መጽሐፍቶችን በpdf📚
"እንኳን ደህና መጣችሁ"Welcome! በpdf(በሶፍት ኮፒ) ለማንበብ ራሳችንን እናስለምድ! ፨ተራ ነገር በመስራት የሚባክነውን ጊዜያችንን በንባብ ላይ ስናውለው ከራሳችን አልፈን ለብዙዎች የመለወጥ ምክንያት እንሆናለን፡የንባብ ባህላችንን እናዳብር! ባለንበት ራሳችንን በእውቀት እንገንባ! ፨በዚህ ቻናል የተለያዩ መፅሐፎች፣ጠቃሚ ሀሳቦች፣አፕልኬሽኖች፣አነቃቂ ምስሎች ቀርቦላችኋል አውርደው ይጠቀሙ።
Ko'proq ko'rsatish📈 Telegram kanali መጽሐፍቶችን በpdf📚 analitikasi
መጽሐፍቶችን በpdf📚 (@pdfffb) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 16 158 obunachidan iborat bo'lib, Kitoblar toifasida 2 245-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 079-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 16 158 obunachiga ega bo‘ldi.
28 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 796 ga, so‘nggi 24 soatda esa 8 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 21.60% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 5.73% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 488 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 925 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 22 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“"እንኳን ደህና መጣችሁ"Welcome!
በpdf(በሶፍት ኮፒ) ለማንበብ ራሳችንን እናስለምድ!
፨ተራ ነገር በመስራት የሚባክነውን ጊዜያችንን በንባብ ላይ ስናውለው ከራሳችን አልፈን ለብዙዎች የመለወጥ ምክንያት እንሆናለን፡የንባብ ባህላችንን እናዳብር! ባለንበት ራሳችንን በእውቀት እንገንባ!
፨በዚህ ቻናል የተለያዩ መፅሐፎች፣ጠቃሚ ሀሳቦች፣አፕልኬሽኖች፣አነቃቂ ምስሎች ቀርቦላችኋል አውርደው ይጠቀሙ።”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 29 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Kitoblar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 29 Iyul | +13 | |||
| 28 Iyul | +8 | |||
| 27 Iyul | +27 | |||
| 26 Iyul | +26 | |||
| 25 Iyul | +45 | |||
| 24 Iyul | +21 | |||
| 23 Iyul | +37 | |||
| 22 Iyul | +15 | |||
| 21 Iyul | +36 | |||
| 20 Iyul | +26 | |||
| 19 Iyul | +7 | |||
| 18 Iyul | +41 | |||
| 17 Iyul | +28 | |||
| 16 Iyul | +25 | |||
| 15 Iyul | +29 | |||
| 14 Iyul | +31 | |||
| 13 Iyul | +27 | |||
| 12 Iyul | +18 | |||
| 11 Iyul | +40 | |||
| 10 Iyul | +25 | |||
| 09 Iyul | +24 | |||
| 08 Iyul | +27 | |||
| 07 Iyul | +19 | |||
| 06 Iyul | +40 | |||
| 05 Iyul | +23 | |||
| 04 Iyul | +33 | |||
| 03 Iyul | +10 | |||
| 02 Iyul | +29 | |||
| 01 Iyul | +25 |
| 2 | Great Expectations
1. The Bildungsroman (Coming-of-Age Novel)
At its core, Great Expectations is a classic Bildungsroman—a story tracking the psychological, moral, and social growth of the protagonist, Pip, from boyhood to maturity.
The Trajectory: We follow Pip from his humble origins as an impoverished orphan in the misty Kent marshes, through his moral compromise as a pretender to the "gentleman" class in London, to his ultimate redemption and realization of true worth.
2. Victorian Social Realism & Satire
Dickens uses social realism to expose the deep flaws of Victorian class structure, wealth, and the legal system.
Critique of Ambition: The novel sharpens its critique on the Victorian obsession with social climbing. Pip’s pursuit of becoming a "gentleman" leads him to reject the genuine affection of those who truly love him, such as Joe Gargery.
Satirical Characterization: Through grotesque and memorable figures like the grandly tragic Miss Havisham (frozen in her decaying wedding dress) and the cold legal figure Jaggers, Dickens satirizes institutional hypocrisy and social decay.
3. Gothic Elements
The novel borrows heavily from the Gothic tradition, creating a moody, atmospheric landscape that mirrors Pip’s inner turmoil.
Atmosphere & Imagery: The eerie, desolate marshes at the start, the terrifying encounter with the escaped convict Abel Magwitch among the graves, and the rotting, cobwebbed interior of Satis House all evoke a haunting, Gothic dread.
4. Retrospective First-Person Point of View
The story is told entirely in the first person by an older, wiser Pip looking back on his youth.
Narrative Irony: This creates a double perspective: the naive, impressionable young Pip experiencing events in real-time, balanced by the mature narrator who looks back on his past foolishness, snobbery, and guilt with deep regret and self-awareness.
5. Serialized Structure
Originally published as a weekly serial in Dickens's periodical All the Year Round (1860–1861), the literary form was shaped by the demands of installment publishing.
Pacing & Cliffhangers: Each chapter or section was engineered with tight plot twists, suspenseful scene endings, and interconnected character arcs to keep readers returning every week.
Engaged in reading always! | 1 058 |
| 3 | 🤌🏾 | 929 |
| 4 | ባለሱቁ
አንድ የሰፈራችን ባለሱቅ የሆነ ቀን በበሩ ሳልፍ "ወንድሜ" ብሎ በአክብሮት ጠራኝና እዚህ ሰፈር ነው የምትኖረው? ብሎ ጠየቀኝ! "አወ" አልኩት እንዴት ረሳኝ ብየ በመገረም! የረዢም አመት ደንበኛየ ነበር። ቀጠል አድርጎ
ሲጃራ ታጨሳለህ እንዴ?
አይ አላጨስም
አቁመህ ነው?
አይ ከመጀመሪያውም አላጨስም
ጫትስ ትቅማለህ እንዴ?
አይ አልቅምም
አቁመህ ነው?
ቅሜ አላውቅም! ለምንድነው ግን የምትጠይቀኝ አልኩ ገርሞኝ ። ጥያቄየን ችላ ብሎ
እ...የስልክ ካርድ ከኔ ትወስድ ነበር እንዴ?
አወ (ደግሞ እውነቴን ነው ከሱ ሱቅ ነበር የምገዛው)
ባለስንት ነበር የምትገዛው?
ባለመቶም ፣ ባለ ሃምሳም ...ባለ ....
ተወው አስታወስኩ! የመቶ ብር ካርድ አለብህ ስምህን መዝገብ ላይ አይቸዋለሁ
ማነው ስሜ ?
ስምህ ምን ያረጋል ጋሸ? ዋናው ካርዱ ነው ....
በኋላ ስሰማ ይሄ ሚስኪን ባለሱቅ አእምሮውን ታሞ አማኑኤል ሆስፒታል ገብቶ ነበር አሉኝ። ሚስቱን ነበር ሱቁ ውስጥ ለረዢም ጊዜ የማያት! እና ዘለግ ላለ ጊዜ ታክሞ ከአማኑኤል ተሽሎት ወጣ። ሁሉ ነገር ተስተካክሎ አንድ ነገር ብቻ ትንሽ ልክ አልመጣለትም እየተባለ ይወራል። ማንኛውም በሱቁ በር የሚያለፍ ሰው ዱቤ ወስዶ ያልከፈለው ይመስለው ስለነበር እያስቆመ አጭር መስቀለኛ ኢንተርቪው ያደርጋል። ከምንም በላይ ግን ያሳቀቀን እትየ ማርታን ጠርቶ ጠየቃት የተባለው ነገር ነው። እትየ ማርታ ዕድሜዋ 40 የተሻገረ ዘናጭ ሴት ናት!
"እህቴ ይቅርታ እዚህ ሰፈር ነሽ?" አላት
አወ ምን ልርዳህ? አለች በሚያምር ፈገግታ
ፔሬድ ማየት አቁመሻል እንዴ ወይስ ታያለሽ ? አበደች ...
"ስድ ምናባህ አገባህ?" በኋላ ባሏ ተነግሮት ሊያናፍጠው ወደሱቁ ሲሄድ "ሞዴስ በዱቤ ወስዳ ያልከፈለችኝ መስሎኝ ነው ጋሸ ! ግን ከመጣህ አይቀር ታጨሳለህ እንዴ....."
©አሌክስ አብርሃም
ሁሌም ማንበብ! | 1 533 |
| 5 | ኑ'ማ | 1 787 |
| 6 | “ምነው አምና በሞትኩ፥ እንዲያ እንዳማረብኝ!?”
ዝምታ ይረብሸኛል።
ለዚያም ነው፥ መንገድ ስሔድ መጽሐፍ ይዤ የምዞረው፣ ሁሌም ጆሮዬ ውስጥ ‘ኤርፎን’ የምወትፈው፣ ልተኛ ስል፥ ያለችውን ፀጥታ እንኳን ላለማስተናገድ፥ የኾነ ነገር ከፍቼ ነው የምተኛው ...
በዝምታ ውስጥ ከመኾን፥ ዝም ብሎ ከሚቀደደው ቱሪናፋው ከቤ ጋር ብውል እመርጣለሁ። ዝምታ ሽሽት የማልደውልበት፣ የማላነበው፣ የማልሰማው ዜና የለም።
ዝምታ እፈራለሁ!
መንገድ ስሔድ… ስቀመጥ!
የማነበው መጽሐፍ ካልያዝኩ፣ ስራመድ የምሰማበት ኤርፎን ካልወተፍኩ…. ፖሊሶች አቻኩለው ከቤት አስወጥተውኝ ነው የሚሆነው!
ዝምታ እፈራለሁ!
አስታውሳለሁ፤ 12ኛ ክፍል ነበርኩ። ሙዚቃ ከፍቼ እያጠናሁ፥ የአጎቴን የለቅሶ ሳግ ሰምቼ ደንግጬ “ምነው አመመህ?” አልኩት፤ እሱ ሙዚቃ እየተጫወተበት ያለውን ‘ቴፕ’ ዐየት አድርጎ፥ ወደ ጣርያው አፍጥጦ፣ እምባው ቁልቁል ወረደ!
አሞት መስሎኝ ነበር… ከዚህ በፊት ሲያመው ያቃስታል፤ ሲብስበትም ማስታገሻ ይውጣል እንጂ አያለቅስም ነበር።
አጎቴ ጥቁር ነው፤ ፊቱ ክስክስ ያለ… ሲያወራ ግን እንደሚታየው ኮስተር ያለ ማንነት እንደሌለው የሚያስታውቅበት፥ ቁጥብ፣ ደስ የሚል ሰው ነው።
ልጅ እያለሁ የገዛልኝን ቼኮሌት እና ብስኩት፥ ታሞ አልጋ ሲይዝ ሲጋራ እያመጣሁ ክሼዋለሁ ።
ቤቢ፥ “ያቺን ነገር አትገዛልኝም?” ይላል፤ እገዛለታለሁ። ሲጋራውን በእጁ እያገላበጠ ካያት በኃላ፥ አፉ ላይ እንዳለ እለኩሰለታለሁ።
ዐብሮን ማንም በሌለበት ጊዜ ሁሉ፥ “አትብላ” የተባለውን፣ “አትንካ” የተባለውን ሁሉ እሰጠው ነበር።
እያጠናሁ ስለነበረ፣ ሲያለቅስ አይቼው ስለማላውቅ፣ ደንግጬ ስለነበረ፣… ዘፋኟን ባውቃትም ግጥሙን አላጤንኩትም ነበር፤ ዘፈኑ እንደረበሸው ሲገባኝ፥ ወተት እንደገነፈለበት ሰው፥ ስበር ሔጄ የቴፑን ሶኬት ነቀልኩለት ።
የማባብልበት መንገድ ስለጠፋኝ፥ “ምግብ ላምጣልህ?”፤ “ውሃ ላምጣ” አልኩት። ጣርያ ጣርያ ዕያየ ዝም ሲለኝ ከፊቱ ዞር አልኩለት።
በዚያው ሰሞን፣ ሲብስበት ሐኪም-ቤት ደግመው አስገቡት፤ አልቆየም፤ ሞተ!
የኾነ ቀን ...
አባቴ፥ ስለወንድሙ ቸርነት፣ ዘናጭነት፣ ስፖርተኛነት፣ ሰው ወዳድነት፣ አለኝታነት፣ ስለጓደኞቹ ብዛት፣… ሲተርክልኝ ያስለቀሰቺው ዘፋኝ፥ የዝና ነጋሽ ትዝ አለቺኝ።
ያስለቀሰውን የዘፈን ካሴት ከፈትኩት፤ ሆዱን ያባባው “ገዳሙ” ዘፈን ጋ ደረስኩ።
እስክስታ ሚያስመታ ‘ሪትም’ ያለው ዘፈን ነው
“.........አሆዬ እኔ ላንተ ብዬ፣ መጣሁኝ ጠቅልዬ
አዬዬ፥ እኔ ላንቺ ብዬ፥ መጣሁኝ ጠቅልዬ
“እሀሀ ገዳሙ፥ አሀሀ ገዳሙ
እሀሀ ገዳሙ፥ አሀሀ ገዳሙ
“አላስኬድ፣ አላስኬድ አለኝ፥ ይሄ ጫማ
እኔም ልበቢስ ነኝ፥ ቢመክሩኝ አልሰማ
“እሾህ ብቻ ኾኖ፥ እግሬን ብዳብሰው
እንዴት መራመጃ፥ መሔጃ ያጣል ሰው?
“ኧረግ እናናዬ፣ አረግ እናናዬ
ኧረግ እናናዬ፣ አረግ እናናዬ
“አሄ አሄ አሄ አሄ
አሄ ኡሁ
“ይወዘውዘኛል፥ ይወዝውዝ አባቱ
እህል አሸክሞኝ አርጎኝ ጎረቤቱ
አሞኝ፣ አሞኝ ውሎ፥ አሞኝ ሊያድር ነወይ?
እህል ሰርቶ መብላት፥ ጤና ላይሆን ነወይ?
“ምነው አምና በሞትኩ፥ እንዲያ እንዳማረብኝ
መለየት በሽታ፥ እንዲ ሳይጠናብኝ
“ያመኝ የነበረው፥ አያመኝም ተውኩት
ያስታማሚ ነገር ሲቸግር አየሁት
“እህህህ ገዳሙ
ጠይሙ፣ ጠይሙ..........”
ይላል
ከዛ ቀን በኋላ፥ ተረጋግቼ ሥራዬ ብዬ ሰምቼው ዐላውቅም፤ ነገር ግን ሁሉም ስንኞች ልቤ ውስጥ በአግባቡ ከመሰነድ አላዳነኝም
ድንገት ከተከፈተ፥ የሚረብሸኝ ዘፈን ኾነ ....
“ድል ስቀዳጅ፣ ደስ ብሎኝ ስጠጣ፣ እንዳማረብኝ ግደለኝ አስታማሚ ሳታሳየኝ!” ማለት ጀመርኩ። “ያደረ የዋለ በሽታ አትሰጠኝ” እለው ጀመር
“ይህ ዘፈን ምን ያህል ይረብሽሃል?” ስባል “ከዝምታ በላይ!” ማለት ጀመርኩ።
የግጥሙ ኀይል ነው፥ ወይስ የአጎቴ ኹኔታ ሕይወትን እንድፈራት ያደረገኝ?
ሕይወትን ምን ያህል ባካብዳት ነው፥ እያሸነፍኩ እንኳን “ምነው አምና በሞትኩ፥ እንዲያ እንዳማረብኝ…” የምትል ስንኝ የምታሳድደኝ?
ፈሪ ሰው እንዲህ ነው፤
ከ ጠ’መንጃ በላይ ፥ ቃል ያሳድደዋል!
© Adhanom Mitiku
ሁሌም ማንበብ! | 2 276 |
| 7 | 🤌🏾 | 2 569 |
| 8 | ዶክተር እጓለ ገብረ ዮሐንስ
ዶክተር እጓለ ገብረ ዮሐንስ (1905 - 1968 ዓ.ም / 1913 - 1976 እ.ኤ.አ) በኢትዮጵያ ዘመናዊ የስነ-ጽሑፍ፣ የፍልስፍና እና የከፍተኛ ትምህርት ታሪክ ውስጥ ታላቅ ስም እና ጉልህ አስተዋጽኦ የነበራቸው ምሁርና ደራሲ ናቸው።
ዶክተር እጓለ ገብረ ዮሐንስ የተወለዱት በሸዋ ክፍለ ሀገር (ቡልጋ) ነው።
እንደ ብዙዎቹ የዚያ ዘመን ምሁራን፣ መጀመሪያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ባህላዊና መንፈሳዊ ትምህርት (ንባብ፣ ዜማ፣ ቅኔና መጻሕፍት) አጠናቀዋል። ይህም ለቋንቋና ለፍልስፍና ያላቸውን ጥልቅ ፍቅር መሠረት ጣለላቸው።
ዘመናዊ ትምህርታቸውን በውጭ ሀገር በመከታተል በጀርመን ሀገር በፖርቱጋልኛና በፍልስፍና ትምህርት ከፍተኛ የዶክቶሬት (Ph.D.) ዲግሪያቸውን አግኝተዋል።
በወቅቱ «ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ» (የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ) በመምህርነት እና በዲንነት አገልግለዋል። ለተማሪዎቻቸው ከፍተኛ የአስተሳሰብና የፍልስፍና መነቃቃትን ፈጥረዋል።
የአማርኛ ቋንቋ የሳይንስና የፍልስፍና ጽንሰ-ሀሳቦችን መሸከም እንደሚችል በተግባር ያሳዩ ምሁር ነበሩ።
ዶክተር እጓለ በኢትዮጵያ ፍልስፍናና ስነ-ጽሑፍ ውስጥ የሚጠቀሱ በርካታ ድንቅ መጻሕፍትን አበርክተዋል፦
«የከፍተኛ ትምህርት ዘይቤ» (1956 ዓ.ም)፦
ለኢትዮጵያ ተማሪዎች የተጻፈ ድንቅ የአካዳሚክና የጥናት መመሪያ ነው።
ዘመናዊ የጥናት ስልቶችን ከኢትዮጵያ ባህላዊ የእውቀት መቅሰሚያ መንገዶች ጋር በማቀናጀት የቀረበበት ሥራቸው ነው።
«የከበሩ ድንጋዮች»፦
የተለያዩ የፍልስፍና፣ የስነ-ምግባር እና የህይወት እውነቶችን በጥበብና በምሳሌያዊ አነጋገር የሚያብራራ የታወቀ የመጣጥፎች ስብስብ ነው።
«የኢትዮጵያ የእውቀት መንገድ» (የአእምሮ ስራ)፦
የኢትዮጵያን የቆየ የፍልስፍናና የትምህርት ባህል ከዘመናዊ እውቀት ጋር የሚያነጻጽርና አቅጣጫ የሚያሳይ ጥልቅ ምሁራዊ ጽሑፍ ነው።
ሀገር በቀል ፍልስፍና (Indigenous Philosophy)፦ ዶክተር እጓለ የውጭ ሀገር እውቀትን እና ፍልስፍናን ቢማሩም፣ የኢትዮጵያን የራሷን የነገረ-መለኮት፣ የቅኔና የፍልስፍና ሀብት ከዘመናዊው ዓለም ጋር ማያያዝ እንደሚገባ አጥብቀው ያምኑ ነበር።
የአጻጻፍ ዘይቤ፦ የሳቸው የጽሑፍ ስልት ረቂቅ የሆኑ የፍልስፍና ሀሳቦችን በተዋበ፣ ግልጽ እና ጥቁር በሆኑ የአማርኛ ቃላት የመግለጽ ልዩ ችሎታ ነበረው።
ሁሌም ማንበብ! | 2 609 |
| 9 | Matn yo'q... | 2 264 |
| 10 | Contested Issues in Ethiopian Historiography
contested Issues in Ethiopian Historiography (2025), edited by Prof. Bahru Zewde—one of Ethiopia’s most prominent historians—is a collaborative publication produced by the Association of Ethiopian Historians in partnership with the Life & Peace Institute.
The book directly addresses how competing interpretations of Ethiopia’s past fuel contemporary political polarization, ethnic tensions, and national identity debates. Rather than claiming to offer a single, authoritative account, it serves as a scholarly attempt to promote civic dialogue, constructive disagreement, and inclusive historical inquiry.
Literature Context & Core Debates
To understand this volume, an intermediate reader should be familiar with the main fault lines in Ethiopian historical literature:
Ethio-Nationalist (Mainstream) Narrative: Historically focused on the state formation, continuity, and political legacy of northern/highland Ethiopia, emphasizing national unity, resistance to colonial aggression (e.g., the Battle of Adwa), and shared historical ties.
Ethno-Nationalist Counter-Narratives: Emerging heavily since the 1960s, these perspectives critique traditional historiography as exclusionary, arguing that state expansion during the late 19th century marginalized southern and non-Semitic populations, reducing multi-ethnic experiences into a single dominant story.
The Search for Plurality: The volume attempts to bridge this chasm by examining controversial themes—such as the role of various ethnic groups (e.g., the Oromo in national discourses), state formation under Emperor Menelik II, regional vs. central power dynamics, and minority rights under federal arrangements—with academic rigor rather than partisan rhetoric.
Accessibility: Despite handling complex historiographical theory, Bahru Zewde and the contributing scholars present arguments in a structured, analytical manner accessible to readers moving beyond introductory textbooks.
Balance and Civility: It deliberately moves away from "my-nation-at-all-costs" polemical writing toward empirical, nuanced historical debate.
Relevance: It provides essential background for understanding current Ethiopian politics, constitutional debates, and peacebuilding efforts.
Potential Challenges
Context Dependency: Readers need a foundational understanding of key Ethiopian historical figures (e.g., Tewodros II, Menelik II, Haile Selassie) and political eras (the 1974 Revolution, 1995 Constitution) to fully grasp the historiographical arguments being critiqued.
Engaged in reading always! | 2 595 |
| 11 | Contested Issues in Ethiopian Historiography.pdf | 2 399 |
| 12 | እናቴዋ ዛላ!
ትምህርት ቤቶች ዕድሚያቸው የገፉ ልጆችን ከሕፃናት ጋር ቀላቅለው ማስተማር የለባቸውም የሚል ፅኑ እምነት አለኝ። ሕፃናቱን እንዳልነበሩ አድርገው ነው የሚያበላሿቸው፤ አደገኛ ነገር ነው። ወላጆች ይህንን ነገር በዝምታ ማለፍ የለባቸውም፤ ትምህርት ቤቶችም ጭምር። በእኛ ጊዜ የተለመደ ነበር፣ አሁን ግን እንጃ!
አምስተኛ ክፍል ሆነን፣ እንዴት እንደሆነ እንጃ፣ ትልልቅ ልጆች ወደ ክፍላችን ገብተው ከኋላ ተቀመጡ። ድምፃቸው የጎረነነና የተስረቀረቀ ጎረምሶች ነበሩ። ሦስቱ እስከ አሁን አይረሱኝም። መዓዛ የምትባል፣ ማርያም ፊቷ ላይ አራት ቦታ ላይ የሳመቻት ድምቅ ያለች ቀይ ልጅ፣ ሕፃን ሕፃን የማትሸት፣ አጠገባችን ስትቀመጥ ሽቶና የላብ ጠረን ከላይዋ ላይ የሚተን ልጅ፤ ማስቲካ ከአፏ የማይለይ፣ ደግሞ ስታላምጥ «ቀጭ ቀጭ» የምታደርግ...
በመጀመሪያው ቀን «ራሳችሁን አስተዋውቁ» ሲባል፣ «መዓዛ እባላለሁ፤ የምሠራው ቢዝነስ ነው» አለች እየተሽኮረመመች። «ቢዝነስ» የሚለውን ቃል መጀመሪያ የሰማሁት ከእሷ ነው። ደግሞ «ተማሪ ሥራ አለው እንዴ?» ብለናልም።ቆይታ፣ በተለይ የሳይንስ ትምህርትን ትደፍነው ጀመር። «እንዴት ነው የደፈንሽው?» አልናት በልጅነት ጉጉት። «ወንድ ያችን ነገር ካገኘ... ሂሂሂሂ...» ነበር መልሷ። ያች ነገር ምን እንደሆነች ለማወቅ የደከምነው ድካም!
በኋላ፣ እዚያ ፊቱ የማይፈታው የሳይንስ አስተማሪያችን ጋር የሆነ አልጋ ቤት ሲገቡ የአልጋ ቤቱ ባለቤቶች ልጅ አይቶ ነገረን (ጠባብ ከተማ!)። ቆይቶ ሴተኛ አዳሪ እንደነበረች አወቅን። በከተማችን ውስጥ ማታ ማታ ሴቶች ለዚሁ ሥራ የሚቆሙበት ሰፈር አለ፤ እኔ ራሴ አንዴ አየኋት። ከእህቴ ጋር ዘመድ ቤት አምሽተን በታክሲ እየተመለስን ነበር። እያለፍን ያኔ ያየኋት መዓዛ (በውልብታ ቢሆንም) ያ ቀይ ፊቷ ከመንገዱ መብራት ጋር በአእምሮዬ ላይ ታትሞ ቀርቷል። በደንብ የታተመው ደግሞ በግርምት አንገቴ እስኪሰበር ዙሬ በታክሲው መስኮት መንገድ ላይ ወደተደረደሩት ሴቶች ስመለከት፣ መብረቅ የሚያስንቅ የእህቴ ጥፊ ጭንቅላቴን 360 ዲግሪ አዞረው (ቸንቧ!)። ከዚያ ቀን ጀምሮ ሰፈሩን እራሱን ዙሬ ባይ፣ እንደ ሎጥ ሚስት የጨው ዓምድ ሆኜ የምቀር ነው የሚመስለኝ። ሴተኛ አዳሪ ምን እንደሆነችም ያወቅነው ያኔ ነው።
የሚገርመው፣ ብዙ ሴት ተማሪዎች ነፍሳቸው እስኪወጣ መዓዛን ይወዷት ነበር። አረማመድና አወራራቸው፣ ማስቲካ አለማመጥና አሳሳቃቸው ሁሉ እንደ እሷ ሆኖ ነበር። ነፍሳቸውን ይማረውና እሷም፣ የሳይንስ አስተማሪያችንም መሞታቸውን አሥረኛ ክፍል ሆነን ሰማን።
ሁለተኛው ልጅ ታጋይ ነበር፤ ዕድሜው 20 ገደማ የሚሆን። አስተማሪያችንን ሁሉ የሚቆጣ፣ በማትስ ክላስ ሳይቀር «ዲሞክራሲ!» የሚል ነበር። ሰብስቦ ስለ ትግል ያወራናል፦ «አነጣጠርኩና ቃታ ስስብ ጠላት ጭንቅላቱ እንደ ሰርዲን ተነደለ... ደሙ ፊን ብሎ ... አንጎሉ...» እያለ ምድረ ሕፃን ስንቃዥ እናድራለን። አስታውሳለሁ እኔ ራሱ ሌሊት ስጨነቅ ነበር የማድረው። ለቤተሰብ ደግሞ አንናገርም። አፋችሁን ከፍታችሁ ወሬ ብለው እኛው ላይ ይዞሩብናል።
ሦስተኛው ልጅ ከገጠር የመጣ ነበር፤ ያኔ ዕድሜው 17 ወይም 18፣ ኧረ ቀንጭሮ ነው እንጂ 25ም ሊሆን ይችላል። ወሬው ሁሉ የወሲብና የሴት ሰውነት ነው። ደግሞ የክፍል አለቃ ነበር። ((አሁን ላይ ሳስበው ከከሰዓት ፈረቃ በኋላ «የቤት ጠረጋ» የሚባል ፕሮግራም ነበር፤ በየሳምንቱ የመማሪያ ክፍል እናፀደለን። ይሄ ልጅ ደጋግሞ ከኋላ የሚያስቀረው ሴቶችን ብቻ ነበር። ልጆቹ አንዳንዶቹ ያለቅሱ ነበር፣ ግን ጊዜው እንደ አሁኑ አልነበረም። አሁን ላይ አስባለሁ፣ ደፍሯቸው ይሆን? ያኔ ምንም አይገባንም ነበር።))
አንድ ቀን የማትስ አስተማሪያችን ቲቸር ፀሐይ ብላክቦርድ ላይ «ሒሳብ» ብላ ልትጽፍ ስትንጠራራ፣ ድብልቅ ባለ ድምፅ ምላሱን «ጧ» አድርጎ አጣጣመና «እናቴዋ ዛላ!» አለ። ዛላ ማለት ሰውነት፣ አቋም ማለት ነው። ለመደብን! ምድረ ማቲ ሬንቦውንም ቡርስሊንም ስናይ «እናቴዋ ዛላ!» እንላለን።
አንድ ቀን «120» ፕሮግራም ላይ ቴሌቪዥን እያየን፣ የሆነች ገጸ ባህሪ(መሠረት መብራቴ ትመስለኛለች) ስትንጠራራ «እናቴዋ ዛላ!» አልኩ። ከእናቴና ከእህቴ እኩል የተወረወሩ ነጠላ ጫማዎች ጎንበስ በማለቴ በባዶ አየር ላይ ተጋጩ (አልበርት አንስታይን ራሱ «በሚሊዮን የብርሃን ዓመት አንዴ የሚከሰት ግጭት» እንዳለው በኋላ ፊዚክስ ስማር ደረስኩበት 😁)።
(ቁም ነገሩ፣ በዕድሜ የጎረመሱ ልጆች በልዩ ሁኔታ የሚማሩበት ፕሮግራም ሊመቻችላቸው ይገባል እንጂ ከሕፃናት ጋር ተቀላቅለው መማር የለባቸውም!!)
©አሌክስ አብርሃም
ሁሌም ማንበብ! | 3 288 |
| 13 | Matn yo'q... | 2 637 |
| 14 | “Injustice anywhere is a threat to justice everywhere.”
— Martin Luther King Jr.
When injustice is ignored in one place, it can spread and affect everyone. A society cannot enjoy lasting peace if people remain silent while others are treated unfairly. Justice is strongest when people stand up for what is right, regardless of who is affected.
This quote reminds us that fairness, equality, and respect for human dignity are everyone’s responsibility. Ignoring injustice because it does not affect us today may allow it to grow until it affects us tomorrow.
A student who speaks up when a classmate is being bullied helps create a safer school for everyone. A community that refuses to tolerate corruption strengthens trust and accountability. A nation that protects the rights of all its citizens is more likely to enjoy peace, unity, and lasting progress.
Stand for justice, even when it does not directly benefit you. A better society is built when ordinary people choose fairness over silence and courage over indifference. Protecting the rights of others helps protect the rights of everyone.
Engaged in reading always! | 3 243 |
| 15 | ሐምሌ 11 /2018 ዓ.ም (ቅዳሜ ከ8:00 ጀምሮ)
ሁላችሁም በነጻ ተጋብዛችኋል!
ነገረ መጻሕፍት!
ተጋባዥ እንግዳ:- ተስፋዬ ኃ/ማርያም
የተመረጡት መጻሕፍት:- የባሻዬ ውጎች
አዘጋጅና አቅራቢ:- እንዳለጌታ ከበደ
አሰናጅ:- ዛጎል የመጻሕፍት ባንክ
የዝግጅት ቦታ:- FSS. አዳራሽ
በዝግጅቶቻችን ላይ በአካል በመገኘት መሳተፍ ለምትፈልጉ አድራሻችን:- ቀበና፣ ካቶሊክ፣ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን አቅራቢያ፣ ወደ ሳንፎርድ ትምህርት ቤት በሚወስደው መንገድ፣ ባማ አዲስ ሕንፃ አጠገብ፣ FSS አዳራሽ ሲሆን፣ የመገኛ ቦታው Google Map link:-
https://maps.app.goo.gl/2n1myQXCCaTteCw69?g_st=ic
ለበለጠ መረጃ:- 0976066720
0900651010 | 3 585 |
| 16 | ጓደኛዬ ቤት ሁሌ የምሄደው ታናሽ እህቱን ለማየት ነበር ። ታናሽ እህቱ ዘቢብ ትባላለች ። አጠያየሟ ፣ ድርብ ጥርሷ ፣ ሳቋ ፣ የፀጉሯ ብዛት፣ ድምጿ ፣ ፈገግታዋ ስለሚናፍቀኝ ቤታቸው እሄዳለሁ ።
የታላቅ ወንድሟ ጓደኛ ስለሆንኩ እንደወንድ እያየችኝ አትሽኮረመምም እንደታላቅ ወንድሟ ነው የምትሰማኝ ።
እሷ ካለች ቤታቸው ጭር አይልም ። እጫወታለሁ፣ አመሻለሁ ፣ ከቤታቸው ውጣ ውጣ አይለኝም ፤ ከሷ ሌላ የማየው ሰው አልነበረም ።
ታላቅ ወንድሟ ሲቆጣት በስሱ አግዝላታለሁ ።
ድንገት ግን ከጓደኛዬም በላይ፣ ከዘቢብም በላይ ጋሽ ንጉሴ ቀልቤን ገዙኝ ። ጋሽ ንጉሴ አባታቸው ናቸው።
ምናቸውም ደስ አይለኝም ነበር ። ኮስተር ይላሉ፣ ግንባራቸው አይፈታም ከሙሉ ቀን ጋር ብቻ ነው የሚጫወቱት። ሙሉቀን የቤቱ የመጀመሪያ ልጅ ነው የአእምሮ እድገት ውስንነት አለበት ።
እቤት ሲገቡ "ሙሌስ?" ይላሉ ። በእጃቸው ይዘው የሚመጡትን በቆሎ ፣ ቆሎ ፣ ዳቦ ጠቅላላ ላንተ ነው ይሉታል። ሁሉንም እንደዋዛ ጨብጠው "ሙሌ" ብለው ያቅፉታል ።
ሙሌን ከጓደኛዬ በላይ፣ ከዘቢብ በላይ፣ ከቤቱ መጨረሻ ልጅ ከሚኪ በላይ ፣ ይወዱታል። ጓደኛቸው ነው ። ብዙ ግዜ አመሻሽ ላይ ሸራተን ሆቴል ጋር ባለው ቁልቁለት እና ዳገት መውረጃ እና መውጫውን በዝግታ እየተላፉ ፣ እየታገሉ ፣ እጅ ለእጅ ተያይዘው ሲንሸራሸሩ አይቻቸው አውቃለሁ ።
ከልጆቻቸው ሁሉ ሙሌን እንደሚወዱት አወቅኩኝ። የጋሽ ንጉሴ እና የሙሌ ሁኔታ ቀልቤን ገዛኝ ፤ ሁሉንም ረሳኋቸው ።
ጓደኛዬን "ጋሽ ንጉሴ ሙሌን ይወዱታል ኣ?" ስለው ፤
"ሰምተኽው አታውቅም እንዴ ? ሙሌ ይሙት እያለ ነው እኮ የሚምለው ። ሙሌ ካመመው እኮ ስራ ራሱ አይሄድም። የኔ ዘንካታ ፣ የኔ የዋህ ሲለው ነው የሚውለው ።
ያበዘዋል ባክህ !
ሲፀልይ ከኔ በፊት ያድርገው እያለ እኮ ነው ። " አለኝ።
ጋሽ ንጉሴ ሙሌ አድጎ እንደማይጦራቸው ፣
ስማቸውን እንደማያስጠራላቸው ፣ ውለታቸውን እንደማይተነትን ያውቃሉ። ግን ሙሌን በበለጠ ይወዱታል ።
እውነተኛ ፍቅር ምላሽ ሳይጠብቁ ውለታ እንደማያገኙ እያወቁ መውደድ ነው አይደል?
© Adhanom Mitiku | 3 502 |
| 17 | Matn yo'q... | 3 934 |
| 18 | Authors: Mark Hatmaker and Doug Werner
Genre: Sports Instructional / Martial Arts Literature
Overview
In the vast landscape of combat sports literature, many texts falter by treating boxing as a simple sequence of punches. Mark Hatmaker and Doug Werner’s Boxing Mastery: Advanced Technique, Tactics and Strategies avoids this pitfall entirely. Positioned not as an introductory primer, but as an advanced masterclass, the book functions as a conceptual and physical blueprint for turning a fundamentally sound boxer into a highly tactical ring general.
Thematic Analysis and Structure
The core thesis of Boxing Mastery is that elite boxing is a cerebral game of chess played at high velocity. The book elegantly moves past basic jabs and crosses to dissect the hidden architecture of ring combat.
Hatmaker’s instructional style is clinical and highly detailed. Rather than offering generic advice, the text breaks down specific strategic scenarios:
The Geometry of the Ring: The authors focus heavily on positional dominance, offering brilliant insights into cutting off the ring, manipulating an opponent into corners, and fighting effectively off the ropes.
Psychological Warfare: A standout element of the book is its dedication to deception. It thoroughly analyzes the mechanics of feints, draws, and traps—teaching practitioners how to manipulate their opponent’s reactions rather than just reacting to them.
Style Adaptability: The literature shines brightest when discussing tactical tailoring. The authors provide concrete, actionable game plans for dismantling various archetypes, such as how a shorter fighter can systematically break down a rangy out-boxer or how to neutralize an aggressive brawler.
Prose and Visual Integration
Written in a pragmatic, no-nonsense prose style, the book reads like a seasoned coach speaking directly to an athlete. There is little room for fluff; every page is dense with technical theory.
Crucially, the book utilizes extensive step-by-step sequential photography. In sports literature, text alone often fails to capture the nuance of weight distribution or micro-pivots. The included visuals successfully bridge this gap, precisely mapping out the kinetic chains required for advanced defensive slipping, counter-punching combos, and fluid infighting.
Critical Verdict
While the text is incredibly thorough, its dense nature and assumption of prior knowledge mean it is not suited for absolute beginners. Those looking for basic fitness boxing or fundamental stance work will find themselves overwhelmed.
However, as a piece of advanced martial arts literature, Boxing Mastery is exceptional. It strips away the mystique of elite boxing and replaces it with logic, physics, and tactical rigor. For intermediate practitioners, coaches, and dedicated students of the "Sweet Science," it remains an indispensable reference manual that rewards repeated reading and gym application.
Engaged in reading! | 3 858 |
| 19 | 🤌🏾 | 2 970 |
| 20 | ሮዛ ሮዚና !
እሰራበት የነበረ ድርጅት ውስጥ ሮዛ የምትባል የሃብታም ልጅ "ስራ ትልመድ" ተብሎ በግድ በአካውንታትነት ተቀጥራ ነበር። የድርጅቱ ባለቤት የእህት ልጅ ናት አሉ። እንዳለ የድርጅቱ ሰራተኛ በአንድ አፍ "ክፍት አፍ ናት" ነበር የሚላት። እኔ ደግሞ በእርግጥ ክፍት አፍ ናት፣ ግን ቆንጆና ስራ ላይ ጎበዝ፣ በዚያ ላይ አዝናኝም ናት አልኩ።
"ስለየትኛው ስራ ነው የምታወራው? በግል የምታውቀው ስራ ሰርታችሁ ከሆነ ንገረን?" አሉ። በጣም እድለኛ ሰው አድርገው ነው እንዴ የሚያዩኝ ?
"በምን እድሌ" ብየ ዝም አልኩ። እሷም እነሱም ጠመዱኝ። (ምናለ እሷ ከምትጠምደኝ ቆንጆ ብቻ ናት ብየ የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ሕዝብ ቢጠምደኝ)
ሮዛ በቃ ድህነት የሚባለው ነገር አይገባትም። እኔ እንኳን ፊት ነሳችኝ እንጅ ልቀርባትና ድህነትን ላስረዳት በጣም ፈልጌ ነበር። እና ሮዛ ሮዚና የመጀመሪያ ቀን ፔሮል ስትሰራ የሰራተኛውን ደመወዝ እያየች ተገርማ ልትሞት! በቃ ደመወዛችንን ስታይ አስጠላናት፤ ቀፈፍናት! ለምን እንደምንኖር ግራ ገባት! ምን አለች አሉ ?
"ኦ ማይ ጋድ! ትልልቅ ሰወች የከረሜላ መግዣ እየተሰጣቸው ወር ሙሉ ይሰራሉ?! ወደዛ ሰጥተዋቸው ለምን አይከፋፈሉም? ለዚች ደግሞ ፔሮል ምናምን...." ይህንን የምትነግረን ፀሐፊዋ ናት። የተነፈሰችው አይቀራትም ፤ስለማትወዳት እያመጣች ትነግረን ነበር። በኋላ ሊያልቅ አንድ እሽሽሽሽሽ ብቻ የቀረው ሽቶ ሰጥታት እኛን ክዳ ከእርሷ ጋር ተሰለፈች። ለሽቶ ዕቃ የአንድ ድርጅት ሰራተኛ ይካዳል?
እና ሮዛ ፔሮል እየሰራች "ፍስሃ ማነው?" አለች አሉ
"ጋሽ ፍስሃ ይሄ የሰው ሃይል አስተዳደር ማናጀሩ ነው"
"ወይኔ ...ይሄ ሱፍ ለብሶ የሚንጎራደደውና ሁሉንም ሰው ጎንበስ እያለ ሰላም የሚለው ሰውየ? እና ደመወዙ እች ናት? እኔ እሱን ብሆን አልንጎማለልም፣ ማንንም ሰላም አልልም!" (ተበሳጨን)
ሳምራዊትስ ?
ሳምሪ የጋሽ ልሳኑ ፀሃፊ ናት
ኦ ያች ሁልጊዜ የቀንድ ሂል ጫማ ለብሳ በተራመደች ቁጥር የምታደነቁረን? በዚች ደመወዝ ነው ሆ! (ሳምሪ ይች ለካፊ ከመምጣቷ በፊት የድርጅታችን ቆንጆ ነበረች፣ የጫማዋ ቋቋታም ቢሆን ሙዚቃችን ነበር)
አብርሃም ማነው? ...
አብርሽ... ነገረቻት ፀሐፊዋ! ስለ እኔ አለች የተባለው ነገር ፅኑ ሰው በመሆኔ እንጅ በረኪና በወተት ያስጠጣ ነበር።
"እና ደመወዙ ይች ናት? ይች? ...አባ ስለሽ ቢቀጥሩት ከዚህ የተሻለ ያገኛል....ምኑ ሙትቻ ነው በማሚ ሞት! ወጣት አይደል በሱዳን ምናምን አይሰደድም! (አባ ስለሽ መስሪያ ቤታችን ፊት ለፊት መንገድ ላይ የሚለምኑ የኔ ቢጤ ናቸው። አይነ ስውርና አመለ ቢስ ስለሆኑ የሚመራቸው ሰው አይበረክትላቸውም፣ ሁሌ አዲስ መሪ ይቀጥራሉ! ያን ሰሞን ራሱ የምትመራቸው ልጅ ትታቸው ሄዳ ሌላ እየፈለጉ ነበር። በስህተት እያስመሰሉ የመሪዋን ደረት አካባቢ እየነካኩ አስቸግረዋት ነው አሉ የሄደችው)
ብበሳጭም "እዳን ወደምንዳ" ለመቀየር በማሰብ ሳገኛት ፈገግ ብየ "ሮዚ ሲቪየን ልስጥሽ አባ ስለሺ ጋር ታስቀጥሪኛለሽ፣ ዘንድሮ በዘመድ ሆኗል ቅጥር" አልኳት። ከእግር እስከራሴ በብስጭት አይታኝ
"እኔን ለማሽሞር ከሆነ ቅጠሩኝ አላልኩም ፤ አምጥተው ነው የጣሉኝ...እና ደግሞ አባ ስለሽን ለመምራት መጀመሪያ ራስህን ምራ" ብላኝ ሰበር ሰካ እያለች ሄደች። ማስቲካዋን ቀጭ እያደረገችና ቁልፏን እያቅጨለጨለች። ማስቲካ ማኘክ የሚያምርባት ሴት እንደሷ አይቸ አላውቅም። ሰው እንዴት በከንፈሩ ማስቲካ ያኝካል?
በኋላ መስሪያ ቤቱን ስትለቅ መቸም የአለቃችን ዘመድ ናት ብለን መሸኛ ተዘጋጀ። አዋጥተን ኮምፎርት የሚባል ብርድ ልብስ ገዝተን ሰጠናት። ለምንና በማን ብርድ ልብሱ እንደተመረጠ አላውቅም። አርብ ቀን ነበር። ሰኞ አርፍጀ ስገባ ሰራተኛው ሁሉ በብስጭት ፀጉሩን እየነጨ ጠበቀኝ ። ያ መላጣ የግዢ ሰራተኛ ሀይሌ ራሱ ፀጉር ስለሌለው በቀጣይ ወር ከሚያቆጠቁጡት ሰባት ፀጉሮች አራቱን ተበድሮ ሲነጭ ነበር😁 ምን አበሳጫችሁ ብል
"ሮዛ አዋጥተን የገዛንላትን ምን የመሰለ ኮምፎርት ለድርጅቱ ዘበኛ ሰጥታቸው ነው የሄደችው" አሉኝ በሳቅ ፈረስኩ! በስርዓት ቃለ ጉባዔ ይዘው "ጥርስህ ይርገፍ" የሚል መግለጫ አወጡብኝ።
©አሌክስ አብርሃም
ሁሌም ማንበብ! | 4 167 |
