከዚሁ ጎን ለጎን የጤና ባለሙያዎቻችንን ትጋት፣ ብቃት እና እምነት ይበልጥ ለማሳደግ ልዩ ትኩረት እንሰጣለን። ከእቅድ ጀምሮ የልህቀት ማዕከሉ እውን እንዲሆን አስተዋጽኦ ያደረጋችሁትን በሙሉ በራሴ፣ በከተማ አስተዳደሩ እና በተጠቃሚዎች ስም ከልብ አመሰግናለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባን የአፍሪካ የከተሞች ልማት ተምሳሌት ያደረገው የ24/7 የመፈጸም አቅም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም "የዛሬ አምስት ዓመት አዲስ አበባ በአፍሪካ ውስጥ እጅግ ውብ ከሚባሉ ከተሞች አንዷ ትሆናለች" በማለት አቅጣጫ ያስቀመጡት ከተማዋ ስሟን የምትመጥን እንድትሆን በማሰብ ነው። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል ዛሬ በከተማዋ ተግባራዊ በሆኑት መዋቅራዊ እና ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች አማካኝነት በተጨባጭ እውን እየሆነ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ራዕይ ወደ መሬት አውርዶ በተግባር ለመተርጎም ደግሞ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያሳየው የአፈጻጸም ብቃት ሁነኛ ሚና ተጫውቷል። በከንቲባ አዳነች አቤቤ የሚመራው የከተማዋ አመራር ቁርጠኝነት የለውጡ ዋነኛ አንቀሳቃሽ ሞተር ሆኖ አዲስ አበባን እንደ ስሟ የፈካች አበባ አድርጓታል። አስተዳደሩ ያሰፈነው የ24/7 (ቀን ከሌሊት) የሥራ ባህል ቀደም ሲል ለዘመናት ስር ሰድዶ የነበረውን ዝግተኛ የመንግሥት ቢሮክራሲ በመስበር፣ ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ እና በከፍተኛ ጥራት የማጠናቀቅ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ከፍቷል። ይህ የሥራ ባህል ለውጥ ከተማዋን የማዘመን ተግባር ብቻ ሳይሆን፣ የከተማዋን ኢኮኖሚ ሌት ተቀን በማንቀሳቀስ ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል የፈጠረ የልማት ኃይል ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። የአመራሩ በቢሮ ከመቀመጥ ይልቅ በምሽት የሥራ እንቅስቃሴዎች ላይ በአካል በመገኘት እና በመከታተል፣ በበዓላት ቀናት ከኮሪደር ልማት ሠራተኞች ጋር ማዕድ በመጋራት፣ እንዲሁም ሠራተኛውን በቅርበት በማበረታታት መሪነትን በተግባር አሳይተዋል። ይህ ዓይነቱ ያልተቋረጠ የአመራር ክትትል እና አብሮነት የሥራ ባህልን በመቀየር ረገድ ትልቅ ሥነ-ልቦናዊ ለውጥ አምጥቷል። የአስተዳደሩ ትጋት ከተማዋ ላይ ያመጣቸው ተጨባጭ ለውጦች ያፈሩት ፍሬ ዛሬ በገሃድ ይታያል፤ በርካቶችንም ተጠቃሚ አድርገዋል። የከተማዋን ገጽታ ሙሉ ለሙሉ የቀየሩት ሰፋፊ የኮሪደር ልማቶች፣ ግዙፉ የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ የአዲስ አበባ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር፣ የወንዝ ዳር ልማቶች፣ ማራኪ የሆኑት የሕዝብ መዝናኛ ስፍራዎች እና ዘመናዊ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የአዲስ አበባን ትክክለኛ ውበት አጉልተው አውጥተውታል። አዲስ አበባን የኪነ ጥበብ እና ፍልስፍና ማዕከል ለማድረግም ዘመናዊ የሲኒማ ኮምፕሌክሶች እና አምፊ ቴአትሮች በስፋት ተሠርተው ለአገልግሎት በቅተዋል። አዲስ አበባ መጪውን ጊዜ ስታስብ ትላንቷንም ሳትረሳ ኢትዮጵያን ላገለገሉት ልጆቿ መታሰቢያ በማቆም ለቅርሶቿ ጥበቃ አድርጋለች። የወንዝ ዳር ልማት፣ ትላንት የበሽታ እና የወንጀል ምንጮች የነበሩ ወንዞችን በማደስ ለከተማዋ አዲስ አስትንፋስ ሰጥቷል። እነዚህ ተከታታይ ስኬቶች አዲስ አበባ ስሟን የሚመጥን ከተማ እንድትሆን ከማድረጋቸውም ባሻገር፣ የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫነቷን እና የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በሚመጥን መልኩ የዓለምን ቀልብ በከፍተኛ ሁኔታ እንድትስብ አድርጓታል። ዛሬ ላይ ቱሪስቶችም ሆኑ ዓለም አቀፍ ልዑካን በከተማዋ ንጽህና እና ፈጣን ዕድገት መገረማቸውን በተደጋጋሚ ከመግለጽ አልፈው በአካል መጥተው ለዓለም አረጋግጠዋል። መዲናችንን የጎበኙ ዓለም አቀፍ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችም ከተማዋ ከየትኛውም የዓለማችን ከተማ ጋር የምትወዳደር ውብ ከተማ እንደሆነች አረጋግጠዋል። ከዚህም በላይ የከተማ አስተዳደሩ የጀመረው የኮሪደር ልማት እና የመልሶ ማልማት ሥራ፣ ማንንም ወደ ኋላ የማይተው ሰው-ተኮር መርሕን የተከተለ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያስመዘገበው ይህ አስደናቂ የመፈጸም አቅም እና የልማት አርአያነት በዋና ከተማዋ ብቻ ተወስኖ አልቀረም። ከተማ አስተዳደሩ ይህን ተጨባጭ ለውጥ ወደ ክልል ከተሞችም በተሳካ ሁኔታ እንዲሰርጽ አድርጓል። ባለሙያዎችን በመመደብ እና የቴክኒክ ድጋፎችን በማቅረብ ታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ የጀመረችውን የኮሪደር ልማት በፍጥነት እና በጥራት እንድታከናውን ትልቅ አሻራውን አሳርፏል። በተመሳሳይ መልኩ የሐይቆች ከተማ የሆነችውን ቢሾፍቱ ከተማን የኮሪደር ልማት እና የቱሪስት መዳረሻነት ለማጠናከር የተደረጉት የልምድ ልውውጦች፣ የአመራሩን አጋርነት እና ሀገራዊ ቁርጠኝነት በተግባር ያሳዩ ናቸው። በአዲስ አበባ የታየው ይህ አስደናቂ ለውጥ በምኞት የመጣ ሳይሆን፣ በጠንካራ መዋቅራዊ ዕቅድ፣ ቀን ከሌሊት በሚተጋ ቁርጠኛ አመራር፣ በተለወጠ የሥራ ባህል እና ከሕዝብ ጋር በተመሠረተ ጠንካራ ትሥሥር የመጣ ውጤት ነው። ይህ ስኬት "የጀመርነውን እናጠናቅቃለን" የሚለውን የይቻላል መንፈስ በዜጎች ልቦና ውስጥ ያሰረጸ እና መላው ኢትዮጵያውያን በመዲናቸው እንዲኮሩ ያደረገ ብሩህ ተስፋ ነው። አዲስ አበባ ዛሬ በአፍሪካ እጅግ ተወዳዳሪ፣ ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ለሌሎች ከተሞች ታላቅ የልማት ትምህርት ቤት ሆና በኩራት ቆማለች። EBC

የልማት ስራዎች የአንድ ወቅት ብቻ አይደሉም፥ ዘመን ተሻጋሪ እንጂ! በተለያዩ የልማት ስራዎች ፈር ቀዳጅ የሆነችው አዲስ አበባ፣ ከ7ኛው ሀገራዊ መርጫ ማግስት በተለያዩ የልማት ስራዎች መገለጥዋን ቀጥላለች፡፡ የልማት ስራዎች የአንድ ወቅት ብቻ አለመሆናቸውን የተረዳው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ከዚህ ቀደም በእንግልት እና በኃላ ቀር አሰራር ህዝብ ሲማረርባቸው የነበሩ የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ይስተዋል የነበረውን ችግር በማስቀረት፣ በአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ቀልጣፋና የተቀናጀ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ዘመናዊ ተቋማት እየተገነቡ ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል። ከዚህም የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ዘንድ ለዓመታት የቆየውን የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ታላቅ ስራ ሲሆን፤ በተለይም በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተደራሽ መሆኑ ነዋሪዎች ከተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚያገኟቸውን አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በተቀናጅና በተናበበ እንዲሁም በሰለጠነ የሰው ኃይል እንዲያገኙ አድርጓል። ቀደም ሲል ቀናትና ሳምንታት ይወስዱ የነበሩ ጉዳዮች፥ ዛሬ በመሶብ የአንድ ማዕከል በደቂቃዎች ውስጥ እልባት ማግኘት ችለዋል፡፡ ከሁሉም በላይ አገልግሎቱ ወደ ነዋሪዎች መቅረቡ ነዋሪዎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ባሉበት ቦታ በተንቀሳቃሽ መሶብ አገልግሎት እንዲያገኙ ተደርጓል። እነዚህ ማዕከላት በውስጣቸው ከንግድ ፈቃድ ምዝገባ ጀምሮ እስከ መታወቂያና የውልና ማስረጃ አገልግሎቶች ድረስ እጅግ በርካታ ፋይዳ ያላቸውን ዘርፎች አካትተዋል። በተለይም ለአገልግሎት ፈላጊዎች ምቹ የሆኑ የጥበቃ ስፍራዎች፣ ዲጂታል የሰልፍ መቆጣጠሪያዎች፣ የህፃና ማቆያና ለአካል ጉዳተኞች ምቹ የሆኑ መሰረት ልማቶችን በመያዛቸው ተገልጋዩ የጊዜ ብክነት እና እንግልት እንዳይገጥመው ታድገዋል፡፡ በአዲስ አበባ የተጀመረውና በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተግባራዊ የሆነው የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቁጥሩን ወደ ስምንት ከፍ በማድረግ እንዲሁም በተንቀሳቃሽ አውቶብስ አገልግሎቱን በማስፉት ነዋሪው እፎይታን እንዲያገኘ ማድረግ ተቸሏል። የልማት ስራዎች የአንድ ወቅት ብቻ አይደሉም፥ ዘመን ተሻጋሪ እንጂ፥ ይቀጥላል!