Addis Ababa Design And Construction Works Bureau
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Addis Ababa Design And Construction Works Bureau 的分析概览
频道 Addis Ababa Design And Construction Works Bureau (@addiscitycon) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 21 221 名订阅者,在 政治 类别中位列第 2 731,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 608 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 21 221 名订阅者。
根据 27 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 111,过去 24 小时变化为 12,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 14.95%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.78% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 173 次浏览,首日通常累积 1 864 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 14。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Government Organization”
凭借高频更新(最新数据采集于 28 八月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 政治 类别中的关键影响点。
21 221
订阅者
+1224 小时
+307 天
+11130 天
帖子存档
+9
"ዓድዋ ናይት ፋይት" በአዲስ አበባ ሰማይ ስር የተጻፈ አዲስ የስፖርት ታሪክ!
በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዝየም የተደረገው ታላቁ "ዓድዋ ናይት ፋይት" (Adwa Night Fight) የሚክስድ ማርሻል አርት (MMA) ውድድር በታላቅ ስኬት፣ በደመቀ ድባብ እና በሰላም ተጠናቋል!
ይህ ታሪካዊ ምሽት የከተማችንን ሁለገብ አቅም፣ የስፖርታዊ ውድድሮች አዲስ እይታን፣ እንዲሁም መዲናችን አዲስ አበባ አለም አቀፍ ደረጃ ያላቸውን ታላላቅ የስፖርት ዝግጅቶች የማስተናገድ ብቃቷ በከፍተኛ ደረጃ ማደጉን ዳግም ያረጋገጠበት ነበር። ዋና ዋና የስኬት ኩነቶች፦
1. ስማርት እና ዘመናዊ አዲስ አበባ :-የኢትዮጵያዊነት እና የፅናት ምልክት በሆነው በዓድዋ ድል መታሰቢያ የተካሄደው ይህ ውድድር፤ የከተማችንን ዘመናዊነት (Smart City) እና ለትላልቅ አለም አቀፍ ኹነቶች ያላትን ዝግጁነት በግልጽ እና በተግባር አሳይቷል።
2. የተወዳዳሪዎች ድንቅ ብቃት:-ተወዳዳሪዎቻችን ያሳዩት ከፍተኛ የቴክኒክ፣ የፅናት እና የስፖርታዊ ጨዋነት ብቃት የምሽቱን ሳቢነት እና አዛኝነቱን በእጅጉ ጨምሮታል።
3. የስፖርቱ አዲስ ምዕራፍ:- እንደ Mixed Martial Arts (MMA) ያሉ አሳታፊ የስፖርት አይነቶች በሀገራችን እያደጉ መምጣታቸውን እና የወጣቶቻችንን ፍላጎት መሰረት ያደረጉ አዳዲስ አሰራሮች እየተተገበሩ መሆናቸውን ማሳያ ነው።
4. የህዝቡ ደማቅ አቀባበል፦ የስፖርት አፍቃሪው ህዝባችን ያሳየው ደማቅ ድጋፍ እና ፍቅር ውድድሩ ልዩ ቀለም እንዲላበስ አድርጎታል።
ይህ ታላቅ ዝግጅት በስኬት እና በሰላም እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ ተወዳዳሪዎች፣ አዘጋጆች፣ የስፖርት አፍቃሪዎች እና ለከተማችን ነዋሪዎች በሙሉ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
አዲስ አበባ፣ የአለም አቀፍ ስፖርታዊ ኹነቶች እና የታላላቅ ህልሞች መድረክ!
+9
በአዲስ አበባ የተገነቡት ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች የተገልጋዩን እንግልት የሚቀንሱ ናቸው - ኢ/ር አያልነሽ ሃ/ማርያም
በአዲስ አበባ የተገነቡት ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች የተገልጋዩን እንግልት የሚቀንሱ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ የዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ቢሮ ኃላፊ ኢ/ር አያልነሽ ሃ/ማርያም ገለጹ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ የትራንስፖርት ሥርዓትን ወደ ተቀናጀና ዘመናዊ አሠራር የሚያሸጋግሩ መሠረተ ልማቶችን የማስፋፋት ሥራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል።
ኢንጂነር አያልነሽ ሃብተ ማርያም እንደገለጹት፤ አዲስ ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉት የተሽከርካሪ ማቆሚያ እና ተርሚናሎች የህብረተሰቡን እንግልት በከፍተኛ ሁኔታ የሚቀንሱ ናቸው።
እያንዳንዳቸው በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደራጁ፣ ሙሉ በሙሉ ደህንነታቸው የተጠበቀ እና ለተገልጋዩ ህብረተሰብ ልዩ ምቾትን የሚያጎናጽፉ ናቸውም ብለዋል፡፡
እነኚሁ ፕሮጀክቶችም በውስጣቸው የታክሲ እና አውቶብስ ተርሚናሎች፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቻርጀሮች እንዲሁም የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎችን እንዳካተቱ የጠቀሱ ሲሆን በተጨማሪም የንግድ ሱቆች፣ ካፊቴሪያ እና ሬስቶራንቶች፣ የልጆች መጫወቻ እና ማረፊያ ስፍራዎች እንዲሁም ምቹ የተሳፋሪ መጠበቂያ ስፍራዎች እንደተሟሉላቸው ጠቁመዋል።
እንደ ኃላፊዋ ገለፃ ተርሚናሎቹ አሳንሰሮችን እና ንጹህ መጸዳጃ ቤቶችን እንዲሁም የደህንነት እና አደጋ ቅድመ መከላከያ ስርዓቶችም የተሟሉላቸው ናቸው፡፡
ኃላፊዋ አያይዘውም ፕሮጀክቶቹ በሙሉ አቅማቸው ወደ አገልግሎት ሲገቡ በከተማዋ ጤናማ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የተሽከርካሪ ፍሰት እና የእግረኛ እንቅስቃሴ እንዲኖር ከማስቻላቸውም ባሻገር ለከተማዋ የ«ስማርት ሲቲ» ውጥን እውን መሆን ጉልህ ሚና ይጫወታሉ ብለዋል።
ዘመናዊዎቹ የቦሌ ፣ የጎተራ ፣ የየካ እና የቀበና ተሽከርካሪ ማቆሚያ ፣ተርሚናል እና ፕላዛዎች ግንባታቸው በጥራት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል።
የዘመነ መሰረተ ልማት፤ የዘመነ አገልግሎት ለዘመናዊ ከተማ!
ዛሬ በከተማችን አራት ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች፣ ተርሚናሎችና ገበያ ማዕከላት (በጎተራ፥ ቦሌ፣ የካ እና ቀበና) መርቀን አገልግሎት አስጀምረናል።
እነዚህ መሰረተ ልማቶች የትራፊክ መጨናነቅን የሚያቃልሉ፣ የትራንስፖርት ሥርዓትን የሚያሻሽሉ፣ ህዝባችንን ከዝናብና ፀሐይ እንግልት የሚከላከሉ፣ በርካታ የስራ እድሎችን የሚፈጥሩ ምቹ ፣ ንፁህ እና የሰውን ክብር የሚመጥኑ የዘመነ አገልግሎት የሚሰጡ ናቸው።
መሰረተ ልማቶቹ በአንድ ጊዜ በርካታ ተሽከርካሪዎችን የማስተናገድ ዓቅም ያላቸው ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች፣ የታክሲ እና የአውቶቡስ ተርሚናሎች፣ የአየር ብክለትን የሚከላከሉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቻርጅ ማድረጊያዎች፣ ሰፊ የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች፣ የንግድ ሱቆች፣ ካፍቴሪያና ሬስቶራንቶች፣ የልጆች መጫወቻና ማረፊያ ስፍራዎች፣ ምቹ የተሳፋሪ መጠበቂያ ስፍራዎች፣ የአስተዳደር እና የትኬት መቁረጫ ቴክኖሎጂዎች፣ አሳንሰሮች እና ንፁህ መፀዳጃ ቤቶች እንዲሁም የደህንነትና የአደጋ ቅድመ መከላከል ሥርዓቶች የተሟሉላቸው የኢኮኖሚና የማህበራዊ አገልግሎትን ለማሳለጥ ትልቅ አስተዋጽዖ የሚያበረክቱ ናቸው።
ከለውጡ በፊት 3 ሺህ ብቻ የነበረውን የአንድ ጊዜ የተሽከርካሪ ማቆሚያ አቅም እና ምንም ያልነበረንን ተርሚናል በአሁኑ ጊዜ በጥራትና በፍጥነት የተገነቡ፣ ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎችን እና ተርሚናሎችን ከ170 ሺህ በላይ ማድረስ ችለናል ።
ለከተማችን ነዋሪዎች ተጠቃሚነት በተጨባጭ ቃላችንን በተግባር ስራዎችን እየፈጸምን በቅንነትና በታማኝነት እየሰራን እንገኛለን። አዲስ አበባ ከዚህ በላይ ይገባታል ቀጣይም ከሰራነው በላይ እንተጋለን!
የዛሬዎቹ ፕሮጀክቶች እውን እንዲሆኑ ለተጋችሁ፣ ላስተባበራችሁ የዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች፣ የትራንስፖርት ቢሮ አመራሮች፣ ኮንትራክተሮች፣ አማካሪዎች በዚህ ስራ የተሳተፋችሁትን ሁሉ ከልብ አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የዘመነ መሰረተ ልማት፤ የዘመነ አገልግሎት ለዘመናዊ ከተማ!
ዛሬ በከተማችን አራት ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች፣ ተርሚናሎችና ገበያ ማዕከላት (በጎተራ፥ ቦሌ፣ የካ እና ቀበና) መርቀን አገልግሎት አስጀምረናል።
እነዚህ መሰረተ ልማቶች የትራፊክ መጨናነቅን የሚያቃልሉ፣ የትራንስፖርት ሥርዓትን የሚያሻሽሉ፣ ህዝባችንን ከዝናብና ፀሐይ እንግልት የሚከላከሉ፣ በርካታ የስራ እድሎችን የሚፈጥሩ ምቹ ፣ ንፁህ እና የሰውን ክብር የሚመጥኑ የዘመነ አገልግሎት የሚሰጡ ናቸው።
መሰረተ ልማቶቹ በአንድ ጊዜ በርካታ ተሽከርካሪዎችን የማስተናገድ ዓቅም ያላቸው ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች፣ የታክሲ እና የአውቶቡስ ተርሚናሎች፣ የአየር ብክለትን የሚከላከሉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቻርጅ ማድረጊያዎች፣ ሰፊ የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች፣ የንግድ ሱቆች፣ ካፍቴሪያና ሬስቶራንቶች፣ የልጆች መጫወቻና ማረፊያ ስፍራዎች፣ ምቹ የተሳፋሪ መጠበቂያ ስፍራዎች፣ የአስተዳደር እና የትኬት መቁረጫ ቴክኖሎጂዎች፣ አሳንሰሮች እና ንፁህ መፀዳጃ ቤቶች እንዲሁም የደህንነትና የአደጋ ቅድመ መከላከል ሥርዓቶች የተሟሉላቸው የኢኮኖሚና የማህበራዊ አገልግሎትን ለማሳለጥ ትልቅ አስተዋጽዖ የሚያበረክቱ ናቸው።
ከለውጡ በፊት 3 ሺህ ብቻ የነበረውን የአንድ ጊዜ የተሽከርካሪ ማቆሚያ አቅም እና ምንም ያልነበረንን ተርሚናል በአሁኑ ጊዜ በጥራትና በፍጥነት የተገነቡ፣ ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎችን እና ተርሚናሎችን ከ170 ሺህ በላይ ማድረስ ችለናል ።
ለከተማችን ነዋሪዎች ተጠቃሚነት በተጨባጭ ቃላችንን በተግባር ስራዎችን እየፈጸምን በቅንነትና በታማኝነት እየሰራን እንገኛለን። አዲስ አበባ ከዚህ በላይ ይገባታል ቀጣይም ከሰራነው በላይ እንተጋለን!
የዛሬዎቹ ፕሮጀክቶች እውን እንዲሆኑ ለተጋችሁ፣ ላስተባበራችሁ የዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች፣ የትራንስፖርት ቢሮ አመራሮች፣ ኮንትራክተሮች፣ አማካሪዎች በዚህ ስራ የተሳተፋችሁትን ሁሉ ከልብ አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ዛሬ የልጆች ኢንቨስትመንት ፈንድ ፋውንዴሽን (CIFF) መስራች እና የቦርድ ሃላፊ ክቡር ክሪስ ሆን እና ቡድናቸውን ለነገዋ የሴቶች የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከልን አስጎብኝተናል።
ለነገዋ ጅማሮው በተለያዩ ማህበራዊ ችግር ውስጥ ያሉ ሴቶች እህቶቻችን ተስፋና እድላቸው እዲለመልም፣ ክብራቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ የተሻለ ሕይወት እንዲመሩ ከልብ በመነጨ ስሜት የተፀነሰ፣ ተፀንሶም ወደ ተግባር የተቀየረ ትልቅ ራዕይን የሰነቀ ስራ ነው።
የእነዚህ እህቶቻችንን ህይወት ለመቀየር፣ ለነገዋ የሴቶች የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል በ2016 ዓ.ም ጀምረነው በ5 ዙር በተለያዩ የሙያ ዘርፎች 3,259 ሰልጣኞችን በክህሎት እና በስብዕና ግንባታ አሰልጥነን ወደ ስራ አሰማርተናል።
ዛሬ ሁሉም ተመራቂዎች ክብር ያለው ኑሮ፣ ብሩህ ተስፋን ሰንቀው አዲስ ህይወት መኖር ጀምረዋል።
“ከምንሰራቸው ስራዎች ሁሉ ትልቁ ስራ በሰው ላይ የምንሰራው፣ በተለይም በሴቶች ላይ የምንሰራው ነው” የሚለውን የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ መልዕክት የስራችን ማዕከል አድርገን እየፈፀምን እንገኛለን።
በከተማችን ላይ ከሚታየው ለውጥ ሁሉ የሚልቀው በለነገዋ ሴቶች ላይ እያየን ያለው ለውጥ ነው።
ለ”ለነገዋ የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል” የሰነቅነው ራዕይ፣ በዓመት እስከ 10 ሺህ ሴቶችን የሚያበቃ፣ እንዲሁም አካታች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ልምድ የሚቀሰምበት የልህቀት ማዕከል እንዲሆን ማስቻል ነው ።
ይህ ራዕይ በተሟላ ሁኔታ እንዲተገበር ሊደግፋን የመጡት የልጆች ኢንቨስትመንት ፈንድ ፋውንዴሽን (CIFF) መስራች ክቡር ክሪስን በለነገዋ የሴቶች የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል የምንሰራቸው ሰው ተኮር ስራዎች አስጎብኝተን በቀጣይም በጋራ በምንሰራቸው ስራዎች ዙሪያ ተወያይተናል።
ለራዕያችን ግብ ስኬት ሌት ተቀን ተግተን እንሰራለን ፤ ፈጣሪም ይረዳናል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+1
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ፤ እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
በዓሉን ስናከብር እንደከዚህ ቀደሙ የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት፤ ለሌላቸው በማካፈል፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የታመሙትን በመጠየቅ እንዲሆን እመኛለሁ።
በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ - ኢድ ሙባረክ!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ
የነቢዩ መሐመድ ታሪክ ትውልድን ለበጎ ከሚቀርጹ ታሪኮች መካከል አንዱ ነው፡፡ የተጠሩበትን ዓላማ ማክበር፤ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ መክፈል፤ የተጠሩበትን ለሌሎች ማካፈል፤ የተጠሩበትን አክብሮ መኖር - እነዚህ ሁሉ ሺ መጻሕፍት የሚወጧቸው ትምህርቶች ናቸው፡፡
ነቢዩ የተጠሩበትን ዓላማ በሚገባ ስለተገነዘቡ አክብረው ኖረዋል፡፡ የተጠሩት ለተራና ርካሽ ነገር እንዳልሆነ ተገንዝበዋል፡፡ የተጠሩት ትውልድን ለመቅረጽና ታሪክን ለመቀየር መሆኑን አምነዋል፡፡ ያንንም በቃላቸው፣ በሥራቸውና በኑሯቸው አክብረውት ነኖረዋል፡፡ ለታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ተጠርተናል ብለን የምናምን ከሆነ ይህ የነቢዩ ሕይወት ታላቅ ትምህርት ይሆነናል፡፡ የተጠራንበትን ዓላማ በንግግራችን፣ በሥራችንና በሕይወታችን እንግለጠው፡፡
ነቢዩ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ ከፍለዋል፡፡ ከቦታቸው ተሰደዋል፤ ምግብና መጠለያ ተነፍገዋል፤ ከቤተሰቦቻቸው ተለይተዋል፡፡ ለሞት በሚያበቁ ፈተናዎች ውስጥ አልፈዋል፡፡ ጦርነት ተከፍቶባቸዋል፡፡ ነገር ግን ሁሉንም በአላህ ኃይል አሸንፈዋል፡፡ ክብር ያለ መከራ አይገኝምና፡፡ እውነተኛ ሰው ለዓላማው እንደ ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ)ዋጋ ይከፍላል፡፡ ዓላማው የሚያስገኘውን ክብርና ጥቅም ብቻ ሳይሆን ዓላማው የሚያስከፍለውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ይሆናል፡፡
ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) ከአላህ የደረሳቸውን መልእክት ለራሳቸው ብቻ አላስቀሩም፡፡ የተጠሩበትን ለሌሎች ለማካፈል ተግተዋል፡፡ መጀመሪያ በጣት ለሚቆጠሩ ሰዎች፣ በኋላም ለቅርብ ሱሐባዎች፣ በመጨረሻም ለዓለም መልእክቱን አዳርሰዋል ፡፡ እሳቸው የዘሩት ዘር እያፈራና እየጎመራ ተጉዟል፡፡ ዓላማችንን እኛ ማወቃችንና ማመናችን ብቻ ጥቅም የለውም፡፡ ሌሎች እንዲያውቁና እንዲያምኑ ልክ እንደነቢዩ ተገትተን መድከም አለብን፡፡
የነቢዩን መውሊድ ስናከብር ከሕይወታቸው እየተማርን፤ የተማርነውንም ለሀገረ መንግሥት ግንባታችን እየተጠቀምን እንዲሆን አደራ እላለሁ፡፡
በድጋሚ መልካም የመውሊድ በዓል ይሁንልን።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
+9
ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች ተጠቃሚነት የሰራነዉ ልማት በተጨባጭ አዳዲስ የአኗኗር ባህል እየገነባ ማህበራዊ መስተጋብሩን ይበልጥ እያጠናከረ ነዉ።
በዉቧ ካዛንችስ የገንባነዉ ስፖርት ፓርክ ለከተማችን ነዋሪዎች የጤንነት መጠበቂያ ፣ የአካልና አእምሮ ማጐልበቻ ፣ የህፃናት መቦረቂያ፣ የብሄራዊ ጀግኖች አትሌቶቻችን ዉለታ መታሰቢያ አከታች ልማት በመሆኑ ለሁሉም ማህበረሰብ ክፍሎች አገልግሎት እየሰጠ ነው።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
Misoomni nuti fayyadamummaa jiraattota Finfinneetiif hojjanne qabatamaan aadaa jireenyaa haaraa ijaaraa hariiroo hawaasummaa caalmaatti cimsaa jira.
Paarkiin Ispoortii Kaazaanchiis miidhagduutti ijaarrre jiraattota magaalaa keenyaaf eegumsa fayyaa, gabbisa qaamaa fi sammuu, bohaartii daa'immanii fi oolmaa yaadannoo gootota atileetota keenya biyyaalessaa misooma of keessa qabu ta'uu isaatiin kutaa hawaasaa hundumaaf tajaajila kennaa jira.
Waaqni Itoophiyaa fi uummata ishee haa eebbisu!
+9
ዛሬ የኒው ሊፍ ሜዲካል ኮምፕሌክስን መርቀን ሥራ አስጀምረናል።
እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!
ከተማችን አዲስ አበባ የጤና ቱሪዝም ማዕከል እናደርጋታለን ስንል በመንግስት ብቻ የምናሳካው ሳይሆን በግሉ ዘርፍ የሚገነቡትንም ታሳቢ በማድረግ ስለሆነ፣ ዛሬ ያስመረቅነው የኒው ሊፍ ሜዲካል ሆስፒታልም የዚህ አንዱ ማሳያ ነው ።
ኒው ሊፍ ሜዲካል ኮምፕሌክስ በሃገራችን ከላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቀጥሎ ሁለተኛው PET-CT SCAN CAT LAB እና ሌሎች ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂዎች የተሟሉለት ትልቅ የጤና ማዕከል ነው። በጤናው ዘርፍ የምናደርገው ኢንቨስትመንት ክፍያው ከሁሉ የላቀ ስለሆነ እንደዚህ አይነት በጤናው ዘርፍ ለሚሰሩ የጤና ተቋማት እና ሆስፒታሎች ድጋፋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን።
የኒው ሊፍ ሜዲካል ኮምፕሌክስ መስራችና ስራአስኪያጅ ዶ/ር ኢማን አብዱልራህማን እና ባለቤታቸው አቡበከር መሃመድ ሳላህን በራሴና በከተማው አስተዳደር ስም በጣም እናመሰግናለን።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ለረዳን ፈጣሪ አምላክ ታላቅ ክብርና ምስጋና ይሁንለት!
አዲስ ታሪክ፣ አዲስ ምእራፍ፣ በአዲስ የመከባበር፣ የመመካከርና የመደማመጥ የመግባባት ታሪክ የተደረገ ሽግግር!!
"ከአሸናፊ-ተሸናፊ” ትርክት በመላቀቅ፣ በሀሳብ ልዕልና ወደ በጋራ የማሸነፍ፣ ለጋራ ተጠቃሚነት ሲባል የጋራ መፍትሄ ለማምጣት በጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብሎ ወደ መግባባት የተሸጋገርንበት ታላቅ የታሪክ እጥፋት ነው፡፡ በዚህ የምክክር ሂደት የተለየ አሸናፊና ተሸናፊ ፈጽሞ አልተፈጠረም፤ ይልቁንም ኢትዮጵያ አሸንፋለች!
እንዲመከሩባቸው ከቀረቡት 400 ከሚጠጉ አበይት ጉዳዮች (ምክረ ሀሳቦች) ኢትዮጵያውያን ተደማምጠውና አንዱ የሌላውን ህመም ተረድተው ወደ አንድ በመሰብሰብ በ99 % ላይ ሙሉ ሙሉ ስምምነት ላይ መድረስ ተችሏል። አንድ አይነት ድምዳሜ ላይ ባልተደረሰባቸው በአራት 4 (1%) ጉዳዮች ላይ ብቻ በአማራጭ መፍትሄዎች እንዲታለፉ በሙሉ መግባባት ላይ ተደርሷል። ይህም ሂደቱን እስካሁን በዓለም ላይ ከሰማናቸው የምክክር ሂደቶች እጅጉን በምሳሌነት የሚጠቀስና አስደናቂ አድርጎታል።
ያለፉት ትውልዶች በጽኑ ተመኝተውት ያላዩትን ይህንን የሰለጠነ አብሮነት የሰፈነበት ታሪካዊ የምክክር መድረክ በዓይናችን እንድናይ ስለፈቀደልን ቸሩ አምላካችንን ከልብ እናመሰግናለን። የእኛም ትውልድ ይህን ስላሳካን በእውነትም እጅግ የታደልን ትውልዶች ነን።
ለዚህ ሀገራዊ ድል መሳካት ከየአካባቢው የመጡ ውድ ኢትዮጵያውያን ያሳዩት አስደናቂ በሳልነት እና ጥልቅ አስተዋይነት እጅግ የሚመሰገን ነው።
ሀገር የምትገነባውና ኢትዮጵያ የምትጸናው በትክክልም በዚህ የሰለጠነ መንገድ ነው! በመተሳሰብ፣ በአብሮነት፣ አንዱ የሌላውን ሀሳብ ለማዳመጥና ለመቀበል ፈቃደኛ በመሆን፣ እንዲሁም በመከባበር የምንገነባት ኢትዮጵያ የሁላችንም ኩራት ናት። ይህ አስደናቂ የመደማመጥ አዲስ ባህል እና የጋራ ታሪካችን በመሆኑ ላሳኩት ሁሉ ክብር ይገባቸዋል።
በርግጥ ዛሬ ተመካክረን በእነዚህ ጉዳዮች ተግባብተናል ማለት ነገ ምንም አይነት ልዩነቶች አያጋጥሙንም ማለት አይደለም። ነገር ግን ልዩነትን በመመካከርና በሰለጠነ መንገድ መፍታት ተጀምሯል፤ በሩም ተከፍቷል፤ ከእንግዲህ ወደ ኋላ አንመለስም። ከእንግዲህ ልጆቻችን ልዩነቶቻቸውን በጠመንጃ ለመፍታት በመሞከር እና እርስ በእርስ በመገዳደል አይቀጥሉም። ይህ የጦርነት እዳ ወደ እነሱ እንደማይተላለፍ እምነት አለን።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+2
"ሰላም እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ ማንኛውንም ዋጋ ልንከፍልለት ይገባል"፦ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ
የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት እና በአፍሪካ ኅብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ በኢትዮጵያ የተካሄደው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ታላቅ ስኬት መሆኑን በመግለጽ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
የኢትዮጵያ አጠቃላይ ልማት፣ የዜጎችን ደኅንነት እና ደስታ ለማረጋገጥ ሰላም፣ ፀጥታ እና መረጋጋት ማስፈን ወሳኝ ነው ብለዋል። "ሰላም እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ ማንኛውንም ዋጋ ልንከፍልለት ይገባል" ያሉት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ፣ ሀገራዊ ምክክሩም የዚሁ ጥረት አካል መሆኑን ተናግረዋል።
የኮሚሽኑ የዝግጅት ምዕራፍ አራት ዓመታት መውሰዱ እና 4000 የሚጠጉ ሰዎች መሳተፋቸው የሒደቱን አሳታፊነት እና ትልቅነት እንደሚያሳይ ጠቁመዋል።
የምክክሩ መፍትሔ ሐሳቦች ብሔራዊ አንድነትን፣ ትሥሥርን እና ልማትን ለማሳካት በጥንቃቄ እና በቅንነት ሊተገበሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የአፍሪካ ኅብረት በአፍሪካ ቀንድ እና በመላው ኢትዮጵያ ሰላም ለማምጣት በሙሉ ልብ ኃላፊነት ወስዶ እየሠራ መሆኑን እና ዘወትር ከኢትዮጵያውያን ጎን እንደሚቆምም አረጋግጠዋል።
የጋራ ደኅንነትን፣ መረጋጋትን እና ብልጽግናን ማሳደግ የሁሉም ኃላፊነት መሆኑን የጠቀሱት ኦባሳንጆ፣ ግጭቶችን እና አድልዎዎችን ማስወገድ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።
የተጠናቀቀው ሀገራዊ ምክክር ለመልካም አስተዳደር ጠንካራ መሠረት እንደሚጥል ያላቸውን እምነት ገልጸው፣ "እኛ ከእናንተ ጋር ነን፣ ከጎናችሁ እንቆማለን" ብለዋል።
+2
"የሀገር ብርታት ጥበብ ብልሃቱ ምክክር ነው"፦ ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ
ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ መዝጊያ ሥነ ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር፣ የኢትዮጵያን አሸናፊነት የሚያረጋግጡ እና አንድነትን የሚያጸኑ የጋራ መሻቶች መገለጻቸውን ገልጸዋል።
ምክክሩ ለትውልድ የሚበጅ ጠንካራ ሐሳብ የተንሸራሸረበት ልዩ ቀን መሆኑን በማንሣት፣ ምክክር የሀገር ብርታት እንዲሁም የጥበብ እና ብልሃት መሠረት መሆኑን አስገንዝበዋል።
ፕሬዚዳንቱ በመልእክታቸው 130 ሚሊዮን ሕዝብን በመወከል ለ46 ቀናት በቆየው ውይይት ላይ የተሳተፉትን ተመካካሪዎች በልዩ ሁኔታ አመስግነዋል።
ተሳታፊዎቹ የአካባቢያቸውን መልካም ተሞክሮ በማምጣት ለኢትዮጵያ በሚበጅ መልኩ ማቅረባቸውን አድንቀው፣ ይኸው የሰላም ውይይት እንዲሳካ ላስቻሉ የመከላከያ ሠራዊት እና መላው የጸጥታ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በተጨማሪም ብሔራዊ ጥቅምን ያማከለ ምቹ የመወያያ መድረክ ላዘጋጁት የምክክር ኮሚሽኑ አባላት እና የዛሬ ሳንሆን የነገው ትውልድ ተስፋ እንድንሆን ላስቻሉ የመንግሥት ኃላፊዎች ከፍ ያለ ዕውቅና ሰጥተዋል።
ፕሬዚዳንት ታየ ምክክር የነባር ባሕላችን አካል ቢሆንም ለፖለቲካ እና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ለማዋል ከዚህ ቀደም ተሞክሮ እንደማያውቅ አስታውሰዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደዚህ ዓይነት የምክክር መድረክ እንዲዘጋጅ በቁርጠኝነት ኃላፊነታቸውን በመወጣታቸው ሊመሰገኑ እንደሚገባም ተናግረዋል።
ውይይቱ ኢትዮጵያን አሸናፊ ለማድረግ የተወጠነ መሆኑን የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፣ ጉባኤው የሁላችንንም ኢትዮጵያ የሚያጸና እና ለመጻኢው ዕጣ ፈንታ ብሩህ ተስፋ የፈነጠቀ መሆኑን አስረግጠዋል።
