መጽሐፍቶችን በpdf📚
"እንኳን ደህና መጣችሁ"Welcome! በpdf(በሶፍት ኮፒ) ለማንበብ ራሳችንን እናስለምድ! ፨ተራ ነገር በመስራት የሚባክነውን ጊዜያችንን በንባብ ላይ ስናውለው ከራሳችን አልፈን ለብዙዎች የመለወጥ ምክንያት እንሆናለን፡የንባብ ባህላችንን እናዳብር! ባለንበት ራሳችንን በእውቀት እንገንባ! ፨በዚህ ቻናል የተለያዩ መፅሐፎች፣ጠቃሚ ሀሳቦች፣አፕልኬሽኖች፣አነቃቂ ምስሎች ቀርቦላችኋል አውርደው ይጠቀሙ።
Ko'proq ko'rsatish📈 Telegram kanali መጽሐፍቶችን በpdf📚 analitikasi
መጽሐፍቶችን በpdf📚 (@pdfffb) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 031 obunachidan iborat bo'lib, Kitoblar toifasida 2 445-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 243-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 031 obunachiga ega bo‘ldi.
16 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 675 ga, so‘nggi 24 soatda esa 22 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 18.88% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 5.49% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 2 836 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 825 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 14 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“"እንኳን ደህና መጣችሁ"Welcome!
በpdf(በሶፍት ኮፒ) ለማንበብ ራሳችንን እናስለምድ!
፨ተራ ነገር በመስራት የሚባክነውን ጊዜያችንን በንባብ ላይ ስናውለው ከራሳችን አልፈን ለብዙዎች የመለወጥ ምክንያት እንሆናለን፡የንባብ ባህላችንን እናዳብር! ባለንበት ራሳችንን በእውቀት እንገንባ!
፨በዚህ ቻናል የተለያዩ መፅሐፎች፣ጠቃሚ ሀሳቦች፣አፕልኬሽኖች፣አነቃቂ ምስሎች ቀርቦላችኋል አውርደው ይጠቀሙ።”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 17 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Kitoblar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 17 Iyun | +12 | |||
| 16 Iyun | +22 | |||
| 15 Iyun | +32 | |||
| 14 Iyun | +18 | |||
| 13 Iyun | +26 | |||
| 12 Iyun | +13 | |||
| 11 Iyun | +9 | |||
| 10 Iyun | +26 | |||
| 09 Iyun | +19 | |||
| 08 Iyun | +24 | |||
| 07 Iyun | +30 | |||
| 06 Iyun | +22 | |||
| 05 Iyun | +46 | |||
| 04 Iyun | +25 | |||
| 03 Iyun | +23 | |||
| 02 Iyun | +28 | |||
| 01 Iyun | +30 |
| 2 | ሰኔ 13/ 2018 ዓ.ም (ቅዳሜ ከ8:00 ጀምሮ)
ሁላችሁም በነጻ ተጋብዛችኋል!
ነገረ መጻሕፍት!
ተጋባዥ እንግዳ:- ሲሳይ ንጉሡ
የተመረጠው መጽሐፍ:- ሣልሳዊ ልደት
አዘጋጅና አቅራቢ:- እንዳለጌታ ከበደ
አሰናጅ:- ዛጎል የመጻሕፍት ባንክ
የዝግጅት ቦታ:- FSS. አዳራሽ
በዝግጅቶቻችን ላይ በአካል በመገኘት መሳተፍ ለምትፈልጉ አድራሻችን:- ቀበና፣ ካቶሊክ፣ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን አቅራቢያ፣ ወደ ሳንፎርድ ትምህርት ቤት በሚወስደው መንገድ፣ ባማ አዲስ ሕንፃ አጠገብ፣ FSS አዳራሽ ሲሆን፣ የመገኛ ቦታው Google Map link:-
https://maps.app.goo.gl/2n1myQXCCaTteCw69?g_st=ic
ለበለጠ መረጃ:- 0976066720
0900651010 | 908 |
| 3 | Matn yo'q... | 716 |
| 4 | የቅናት ዛር - ሲሳይ ንጉሡ .pdf | 721 |
| 5 | 👌🏾 | 699 |
| 6 | ትንሳኤ - ሲሳይ ንጉሱ.pdf | 699 |
| 7 | ረቂቅ አሻራ @ETHIO_PDF_BOOKS.pdf | 711 |
| 8 | ደራሲ ሲሳይ ንጉሡ
1. የህይወት መጀመሪያና ትምህርት
የትውልድ ቦታ: ሲሳይ ንጉሱ የተወለደውና ያደገው በጎንደር አካባቢ ነው።
ትምህርት: የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ካጠናቀቀ በኋላ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቋንቋና ስነ-ጽሁፍ (Language and Literature) ዘርፍ ተመርቋል።
2. ወደ ስነ-ጽሁፍ አለም መግባትና ታዋቂነት
ሲሳይ ንጉሱ በኢትዮጵያ ስነ-ጽሁፍ ውስጥ ስሙ በጉልህ መነሳት የጀመረው በ1970ዎቹና 80ዎቹ አጋማሽ አካባቢ ባሳተማቸው ድንቅ ልብ ወለዶቹ ነው። በተለይ በወቅቱ የነበረውን ወጣት ማህበረሰብ ስነ-ልቦና፣ የከተማ ኑሮንና ፍቅርን የዳሰሰበት መንገድ ትልቅ ተቀባይነትን አትርፎለታል።
3. ታዋቂ ስራዎቹ
ሲሳይ በርካታ ተነባቢ መጽሐፍትን ለንባብ ያበቃ ሲሆን፣ ከነዚህም መካከል ዋና ዋናዎቹ፡-
ሲሳይ ንጉሱ የ11ኛ ክፍል ተማሪ እያለ “ጉዞው” የተሰኘ ድረሰቱን የመጀመሪያ ስራው አድርጎ አሳትሟል፡፡ይህንን ጨምሮ 6 ያህል መፅሃፍትን እስካሁን ለአንባቢያን አድርሷል፡፡
“ሰመመን” የተሰኘው የረጅም ልብወለድ ድርሰቱ ከፍተኛ ተነባቢነትን በአጭር ጊዜ ውስጥ ያገኘለት ስራው ሲሆን በወቅቱም 60 ሺ ያህል ቅጂዎች ተሸጠውለታል፡፡በ1978 ዓ.ም የታተመው እና 378 ገፆች ያሉት “ሰመመን” በዩኒቨርስቲ ህይወት ዙሪያ እና በፍቅር ታሪክ ላይ ያተኩራል፡፡ መፅሃፉ የተፃፈው ደራሲ ሲሳይ ንጉሱ በአስመራ ዩኒቨርሰቲ የ 3ኛ አመት ተማሪ እያለ ነበር፡፡
1. ጉዞው
2. ሰመመን
3. ግርዶሽ
4. ትንሳኤ
5. የቅናት ዛር
6. ረቂቅ አሻራ
ደራሲ ሲሳይ ንጉሱ በ1991 ዓ.ም ከኢትዮጵያ ስነ ጥበባት እና መገናኛ ብዙሃን ሽልማት ድርጅት በስነ ፅሁፍ ዘርፍ ተሸላሚ ነበር፡፡በወቅቱም 20 ሺ ብር፣ የክብር ዲፕሎማ እና የወርቅ ሜዳሊያ ተበርክቶለታል፡፡
4. የአጻጻፍ ስልቱ ልዩ ባህሪ
"የሲሳይ ንጉሱ አጻጻፍ ገጸ-ባህሪያትን በጥልቀት የመሳል፣ አንባቢን በቀላሉ የመሳብ እና ታሪኩን ልክ በዓይን እንደሚታይ ፊልም የማቅረብ ከፍተኛ ችሎታ አለው።"
ቋንቋው ቀላል፣ ስሜትን የሚነካ በመሆኑ ስራዎቹ ዛሬም ድረስ በየዘመኑ ባሉ ወጣቶች ዘንድ በከፍተኛ ጉጉት ይነበባሉ።
በአጠቃላይ ሲሳይ ንጉሱ በኢትዮጵያ ዘመናዊ ስነ-ጽሁፍ እድገት ውስጥ የራሱን አሻራ ያሳረፈ፣ በተለይም በልብ ወለድ ዘውግ (Novel genre) ውስጥ ስሙ በቀዳሚነት ከሚነሱ ጥቂት ተጽዕኖ ፈጣሪ ደራሲያን አንዱ ነው።
ሁሌም ማንበብ! | 822 |
| 9 | Matn yo'q... | 1 712 |
| 10 | የፀሐይ እልፍኝ
በትላንትናው ዕለት እኔና ባልደረቦቼ ስድስት ኪሎ በሚገኘው «የፀሐይ እልፍኝ» የፀሐይ አሳታሚ የምርምር ማዕከል የጉብኝትና ፍሬያማ ውይይት አድርገናል።
የፀሐይ አሳታሚ መሥራችና ባለቤት ለሆነው ወንድማችን ኤልያስ ወንድሙ እና ባለቤቱ ታዋቂዋ አርቲስት ብሩክታዊት ጌታሁን (ቤቲ ጂ) እና ባልደረቦቻቸው ላደረጉልን ሞቅ ያለ አቀባበል ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
ፀሐይ አሳታሚ የሀገራችንን ታሪክ፣ ባህል እና ቅርስ ሰንዶ ለትውልድ የሚያስተላልፍ ዘመን ተሻጋሪ ተቋም ነው። በዓለም ዙሪያ ተበታትነው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ምሁራንን እና ስለ ኢትዮጵያ ያጠኑ የውጭ አገር ተመራማሪዎችን በማፈላለግና በማሰባሰብ ረገድ የሚከተሉትን አንጸባራቂ ሥራዎች አከናውኗል፦
1. አያሌ ቁጥር ያላቸው አዳዲስ መጻሕፍትን በጥራት አሳትሟል።
2. ከገበያ የጠፉ ነባርና ንጥር ሥራዎችን (classics) እንደገና እያሳተመ አሰራጭቷል።
3. "International Journal of Ethiopian Studies" እንዲሁም "Ethiopian Journal of Religious Studies" የተሰኙ ዓለም አቀፍ ጥናታዊ መጽሔቶችን ያሳትማል።
4. በውጭ አገራት የመጻሕፍት አውደ-ርዕዮችንና ልዩ ልዩ ከጥበብና ከመጻሕፍት ጋር የተገናኙ ዝግጅቶችን ያቀርባል።
5. የአገር መሪዎችን (ከነገሥታቱ ጀምሮ እስከ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ድረስ) መጻሕፍት በጥራት አሳትሞ ለንባብ አብቅቷል።
6. በግል ደረጃም በርካታ ጠቃሚ ሥራዎችን አዘጋጅቶ አሳትሟል።
በአሜሪካ አገር ከ28 ዓመታት በፊት የተቋቋመው ፀሐይ አሳታሚ፣ በአሁኑ ወቅት በአገራችን በአንድነት ፓርክ ውስጥ እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ ግቢ (ታሪካዊው የካቲት 12 መታሰቢያ ትይዩ በሚገኘው የፎረም ሕንጻ ሥር) የፀሐይ የምርምር ማዕከል ከፍቶ በመሥራት ላይ ይገኛል።
በቀጣይም ኢትዮጵያን የአፍሪካ የዕውቀት ማዕክል የሚያደርጉና አገራችንንም ብቃት የሚያግዙ ስራዎችን እየሰሩ ይገኛል።
የአቶ ኤልያስ ባለቤትና ሁላችንም የምናከብራት አርቲስት ብሩክታዊት ጌታሁን (ቤቲ ጂ) በበኩሏ በረቂቅ የጥበብ ሥራዎቿ አገሯን በዓለም አደባባይ እያስጠራች ትገኛለች። እዚህ ላይ አንድ ወንድሜ የነገረኝን ገጠመኝ ማጋራት ይገባኛል። "Kinokuniya" የተባለ ዓለም አቀፍ የጃፓን የመጻሕፍት መደብር አለ፤ ይህ ወንድሜ በሲንጋፖር በሚገኘው ቅርንጫፍ ውስጥ መጻሕፍት እየመረጠ ሳለ የቤቲ ጂ ሙዚቃ በመደብር ውስጥ ይሰማና በደስታ ይፈነጥዛል። "በሰው አገር፣ ያውም በትልቅ የመጻሕፍት መደብር ውስጥ የአገሬን ሙዚቃ ስሰማ ሰውነቴን ነዘረኝ፤ ደስታዬን የሚጋራኝ ሰው በአቅራቢያዬ በማጣቴ ግን ቆጨኝ" ብሎ በስልክ ነግሮኛል።
ፀሐይ አሳታሚ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ ከዩኒቨርሲቲያችን ጋር የአጋርነት ስምምነት ተፈራርሞ እየሠራ ይገኛል። በቅርቡ የጀመርነው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ (UoG Press) እውን መሆንና በቀጣይም ፕሬሱ የሚጠበቅበትን አገራዊና ሳይንሳዊ ተልዕኮ በስኬት እንዲወጣ የፀሐይ አሳታሚ አጋርነትና ተሞክሮ ወሳኝ ነው።
አቶ ኤልያስ ወንድሙና ባለቤቱ አርቲስት ብሩክታዊት (ቤቲ ጂ) ላደረጉልን አቀባበልና ፍሬያማ ውይይት በራሴና በባልደረቦቼ ስም ከልብ አመሰግናለሁ!
© አስራት አፀደወይን
ሁሌም ማንበብ! | 1 513 |
| 11 | Matn yo'q... | 1 520 |
| 12 | Trauma has a way of turning shame into an inner voice that says:
“You’re too sensitive.”
“You’re too much.”
“You’re difficult.”
“You’re a burden.”
“You’ll never be enough.”
Those beliefs didn't appear out of nowhere.
They're often the echoes of environments where you had to shrink yourself, stay quiet, overperform, people-please, or blame yourself just to survive.
That is not the same thing as truth.
Healing begins when you reject the shame and labels that were never yours to carry.
You are not “too sensitive” for being affected by what hurt you.
You are not weak for needing support.
You are not difficult for needing safety, boundaries, rest, or care.
You were injured.
And you deserve the space to heal without carrying shame that never belonged to you in the first place.
Engaged in reading always! | 1 795 |
| 13 | Matn yo'q... | 1 899 |
| 14 | 👉ቡና መጀመሪያ ላይ እንደ ምግብ ነበር የሚጠቀሙት
ቡና እንደ መጠጥ ከመታወቁ በፊት፣ ሰዎች የቡና ፍሬን ከቅቤ ጋር በመለወስ እንደ "ኢነርጂ ቦል" ለረጅም ጉዞ እና ለጥንካሬ ይበሉት ነበር። ዛሬም ድረስ በአንዳንድ የኢትዮጵያ አካባቢዎች "ቡና ቁርስ" ላይ ይህ ባህል ይስተዋላል።
👉በአለም ላይ ከውሃ ቀጥሎ በብዛት የሚጠጣ መጠጥ ነው
በአለም ዙሪያ በየቀኑ ከ2 ቢሊዮን ሲኒ በላይ ቡና ይጠጣል። ከነዳጅ (Oil) ቀጥሎም በአለም አቀፍ ግብይት ላይ ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዝ ምርት ነው።
👉ቡና ፍራፍሬ እንጂ ጥራጥሬ አይደለም
ምንም እንኳን "የቡና ፍሬ" ብንላቸውም፣ በሳይንሳዊ አነጋገር ቡና የቤሪ አይነት ፍሬ ውስጥ የሚገኝ ዘር ነው። ራሱ የቡና ፍሬው ሲበስል ጣፋጭነት አለው።
👉ሌሎች አጫጭር እውነታዎች፡-
ረጅም እድሜ፡ ቡና ለልብ ጤና እና ለተለያዩ በሽታዎች መከላከያነት ጠቃሚ የሆኑ አንቲ-ኦክሲዳንቶች አሉት።
ቡናን ማሽተት፡ አንድ ጥናት እንደሚለው ቡናን መጠጣት ብቻ ሳይሆን ሽታውን ማሽተት እንኳ አንጎላችን እንዲነቃቃ ያደርጋል።
ውድ ቡና፡ በዓለም ላይ በጣም ውድ የሚባሉት የቡና አይነቶች (ለምሳሌ 'Kopi Luwak') የሚመረቱት እንስሳት የቡናውን ፍሬ በልተው ካስወጡት በኋላ ተለቅሞ የሚዘጋጀው ነው።
ሁሌም ማንበብ! | 1 876 |
| 15 | Matn yo'q... | 2 059 |
| 16 | Real power is not about controlling the world.
It is about learning how to control yourself.
Your mind. Your emotions. Your body. Your time. Your habits. Your focus. Your standards. Your environment. Your purpose.
Because if your inner system is not trained, even the right opportunities can get blocked by old patterns.
You can know what to do and still not do it.
You can want more and still keep returning to the same version of yourself.
You can have ambition, goals, and potential — but still feel like something inside keeps pulling you back.
That is often where self-sabotage begins. Not because you are weak.
But because there may be hidden inner blocks, subconscious rules, fear, guilt, shame, limiting beliefs, or old identity patterns running underneath the surface.
Inside Mental Fitness Gym, I created the 3-Phase Self-Sabotage Reset System to help you identify what’s holding you back, reset the inner block, and protect the breakthrough.
Engaged in reading always! | 2 282 |
| 17 | እንኳን ጨፋሪወቹ ጨፍጫፊወቹም ኢትዮጵያዊያን ናቸው!
ሁልጊዜ ንፁሀን በግፍ በተገደሉ ቁጥር ብዙሃኑ ያዝናል ይንገበገባል፣ የሰብዓዊነት የፍትህ ጥያቄ ያነሳል። አልፎ አልፎ እንደ ዘፈን እና ሌላ የደስታ መግለጫ የሆኑ ጉዳዮች ከእንደዚህ ያለ ሐዘን ጋር ቢገጣጠሙ እንኳን ባህላችን ብቻ ሳይሆን ሰብዓዊነትም ግድ ብሎን ፕሮግራም ይሰረዛል አልያም ይራዘማል።
ግን ደግሞ እንደትላንቱ ያለ ብሽሽቅ የሚመስል ድርጊት ከሐዘኑ ባለፈ የሚነግረን እንደ ህዝብ የደረሰብንን የሰብዓዊነት መናጋት፣ እንደ መንግስት ያቃተንን ሐላፊነት ያለመወጣት ድክመት በጨረባ የማድበስበስ ባህሪ ነው። የሰው ልጅ ሕይወት በግፍ ሲቀጠፍ አብሮ ማዘን፣ ቆም ብሎ ማሰብ እና ለሟቾች ክብር መስጠት የሰው ልጅነት መሠረታዊ መገለጫ ነው። አንድ የጥበብ ሰው ሲሞት ከዳር እስከ ዳር ቀልድና የእለት ጉዳዮን ትቶ ሶሻል ሚዲያውን በሐዘን መግለጫ የሚያጥለቀልቅ ሕዝብ ላይ ምላስ አውጥቶ የማላገጥ ያህል የተደረገው ነገር ይቀፋል።
ሰው ሲሞት ለቅሶ አለመድረስ ይቻላልኮ፤ ግን የሟች በር ላይ ቁሞ እስክስታ መውረድ ፀያፍ ድርጊት ነው!! ንፁሐን አርሲ ላይ በገፍ ተጨፍጭፈዋል። አንዴ ሁለቴ ሶስቴ አይደለም... በተደጋጋሚ! መንግስት ተቀዳሚ ተግባሩ የሆነውን ደርሶ ለዜጎቹ የደህንነት ዋስትና መስጠትና መታደግ አልቻለም! ይሁንና አገር አቀፍ የሐዘን ቀን ማወጅ፣ ቁጭ ብሎ ተነጋግሮ በቀጣይ የማያዳግም ውሳኔ አስተማማኝ የደህንነት ዋስትናና ህጋዊ ተጠያቂነት ማስቀመጥ የሚገባው አካል የጭፈራ ስፖንሰር መሆኑና "ሁሉ ሰላም ነው" በሉልኝ ማለት ያሳዝናል።
ኢትዮጵያዊ ነን ፣ ለኢትዮጵያ ማሰብ ከእኛ ወዲያ ላሳር ማለት ብቻውን ምንድነው? ገዳዮቹም'ኮ ኢትዮጵያዊያን ናቸው!! "ማንነን" የሚለውን የሚወስነው "ምን እያደረግን ነው " በሚለው ነው።
አሁንም አስተማማኝ የደህንነት ዋስትና ለዜጎች፣ አሁንም ፍትህ
© አሌክስ አብርሃም
ሁሌም ማንበብ! | 2 486 |
| 18 | Matn yo'q... | 2 804 |
| 19 | ሰው ሲሸነፍ
ማሸነፍ ምንድነው?
የምኞት አዝመራ
የደስታ መከር፤
የታጨደ ጣጣ
የተወቃ ችግር፤
የሞተ መከራ፤
የሚነድ እሳት ነው ተዳፍኖ የበራ።
እያደር ጠፊ ነው፤
እያደር ቀሪ ነው ሲቆይ ይሰለቻል፤
ዋጋው ይቀነሳል።
ሁልጊዜ በማግኘት፤
ዘወትር በማሸነፍ ዘወትር በመመከት፤
በመግዛት በመቅጣት፤
ደስታ አይገኝም።
ሌላ ይፈልጋል የሰው ልብ አይጠግብም።
ለጥቅሙ የሚያስብ የተስገበገበ፤
መንገዱን የማያቅ ግቡ የጠበበ፤
ስስታም ይሆናል
ለፍቶ ጥሮ ግሮ ሲያጋጥመው ዕድል።
ዕረፍት አያገኝም።
ሲያስብ፣ ሲያጠነጥን፣ ሲታትር፤ ሲደክም፤
አንዱን በመጨረስ መጥኖ ሌላውን፤
ያንን በመሰልቸት ሲጀምር አዲሱን፤
ያቅበዘብዘዋል፤
ትዕግሥት ይነሳዋል።
ትንሽ መሰናክል እሾህ መንገዱ ላይ፤
የኑሮ ሕመም ነው የሕይቱ ሥቃይ።
ያገባዋል እልክ ደሙን አስቆጥቶ፤
ንዴቱን አምጥቶ።
ይተዋል ይሉኝታን ከግቡ ለመድረስ
ወዲያ ወዲህ ብሎ ኃይሉን እስኪጨርስ።
በመሸነፍም ነው፤
ሰው ደስታ ያለው።
በመተው በመርሳት፤
በመልቀቅ በማጣት፤
በመሸሽ በመፍራት።
ወደፊት ከመሔድ አውቆ በማፈግፈግ፤
ከማሰብ ለብዙ ጥቂት በመፈለግ፤
በማነስ ከማደግ።
በመጣል ከማንሣት፤ በመስጠት ከመውሰድ፤
በማልቀስ ከመሣቅ በመቅረት ከመሔድ፤
ከመውጣታት በመውረድ።
ከመልበስ መታረዝ፤
ከማምለጥ በመያዝ።
ክብርን ለመጠበቅ ደፍሮ ከመናገር፤
አንገት በማቀርቀር።
በመዋረድና በችግር ተጎድቶ፤
በመውደቅ ተገፍቶ፤ በመናቅ ተጠልቶ፤
በሐዘን፤ በድካም፤ በሕመም፤ ባርምሞ፤
አግኝቶ በመስከር በመሻር ተሹሞ፤
ያውቃል ማ መሆኑን፤
ይረዳል አቅሙን።
የሕይወት ለውጥ ነው ያለ በኑሮ ላይ፤
እንደ ቀን፤ እንደ ሌት፤ እንደ መሬት ሰማይ፤
እንደ ውሀ እንደሳት እንደ ልቅሶ ሣቅ፤
እንደርጥብ ደረቅ፤
ሁሉም ተለውጦ አንጻሩን ይይዛል፤
የሚሮጠው ጊዜ ጥቂት ይታገሣል።
ሰዓቱ ይቆማል፤
ደቂቃው ይተኛል።
ይሸፈናል ወሩ፤
ይታሰራል ቀኑ፤
ቀስ ይላል ዘመኑ።
© ገብረክርስቶስ ደስታ
ሁሌም ማንበብ! | 2 794 |
| 20 | Matn yo'q... | 2 912 |
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
