uz
Feedback
Top Students

Top Students

Kanalga Telegram’da o‘tish

#ይህ ቻናል ከ9-12ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የተለያዩ ትምህርታዊ መረጃዎችን እና ቁሳቁሶችን የሚያጋራ የተማሪዎች ገፅ ነዉ:: በትምህርት ዓለም ትናንትም ነገም ዛሬ ነው:: ስለዚህ ዛሬውኑ አቅደህ ጀምር:: @UAT_Preparation1 @Freshman_Classroom @Exit_Exam_Passway እኛን ለማግኘት @mulea27 / 0908398610

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Top Students analitikasi

Top Students (@topstudents1) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 57 053 obunachidan iborat bo'lib, Taʼlim toifasida 2 945-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 582-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 57 053 obunachiga ega bo‘ldi.

16 Sentabr, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -595 ga, so‘nggi 24 soatda esa -49 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 18.93% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 8.62% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 10 802 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 4 916 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 21 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
#ይህ ቻናል ከ9-12ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የተለያዩ ትምህርታዊ መረጃዎችን እና ቁሳቁሶችን የሚያጋራ የተማሪዎች ገፅ ነዉ:: በትምህርት ዓለም ትናንትም ነገም ዛሬ ነው:: ስለዚህ ዛሬውኑ አቅደህ ጀምር:: @UAT_Preparation1 @Freshman_Classroom @Exit_Exam_Passway እኛን ለማግኘት @mulea27 / 0908398610

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 17 Sentabr, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Taʼlim toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

57 053
Obunachilar
-4924 soatlar
-2557 kun
-59530 kun
Postlar arxiv
የዩኒቨርሲቲ ምደባ ተለቋል ገብታችሁ እዩ። Here is the link https://student.ethernet.edu.et/view-placement JOIN: @FRESHMAN_CLASSROOM
የዩኒቨርሲቲ ምደባ ተለቋል ገብታችሁ እዩ። Here is the link https://student.ethernet.edu.et/view-placement JOIN: @FRESHMAN_CLASSROOM

የ Freshman ውጤታችሁ ሙሉ የUniversity ቆይታችሁን ይወስነዋል || እንዴት አሪፍ ውጤት እንደምታመጡ ልንገራችሁ 👇👇👇 https://youtu.be/QQ5_mcrPqn8?si=UsxpD1WZT1GtCvYv

#AAU በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛው መርሐግብር በ2019 ዓ.ም ለመማር ቅበላ ያገኛችሁ የአንደኛ ዓመት የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች (ከአዲስ አበባ ውጪ ለምትመጡ ተማሪዎች) መስከረም 06 እና 07
+1
#AAU በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛው መርሐግብር በ2019 ዓ.ም ለመማር ቅበላ ያገኛችሁ የአንደኛ ዓመት የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች (ከአዲስ አበባ ውጪ ለምትመጡ ተማሪዎች) መስከረም 06 እና 07/2019 ዓ.ም በየተመደባችሁበት የዩኒቨርሲቲው ካምፓሶች በመገኘት ሪፖርት እንድታደርጉ ተብሏል፡፡ ለምዝገባ የሚያስፈልጉ ● የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣ ● አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣ ● የማደሪያ ምድብ (Dormitory) ለተሰጣችሁ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ እና የስፖርት ትጥቅ መያዝ ይኖርባችኋል። በተጠቀሱት ቀናት ከአዲስ አበባ ውጭ ለምትመጡ ተማሪዎች በመርካቶ አውቶብስ ተራ፣ በላም በረት፣ በአቃቂ እና በአስኮ የመኪና መናኸሪያዎች እንዲሁም በቦሌ የአውሮፕላን ማረፊያ ዩኒቨርሲቲው ወደ አዲስ አበባ እና ቢሾፍቱ ወደሚገኙት ካምፓሶቹ የትራንስፖርት አገልግሎት ያቀርባል፡፡ ነዋሪነታችሁ አዲስ አበባ ከተማ ሆኖ ቅበላ ያገኛችሁ ተማሪዎች ከላይ የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ይዛችሁ ሪፖርት የምታደርጉት መስከረም 07/2019 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል፡፡ ለሁሉም ተማሪዎች አጠቃላይ ስለ ዩኒቨርስቲው የመማር ማስተማር ሒደት ገለጻ አርብ መስከረም 08/2019 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ ዘግይቶ ምዝገባ መስከረም 11/2019 ዓ.ም ሲሆን፣ የመጀመሪያ ሴሚስተር ትምህርት በዕለቱ ይጀመራል፡፡ @tikvahuniversity

#ነገ ትምህርት ይጀመራል! 🎒📖 መልካም የትምህርት ዘመን ይሁንላችሁ!!!

የሪሚዲያል መርሃ ግብር የዩኒቨርሲቲ ቅበላ መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ። ለ2019 ዓ/ም የሪሚዲያል መርሃ ግብር ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችላቸው የመቁረጫ ነጥብ በተማሪዎች ውጤት፣ በዩኒቨ
+1
የሪሚዲያል መርሃ ግብር የዩኒቨርሲቲ ቅበላ መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ። ለ2019 ዓ/ም የሪሚዲያል መርሃ ግብር ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችላቸው የመቁረጫ ነጥብ በተማሪዎች ውጤት፣ በዩኒቨርሲቲዎች የቅበላ አቅም፣ እና በሀገራዊ የትምህርት ፍትሃዊነት መርህ ላይ ተመስርቶ መወሰኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። በዚህም መሰረት ከታችን የተገለጸውን ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ለሪሚዲያል መርሃ ግብርየዩኒቨርሲቲ ቅበላ ብቁ መሆናቸውን ሚኒስቴሩ አሳውቋል። 1. የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 👉 ከ600 ውስጥ 240 እና ከዚያ በላይ (40%) 2. የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 👉 ከ600 ውስጥ 228 እና ከዚያ በላይ (38%) በልዩ ድጋፍ የሚታይ የተማሪ ምድብ 1. ከአፋር፣ ሶማሌ፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝ እና ጋምቤላ ክልሎች የተፈጥሮ ወይም ማህበራዊ ሳይንስ ለተፈተኑ ወንድና ሴት ተማሪዎች 👉 ከ600 ውስጥ 222 እና ከዚያ በላይ (37%) 2. ከአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች የተፈጥሮ ወይም ማህበራዊ ሳይንስ ለተፈተኑ ተማሪዎች 👉 ከ600 ውስጥ 222 እና ከዚያ በላይ (37%) 3. በማህበራዊ ሳይንስ የተፈተኑ ዓይነ ስውር ወንድና ሴት ተማሪዎች 👉 ከ500 ውስጥ 185 እና ከዚያ በላይ (37%) 4. በተፈጥሮ ወይም በማህበራዊ ሳይንስ የተፈተኑ መስማት የተሳናቸው ወንድና ሴት ተማሪዎች 👉 ከ600 ውስጥ 222 እና ከዚያ በላይ (37%) ቲክቫህ ኢትዮጵያ መስከረም 4 ቀን 2019 ዓ/ም @tikvahethiopia

📚BEST ETHIOPIAN EDUCATIONAL CHANNELS🤗 -------------------------------------------------- 1⃣• FANA EDUCATION 🔗ᴊᴏɪɴ ᴄʜᴀɴɴᴇʟ 2⃣• TOP STUDENTS       🔗 ᴊᴏɪɴ ᴄʜᴀɴɴᴇʟ 3⃣• QUIZ TIME 🔗ᴊᴏɪɴ ᴄʜᴀɴɴᴇʟ 4⃣• A+ ETHIOPIA 🔗ᴊᴏɪɴ ᴄʜᴀɴɴᴇʟ 5⃣• ETHIOPIAN STUDENTS 🔗ᴊᴏɪɴ ᴄʜᴀɴɴᴇʟ 6⃣• BLUE NILE ACADEMY 🔗ᴊᴏɪɴ ᴄʜᴀɴɴᴇʟ 7⃣• Extreme Book Series       🔗ᴊᴏɪɴ ᴄʜᴀɴɴᴇʟ 8⃣• FRESHMAN TUTORIAL 🔗 FRESHMAN 2019 Join አድርጉ ተጠቃሚ ትሆናላቹ 🙌

📢 UAT ውጤት ተለቋል። ለNatural 76.17 ለSocial 58.75 ውጤት ለማየት https://admission.aau.edu.et/dashboard JOIN: @TOPSTUDENTS1
📢 UAT ውጤት ተለቋል። ለNatural 76.17 ለSocial 58.75 ውጤት ለማየት https://admission.aau.edu.et/dashboard JOIN: @TOPSTUDENTS1

✅ ለ2019 ዓ.ም FRESHMAN ተማሪዎች በሙሉ ....... 💠 Mid exams 💠 Final exams 💠 Short note 💠 Power point 💠 COC Exam  💠 Mid & Final Exam ከነመልሱ የምንለቅበትን ቻናል ተቀላቀሉ:: 📌 እንዲሁም ከFreshman ጋር የተገናኙ  የተለያዩ መረጃዎችን የምታገኙበት ቻናል ነው:: 📌 ለጓደኞቻችሁ ሼር አድርጉላቸው ✨ Join us👇👇 @Freshman_2019

#AASTU በ2019 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የተፈተናችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና ውጤታችሁ ተለቋል፡፡ ፈተናውን የወሰዳችሁ ተማሪዎች ተከታዩን ሊንክ በመጠቀምና
#AASTU በ2019 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የተፈተናችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና ውጤታችሁ ተለቋል፡፡ ፈተናውን የወሰዳችሁ ተማሪዎች ተከታዩን ሊንክ በመጠቀምና አድሚሽን ቁጥራችሁን በማስገባት ውጤታችሁን መመልከት የምትችሉ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ https://www.aastu.edu.et/result/ @TOPSTUDENTS1

በ2019 ዓ.ም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በአፕላይድ ሳይንስ እና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ለመማር አመልክታችሁ የመግቢያ ፈተና ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም የወሰዳችሁ ተማሪዎች ውጤታችሁን https://stu.astu.edu.et/astu-results ላይ በመግባት ማየት ትችላላችሁ።

ተራዝሟል! በ2018 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስክ ምርጫ ማድረጊያ ጊዜ እ
ተራዝሟል! በ2018 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስክ ምርጫ ማድረጊያ ጊዜ እስከ መስከረም 05/2019 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። ስለሆነም በተለያዩ ምክንያቶች እስካሁን ምርጫችሁን ያላስገባችሁ ተማሪዎች በተራዘመው የጊዜ ገደብ ውስጥ https://student.ethernet.edu.et  ላይ በመግባትና የፋይዳ መለያ ቁጥራችሁን በመጠቀም ምርጫችሁን እንድታጠናቅቁ አሳስቧል። JOIN: @TOPSTUDENTS1

#UPDATE ✅የ2019 የ 12 ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሰኔ28-ሐምሌ 9 እንደሚሰጥ ተገለጸ 🟡የትምህርት ሚንስትር አጠቃላይ የአመት ካላንደር ከላይ ተያይዟል! JOIN: @TOPSTUDENTS1

🌻🌻እንኳን ለ2019 አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ። 🌻🌻 ➡️ አዲሱ አመት የሰላም እና የጤና እንዲሆንላችሁ እንመኝላችኃለን🥰 🙌 በ2018 በብዙ ፈተናዎች እና አስቸጋሪ ጊዜዎችን አልፋችሁ ይሄው ነገ 2019 ልገባ ነዉ:: 🤗 በአዲሱ አመትም ያሰባችሁት ሁሉ የሚሳካበት የምትፈልጉትን ሁሉ የምታገኙበት የስኬት እና የደስታ አመት ይሁንላችሁ 🙏 መልካም አዲስ አመት 🙏 #Share #Share JOIN: @TOPSTUDENTS1

እነዚህን 7 ነገሮች ቀድሜ ባውቃቸው ብዙ ነገር ያቀሉልኝ ነበር  || 7 Things I Wish I Knew Before The Year Began👇👇 https://youtu.be/arEszceQhpE?si=5JEPmOBPPikrN4S_

#AAU #ልዩ_የቅበላ_ዕድል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም በቅድመ-ምረቃ ዲግሪ ፕሮግራም ለመማር ፈልጋችሁ በተለያየ ምክንያት በመጀመሪያው ዙር የመግቢያ ፈተና መውሰድ ላልቻለሁና በግል ከፍ
#AAU #ልዩ_የቅበላ_ዕድል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም በቅድመ-ምረቃ ዲግሪ ፕሮግራም ለመማር ፈልጋችሁ በተለያየ ምክንያት በመጀመሪያው ዙር የመግቢያ ፈተና መውሰድ ላልቻለሁና በግል ከፍላችሁ በቀን ወይም በማታው መርሐግብር ለመማር መስፈርቶቹን የምታሟሉ አመልካቾች ከጳጉሜን 05/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 02/2019 ዓ.ም ከቀኑ 6፡30 ድረስ ብቻ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ የመመዝገቢያ መስፈርቶች ● በ2015፣ 2016፣ 2017 እና 2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ያመጣችሁ ወይም በቴክኒክና ሙያ ደረጃ 4 አጠናቃችሁ COC ያለፋችሁ ● በተገለፁት ዓመታት የተሰጠውን የመግቢያ ፈተና (UAT) ያልወሰዳችሁ የመግቢያ ፈተና የሚሰጥበት ቀን 👇 መስከረም 04/2019 ዓ.ም   ይመዝገቡ 👇 https://admission.aau.edu.et 🔔 በመጀመሪያው ዙር ጳጉሜን 02 እና 03/2018 ዓ.ም የተሰጠውን የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ነጥብ ማምጣት ያልቻላችሁ (ከ50 ነጥብ በታች ያስመዘገባችሁ) አመልካቾች ይህ ዕድል አይመለከታችሁም ተብሏል፡፡ JOIN: @FRESHMAN_CLASSROOM

➡️ የ2018 ዓ.ም ማትሪክ ፈተና ያለፋችሁ እና Remedial ያለፋችሁ ይሄንን ቻናል ተቀላቀሉት:: Freshman ኮርስ ስትጀምሩ ልዩ ድጋፍ ያደርግላችኃል:: JOIN: @FRESHMAN_CLASSROOM

📚BEST ETHIOPIAN EDUCATIONAL CHANNELS🤗 -------------------------------------------------- 1⃣• FANA EDUCATION 🔗ᴊᴏɪɴ ᴄʜᴀɴɴᴇʟ 2⃣• TOP STUDENTS       🔗 ᴊᴏɪɴ ᴄʜᴀɴɴᴇʟ 3⃣• QUIZ TIME 🔗ᴊᴏɪɴ ᴄʜᴀɴɴᴇʟ 4⃣• A+ ETHIOPIA 🔗ᴊᴏɪɴ ᴄʜᴀɴɴᴇʟ 5⃣• ETHIOPIAN STUDENTS 🔗ᴊᴏɪɴ ᴄʜᴀɴɴᴇʟ 6⃣• BLUE NILE ACADEMY 🔗ᴊᴏɪɴ ᴄʜᴀɴɴᴇʟ 7⃣• Extreme Book Series       🔗ᴊᴏɪɴ ᴄʜᴀɴɴᴇʟ 8⃣• FRESHMAN TUTORIAL 🔗 FRESHMAN 2019 Join አድርጉ ተጠቃሚ ትሆናላቹ 🙌

🎯 ግቢ ላይ ውጤት እንዴት መስራት እንችላለን። 📌 Worksheet Worsheet ማለት መምህሩ የሆነ chapter አስተምሮ እንደጨረሰ በተማራችሁት ትምህርት ዙሪያ ከበድ ከበድ ያሉ እና የ concept ጥያቄዎች ከተለያዩ መፅሀፍት አውጣጥቶ ፈተና ሊደርስ አካባቢ የሚሰጣችሁ ነው። በተለይ ፈለጣ የሚበዛበት ዲፓርትመንት የምትገቡ ልጆች worksheet የተለመደ ነው። መምህሩ worsheet ከሰጣችሁ ፡ ፈተናውን በዚህ መልክ ተዘጋጁ ማለቱ ነው። ከ worksheet ቱ ላይ ጥቂት የማይባሉ ጥያቄዎች ፈተና ላይ ይወጣሉ። መምህሩ ጥያቄዎቹን የሚያወጣው ከ መፅሀፍ ስለሆነ የጥያቄዎቹን መልስ ከዛው መፅሀፍ ታገኙታላችሁ ፡ ከሌለ ደግሞ Google ማድረግ ይጠበቅባችሗል። ስለዚህ የሚሰጣችሁን worksheet ጥሩ አድርጋችሁ ከሰራችሁ ፡ ፈተናውን ትሰሩታላችሁ። 📌 የአጠናን መንገድ(ስልት) እንዴት አድርገን ብናጠና ነው ፡ ግቢ ላይ ውጤት መስራት የምንችለው🤔? 🎯 አንዳንድ መምህሮች ሙሉ chapter ሩን እንድትፅፋ አድርገው ፈተና የሚያወጡ አሉ። ለምሳሌ ፡ List and describe , explain and discuss ምናምን እያለ handout ቱ ላይ ያሉትን ኖቶች እንድትፅፋ አድርጎ የሚያወጣ መምህር አለ። 🎯 አንዳንድ መምህሮች ደግሞ የ concept ጥያቄ የሚያወጡ አሉ። የ እናንተን የመረዳት ችሎታ የሚጠይቁ ጥያቄዎችን የሚያወጡ መምህሮች አሉ። 🎯 አንዳንድ መምህሮች ደግሞ የ case ጥያቄዎችን ይጠይቃሉ። የ case ጥያቄዎች ደግሞ የእናንተን የመረዳት ፡ የማብራራት ፡ እና ተግባራዊነት የሚጠይቁ ናቸው። ስለዚህ እንዴት እናብብ🤔 🔔 የመጀመሪያው ፈተና ላይ መምህሩ ምን አይነት የፈተና አወጣጥ ስታይል እንዳለው አታውቁም🤷‍♀። ከመጀመሪያው ፈተና በሗላ ግን የመምህሩን የፈተና አወጣጥ ስታይል ማወቅ ትችላላችሁ። ስለዚህ 🎯 የ ሽምደዳ ጥያቄዎችን የሚያወጣ ከሆነ ፡ እናንተም በዛው ልክ handout ቱን በ straw ምጥጥ አድርጋችሁ ማንበብ ነው። በርግጥ ሽምደዳ boring ነው ፡ በተለያየ ስልት አንብባችሁ መያዝ ነው። 🎯 መምህሩ የ concept ጥያቄችን የሚያወጣ ከሆነ ፡ እናንተም በቻላችሁ መጠን የብልጠት አነባበብ መከተል ነው። በቻላችሁት መጠን ሳይንሱን ለመረዳት ብላችሁ አንብቡ። 🎯 የ case ጥያቄዎች ከበድ ይላሉ ። ስለዚህ ስታነቡ ፡ የምታነቡት ትምህርት ተግባራዊ እውነታውን ማወቅ ፡ የት የት ቦታ apply እንደሚደረግ ፡ advantage and disadvantage ን ማወቅ ። ከዛ በዚህ መሰረት ማብራራት ነው ከእናንተ የሚጠበቀው። 🗣 ስለዚህ የአጠናን ስልታችሁ እንደመምህሩ ፈተና አወጣጥ ቢሆን ብለን እንመክራለን። 📌 የጊዜ አጠቃቀም ሌላኛው ና መሰረታዊ ነገር ጊዜያችሁን በአግባቡ የመጠቀም ጉዳይ ነው። ምንድን መሰላችሁ ፡ ብዙዎቻችን ቆይ ነገ አነበዋለሁ ፡ ቆይ ቡሗላ አነበዋለሁ እያልን የመዘናጋት አባዜ አለብን። ይህ ደግሞ የምናነባቸው ትምህርቶች እንዲደራረቡን ያደርጋል። ከ ተደራረቡብን ደግሞ በ tension ልንጨልል እንችላለን። ስለዚህ በተቻለን መጠን ፡ ሳንዘናጋ ፈተናዎች ከመድረሳቸው በፊት ብናነብ መልካም ነው። 📌 አለመሰልቸት ግቢ ላይ ፈተናዎች ፡ አሳይመንቶች ፡ ፕሮጀክቶች ይደራረባሉ። በተለይ በቀጣይ ወደ ግቢ የምትገቡ ፍሬሽ ተማሪዎች ፡ ለ እያንዳንዱ ሴሚስተር የሚሰጣችሁ ጊዜ አጭር ነው። በዚህ ምክንያት ፈተና ቶሎ ቶሎ ነው የምትፈተኑት ፡ አሳይመንት ተደራርቦ ነው የሚሰጣችሁ። ምናልባት ዛሬ ተፈትናችሁ ፡ ነገም ሌላ ፈተና ትፈተናላችሁ ። ከፈተና እንደተመለሳችሁ አሳይመንት ልትሰሩ ትችላላችሁ ምናምን። እና ይኸ መደራረብ መሰልቸን ያመጣል። ስለዚህ ፅኑ መሆን ይጠበቅባችሗል። 📌 ከመምህር ጋር ሰላማዊ መሆን። ሁሉንም ማለት ባይቻልም የግቢ መምህሮች ባህሪያቸው አስቸጋሪ ነው። በቻላችሁ መጠን ከመምህራኖቻችሁ ጋር ሰላማዊ መሆን ፡ በትህትና መነጋገር ፡ ለመምህሩ የሚመች ክላስ መፍጠር አለባችሁ። ከመምህር ጋር የምትንገራገጩ ከሆነ ግን ፡ ሆን ብሎ ውጤታችን ያወርድባችሗል። ብዙ ገጠመኝ ስለማውቅ ነው በዚህ ጉዳይ። 📌 Google ለ ግቢ Google በጣም ወሳኝ ነገር ነው። Assignment መስራት ብትፈልጉ ፡ practical education በ video ማየት ብትፈልጉ ፡ የተለያዩ መፅሀፎችን እና የመፅሀፍ solution ማውረድ ብትፈልጉ ፡ ምናልባት መምህሩ የሰጣችሁ ኖት ካልገባችሁ እና ሳይንሱን መረዳት ብትፈልጉ ፡ Google ለነዚህ ሁሉ በቂ መፍትሔ አለው። ስለዚህ Google ን የቅርብ ወዳጅ አድርጋችሁ ወጤት መስራት ትችላላችሁ ፡ ሳይንሱን መረዳት ትችላላችሁ። በዚሁ አጋጣሚ ለ Google ምስጋና ማቅረብ እፈልጋለሁ😘። 😊 The End Share በማድረግ ለዩንቨርስቲ ተማሪዎች አድርሱ:: JOIN: @FRESHMAN_CLASSROOM -----------------------------------------------------

✅ ለFreshman ተማሪዎች በሙሉ 💠 Mid exams 💠 Final exams 💠 Short note 💠 Power point 💠 COC Exam  💠 Mid & Final Exam ከነመልሱ የምንለቅበትን ቻናል ተቀላቀሉ:: እንዲሁም ከFreshman ጋር የተገናኙ  የተለያዩ መረጃዎችን የምታገኙበት ቻናል ነው:: 📌 ለጓደኞቻችሁ ሼር አድርጉላቸው ✨ Join us👇👇 @Freshman_2019

Dear UAT Test Takers, Please note that test takers who selected examination sites outside AAU will take the UAT on Monday, September 7, 2026, during Session II (11:30 a.m. – 2:00 p.m.). The examination venues for the following sites are: a)   Ambo University: Hachalu Hundessa Campus b)  Bahir Dar University: Peda Campus c)   Jimma University: Main Campus – CISCO Building and CISCO Lab d)  Debre Markos University: Main Campus – Building 621 and Building 22 e)   Jijiga University: CB20, Computer Lab 1 (CB20-R1) f)   University of Gondar: Tewodros Campus The examination venues for the remaining sites will be announced shortly. Please follow the updates or consult the UAT coordinator at your respective site for further information. Sincerely, AAU Testing Center

Top Students - Telegram kanali @topstudents1 statistikasi va tahlili