uz
Feedback
Hawassa University

Hawassa University

Kanalga Telegram’da o‘tish

One of the top ranking first generation Universities in Ethiopia.

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Hawassa University analitikasi

Hawassa University (@hucommunicationsoffice) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 35 904 obunachidan iborat bo'lib, TaĘźlim toifasida 5 180-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 963-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 35 904 obunachiga ega bo‘ldi.

29 Avgust, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 1 109 ga, so‘nggi 24 soatda esa 41 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 17.85% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 9.53% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 6 401 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 3 419 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 0 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“One of the top ranking first generation Universities in Ethiopia.”

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 30 Avgust, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Taʼlim toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

35 904
Obunachilar
+4124 soatlar
+7667 kunlar
+1 10930 kunlar
Postlar arxiv
የልማቷ አጋር እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል። የቀድሞ ተማሪዎቹ በሀዋሳ በሚኖራቸው የሦስት ቀናት ቆይታ የተለያዩ ሁነቶችን የሚያከናውኑ ዛሬ ከሰዓዓ በኋላ ደግሞ ወደ ቀድሞ ቤታቸው ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አቅንተው ትዝታቸውን እያወሱ የነገ ራዕያቸው ላይ የሚመክሩበት መርሃግብር አላቸው፡፡ በነሐሴ 24/2018 ዓ/ም በሚከናወነው የማጠቃለያ መርሃግብር ላይ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር ምስረታ የሚታወጅበት፤ "አንለያይም" በሚል ርዕስ የተዘጋጀ መጽሐፍ የሚመረቅበት፣ እንዲሁም ማህበሩ ከዩኒቨርሲቲው እና ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በአጋርነት ለመስራት ውል የሚገቡበት መድረክ እንደሚኖር ማወቅ ተችሏል፡፡ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

የ"አንለያይም" ትውልድ ወደ የፍቅር መናገሻዋ ሐዋሳ ገብቷል፤ ሐዋሳም ዳዎኤ ቡሹ ብላለች! ***//*** ነሐሴ 23/2018 ዓ/ም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች "አንለያይም!" በሚል መሪ ቃል
+6
የ"አንለያይም" ትውልድ ወደ የፍቅር መናገሻዋ ሐዋሳ ገብቷል፤ ሐዋሳም ዳዎኤ ቡሹ ብላለች! ***//*** ነሐሴ 23/2018 ዓ/ም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች "አንለያይም!" በሚል መሪ ቃል ከነሐሴ 22 -24/2018 ዓ/ም የሚካሄደው የአብሮነት፣ የትብብርና የትውስታ መርሃግብር ትላንት ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ/ም በድምቀት ተጀምሯል፡፡ ስሟ ሲጠራ በፍቅር የሚነዝረው ብዙ ወዳጅ ያፈራችው የውቢቷ ሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በወጣትነት ዘመናቸው ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ገብተው ሶስትም፣ አራትም፣ አምስትም፣ ሰባትም ዓመታትን ተምረው፣ ከ20 ዓመታት በፊት ተመርቀው ለወግ ማዕረግ የበቁትን ልጆቿን ዳኤ ቡሹ ብለው በክብር ተቀብለዋል፡፡ ከሃዋሳ መግቢያው ከሳውዝስፕሪንግ የጀመረው የምሽት የኮሪደር ልማት ጉብኝት በብርሃን የተሞላችውና በልማት ትራንስፎርሜሽን ላይ የምትገኘው ሐዋሳ መልክ በናፍቆት ሊያዩዋት ለመጡት ልጆቿ የደስታና ኩራት እንዲሁም የዕድገትና ብልጽግና ተስፋ መሆኗን አስመስክረዋል፡፡ 200 የሚደርሱ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች በዚህ መርሃግብር ላይ የተካፈሉ ሲሆን በዛሬው ዕለት ማለዳ ላይ የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር እና የእግር ጉዞ አድርገዋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩን ወክለው አቀባበል ያደረጉት የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታደሰ ፍቅሬ በመክፈቻ ንግግራቸው ኢትዮጵያዊነት በጋራ ራዕይ እና ኃላፊነት በመተሳሰር የሚገለጥ መሆኑን አስረድተዋል። አቶ ታደሰ "ውቧ ከተማችን ሀዋሳ በደማቅ እንግዳ ተቀባይነት ስሜት 'ዳዎኤ ቡሹ ብላ' ዛሬም ያንኑ የቀድሞ ፍቅሯን በበርካታ የልማት ሥራዎች አብባና አምራ ታስተናግዳችኋለች" ሲሉ ለቀድሞ ተማሪዎች ገልጸዋል። አያይዘውም ተማሪዎቹ የከተማዋን ተናፋቂ ገጽታ በአካል በመገኘት እንዲያጣጥሙ እና በቀጣይም የልማቷ

ማስታወቂያ! *//* "ከምርምር ዓለም" የተሰኘው የሬድዮ ፕሮግራም በደቡብ ኤፍ ኤም 100.9 ዘወትር ዓርብ ከ11 :00 -- 11:50 ወደ አድማጮች ሊደርስ ነው! ፕሮግራሙ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በየዘር
ማስታወቂያ! *//* "ከምርምር ዓለም" የተሰኘው የሬድዮ ፕሮግራም በደቡብ ኤፍ ኤም 100.9 ዘወትር ዓርብ ከ11 :00 -- 11:50 ወደ አድማጮች ሊደርስ ነው! ፕሮግራሙ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በየዘርፉ የሚካሄዱ የሳይንሳዊ ምርምር ዉጤቶች በስፋት ለአድማጮች የሚቀርቡበት ሳምንታዊ የሬድዮ ፕሮግራም ነው:: ነባሩ የሬድዮ ፕሮግራም በ2019 ዓ/ም ለእርስዎ በአዲስ መልክ ቀርቧል:: ምርምርን ከተመራማሪዎች መረጃን ከምንጩ አድምጠዉ ስራዎን በሳይንሳዊ መንገድ ይምሩት! በፕሮግራሙ እንዲዳሰስ የሚፈልጉትን የምርምር ርዕሰ-ጉዳይ ወይም የማህበረሰብ ችግር አሊያም እንዲጋበዝ የሚፈልጉትን ተመራማሪ ይጠቁሙን እናስተናግዳለን:: ያድምጡን ፣ ይሳተፉ፣ ይጠቀሙበት! የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ትብብር ም/ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ከደቡብ ሬድዮና ቴሌዚዥን ድርጅት ጋር በመተባበር ከምርምር ዓለም! ለበለጠ መረጃ;- [ ] በአጭር የጽሁፍ መልእክት +251 925629589 [ ] በኢ-ሜይል አድራሻ iraad@hu.edu.et [ ] በአካል;- ዋና ግቢ አዲሱ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ህንጻ ቢሮ ቁ 401 [ ] ፓ.ሳ.ቁ. 05 ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

የዩኒቨርስቲዉ ፋይናንስና በጀት ስራ አስፈጻሚ  ወ/ሮ ፀዳለች አሽናፊ የስልጠናውን ይዘት ሲያብራሩ በስትራቴጂክ እቅድ፣ በፕሮግራም በጀት አሰራር መርሆዎች፣ በፋይናንስ ግልጸኝነትና ተጠያቂነት መመሪያ እንዲሁም በተሻሻለው የጥሬ ገንዘብ አስተዳደር ዙሪያ ገለጻ ተደርጎ ሰፊ ውይይት መካሄዱን ገልጸው ሰልጣኞች በሂደቱ ያገኙትን እውቀት በአግባቡ በመጠቀም የዩኒቨርሲቲውን እቅዶች በተሻለ ደረጃ ለመፈጸም የሚደረገውን ስራ ማገዝ እንደሚገባቸዉ አሳስበዋል። ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ በፕሮግራም በጀት አዘገጃጀት እና አሰራር ስርዓት ላይ ለባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ። *//* ነሐሴ 21/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የስትራቴ
+7
የስትራቴጂክ ጉዳዮች ሾል አስፈጻሚ  በፕሮግራም በጀት አዘገጃጀት እና አሰራር ስርዓት ላይ ለባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ። *//* ነሐሴ 21/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የስትራቴጂክ ጉዳዮች ሾል አስፈጻሚ ለኮሌጆች የዕቅድና ዳታ አስተባባሪዎች፣ ለፋይናንስ በጀት ቡድን መሪዎች፣ ለመረጃ አስተዳደር  አስተባባሪዎች፣ ለእቅድ ዝግጅትና ክትትል ቡድን መሪዎች እንዲሁም ለኦዲት ባለሙያዎችና ቡድን መሪዎች በፕሮግራም በጀት አዘገጃጀት እና አሰራር ስርአት እንዲሁም በፋይናንስ ግልጸኝነት ላይ ያተኮረ  የአቅም ግንባታ ስልጠና ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ/ም ሰጥቷል። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዚደንት ዶ/ር ሳሙኤል ጂሎ በዚሁ መድረክ ባስተላለፉት መልዕክት ወቅቱ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ወደ ልሾ-ገዝነት ሽግግር እያደረገ ያለበት ወሳኝ ወቅት በመሆኑ የበጀት እቅድ እና አፈጻጸምን በተናበበ መልኩ ማስኬድ ያስፈልጋል ብለዋል።  የሚበጀተውን ገንዘብ ለታለመለት አላማ ብቻ እና በእቅድ መሰረት ሼል ላይ ማዋል እንደሚገባ አጽንኦት የሰጡት ዶ/ር ሳሙኤል የስራ ሂደቱ በገንዘብ ሚኒስቴር የጥሬ ገንዘብ አስተዳደር መመሪያ መሰረት መከናወን እንዳለበት አሳስበዋል። የስትራቴጂክ ጉዳዮች ሾል አስፈጻሚ አቶ ሙሉጌታ ቡርቃ በበኩላቸው፤ የተመደበውን በጀት ከዩኒቨርሲቲው አመታዊ እና መካከለኛ ዘመን እቅዶች ጋር የማስተሳሰሩን አስፈላጊነት ጠቁመው ስልጠናው የተዘጋጀው እነዚህን እቅዶች ከበጀት አሰራር ጋር ለማቀናጀት አቅም ለመፍጠር እንደሆነ ገልጸዋል። አቶ ሙሉጌታ እንዳሉት ስልጠናው የበጀት አሰራር ስርዓትን በተዘጋጀው መመሪያና ስትራቴጂ መሰረት በጥራትና በግልጽነት መተግበር ተቋማዊ አሰራርን ለማጠናከር እና ሀብትን በአግባቡ ሾል ላይ ለማዋል ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ያሰርፃል ብለዋል::

It's almost time! Hawassa university alumni coming back home and making history!
It's almost time! Hawassa university alumni coming back home and making history!

የ"አንለያይም" ትውልድ ሐዋሳ ሊመጣ አንድ ቀን ብቻ ቀረው! ***//*** ነሐሴ 20/2018 ዓ/ም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች "አንለያይም" ብለው ያስተማራቸውን፣ አዋቂ ብቻ ሳይሆን ኃላፊነ
የ"አንለያይም" ትውልድ ሐዋሳ ሊመጣ አንድ ቀን ብቻ ቀረው! ***//*** ነሐሴ 20/2018 ዓ/ም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች "አንለያይም" ብለው ያስተማራቸውን፣ አዋቂ ብቻ ሳይሆን ኃላፊነትን በብቃትና በስነምግባር መሸከም የሚችሉበትን አቅም ለግሶ ከየአቅጣጫው አሰባስቦ፣ መልሶ ወደ ዓለም የላካቸውን የዕውቀት ማዕድ፣ ልዩ የፍቅር ቦታ ሰላማዊና ተናፋቂውን ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዳግም ከ20 ዓመታት ቆይታ በኋላ በልዩ ናፍቆት ሊጎበኙት፣ እድገትና ራዕዩን ሊያስቀጥሉ አልመው እነሆ ሊመጡ ነው! ገና ስሟ ሲጠራ ወዳጆቿ የልብ ትርታቸው የሚጨምርላት ውቢቷ የፍቅር ከተማ ሐዋሳ፣ ዩኒቨርሲቲ ገብተው ሶስትም፣ ራትም፣ አምስትም፣ ሰባትም ዓመታትን ተምረው፣ ተመርቀው ለወግ ማዕረግ ከደረሱ በኋላ በሃገር ውስጥና በዓለም ዙርያ ተበትነው በየሰለጠኑበት የሙያ ዘርፍ ህዝብን ሲመሩና ሲያገለግሉ የቆዩ፣ እየመሩ ያሉ፣ ብርቅዬ ልጆቿ አንለያይም በሚል መፈክር ከያሉበት ተፈላልገው የቀድሞ የፍቅርና የትዝታ ቤታቸውን ሊጎበኙ፣ ብሎም ልማት እድገቷን ሊደግፉ እ.የ.መ.ጡ… ነው! "አንለያይም" ያሉት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፍሬዎች ሐዋሳ ሊመጡ አንድ ቀን ብቻ ቀርቶታል! ከተማዋም ዩኒቨርሲቲውም በፍቅርና በናፍቆት ይሄንን ባለራዕይ ትውልድ "ዳኤ ቡሹ" ሊሉት ዝግጁ ናቸው! ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

Please, check the following link. https://mfonokpok.com/seminar/
Please, check the following link. https://mfonokpok.com/seminar/

Let's begin the countdown for Hawassa university Alumni Homecoming and Reunion!
Let's begin the countdown for Hawassa university Alumni Homecoming and Reunion!

IOT Placement

IOT Placement

Dear Applicants for NGAT, please check your placement for IOT at Hawassa University Here.

ንኳን ለመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ***//*** ነሐሴ 19/2018 ዓ/ም ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፡- እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነብዩ መሃመድ የልደት በዓል (መውሊድ) በሰላምና
ንኳን ለመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ***//*** ነሐሴ 19/2018 ዓ/ም ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፡- እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነብዩ መሃመድ የልደት በዓል (መውሊድ) በሰላምና በጤና አደረሳችሁ! በዓሉ የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የፍቅር እና የደስታ ይሁንላችሁ! መልካም በዓል! ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

የሀዋሳ፣ አርሲ፣ መደወላቡ፣ አርባምንጭ፣ ጂንካ፣ ዋቸሞ፣ ዲላ፣ ቡሌ ሆራ፣ ወላይታ እና ወራቤ ዩኒቨርሲቲዎች የፌደራል ፖሊስ የሬጅመንት ኃላፊ ኮማንደር ዳምጠው ኩሳ በበኩላቸው፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ጸጥታና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ በመጠበቅ የዕለት ተዕለት የማስተማርና የመማር ሂደቱ ያለ ምንም ስጋት እንዲከናወን የተደረገው ጥረት ውጤታማ መሆኑን አብራርተው በ2018 ዓ/ም የነበረውን መደበኛ የትምህርትና የፈተና ጊዜ እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ በዩኒቨርሲቲዎቹ የተሰጠውን የመውጫ ፈተና በስኬታማነት መፈጸም መቻሉን ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲ ደህንነት ፖሊስ መምሪያ ሬጅመንት አማካኝነት በበጀት አመቱ የተከናወኑ አጠቃላይ የጥበቃና የደህንነት ስራዎችን አመታዊ አፈጻጸም በተመለከተ ገለጻ ያደረጉት እና የአጋር ተቋማትና የዩኒቨርሲቲዎቹ አመራሮች የነበረ ተሳትፎ እንዴት በተሻለ መልኩ ማስቀጠል ይገባል በሚለው ላይ ሀሳባቸውን የገለጹት በፌደራል ፖሊስ የተቋማትና መሰረተ ልማት ጥበቃ ም/ዋና መምሪያ አዛዥ የሆኑት የተከበሩ ረ/ኮሚሽነር ሰለሞን ከበደ ናቸው። በመድረኩ ላይ የፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አመራሮች፣ የሲዳማ ክልል ፖሊስ መምሪያ ኃላፊዎች፣ የአስሩ ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዚደንቶች፣ በየደረጃው ያሉ የጸጥታ እና የደህንነት አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው አጋር ድርጅቶች የተገኙ ሲሆን በበጀት ዓመቱ የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ለአስሩ የዩኒቨርሲቲ ፖሊስ አመራሮች፣ ለዩኒቨርሲቲዎቹ ፕሬዚደንቶች፣ ለተለያዩ አጋር ድርጅቶችና ተቋማት እውቅና እና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

ፌደራል ፖሊስ በዩኒቨርሲቲ ደህንነት ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የላቀ የስራ አፈጻጸም ላስመዘገበው ሬጅመንት 2 የእውቅናና ተሃድሶ ፕሮግራም ተካሄደ። ***//*** ነሐሴ 18/2018 ዓ/ም ሀዋሳ ዩ
+9
ፌደራል ፖሊስ በዩኒቨርሲቲ ደህንነት ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የላቀ የስራ አፈጻጸም ላስመዘገበው ሬጅመንት 2 የእውቅናና ተሃድሶ ፕሮግራም ተካሄደ። ***//*** ነሐሴ 18/2018 ዓ/ም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ በደቡባዊው የኢትዮጵያ ክፍል የሚገኙ አስር ዩኒቨርሲቲዎችን እና ዘጠኝ ካምፓሶችን ደህንነት ለማረጋገጥ ኃላፊነት የተሰጠው የፌደራል ፖሊስ የዩኒቨርሲቲ ደህንነት ፖሊስ መምሪያ ሬጅመንት በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ስራ አፈጻጸም ግምገማ ከ6ቱ ሬጅመንቶች መካከል የላቀ የስራ አፈፃፀም በማስመዝገብ ሬጅመንት 2 1ኛ መውጣቱን ተከትሎ ለሬጅመንት 2 ስታፍ፣ ሻምበል 2 አመራርና አባላት የምስጋና እውቅና አሰጣጥና ተሃድሶ መርሃግብር ነሐሴ 17/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አፍሪካ ህብረት አዳራሽ ተካሂዷል፡፡ በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ክቡር ም/ኮሚሽነር መላኩ ፈንታ በሀገራችን በሁሉም ተቋማት መተግበር ከጀመረው የለውጥ አሰራር ጋር ተያይዞ ፌደራል ፖሊስም ዘመናዊ የፖሊስ ተቋም በመሆን ረገድ አሰራሩን አዝምኖ ስኬታማ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ቀደም ሲል ዩኒቨርሲቲዎች የፖለቲካ ሀሳብ ማስፈጸሚያ በመሆን ከተቋቋሙበት ዋነኛ ዓላማ ባፈነገጠ መልኩ የሁከትና ብጥብጥ ማዕከላት ሆነው ይገኙ እንደነበር ያስታወሱት ም/ኮሚሽነር መላኩ ይህንን የወቅቱን አደጋ በመቀልበስና በእነኚህ ተቋማት ያለውን ሰላምና ጸጥታ በማረጋገጥ ረገድ የፌደራል ፖሊስ የተቋማትና መሠረተ ልማት ጥበቃ ምክትል ዋና መምሪያ በሬጅመንቶቹ በኩል አይተኬ ስራ መስራቱን ተናግረዋል።

photo content

Day 2 Session 1 NGAT Placement.pdf4.95 KB

Day 1 Session 2 NGAT Placement.pdf5.00 KB

Day 1 Session 1 NGAT placement.pdf5.04 KB