መጽሐፍቶችን በpdf📚
"እንኳን ደህና መጣችሁ"Welcome! በpdf(በሶፍት ኮፒ) ለማንበብ ራሳችንን እናስለምድ! ፨ተራ ነገር በመስራት የሚባክነውን ጊዜያችንን በንባብ ላይ ስናውለው ከራሳችን አልፈን ለብዙዎች የመለወጥ ምክንያት እንሆናለን፡የንባብ ባህላችንን እናዳብር! ባለንበት ራሳችንን በእውቀት እንገንባ! ፨በዚህ ቻናል የተለያዩ መፅሐፎች፣ጠቃሚ ሀሳቦች፣አፕልኬሽኖች፣አነቃቂ ምስሎች ቀርቦላችኋል አውርደው ይጠቀሙ።
Ko'proq ko'rsatish📈 Telegram kanali መጽሐፍቶችን በpdf📚 analitikasi
መጽሐፍቶችን በpdf📚 (@pdfffb) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 620 obunachidan iborat bo'lib, Kitoblar toifasida 2 343-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 162-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 620 obunachiga ega bo‘ldi.
08 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 757 ga, so‘nggi 24 soatda esa 27 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 12.61% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 4.86% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 1 969 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 759 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 11 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“"እንኳን ደህና መጣችሁ"Welcome!
በpdf(በሶፍት ኮፒ) ለማንበብ ራሳችንን እናስለምድ!
፨ተራ ነገር በመስራት የሚባክነውን ጊዜያችንን በንባብ ላይ ስናውለው ከራሳችን አልፈን ለብዙዎች የመለወጥ ምክንያት እንሆናለን፡የንባብ ባህላችንን እናዳብር! ባለንበት ራሳችንን በእውቀት እንገንባ!
፨በዚህ ቻናል የተለያዩ መፅሐፎች፣ጠቃሚ ሀሳቦች፣አፕልኬሽኖች፣አነቃቂ ምስሎች ቀርቦላችኋል አውርደው ይጠቀሙ።”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 09 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Kitoblar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 09 Iyul | +7 | |||
| 08 Iyul | +27 | |||
| 07 Iyul | +19 | |||
| 06 Iyul | +40 | |||
| 05 Iyul | +23 | |||
| 04 Iyul | +33 | |||
| 03 Iyul | +10 | |||
| 02 Iyul | +29 | |||
| 01 Iyul | +25 |
| 2 | Matn yo'q... | 714 |
| 3 | ራስ ቢትወደድ መኰንን እንዳልካቸው
ራስ ቢትወደድ መኰንን እንዳልካቸው በ20ኛው ክፍለ ዘመን የነበሩ ታላቅ የሀገር መሪ፣ ዲፕሎማት፣ ወታደራዊ አዛዥ እና በኢትዮጵያ ስነጽሁፍ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ ያላቸው ቀዳሚ ጸሐፊ ናቸው። በአጼ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን ማገልገላቸው ይታወቃል።
ራስ ቢትወደድ መኰንን እንዳልካቸው በየካቲት 1890 ዓ.ም. (በፈረንጆቹ 1898) በሸዋ ጠቅላይ ግዛት፣ በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ተወለዱ። አስተዳደጋቸውና የቀለም ትምህርታቸው በቤተ እምነትና በባህላዊው የቅኔና የሃይማኖት ትምህርት የተቃኘ ነበር። ይህም በኋላ ላይ ለሚጽፏቸው መጻሕፍት ጥልቅ የሆነ የሃይማኖት፣ የሞራልና የባህል እውቀት መሠረት ሆኗቸዋል። በተጨማሪም በዘመኑ የነበረውን የፈረንሳይኛ ቋንቋና ዘመናዊ ትምህርት ተከታትለዋል።
መኰንን እንዳልካቸው በአጼ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት ውስጥ እጅግ ታማኝና ተደማጭነት ያላቸው ባለሥልጣን ነበሩ። ያገለገሉባቸው ዋና ዋና የኃላፊነት ቦታዎች፦
የውጭ ሀገር አምባሳደር፦ በ1920ዎቹ መጀመሪያ ላይ በዩናይትድ ኪንግደም (ለንደን) የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል።
የአገር መከላከያና የጦር ሜዳ ተሳትፎ፦ ፋሺስት ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት (1928 ዓ.ም.) በኦጋዴን ግንባር የነበረውን የጦር ሰራዊት በበላይነት ከመሩት አዛዦች አንዱ ነበሩ።
ሀገሪቱ በጣሊያን እጅ ስትወድቅ ከአጼ ኃይለ ሥላሴ ጋር ወደ ኢየሩሳሌም በመሰደድ የነጻነት ዲፕሎማሲያዊ ትግሉን ቀጥለዋል። በኋላም በ1933 ዓ.ም. የሀገር ፍቅር አርበኞችን በማስተባበርና ከጃንሆይ ጋር ወደ ሀገር ውስጥ በመግባት ጣሊያንን በማስወጣት ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።
ሀገር ነጻ ከወጣች በኋላ፣ መዋቅራዊ ለውጥ ሲደረግ በ1935 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ. 1943) የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ። በዚህ ሥልጣን ላይ እስከ 1950 ዓ.ም. ድረስ ለ15 ዓመታት አገልግለዋል።
ከጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው ከተነሱ በኋላ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት (ሴኔት) ፕሬዝዳንት ሆነው እስከ ጡረታቸው ድረስ ሰርተዋል።
ራስ ቢትወደድ መኰንን እንዳልካቸው በፖለቲካው ስራቸው ብቻ ሳይሆን በብዕራቸውም የሚታወቁ ክላሲክ ጸሐፊ ናቸው። የአጻጻፍ ስልታቸው በአብዛኛው ታሪክን፣ ፍልስፍናን፣ ክርስትናንና የሞራል እሴቶችን ያጣመረ ነው። በወቅቱ ማህበረሰቡ ከቅኝ ግዛትና ከጦርነት ማግስት ሊኖረው ስለሚገባው ስነ-ምግባር አጥብቀው ይጽፉ ነበር።
«አልሞትኩም ብዬ አልዋሽም»፦ በጣሊያን ወረራ ወቅት የነበረውን መከራ፣ የሕዝቡን ስቃይ እና የነጻነት ተስፋን የሚያሳይ ግሩም ታሪካዊ መጽሐፍ ነው።
«ጣይቱ ብጡል»፦ የታላቋን እቴጌ ጣይቱን ታሪክና የአድዋን ድል የሚዘክር ተውኔት (ድራማ) ነው።
«የአርሙኝሙኝ ጋብቻ» እና «የደመ ነፍስ ህይወት»፦ ማህበራዊና ሃይማኖታዊ ይዘት ያላቸው፣ የሰው ልጅ በምድር ላይ ስላለው ፈተናና ስለ ጽድቅ የሚተርኩ ስራዎች ናቸው።
«ያይኔ አበባ»፦ ሌላኛው ታዋቂ ልብወለዳዊ ስራቸው ነው።
ራስ ቢትወደድ መኰንን እንዳልካቸው የጦር መሪ፣ የሀገር መተዳደሪያ ሕግጋት አርቃቂ እና የጥበብ ሰው ነበሩ። በተለይ በሳቸው ዘመን የተነሱትን እንደ ከበደ ሚካኤል ያሉ ታላላቅ ጸሐፊያንን ያበረታቱና ይረዱ እንደነበር ይነገራል።
ይህ ታላቅ የሀገር ባለውለታ በየካቲት ወር 1955 ዓ.ም. (በፈረንጆቹ 1963) በተወለዱ በ65 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ስማቸውና ስራዎቻቸው ግን ዛሬም ድረስ በኢትዮጵያ የፖለቲካና የስነጽሁፍ ታሪክ ውስጥ በታላቅነት ይጠቀሳሉ።
ሁሌም ማንበብ! | 1 334 |
| 4 | ፀሐይ_መስፍን_ልብ_ወለድ_ታርክ_በ_ቢትወደድ_መኰንን.pdf | 1 207 |
| 5 | አርቲስት ጌትነት እንየው
አምነው የወደዱ፣
ወደው የተካዱ፣
ተክደው የራዱ፣
ፍርሃት አንሸራቶ ቁልቁል የጣላቸው፣
የብቸኛ ልቦች የትነው መውደቂያቸው?
የትነው መድረካቸው?
ማነው አጃቢያቸው?
እንዴት ነው ምታቸው?
የተካዱ ልቦች አጋር የራቃቸው፣
የሚያቀነቅኑት ምንድን ነው ዜማቸው?
የተመረኮዙት እምነት ታጥፎባቸው፣
ድንገት የወደቁ ፍቅር ያዳጣቸው፣
ሚስጥር የሚያጋሩት ሰው የበረዳቸው፣
ብቸኝነት ሰርጎ ብቻ ያስቀራቸው፣
ዝምተኛ ልቦች ምን ይሆን ቋንቋቸው?
ከየት ነው ጥሪያቸው?
በየት ነው ጉዟቸው?
የት ነው መድረሻቸው?
እንደ ሰብአሰገል ጠቅሶ የሚመራቸው፣
የቃተቱ ልቦች የታል ኮከባቸው?
መቼም ከአምላክ ትንፋሽ ከውሃ ከአፈሩ፣
ከእምንት እና እውነት ከፍቅር ሲሰሩ፣
ዝምተኛ ልቦች ጥንቱን ሲፈጥሩ፣
ተገፍትረው ወድቀው፣
ደቀው እንዳይቀሩ፣
በተስፋ ጸንተው ነው ዘላለም ሊኖሩ።
© አርቲስት ጌትነት እንየው
ሁሌም ማንበብ! | 1 963 |
| 6 | 👌🏾 | 2 125 |
| 7 | The Pyramid Principle: Logical Writing, Thinking and Problem Solving is a seminal business book written by Barbara Minto, a former consultant at McKinsey & Company. Originally published in 1987, it has become the gold standard for structured communication in consulting, corporate management, and professional writing.
Here is a brief breakdown of what the book is about:
The Core Concept
The "Pyramid Principle" is a hierarchical framework for organizing ideas. Minto argues that the human brain naturally groups information into patterns, so your writing should mirror this structure to be easily understood.
The structure is organized like a pyramid:
The Top (The Answer): Start with your main conclusion, recommendation, or overarching idea first.
The Middle (The Arguments): Support your main point with three to four key arguments or pillars.
The Bottom (The Data): Provide the detailed facts, data, and evidence that support each of your key arguments.
Why It Matters
Most people write using a "bottom-up" approach—they lay out all their facts, walk the reader through their thought process, and finally arrive at a conclusion at the end. Minto flips this. By using a "top-down" approach, you respect the reader's time, reduce cognitive load, and make your message significantly more persuasive.
Key Takeaways
Group and Summarize: Ideas at any level in the pyramid must be summaries of the ideas grouped below them.
Logical Ordering: Ideas within a grouping must always follow a logical order (e.g., chronological, structural, or sequential).
Mutually Exclusive, Collectively Exhaustive (MECE): This famous consulting framework (popularized by Minto) dictates that when you break down a problem into categories, they should not overlap, and together they should cover everything.
In short, the book teaches you how to cut through the noise, structure your thoughts rigorously, and write in a way that gets decisions made.
The Golden Rule: Always state your main point first, then support it. Never make your reader hunt for the bottom line. | 2 069 |
| 8 | አ ት ቅ ሩ 🤌🏾 | 2 038 |
| 9 | Matn yo'q... | 1 861 |
| 10 | መኖሪያ ቤታቸውን የህዝብ ቤተ-መጻሕፍት ያደረጉት አዛውንት
#Ethiopia | የንባብ ባህል ማደግ የግለሰቦችን ስብዕና ከማነፅ ጀምሮ አገር በመገንባት ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
ኢትዮጵያ ያልታዩና ያልተነገሩ በርካታ ታሪኮች እንዳሏት ቢታወቅም፤ የዜጎቿ የንባብ ባህል ግን የታሪኳን ያህል አለማደጉ ይነገራል። ለዚህ ደግሞ ዘመኑ የፈጠረው የማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ፣ የመጻሕፍት ዋጋ መናር እንዲሁም በቂና ምቹ የቤተ-መጻሕፍት አለመኖር በምክንያትነት የሚጠቀሱ ናቸው።
ታዲያ የንባብ ባሕልን ለማዳበርና ምክንያታዊ ትውልድ ለመፍጠር የንባብ ማዕከላትን ከማስፋፋት ጀምሮ አስፈላጊውን ግብዓት ማሟላት ለነገ የማይባል ተግባር ነው።
ያነበበና ያወቀ ትውልድ የመፍጠር ኃላፊነት ከመንግሥት ባሻገር የረድኤት ድርጅቶችና የሌሎች በጎ ፈቃደኛ ግለሰቦች ሚና የጎላ መሆኑን በተግባር ያሳዩ አንድ አዛውንት በባሕር ዳር ከተማ ይገኛሉ።
እኚህ በጎ ፈቃደኛ የ74 ዓመቱ አዛውንትና ጡረተኛው የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪ አቶ ሕሩይ ደመላሽ ናቸው። ግለሰቡ አገራቸውን ለ37 ዓመታት በተለያዩ የሙያ መስኮች በታማኝነት ያገለገሉ ሲሆን፤ በጡረታ ከተሰናበቱበት ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ በመኖሪያ ቤታቸው መለስተኛ ቤተ-መጻሕፍት በመክፈት ለአካባቢው ማኅበረሰብ ነፃ የንባብ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ።
ከ20 ዓመታቸው ጀምሮ መጻሕፍትን መግዛትና ማንበብ የጀመሩት አቶ ሕሩይ፤ "ንባብ ለሕይወቴ መሠረት፣ ከሰዎች ጋር መግባቢያ፣ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴዬን የምመለከትበት እንዲሁም ማኅበረሰቡን በጥልቀት የማውቅበት መነጽሬ ነው" ይላሉ።
አዛውንቱ ባለፉት 50 ዓመታት በትጋት የሰበሰቧቸውን ከ2,530 በላይ መጻሕፍት በመኖሪያ ቤታቸው ቅጥር ግቢ ባዘጋጁት መለስተኛ ቤተ-መጻሕፍት ውስጥ ለንባብ በማብቃት ለአንባቢያን አገልግሎት በመስጠት ላይ ናቸው።
ሳይንሳዊ፣ ታሪካዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን የሚዳስሱ መጻሕፍትን በዕድሜ ዘመናቸው መሰብሰብ የቻሉት አቶ ሕሩይ፤ ለባሕር ዳር ከተማና ለአካባቢው ማኅበረሰብ ያለምንም ክፍያ መጻሕፍትን በውሰት በመስጠት ትውልዱ እንዲያውቅና እንዲያነብ በማድረግ የዜግነት ድርሻቸውን በከፍተኛ ኃላፊነት እየተወጡ ይገኛሉ። በአሁኑ ወቅትም በርካታ መደበኛ አንባቢ ደንበኞችን ማፍራት እንደቻሉ ተናግረዋል።
አሁን ላይ የንባብ ባህል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ መምጣቱን የሚጠቁሙት አቶ ሕሩይ፤ ለዚህም ማኅበራዊ ሚዲያ፣ የመጻሕፍት ዋጋ መናርና የምቹ ቦታዎች እጥረት ተግዳሮት መሆናቸውን ያነሳሉ።
ትውልዱ ከስሜት የፀዳና ምክንያታዊ መሆን ይኖርበታል ያሉት አዛውንቱ፤ የንባብ ባሕልን ለማዳበር ከግለሰቦች ጀምሮ ማኅበረሰቡ፣ ረድኤት ድርጅቶችና መንግሥት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ አሳስበዋል።
Credit : ebc
©Getu Temesgen
ሁሌም ማንበብ! | 2 026 |
| 11 | Matn yo'q... | 1 729 |
| 12 | የአዳራሽ ለውጥ ማሳወቂያ
========
የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ “ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና ኪነጥበብ፤ ዕድሉ፣ ተግዳሮቱ እና መፍትሔው” በተሰኘ ርዕስ ያዘጋጀውን የፓናል ውይይት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና ቢልት ኢንቫይሮመንት ኮሌጅ (5 ኪሎ ካምፓስ) አዳራሽ ለማካሄድ ቀደም ሲል ጥሪ ማስተላለፉ ይታወሳል።
ሆኖም ግን፣ በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና እየተሰጠ በመሆኑ የፓናል ውይይቱን እዚያው አቅራቢያ ከዩኒቨርስቲው ፊት ለፊት ወደሚገኘው #የኢትዮጵያ_ቅርስ_ባለሥልጣን _አዳራሽ (በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም 5 ኪሎ ግቢ) የተቀየረ መሆኑን በአክብሮት እንገልጻለን።
🗓ቀን፦ ሐሙስ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም
⏰ሰዓት፦ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት -12፡00 ሰዓት
መድረኩ ለሁሉም ክፍትና ነፃ በመሆኑ፤ ጥሪ የተደረገላችሁ የመንግሥትና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ተወካዮች፣ የክብር እንግዶች፣ የዘርፉ ባለሙያዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ተማሪዎች እና ፍላጎቱ ያላችሁ ዜጎች በሙሉ በተለወተለወጠው አዳራሽ በተጠቀሰው ሰዓት ተገኝታችሁ እንድትሳተፉ በአክብሮት እንጋብዛለን።
በአካል መገኘት ለማትችሉ በዙም (Zoom) ወይም በፖስተሩ ላይ ያለውን QR code በመጠቀም መከታተል ትችላላችሁ።
🔗Zoom link: https://us06web.zoom.us/j/86023294307?pwd=p6iQ4yPvX5udQy5OAmbCER2NIYLO4J.1
👉Meeting ID: 860 2329 4307
👉Passcode: 798030 | 2 344 |
| 13 | Matn yo'q... | 1 923 |
| 14 | ሁላችሁም በአክብሮት በነጻ ተጋብዛችኋል!
```````````````
የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የፓናል ውይይት መድረክ
አካዳሚው በተለያዩ ሀገራዊ ፋይዳ ባላቸው ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የኅብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግና ሳይንሳዊ አሠራሮችን ለማጎልበት ሕዝባዊ የገለጻና የፓናል ውይይት መድረኮችን ሲያካሂድ ቆይቷል።
ይህንን ሂደት በማስቀጠል “ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና ኪነጥበብ፤ ዕድሉ፣ ተግዳሮቱ እና መፍትሔው” በሚል ርዕስ በዕውቀትና የመረጃው ዓለም ላይ ጉልህ ተጽዕኖ እየፈጠረ በሚገኘው የሰው ሠራሽ አስተውሎት (#ArtificialIntelligence/ #AI) ላይ አካዳሚው ሊያከናውናቸው ካቀዳቸው ተከታታይ መድረኮች የመጀመሪያውን የፓናል ውይይት በዘርፉ ከፍተኛ ምሑራን አቅራቢነትና አወያይነት ያካሂዳል።
አቅራቢዎች፡-
🟢ሰርጸ ፍሬ ስብሃት፡- ፖሊሲ፣ አርካይቭ እና የኪነጥበብ ሀብቶች ጥበቃ
🟢ወንድወሰን ሙሉጌታ (ዶ/ር): - ለሰውሠራሽ አስተውሎት ሀገራዊ የቋንቋ እና ሥነጥበብ
መረጃን ማሰልጠን (Data Feeding) እና ማላመድ ላይ ህጋዊና ሥነምግባራዊ መርሆዎች
🟢በአካል ግዛቸው (ዶ/ር): -የቴክኖሎጂውእድገትና ዓለም አቀፋዊ ተጽዕኖ
🟢በሰናይት ጥበቡ (AI እና ሥነጽሑፍ) እንዲሁም በመድኅን ተሰማ (AI እና የኢትዮጵያ
ሙዚቃ ዳሰሳ ጥናት) ተግባራዊ ልምድ እና ዳሰሳ ይካሄዳል።
🟢የፓናል ውይይቱን ብርሃኑ በሻህ (ዶ/ር) ይመሩታል።
ስለሆነም የዘርፉ ባለሙያዎች፣ ጥሪ የተደረገላችሁ የክብር እንግዶች፣ ጋዜጠኞች፣ ተማሪዎች እና በፓናል ውይይቱ መሳተፍ የምትፈልጉ ዜጎች በሙሉ መድረኩ ለሁሉም ነጻና ክፍት ስለሆነ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት በአካል በመገኘት እንድትሳተፉ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።
🗓ቀን፦ ሐሙስ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም
⏰ሰዓት፦ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት -12፡00 ሰዓት
📍ቦታ፦ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና ቢልት ኢንቫይሮመንት ኮሌጅ (አአዩ-5 ኪሎ ካምፓስ)
ኦዲተሪየም - አዳራሽ በአካል መገኘት ለማትችሉ በዙም (Zoom) ወይም በፖስተሩ
ላይ ያለውን QR code በመጠቀም መከታተል ትችላላችሁ።
🔗Zoom link: https://us06web.zoom.us/j/86023294307?
pwd=p6iQ4yPvX5udQy5OAmbCER2NIYLO4J.1
👉Meeting ID: 860 2329 4307
👉Passcode: 798030 | 281 |
| 15 | Matn yo'q... | 281 |
| 16 | Matn yo'q... | 1 |
| 17 | ❝ሀገር የምትራመደው በአንድ ሳንቲ ሜትር ዕውቀት፤ መቶ ሳንቲ ሜትር ሥነ-ሥርዓት ነው።❞
አንዳንድ ጊዜ ሰዎች መጽሐፍን ከመክፈታቸው በፊት ይመዝኑታል። ሐሳቡን ከመረዳት ይልቅ ገጾቹን መቁጠር ይቀላቸዋል። ምክንያቱም ቁጥር መቁጠር ቀላል ነው፤ ሐሳብን መሸከም ግን ከባድ ነው።
የወረቀት ብዛት ብዙዎችን ያስጨንቃል፤ የሐሳብ ብዛት ግን ጥቂቶችን ብቻ ያስደስታል። ወረቀት ለመግዛት ገንዘብ ያስፈልጋል፤ ሐሳብን ለመቀበል ግን ክፍት አእምሮ፣ ትዕግሥት እና ራስን ለመጠየቅ ድፍረት ያስፈልጋል።
ሰውን የሚያስፈራው ብዙ ጊዜ የመጽሐፉ ዋጋ አይደለም፤ የሚያስፈራው ከመጽሐፉ ጋር የሚጀምረው ውይይት ነው።
ጥልቅ መጽሐፍ መረጃ አይጨምርልህም፤ የነበርክበትን አስተሳሰብ ይፈታተነዋል። አንዳንድ መጽሐፍት ሲዘጉ አያልቁም፤ ያኔ ነው በውስጥህ መነበብ የሚጀምሩት።
1,008 ገጽ ያለውን መጽሐፍ ሲያዩ በመጀመሪያ የሚያስቡት "ስንት ይሆን?" የሚለውን ነው። ነገር ግን 1,008 ሰዓት በስልካቸው ላይ ሲያሳልፉ የጠፋውን ጊዜ አይቆጥሩትም። ገንዘብ ሲወጣ ዓይናችን ያየዋል፤ ጊዜ ሲወጣ ግን ሕይወታችን ብቻ ያውቀዋል።
እውነታው ግን መጽሐፍ በገጹ አይመዘንም፤ በውስጡ በተቀመጠው ሕይወት ነው የሚመዘነው። 1,008 ገጾች 1,008 ወረቀቶች አይደሉም፤ 1,008 ሐሳቦች፣ 1,008 ጥያቄዎች፣ 1,008 ጉዞዎች፣ 1,008 ነፍሳት የተደበቁባቸው መስኮቶች ናቸው። ታላቅ መጽሐፍ ወረቀት አይሸጥም፤ አዲስ የማየት ዓይን ይሰጣል።
ይህን ስንረዳ ደግሞ መጽሐፉ የማን እንደሆነ ማወቅ ይገባናል።
"መዝሙረ ሄላም" የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሑፍ ውስጥ ልዩ አሻራ ያለው ደራሲ አዳም ረታ አዲስ ለኛ የሚሰጠን መጽሀፉ ነው። አዳም ረታን የሚያነብ ሰው በቀላሉ ታሪክ አያነብም፤ ቋንቋ ውስጥ ይጓዛል። ሐረጎቹን ብቻ አይከተልም፤ በእነሱ መካከል የተደበቁትን ዝምታዎችም ያዳምጣል።
ደራሲው "ማሕሌት"፣ "አለንጋና ምስር"፣ "እቴሜቴ ሎሚ ሽታ"፣ "ከሰማይ የወረደ ፍርፍር"፣ "ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ"፣ "ሕማማትና በገና" የተሰኙ የአጫጭር ልቦለዶችን፣ እንዲሁም "ግራጫ ቃጭሎች"፣ "የስንብት ቀለማት" እና "መረቅ" የተሰኙ ረጅም ልቦለዶችን ለአንባቢያን አበርክቷል። በአጻጻፍ ስልቱ ልዩነት፣ በቋንቋው ውበት እና በሐሳቡ ጥልቀት የሚጠቀስ ደራሲ ነው።
እናም 1,008 ገጽ ሲባል የሚቆጠረው የወረቀት ብዛት ብቻ አይደለም፤ የአንድ ደራሲ የዓመታት ጉዞ፣ የንባብ ትዕግሥት፣ የጥናት ልፋት፣ የልምድ ጭማቂ፣ የጥያቄ ሸክም እና የሕይወት ትርጉም ነው። የምንከፍለውም ለወረቀት ሳይሆን፣ ለዚያ የተጨመቀ ዘመን ነው።
የሐሳብ ዋጋ በብር ሊለካ ቢችል ኖሮ፣ የዓለም ታላላቅ መጽሐፍት በሀብታሞች መደርደሪያ ላይ ብቻ በተቀመጡ ነበር። ነገር ግን ታሪክ የሚያስተምረን ሌላ ነው፤ ዓለምን የለወጡት መጽሐፍት በወረቀታቸው ብዛት አይደለም፣ በያዙት ሐሳብ ጥልቀት ነው።
ስለዚህ መጽሐፍን በገጹ አትመዝነው። አንዳንድ ጊዜ በጣም ውድ የሆነው የገዛኸው መጽሐፍ አይደለም፤ በፍርሃትህ ምክንያት ሳታነበው የተውኸው መጽሐፍ ነው።
ምክንያቱም እውቀት ዋጋ አለው፤ ግን የእውቀት ዋጋ በብር አይለካም፤ በሕይወትህ ውስጥ በሚፈጥረው ለውጥ ነው እንጂ።
©የሶሪት ማስታወሻ
ሁሌም ማንበብ! | 2 374 |
| 18 | Matn yo'q... | 2 292 |
| 19 | Matn yo'q... | 1 694 |
| 20 | Matn yo'q... | 1 739 |
