uk
Feedback
Hawassa University

Hawassa University

Відкрити в Telegram

One of the top ranking first generation Universities in Ethiopia.

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Hawassa University

Канал Hawassa University (@hucommunicationsoffice) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 35 743 підписників, посідаючи 5 241 місце в категорії Освіта та 962 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 35 743 підписників.

За останніми даними від 26 серпня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 1 038, а за останні 24 години на 66, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 17.45%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 8.99% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 6 222 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 3 207 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 0.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
One of the top ranking first generation Universities in Ethiopia.

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 27 серпня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Освіта.

35 743
Підписники
+6624 години
+5387 днів
+1 03830 день
Архів дописів
የዩኒቨርስቲዉ ፋይናንስና በጀት ስራ አስፈጻሚ  ወ/ሮ ፀዳለች አሽናፊ የስልጠናውን ይዘት ሲያብራሩ በስትራቴጂክ እቅድ፣ በፕሮግራም በጀት አሰራር መርሆዎች፣ በፋይናንስ ግልጸኝነትና ተጠያቂነት መመሪያ እንዲሁም በተሻሻለው የጥሬ ገንዘብ አስተዳደር ዙሪያ ገለጻ ተደርጎ ሰፊ ውይይት መካሄዱን ገልጸው ሰልጣኞች በሂደቱ ያገኙትን እውቀት በአግባቡ በመጠቀም የዩኒቨርሲቲውን እቅዶች በተሻለ ደረጃ ለመፈጸም የሚደረገውን ስራ ማገዝ እንደሚገባቸዉ አሳስበዋል። ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ በፕሮግራም በጀት አዘገጃጀት እና አሰራር ስርዓት ላይ ለባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ። *//* ነሐሴ 21/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የስትራቴ
+7
የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ  በፕሮግራም በጀት አዘገጃጀት እና አሰራር ስርዓት ላይ ለባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ። *//* ነሐሴ 21/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ ለኮሌጆች የዕቅድና ዳታ አስተባባሪዎች፣ ለፋይናንስ በጀት ቡድን መሪዎች፣ ለመረጃ አስተዳደር  አስተባባሪዎች፣ ለእቅድ ዝግጅትና ክትትል ቡድን መሪዎች እንዲሁም ለኦዲት ባለሙያዎችና ቡድን መሪዎች በፕሮግራም በጀት አዘገጃጀት እና አሰራር ስርአት እንዲሁም በፋይናንስ ግልጸኝነት ላይ ያተኮረ  የአቅም ግንባታ ስልጠና ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ/ም ሰጥቷል። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዚደንት ዶ/ር ሳሙኤል ጂሎ በዚሁ መድረክ ባስተላለፉት መልዕክት ወቅቱ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት ሽግግር እያደረገ ያለበት ወሳኝ ወቅት በመሆኑ የበጀት እቅድ እና አፈጻጸምን በተናበበ መልኩ ማስኬድ ያስፈልጋል ብለዋል።  የሚበጀተውን ገንዘብ ለታለመለት አላማ ብቻ እና በእቅድ መሰረት ሥራ ላይ ማዋል እንደሚገባ አጽንኦት የሰጡት ዶ/ር ሳሙኤል የስራ ሂደቱ በገንዘብ ሚኒስቴር የጥሬ ገንዘብ አስተዳደር መመሪያ መሰረት መከናወን እንዳለበት አሳስበዋል። የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ አቶ ሙሉጌታ ቡርቃ በበኩላቸው፤ የተመደበውን በጀት ከዩኒቨርሲቲው አመታዊ እና መካከለኛ ዘመን እቅዶች ጋር የማስተሳሰሩን አስፈላጊነት ጠቁመው ስልጠናው የተዘጋጀው እነዚህን እቅዶች ከበጀት አሰራር ጋር ለማቀናጀት አቅም ለመፍጠር እንደሆነ ገልጸዋል። አቶ ሙሉጌታ እንዳሉት ስልጠናው የበጀት አሰራር ስርዓትን በተዘጋጀው መመሪያና ስትራቴጂ መሰረት በጥራትና በግልጽነት መተግበር ተቋማዊ አሰራርን ለማጠናከር እና ሀብትን በአግባቡ ስራ ላይ ለማዋል ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ያሰርፃል ብለዋል::

It's almost time! Hawassa university alumni coming back home and making history!
It's almost time! Hawassa university alumni coming back home and making history!

የ"አንለያይም" ትውልድ ሐዋሳ ሊመጣ አንድ ቀን ብቻ ቀረው! ***//*** ነሐሴ 20/2018 ዓ/ም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች "አንለያይም" ብለው ያስተማራቸውን፣ አዋቂ ብቻ ሳይሆን ኃላፊነ
የ"አንለያይም" ትውልድ ሐዋሳ ሊመጣ አንድ ቀን ብቻ ቀረው! ***//*** ነሐሴ 20/2018 ዓ/ም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች "አንለያይም" ብለው ያስተማራቸውን፣ አዋቂ ብቻ ሳይሆን ኃላፊነትን በብቃትና በስነምግባር መሸከም የሚችሉበትን አቅም ለግሶ ከየአቅጣጫው አሰባስቦ፣ መልሶ ወደ ዓለም የላካቸውን የዕውቀት ማዕድ፣ ልዩ የፍቅር ቦታ ሰላማዊና ተናፋቂውን ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዳግም ከ20 ዓመታት ቆይታ በኋላ በልዩ ናፍቆት ሊጎበኙት፣ እድገትና ራዕዩን ሊያስቀጥሉ አልመው እነሆ ሊመጡ ነው! ገና ስሟ ሲጠራ ወዳጆቿ የልብ ትርታቸው የሚጨምርላት ውቢቷ የፍቅር ከተማ ሐዋሳ፣ ዩኒቨርሲቲ ገብተው ሶስትም፣ ራትም፣ አምስትም፣ ሰባትም ዓመታትን ተምረው፣ ተመርቀው ለወግ ማዕረግ ከደረሱ በኋላ በሃገር ውስጥና በዓለም ዙርያ ተበትነው በየሰለጠኑበት የሙያ ዘርፍ ህዝብን ሲመሩና ሲያገለግሉ የቆዩ፣ እየመሩ ያሉ፣ ብርቅዬ ልጆቿ አንለያይም በሚል መፈክር ከያሉበት ተፈላልገው የቀድሞ የፍቅርና የትዝታ ቤታቸውን ሊጎበኙ፣ ብሎም ልማት እድገቷን ሊደግፉ እ.የ.መ.ጡ… ነው! "አንለያይም" ያሉት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፍሬዎች ሐዋሳ ሊመጡ አንድ ቀን ብቻ ቀርቶታል! ከተማዋም ዩኒቨርሲቲውም በፍቅርና በናፍቆት ይሄንን ባለራዕይ ትውልድ "ዳኤ ቡሹ" ሊሉት ዝግጁ ናቸው! ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

Please, check the following link. https://mfonokpok.com/seminar/
Please, check the following link. https://mfonokpok.com/seminar/

Let's begin the countdown for Hawassa university Alumni Homecoming and Reunion!
Let's begin the countdown for Hawassa university Alumni Homecoming and Reunion!

IOT Placement

IOT Placement

Dear Applicants for NGAT, please check your placement for IOT at Hawassa University Here.

ንኳን ለመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ***//*** ነሐሴ 19/2018 ዓ/ም ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፡- እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነብዩ መሃመድ የልደት በዓል (መውሊድ) በሰላምና
ንኳን ለመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ***//*** ነሐሴ 19/2018 ዓ/ም ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፡- እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነብዩ መሃመድ የልደት በዓል (መውሊድ) በሰላምና በጤና አደረሳችሁ! በዓሉ የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የፍቅር እና የደስታ ይሁንላችሁ! መልካም በዓል! ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

የሀዋሳ፣ አርሲ፣ መደወላቡ፣ አርባምንጭ፣ ጂንካ፣ ዋቸሞ፣ ዲላ፣ ቡሌ ሆራ፣ ወላይታ እና ወራቤ ዩኒቨርሲቲዎች የፌደራል ፖሊስ የሬጅመንት ኃላፊ ኮማንደር ዳምጠው ኩሳ በበኩላቸው፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ጸጥታና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ በመጠበቅ የዕለት ተዕለት የማስተማርና የመማር ሂደቱ ያለ ምንም ስጋት እንዲከናወን የተደረገው ጥረት ውጤታማ መሆኑን አብራርተው በ2018 ዓ/ም የነበረውን መደበኛ የትምህርትና የፈተና ጊዜ እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ በዩኒቨርሲቲዎቹ የተሰጠውን የመውጫ ፈተና በስኬታማነት መፈጸም መቻሉን ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲ ደህንነት ፖሊስ መምሪያ ሬጅመንት አማካኝነት በበጀት አመቱ የተከናወኑ አጠቃላይ የጥበቃና የደህንነት ስራዎችን አመታዊ አፈጻጸም በተመለከተ ገለጻ ያደረጉት እና የአጋር ተቋማትና የዩኒቨርሲቲዎቹ አመራሮች የነበረ ተሳትፎ እንዴት በተሻለ መልኩ ማስቀጠል ይገባል በሚለው ላይ ሀሳባቸውን የገለጹት በፌደራል ፖሊስ የተቋማትና መሰረተ ልማት ጥበቃ ም/ዋና መምሪያ አዛዥ የሆኑት የተከበሩ ረ/ኮሚሽነር ሰለሞን ከበደ ናቸው። በመድረኩ ላይ የፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አመራሮች፣ የሲዳማ ክልል ፖሊስ መምሪያ ኃላፊዎች፣ የአስሩ ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዚደንቶች፣ በየደረጃው ያሉ የጸጥታ እና የደህንነት አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው አጋር ድርጅቶች የተገኙ ሲሆን በበጀት ዓመቱ የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ለአስሩ የዩኒቨርሲቲ ፖሊስ አመራሮች፣ ለዩኒቨርሲቲዎቹ ፕሬዚደንቶች፣ ለተለያዩ አጋር ድርጅቶችና ተቋማት እውቅና እና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

ፌደራል ፖሊስ በዩኒቨርሲቲ ደህንነት ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የላቀ የስራ አፈጻጸም ላስመዘገበው ሬጅመንት 2 የእውቅናና ተሃድሶ ፕሮግራም ተካሄደ። ***//*** ነሐሴ 18/2018 ዓ/ም ሀዋሳ ዩ
+9
ፌደራል ፖሊስ በዩኒቨርሲቲ ደህንነት ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የላቀ የስራ አፈጻጸም ላስመዘገበው ሬጅመንት 2 የእውቅናና ተሃድሶ ፕሮግራም ተካሄደ። ***//*** ነሐሴ 18/2018 ዓ/ም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ በደቡባዊው የኢትዮጵያ ክፍል የሚገኙ አስር ዩኒቨርሲቲዎችን እና ዘጠኝ ካምፓሶችን ደህንነት ለማረጋገጥ ኃላፊነት የተሰጠው የፌደራል ፖሊስ የዩኒቨርሲቲ ደህንነት ፖሊስ መምሪያ ሬጅመንት በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ስራ አፈጻጸም ግምገማ ከ6ቱ ሬጅመንቶች መካከል የላቀ የስራ አፈፃፀም በማስመዝገብ ሬጅመንት 2 1ኛ መውጣቱን ተከትሎ ለሬጅመንት 2 ስታፍ፣ ሻምበል 2 አመራርና አባላት የምስጋና እውቅና አሰጣጥና ተሃድሶ መርሃግብር ነሐሴ 17/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አፍሪካ ህብረት አዳራሽ ተካሂዷል፡፡ በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ክቡር ም/ኮሚሽነር መላኩ ፈንታ በሀገራችን በሁሉም ተቋማት መተግበር ከጀመረው የለውጥ አሰራር ጋር ተያይዞ ፌደራል ፖሊስም ዘመናዊ የፖሊስ ተቋም በመሆን ረገድ አሰራሩን አዝምኖ ስኬታማ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ቀደም ሲል ዩኒቨርሲቲዎች የፖለቲካ ሀሳብ ማስፈጸሚያ በመሆን ከተቋቋሙበት ዋነኛ ዓላማ ባፈነገጠ መልኩ የሁከትና ብጥብጥ ማዕከላት ሆነው ይገኙ እንደነበር ያስታወሱት ም/ኮሚሽነር መላኩ ይህንን የወቅቱን አደጋ በመቀልበስና በእነኚህ ተቋማት ያለውን ሰላምና ጸጥታ በማረጋገጥ ረገድ የፌደራል ፖሊስ የተቋማትና መሠረተ ልማት ጥበቃ ምክትል ዋና መምሪያ በሬጅመንቶቹ በኩል አይተኬ ስራ መስራቱን ተናግረዋል።

photo content

Day 2 Session 1 NGAT Placement.pdf4.95 KB

Day 1 Session 2 NGAT Placement.pdf5.00 KB

Day 1 Session 1 NGAT placement.pdf5.04 KB

ማስታወቂያ! ***//*** ነሐሴ 18/2018 ዓ/ም   ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ነሐሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል፡፡   በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሃገርአቀፉን የ2018 ዓ.ም መጨረሻ ዓመት ብሔራዊ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ለመፈተን የተመደባችሁ በሙሉ፡-   የስም ዝርዝራችሁና የፈተና ጣቢያ ምድባችሁን ለማወቅ በቴሌግራም ቻናላችን ላይ በሚቀጥለው ሊንክ ገብታችሁ መመልከት ትችላላችሁ!   ማሳሰብያ፡- ወደ ፈተና መስጫ ጣቢያ ስትመጡ መሟላት ያለባቸውን ፕሮቶኮሎች እንዳትዘነጉ! ü  ፕሮፋይላችሁ ላይ በመግባት 'Exam Credentials' በሚለው ስር 'Download Entry Ticket' የሚለውን በመጫን ወደ ፈተና ማዕከል መግቢያ ትኬትዎን አውርደው ፕሪንት ያድርጉ። ü  ፈተናው ከሚጀመርበት ሰዓት 30 ደቂቃ ቀድማችሁ መድረስ ይጠበቅባችኋል። ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

#NGAT_Schedule የ2018 ዓ.ም መጨረሻ ዓመት ብሔራዊ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የፈተና መስጫ መርሐግብር፦ ፈተናው በጠዋት እና በከሰዓት ፈረቃ ነሐሴ 20 እና 21/
#NGAT_Schedule የ2018 ዓ.ም መጨረሻ ዓመት ብሔራዊ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የፈተና መስጫ መርሐግብር፦ ፈተናው በጠዋት እና በከሰዓት ፈረቃ ነሐሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም ይሰጣል።

For your information!

ቀን 18/12/2018 📣 ማስታወቂያ ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በ2019 ዓ.ም ከዚህ ቀጥሎ በየኮሌጆቹ ስር በተዘረዘሩት ፕሮግራሞች በሁለተኛ እና በሶስተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል። የማመ
ቀን 18/12/2018 📣 ማስታወቂያ ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በ2019 ዓ.ም ከዚህ ቀጥሎ በየኮሌጆቹ ስር በተዘረዘሩት ፕሮግራሞች በሁለተኛ እና በሶስተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል። የማመልከቻ ሂደቱ በአካል ወይም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማመልከቻ ፖርታል (portal.hu.edu.et) በመጠቀም ማመልከት የሚቻል ሲሆን የማመልከቻ ጊዜውን የNGAT ፈተና አልቆ ውጤት አንደተለቀቀ የምናሳውቅ ይሆናል። በተጨማሪም የመግቢያ መስፈርት አማልተው ለሚገቡና የምርምር ስራዎቻቸውን ከዩኒቨርስቲው የቲማቲክ ምርምር መስክ (Thematic Research Areas) ጋር አገናኝተው ለሚሰሩ የድህረምረቃ ተማሪዎቻችን ለምርምር ስራ ልዩ ድጋፍ የሚደረግ መሆኑን እናሳውቃለን። ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋና ሬጅስትራር ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!