ወግ ብቻ
✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13 ✔ @wegoch @Words19 ✔ @seiloch ✔ @zefenbicha Creator @leul_mekonnen1
Ko'proq ko'rsatish📈 Telegram kanali ወግ ብቻ analitikasi
ወግ ብቻ (@wegoch) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 17 180 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 4 874-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 1 943-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 17 180 obunachiga ega bo‘ldi.
29 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 64 ga, so‘nggi 24 soatda esa -3 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 31.79% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 6.28% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 5 461 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 079 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 89 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
Creator @leul_mekonnen1”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 30 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 30 Iyun | 0 | |||
| 29 Iyun | 0 | |||
| 28 Iyun | +4 | |||
| 27 Iyun | 0 | |||
| 26 Iyun | +1 | |||
| 25 Iyun | 0 | |||
| 24 Iyun | +4 | |||
| 23 Iyun | +1 | |||
| 22 Iyun | +1 | |||
| 21 Iyun | +1 | |||
| 20 Iyun | +4 | |||
| 19 Iyun | +6 | |||
| 18 Iyun | +20 | |||
| 17 Iyun | +17 | |||
| 16 Iyun | +4 | |||
| 15 Iyun | +3 | |||
| 14 Iyun | +8 | |||
| 13 Iyun | +11 | |||
| 12 Iyun | +21 | |||
| 11 Iyun | +3 | |||
| 10 Iyun | +2 | |||
| 09 Iyun | +3 | |||
| 08 Iyun | +3 | |||
| 07 Iyun | 0 | |||
| 06 Iyun | 0 | |||
| 05 Iyun | +4 | |||
| 04 Iyun | +13 | |||
| 03 Iyun | +6 | |||
| 02 Iyun | 0 | |||
| 01 Iyun | +6 |
| 2 | ሰራተኛ እያፈላለኩ በደላላ አንዲት ልጅ አገኘው
አንገቷን እንደደፋች "ጋሽዬ እኔ የስራ ሆነ የሙያ ችግር የለብኝም ብቻ ስራ እንዳልቆይ ተደግሞብኛል ፤ ሰርቼ እንዳልለወጥ አሰርተውብኛል" ምናምን ብላ ዘበዘበች
"ብሎ ነገር የለም እኔ ተረት ተረት አልወድም ድግምት ምናምን የለም " ብዬ ካለችው አምስት መቶ ብር ጨምሬ ቀጠርኳት
21 ቀን እንደሰራች
አንዴ
ጠረጴዛዬ ላይ አንገቴን ደፍቼ እየፃፍኩ አንድ ሶስቴ ስጠራኝ አልሰማ ብያታለሁ መሰለኝ
"ምን አባህ ይዘጋሃል ብላ"
ይዛው በነበረው ፔርሙዝ አናቴን አለቺኝ
ተጮኸ። I think እኔ ነኝ የጮህኩት
ጎረቤት ተሰበሰበ መቼ ፣ ማን እንደመታኝ በደንብ ያወቅኩት ከሁለት ቀን በኋላ ነው
መንፈስ ፣ ድግምት ፣ ተተብትቦብኛል የሚለኝ ሰው ሲገጥመኝ የጀመረውን አረፍተነገር ሳይጨረሰው ነው የማመልጠው
የሻሼን ፍንክት የቀመሰ ሰው በዚህ ነገር አይፈላሰፍም 😁
By Adhanom Mitiku
@wegoch
@wegoch
@paappii | 3 535 |
| 3 | የቀድሞ የአርጀንቲና እና የቺሊ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆርጌ ሳምፓሊ 🗣️:
"ከእለታት አንድ ቀን ምሽት ላይ አንዲት ቆንጆ ሴት ጋር ወደ ቡና ቤት ሄድኩ። ለብዙ ሰዓት አብረን ተቀምጠን በጣም ብዙ ነገር አወራን። ስለ እራሴ የዋህ እና ደግ እንደሆንኩ ነገርኳት። ስለ ህይወቴ በደንብ አወራኋት። ከእሷ ጋር በጥልቀት ለመተዋወቅ ፈልጌ ነበር። ለጠጣነው መጠጥ እንኳን ከፍዬ ነበር።"
"በዚህ ጊዜ አንድ መልከ መልካም ሰው መጥቶ ከጎናችን ተቀመጠ። ለአምስት ደቂቃ ያህል ካወራት በኋላ ነይ አላት። እሷም ምንም ሳታቅማማ ተነስታ ሄደች። በቀጥታ ወደ መጸዳጃ ቤት ወሰዳት እና ወሲብ ፈጸሙ።"
"ከዚያች ምሽት ጀምሮ የኳስ ቁጥጥር ብልጫ መውሰድ ወይም ኳስ መቆጣጠር በህይወት ውስጥ ምንም እንደማይጠቅም ተገነዘብኩ።"
@wegoch
@wegoch
@paappii | 3 931 |
| 4 | አንድ ጓድኛዬ የሁለት አመት ፍቅረኛው ታማበት ፀበል ነገር ይዟት ይሄዳል ወደ ገዳም!
እንደወሰዳትም "አንተ የseyጣን ነገር ነው መለፍለፍ ጀመረች ሳምንት እንቆያለን" ብሎ ደወሎ አሳወቀኝ!
በመጨረሻም በሳምንቱ ከፀበል መመለሱን ነገሮኝ እንገናኝ ብሎኝ ተገናኝን...
ያው እኔም እንዳገኘውት እንዴት ሆነች ተሻላት ወይ ምናምን ብየ ጠየኩት!
"አዎ!...ግን የሷን ነገር አታውራብኝ " ምናምን አለኝ
ነገሩ ግራ ሲገባኝ ምን ተፈጥረ? ምናምን ስለው ...መለያየታቸውን ነገረኝ!
ግራ ገብቶኝ የታመመች ልጅ ወስደህ ፀበል አስጠምቀሃት (seytan ኬዙ ሲሻላት ) ለምን ተለያያችሁ?... ስለው
እሱም ቀጠለና "ባክህ ከፀበል ስንወጣ 'ይቅርታ መለያየት አለብን አለችኝ! ራሷ...' እኔም ደንግጨ ለምን ? ስላት ...'አንተን የሚያፍቅርህ እኔ አልነበርኩም ሰይጣኑ ነበረ " አትለኝም መሰለህ"....ብሎ ነገረኝ ....
By Jah mac
@wegoch
@wegoch
@paappi | 10 115 |
| 5 | እየመጡ ነው!
(አሌክስ አብርሃም)
ቦሌና መገናኛ ጫማ ልትገዙ ስትሄዱ ድንገት አግኝታችሁት እንዳትደነግጡ ከወዲሁ ልንገራችሁ።
የቻይናው ብሔራዊ የሕክምና ምርቶች አስተዳደር NEO (Neural Electronic Opportunity) ጭንቅላት ውስጥ የሚቀበር ቺፕ ለገበያ እንዲውል በይፋ ፈቅዷል። በዓለም ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የጭንቅላት ውስጥ ቺፕ የንግድ ፈቃድ ተሰጠ ማለት ነው። (እንደፈራነው) ጦቢያዊያን ለአመታት ችብስ 666 ...ስንለው የነበረው ጉዳይ ያው እየመጣ ነው። ነገ እንደጥርስ ማስታወቂያ በተወሳሰቡ የህክምና ቃላት ታጅቦ "አስመጥተናል" የሚል ማስታወቂያ መነገሩ አይቀሬ ነው።
ለጊዜው ለአካል ጉዳተኞች ረዳትነት ብቻ ይውላል ብለዋል። ያው አንድ ነገር ከተመረተ በኋላ የቴክኖሎጅውን ፍጥነት በስልክ ማየት ነው። ዝርዝሩ ይቅርብን ግን ኤሎን ማስክ 'Neuralink' ብሎ የጀመረውን ፕሮጀክት ቻይናወቹ ቀድመው ለገበያ አውለውታል።የሆነ ቀን ቱርክ ፀጉር ከቱርክ አንጎል ከቻይና አሰገጥመን ሸገር ላይ እንግሊዝኛውን ልናዶለዱለው እንችላለን።
ችግሩ ሀክ ሊደረግም ይችላል የሚል ስጋት መኖሩ ነው። አስበሽዋል እናት የሰርግሽ ቀን የባልሽ አንጎል ሃክ ቢደረግ? ወጩ ጋር ተዳምሮ...
@wegoch
@wegoch
@paappii | 4 664 |
| 6 | የጠቋር ሚስት
ጓደኛዬ አዲስ ሙሽራ ነው። ገና ስድስት ወሩ ነው ካገባ። የሆነ እሁድ ጠዋት ልጠይቃቸው ቤታቸው ስሄድ ይሄን ገንገበት ጓደኛዬን ባለቤቱ “ዳዲ” እያለች ስትጠራው ሰማሁ። ተወልዳ እስክታድግ በአንድ የአምበሳ ቆዳ ጫማ እየዳከረ ያሳደጋትን የአባቷን ስም እንደቀልድ ለስድስት ወር ባሏ መስጠቷ ግርም አለኝ። አጎቴ "ሴትና የቀበሌ ቤት የኔ ነው አይባልም" የሚለው እውነት ሳይሆን አይቀርም።
ቤታቸው የሄድኩት እሁድ ጠኋት ስለነበር “ቸርች ልንሄድ ስንል መጣህ” ብለው አብረን ካልሄድን አሉኝ። ላለመሄድ ብሞክርም ባለቤቱ ቆጣ ብላ “ኖህ! ወደድራፍት ቤት እንሂድ ቢሉህ መች እምቢ ትላለህ? በል ተነስ” አለችኝ።
ይሄ ግምብ ራስ ባሏ ድራፍት እንደምወድ ነግሯታል ማለት ነው። ሰነድ መሻሻጥ ተጀመረ? ብዬ እያመነታሁ አብሬያቸው ሄድኩ።
የወሰዱኝ ቸርች አንድ ነብይ የሚያገለግልበት አዲስ የፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያን ነው። ጓደኛዬ ባለቤቱ በቅርቡ ጌታን እንደተቀበለች ነግሮኛል። ገና ውስጥ ገብተን አረፍ እንዳልን በከፍተኛ ድምፅ እየጮኸች ትፀልይ ጀመር።
“ጌታ ሆይ ለዚህ አብሮን ለመጣው፣ ነፍሱ በሃጢአት ለታሰረችው ጎስቋላ ወንድሜ ዛሬ ድረስለት” ስትል ደነገጥኩ። ጭራሽ ስለኔ ነው ፀሎቱ?
“ጌታ ሆይ” አለች ጭራሽ ተንጠራርታ እጇን ትከሻዬ ላይ ጭና። ድምጿ እየጨመረ ነው
“ጌታ ሆይ፥ ዛሬ ስለዚች ነፍስ እፀልያለሁ ...” አለች። {እቺ ነፍስ የተባልኩት እኔው ነኝ}
“ዛሬ እቺ ነፍስ ከስካርና ከሃጢአት ቀምበር እንድትላቀቅ እፀልያለሁ፥ እቺ ነፍስ ዛሬ ከዝሙትና ጌታ ከማይከብርበት የሃጢአት ልምምድ እንድትፈታ እፀልያለሁ” ስትል ቀና ብዬ ምእመኑን አየሁ። እኛ አጠገብ ያሉ ምእመናን ሁሉም ወደኔ እጃቸውን ዘርግተው ይፀልዩልኛል። የት ልግባ? ጭራሽ በሰው ሁሉ ፊት ሰካራም ነው። ያመነዝራል። ትበለኝ? ለምን አንደኛዋን የቲክቶክ ቪዲዮ አትሰራብኝም?
ዞር ብዬ ጓደኛዬን ሳየው ሳቁን አፍኖ በቆረጣ ያየኛል። በስጋ ብገለጥበት ደስ ባለኝ። እሱ ነው አብረን በነበርን ግዜ ምንሰራውን ነገር ሁሉ ዘክዝኮ ነግሯት የሰው መሳቂያ ያረገኝ።
የተወሰነ ቆይቶ ነብዩ ወደመድረክ ወጥቶ ፀሎት ማድረግ ጀመረ። ቤቱ ፀጥ አለ። አንዳንድ ሰዎች ብቻ በየመሃሉ አሜን ይላሉ። እሱም ትንሽ ከፀለየ በኋላ ...
“የጌታ መንፈስ ጅብ ጋላቢ መንፈስ ያሳየኛል” አለ። የዚህ ግዜ የጓደኛዬ ሚስት ዞር ብላ አታየኝም መሰላችሁ? ምናባሽ ላርግሽ? ብላት ደስ ባለኝ። አንተ ነህ ለማለት ፈልጋ ነው? ይሄ የተረገመ ልጅ ጅብም ይጋልባል ብሏት ይሆን እንዴ?
ነብዩ ቀጠለ። “በጉባኤ ውስጥ አንድ ሰው ይታየኛል። ቤተሰቦቹ ቃልቻ ነው ሚያመልኩት። እሱንም በልጅነቱ በአጋዘን ደም ያጥቡት ነበር። ዋናው የአጋንንቶች አለቃ ይጠቀምበታል” ሲል በሃዘኔታ እንደገና ዞራ አየችኝ። አረ እቺ ሴትዮ ለምን አትፋታኝም? እያልኩ ፀሎቱን መከታተል ጀመርኩ።
ነብዩ ወደኔ አካባቢ ፍጥጥ ብሎ ካየ በኋላ ከመድረክ ወርዶ ቀጥ ብሎ መጣ ..... አሁንስ እኔም ፈራሁ። ስለኔ ነው እንዴ ሚያወራው? የሚል ሃሳብ ውልብ አለብኝ። ምናልባት ነፍስ ሳላውቅ ቤተሰቦቼ እንዳለው በአጋዘን ደም አጥበውኝ ይሆን እንዴ? መቸስ ሰው ማመን ከባድ ነው በዚህ ዘመን ምናምን እያልኩ ሳስብ ነብዩ አይኑን አፍጥጦ ቀጥ ብሎ እኛ ወዳለንበት መጣና እጁን አንስቶ....... የጓደኛዬ ሚስት ላይ ሲጭን ከተቀመጠችበት ወምበር ሁለት ሜትር ወደላይ ነጥራ መሬት ላይ ተነጠፈች። እግዚኦ ማህረነ ክርስቶስ። ምን ጉድ ነው?
በኔ ሲስቅ የነበረው ጓደኛዬ ሚስቱ እንደዚያ ስትሆን ሲያያት ክፉኛ ደነገጠ። እኔም ምን መጣ ብዬ አንዴ ነብዩን አንዴ እሷን ማየት ጀመርኩ
ነብዩ “ዋናው መንፈስ ተያዘ!” ሲል ጉባኤው በጩኸትና በጭብጨባ ተሞላ። ከዚያማ ያቺ ድምፀ ለስላሳዋ የጓደኛዬ ሚስት በሙላቱ አስታጥቄ ድምፅ ትለፈልፍ ጀመር
“ተቃጠልኩ! አረርኩ!”
“ማነህ?” አለ ነብዩ
“ጠቋር ነኝ”
“ተናገር የት ነው የያዝካት?”
“ባሏ ነኝ። ከልጅነቷ አሳድጌ ነው ያገባኋት” አለ ሴጣኑ። ጓደኛዬን አየሁት ሚገባበት ጠፍቶታል። “ጭራሽ የሌላ አካልን ሚስት ነው ያገባሁት?” የሚል ይመስላል።
አጋንንቱ ጭራሽ ወደሱ አፍጥጦ “አጠፋሃለሁ አንተ እርጉም ሚስቴን ነጠቅከኝ” እያለ መጮህ ጀመረ። ቺት አድርጋበት መሆኑ ነው።
ጓደኛዬ እንዲሁም ፈሪ ነው ጭራሽ አሁን ከሰይጣን ጋር የግል ፀብ ውስጥ በመግባቱ ያልበው ጀመር።
ያቺ መላአክ የመሰለች ሚስቱ ጭራሽ አይኗን አፍጣ በወፍራም ድምፅ ዛቻዋን ቀጠለች።
“ወንድወሰን ደበበ ጊሚራው” አለችው ሌባ ጣቷን ወደሱ ጠቁማ። {ዳዲ ቀረ በቃ}
ነብዩ ዝም ብሎ ያያል።
“አንተን ካላጠፋሁ እኔ ጠቋር አይደለሁም” አለ መንፈሱ። ጓደኛዬ እንባ ተናነቀው። በሆዱ "Who TF did i marry?" እያለ ነው
“ብዙ ግዜ በተኛህበት በገጀራ እንድትሰነጥቅህ አቅጄ ነበር። ዛሬ ይሄ ነብይ ቀደመኝ” እያለ ማጓራት ጀመረ። ጓደኛዬ እንባውን በአራት መንታ አወረደው። ምን ውስጥ ነው የገባሁት? የሚል ይመስላል።
ብቻ አጋንንቱ ከነብዩ ጋር ውጣ አትውጣ እያለ ሲታገል እኔ እንደምንም ሾልኬ ወጥቼ ወደቀበሌ ጃምቦ ቤት ሮጥኩ። ከአዳራሹ ወጥቼ ጥቂት እንደሮጥኩ ሩጫዬን አቀዘቀዝኩና ወደኋላዬ ስዞር ጓደኛዬ ኮቱን ጥሎ በሩጫ ወደኔ ይመጣል። አጠገቤ ሲደርስ እያለከለከ ቆመና
“ወዴት ነው ጥለኸኝ ምትሮጠው” አለኝ
“እንዴ አንተስ ሚስትህን ጥለህ ወዴት ነው?” ስለው
“አፍህን ዝጋ” ብሎኝ አብሮኝ ወደግሮሰሪ አመራ።
አሁን ሰባተኛ ጃምቧችን ላይ ደርሰናል። “እኔ ግደሉኝ እንጂ ያቺን ሴት አምኜ እዛች ቤት አላድርም” ስላለ ተሰብስበን ወደቤቱ እንዲሄድ እየለመንነው እንገኛለን።
By Noah Daniel
@wegoch
@wegoch
@paappii | 6 054 |
| 7 | የቆሰለ ነገር ፣የከሳ ፣የኮሰመነ እንሰሳ እሚያድን አውሬ ያስጠላኛል ምቹ ግዜ እየጠበቀ ድምፁን እና ሁኔታውን የሚቀያይር ሰው ግን ያስፈራኛል።
ስዩም ፦
ጓደኛው ነኝ ጓደኛዬ ግን አይደለም።
ብዙኅ አሳልፈናል ። ቢሰማብኝ የማፍረውን ነገር ወይ ቢሰማብኝ ጉድ የሚያደርግብኝን ነገር አልነግረውም ።
እፈራዋለሁ። ቋሚ ወዳጅ ስለሌለው እና
ዋሉልኝ ያለቸውን ሰዎች ሁሉ በየምክንያቱ ስለሚተዋቸው እፈራዋለሁ ።
ከጓደኞቹ X ስር ስለማይጠፋ ስሜቱን ሁሉ የተሰማው ሰዓት ስለማያንፀባርቅ
አብሬው ሆኜ አይጥ ለመያዝ ትክ ብላ እንደምታደባ ድመት ነው የማየው። እሱ እንደድመቷ ትኩረት ሲያደርግ ሁኔታው እንደድመቷ አይነት አይደለም አያስታውቅበትም ።
ዘና እያለ እየሳቀ ሚስጥር እየነገረ ነው
ሚስጥር የሚያስወጣው ።
ስዩምን እፈራው ነበረ .....!
ችግር ገጠመኝ ከሁሉም በላይ አብሮኝ ሆነ ያለውን ሁሉ ሰጠኝ አሰጣጡ ስሙልኝ እዩልኝ ያለው አልነበረም
በችግሬ አብረውኝ ያልነበሩትን ስወቅሳቸው እያገዘ አላባባሰብኝም... "ተዋቸው አልሞላ ብሎቸው ነው" አለኝ ....ከነሱ ጋ ሆኜ ያጣጣልኩት ስዩም አብሮኝ ቆመ ....
ተፀፀትኩ ...!
ከብዙ ግዜያት በኋላ ስዩምን በየወሬው እንደዚ አትመስለኝም ነበር እያልኩ እሱ ላይ ያለኝን አቋም ተናዘዝኩ
አልተናደደም ሳቀ
ስልከው እና ሲላከኝ እንደኩያ አይደለም እንደታናሽ ነው ሲተማመንብኝ እንደታላቅ ነው ...!
እሚያግዘን እና የሚኮራብን ወዳጅ የኛ ሲሆን የሚሰማውን ምቾት አሰማኝ
ከጥቂት ግዜ በኃላ ...
ስራ በዛብኝ ብዬ የሰጠሁንት ላግዝ ብሎ የወሰደውን ሙሉ ውክልና ተጠቅሞ መኪናዬን ሸጦ አውሮፓ መግባቱን ከሳምንት በሆላ ሰማሁኝ ...
ስስቅ ላየኝ ሰው ተታልዬ አልመስልም ነበር ...
ማመን ከመጠራጠር በላይ ዋጋ ያስከፍላል ማለት ነው ??
መፍራት ከመድፈር በላይ አቅም አለው ማለት ነው ??
ኮቴ በሰማን ቁጥር እየባነንን የት ድረስ እንሄዳለን ??
የሄድንበትን መንገድ እየጠየቅን መሄድ የሰውነት እጣ ፈንታ ነው ??....
በርግጥ
የግዜ ጉዳይ እንጂ
ከተካደ ሰው የከዳ ሰው ያሳዝናል!!
By Adhanom Mitiku
@wegoch
@wegoch
@paappii | 5 560 |
| 8 | 🌄 We’re Back And We’re Hiking Again
Hey Sunset community 🌄
Life happened. The city got louder.
And for a while, the sunsets were quieter without us.
Sunset Hiking is officially back with a stronger team, clearer plan, and a growing 4,000+ hiking community ready to move again.
Over the next weeks, we’ll be sharing:
🥾 Upcoming sunset hikes
🌅 Community moments
🧭 Safe, well-organized experiences
If you’re still here, it means you love nature as much as we do.
Let’s start again one sunset at a time. 🌄👣 | 4 684 |
| 9 | የ ሥዓሊ እና መምህር ኃይሉ ክፍሌ
"ተገማች፡ ዋዜማ" የሥዕል አውደርዕይ
እዚህ ትርዒት ላይ ተገኝቼ፣ በከተማ ዝመና ውስጥ የማንነትንና የትዝታን ትርጉም የሚፈትሹ ስራዎችን ተመልክቻለሁ። የጥበብ ስራዎቹ የሚጠቀሟቸው ቁሶችና የሚያነሷቸው ሰብአዊ ጥያቄዎች ቆም ብሎ ለማሰብ ትልቅ እድል ይሰጣሉ። የለውጥ ሂደቱ ወዴት እየወሰደን ነው? የጋራ ትዝታችንን እያካተትን ነው ወይስ እየረሳን?
እነዚህንና መሰል ጥያቄዎችን የሚመልስ ድንቅ ትርዒት ነው። እድሉ ያላችሁ እንዳያመልጣችሁ!
📍 እስከ ግንቦት 24 ድረስ ክፍት ነው
@Seiloch
#Hailukifle #artExhibition. | 5 035 |
| 10 | ሰው ብቻ አይደለሽም!
Sirak Wondemu
እናትነት ዓለምን አምጦ መውለድ ነው።
በምጥ ጣር ተይዞ ለሚቃትት ነፍስ የውልደት እልልታን በከንፈሩ ሰማይ ይዞ እንደሚዞር ደመና ነው።
ሰው እውነትን መፃፊያ ጠመኔ ሲሆን እናት የጠመኔው መዳረሻ ሰፊ ሰሌዳ ናት። ትሁንልህ መወደሻ ተብላ በባርኮት የተሰጠች ስጦታ!
በግምባሯ መስመር ላይ ዘመን ፅፋለች። በመዳፏ ስር ሕይወት ወልዳለች። ሽብሽብ ቆዳዋ እድሜን ዘምሯል። ዳሳሽ ጣቶቿ ቀንን ፈክሯል።
ሰው ብቻ አይደለችም!
በወዟ ጠፈፍ ከራሰ የሻሿ ጨርቅ የበለጠ የዓለም ታሪክ የለም። ጊዜና የሕይወት ዑደት አዳውረው በጥቁር ጸጉሯ መሀል እንደበተኑት የሽበት ተክል ያህል መቆዘሚያ ሀሳብ አልነበረም።
እማማ ንፁህ ፈገግታሽ የንግስ ቀን ነው። የእሺታ ደጅሽ የዓለም ብርሃን ነው። ሁሉን ቻይ ልብሽ ዕፁብ ተምሳሌት ... በጊዜ ጣይ ፊት የማይሞት አይነት ፤ ነው።
ኩርፊያሽ ውስጥ እንደነገሩ የወለድሽው ልጅ ፈገግታሽ ያጫውተኛል። የውሸት ተኮሳትረሽ ከሸበሸብሽው የግምባርሽ መስመር ላይ መጥምቁ ዮሐንስ እየሱስን ባጠመቀበት ቅፅበት ትከሻው ላይ ያረፈችውን ፀዓዳ እርግብ እመለከታለሁ። አለሀሳብ መከደን ካማረው መንታ ዓይኖችሽ ውስጥ ፍቅር ጠምቃለሁ። ሰው ይርበኛል።
ተስፋ ጠምጄ... እምነት አርሳለሁ!
እማማ ልጄ ሰው ሆነልኝ ዩኒቨርስቲ ገባልኝ ብለሽ ግማሽ ደስታ ግማሽ ሀዘን ሆነሽ የሸኘሽኝ ቀን ትምህርትን ለዘላለም ረገምኩ። ከእነዚያ ብርሃናማ ዓይኖች ብርቅ ... ከህመም ፈዋሽ ጠረኖችሽ ብሸሽ ... ከሞት መላሽ ዳሳሽ ጣቶችሽ ብሰደድ ፤ ማወቅ የገሀነም ፀሎት ሆነብኝ። ክረምቱ መጥቶ ጉያሽ ውስጥ ሽሽግ እንድል አርጩሜ ቆርጠሽ በጋውን አባሪልኝ። ኮስተር ብለሽ ሀምሌን ጥሪው። ነሀሴም ይምጣ! አንቺ ከተቆጣሽ ሁሉም ቀና ይሆናል!
እማማ እምባ አርግዞ በስስት የሚያየኝ ክርትት አይኖችሽ እንዴት ናቸው? ዛሬም ለመንገደኛ እንዳዘኑ ነው? ለነፍሰጡር ላም እንደተንሰፈሰፉ ነው? በቅርሻቴ ያረጠብኩት ጀርባሽ ... ዓለሜን የተሸከመው ጫንቃሽ ዛሬም ከመቻሉ አልተፈታም?
እኔማ እነሱን ለማየት ለመንካት በስንት ቀናትና ወራቶች ደረት ላይ ተሳብኩ!
ሺህ ናፍቆት ከፊቴ ሺህ ጉጉት ከኋላዬ አጅቦኝ በርሽ ለመቆም ተሳልኩ!
ለስንት ንጋቶች ለፈፍኩ!
ሰው ብቻ አይደለሽም። ብትይኝም አላምንሽም!
ሞገስሽ ልክ እንደታቦት ነው። ቁጣሽ ሀገር ያርማል። የወደቀ ቀዬን አንስቶ በውል ያቆማል። ዝምታሽ እንደፍርድ ቀን ይጨንቃል። ይጠባል። ሳቅሽ እንደእሸት ባቄላ ታኝኮ አይጠገብም። መርቀሽ የሳምሽኝ ግንባሬ ዛሬም በብርሃን እንደታጀበ ነው። ኑርልኝ ብለሽ የመረቅሽኝ ምርቃት እኔ ካልሰለቸኝ ከሞት እንደሚታደገኝ ቃል ገብቶልኛል።
እማዬ ከእንግዲህ ይራባል ብለሽ አትስጊ! ይልቅ የስጋት በርሽን ዝጊ! ያኔ በጨቅላነቴ ዘመኔ እንደወፍ ልጅ ከአፍሽ ነጥቄ የጎረስኩት እስከ እለተ ሞቴ ከአንጀቴ ይኖራል።
አምሳያ የሌለው ውዴታሽ ሞትን ማምለጫዬ ነው። የአንቺ ትካዜ የሀገር መፍረስ ነው። ያ ልዝብ ቃልሽ የንጋት ቀን ነው።
ሰው ብቻ አይደለሽም!
በነጠላሽ ጫፍ የሰው ልጅ ቋንቋ የማይገልፀው የእረፍት ዋኔ - በመቀነትሽ ስር ያልታየ ያልተሰማ ስውር ቅኔ ተቋጥሯል።
ከአንቺ ጋር አይደለም አስር ሀያዬን ሰባ ሰማኒያዬን መሰንበት እፈልጋለሁ።
እማ አንቺ ወዳጅ የለሽም ወዳጅሽ እኔ ነኝ። እኔም የአንቺን ያህል ግምት ሰጥቶ የሚቀበለኝ ወዳጅ የለኝም። ወዳጄ አንቺ ነሽ!
ቀሚስሽን በለጋ ጣቶቼ ጨብጬ የቆምኩባቸው የጎረቤት ቡና ቅፅበቶች አይረሱኝም። ገበያ ሄደሽ እስክትመለሺ መንገድ መንገዱን እያየሁ ጉበን ታቅፌ የተኮራመትኩባቸው ወቅቶች አይኔ ላይ ናቸው። አባቴ ነጥቆሽ ዓመት ከዓይንና ድምፅሽ ርቄ የተመለስኩ ቀን ዘማች በህይወት ተርፎ እንደመጣልሽ ሁሉ በስስት ያነባሽው ዕምባ አንቺ ብትፈቅጂ ወንዝ ሆኖ ይወስደኝ ነበር።
ሰውነትን የለካሁብሽ ፤ የፍቅርን ትርጉም የሰፈርኩብሽ ፤ ትናንትን ፣ ዛሬንና ነገን የመዘንኩብሽ ሚዛኔ ነሽ።
ሳቅሽ ውሎ ሳይገባ እንዳይመሽ እፀልያለሁ። ስጋትሽ ስጋት በልቶት ሳይጠፋ ዘመን እንዳያልፍ እፈልጋለሁ።
በትከሻሽ ላይ ቆሜ ጎበዝ ተብያለሁ። አንድ የናፍቆትሽ ዘለላ አንገቴ ላይ ቢታሰር ይዞኝ ጥልቅ እንደሚወርድ ግን የተረዳኝ የለም።
አድጌ አንቺን ረሳለሁ? ቤት ይኖረኛል? እሸሽሻለሁ? አመመኝ ብትይ እረጋጋለሁ? ልቤ ይሰክናል?
እኔ'ንጃ !
ልጅ ሆኜ አጎቴ ሞቶ በሀዘን ቅስምሽ ስብር ሲል ፤ ማቅ ስትለብሺ እግዜር ከትምህርት ቤታችን ዳገት በላይ ያለ እየመሰለኝ ሄጄ «አንተ አትችልም እናቴ ትሁን! » ብዬ መኮሳተር ያምረኛል።
ሰፈር ሰው ሞቶ ለቅሶ ስትሄጂ መንደርተኛው እርር ሲል ... ምርር ብሎ እምባውን በጉንጩ በራፍ ሲደፋ ያ አባባሌ እውነት ሆኖ እታዘባለሁ።
« በቃ እሱ አይችልም እናቴ ትሁን! » እላለሁ በልቤ።
እዝነት እንደሌለው ሁሉ ፤ ምህረትን እንደማያውቅ ዝንጉ አባት ፍፁምነቱን እንድጠራጠር ያደረገኝ ፍቅርሽ ነው።
ለሁሉም ነገር ሆደ ባሻ የሚሆነው አዛኝ አንጀትሽ ነው። አንቺ እኮ እግዜርን ብትሆኚ የሰፈራችን ሰዎች በሙሉ ማሪያም ቤተክርስቲያን እንዳሉ ዛፎች ሰማይ ጠቀስ እንደሆኑ ይሸብቱ ነበር።
እማማ እርጅና በአንቺ ላይ ስልጣን እንዳይኖረው የአንቺን ቁጣ ኮርጄ እቆጣዋለሁ። ሞት በሰፈርሽ እንዳያልፍ በርሽ ላይ አያ-ጅቦ እንዳለ ነግሬ አስፈራራዋለሁ። እማማዬ ቃል የእምነት እዳ ነው ይላል ፀጋዬ። ቃል የእምነት ዕዳ መሆኑን የተረዳሁት ግን በአንቺ ነው። ዛሬም በሰው ሀገር ሆኜ የተቆላ ቡና ሲሸተኝ ትዝ ትይኛለሽ። ትኩስ ሽሮ ሲሸተኝ ፤ ጠይም ፈገግታም እናት ስመለከት ዓይኔ በእምባ ይሞላል።
ማን ያውቃል ዛሬም ህፃን ልጅ ሲጮህ ትደነግጫለሽ አይደል? በሌለሁበት ቀዬ ተጋደሉ ሲሉሽ እግርሽን ብርክ ብርክ ይልሻል አይደል?
እማዬ ጌሾ ያልወቀጠልሽ እጄን እጠላዋለሁ። ስታዢኝ በእምቢታ የሰበቅኳቸውን ትከሻዎቼን እጠየፋቸዋለሁ።
ለእነዚያ ጊዜ ... ለእነዚያ ወቅቶች መዳፍሽ ስር ፊቴን ቀብሬ ማልቀስ እፈልጋለሁ።
ስትገርፊኝ ያኮረፍኩባቸውን ቀኖች ባገኛቸው እንደልጅነቴ ድንጋይ ወርውሬባቸው ሮጣለሁ።
ማጀትሽ በጥጋብ ይሙላ! ... ሰላምሽ እንደአሸን ይፍላ! የጦር ቃል ጆሮው ይደፈን ... በደጅሽ ፍቅር ይሸመን!
ማሳሽ ላይ አዝዕርት ይብቀል! ... ይመር ሰማዩ እንደምንጭ ይጥለል።
አዛኝ ነሽና መርቂኝ አለሁ... ክፉሽን ከቶ አልስማ ሳለሁ! ገብያሽን ጥጋብ ይውረሰው አይጉደል ዘመኑን ሙሉ... የተኳረፈም ይታረቅ ሁሉ! አካል ነሽና ለምድሩ ለሰው... ስሁት ደስታሽን ቀን ይደግሰው!
ብቻ እማማ አንቺ
ሰው ብቻ አይደለሽም ፤ እግዜር ነሽ ለልጅሽ ... ሚዛን ነሽ ለምድሩ.. ባርኮት ነሽ ለሰማይ አድባር ነሽ አውጋር ነሽ የኔ አድባር። መላዕክ ነሽ ልዩ ሰው! የአጥቢያ ዳኛ የአንቺን ያህል ፍትሕ አያውቅም! ውብ አዝማሪ ከእሽሩሩሽ የተሻለ ዜማ አይደርስም። በዓይኖችሽ ስር የፀነስሽው የተስፋ እምባ ለመኖሬ ለመዳኼ ሆኗል መባ! አለው ዋጋ! አለው ፀጋ።
አስራቴ ነሽ ጃኖ ጥለት... ወደር የለሽ የሰው ቁመት።
ብቻ ብቻ . . .
አንቺ ሰው ብቻ አይደለሽም... ብትይኝም አላምንሽም።
. . .
መልካም የእናቶች ቀን ❤ | 4 594 |
| 11 | ሶምሶማ የአጫጭር ልቦለዶች መጽሐፍ
-በጃፋር መጽሐፍት መደብር(ለገሀር)
-አብዱ book delivery (ፒያሳ)
- +251994886247 ሰለሞን አራት ኪሎ ያገኙታል።@sirakoo
@wegoch
@wegoch
@wegoch | 4 205 |
| 12 | ADDIS ABABA — FOR SUDAN
Voices From Sudan
On April 21, join us for a powerful evening where film, music, and community come together to mark the 3rd anniversary of the Sudan war.
The night opens with a special live performance by The Tana Quintet by Hazim Alshafei, bringing the rhythm, soul, and resilience of Sudan to life—followed by a screening of the acclaimed film Khartoum.
✨ Free Entrance
This is more than a screening.
It’s a gathering.
It’s a shared moment.
It’s solidarity in action.
Expect a full house, a powerful atmosphere, and a night that will stay with you.
📅 Tuseday, April 21, 2026
📍 Bata Complex 22, around Golagul
🕠 5:30 PM
Bring your friends. Be present. Stand with Sudan.
#Khartoum #Sudan #AddisAbaba #InDeepCultures #FilmScreening #LiveMusic #1960Films #AddisCinemaClub | 0 |
| 13 | 📌 በሀዋሳ ከተማ አዲስ የስነ-ጥበብ ትምህርት ቤት የምዝገባ ጥሪ!
ጥበብን ለሚወዱ እና ተሰጥኦአቸውን ማሳደግ ለሚፈልጉ ሁሉ ታላቅ እድል! በሀዋሳ ከተማ ከዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር አዲስ የስነ-ጥበብ (ስዕል) ትምህርት ቤት ስራ ሊጀምር ዝግጅቱን አጠናቋል።
🎨 ለምን ይመዘገባሉ?
• በዘርፉ ብቁ በሆኑ ባለሙያዎች የታገዘ ስልጠና ለማግኘት።
• ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በተቀናጀ መልኩ እውቀትን ለማዳበር።
• የፈጠራ ስራዎትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር።
🌟 የእርስዎ ድርሻ፦
ጥበብ የሀገር መገለጫ ናት! ይህ መልዕክት እንዲደርሳቸው የሚገባቸው ወጣቶች እና ፍላጎቱ ያላቸው ግለሰቦች እንዲያውቁት በማጋራት (Share በማድረግ) ማህበራዊ ሀላፊነትዎን ይወጡ።
ምዝገባው ተጀምሯል!👇👇 link ይጫኑ
https://tally.so/r/D4Jjrl. | 0 |
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
