ch
Feedback
Hawassa University

Hawassa University

前往频道在 Telegram

One of the top ranking first generation Universities in Ethiopia.

显示更多

📈 Telegram 频道 Hawassa University 的分析概览

频道 Hawassa University (@hucommunicationsoffice) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 35 743 名订阅者,在 教育 类别中位列第 5 241,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 962

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 35 743 名订阅者。

根据 26 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 1 038,过去 24 小时变化为 66,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 17.45%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.99% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 6 222 次浏览,首日通常累积 3 207 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
One of the top ranking first generation Universities in Ethiopia.

凭借高频更新(最新数据采集于 27 八月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

35 743
订阅者
+6624 小时
+5387
+1 03830
帖子存档
የዩኒቨርስቲዉ ፋይናንስና በጀት ስራ አስፈጻሚ  ወ/ሮ ፀዳለች አሽናፊ የስልጠናውን ይዘት ሲያብራሩ በስትራቴጂክ እቅድ፣ በፕሮግራም በጀት አሰራር መርሆዎች፣ በፋይናንስ ግልጸኝነትና ተጠያቂነት መመሪያ እንዲሁም በተሻሻለው የጥሬ ገንዘብ አስተዳደር ዙሪያ ገለጻ ተደርጎ ሰፊ ውይይት መካሄዱን ገልጸው ሰልጣኞች በሂደቱ ያገኙትን እውቀት በአግባቡ በመጠቀም የዩኒቨርሲቲውን እቅዶች በተሻለ ደረጃ ለመፈጸም የሚደረገውን ስራ ማገዝ እንደሚገባቸዉ አሳስበዋል። ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ በፕሮግራም በጀት አዘገጃጀት እና አሰራር ስርዓት ላይ ለባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ። *//* ነሐሴ 21/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የስትራቴ
+7
የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ  በፕሮግራም በጀት አዘገጃጀት እና አሰራር ስርዓት ላይ ለባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ። *//* ነሐሴ 21/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ ለኮሌጆች የዕቅድና ዳታ አስተባባሪዎች፣ ለፋይናንስ በጀት ቡድን መሪዎች፣ ለመረጃ አስተዳደር  አስተባባሪዎች፣ ለእቅድ ዝግጅትና ክትትል ቡድን መሪዎች እንዲሁም ለኦዲት ባለሙያዎችና ቡድን መሪዎች በፕሮግራም በጀት አዘገጃጀት እና አሰራር ስርአት እንዲሁም በፋይናንስ ግልጸኝነት ላይ ያተኮረ  የአቅም ግንባታ ስልጠና ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ/ም ሰጥቷል። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዚደንት ዶ/ር ሳሙኤል ጂሎ በዚሁ መድረክ ባስተላለፉት መልዕክት ወቅቱ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት ሽግግር እያደረገ ያለበት ወሳኝ ወቅት በመሆኑ የበጀት እቅድ እና አፈጻጸምን በተናበበ መልኩ ማስኬድ ያስፈልጋል ብለዋል።  የሚበጀተውን ገንዘብ ለታለመለት አላማ ብቻ እና በእቅድ መሰረት ሥራ ላይ ማዋል እንደሚገባ አጽንኦት የሰጡት ዶ/ር ሳሙኤል የስራ ሂደቱ በገንዘብ ሚኒስቴር የጥሬ ገንዘብ አስተዳደር መመሪያ መሰረት መከናወን እንዳለበት አሳስበዋል። የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ አቶ ሙሉጌታ ቡርቃ በበኩላቸው፤ የተመደበውን በጀት ከዩኒቨርሲቲው አመታዊ እና መካከለኛ ዘመን እቅዶች ጋር የማስተሳሰሩን አስፈላጊነት ጠቁመው ስልጠናው የተዘጋጀው እነዚህን እቅዶች ከበጀት አሰራር ጋር ለማቀናጀት አቅም ለመፍጠር እንደሆነ ገልጸዋል። አቶ ሙሉጌታ እንዳሉት ስልጠናው የበጀት አሰራር ስርዓትን በተዘጋጀው መመሪያና ስትራቴጂ መሰረት በጥራትና በግልጽነት መተግበር ተቋማዊ አሰራርን ለማጠናከር እና ሀብትን በአግባቡ ስራ ላይ ለማዋል ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ያሰርፃል ብለዋል::

It's almost time! Hawassa university alumni coming back home and making history!
It's almost time! Hawassa university alumni coming back home and making history!

የ"አንለያይም" ትውልድ ሐዋሳ ሊመጣ አንድ ቀን ብቻ ቀረው! ***//*** ነሐሴ 20/2018 ዓ/ም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች "አንለያይም" ብለው ያስተማራቸውን፣ አዋቂ ብቻ ሳይሆን ኃላፊነ
የ"አንለያይም" ትውልድ ሐዋሳ ሊመጣ አንድ ቀን ብቻ ቀረው! ***//*** ነሐሴ 20/2018 ዓ/ም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች "አንለያይም" ብለው ያስተማራቸውን፣ አዋቂ ብቻ ሳይሆን ኃላፊነትን በብቃትና በስነምግባር መሸከም የሚችሉበትን አቅም ለግሶ ከየአቅጣጫው አሰባስቦ፣ መልሶ ወደ ዓለም የላካቸውን የዕውቀት ማዕድ፣ ልዩ የፍቅር ቦታ ሰላማዊና ተናፋቂውን ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዳግም ከ20 ዓመታት ቆይታ በኋላ በልዩ ናፍቆት ሊጎበኙት፣ እድገትና ራዕዩን ሊያስቀጥሉ አልመው እነሆ ሊመጡ ነው! ገና ስሟ ሲጠራ ወዳጆቿ የልብ ትርታቸው የሚጨምርላት ውቢቷ የፍቅር ከተማ ሐዋሳ፣ ዩኒቨርሲቲ ገብተው ሶስትም፣ ራትም፣ አምስትም፣ ሰባትም ዓመታትን ተምረው፣ ተመርቀው ለወግ ማዕረግ ከደረሱ በኋላ በሃገር ውስጥና በዓለም ዙርያ ተበትነው በየሰለጠኑበት የሙያ ዘርፍ ህዝብን ሲመሩና ሲያገለግሉ የቆዩ፣ እየመሩ ያሉ፣ ብርቅዬ ልጆቿ አንለያይም በሚል መፈክር ከያሉበት ተፈላልገው የቀድሞ የፍቅርና የትዝታ ቤታቸውን ሊጎበኙ፣ ብሎም ልማት እድገቷን ሊደግፉ እ.የ.መ.ጡ… ነው! "አንለያይም" ያሉት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፍሬዎች ሐዋሳ ሊመጡ አንድ ቀን ብቻ ቀርቶታል! ከተማዋም ዩኒቨርሲቲውም በፍቅርና በናፍቆት ይሄንን ባለራዕይ ትውልድ "ዳኤ ቡሹ" ሊሉት ዝግጁ ናቸው! ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

Please, check the following link. https://mfonokpok.com/seminar/
Please, check the following link. https://mfonokpok.com/seminar/

Let's begin the countdown for Hawassa university Alumni Homecoming and Reunion!
Let's begin the countdown for Hawassa university Alumni Homecoming and Reunion!

IOT Placement

IOT Placement

Dear Applicants for NGAT, please check your placement for IOT at Hawassa University Here.

ንኳን ለመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ***//*** ነሐሴ 19/2018 ዓ/ም ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፡- እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነብዩ መሃመድ የልደት በዓል (መውሊድ) በሰላምና
ንኳን ለመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ***//*** ነሐሴ 19/2018 ዓ/ም ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፡- እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነብዩ መሃመድ የልደት በዓል (መውሊድ) በሰላምና በጤና አደረሳችሁ! በዓሉ የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የፍቅር እና የደስታ ይሁንላችሁ! መልካም በዓል! ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

የሀዋሳ፣ አርሲ፣ መደወላቡ፣ አርባምንጭ፣ ጂንካ፣ ዋቸሞ፣ ዲላ፣ ቡሌ ሆራ፣ ወላይታ እና ወራቤ ዩኒቨርሲቲዎች የፌደራል ፖሊስ የሬጅመንት ኃላፊ ኮማንደር ዳምጠው ኩሳ በበኩላቸው፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ጸጥታና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ በመጠበቅ የዕለት ተዕለት የማስተማርና የመማር ሂደቱ ያለ ምንም ስጋት እንዲከናወን የተደረገው ጥረት ውጤታማ መሆኑን አብራርተው በ2018 ዓ/ም የነበረውን መደበኛ የትምህርትና የፈተና ጊዜ እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ በዩኒቨርሲቲዎቹ የተሰጠውን የመውጫ ፈተና በስኬታማነት መፈጸም መቻሉን ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲ ደህንነት ፖሊስ መምሪያ ሬጅመንት አማካኝነት በበጀት አመቱ የተከናወኑ አጠቃላይ የጥበቃና የደህንነት ስራዎችን አመታዊ አፈጻጸም በተመለከተ ገለጻ ያደረጉት እና የአጋር ተቋማትና የዩኒቨርሲቲዎቹ አመራሮች የነበረ ተሳትፎ እንዴት በተሻለ መልኩ ማስቀጠል ይገባል በሚለው ላይ ሀሳባቸውን የገለጹት በፌደራል ፖሊስ የተቋማትና መሰረተ ልማት ጥበቃ ም/ዋና መምሪያ አዛዥ የሆኑት የተከበሩ ረ/ኮሚሽነር ሰለሞን ከበደ ናቸው። በመድረኩ ላይ የፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አመራሮች፣ የሲዳማ ክልል ፖሊስ መምሪያ ኃላፊዎች፣ የአስሩ ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዚደንቶች፣ በየደረጃው ያሉ የጸጥታ እና የደህንነት አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው አጋር ድርጅቶች የተገኙ ሲሆን በበጀት ዓመቱ የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ለአስሩ የዩኒቨርሲቲ ፖሊስ አመራሮች፣ ለዩኒቨርሲቲዎቹ ፕሬዚደንቶች፣ ለተለያዩ አጋር ድርጅቶችና ተቋማት እውቅና እና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

ፌደራል ፖሊስ በዩኒቨርሲቲ ደህንነት ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የላቀ የስራ አፈጻጸም ላስመዘገበው ሬጅመንት 2 የእውቅናና ተሃድሶ ፕሮግራም ተካሄደ። ***//*** ነሐሴ 18/2018 ዓ/ም ሀዋሳ ዩ
+9
ፌደራል ፖሊስ በዩኒቨርሲቲ ደህንነት ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የላቀ የስራ አፈጻጸም ላስመዘገበው ሬጅመንት 2 የእውቅናና ተሃድሶ ፕሮግራም ተካሄደ። ***//*** ነሐሴ 18/2018 ዓ/ም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ በደቡባዊው የኢትዮጵያ ክፍል የሚገኙ አስር ዩኒቨርሲቲዎችን እና ዘጠኝ ካምፓሶችን ደህንነት ለማረጋገጥ ኃላፊነት የተሰጠው የፌደራል ፖሊስ የዩኒቨርሲቲ ደህንነት ፖሊስ መምሪያ ሬጅመንት በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ስራ አፈጻጸም ግምገማ ከ6ቱ ሬጅመንቶች መካከል የላቀ የስራ አፈፃፀም በማስመዝገብ ሬጅመንት 2 1ኛ መውጣቱን ተከትሎ ለሬጅመንት 2 ስታፍ፣ ሻምበል 2 አመራርና አባላት የምስጋና እውቅና አሰጣጥና ተሃድሶ መርሃግብር ነሐሴ 17/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አፍሪካ ህብረት አዳራሽ ተካሂዷል፡፡ በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ክቡር ም/ኮሚሽነር መላኩ ፈንታ በሀገራችን በሁሉም ተቋማት መተግበር ከጀመረው የለውጥ አሰራር ጋር ተያይዞ ፌደራል ፖሊስም ዘመናዊ የፖሊስ ተቋም በመሆን ረገድ አሰራሩን አዝምኖ ስኬታማ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ቀደም ሲል ዩኒቨርሲቲዎች የፖለቲካ ሀሳብ ማስፈጸሚያ በመሆን ከተቋቋሙበት ዋነኛ ዓላማ ባፈነገጠ መልኩ የሁከትና ብጥብጥ ማዕከላት ሆነው ይገኙ እንደነበር ያስታወሱት ም/ኮሚሽነር መላኩ ይህንን የወቅቱን አደጋ በመቀልበስና በእነኚህ ተቋማት ያለውን ሰላምና ጸጥታ በማረጋገጥ ረገድ የፌደራል ፖሊስ የተቋማትና መሠረተ ልማት ጥበቃ ምክትል ዋና መምሪያ በሬጅመንቶቹ በኩል አይተኬ ስራ መስራቱን ተናግረዋል።

photo content

Day 2 Session 1 NGAT Placement.pdf4.95 KB

Day 1 Session 2 NGAT Placement.pdf5.00 KB

Day 1 Session 1 NGAT placement.pdf5.04 KB

ማስታወቂያ! ***//*** ነሐሴ 18/2018 ዓ/ም   ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ነሐሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል፡፡   በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሃገርአቀፉን የ2018 ዓ.ም መጨረሻ ዓመት ብሔራዊ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ለመፈተን የተመደባችሁ በሙሉ፡-   የስም ዝርዝራችሁና የፈተና ጣቢያ ምድባችሁን ለማወቅ በቴሌግራም ቻናላችን ላይ በሚቀጥለው ሊንክ ገብታችሁ መመልከት ትችላላችሁ!   ማሳሰብያ፡- ወደ ፈተና መስጫ ጣቢያ ስትመጡ መሟላት ያለባቸውን ፕሮቶኮሎች እንዳትዘነጉ! ü  ፕሮፋይላችሁ ላይ በመግባት 'Exam Credentials' በሚለው ስር 'Download Entry Ticket' የሚለውን በመጫን ወደ ፈተና ማዕከል መግቢያ ትኬትዎን አውርደው ፕሪንት ያድርጉ። ü  ፈተናው ከሚጀመርበት ሰዓት 30 ደቂቃ ቀድማችሁ መድረስ ይጠበቅባችኋል። ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

#NGAT_Schedule የ2018 ዓ.ም መጨረሻ ዓመት ብሔራዊ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የፈተና መስጫ መርሐግብር፦ ፈተናው በጠዋት እና በከሰዓት ፈረቃ ነሐሴ 20 እና 21/
#NGAT_Schedule የ2018 ዓ.ም መጨረሻ ዓመት ብሔራዊ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የፈተና መስጫ መርሐግብር፦ ፈተናው በጠዋት እና በከሰዓት ፈረቃ ነሐሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም ይሰጣል።

For your information!

ቀን 18/12/2018 📣 ማስታወቂያ ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በ2019 ዓ.ም ከዚህ ቀጥሎ በየኮሌጆቹ ስር በተዘረዘሩት ፕሮግራሞች በሁለተኛ እና በሶስተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል። የማመ
ቀን 18/12/2018 📣 ማስታወቂያ ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በ2019 ዓ.ም ከዚህ ቀጥሎ በየኮሌጆቹ ስር በተዘረዘሩት ፕሮግራሞች በሁለተኛ እና በሶስተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል። የማመልከቻ ሂደቱ በአካል ወይም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማመልከቻ ፖርታል (portal.hu.edu.et) በመጠቀም ማመልከት የሚቻል ሲሆን የማመልከቻ ጊዜውን የNGAT ፈተና አልቆ ውጤት አንደተለቀቀ የምናሳውቅ ይሆናል። በተጨማሪም የመግቢያ መስፈርት አማልተው ለሚገቡና የምርምር ስራዎቻቸውን ከዩኒቨርስቲው የቲማቲክ ምርምር መስክ (Thematic Research Areas) ጋር አገናኝተው ለሚሰሩ የድህረምረቃ ተማሪዎቻችን ለምርምር ስራ ልዩ ድጋፍ የሚደረግ መሆኑን እናሳውቃለን። ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋና ሬጅስትራር ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!