es
Feedback
Hawassa University

Hawassa University

Ir al canal en Telegram

One of the top ranking first generation Universities in Ethiopia.

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Hawassa University

El canal Hawassa University (@hucommunicationsoffice) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 35 743 suscriptores, ocupando la posición 5 241 en la categoría Educación y el puesto 962 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 35 743 suscriptores.

Según los últimos datos del 26 agosto, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 1 038, y en las últimas 24 horas de 66, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 17.45%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 8.99% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 6 222 visualizaciones. En el primer día suele acumular 3 207 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 0.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
One of the top ranking first generation Universities in Ethiopia.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 27 agosto, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Educación.

35 743
Suscriptores
+6624 horas
+5387 días
+1 03830 días
Archivo de publicaciones
የዩኒቨርስቲዉ ፋይናንስና በጀት ስራ አስፈጻሚ  ወ/ሮ ፀዳለች አሽናፊ የስልጠናውን ይዘት ሲያብራሩ በስትራቴጂክ እቅድ፣ በፕሮግራም በጀት አሰራር መርሆዎች፣ በፋይናንስ ግልጸኝነትና ተጠያቂነት መመሪያ እንዲሁም በተሻሻለው የጥሬ ገንዘብ አስተዳደር ዙሪያ ገለጻ ተደርጎ ሰፊ ውይይት መካሄዱን ገልጸው ሰልጣኞች በሂደቱ ያገኙትን እውቀት በአግባቡ በመጠቀም የዩኒቨርሲቲውን እቅዶች በተሻለ ደረጃ ለመፈጸም የሚደረገውን ስራ ማገዝ እንደሚገባቸዉ አሳስበዋል። ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ በፕሮግራም በጀት አዘገጃጀት እና አሰራር ስርዓት ላይ ለባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ። *//* ነሐሴ 21/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የስትራቴ
+7
የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ  በፕሮግራም በጀት አዘገጃጀት እና አሰራር ስርዓት ላይ ለባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ። *//* ነሐሴ 21/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ ለኮሌጆች የዕቅድና ዳታ አስተባባሪዎች፣ ለፋይናንስ በጀት ቡድን መሪዎች፣ ለመረጃ አስተዳደር  አስተባባሪዎች፣ ለእቅድ ዝግጅትና ክትትል ቡድን መሪዎች እንዲሁም ለኦዲት ባለሙያዎችና ቡድን መሪዎች በፕሮግራም በጀት አዘገጃጀት እና አሰራር ስርአት እንዲሁም በፋይናንስ ግልጸኝነት ላይ ያተኮረ  የአቅም ግንባታ ስልጠና ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ/ም ሰጥቷል። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዚደንት ዶ/ር ሳሙኤል ጂሎ በዚሁ መድረክ ባስተላለፉት መልዕክት ወቅቱ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት ሽግግር እያደረገ ያለበት ወሳኝ ወቅት በመሆኑ የበጀት እቅድ እና አፈጻጸምን በተናበበ መልኩ ማስኬድ ያስፈልጋል ብለዋል።  የሚበጀተውን ገንዘብ ለታለመለት አላማ ብቻ እና በእቅድ መሰረት ሥራ ላይ ማዋል እንደሚገባ አጽንኦት የሰጡት ዶ/ር ሳሙኤል የስራ ሂደቱ በገንዘብ ሚኒስቴር የጥሬ ገንዘብ አስተዳደር መመሪያ መሰረት መከናወን እንዳለበት አሳስበዋል። የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ አቶ ሙሉጌታ ቡርቃ በበኩላቸው፤ የተመደበውን በጀት ከዩኒቨርሲቲው አመታዊ እና መካከለኛ ዘመን እቅዶች ጋር የማስተሳሰሩን አስፈላጊነት ጠቁመው ስልጠናው የተዘጋጀው እነዚህን እቅዶች ከበጀት አሰራር ጋር ለማቀናጀት አቅም ለመፍጠር እንደሆነ ገልጸዋል። አቶ ሙሉጌታ እንዳሉት ስልጠናው የበጀት አሰራር ስርዓትን በተዘጋጀው መመሪያና ስትራቴጂ መሰረት በጥራትና በግልጽነት መተግበር ተቋማዊ አሰራርን ለማጠናከር እና ሀብትን በአግባቡ ስራ ላይ ለማዋል ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ያሰርፃል ብለዋል::

It's almost time! Hawassa university alumni coming back home and making history!
It's almost time! Hawassa university alumni coming back home and making history!

የ"አንለያይም" ትውልድ ሐዋሳ ሊመጣ አንድ ቀን ብቻ ቀረው! ***//*** ነሐሴ 20/2018 ዓ/ም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች "አንለያይም" ብለው ያስተማራቸውን፣ አዋቂ ብቻ ሳይሆን ኃላፊነ
የ"አንለያይም" ትውልድ ሐዋሳ ሊመጣ አንድ ቀን ብቻ ቀረው! ***//*** ነሐሴ 20/2018 ዓ/ም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች "አንለያይም" ብለው ያስተማራቸውን፣ አዋቂ ብቻ ሳይሆን ኃላፊነትን በብቃትና በስነምግባር መሸከም የሚችሉበትን አቅም ለግሶ ከየአቅጣጫው አሰባስቦ፣ መልሶ ወደ ዓለም የላካቸውን የዕውቀት ማዕድ፣ ልዩ የፍቅር ቦታ ሰላማዊና ተናፋቂውን ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዳግም ከ20 ዓመታት ቆይታ በኋላ በልዩ ናፍቆት ሊጎበኙት፣ እድገትና ራዕዩን ሊያስቀጥሉ አልመው እነሆ ሊመጡ ነው! ገና ስሟ ሲጠራ ወዳጆቿ የልብ ትርታቸው የሚጨምርላት ውቢቷ የፍቅር ከተማ ሐዋሳ፣ ዩኒቨርሲቲ ገብተው ሶስትም፣ ራትም፣ አምስትም፣ ሰባትም ዓመታትን ተምረው፣ ተመርቀው ለወግ ማዕረግ ከደረሱ በኋላ በሃገር ውስጥና በዓለም ዙርያ ተበትነው በየሰለጠኑበት የሙያ ዘርፍ ህዝብን ሲመሩና ሲያገለግሉ የቆዩ፣ እየመሩ ያሉ፣ ብርቅዬ ልጆቿ አንለያይም በሚል መፈክር ከያሉበት ተፈላልገው የቀድሞ የፍቅርና የትዝታ ቤታቸውን ሊጎበኙ፣ ብሎም ልማት እድገቷን ሊደግፉ እ.የ.መ.ጡ… ነው! "አንለያይም" ያሉት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፍሬዎች ሐዋሳ ሊመጡ አንድ ቀን ብቻ ቀርቶታል! ከተማዋም ዩኒቨርሲቲውም በፍቅርና በናፍቆት ይሄንን ባለራዕይ ትውልድ "ዳኤ ቡሹ" ሊሉት ዝግጁ ናቸው! ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

Please, check the following link. https://mfonokpok.com/seminar/
Please, check the following link. https://mfonokpok.com/seminar/

Let's begin the countdown for Hawassa university Alumni Homecoming and Reunion!
Let's begin the countdown for Hawassa university Alumni Homecoming and Reunion!

IOT Placement

IOT Placement

Dear Applicants for NGAT, please check your placement for IOT at Hawassa University Here.

ንኳን ለመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ***//*** ነሐሴ 19/2018 ዓ/ም ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፡- እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነብዩ መሃመድ የልደት በዓል (መውሊድ) በሰላምና
ንኳን ለመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ***//*** ነሐሴ 19/2018 ዓ/ም ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፡- እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነብዩ መሃመድ የልደት በዓል (መውሊድ) በሰላምና በጤና አደረሳችሁ! በዓሉ የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የፍቅር እና የደስታ ይሁንላችሁ! መልካም በዓል! ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

የሀዋሳ፣ አርሲ፣ መደወላቡ፣ አርባምንጭ፣ ጂንካ፣ ዋቸሞ፣ ዲላ፣ ቡሌ ሆራ፣ ወላይታ እና ወራቤ ዩኒቨርሲቲዎች የፌደራል ፖሊስ የሬጅመንት ኃላፊ ኮማንደር ዳምጠው ኩሳ በበኩላቸው፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ጸጥታና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ በመጠበቅ የዕለት ተዕለት የማስተማርና የመማር ሂደቱ ያለ ምንም ስጋት እንዲከናወን የተደረገው ጥረት ውጤታማ መሆኑን አብራርተው በ2018 ዓ/ም የነበረውን መደበኛ የትምህርትና የፈተና ጊዜ እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ በዩኒቨርሲቲዎቹ የተሰጠውን የመውጫ ፈተና በስኬታማነት መፈጸም መቻሉን ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲ ደህንነት ፖሊስ መምሪያ ሬጅመንት አማካኝነት በበጀት አመቱ የተከናወኑ አጠቃላይ የጥበቃና የደህንነት ስራዎችን አመታዊ አፈጻጸም በተመለከተ ገለጻ ያደረጉት እና የአጋር ተቋማትና የዩኒቨርሲቲዎቹ አመራሮች የነበረ ተሳትፎ እንዴት በተሻለ መልኩ ማስቀጠል ይገባል በሚለው ላይ ሀሳባቸውን የገለጹት በፌደራል ፖሊስ የተቋማትና መሰረተ ልማት ጥበቃ ም/ዋና መምሪያ አዛዥ የሆኑት የተከበሩ ረ/ኮሚሽነር ሰለሞን ከበደ ናቸው። በመድረኩ ላይ የፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አመራሮች፣ የሲዳማ ክልል ፖሊስ መምሪያ ኃላፊዎች፣ የአስሩ ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዚደንቶች፣ በየደረጃው ያሉ የጸጥታ እና የደህንነት አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው አጋር ድርጅቶች የተገኙ ሲሆን በበጀት ዓመቱ የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ለአስሩ የዩኒቨርሲቲ ፖሊስ አመራሮች፣ ለዩኒቨርሲቲዎቹ ፕሬዚደንቶች፣ ለተለያዩ አጋር ድርጅቶችና ተቋማት እውቅና እና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

ፌደራል ፖሊስ በዩኒቨርሲቲ ደህንነት ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የላቀ የስራ አፈጻጸም ላስመዘገበው ሬጅመንት 2 የእውቅናና ተሃድሶ ፕሮግራም ተካሄደ። ***//*** ነሐሴ 18/2018 ዓ/ም ሀዋሳ ዩ
+9
ፌደራል ፖሊስ በዩኒቨርሲቲ ደህንነት ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የላቀ የስራ አፈጻጸም ላስመዘገበው ሬጅመንት 2 የእውቅናና ተሃድሶ ፕሮግራም ተካሄደ። ***//*** ነሐሴ 18/2018 ዓ/ም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ በደቡባዊው የኢትዮጵያ ክፍል የሚገኙ አስር ዩኒቨርሲቲዎችን እና ዘጠኝ ካምፓሶችን ደህንነት ለማረጋገጥ ኃላፊነት የተሰጠው የፌደራል ፖሊስ የዩኒቨርሲቲ ደህንነት ፖሊስ መምሪያ ሬጅመንት በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ስራ አፈጻጸም ግምገማ ከ6ቱ ሬጅመንቶች መካከል የላቀ የስራ አፈፃፀም በማስመዝገብ ሬጅመንት 2 1ኛ መውጣቱን ተከትሎ ለሬጅመንት 2 ስታፍ፣ ሻምበል 2 አመራርና አባላት የምስጋና እውቅና አሰጣጥና ተሃድሶ መርሃግብር ነሐሴ 17/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አፍሪካ ህብረት አዳራሽ ተካሂዷል፡፡ በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ክቡር ም/ኮሚሽነር መላኩ ፈንታ በሀገራችን በሁሉም ተቋማት መተግበር ከጀመረው የለውጥ አሰራር ጋር ተያይዞ ፌደራል ፖሊስም ዘመናዊ የፖሊስ ተቋም በመሆን ረገድ አሰራሩን አዝምኖ ስኬታማ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ቀደም ሲል ዩኒቨርሲቲዎች የፖለቲካ ሀሳብ ማስፈጸሚያ በመሆን ከተቋቋሙበት ዋነኛ ዓላማ ባፈነገጠ መልኩ የሁከትና ብጥብጥ ማዕከላት ሆነው ይገኙ እንደነበር ያስታወሱት ም/ኮሚሽነር መላኩ ይህንን የወቅቱን አደጋ በመቀልበስና በእነኚህ ተቋማት ያለውን ሰላምና ጸጥታ በማረጋገጥ ረገድ የፌደራል ፖሊስ የተቋማትና መሠረተ ልማት ጥበቃ ምክትል ዋና መምሪያ በሬጅመንቶቹ በኩል አይተኬ ስራ መስራቱን ተናግረዋል።

photo content

Day 2 Session 1 NGAT Placement.pdf4.95 KB

Day 1 Session 2 NGAT Placement.pdf5.00 KB

Day 1 Session 1 NGAT placement.pdf5.04 KB

ማስታወቂያ! ***//*** ነሐሴ 18/2018 ዓ/ም   ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ነሐሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል፡፡   በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሃገርአቀፉን የ2018 ዓ.ም መጨረሻ ዓመት ብሔራዊ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ለመፈተን የተመደባችሁ በሙሉ፡-   የስም ዝርዝራችሁና የፈተና ጣቢያ ምድባችሁን ለማወቅ በቴሌግራም ቻናላችን ላይ በሚቀጥለው ሊንክ ገብታችሁ መመልከት ትችላላችሁ!   ማሳሰብያ፡- ወደ ፈተና መስጫ ጣቢያ ስትመጡ መሟላት ያለባቸውን ፕሮቶኮሎች እንዳትዘነጉ! ü  ፕሮፋይላችሁ ላይ በመግባት 'Exam Credentials' በሚለው ስር 'Download Entry Ticket' የሚለውን በመጫን ወደ ፈተና ማዕከል መግቢያ ትኬትዎን አውርደው ፕሪንት ያድርጉ። ü  ፈተናው ከሚጀመርበት ሰዓት 30 ደቂቃ ቀድማችሁ መድረስ ይጠበቅባችኋል። ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!

#NGAT_Schedule የ2018 ዓ.ም መጨረሻ ዓመት ብሔራዊ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የፈተና መስጫ መርሐግብር፦ ፈተናው በጠዋት እና በከሰዓት ፈረቃ ነሐሴ 20 እና 21/
#NGAT_Schedule የ2018 ዓ.ም መጨረሻ ዓመት ብሔራዊ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የፈተና መስጫ መርሐግብር፦ ፈተናው በጠዋት እና በከሰዓት ፈረቃ ነሐሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም ይሰጣል።

For your information!

ቀን 18/12/2018 📣 ማስታወቂያ ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በ2019 ዓ.ም ከዚህ ቀጥሎ በየኮሌጆቹ ስር በተዘረዘሩት ፕሮግራሞች በሁለተኛ እና በሶስተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል። የማመ
ቀን 18/12/2018 📣 ማስታወቂያ ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በ2019 ዓ.ም ከዚህ ቀጥሎ በየኮሌጆቹ ስር በተዘረዘሩት ፕሮግራሞች በሁለተኛ እና በሶስተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል። የማመልከቻ ሂደቱ በአካል ወይም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማመልከቻ ፖርታል (portal.hu.edu.et) በመጠቀም ማመልከት የሚቻል ሲሆን የማመልከቻ ጊዜውን የNGAT ፈተና አልቆ ውጤት አንደተለቀቀ የምናሳውቅ ይሆናል። በተጨማሪም የመግቢያ መስፈርት አማልተው ለሚገቡና የምርምር ስራዎቻቸውን ከዩኒቨርስቲው የቲማቲክ ምርምር መስክ (Thematic Research Areas) ጋር አገናኝተው ለሚሰሩ የድህረምረቃ ተማሪዎቻችን ለምርምር ስራ ልዩ ድጋፍ የሚደረግ መሆኑን እናሳውቃለን። ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋና ሬጅስትራር ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁሌም ለልህቀት!