fa
Feedback
Hawassa University

Hawassa University

رفتن به کانال در Telegram

One of the top ranking first generation Universities in Ethiopia.

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Hawassa University

کانال Hawassa University (@hucommunicationsoffice) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 37 472 مشترک است و جایگاه 4 977 را در دسته آموزش و رتبه 936 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 37 472 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 16 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 1 997 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 56 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 27.35% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 12.33% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 10 144 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 4 571 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
One of the top ranking first generation Universities in Ethiopia.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 17 سپتامبر, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کرده‌اند.

37 472
مشترکین
+5624 ساعت
+3747 روز
+1 99730 روز
آرشیو پست ها
የትምህርትና ስነ-ባህሪ ሳይንስ ኮሌጅ ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ለተወጣጡ ርዕሳነ መምህራን፣ ሱፐርቫይዘሮችና ደጋፊ የትምህርት ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና መርሃ-ግብር አስጀመረ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የትምህርትና ስነ-ባህሪ ሳይንስ ኮሌጅ ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ለተወጣጡ ርዕሳነ መምህራን፣ ሱፐርቫይዘሮችና ደጋፊ የትምህርት ባለሙያዎች የሚሰጥ ለ3 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የአቅም ግንባታ ስልጠና በቀን 07/01/2019 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲዉ ዋና ግቢ አስጀምሯል፡፡ የዩኒቨርሲቲዉ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር እንጂነር ፍሰሃ ገታቸዉ በስልጠናዉ መክፈቻ ስነ-ስርዓት ላይ ተገኝተዉ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ እና ከተማ አስተዳድሩ በብዙ ጉዳዮች ላይ ለረጅም ዘመናት አብረዉ ሲሰሩ መቆየታቸዉን አስታዉሰዉ፣ የትምህርት ጉዳይ ትልቅ እና ቅድሚያ የሚሰጠዉ ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል:: ም/ፕሬዝዳንቱ ስለ ትምህርት አይተኬ ሚና ሲናገሩ ጠንካራ ህገራት የተመሰርቱት በጠንካራ የትምህርት ስርዓት በመገንባት ነዉ ብልዋል:: ዶ/ር እንጅነር ፍስሃ አክለዉም ትምህርት የህይወት ዘመን ጉዳይ በመሆኑ በስራ ላይ ያሉ ባለሙያዎችም ሆኑ መሪዎች ራሳቸዉን ዘወትር ለትምህርትና ስልጠና ክፍት ማድረግ አለባቸዉ ብለዋል:: የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ት/መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ብርሃኑ ደሳለኝ በበኩላቸዉ መምሪያዉ ክሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር ብዙ ስራዎችን እየሰራ እንዳለ ጠቅስዉ፣ አጠገባችን ላይ በሀገር አቀፍ ደረጃ የትምህርት ልህቀት ማዕክል የሆነዉ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ መኖሩ ለከተማዉ የትምህርት ማህበረሰብ ልዩ ዕድል መሆኑን ተናግረዋል:: ዩኒቨርሲቲዉ እስካሁን ለከተማ አስተዳደሩ ት/ት ዘርፍ እያደረገ ያለዉን ሁለንተናዊ ድጋፍ አድንቀዉ በቀጣይ በመምህራን ልማትና ተያያዥ ጉዳዮች ተጨማሪ ስራዎችን ለመስራት ከዩነቨርሲቲዉ ገር እየተነጋገሩ እንደሆነ ጠቁመዋል:: የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ሳሙኤል አሰፋ ለስልጠናዉ ተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያስተላለፉ ሲሆን ኮልጁ በህገር አቀፍ ደረጃ ደረጃ ብዙ አብነት ሊሆኑ የሚችሉ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዉ፣ በሲዳማ ከልል የሚስተዋለዉን የትምህርት ጥራት ችግርና የተማሪዎች በሀገር አቀፍ ፈተናዎች ላይ እየተመዘገበ የሚገኘዉን ዝቅተኛ ዉጤት ለማሻሻል የሚደረገዉን ጥረት ለመደገፍ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ለመስራት እቅድ እንዳለዉ ተናግረዋል:: በዚህ ዙር ለት/ት አመራሩና ደጋፊ ባለሙያዎች የተዘጋጀዉ ስልጠና የማስተማር መሪነት፣ ብቃት መር ስርዓተ ትምህርት እና ክትትልና ግምገማ ላይ የሚያተኩር እንደሆነ ዶ/ር ሳሙኤል ጠቁመዋል:: የስልጠናዉን አስፈላጊነትና ከስልጠናዉ የሚጠበቀዉን ዉጤት በተመለከተ የኮሌጁ ተ/ዲን እና ስነ-ባህሪ ሳይንስ ረ/ፕሮፌሰር ዶ/ር ሀብተማሪያም ካሳ ሳይንሳዊ ገለጻ ያቀረቡ ሲሆን፣ ለለዉጥ እና ዕድገት ወሳኙ ነገር የአዕምሯችን እንደሆነ ገልጸዉ፣ የዓለማችንን ታሪክ የቀየሩ ግለሰቦች ትላልቅ የሚባሉ ፈጠራዎችን እዉን ማድረግ የቻሉት አእምሯቸዉን አሰርተዉና ትልቅ ህልምና ቁርጠኝነት ስለነበራቸዉ እንደሆነ ተናግረዋል:: የትምህርት፣ ስልጠና እና ዕዉቀት ግቡም ማወቅ ብቻ ሳይሆን በገሃዱ ዓለም ላይ በተግባር የሚተገበር ድርጊት እንደሆነ አስረድተዋል:: በስልጠናዉ 256 ሰልጣኛች እየተሳተፉ የሚገኙ ሲሆን በተዘጋጁት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ከኮሌጁ በተወጣዉ የዘርፉ ምሁራን ስልጠናዉ በተለያዩ ክፍሎች እንደሚሰጥ ለማወቅ ተችሏል::

photo content
+8

Wondo Genet College of Forestry and Natural Resources Successfully Hosts an International Dialogue ,"African Fire Dialogue" ***//*** September 17, 2026 The second day of "African Fire Dialogue: From Balem to Addis Ababa — Building an African Agenda for Fire-Resilient Landscapes," was conducted at Wondo Genet College of Forestry and Natural Resources (WGCFNR) on 16 September, 2026. This high-level multi-sectorial dialogue, which was officially began a day before this event continued today with important and engaging activities. The first activity of the event included visit to the forest and areas of wild fire-prone sites in WGCFNR compound. The trip aimed at looking at the infrastructures available on the ground in line with fire management, including the forest roads that serve to access the forests, the fire breaks that are used to suppress the transmission of fire, and the towers that are used to detect fire incidence. After the visit, a discussions on the causes, impacts, and the strategies the college put in place to manage fire along with experience sharing by participants from African countries including Uganda, Tanzania, DRC, Nigeria and other countries and also Focus Group Discussions with communities from surrounding Kebeles were conducted one after another. The main points of discussions with the communities were on causes, impacts and indigenous fire management activities practiced by the community. In the afternoon, there was a general discussion and reflection sessions held at SIDA Hall of the College. The session was chaired by Mr. Joost van Montfort, Dr Motuma Tolera, and Dr Teshale Woldeamanuel. Participants reflected on the activities and events they participated over the past two days. While some of the participants appreciated the College for its commitment in forest management and community engagement, others suggested ways of scaling up best practices and strong collaboration at local and international level. The initiative, according to organizers, aims to build an African Agenda thorough creating space to learn from community experiences and identify what is needed to strengthen locally led prevention, which connects landscape-level fire management with national climate commitments, restoration agendas and regional forest and climate platforms. The event brought together participants from various African, South American, European and Asian countries and representatives of international organization and government agencies.

photo content
+7

የሐዘን መግለጫ *//* መስከረም 07/2019 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሜዲካል ላቦራቶሪ ክፍል ባልደረባ በነበሩት ወ/ሮ ጽዮን ማቴ
የሐዘን መግለጫ *//* መስከረም 07/2019 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሜዲካል ላቦራቶሪ ክፍል ባልደረባ በነበሩት ወ/ሮ ጽዮን ማቴዎስ ድንገተኛ ሕልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቻቸው: ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና የሥራ ባልደረቦቻቸው ልባዊ መጽናናትን እንመኛለን። ነብስ ይማር! ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ

photo content
+1

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዓመታዊ የመምህራን ጠቅላላ ጉባኤ ተካሄደ። ********\\******** መስከረም 6/2019 ዓ.ም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዓመታዊ የመምህራን ጠቅላላ ጉባዔ በዩኒቨርሲቲው ሥር በሚገኙ 7ቱም ግቢዎች የሚያስተምሩ መምህራን በተገኙበት መስከረም 6/2019 ዓ.ም በዋና ግቢ አፍሪካ ህብረት አዳራሽ በድምቀት ተካሂዷል። በጉባዔው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ፣ ዩኒቨርሲቲዉ በ2018 በጀት ዓመት በአካዳሚክ፣ በምርምርና ትብብር እንዲሁም በአስተዳደርና ልማት ዘርፎች ያከናወናቸው ተግባራትና የተመዘገቡት ዉጤቶች የሁሉም የዩኒቨርሲቲዉ ማህበረሰብ፣ ባለ ድርሻና አጋር አካለት ተሳትፎ ዕዉን የሆነ በመሆኑ አስተዋጽኦ ያደረጉ አካላትን በሙሉ አመስግነዋል። ፕሬዝዳንቱ ዩኒቨርሲቲው በ2019 ዓ.ም በየዘርፉ ለማሳካት ያቀዳቸውን ዐበይት ግቦችና አቅጣጫዎች በማብራራት መምህራኑ የላቀ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስበዋል። መልካም አስተዳደርን ማስፈንና ተጠያቅነትን ማረጋገጥ ላይ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረዉ እንደሚቀጥል ተናግረዉ፣ መምህራን ለሙያቸዉ፣ ተማሪዎቻቸዉን ለዩኒቨርሲቲዉ ማህበረሰብ በአጠቃላይ ታማኝ በመሆን አርአያ ሊሆኑ እንደሚገባ አሳስበዋል:: የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኢንጂነር ፍስሀ ጌታቸው በ2018 ዓ.ም የአካዳሚክ ካሌንደሩን በታቀደለት ጊዜ አስጀምሮ ለማጠናቀቅ የተደረገውን ጥረት እና ስኬት፣ የትምህርት ክፍለ ጊዜ ብክነትን ለመቀነስ የተሰራውን ስራ፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ ትምህርት ለመስጠት የመምህራንና ተማሪዎች አቅም መገንባት ላይ፣ አስፈላጊ የትምህርት ግብዓቶችን ማሟላት፣ በሀገር አቀፍ መዉጫ ፈተና የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ላይ የታዩ መሻሻሎችን፣ በት/ት ዘመኑ 73 የ3ኛ ድግሪ ተማሪዎችን ማስመረቅ መቻሉን እንዲሁም 9 መምህራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ማግኘታቸዉን አንስተዋል:: በ2019 ዓ.ም የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ፣ የድህረ-ምረቃ ተማሪዎችን ቁጥር ለመጨመር፣ ለመምህራን አስፈላጊ የት/ት ግብዓቶችን በየደረጃዉ ለማቅረብና የተማሪዎችን ዉጤታማነትን ይበልጥ ለማሻሻል ይሰራል ብለዋል:: የምርምርና ትብብር ም/ፕሬዚደንት ዶ/ር ታፈሰ ማቴዎስ በበኩላቸዉ ባቀረቡት ገለጻ፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሁሉም ዘርፍ ከፍተኛ ዉጤት መመዝገቡን ጠቅሰዉ፣ የምርምር በጀት በፊት ከነበረዉ ትርጉም ባለዉ መልኩ እንዲጨምር መደረጉን፣ በምርምር ስራ ላይ የሚሳተፉ መምህራን ቁጥር ከፍ ማለቱን፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ በመንግስት እና በትብብር የሚተገበሩ የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ፕሮጀክቶች መከናወናቸዉን፣ 1ሺ የሚሆኑ የምርምሮ ጽሁፎች በዓለም አቀፍ የምርምር መጽሄቶች መታተማቸዉን፣ የዩኒቨርሲቲዉንና የሀገሪቱን በጎ ገጽታ መገንባትና ለዓለም አቀፍ ትብብር በር የከፈቱ ግዙፍ ዓለምአቀፍ ጉባዔዎች መካሄዳቸዉን፣ ሀገራዊና ወቅታዊ አጀንዳዎችን የዳሰሱ የፓናል ዉይይቶችና ፖሊሲ ገለጻዎች መካሄዳቸዉን እንዲሁም 3 አዳዲስ የምርምር ማዕከላት መመስረታቸዉን አንስተዉ፣ በ2019 በጀት ዓመትም መሰል ስራዎች ተጠናክረዉ እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል:: የዩኒቨርሲቲዉን የአስተዳደርና ልማት ዘርፍ ስራ እንቅስቃሴን በተመለከተ የዘርፉ ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ጂሎ ገለጻ ያቀረቡ ሲሆን፣ የዘርፉን አሠራር በሕግና በሥርዓት እንዲሁም በቴክኖሎጂ በመታገዝ ለመምራት የተከናወኑ ተግባራትን አንስተዉ፣ የሰዉ ሃብት መረጃ፣ ፋይናንስ፣ ግዥና ንብረት አስተዳደር ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ዲጂታል መደረጉን፣ ሰፋፊ የግንባታ ፕሮጀክቶች በተለያዩ ካምፓሶች መከናወናቸዉን ጠቅሰዋል:: በተያዘዉ በጀት ዓመት መማር-ማስተማሩን፣ ምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ስራዎችን የሚያግዙ ግብዓቶችን የማሟላት፣ በሂደት ላይ ያሉ ግንባታዎችን ለማጠናቀቅ፣ ከግዥ ጋር የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ፣ በጀት አጠቃቀምን በእጅጉ ከፍ ለማድረግ፣ የመምህራን መኖሪያ ቤት ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት እና የተማሪዎች አገልግሎትን ለማሻሻል ሰፋፊ ዕቅዶች መያዛቸዉን ተናግግዋል:: ከገለጻዎቹ በማስከተል በነበረዉ የዉይይት ክፍለ-ጊዜ መምህራን ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን ያነሱ ሲሆን፣ ከም/ፕሬዚደንቶቹ አስፈላጊው ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል። በመጨረሻም የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው የማጠቃለያ ሀሳብና የሥራ መመሪያ ስጥተዉ መድረኩ ተጠናቋል::

photo content
+8

photo content
+9

Wondo Genet College of Forestry and Natural Resources Co-Organizes International Dialogue on Wildfire Management ***//*** September 16, 2026  Hawassa University’s Wondo Genet College of Forestry and Natural Resources (WGCFNR), in collaboration with international partners, hosted a high-level multi-sectorial dialogue on September 15, 2026. Held under the theme "African Fire Dialogue: From Balem to Addis Ababa — Building an African Agenda for Fire-Resilient Landscapes," the event gathered experts, development partners, government representatives, researchers, and community leaders. Officially opening the event, Dr. Chirotaw Ayele, President of Hawassa University, emphasized that protecting forests from wildfires is critical to achieving Ethiopia’s Green Legacy Initiative and related national development goals. He reaffirmed the university's commitment to strategic partnerships that advance both national targets and the Sustainable Development Goals (SDGs). Welcoming delegates, WGCFNR Dean Dr. Teshale Woldeamanuel highlighted the dialogue as a collaborative platform to bridge local knowledge with global expertise. Dr. Teshale also presented the college's 50-year legacy as a premier research and academic institution specializing in forestry, land management, and wild life, outlining its vision to serve as a regional center of excellence. In his keynote address, Mr. Joost van Montfort, Director at Tropenbos International, shared global lessons on community-led fire management. He stressed the importance of recognizing indigenous community efforts and integrating them into evidence-based policy decisions. Additionally, Kefyalew Sahle, a GISc lecturer at WGCFNR, delivered a data-driven presentation on Ethiopia’s wildfire trends, local best practices, and the college's ongoing contributions to wildfire mitigation. The multi-day dialogue continues tomorrow with field visits and interactive workshop sessions.

To: All Students of Hawassa University (Regular, Evening, Weekend and Certificate Programs) This is to inform you that the registration for the first semester of 2019 E.C. academic year will be conducted as outlined below: 1.    First Degree Regular Program and all Postgraduate Students (Regular and Weekend) - Meskerem 21–22, 2019 E.C. (Oct 01-02, 2026bGC) 2.    First Degree Evening and Weekend Students - Meskerem 22–23, 2019 E.C. (Oct 02-03, 2026 GC) Reminders: a) Registration for second-year regular first degree (UG) program students will take place at the campus to which they are assigned. b) Registration will not be conducted outside the given dates. c) Class will start on Mesekerm 25/2019 E.C (Oct 5, 2026 GC).   Office of the Main Registrar, Hawassa University Ever to Excel!

ማስታወቂያ መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ/ም ለሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የመደበኛ፣ የማታ እና የእረፍት ቀናት ፕሮግራም ነባር ተማሪዎች በሙሉ፡- የ2019 ዓ.ም የመጀመርያ ሴሚስተር ምዝገባ ከዚህ በታች በተገለ
ማስታወቂያ መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ/ም ለሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የመደበኛ፣ የማታ እና የእረፍት ቀናት ፕሮግራም ነባር ተማሪዎች በሙሉ፡- የ2019 ዓ.ም የመጀመርያ ሴሚስተር ምዝገባ ከዚህ በታች በተገለጸው መሰረት የሚከናወን መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ 1. የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ፕሮግራም እና ሁሉም የድህረ ምረቃ ተማሪዎች (ማለትም መደበኛ እና የእረፍት ቀናት) - ከመስከረም 21-22 ቀን 2019 ዓ.ም 2. የማታና የእረፍት ቀናት የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች - ከመስከረም 22-23 /2019 ዓ.ም ማሳሰብያ፡- (ሀ) የ2ኛ ዓመት መደበኛ ፕሮግራም ተማሪዎች ምዝገባ የሚከናወነው በየተመደባችሁበት ካምፓስ ይሆናል። (ለ) ከተጠቀሰው ቀን ውጭ ምዝገባ የማይካሄድ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡ (ሐ) ትምህርት መስከረም 25/2019 ዓ.ም የሚጀመር ይሆናል። ዋናው ሬጅስትራር ጽ/ቤት ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

Greetings and Happy New Year dear all families of Hawassa American Corner! We are pleased to share with you a special undergr
Greetings and Happy New Year dear all families of Hawassa American Corner! We are pleased to share with you a special undergraduate information session by representatives from Dartmouth College, the University of Pennsylvania, Vanderbilt University, and Yale University – a virtual session at Hawassa American Corner on September 16 / 2026 starting from 3:00–5:00 PM to be livestreamed right from International Community School (ICS) of Addis Ababa. All interested may benefit from this orientation session but special focus is on Grade 11 and Grade 12 students and families who might make use of the information right away. Please register at this link - https://forms.gle/DgdXyCuu8yzWQu1PA and let us meet at our corner located at the ground floor of Hawassa University, College of Agriculture the white building facing Hawassa Lewi Hotel Piasa Branch. Please join HAC @ https://t.me/HawassaAmericanSpace Once again Happy New Year 2019!

በተጨማሪም 250 ተማሪዎች በSTEM ማዕከል ስልጠና ያገኙ ሲሆን፣ 43,965 ችግኞች ተተክለዋል፤ በትራፊክ አደጋ፣ በአደንዛዥ ዕፅ እና በሕገ-ወጥ ሰዎች ዝውውር ዙሪያም የውይይት መድረኮች ተዘጋጅተዋል። በትብብርና ስትራቴጂያዊ አጋርነት ዘርፍ ዩኒቨርሲቲው በጠቅላላ በጀታቸው 1.2 ቢሊዮን ብር የሆኑ 134 የትብብር ፕሮጀክቶች የነበሩት ሲሆን፣ ከእነዚህ መካከል 32ቱ በበጀት ዓመቱ የተገኙ ናቸው። በዓመቱ 25 ሚሊዮን ብር ከአስተዳደራዊ ወጪ (Overhead) የተሰበሰበ ሲሆን፣ ለ6 ፕሮጀክት አምጪዎች እውቅና ተሰጥቷል፤ 70 መምህራንም የትምህርት ዕድል አግኝተዋል። ጽሕፈት ቤታችን ለእነዚህ ስኬቶች አስተዋጽኦ ላደረጉ ለዩኒቨርሲቲያችን መምህራን፣ የአስተዳደር ሰራተኞች፣ የጤና ባለሙያዎች፣ ተማሪዎች፣ ለአካባቢው ህብረተሰብ፣ ለአጋሮቻችን እንዲሁም በፌደራልና በሲዳማ ክልል ለሚገኙ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች የላቀ ምስጋና ያቀርባል። ከ2019 ዓ.ም ጀምሮ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት የሚሸጋገር በመሆኑ የምርምርና ቴክኖሎጂ ፈጠራ አቅምን በማሳደግ፣ ችግር ፈቺ ምርምሮችን በማካሄድ፣ ኢንተርፕረነርሺፕንና ቴክኖሎጂ ማበልጸግን በማጠናከር፣ የማህበረሰብ ጉድኝትን፣ የዩኒቨርሲቲ-ኢንዱስትሪ ትስስርን እንዲሁም ስትራቴጂያዊ አጋርነትና ዓለም አቀፋዊነትን በማሳደግ በትኩረት ይሰራል፡፡ ለመላዉ የዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የደስታ እና የስኬት እንዲሆንላችሁ ጽ/ቤችን ይመኛል! ታፈሰ ማቴዎስ ካሮ (ዶ/ር) የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ትብብር ም/ፕሬዚዳንት ጳጉሜ 5/2018 ዓ.ም ሀዋሳ

የምርምርና ትብብር ም/ፕሬዚዳንት የአዲስ ዓመት መልካም ምኞት መግለጫ *** እንኳን ለ2019 አዲሱ ዓመት እና ለሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 50ኛ ዓመት እንኳን በሰላም አደረሳችሁ! የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምር
የምርምርና ትብብር ም/ፕሬዚዳንት የአዲስ ዓመት መልካም ምኞት መግለጫ *** እንኳን ለ2019 አዲሱ ዓመት እና ለሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 50ኛ ዓመት እንኳን በሰላም አደረሳችሁ! የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት በ2018 የትምህርት ዘመን በርካታ ስራዎችን በማከናወን አመርቂ ውጤቶችን አሳክቷል። በበጀት ዓመቱ በ93.34 ሚሊዮን ብር ወጪ 244 የምርምር ፕሮጀክቶች የተከናወኑ ሲሆን፣ 5 የዩኒቨርሲቲው የምርምር ጆርናሎች ሀገር አቀፍ እውቅና አግኝተዋል። በተጨማሪም 968 የምርምር ውጤቶች እውቅና ባላቸው ጆርናሎች የታተሙ ሲሆን፣ 25 የፖሊሲ ገለጻዎች ተዘጋጅተዋል። 22ኛው ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ጥናት ጉባኤ እና 7 ሀገር አቀፍ ኮንፈረንሶች በተሳካ ሁኔታ የተካሄዱ ሲሆን፣ ዓለም አቀፍ እውቅና ባላቸው ጆርናሎች ላሳተሙ 255 ተመራማሪዎች 2.6 ሚሊዮን ብር የሽልማት ክፍያ ተፈጽሟል። በአገራዊ ምርጫ፣ በባህር በር፣ በአገር በቀል እውቀት እንዲሁም በኮሪደርና ወንዝ ዳርቻ ልማቶች ዙሪያ 4 የፓናል ውይይቶች ተካሂደዋል፤ 3 አዳዲስ የምርምር ማዕከላትም ተመስርተዋል። በተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ በ3.5 ሚሊዮን ብር 24 የቴክኖሎጂ ፈጠራ ፕሮጀክቶች ተከናውነው 5 የፓተንት መብቶች ሲገኙ፣ 6 ስታርት-አፖች የንግድ ፈቃድ አውጥተው ወደ ሥራ ገብተዋል፤ ከልዩ ልዩ ተቋማት ጋርም 52 ስምምነቶች ተፈርመዋል። በማህበረሰብ ጉድኝት በ20.5 ሚሊዮን ብር 33,786 የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ያደረጉ 23 ፕሮጀክቶች የተከናወኑ ሲሆን፣ ለ9 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የስልጠና፣ የመጻሕፍት ድጋፍና የትምህርት ቤት መመሪያ ክፍሎች ግንባታ ተካሂዷል።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ም/ፕሬዝዳንት የአዲስ ዓመት መልካም ምኞት መግለጫ ጳጉሜ 5/2018 ዓ.ም *//* ለመላው የዩኒቨርሲቲውያችን ማህበረሰብ እንዲሁም የክልላችንና የሀገራችን ህዝቦ
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ም/ፕሬዝዳንት የአዲስ ዓመት መልካም ምኞት መግለጫ ጳጉሜ 5/2018 ዓ.ም *//* ለመላው የዩኒቨርሲቲውያችን ማህበረሰብ እንዲሁም የክልላችንና የሀገራችን ህዝቦች ሁሉ እንኳን ለ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ/ አደረሰን፡፡ አዲሱ ዓመት የሰላም የጤና የፍቅርና የብልጽግና እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለሁ፡፡ ዩኒቨርሲቲያችን ባሳለፍነው 2018 በጀት ዓመት በርካታ የአስተዳደር፣ የተማሪዎች አገልግሎት የመሠረተ ልማት እና የዲጅታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ሥራዎችን በማከናወን ስኬታማ የትምህርት ዘመን አሳልፏል፡፡ የግዥ፣ የፋይናንስ፣ የንብረት እና የሰው ሀብት አስተዳደር፣ የተማሪዎች አገልግሎት አሰጣጥ፣ የትምህርት ግብአቶችን የማሟላት፣ የግንባታ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ፣ የኦዲት ውጤትም ከነቀፌታ የፀዳ እንዲሆን ዉጤታማ ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ በአጠቃላይ ዩኒቨርሲቲያችን በ2018 ዓ.ም በርካታ የለውጥ ሥራዎችን ያከናወነ ሲሆን ለ2019 በጀት ዓመት ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን የውስጥ ሥራዎችን አጠናቆ የመንግሥትን ፈቃድ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል፡፡ ዩኒቨርሲቲያችን ከተመሠረተ 50ኛውን ዓመት የወርቅ እዩቤልዩ ክብረ በአል በ2019 ዓ.ም በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ለማክበር እየሠራ ይገኛል፡፡ በ2018 በጀት ዓመት ላስመዘገብነው ውጤት አስተዋጽኦ ያደረጋችሁ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና በአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጭ ያላችሁ አጋሮቻችን ከልብ እናመሰግናለን፡፡ በ2019 ዓ.ም ለሚከናወኑ የለውጥ ሥራዎች ከጐናችን እንድትቆሙ ጥሪዬን እያቀረብኩ በድጋሚ መልካም አዲስ ዓመት እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ፡፡ አመሰግናለሁ! ዶ/ር ሳሙኤል ጂሎ ዲራ የአስተዳደርና ልማት ም/ፕሬዝዳንት

I am confident that, together with a shared vision and commitment, we can achieve even greater results in the coming academic year. I wish you and your families a joyful New Year and a year filled with success, peace, good health, and prosperity. Happy Ethiopian New Year 2019! Best regards, Dr. Eng. Fisiha Getachew Academic Vice President, Hawassa University

Dear Colleagues, As we celebrate the Ethiopian New Year 2019, I would like to extend my warmest wishes to the entire Universi
Dear Colleagues, As we celebrate the Ethiopian New Year 2019, I would like to extend my warmest wishes to the entire University community for a happy, peaceful, healthy, and prosperous New Year. Looking back, we can take pride in the progress and accomplishments we achieved together during the past academic year. Through our collective commitment and hard work, we successfully carried out many important academic, and institutional activities. These achievements are a reflection of the dedication and contribution of each member of our academic staff and the University community. As we begin the new academic year, let us build on these achievements. The year ahead also brings new responsibilities, opportunities, and challenges. Let us renew our commitment to excellence, strengthen our teamwork, and work with greater determination and sense of responsibility to accomplish more. In particular, let us continue to enhance quality of education and contribute to transformation and advancement of our University.

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተ/ፕሬዚዳንት የአዲስ ዓመት መልካም ምኞት መግለጫ *//* ጳጉሜ 5/2018 ዓ/ም የተከበራችሁ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት እና በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የምትኖሩ ውድ
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተ/ፕሬዚዳንት የአዲስ ዓመት መልካም ምኞት መግለጫ *//* ጳጉሜ 5/2018 ዓ/ም የተከበራችሁ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት እና በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የምትኖሩ ውድ ኢትዮጵያውያን! እንኳን ለ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ !! አዲሱ ዓመት የስኬት የብልጽግና እና የሰላም እንዲሆንልን እመኛለሁ!! 2019 ዓ.ም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 50ኛ አመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች የምናከብር ይሆናል። መልካም አዲስ አመት ! መልካም 50ኛ ዓመት ! መልካም የትምህርት ዘመን! አመሰግናለሁ! ችሮታዉ አየለ ግዛዉ (ዶ/ር) የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተ/ፕሬዚዳንት

የማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የኢኮኖሚ አቅም ውስንነት ላለባቸው ወገኖች ድጋፍ አደረገ:: *//* ጳጉሜ 4/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የአዲስ ዓመት ዘ
+2
የማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የኢኮኖሚ አቅም ውስንነት ላለባቸው ወገኖች ድጋፍ አደረገ:: *//* ጳጉሜ 4/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የአዲስ ዓመት ዘመን መለወጫ በዓልን ምክንያት በማድረግ ከተለያዩ የስራ ክፍሎች ለተወጣጡ የኢኮኖሚ አቅም ውስንነት ላለባቸው የዋናው ግቢ ሠራተኞች ለበዓል መዋያ የሚሆኑ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርጓል፡፡ በድጋፍ መርሃ-ግብሩ ላይ ተገኝተዉ መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን ፕ/ር ዘለቀ አርፍጮ ይህንን መጠነኛ ድጋፍ ማድረግ የተቻለዉ ከኮሌጁ መምህራን በየወሩ ከደመወዛቸው ተቆራጭ በሚያደርጉት ገንዘብ መሆኑን ጠቅሰዉ፣ ከዚህ በተጨማሪ ከዚሁ ከመምህራን በየወሩ ከሚሰበሰበዉ ገንዘብ የትምህርት ቤት ምገባን በመደገፍ የማህበራዊ ኃላፊነት ዓይነትና አድማስ በማስፋት ላይ እንገኛለን ብለዋል፡፡ ድጋፍ የሚያሻቸዉን አካት በመመልመልና መርሃ-ግብሩን በማሰናዳት የዩኒቨርሲቲዉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ እንደተሳተፈ የገለጹት ዲኑ ለጽ/ቤቱ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ በተጨማሪም ለድጋፉ አስፈላጊ የሆነዉን ገንዘብ በፈቃዳቸዉ በየወሩ የገንዘብ መዋጮ ያዋጡትን የኮሌጁን መምህራና እና የበጎ አድራጎት አገልግሎቱን የሚመሩትን ዶ/ር ብርሃን ደመቀን ለበጎ አድራጎት ስራቸዉ አመስግነዋል፡፡ የበዓል ስጦታዉ 5 ኪሎግራም ነጭ የስንዴ ዱቄት እና 3 ሊትር የምግብ ዘይትን ያካተተ ሲሆን የዕድሉ ተጠቃሚዎች ድጋፉን ላደረጉ አካላት ያላቸዉን አክብሮትና ምስጋና አቅርበዉ በተደረገላቸዉ ድጋፍ ደስተኛ መሆናቸዉን ተናግረዋል:: ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!