ar
Feedback
Hawassa University

Hawassa University

الذهاب إلى القناة على Telegram

One of the top ranking first generation Universities in Ethiopia.

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Hawassa University

تُعد قناة Hawassa University (@hucommunicationsoffice) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 34 370 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 507 في فئة التعليم والمرتبة 970 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 34 370 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 04 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 910، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -11، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 17.47‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 8.68‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 6 006 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 983 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 0.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
One of the top ranking first generation Universities in Ethiopia.

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 05 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.

34 370
المشتركون
-1124 ساعات
-307 أيام
+91030 أيام
أرشيف المشاركات
Highlights of Hawassa University Students Graduation 2026

አንድ የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ራስ-ገዝ ለመሆን በሁሉም ፕሮግራሞች ለሦስት ተከታታይ ዓመታት 80 በመቶ ተማሪዎቹን በመውጫ ፈተና ማሳለፉን እንደ አንድ አካዳሚክ መመዘኛ ነጥብ የሚይዝ መመሪያ ትምህርት ሚኒስቴር አውጥቷል። • ማንኛውም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ለመሆን በመመዘኛ ነጥቦቹ 60 በመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅበታል የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ካሉባቸው የአደረጃጀት እና የአሰራር ውሱንነቶች ወጥተው፣ ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድሩ የሚያስችላቸውን “የመንግስት ዩኒቨርሲቲ የራስ-ገዝነት የሽግግር መምረጫ መመሪያ ቁጥር 1143/2018” አውጥቷል። ትምህርት ሚኒስቴር መመሪያውን ማውጣት ያስፈለገበትን ምክንያት ሲያስረዳ፤ እስካሁን በነበረው አሰራር ዩኒቨርሲቲዎች በቂ ተቋማዊ ነፃነት ባለመኖሩ ምክንያት የመማር ማስተማር፣ የምርምር እና የማህበረሰብ አገልግሎት ተልዕኮዎቻቸውን በአግባቡ ለመወጣት እንቅፋት ሆኖባቸው መቆየቱን ገልጿል። በመሆኑም ተቋማቱ ከመንግስት ጣልቃ ገብነት ነፃ ሆነው በሰው ኃይል፣ በሀብት አጠቃቀም እና በአካዳሚክ ጉዳዮች ላይ ራሳቸውን እንዲያስተዳድሩ ማስቻል አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ገልጿል። ይህ መመሪያ በራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ አዋጅ ቁጥር 1294/2015 አንቀጽ 5 እና 45 መሠረት የተዘጋጀ ነው። እንደ መመሪያው ገለጻ፣ አንድ የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር በአራት ዋና ዋና አምዶች ላይ ተመስርቶ ግምገማ ይደረግበታል። እነዚህም አስተዳደር (30%)፣ ፋይናንስ (20%)፣ የሰው ኃይል (15%) እና አካዳሚክ (35%) ጉዳዮች ናቸው። የሽግግር ሂደቱም በተጨባጭ መረጃ፣ በላቀ ብቃት፣ በውጤታማነት፣ በአካታችነት፣ በግልጽነት እና በተጠያቂነት መርሆዎች ላይ ተመስርቶ የሚከናወን ይሆናል። ዩኒቨርሲቲዎች ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ለመሸጋገር በዝግጅት ምዕራፍ ወቅት ቢያንስ 60 በመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል። በመመሪያው ላይ በዝርዝር የተቀመጡ እና ተቋማቱ ሊያሟሏቸው የሚገቡ መመዘኛዎች መስፈርቶች መካከል:- • ተቋማቱ ቢያንስ 15 በመቶ የሚሆኑ የመማሪያ ክፍሎቻቸውን ወደ “ስማርት ክላስሩም” የቀየሩ • 80 በመቶ እና ከዚያ በላይ የሚሆኑ ተማሪዎቻቸው ብሄራዊ የመውጫ ፈተናን ያለፉ •ቢያንስ 5 በመቶ የሚሆኑ የትምህርት ፕሮግራሞቻቸው ዓለም አቀፍ እውቅና (Accreditation) ማግኘታቸው እና የዲጂታል ቤተ-መጽሐፍት አገልግሎታቸው ከ70 በመቶ በላይ መድረስ አለበት • አንድ ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር ላለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት የሂሳብ ምርመራ (Audit) ያስደረገና የኦዲት ግኝቱም “ንጹህ” (Unqualified) ወይም አስተያየት ያልተሰጠበት መሆን ይኖርበታል። • ተቋሙ ካለው አጠቃላይ በጀት ውስጥ ቢያንስ 15 በመቶውን ከውስጥ ገቢና ከውጭ የገቢ ምንጮች መሸፈን ይጠበቅበታል። • ለገቢ ምንጭነትም ቢያንስ አምስት እና ከዚያ በላይ የገቢ ማመንጫ ዘርፎችን ወደ ስራ ማስገባት እንደ ግዴታ ተቀምጧል። • የዩኒቨርሲቲው መምህራን የትምህርት ደረጃ ስብጥር 0፡ 60፡ 40 (የመጀመሪያ ዲግሪ 0%፣ ሁለተኛ ዲግሪ 60% እና ሦስተኛ ዲግሪ 40%) መድረስ እንዳለበት ተደንግጓል። • በተጨማሪም የአካዳሚክ ማዕረግ ስብጥሩ ሌክቸረር 46%፣ ረዳት ፕሮፌሰር 31%፣ ተባባሪ ፕሮፌሰር 20% እና ፕሮፌሰር እና ከዚያ በላይ 3% መሆኑ መረጋገጥ ይኖርበታል። • ተቋማቱ በምርምር ዘርፍ ያላቸውን ጥንካሬ ለማሳየትም ቢያንስ አምስት እና ከዚያ በላይ የሆኑ የአእምሯዊ ንብረት መብት (IP) ባለቤት መሆን እንዳለባቸው በመመሪያው ተመላክቷል። • ተቋማዊ አገልግሎትንና የተገልጋይ እርካታን በተመለከተም፣ ዩኒቨርሲቲዎች በመምህራን፣ በሠራተኞችና በተማሪዎች ዘንድ ቢያንስ 75 በመቶ የእርካታ ደረጃ ማረጋገጥ ይጠበቅባቸዋል። • ከአካባቢው ማህበረሰብና ከኢንዱስትሪ ተዋንያን ጋር ባላቸው ግንኙነት ደግሞ የ70 በመቶ የእርካታ ደረጃን በጥናት ማሳየት ይኖርባቸዋል። • በቴክኒክ ረገድም ካሏቸው ቤተ-ሙከራዎች (Laboratories) ውስጥ 10 በመቶ የሚሆኑት፣ ከወርክሾፖቻቸው ደግሞ 5 በመቶው በዓለም አቀፍ ስታንዳርድ የተደራጁ መሆናቸው በሽግግር ግምገማው ወቅት ትልቅ ዋጋ ይሰጠዋል። የሽግግር ሂደቱ በሁለት ደረጃዎች የሚከናወን ሲሆን፣ መጀመሪያ ዩኒቨርሲቲው በራሱ ኮሚቴ አማካኝነት የውስጥ ግለ-ግምገማ (Self-assessment) ያካሂዳል ይህ ግምገማ በዩኒቨርሲቲው ስራ አመራር ቦርድ ጸድቆ ለትምህርት ሚኒስቴር ይቀርባል። ሚኒስቴሩ የቀረበለትን ሪፖርት መነሻ በማድረግ በገለልተኛ ባለሙያዎች የታገዘ የመስክ ምልከታና ማረጋገጫ ከሰጠ በኋላ፣ መስፈርቱን አሟልተው ለተገኙ ተቋማት ወደ ራስ-ገዝነት እንዲሸጋገሩ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት የውሳኔ ሃሳብ ያቀርባል። ወደ ራስ-ገዝነት የተሸጋገረ ዩኒቨርሲቲ የሽግግር ጊዜው ለሁለት ተከታታይ ዓመታት የሚቆይ ሲሆን፣ በዚህ ጊዜ ውስጥ ተቋማዊና አካዳሚክ ነፃነቱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል አቅም ይገነባል። ይሁን እንጂ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ መግባት ካልቻለ፣ ሚኒስቴሩ ተጨማሪ ጊዜ ሊሰጠው ወይም ከቦርዱ ጋር በመመካከር ሌሎች ውሳኔዎችን ሊያስተላልፍ እንደሚችል መመሪያው ደንግጓል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ መመሪያ በፍትህ ሚኒስቴር ተመዝግቦ የጸደቀ መሆኑን ከትምህርት ሚኒስቴር አረጋግጧል። የመረጃው ምንጭ:- @tikvahethiopia

የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በተሻሻለው የአካዳሚክ ሰራተኞች የደረጃ ዕድገት መመሪያ ላይ ስልጠና ሰጠ። በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ለትምህርት ክፍል ኃላፊዎች፣ ለኮሌጅ አስተ
+8
የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በተሻሻለው የአካዳሚክ ሰራተኞች የደረጃ ዕድገት መመሪያ ላይ ስልጠና ሰጠ። በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ለትምህርት ክፍል ኃላፊዎች፣ ለኮሌጅ አስተባባሪዎች እና የአካዳሚክ ሠራተኞች የደረጃ ዕድገት ኮሚቴ አባላት በትምህርት ሚኒስቴር አዘጋጅነት ወደ ትግበራ የገባውንና በርካታ ማሻሻያዎችን በውስጡ በያዘው የአካዳሚክ ሠራተኞች የደረጃ ዕድገት መመሪያ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅቷል። የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ዘፋን በደዊ መድረኩን በተመለከተ በአካዳሚክ ሰራተኞች የደረጃ ዕድገት አፈጻጸም ዙሪያ በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ሰፊ የአሰራር ክፍተቶች እንዳሉ መለየቱን አስታውሰው ይህንን ከግንዛቤ ባስገባ መልኩ የተዘጋጀ የተሻሻለ መመሪያ እየተተገበረ መሆኑን ገልጸዋል። በኮሌጅ ደረጃም ቢሆን በአዲሱ መመሪያ ላይ ጉዳዩ በሚመለከታቸው ሰዎች ዘንድ በቂ ግንዛቤ ባለመኖሩ በርካታ የደረጃ ዕድገት ጥያቄዎች ወደ ኋላ ሲመለሱና አስተደደራዊ ችግሮች ሲገጥማቸው እንደነበር የጠቆሙት ዶ/ር ዘፋን፣ እነዚህን ክፍተቶች በዘላቂነት ለመሙላትና ግንዛቤ መፍጠር የግድ የሚልበት ደረጃ ላይ መደረሱን ተናግረዋል። የኮሌጁ የምርምርና ትብብር ተባባሪ ዲን ዶ/ር ከድር ወልየ በበኩላቸው በደረጃ ዕድገት ስራዎችና ምዘናዎች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ የሚያደርጉ ሁሉም የኮሚቴ አባላት መመሪያውን በትክክል ተረድተው መስራት እንዲችሉ ማስቻል የመድረኩ ዋና ዓላማ መሆኑን አብራርተዉ፣ በምዘና ወቅት ውጤት ሊሰጥባቸው የሚገቡ እና የማይያዙ ነጥቦችንና መስፈርቶችን ባለድርሻ አካላት እና የኮሚቴ አባላት ጠንቅቀው መረዳት እንዳለባቸው አሳስበዋል:: ይህም ወጥ የሆነ አሰራር ለመዘርጋትና በጋራ ግንዛቤ ላይ ተመስርቶ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው አሰራርን ለማስፈን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አስረድተዋል:

የምርምር ቡድኑ ዋና ተመራማሪ ዶ/ር መልሰዉ ደጀኔ የጥናቱን አጠቃላይ ሂደትና ዋና ዋና ግኝቶች አቅርበዉ በምርምሩ የተለዩ መፍትሄ የተባሉ ምክረ-ሀሳቦችን ከሰፊ ገለጻና ማብራሪያ ጋር ለተሳታፊዎች አቅርበዋል:: ዶ/ር መልሰዉ ለጥናቱ መነሻ የነበሩትን ምክንያቶች ሲገልጹ፣ በሀዋሳ ከተማ ለጎዳና ህይወት የተጋለጡ ዜጎች ሁኔታን በሳይንሳዊ መንገድ በማጥናት ዘላቂ መፍትሄ ለማበጀት በመሻት የሀዋሳ ከተማ አስተደደር ለሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፍላጎቱን በማሳወቁ፣ ዩኒቨርሲቲዉ በጉዳዩ ላይ ምርምር የሚያካሄድ ቡድን ማቋቋሙን ተናግረዋል:: የምርምር ቡድኑ እሳቸዉን ጨምሮ፣ ዶ/ር ሃብተማሪያም ካሳ እና ሌሎች ተባባሪ እና ረዳት ተመራማሪዎችን ያካተተ እንደሆነም ጠቅሰዋል:: በምርምሩ ለጎዳና ህይወት የተዳረጉ ዜጎችን ጨምሮ ቁልፍ ባለ ድርሻ አካላት በመረጃ ሰጪነት እንደ ተሳተፉ የገለጹት ዶ/ር መልሰው፣ በጥናቱ ግኝቶች መሰረት ተገቢነት ያላቸዉን ዘላቂ መፍትሄ ሊያበጁ ይችላሉ የተባሉ ምክረ ሀሳቦችን አቅርበዉ ዉይይት ተደርጎባቸዋል:: የመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ንግግር ያደረጉት የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ቅድስት ደሜ በበኩላቸዉ ግኝቶቹን መነሻ በማድረግ በቀጣይ መምሪያቸዉ ብቻዉን ሳይሆን የከተማ አስተዳደሩን ከንቲባ ጽ/ቤት ጨምሮ ከሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ጋር በመሆን ቅንጅታዊ አሰራር እንደሚዘረጋ ተናግረዉ፣ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲንና የምርምር ቡድኑን አመስግነዋል:: ኃላፊዋ ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር የተጀመረዉ የትብብር ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል:: ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

ለጎዳና ህይወት የተጋለጡ ዜጎች ጉዳይ ላይ የተሰራ ምርምር ለግምገማ ቀርቦ ዉይይት ተደረገበት:: *//* ሰኔ 23/2018 ዓ/ም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ
+7
ለጎዳና ህይወት የተጋለጡ ዜጎች ጉዳይ ላይ የተሰራ ምርምር ለግምገማ ቀርቦ ዉይይት ተደረገበት:: *//* ሰኔ 23/2018 ዓ/ም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ጋር በመተባበር በሀዋሳ ከተማ ለጎዳና ህይወት የተጋለጡ ዜጎች ላይ ያተኮረ ‘’Street Children and The Rise of Streetism in Hawassa City: Pathways for Strategic Interventions‘’ በሚል ርዕስ ያካሄደዉ ጥናት ዉጤት ሰኔ 22/2018 ዓ/ም ለባለ ድርሻ አካላት ለግምገማ ቀርቧል:: መድረኩን በመክፈቻ ንግግር የከፈቱት የዩኒቨርሲቲዉ ማህበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክተርና የምርምርና ትብብር ም/ፕሬዝደንት ተወካይ አቶ ማርቆስ ፍስሃ፣ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዘርፈ ብዙ የማህበረሰብ ጉድኝት ስራዎችን በሀዋሳ ከተማና አካባቢዉ በማከናወን ለሀዋሳ ከተማ ሁለንተናዊ ልማት ንቁ ተሳታፊ ተቋም እንደሆነ ገልፀዋል:: ዩኒቨርሲቲው እንደ አንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ያለዉ ትልቁ ሃብት በየዘርፉ የሰለጠነ የሰዉ ሃይል መሆኑን ጠቁመዉ፣ ተቋሙ የአካባቢዉን ማህበረሰብም ሆነ ተቋማት በዋናነት ሊያገለግል የሚችለዉ በዕዉቀትና ቴክኖሎጂን በማሸጋገር እንደሆነ አቶ ማርቆስ አክለዋል:: ለተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የጥናት ቡድኑ አባል የሆኑት ዶ/ር ሃብተማሪያም ካሳ የመድረኩ ዓላማ በትብብር የተሰራዉ ምርምር የደረሰበትን ሂደት ለባለ ድርሻ አካላት በማሳወቅ ገንቢ አስተያየቶችን በመሰብሰብ ይሄንኑ እንደ ግብዓት ተጠቅሞ የምርምር ስራዉን ይበልጥ ተገቢነትና ጥራት እንዲኖረዉ በማድረግ በቀጣይ ለሁሉም ለሚመለከታቸዉ ባለ ድርሻ አካላት በማቅረብ ተግባራዊ እንዲደረግ ማገዝ እንደሆነ ተናግረዋል::

Program Coordinator at GIZ CPS-IDP project, Dr. Thomas Gakire, highlighted the German Government's commitment to supporting Ethiopia's efforts to build a peaceful society. He explained that the GIZ Civil Peace Service–Internally Displaced Persons (CPS-IDP) Project is an initiative of the German Corporation for International Cooperation aimed at building trust, fostering social cohesion, and strengthening the capacities of local organizations working on peace and security issues affecting displaced populations, where he remarked that the project has been implemented in collaboration with Hawassa University's College of Law and Governance for the past three years. Three research papers were presented at the workshop followed by reflections and evaluations from both internal and external reviewers. The event was concluded with plenary discussions, where participants exchanged views and provided recommendations to further strengthen the quality and relevance of research papers. Hawassa University Ever to Excel!

College of Law and Governance Organizes a Research Validation Workshop *//* June 29, 2026 The College of Law and Governance (
+9
College of Law and Governance Organizes a Research Validation Workshop *//* June 29, 2026 The College of Law and Governance (CLG) at Hawassa University, in collaboration with GIZ CPS-IDP project, organized a validation workshop for research papers focusing on peace and security issues in Ethiopia, on June 25, 2026. Dr. Debrework Debebe, CLG Dean, emphasized in his opening remarks that the event was both timely and highly relevant in the Ethiopian and global context. He noted that changing socio-political dynamics, increasing internal and external pressures, conflicts over resources, displacement, migration, social polarization, and emerging security threats demand rigorous academic inquiry and informed policy responses. Dr. Debrework stated that the workshop provides an important platform for researchers, reviewers, and participants to critically review, discuss, and validate research findings.

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸዉን 3,317 ተማሪዎች አስመረቀ። *//* ሰኔ 20/2018 ዓ/ም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ27ኛ ዙር በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 3,317
+9
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸዉን 3,317 ተማሪዎች አስመረቀ። *//* ሰኔ 20/2018 ዓ/ም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ27ኛ ዙር በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 3,317 ተማሪዎች በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በሁለተኛ ዲግሪ፣ እና በሦስተኛ ዲግሪ ያስመረቀ ሲሆን በተጨማሪም በምህንድስና ትምህርት፣ ምርምር እና ዓለምአቀፍ ትብብር ዘርፎች ለዩኒቨርሲቲው ያደረጉትን የላቀ አስተዋፅኦ ምክንያት በማድረግ ለጀርመናዊው ፕሮፌሰር ዶ/ር ኢ/ር ዮሐንስ ሽታይንብሩን የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጥቷል:: በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ የከብር እንግዳ የሆኑት የሐዋሳ ከተማ አሰተዳድር ከንቲባ እና የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርድ አባል ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ፣ የፌደራልና የሲዳማ ክልል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው የስራ አመራር ቦርድ አባላት፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የዩኒቨርሲቲዉ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች፣ ተመራቂዎችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ ለተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከሐዋሳ ክተማ ዕድገትና በጎ ለውጦች ጋር ያላችዉን ጥብቅ ትስስር በማስታወስ ዩኒቨርሲቲዉ ለሀዋሳ ከተማ ሁለንተናዊ እድገት በምርምር፣ የማህበረሰብ አገልግሎት እና ልማት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ለግማሽ ምዕተ አመት የቆየ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል። ከንቲባው አክለውም ተመራቂዎች በቀጣይ በሚሰማሩብት የሰራ መስክ ሀገራቸዉን በትጋትና በመልካም ሥነ ምግባር ሊያገለግሉ እንደሚገባ አስገንዝበዉ፣ በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸዉ ያገኙትን ዕዉቀት ለሌሎችም እንዲያካፍሉና ለዩኒቨርሲቲዉም ሆነ ለሀዋሳ ከተማ የአምባሳደርነት ሚናቸዉን እንዲወጡ ጥሪ አስተላልፈዋል::

It's happening tomorrow...
It's happening tomorrow...

የሃዘን መግለጫ *** ሰኔ 19/2018 ዓም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ የተማሪዎች አገልግሎት የሥራ ባልደረባ በነበሩት አቶ ዋሲሁን አለሙ ሞት የተሰማንን ጥልቅ ሃዘን እየገለፅን ለወዳጅ፣ ቤተሰብ፣
የሃዘን መግለጫ *** ሰኔ 19/2018 ዓም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ የተማሪዎች አገልግሎት የሥራ ባልደረባ በነበሩት አቶ ዋሲሁን አለሙ ሞት የተሰማንን ጥልቅ ሃዘን እየገለፅን ለወዳጅ፣ ቤተሰብ፣ ለስራ ባልደረቦቹ እንዲሁም በሙያው በቅንነትና በታማኝነት ሲያገለግላቸው ለቆየው የዩንቨርስትያችን ተማሪዎች ልባዊ መፅናናትን እንመኛለን! አቶ ዋሲሁን አለሙ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ክሊኒክ ከላብራቶሪ አቴንዳንትነት እስከ ክሊኒካል ነርስነት ከአስር ዓመታት በላይ ሲያገለግል የነበረ ቅን ሰራተኛ ሲሆን ባደረበት ድንገተኛ ህመም ምክንያት ሕክምና ሲከታተል ቆይቶ ሰኔ 17/2018 ዓ/ም በ39 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል:: አቶ ዋሲሁን አለሙ ባለትዳርና የአንድ ወንድ ልጅ አባት ነበር :: ነብስ ይማር! 😭 ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ

ሊደረግ እንደሚገባም አሳስበዋል። በዚሁ የምርምርና የተሞክሮ ልውውጥ መድረክ ላይ በኮሌጁ አንጋፋ ተመራማሪዎች በዶ/ር ራማቶ አበበና በዶ/ር መለሰ ቢርመካ አማካኝነት በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በተለያዩ ወረዳዎች የተከናወኑ የእንስሳት ጤና አጠባበቅና አያያዝ ዙሪያ የተሰሩ የምርምር ስራዎች፣ ከዚህም በተጨማሪ የወባ በሽታ ስርጭት፣ የመድኃኒት ፈዋሽነትና ተያያዥ ርዕሶችን የዳሰሱ በፖሊሲ ላይ ያተኮሩ ሰነዶች ቀርበው ከተሳታፊ መምህራን ጋር ሰፊና ጥልቅ ውይይት ተደርጎባቸዋል። ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በፖሊሲ ገለጻ አዘገጋጀት ዙሪያ የተሞክሮ ልውውጥ መድረክ አካሄደ። *//* ሰኔ 18/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ከረ/ፕሮፌሰር በላ
+7
የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በፖሊሲ ገለጻ አዘገጋጀት ዙሪያ የተሞክሮ ልውውጥ መድረክ አካሄደ። *//* ሰኔ 18/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ከረ/ፕሮፌሰር በላይ አካዳሚክ ማዕረግ ላላቸውና በተለያዩ የምርምር ስራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፉ ለሚገኙ መምህራን ያዘጋጀው የፖሊሲ ገለጻ ዝግጅት የተሞክሮ ልውውጥ መድረክ ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ተካሂዷል። የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ዙፋን በደዊ መድረኩን በንግግር በከፈቱበት ወቅት እንደገለጹት፣ በኮሌጁ ውስጥ የሚካሄዱ ሳይንሳዊ ምርምሮች ሁሉ ማህበረሰቡን በቀጥታ የሚጠቅሙና በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚወጡ ፖሊሲዎች እንደ ግብዓት የሚያገለግሉ መሆን ይገባቸዋል ብለዋል። ዶ/ር ዙፋን አክለውም ተመራማሪዎች የሚያገኟቸውን የምርምር ውጤቶች በተግባር ላይ ለማዋል እንዲችሉ ኮሌጁ መሰል የተሞክሮ ልውውጥ መድረኮችና አቅም ግንባታ ስልጠናዎች ላይ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው፣ በዚህም መነሻነት ከጊዜ ወደጊዜ የሚሰሩ የምርምር ስራዎችን ብዛት፣ ጥራት እና የተሳትፎ ምጣኔ እያሳደገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የኮሌጁ ምርምርና ትብብር ተባባሪ ዲን የሆኑት ዶ/ር ከድር ወልየ በበኩላቸው ተመራማሪዎች የሚያከናውኗቸውን ስራዎች ከምርምር ወደ ህትመት እንዲሁም ከህትመት ደግሞ ወደ ፖሊሲ ግብዓትነት ማሳደግ ቀጣይነት ያለው የምርምር ስራ ማሳያ በመሆኑ አብዛኛዎቹ ምርምሮች በዚሁ አግባብ ሊሰሩ እንደሚገባ ተናግረዋል። የጥናትና ምርምር ውጤቶች በተመራማሪዎች እጅና በሳይንሳዊ መጽሔቶች ላይ ብቻ ተቀምጠው መቅረት እንደሌለባቸው የገለጹት ዶ/ር ከድር፣ ወደ ፖሊሲ አዉጪዎችና ውሳኔ ሰጪ አካላት የሚደርሱ አጫጭርና ግልጽ የፖሊሲ አቅጣጫ ጠቋሚ ሰነዶችን ማዘጋጀት ላይ ትኩረት

Counting down to the big day! CONGRATULATIONS TO YOU ALL! Hawassa University Ever to Excel!
+2
Counting down to the big day! CONGRATULATIONS TO YOU ALL! Hawassa University Ever to Excel!

photo content

By bridging high-impact academic research with practical public policy, this enduring 30-year alliance continues to empower communities and inspire sustainable solutions for national development. Our sincere gratitude goes to NMBU, NORAD, and the Royal Norwegian Embassy in Addis Ababa for their unwavering commitment to academic excellence and shared progress in Ethiopia over the years and still counting. Hawassa University Ever to Excel!

A high-level delegation led by Hawassa University President Visits Norway 24/6/2026 A high-level delegation led by Hawassa Un
+5
A high-level delegation led by Hawassa University President Visits Norway 24/6/2026 A high-level delegation led by Hawassa University President, Dr. Chirotaw Ayele, is currently on an official visit to Norway, marking another major milestone in over three decades of fruitful Ethio-Norwegian cooperation. The primary focus of the visit is evaluating the performance of the Institutional Collaboration Program Phase V (ICP V), a landmark initiative generously supported by the Royal Norwegian Embassy in Addis Ababa. Key highlights from the high-level engagements include: reviewing the impact of ICP V in driving climate-resilient agriculture, graduate training, and institutional capacity building at the Norwegian University of Life Sciences (NMBU; and conducting strategic discussions at the Oslo headquarters of the Norwegian Agency for Development Cooperation (NORAD) to reinforce the long-standing strategic partnership and explore new avenues for sustainable development, academic governance, and joint research.

ለመፍጠር እንደተሰራና በሂደት ምክረሃሳቡ ተገምግሞና ተጠናክሮ ከወጣ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በሀገራችን በዚህ ረገድ ፈር ቀዳጅ ዩኒቨርሲቲ እንዲሆን ያስችለዋል ብለዋል:: በኢትዮጵያ የሰላም ተቋም ፕሮግራም ኦፊሰር አቶ ካሳሁን አብደታ እንደዚሁ ዩኒቨርሲቲው ስራቸውን በስኬት ለማከናወን ላደረገላቸውን ድጋፍ አመስግነው የተዘጋጀው መዋቅር ከዜሮ ድራፍት ከፍ ያለ እና በአነስተኛ ማሻሻያ የመጀመሪያ ንድፍ ሆኖ መቅረብ እንደሚችል ተናግረዋል:: ከ Life & Peace Institute ሲንየር ፕሮግራም ኦፊሰር የሆኑት አቶ ይበልጣል አሰፋ በዚሁ ወቅት ሲናገሩ "እስካሁን አብረን ለመስራት መሰል ፕሮጀክት ከጀመርንባቸው በርካታ ዩኒቨርሲቲዎች እንደ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በጣም ውጤታማና አርአያ መሆን የሚችል አላየንም" ያሉ ሲሆን ይሄ የተዘጋጀው መዋቅር አስፈላጊውን ሁሉ ግብዓት ይዞ ከፀደቀ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ሆኖ ለሌሎቹ እንደ ሞዴል ማገልገል ይችላል ሲሉ አክለዋል:: የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደርና ልማት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ጅሎ እስካሁን ፕሮጀክቱ እየሰራቸው ያሉትን መልካም ሥራዎች አድንቀው ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ጠቃሚ የሆነ እና ፍሬያማ መዋቅር መመስረት መቻሉ ታይቶ ወደ ትግበራ እንዲገባ ዩኒቨርሲቲው አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገልፀዋል:: ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና ፈጣን ምላሽ መዋቅር መመስረቻ ዎርክሾፕ ተካሄደ: 16/10/2018 ዓም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ የሰላም ተቋም ጋር በመተባበር የሚሰሩበት እና በላይ
+9
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና ፈጣን ምላሽ መዋቅር መመስረቻ ዎርክሾፕ ተካሄደ: 16/10/2018 ዓም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ የሰላም ተቋም ጋር በመተባበር የሚሰሩበት እና በላይፍ ኤንድ ፒስ ተቋም (Life &Peace Institute) የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግለት የሰላማዊ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ፕሮጀክት (Peaceful University Community Project) በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና ፈጣን ምላሽ መዋቅር ለመመስረት የምያስችል የሶስት ቀናት ወርክሾፕ አካሂዷል:: የፕሮጀክቱ አስተባባሪና የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊው ዶ/ር አየለ አዳቶ በወርክሾፑ ማጠቃለያ ላይ እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ከከፍተኛ አመራሮች እስከ ተማሪዎች ድረስ ያሉትን ባለድርሻ አካላት ያሳተፉ የተለያዩ ግዜያት ላይ የተሰጡ የሰላማዊ ማህበረሰብ ግንዛቤና የሰላም እሴቶች ላይ ያተኮሩ ስልጠናዎች እንደነበሩ አስታውሰው የአሁኑ ስልጠና ዓላማ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የግጭት ቅድመ-ማስጠንቀቂያና ፈጣን ምላሽ መዋቅር ለመስራት አንድ እርምጃ ወደፊት የሄደ ነው:: በወርክሾፑ ላይ ተሳታፊ የሆኑትን ባለድርሻ አካላት ሲያሰለጥኑ የነበሩት የኢትዮጵያ ሰላም ተቋም ሲንየር ፕሮግራም ማናጀር አቶ ንጉሴ አንገሳ በበኩላቸው ሰላማዊ የዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ለመፍጠር አንዱና ቁልፉ ጉዳይ በማንኛውም ግዜ ሊፈጠሩ የሚችሉ ግጭቶችን አስቀድሞ መለየት እና ለግጭቶቹ ፈጣን ምላሽ መስጠት መሆኑን ገልፀው ይሄንን ለማድረግ የሚያስችል መዋቅር መፍጠር ለተቋማት እጅግ ጠቃሚ መሆኑን አስረድተዋል:: አቶ ንጉሴ እንዳሉት ስልጠናው ሳይንሳዊ የግጭት ልየታና ትንተና ዘዴዎችን ብቻ ሳይሆን ከታችኛው የካምፓስ ማህበረሰብ አካላት እስከ ከፍተኛ አመራሩ ድረስ በጥምረትና በመናበብ የሚሰራበት መዋቅር

UPCOMING GRAND EVENT @ Hawassa University THIS WEEKEND! The 27th Students Convocation! CONGRATULATIONS TO YOU ALL! Hawassa Un
UPCOMING GRAND EVENT @ Hawassa University THIS WEEKEND! The 27th Students Convocation! CONGRATULATIONS TO YOU ALL! Hawassa University Ever to Excel!

from the International Institute for Land Reclamation and Improvement (IILRI), the Netherlands; a Master of Science (MSc) in Agricultural Engineering from the University of Nairobi, Kenya; and a BSc in Agricultural Engineering from Alemaya College of Agriculture, Addis Ababa University, Ethiopia. Throughout his distinguished career, Prof. Awdenegest has held several key academic and administrative leadership positions at Hawassa University including being the Founding Director of the Institute of Technology, Founding Dean of the Faculty of Technology, Regional Coordinator of the Ethiopian Management Development Program (EMDP), and Chairman of the Department of Agricultural Engineering. His leadership has contributed significantly to institutional development, academic program expansion, and capacity building in Institute of Technology, Hawassa university. Prof. Awdenegest has led and participated in numerous nationally and internationally funded research projects focusing on land degradation, climate resilience, ecosystem restoration, soil and water conservation, watershed management, and sustainable livelihoods. Notable projects include ALTER, BREAD, PDPL, RALENTIR, SMILE, and CROSSROADS, supported by organizations such as UK Research and Innovation (UKRI), the Economic and Social Research Council (ESRC), DFID-NERC, the Foreign, Commonwealth & Development Office (FCDO), and the Czech Development Agency. His research combines biophysical and socio-environmental approaches, emphasizing participatory assessment of natural resources, community perceptions of environmental change, and the development of practical solutions for sustainable land management. Prof. Awdenegest has authored and co-authored more than 75 peer-reviewed journal articles, technical reports, policy briefs, and conference proceedings. He currently serves as a Topical Editor for SOILS, a journal of the European Geosciences Union, and previously served as Associate Editor of the Journal of Science and Development. In recognition of his outstanding contributions to research, innovation, grant acquisition, and academic services, Prof. Awdenegest received multiple awards from Hawassa University as his career reflects a sustained commitment to scientific excellence, environmental sustainability, institutional leadership, and the advancement of higher education and natural resource management in Ethiopia and beyond. CONGRATULATIONS Professor Awdenegest! Hawassa University Ever to Excel!