Hawassa University
One of the top ranking first generation Universities in Ethiopia.
Ko'proq ko'rsatish📈 Telegram kanali Hawassa University analitikasi
Hawassa University (@hucommunicationsoffice) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 34 833 obunachidan iborat bo'lib, Taʼlim toifasida 5 476-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 977-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 34 833 obunachiga ega bo‘ldi.
02 Avgust, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 452 ga, so‘nggi 24 soatda esa 22 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 18.20% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 8.52% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 6 340 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 969 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 0 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“One of the top ranking first generation Universities in Ethiopia.”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 03 Avgust, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Taʼlim toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 02 Avgust | +22 | |||
| 01 Avgust | +28 |
| 2 | በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 15ኛው ዙር ብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስልጠና ተጀመረ።
*//*
ሐምሌ 26/2018 ዓ/ም
ሰላም ሚኒስቴር ከሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር “በጎነት ለአብሮነት” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የ15ኛው ዙር ብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስልጠና የመክፈቻ ስነ-ስርዓት 1,000 የሚደርሱ በጎ ፈቃደኛ ሰልጣኞች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ ልዩ ልዩ እንግዶች እና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የሐዋሳ ከተማ ሚሊኒየም አዳራሽ ላይ ዛሬ ተካሂዷል።
የሰላም ሚኒስቴር የብሔራዊ በጎ ፈቃድ አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ገዛኸኝ ጥላሁን በመክፈቻ ንግግራቸው በ2011 ዓ.ም የተጀመረው ይህ ፕሮግራም ኢትዮጵያ ያሏትን መልካም እሴቶች ለወጣቱ በማስተላለፍ የህብረተሰቡን ማህበራዊ ትስስር ለማጠናከርና የሰላም ባህልን ለማጎልበት የማይተካ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ብለዋል። አቶ ገዛኸኝ አክለውም ሰልጣኞች በስልጠናው ወቅት የሚያገኙትን እውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ለሀገር አንድነትና ለወንድማማችነት መጠናከር በግንባር ቀደምትነት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳሳበዋል።
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር አየለ አዳቶ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላሟን ለማረጋገጥና በጸና መሰረት ላይ የተገነባች ሀገር ለመሆን በወሳኝ አጀንዳዎች ላይ እየመከረች ያለችበት ታሪካዊ ወቅት ላይ የምንገኝ በመሆኑ የወጣቶች የነቃ ተሳትፎ ለሀገር ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በመቀጠልም ይህ ስልጠና ወጣቶች የነገ ሀገር ተረካቢነታቸውን በስነ-ምግባርና በበጎ ፈቃደኝነት ለማረጋገጥ የሚያስችላቸው መልካም እድል እንደሚፈጥርላቸው በመገንዘብ ስልጠናውን በአላማ እንዲከታተሉ አሳስበዋል:: | 1 555 |
| 3 | ዩኒቨርሲቲ ሽግግር ስትራቴጂ ቀረጻ ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ታፈሰ ማቴዎስ ሰፊ ገለጻና ማብራሪያ አቅረበዋል፡፡ ዶ/ር ታፈሰ ባቀረቡት ጽሑፍ ዩኒቨርሲቲዎች ለሀገር ልማት ያላቸዉን ሁለንተናዊ እና አይተኬ ሚና ከተጨባጭ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች አንጻር አጉልተዉ ለማሳየት ሞክረዋል፡፡ በተጨማሪም የሀገራችን ዩኒቨርሲቲዎች በሂደት ወደ ራስ-ገዝ ተቋምነት እዲሸጋገሩ መንግስት ፖሊሲ ቀርፆ አቅጣጫ ማስቀመጡንና በዚህም መሰረት ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ባለፉት 50 ዓመታት በሰዉ ሃይል ልማት፣ በምርምርና ማህረሰብ አገልግሎት ለአካባቢዉ፣ ለሀገሪቱና ለዓለም ህዝቦች እያበረከተ የቆየዉን አስታዋጽኦ በማስረጃ አስደግፈዉ ያቀረቡት ዶ/ር ታፈሰ፣ በቀጣይም የላቀ አገልግሎት ለመስጠት ቅልጥፍና፣ ዉጤታማነትና ጥራት ላይ መሥራት የሽግግሩ ዋንኛ ዓላማዎች እንደሆኑ አስረድተዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲዉ ራስ-ገዝ ሽግግር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃን መሸሻ በበኩላቸዉ የሽግግር ሂደቱ አራት ዓመታትን የፈጀ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ያካተተና በቀጣይ ለሁለት ዓመታት የሚቆይ የሙከራ ትግበራ ጊዜን የሚያልፍና ከዚያም ወደ ሙሉ ትግበራ የሚገባ አካሄድ መሆኑን ለተሳታፊዎች አስረድተዋል፡፡ አቶ ብርሃን አክለዉም ዩኒቨርሲቲዉ በቅድመ ዝግጅት ምዕራፉ የሚጠበቅበትን እጅግ ዉስብስብና አድካሚ የሆኑ ወሳኝ ሂደቶችን ማጠናቀቁንና አሁን በ 2019 ዓ/ም ወደ ሙከራ ትግበራ ለመግባት የዩኒቨርሲቲዉ ሥራ አመራር ቦርድ አስተያየትና የትምህርት ሚንስቴር ዉሳኔን በመጠባበቅ ላይ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ገለጻዎቹን ተከትሎ በተደረገዉ የተሳታፊዎች ዉይይት በርካታ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ቀርበዉ ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷባቸዋል፡፡ የክልሉን ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ወክለው የተገኙት የፕሬዝዳንቱ የኢኮኖሚ አማካሪ ክቡር አቶ ግዛቸው ኖኦራን ጨምሮ ከ64 የተለያዩ የመንግስት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ባለድርሻ ተቋማት የተወከሉ የመድረኩ ተሳታፊዎች ዩኒቨርሲቲዉ እያደረገ ባለዉ ወሳኝ የሽግግር ምዕራፍ ላይ ባለድርሻ አካላትን ማሳተፉን አድንቀዉ በቀጣይ ቢሰሩ ያሏቸዉን ተግባራት ጠቁመዋል፡፡
ለአብነትም፡- ከተቀሩ ባለድርሻ አካላት ጋር መሰል ዉይይቶችን ማካሄድና ግንዛቤን መፍጠር፣ በአቅራቢያ ካሉ የተለያዩ ባለ ድርሻ እና አጋር አካላት ጋር ስትራቴጅያዊ ጉዳዮች ላይ ይበልጥ ተቀራርቦ በዘላቂነትና በትብብር መስራት፣ ዩኒቨርሲቲዉ የሚያስተላልፋቸዉን ዉሳኔዎችና የሽግግር ሂደቱን በተመለከተ ወቂታዊና በቂ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ በመስጠት አሉባልታዎችንና የመረጃ ክፍተቶችን መቅረፍ አስፈላጊ እንደሆነ ተጠቁሟል:: በተለይ ደግሞ በማህበራዊ ሚድያ ላይ የሚታዩ የዩኒቨርሲቲውን እውነታ የማይገልፁ አሉታዊ መረጃዎችን ለማጥራት መሰል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች በስፋት እንደሚያስፈልጉ ጠቁመዋል::
በመድረኩ ማጠቃለያም የዩኒቨርሲቲዉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የተነሱትን አስተያየቶችና ጥያቄዎች በመቀበል በቀጣይ በየደረጃዉ በሂደት ለመስራት ጥረት እደሚደረግ ለመድረኩ ተሳታፊዎች አረጋግጠዉላቸዋል፡፡ በዚህም በተለይ "የበንሳ ዳዬ እና አዋዳ ካምፓሶች ሊዘጉ ነው" የሚል መሰረተቢስ ሐሰተኛ መረጃ በሰፊው እየተሰራጨ መሆኑ ዩኒቨርሲቲው በማህበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነት እንዳይኖረው ለማድረግ በግለሰቦች የሚደረግ ከንቱ ዘመቻ መሆኑን እና የራስገዝነት ሁለት ዋነኛ ኢላማዎች ጥራትን ማረጋገጥ እና ትብብርን ማጠናከር ብሎም እውቀትና ዓለምአቀፋዊነትን የተላበሱና መልካም ስነ ምግባር ያላቸው ምሁራንን ማፍራት ላይ መሆኑን ኃላፊዎቹ አስረድተዋል::
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት! | 4 724 |
| 4 | በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግር ሂደት ላይ የውጭ ባለድርሻ አካላት ውይይት ተካሄደ::
*//*
ሐምሌ 23/2018 ዓ/ም
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ራስገዝ ሽግግር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በሲዳማ ብሔራዊ ክልል ለሚገኙ የውጪ ባለድርሻ አካላት በዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግር ዝግጅት ላየይ የግንዛቤ ማስጨበጫና ግብረመልስ ማሰባሰቢያ የውይይት መድረክ በዋናው ግቢ አፍሪካ ህብረት አዳራሽ አካሂዷል::
የዩኒቨርሲቲዉ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚደንትና ዶ/ር ኢንጅነር ፍስሃ ጌታቸዉ መድረኩን ሲከፍቱ እንደገለፁት ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ባለፉት 50 ዓመታት ዉስጥ ወሳኝ የሚባሉ ሂደቶችን አልፎ አሁን ደግሞ ሌላ የሽግግር ምዕራፍ ላይ የደረሰዉ ከበርካታ ዓለምአቀፍና ክልላዊ ባለ ድርሻና አጋር አካላት ጋር በፈጠረዉ ጠንካራ ተቋማዊ ትስስርና ትብብር መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲዉ በቀጣይ ወደ ራስ-ገዝ የምርምር ዩኒቨርሲቲነት ለመሸጋገር እያደረገ ባለዉ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ከባለ ድርሻ እና አጋር አካላት ጋር መወያየት ያስፈለገውም ዓላማውን በግልፅ አስረድቶ አብሮ ለመስራት ወደ ጋራ ግብ ለመድረስ ታስቦ እንደሆነ ተናግረዋል:: የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዕድገት ከየት ወዴት እንደሆነ ሲገልፁም የዛሬ 50 ዓመት ሥራ ሲጀምር ከነበረው 4 የዲፕሎማ ፕሮግራሞች ወደ 300 በላይ የትምህርት ፕሮግራሞች፣ ከ30 መምህራን ወደ 2000 በላይ መምህራን፣ ከ230 ተማሪዎች ዛሬ ከ20 ሺህ በላይ ተማሪዎችን የሚያስተናግድ እና ዩኒቨርሲቲ ከሆነበት ግዜ ጀምሮ እንኳን እስካሁን ከ120 ሺህ በላይ ምሩቃንን ያፈራ አንጋፋ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን አስረድተዋል::
የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ ምንነት፣ የመንግስት ፖሊሲ አቅጣጫ፣ አስፈላጊነትና በሂደቱ ላይ የባለድርሻ አካላትን ሚና በተመለከተ የዩኒቨርሲቲዉ ምርምርና ትብብር ም/ፕሬዚደንትና የራስ-ገዝ | 4 291 |
| 5 | Matn yo'q... | 4 558 |
| 6 | የNGAT ምዝገባ ለማድረግ በቴሌብር ክፍያ ከመፈፀም ጋር አጋጥሞ የነበረው ችግር ከትናንት ምሽት ጀምሮ መፈታቱ ተገልጿል፡፡ አሁን ላይ አገልግሎቱ በደንብ እየሠራ በመሆኑ ክፍያዎን በመፈፀም ምዝገባዎን ማድረግ ይችላሉ፡፡
ለድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ እስከ ቅዳሜ ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም ብቻ የሚከናወን መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወቃል፡፡
ምዝገባዎን ያድርጉ 👇
https://ngat.ethernet.edu.et
ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ የግድ እንደሚያስፈልግ ያስታውሱ፡፡ | 5 106 |
| 7 | ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት የሚደረገውን የሽግግር ሥራዎች 5ኛ ዙር የሂደት ሪፖርት ገመገመ።
ሐምሌ 22/2018 ዓ/ም
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝ ተቋምነት ለማሸጋገር የሚያስችሉ ስትራቴጂክ ሰነዶች ዝግጅት ላይ 5ኛው ዙር የሂደት ሪፖርት ላይ ውይይትና ግምገማ ተካሂዷል።
የዩኒቨርሲቲው ተ/ፕሬዚደንትና የራስ-ገዝ ሽግግር አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢው ዶ/ር ችሮታው አየለ የራስ-ገዝነት የሽግግር ጉዞ የእስካሁን ሂደት ጥሩ በሚባል ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ገልጸው ሂደቱ ቀጣይነት ያለው በመሆኑ ወደ ተግባር ሲገባም ተጨማሪና ሰፊ ስራዎች እንደሚጠብቁን ተረድተን በበቂ ሁኔታ መዘጋጀት ይኖርብናል ብለዋል። ዶ/ር ችሮታው አክለውም ንዑሳን ኮሚቴዎቹ በየዘርፋቸው የሚያቀርቧቸውን ሪፖርቶች መሰረት በማድረግ ቀጣይ ምን መደረግ አለበት የሚለውን ግብረ ሀይሉ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጥ ጠቁመው ከዚህ በተጨማሪ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ሀሳቦችንና አስተያየቶችን ለመቀበል ያለመ የውይይት መድረክ እንደሚዘጋጅ ተናግረዋል።
የራስ-ገዝ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃን መሸሻ በበኩላቸው ከ5ኛው ዙር በፊት በቀረቡ ሪፖርቶች ላይ የተሰጡ ግብረ-መልሶችንና ማስተካከያዎችን መሰረት በማድረግ የተዘጋጁ ስራዎች በዚህኛው ዙር መቅረባቸውን እና በስድስቱም ንዑሳን ኮሚቴዎች አማካኝነት አጠቃላይ የስራ ዶክመንቶች፣ መመሪያዎችና የስትራቴጂክ ቅየሳ ሪፖርቶች ተጠናቀው ለተሳታፊዎች ለውይይት መቅረባቸውን አስረድተዋል።
በውይይት መድረኩ የስትራቴጂክ እቅድ፣ የተቋሙ መዋቅርና የስራ መደቦች፣ መመሪያዎችና ፖሊሲዎች፣ የትምህርት ፕሮግራሞች ማሻሻያ ሰነድ፣ ደረጃዎችና እውቅና እንዲሁም የስትራቴጂክ ኮሚዩኒኬሽን ንዑሳን ኮሚቴዎች የደረሱበትን ደረጃ የሚያሳዩ ሪፖርቶች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት! | 6 447 |
| 8 | ማስታወቂያ
በክረምት መርሃ ግብር ለመማር ለተመረጣችሁ መምህራን በሙሉ
ትምህርት ሚኒስቴር በማስተማር ሥራ ላይ ያሉ መምህራንን ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ለመጀመር በርካታ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል። በቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ጋር የተናበበ የሥልጠና ማዕቀፍ፣ ፕሮግራሙን ለመምራት የሚያስችሉ የትግበራ ሰነዶችንና የሰልጣኝ መምህራንን ምልመላ፣ መረጣ እና ምደባ ተከናውነዋል።
ስለሆነም ባለፉት አመታት በስልጠናው አሰጣጥ ጥራት ችግር ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን የመምህራን የክረምት የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና በዚህ ክረምት ለማስጀመር ስምንት ዩኒቨርሲቲዎች ተለይተዋል። እነዚህም ባህር ዳር ፣ ሀዋሳ ፣ መቀሌ ፣ ጂማ ፣ ሃሮማያ ፣ ጎንደር እና አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲዎች ሲሆኑ በ2018 ዓ.ም ክረምት 8273 መምህራንን ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ወደ ስልጠና ለማስገባት ዝግጅት ተጠናቋል፡፡
በዚህ መሰረት የመግቢያ ምዘና ወስዳችሁ ያለፋችሁ እና በየዩኒቨርሲቲዎች የተመደባችሁ ሰልጣኝ መምህራን ምዝገባው ሐምሌ 24 እና 25/2018 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን በተጠቀሱት ቀናት በየተመደባችሁባቸው ዩኒቨርስቲዎች በመገኘት እንድትመዘገቡ እያሳሰብን የተመደባችሁበትን ዩኒቨርስቲ ለማዎቅ ይህንን https://shorturl.at/ZjN9e ማስፈንጠሪያ በመጫን ማወቅ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። | 5 951 |
| 9 | ማስታወቂያ ለ NGAT ቱቶሪያል እና NGATየፈተና አመልካቾች በሙሉ፡-
*//*
ሐምሌ 21/2018 ዓ/ም
ከክፍያ ጋር በተገናኘ የተፈጠረውን ብዥታ ለማጥራት ይህ ማስታወቂያ ወጥቷል። በመሆኑም አመልካቾች የሚከተለውን መረጃ በጥንቃቄ እንድትገነዘቡ እናሳስባለን፡-
ስለ 400 ብር ክፍያ፡ ከዚህ ቀደም የከፈላችሁት 400 (አራት መቶ) ብር ለ NGAT ቱቶሪያል (የዝግጅት ትምህርት) ብቻ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን። ይህ ክፍያ ለዋናው የ NGAT ፈተና የምዝገባ ክፍያን አያካትትም።
ስለ NGAT ፈተና ምዝገባ፡ ለዋናው የ NGAT ፈተና (Exam) ለመመዝገብ፣ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት 750 (ሰባት መቶ ሃምሳ) ብር ለብቻው መክፈል ይጠበቅባችኋል።
ስለሆነም የቱቶሪያል ተሳታፊዎች ለፈተናው ለመቀመጥ የተገለጸውን የፈተና ክፍያ በወቅቱ በመፈጸም እንድትመዘገቡ እናሳስባለን።
ድህረ-ምረቃ ዳይሬክቶሬት
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ | 5 422 |
| 10 | ከሰው ምግብነትና መድሃኒትነት እስከ መጠለያ መስሪያ እና የእንስሳት ምግብነት ሰፊ ጠቀሜታ የሚሰጥ፣ የሚሊዮኖችን የምግብ ዋስትና የሚያረጋግጥ በመሆኑ ዝርያዎቹን ከመጥፋት ለመታደግ ብሎም የተመረጡ ዝርያዎችን የሚያጠቁ በሽታዎችን ለመለየትና በምርምር የተለየ በሽታ የመቋቋም አቅም ለመፍጠር እንደዚሁም ከመሬት ጥበት ጋር ተያይዞ የመጣው የከብቶች ቁጥር መመናመን ለእንሰት በጣም አስፈላጊ የሆነውን የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማሳጣቱን ታሳቢ በማድረግ ተተኪ የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት ጭምር ለመስራት ዩኒቨርሲቲው ከማህበሩ ጋር በትብብር ለመስራት በቂ ሃብት መመደቡን ዶ/ር ታፈሰ ገልፀዋል:: ከዚህ በፊት በአንጋፋው የግብርና ኮሌጅ ምሁራን ከ30 ዓመታት በላይ በእንሰት ላይ ብዙ የምርምር ውጤቶችን በማሳተም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ቀዳሚ ተቋም ቢሆንም ስራዎቹ በአንድ ላይ ተሰብስበው ወደ ፖሊሲ ለውጥና ትግበራ አለመለወጣቸውና በተበጣጠሰ መልኩ መሰራቱን ጠቁመው የዚህ ማዕከል ምስረታ ይሄንን ችግር በመቅረፍ ውጤታማና ቀጣይነት ያለው ሥራ ለመስራት ዕድል ይሰጣል ብለዋል፡፡ ም/ፕሬዝዳንቱ በሲዳማ ክልል ሁላ ወረዳ የሚቋቋመው የእንሰት ጥበቃ፣ ምርምርና ስልጠና ማዕከል ለመነሻ የሚሆን ከኖርዌይ መንግስት (ICP V Project) በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ የሚጀመር ቢሆንም የማዕከሉን ዘለቄታዊ ስራ ለማረጋገጥ ዩኒቨርሲቲው በራሱ መደበኛ በጀት የሚያስቀጥለው መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ስለ ሲዳማ ልማት ማህበርና ስለ ትብብሩ አጠር ያለ ገለጻ ያቀረቡት አቶ ግሩም ሽኒቴ የእንሰት ተክል የሲዳማ ክልልን ጨምሮ በሰፊው የደቡባዊ ኢትዮጵያ ክፍል ህዝቦች ዘንድ እንደዋና ሰብል የሚመረት እና በተለይም ሲዳማ የእንሰት መገኛ ምድር እንደመሆኑ ሰብሉን ከጥፋት ለመታደግና የህዝቡን ምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ የሲዳማ ልማት ማህበር ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር ይሄንን ወሳኝ የትብብር ፕሮጀክት ማስጀመሩ እጅግ ወሳኝ እንቅስቃሴ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አቶ ግሩም እንዳሉት የማህበሩ የድጋፍ ድርሻ በየጊዜው የሚያድግ ሆኖ አሁን ላይ አንድ አራተኛውን ወጪ የሚሸፍን ሲሆን ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሶስት አራተኛውን (75%) የፋይናንስ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል፡፡ የትብብር ፕሮጀክቱ በዝርያ ጥበቃ (landrace conservation)፣ አሳታፊ ምርምር (participatory research)፣ የወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ (youth employment and farmers associations)፣ እና የአቅም ግንባታ ሥራ (capacity building for community through training and knowledge sharing) በሚሉ አራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የተመሰረተ መሆኑ ተገልጽዋል፡፡
በፊርማ ስነ ሥርዓቱ ላይ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲና የግብርና ኮሌጅ ኃላፊዎችና ተመራማሪዎች፣ የሲዳማ ልማት ማህበር አመራሮች፣ የደቡባዊ ሲዳማ ዞን እና የሁላ ወረዳ አስተዳደሪዎች ተገኝተዋል፡፡
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት! | 4 799 |
| 11 | ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከሲዳማ ልማት ማህበር ጋር የእንሰት ሰብል ጥበቃ፣ ምርምር እና ስልጠና ማዕከል ምስረታ የትብብር ስምምነት ውል ተፈራረመ፡፡
ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ/ም
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከሲዳማ ልማት ማህበር ጋር በመተባበር በደቡባዊ ሲዳማ ዞን በሁላ ወረዳ ላይ የእንሰት ሰብል ጥበቃ፣ ምርምር እና ስልጠና ማዕከል ለማቋቋም ሐምሌ 20/2018 ዓ/ም የትብብር ስምምነት ውል ተፈራርሟል፡፡
በፊርማ ስነስርዓቱ ለይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የሲዳማ ልማት ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ወይንሸት መንገሻ እንደገለጹት የሲዳማ ልማት ማህበር የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ አኗኗር ለማሻሻል ላለፉት 30 በላይ ዓመታት በጥናት ሲሰራ መቆየቱን ገልጸው በሂደትም በጥናት በተለዩ ስድስት ዘርፎች ላይ የማህበረሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ያለ ማህበር ነው ብለዋል፡፡ ወ/ሮ ወይንሸት አክለውም እንሰት በሀገራችን ከ25 ሚልዮን በላይ ሕዝብ ለምግብነት ብቻ ሳይሆን ለሁለገብ አኗኗሩ የሚደገፍበት ሃገርበቀል ሰብል መሆኑን አንስተው ይሄንን ሁሉ ሰፊ ማህበረሰብ የተሸከመ ቢሆንም በሰብሉ ዙርያ በቂ ምርምር ተደርጎ ምርታማነትና ጤናማነቱን ለማረጋገጥ ተጨማሪ ሥራ ለመስራት ከአንጋፋው ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተሸለ አጋር ባለመኖሩ ከዩኒቨርሲቲው ጋር በትብብር ለመስራት ታቅዶ ወደ ስራ ለመግባት ጫፍ ላይ በመድረሳችን እጅግ ደስተኛ ነኝ ብለዋል፡፡
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ትብብር ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታፈሰ ማቲዎስ በበኩላቸው በእንሰት ሰብል ዙርያ ያለው ችግር ከዝርያው መመናመን አንስቶ ሰብሉ ላይ አሁን ከሚታየው የመጥፋት አደጋ ለመታደግ ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በላይ ቁልፍ ባለድርሻ አለ ብዬ አላምንም ብለዋል:: እንሰት ድርቅ በቀላሉ የማያጠቃው፣ ከስሩ ጀምሮ አንድም የተክሉ ክፍል ጥቅም ላይ የማይውል የሌለው | 5 295 |
| 12 | Career Path in Aerospace
Are you curious about: Aerospace career Path in Ethiopia opportunities and challenges or maybe Aerospace career Path in the U.S. opportunities and challenges?
If yes, then surely you don't want to miss this webinar!
Date: 30 July (Thursday), 2026; Time: 2:30 PM – 4:05 PM
Venue: Satchmo Center, US Embassy Addis Ababa
Webinar will be shared live at: Hawassa American Corner, Inside Hawassa University Agri Campus, the white building facing and Q&A session will be held live with the presenters
Google Maps: https://maps.app.goo.gl/EtyHrhUfSDLukHdc6
Register here:https://forms.gle/tvC2DPhKNSyTiQxs5 | 4 449 |
| 13 | Dear friends,
Greetings from American Spaces Hawassa located at Hawassa University College of Agriculture, the white building facing Lewi Hotel Piasa branch.
We are holding an exciting virtual session promoted at the post below.
Another exciting point is, our space is a wonderful place for reading, has free wifi and we have limited laptop computers for use in the space only for students who took training at our space and adults who have reasonable experience in using computers for academic use only.
While you may come and read some books at our corner for free, we need your National ID card (Fayda) or school ID to borrow laptops as we need to take good care for our equipment. Students who took training at our space may bring their ID cards but not must as they have taken basic training to use computers plus we have information regarding their schools …
Please visit us during office hours, join our telegram group (https://t.me/HawassaAmericanSpace) and attend our upcoming sessions.
As the Space may at times get busy with events, don't forget to check our telegram channel before you come or just get prepared to use your time at alternative places in case the place is busy with scheduled events.
You may also like to volunteer at our space and if you may do that please contact us regarding your expertise and what training you can give to your juniors / the community at large. Areas are not very specific, English language, computer / programing, life skills, entrepreneurships, health … just whatever that can be of service to our community and can be done in professional / structured way can be done.
Thank you for joining hands with American Space Hawassa and have a great day!
The Coordinators, | 4 541 |
| 14 | scientific writing, and the effective use of digital data collection tools is essential for producing high-quality research, winning competitive research grants, and increasing scientific publications. Dr. Shemelis encouraged participants to apply the knowledge and skills gained during the training in their teaching, research, and community engagement activities.
The trainees expressed their appreciation to the College and ReREd Project for organizing the timely training, noting that it enhanced their confidence and would significantly contribute to improving their research and publication activities.
Hawassa University
Ever to Excel! | 4 391 |
| 15 | Wondo Genet College of Forestry and Natural Resources conducs capacity-building training for Junior Academic Staff
*//*
July 27, 2026
Wondo Genet College of Forestry and Natural Resources at Hawassa University conducted a three-day capacity-building training for 22 junior academic staff members on research methods, scientific writing, and data collection tools with the objective of enhancing their knowledge and practical skills in conducting quality research and producing publishable scientific outputs.
The training was delivered by two senior academics from the college and was financially supported by the ReREd Project, reflecting the project's commitment to strengthening research and innovation capacity within the University.
Speaking at the opening session, the ReREd Project Coordinator, Dr. Shemelis Nigatu, emphasized that the training is both timely and strategic particularly in supporting junior academic staff as they embark on their research career. | 5 048 |
| 16 | አበባ ያላቸው ተክሎች መሆናቸውን ጠቁመው ችግኞቹ የሚተከሉበትን የአፈር ዓይነትና የወቅቱን ደረቅ የአየር ጸባይ ከግምት ዉስጥ በማስገባት ችግኞቹ እንዲጸድቁ ተገቢዉን ቀጣይነት ያለዉ እንክብካቤ ለማድረግ አስፈላጊዉ ዝግጅት የተደረገበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ የዩኒቨርሲቲዉን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጨምሮ፣ ዲኖች፣ ዳይሬክተሮች፣ ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ ት/ት ክፍል ኃላፊዎች፣ ቡድን መሪዎች፣ መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች እንዲሁም የካምፓሱ ፌደራል ፓሊስ አመራርና አባላት ተገኝተዉ ከ2ሺ በላይ ችግኞች መትከል ተችሏል፡፡
በቀጣይም በዩኒቨርሲቲዉ የተለያዩ ካምፓሶች ተመሳሳይ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሮች እንደሚካሄድ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት! | 5 984 |
| 17 | ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ/ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብርን በይፋ አስጀመረ::
*//*
ሐምሌ 18/2018 ዓ/ም
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለተከታታይ ዓመታት በየዓመቱ እየተካሄደ የሚገኘዉን ሀገርአቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ዛሬ ጠዋት "ተስፋን እንትከል!" በሚል መሪ ቃል በዋና ግቢ በይፋ አስጀመሯል፡፡
የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዚደንት ዶ/ር ችሮታዉ አየለ መርሃ-ግብሩን በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት እንደተናገሩት የአረንጓዴ አሻራ ምርሃግብር ዓላማ ከአካባቢ ጥበቃ፣ አየር ንብረት ለዉጥን ከመቆጣጠር እና የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ጋር ተያያዥነት ያለዉና በሳይንስ የተደገፈ ተግባር መሆኑን ጠቅሰዉ፣ ሁሉም የዩኒቨርሲቲዉ ማህበረሰብ አካላት በችግኝ ተከላዉና እንክብካቤ በንቃት መሳተፍ እደሚገባቸዉ ጥሪያቸዉን አስተላልፈዋል፡፡ ፕሬዚደንቱ ለመርሃ-ግብሩ አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችን በማዘጋጀትና በማስፈጸም የተሰጠዉን ተልዕኮ እየተወጣ ያለዉን በምርምርና ትብብር ም/ፕሬዝደንት ጽ/ቤት ሥር የሚገኘዉን የማህበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት እንዲሁም በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙትን የዩኒቨርሲቲዉን ማህበረሰብ አካላት አመስግነዋል፡፡
በዘንድሮዉ የአረንጓዴ አሻራ ማሳረፍ መርሃ-ግብር ስለሚተከሉ የችግኝ አይነቶችና ትክክለኛ የችግኝ ተከላ ሂደቱን አስመልከቶ ሙያዊ ገለጻ የሰጡት የማህበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ማርቆስ ፍስሃ ለተከላ የተዘጋጁት የዛፍ ችግኞች ሀገር በቀልና ዘርፈ-ብዙ ግልጋሎቶችን እንዲሰጡ ታስቦ የተዘጋጁ እንደሆኑ ተናግረዋል:: አቶ ማርቆስ አክለውም ችግኞቹ የተመረጡበት አንዱ መስፈርት በዋናው ግቢ ለሚደረገው የማር ምርት ምርምር ጣቢያ የሚጠቅሙ ለማር ምርት በጣም ተፈላጊ የሆኑት የብሳና፣ ዋንዛ፣ ገተሜ እና ሌላ ከፍተኛ ጥራት ያለው ማር ለማምረት የሚጠቅም | 6 519 |
| 18 | የድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT Exam) የምዝገባ ጊዜን ስለማሳወቅ
*//*
ሐምሌ 18/2018 ዓ/ም
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 ዓ.ም የሚሰጠውን መደበኛ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና /National Graduate Admission Test/ ለመስጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ፈተናውን ለመውሰድ እየተጠባበቃችሁ ላላችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት አመልካቾች በሙሉ ምዝገባ የሚካሄደው ከሀምሌ 15 – 25/2018 ዓ.ም ብቻ መሆኑን አውቃችሁ ከታች በተቀመጠው የመመዝገቢያ ሊንክ ገብታችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ለፈተናውም አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን። የፈተና መስጫ ጊዜው ወደፊት የሚገለጽ ይሆናል፡፡
የመመዝገቢያ ሊንክ፡- https://ngat.ethernet.edu.et
ማሳሰቢያ:-
ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ እንደ ቅድመ ሁኔታ መቀመጡን አውቃችሁ ከወዲሁ እንድትዘጋጁ።
የአገልግሎት ክፍያ 750 ብር (ሰባት መቶ ሀምሳ ብር) መሆኑን አውቃችሁ በቴሌ ብር በኩል በምዝገባው ወቅት የሚፈጸም ይሆናል።
ምዝገባው የሚከናወነው በሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ሲሆን የፈተና ጣቢያውን በሚመለከት ግን ከምዝገባ በኋላ የተመዝጋቢ ቁጥሩ ታይቶ በስታንዳርዱ መሰረት የሚወሰን ይሆናል፡፡
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት | 7 200 |
| 19 | የዘንድሮውን መርሃ-ግብር በይፋ ያስጀመሩት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር ችሮታዉ አየለ ትብብር ለሰዉ ልጆች በተፈጥሮ የተቸረ ስጦታ መሆኑን አዉስተዉ፣ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ጋር ያለዉን ሁለንተናዊ ትብብር አጠናክሮ እደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ ለዚህም የዩኒቨርሲቲዉ ማህበረሰብ አካላት ለማዕከሉ ዉጥኖች እንደ ዜጋና እንደ ማሕበረሰብ አካልየሚችሉትን ሁሉ ድጋፍ እዲያደርጉ ጥሪ አስተላልፈዋል::
በመርሃግብሩ ላይ ስለ ኩላሊት ህመም ባህርያት፣ አጋላጭ ሁኔታዎች፣ የመከላከያ መንገዶች እና የህክምናውን ባህሪ በተመለከተ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ህ/ጤ/ሳ/ኮ የኩላሊት ህክምና ሰብ-ስፔሻሊስት ሐኪም ዶ/ር ትዕግስት ተስፋዬ ሰፊ ሙያዊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን የኩላሊት እጥበት ተጠቃሚዎች ለቲቢ በሽታ ያላቸውን ተጋላጭነት ለመቀነስ ስለሚሰጠው ሕክምና ደግሞ በኮሌጁ የሳምባ ሰብ-ስፔሻሊስት ሐኪም የሆኑት ዶ/ር ታሪኩ ተስፋዬ ለታዳሚዎች ሰፊ ማብራሪያ እና ሙያዊ ምክር ሰጥተዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው ለሜሪ ጆይ የኩላሊት እጥበት ማዕከል ለ80 ታካሚዎች ለሶስት ወር የሚሆን የቲቢ መከላከያ መድሃኒት የለገሰ ሲሆን 40 የሚሆኑ የኮሌጁ ሰራተኞች ደግሞ በክረምቱ የበጎ ፈቃደኝነት በነፃ አገልግሎት ለመስጠት ቃል እንደገቡ ተገልፅዋል:: ከዚህ በተጨማሪ የኮሌጁና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አካላት በበጎ ፍቃደኛነት በነቂስ እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል::
በመድረኩ ቁልፍ ንግግር ያደረጉት የሀዋሳ ከተማ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ይርዳቸዉ አናቶ በበኩላቸው ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በማህበረሰቡ ዘንድ እያከናወናቸዉ ያሉትን መደበኛ የሆኑ እና የክረምት በጎ ፈቃድ ሰፋፊ የህክምና አገልግሎቶችን አድንቀዉ በዘርፉ መምሪያቸዉ በትብብር ለመስራት ያለዉን ቁርጠኝነት ገልጸዋል፡፡
የሜሪጆይ ኢትዮጵያ መስራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ ሲ/ር ዘቢደር ዘዉዴ በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲና የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጁ ለሜሪጆይ ኩላሊት እጥበት ማዕከል እያበረከቱት ያለዉን ሁለንተናዊ ድጋፍ አድንቀዉ፣ የኩላሊት በሽታ በሀገራችን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋና በርካታ ዜጎችና ቤተሰቦችን ለከፋ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እያዳረገ በመሆኑ ልዩ ትኩረት ሊሰጠዉና በትብብር ሊሰራ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
በመርሃግብሩ የተገኙ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አካላት የደም ግፊት፣ ስኳር፣ ኩላሊትና ሳምባ ምርመራ እና ደም ልገሳ አከናዉነዋል:: የማዕከሉ አባል ለመሆንም ተመዝግበዋል፡፡
በ2018 ዓ/ም የክረምት በጎ ፈቃድ ህክምና እና ጤና አገልግሎት ከ129 ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች በተመረጡ የጤና ጉዳዮች ላይ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ለመፍጠር፣ ነጻ የምርመራ እና ህክምና አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት መደረጉን በመርሃ-ግብሩ ተገልጿል፡፡
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት! | 5 885 |
| 20 | የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ-ግብር በሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ የኩላሊት እጥበት ማዕከል አስጀመረ::
*//*
ሐምሌ 17/2018 ዓ/ም
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ (ህ/ጤ/ሳ/ኮ) "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የሚከናወነውን የ2018 ዓ/ም ሃገር አቀፍ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር የዩኒቨርሲቲዉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ኃላፊ እና ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች በተገኙበት በሀዋሳ ከተማ በሚገኘዉ ሜሪጆይ የኩላሊት እጥበት ማዕከል አካሂዷል፡፡
"የላቀ የኩላሊት ሕክምና ለጤናማ ማህበረሰብ!" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው መርሃግብር ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የህ/ጤ/ሳ/ኮ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ፍጹም ወ/ገብርኤል ኮሌጁ ሀገራዊ ተልዕኮዉን በመቀበል በየዓመቱ መሰል የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን ለአካባቢዉ ማህበረሰብ በስፋት እንደሚሰጥ ጠቅሰዉ፣ በ2017 ዓ/ም በተከናወነዉ መሰል ስራ ኮሌጁ በሀገር አቀፍ ደረጃ ካሉ የዩኒቨርሲቲ ሆስፒታሎች መካከል ከቀዳሚዎቹ ሶስት ሆስፒታሎች አንዱ በመሆን ዕዉቅና እና ሽልማት ማግኘቱን ተናግረዋል፡፡ ዳይሬክተሯ ለዚህ ስኬት የጀርባ አጥንት የሆኑትን የኮሌጁን ሀኪሞች፣ የጤና ባለሙያዎች፣ አመራሮች፣ የድጋፍ ሰራተኞች፣ አጋር ተቋማትና ሁሉንም ባለ ድርሻ አካላት አመስግነዋል፡፡ ዶ/ር ፍፁም በንግግራቸው የኩላሊት ህመም በሕክምናው ዓለም 'ድምፅ አልባው ገዳይ' የሚል መታወቂያ እንዳለው ጠቅሰው አብዛኛው ታካሚ ህመሙ እንዳለበት ሳያውቁ ለከፍተኛ ጉዳትና የሕይወት ማጣት እንደሚዳረጉ በመረጋገጡ አገልግሎቱ ከግንዛቤ ማስጨበጫ ጀምሮ፣ ምርመራና ልየታ እንዲሁም ነፃ ህክምና መስጠትን እንደሚያካትት ገልፀዋል:: | 6 019 |
