uz
Feedback
ወግ ብቻ

ወግ ብቻ

Kanalga Telegram’da o‘tish

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13@wegoch @Words19@seiloch@zefenbicha Creator @leul_mekonnen1

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ወግ ብቻ analitikasi

ወግ ብቻ (@wegoch) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 17 186 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 4 889-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 1 951-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 17 186 obunachiga ega bo‘ldi.

30 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 67 ga, so‘nggi 24 soatda esa -1 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 32.37% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 6.28% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 5 561 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 079 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 89 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13 ✔ @wegoch @Words19 ✔ @seiloch ✔ @zefenbicha Creator @leul_mekonnen1

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 01 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

17 186
Obunachilar
-124 soatlar
-187 kunlar
+6730 kunlar
Postlar arxiv
መሀመድ ጠዊል (ራስታው) [ ልዑል ዘወልደ ] [ 1 ] ልጅነቴን ከማስታውስባቸው ዘፋኞች አንዱ ነው ፤ መሀመድ ጠዊል ። ፀጉሬ ምኔ አድጎ እንደሱ ባወዛወዝኩ የምልባቸው ጊዜያት ነበሩ ። ሀሙስ ማታ do'ii sirbaa ላይ አይረሳም ። አላህን ሲል ሙዚቃን ትቶ በተውበት ከመመለሱ በፊት (አመታት ይሆነዋል) ባዛር ላይ ለመጀመሪያ ግዜ አየሁት ። ከካናዳ ይመስለኛል ፥ ብቻ ከረጅም ግዜ የውጪ ቆይታ መመለሱ ነበር ። ሲዘል ፥ ሲቦርቅ መድረክ ጠባዋለች ። በሚገርም ጉልበትና ሞራል ሶስት ዘፈኖችን አከታትሎ ዘፈነ ። ከሶስተኛው ዘፈን በኋላ ፥ ተወዳጇ ዘፈን መጣች "ሲ...ሲ" ፤ ይሄኔ ፥ ህዝቡም ማሜም አልቻሉም ፤ ታ...በ...ደ... ። ማሜ ይባሱን ወደ ህዝቡ መሀል ተወረወረ ። ጋርዶቹ ለአመታት የተነፋፈቁትን ህዝብና አርቲስት ለመለየት አልሆነላቸውም ። ለዘመናት ከተለየው ህዝብ ጋር ተቃቅፎ ተፋፍጎ ጨፈረ ። በመጨረሻም ፤ እወዳችኋለሁ ! ብሎ በእጁ ስሞን ተሰናበተ ። ቀጣይ መድረኩን የያዘችው ዘፋኝ ተስረቅራቂዋ ፍቅር አዲስ ነበረች ። የሆነ እንጉርጉሮዋን ጀምራ ድምጿ ወደላይ አቅጥና እያወጣች ሳለ ድንገት ማይክ ከአፏ ተመነተፈች ... (አለ ማይክ) ... ም...ሰ...ክ...ር ! ሃሃ ባንዱ እርሷን ተከትሎ ማጀቡን በድንገት አቆመ ። መድረኩም ፀጥ ሲል ሰውም ረጭ አለ ። ሁሉም በያለበት ተደናግጧል ። እንደምንም ፥ ማይኩን የቀማት ሰው ለየን ። ከርሷ በፊት ሲዘፍን የነበረው ፥ መሀመድ ጠዊል ነበር ። ሁሉም እያየው ነው ፤ በሆነ አስተያየት ፥ ይሄ ሰውዬ በቃ አልጠገበም ማለት ነው ሃሃ ... ፊቱ ግን እንደቅድሙ ልክ አልነበረም ። ጭራሽ ፥ በተጎማዘዘ የለቅሶ ፊት መድረኩ ላይ ተንበረከከ ። ምን ሊለን ነው ብለን ስንጠብቅ ... - ዋሌቴን እሺ ውሰዱት ! በአላህ ፓስፖርቴን ? ሃሃሃ @wegoch @wegoch @paappii

‎ሰራተኛ እያፈላለኩ በደላላ አንዲት  ልጅ አገኘው ‎ ‎አንገቷን እንደደፋች "ጋሽዬ እኔ የስራ ሆነ የሙያ ችግር የለብኝም ብቻ ‎ስራ እንዳልቆይ ተደግሞብኛል ፤ ሰርቼ እንዳልለወጥ አሰርተውብኛል" ምናምን ብላ ዘበዘበች ‎ ‎ ‎"ብሎ ነገር የለም እኔ ተረት ተረት አልወድም ድግምት ምናምን የለም " ብዬ ካለችው አምስት መቶ ብር ጨምሬ ቀጠርኳት ‎ ‎21 ቀን እንደሰራች ‎አንዴ ‎ ‎ጠረጴዛዬ ላይ አንገቴን ደፍቼ እየፃፍኩ አንድ ሶስቴ ስጠራኝ አልሰማ ብያታለሁ መሰለኝ ‎"ምን አባህ ይዘጋሃል ብላ" ‎ይዛው በነበረው ፔርሙዝ  አናቴን አለቺኝ ‎ ‎ተጮኸ። I think እኔ ነኝ የጮህኩት ‎ጎረቤት ተሰበሰበ ‎መቼ ፣ ማን እንደመታኝ በደንብ ያወቅኩት ከሁለት ቀን በኋላ ነው ‎ ‎መንፈስ ፣ ድግምት ፣ ተተብትቦብኛል የሚለኝ ሰው ሲገጥመኝ የጀመረውን አረፍተነገር ሳይጨረሰው ነው የማመልጠው ‎ ‎የሻሼን ፍንክት የቀመሰ ሰው በዚህ ነገር አይፈላሰፍም 😁 By Adhanom Mitiku @wegoch @wegoch @paappii

የቀድሞ የአርጀንቲና እና የቺሊ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆርጌ ሳምፓሊ 🗣️: "ከእለታት አንድ ቀን ምሽት ላይ አንዲት ቆንጆ ሴት ጋር ወደ ቡና ቤት ሄድኩ። ለብዙ ሰዓት አብረን ተቀምጠን በጣም ብዙ ነገር አወራን። ስለ እራሴ የዋህ እና ደግ እንደሆንኩ ነገርኳት። ስለ ህይወቴ በደንብ አወራኋት። ከእሷ ጋር በጥልቀት ለመተዋወቅ ፈልጌ ነበር። ለጠጣነው መጠጥ እንኳን ከፍዬ ነበር።" "በዚህ ጊዜ አንድ መልከ መልካም ሰው መጥቶ ከጎናችን ተቀመጠ። ለአምስት ደቂቃ ያህል ካወራት በኋላ ነይ አላት። እሷም ምንም ሳታቅማማ ተነስታ ሄደች። በቀጥታ ወደ መጸዳጃ ቤት ወሰዳት እና ወሲብ ፈጸሙ።" "ከዚያች ምሽት ጀምሮ የኳስ ቁጥጥር ብልጫ መውሰድ ወይም ኳስ መቆጣጠር በህይወት ውስጥ ምንም እንደማይጠቅም ተገነዘብኩ።" @wegoch @wegoch @paappii

አንድ ጓድኛዬ የሁለት አመት ፍቅረኛው ታማበት ፀበል ነገር ይዟት ይሄዳል ወደ ገዳም! እንደወሰዳትም "አንተ የseyጣን ነገር ነው  መለፍለፍ  ጀመረች ሳምንት እንቆያለን" ብሎ ደወሎ አሳወቀኝ! በመጨረሻም በሳምንቱ ከፀበል መመለሱን ነገሮኝ  እንገናኝ ብሎኝ ተገናኝን... ያው እኔም እንዳገኘውት እንዴት ሆነች ተሻላት ወይ ምናምን ብየ ጠየኩት! "አዎ!...ግን  የሷን ነገር አታውራብኝ " ምናምን አለኝ ነገሩ ግራ ሲገባኝ ምን ተፈጥረ? ምናምን ስለው ...መለያየታቸውን ነገረኝ! ግራ ገብቶኝ የታመመች ልጅ ወስደህ ፀበል  አስጠምቀሃት (seytan ኬዙ ሲሻላት ) ለምን ተለያያችሁ?... ስለው እሱም ቀጠለና "ባክህ ከፀበል ስንወጣ 'ይቅርታ መለያየት አለብን አለችኝ! ራሷ...'  እኔም ደንግጨ ለምን ? ስላት ...'አንተን የሚያፍቅርህ እኔ አልነበርኩም ሰይጣኑ ነበረ " አትለኝም መሰለህ"....ብሎ ነገረኝ .... By Jah mac @wegoch @wegoch @paappi

እየመጡ ነው! (አሌክስ አብርሃም) ቦሌና መገናኛ ጫማ ልትገዙ ስትሄዱ ድንገት አግኝታችሁት እንዳትደነግጡ ከወዲሁ ልንገራችሁ። የቻይናው ብሔራዊ የሕክምና ምርቶች አስተዳደር NEO (Neural Electronic Opportunity) ጭንቅላት ውስጥ የሚቀበር ቺፕ ለገበያ እንዲውል በይፋ ፈቅዷል። በዓለም ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የጭንቅላት ውስጥ ቺፕ የንግድ ፈቃድ ተሰጠ ማለት ነው። (እንደፈራነው) ጦቢያዊያን ለአመታት ችብስ 666 ...ስንለው የነበረው ጉዳይ ያው እየመጣ ነው። ነገ እንደጥርስ ማስታወቂያ በተወሳሰቡ የህክምና ቃላት ታጅቦ "አስመጥተናል" የሚል ማስታወቂያ መነገሩ አይቀሬ ነው። ለጊዜው ለአካል ጉዳተኞች ረዳትነት ብቻ ይውላል ብለዋል። ያው አንድ ነገር ከተመረተ በኋላ የቴክኖሎጅውን ፍጥነት በስልክ ማየት ነው። ዝርዝሩ ይቅርብን ግን ኤሎን ማስክ 'Neuralink' ብሎ የጀመረውን ፕሮጀክት ቻይናወቹ ቀድመው ለገበያ አውለውታል።የሆነ ቀን ቱርክ ፀጉር ከቱርክ አንጎል ከቻይና አሰገጥመን ሸገር ላይ እንግሊዝኛውን ልናዶለዱለው እንችላለን። ችግሩ ሀክ ሊደረግም ይችላል የሚል ስጋት መኖሩ ነው። አስበሽዋል እናት የሰርግሽ ቀን የባልሽ አንጎል ሃክ ቢደረግ? ወጩ ጋር ተዳምሮ... @wegoch @wegoch @paappii

የጠቋር ሚስት ጓደኛዬ አዲስ ሙሽራ ነው። ገና ስድስት ወሩ ነው ካገባ። የሆነ እሁድ ጠዋት ልጠይቃቸው ቤታቸው ስሄድ ይሄን ገንገበት ጓደኛዬን ባለቤቱ “ዳዲ” እያለች ስትጠራው ሰማሁ። ተወልዳ እስክታድግ በአንድ የአምበሳ ቆዳ ጫማ እየዳከረ ያሳደጋትን የአባቷን ስም እንደቀልድ ለስድስት ወር ባሏ መስጠቷ ግርም አለኝ። አጎቴ "ሴትና የቀበሌ ቤት የኔ ነው አይባልም" የሚለው እውነት ሳይሆን አይቀርም። ቤታቸው የሄድኩት እሁድ ጠኋት ስለነበር “ቸርች ልንሄድ ስንል መጣህ” ብለው አብረን ካልሄድን አሉኝ። ላለመሄድ ብሞክርም ባለቤቱ ቆጣ ብላ “ኖህ! ወደድራፍት ቤት እንሂድ ቢሉህ መች እምቢ ትላለህ? በል ተነስ” አለችኝ። ይሄ ግምብ ራስ ባሏ ድራፍት እንደምወድ ነግሯታል ማለት ነው። ሰነድ መሻሻጥ ተጀመረ? ብዬ እያመነታሁ አብሬያቸው ሄድኩ። የወሰዱኝ ቸርች አንድ ነብይ የሚያገለግልበት አዲስ የፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያን ነው። ጓደኛዬ ባለቤቱ በቅርቡ ጌታን እንደተቀበለች ነግሮኛል። ገና ውስጥ ገብተን አረፍ እንዳልን በከፍተኛ ድምፅ እየጮኸች ትፀልይ ጀመር። “ጌታ ሆይ ለዚህ አብሮን ለመጣው፣ ነፍሱ በሃጢአት ለታሰረችው ጎስቋላ ወንድሜ ዛሬ ድረስለት” ስትል ደነገጥኩ። ጭራሽ ስለኔ ነው ፀሎቱ? “ጌታ ሆይ” አለች ጭራሽ ተንጠራርታ እጇን ትከሻዬ ላይ ጭና። ድምጿ እየጨመረ ነው “ጌታ ሆይ፥ ዛሬ ስለዚች ነፍስ እፀልያለሁ ...” አለች። {እቺ ነፍስ የተባልኩት እኔው ነኝ} “ዛሬ እቺ ነፍስ ከስካርና ከሃጢአት ቀምበር እንድትላቀቅ እፀልያለሁ፥ እቺ ነፍስ ዛሬ ከዝሙትና ጌታ ከማይከብርበት የሃጢአት ልምምድ እንድትፈታ እፀልያለሁ” ስትል ቀና ብዬ ምእመኑን አየሁ። እኛ አጠገብ ያሉ ምእመናን ሁሉም ወደኔ እጃቸውን ዘርግተው ይፀልዩልኛል። የት ልግባ? ጭራሽ በሰው ሁሉ ፊት ሰካራም ነው። ያመነዝራል። ትበለኝ? ለምን አንደኛዋን የቲክቶክ ቪዲዮ አትሰራብኝም? ዞር ብዬ ጓደኛዬን ሳየው ሳቁን አፍኖ በቆረጣ ያየኛል። በስጋ ብገለጥበት ደስ ባለኝ። እሱ ነው አብረን በነበርን ግዜ ምንሰራውን ነገር ሁሉ ዘክዝኮ ነግሯት የሰው መሳቂያ ያረገኝ። የተወሰነ ቆይቶ ነብዩ ወደመድረክ ወጥቶ ፀሎት ማድረግ ጀመረ። ቤቱ ፀጥ አለ። አንዳንድ ሰዎች ብቻ በየመሃሉ አሜን ይላሉ። እሱም ትንሽ ከፀለየ በኋላ ... “የጌታ መንፈስ ጅብ ጋላቢ መንፈስ ያሳየኛል” አለ። የዚህ ግዜ የጓደኛዬ ሚስት ዞር ብላ አታየኝም መሰላችሁ? ምናባሽ ላርግሽ? ብላት ደስ ባለኝ። አንተ ነህ ለማለት ፈልጋ ነው? ይሄ የተረገመ ልጅ ጅብም ይጋልባል ብሏት ይሆን እንዴ? ነብዩ ቀጠለ። “በጉባኤ ውስጥ አንድ ሰው ይታየኛል። ቤተሰቦቹ ቃልቻ ነው ሚያመልኩት። እሱንም በልጅነቱ በአጋዘን ደም ያጥቡት ነበር። ዋናው የአጋንንቶች አለቃ ይጠቀምበታል” ሲል በሃዘኔታ እንደገና ዞራ አየችኝ። አረ እቺ ሴትዮ ለምን አትፋታኝም? እያልኩ ፀሎቱን መከታተል ጀመርኩ። ነብዩ ወደኔ አካባቢ ፍጥጥ ብሎ ካየ በኋላ ከመድረክ ወርዶ ቀጥ ብሎ መጣ ..... አሁንስ እኔም ፈራሁ። ስለኔ ነው እንዴ ሚያወራው? የሚል ሃሳብ ውልብ አለብኝ። ምናልባት ነፍስ ሳላውቅ ቤተሰቦቼ እንዳለው በአጋዘን ደም አጥበውኝ ይሆን እንዴ? መቸስ ሰው ማመን ከባድ ነው በዚህ ዘመን ምናምን እያልኩ ሳስብ ነብዩ አይኑን አፍጥጦ ቀጥ ብሎ እኛ ወዳለንበት መጣና እጁን አንስቶ....... የጓደኛዬ ሚስት ላይ ሲጭን ከተቀመጠችበት ወምበር ሁለት ሜትር ወደላይ ነጥራ መሬት ላይ ተነጠፈች። እግዚኦ ማህረነ ክርስቶስ። ምን ጉድ ነው? በኔ ሲስቅ የነበረው ጓደኛዬ ሚስቱ እንደዚያ ስትሆን ሲያያት ክፉኛ ደነገጠ። እኔም ምን መጣ ብዬ አንዴ ነብዩን አንዴ እሷን ማየት ጀመርኩ ነብዩ “ዋናው መንፈስ ተያዘ!” ሲል ጉባኤው በጩኸትና በጭብጨባ ተሞላ። ከዚያማ ያቺ ድምፀ ለስላሳዋ የጓደኛዬ ሚስት በሙላቱ አስታጥቄ ድምፅ ትለፈልፍ ጀመር “ተቃጠልኩ! አረርኩ!” “ማነህ?” አለ ነብዩ “ጠቋር ነኝ” “ተናገር የት ነው የያዝካት?” “ባሏ ነኝ። ከልጅነቷ አሳድጌ ነው ያገባኋት” አለ ሴጣኑ። ጓደኛዬን አየሁት ሚገባበት ጠፍቶታል። “ጭራሽ የሌላ አካልን ሚስት ነው ያገባሁት?” የሚል ይመስላል። አጋንንቱ ጭራሽ ወደሱ አፍጥጦ “አጠፋሃለሁ አንተ እርጉም ሚስቴን ነጠቅከኝ” እያለ መጮህ ጀመረ። ቺት አድርጋበት መሆኑ ነው። ጓደኛዬ እንዲሁም ፈሪ ነው ጭራሽ አሁን ከሰይጣን ጋር የግል ፀብ ውስጥ በመግባቱ ያልበው ጀመር። ያቺ መላአክ የመሰለች ሚስቱ ጭራሽ አይኗን አፍጣ በወፍራም ድምፅ ዛቻዋን ቀጠለች። “ወንድወሰን ደበበ ጊሚራው” አለችው ሌባ ጣቷን ወደሱ ጠቁማ። {ዳዲ ቀረ በቃ} ነብዩ ዝም ብሎ ያያል። “አንተን ካላጠፋሁ እኔ ጠቋር አይደለሁም” አለ መንፈሱ። ጓደኛዬ እንባ ተናነቀው። በሆዱ "Who TF did i marry?" እያለ ነው “ብዙ ግዜ በተኛህበት በገጀራ እንድትሰነጥቅህ አቅጄ ነበር። ዛሬ ይሄ ነብይ ቀደመኝ” እያለ ማጓራት ጀመረ። ጓደኛዬ እንባውን በአራት መንታ አወረደው። ምን ውስጥ ነው የገባሁት? የሚል ይመስላል። ብቻ አጋንንቱ ከነብዩ ጋር ውጣ አትውጣ እያለ ሲታገል እኔ እንደምንም ሾልኬ ወጥቼ ወደቀበሌ ጃምቦ ቤት ሮጥኩ። ከአዳራሹ ወጥቼ ጥቂት እንደሮጥኩ ሩጫዬን አቀዘቀዝኩና ወደኋላዬ ስዞር ጓደኛዬ ኮቱን ጥሎ በሩጫ ወደኔ ይመጣል። አጠገቤ ሲደርስ እያለከለከ ቆመና “ወዴት ነው ጥለኸኝ ምትሮጠው” አለኝ “እንዴ አንተስ ሚስትህን ጥለህ ወዴት ነው?” ስለው “አፍህን ዝጋ” ብሎኝ አብሮኝ ወደግሮሰሪ አመራ። አሁን ሰባተኛ ጃምቧችን ላይ ደርሰናል። “እኔ ግደሉኝ እንጂ ያቺን ሴት አምኜ እዛች ቤት አላድርም” ስላለ ተሰብስበን ወደቤቱ እንዲሄድ እየለመንነው እንገኛለን። By Noah Daniel @wegoch @wegoch @paappii

የቆሰለ ነገር ፣የከሳ ፣የኮሰመነ እንሰሳ እሚያድን አውሬ ያስጠላኛል ምቹ ግዜ እየጠበቀ ድምፁን እና ሁኔታውን የሚቀያይር ሰው ግን ያስፈራኛል። ስዩም ፦ ጓደኛው ነኝ ጓደኛዬ ግን አይደለም። ብዙኅ አሳልፈናል ። ቢሰማብኝ የማፍረውን ነገር ወይ ቢሰማብኝ ጉድ የሚያደርግብኝን ነገር አልነግረውም ። እፈራዋለሁ። ቋሚ ወዳጅ ስለሌለው እና ዋሉልኝ ያለቸውን ሰዎች ሁሉ በየምክንያቱ ስለሚተዋቸው እፈራዋለሁ ። ከጓደኞቹ X ስር ስለማይጠፋ ስሜቱን ሁሉ የተሰማው ሰዓት ስለማያንፀባርቅ አብሬው ሆኜ አይጥ ለመያዝ ትክ ብላ እንደምታደባ ድመት ነው የማየው። እሱ እንደድመቷ ትኩረት ሲያደርግ ሁኔታው እንደድመቷ አይነት አይደለም አያስታውቅበትም ። ዘና እያለ እየሳቀ ሚስጥር እየነገረ ነው ሚስጥር የሚያስወጣው ። ስዩምን እፈራው ነበረ .....! ችግር ገጠመኝ ከሁሉም በላይ አብሮኝ ሆነ ያለውን ሁሉ ሰጠኝ አሰጣጡ ስሙልኝ እዩልኝ ያለው አልነበረም በችግሬ አብረውኝ ያልነበሩትን ስወቅሳቸው እያገዘ አላባባሰብኝም... "ተዋቸው አልሞላ ብሎቸው ነው" አለኝ ....ከነሱ ጋ ሆኜ ያጣጣልኩት ስዩም አብሮኝ ቆመ .... ተፀፀትኩ ...! ከብዙ ግዜያት በኋላ ስዩምን በየወሬው እንደዚ አትመስለኝም ነበር እያልኩ እሱ ላይ ያለኝን አቋም ተናዘዝኩ አልተናደደም ሳቀ ስልከው እና ሲላከኝ እንደኩያ አይደለም እንደታናሽ ነው ሲተማመንብኝ እንደታላቅ ነው ...! እሚያግዘን እና የሚኮራብን ወዳጅ የኛ ሲሆን የሚሰማውን ምቾት አሰማኝ ከጥቂት ግዜ በኃላ ... ስራ በዛብኝ ብዬ የሰጠሁንት ላግዝ ብሎ የወሰደውን ሙሉ ውክልና ተጠቅሞ መኪናዬን ሸጦ አውሮፓ መግባቱን ከሳምንት በሆላ ሰማሁኝ ... ስስቅ ላየኝ ሰው ተታልዬ አልመስልም ነበር ... ማመን ከመጠራጠር በላይ ዋጋ ያስከፍላል ማለት ነው ?? መፍራት ከመድፈር በላይ አቅም አለው ማለት ነው ?? ኮቴ በሰማን ቁጥር እየባነንን የት ድረስ እንሄዳለን ?? የሄድንበትን መንገድ እየጠየቅን መሄድ የሰውነት እጣ ፈንታ ነው ??.... በርግጥ የግዜ ጉዳይ እንጂ ከተካደ ሰው የከዳ ሰው ያሳዝናል!! By Adhanom Mitiku @wegoch @wegoch @paappii

Repost from Sunset Hiking
🌄 We’re Back And We’re Hiking Again Hey Sunset community 🌄 Life happened. The city got louder. And for a while, the sunsets
🌄 We’re Back And We’re Hiking Again Hey Sunset community 🌄 Life happened. The city got louder. And for a while, the sunsets were quieter without us. Sunset Hiking is officially back with a stronger team, clearer plan, and a growing 4,000+ hiking community ready to move again. Over the next weeks, we’ll be sharing: 🥾 Upcoming sunset hikes 🌅 Community moments 🧭 Safe, well-organized experiences If you’re still here, it means you love nature as much as we do. Let’s start again one sunset at a time. 🌄👣

የ ሥዓሊ እና መምህር ኃይሉ ክፍሌ "ተገማች፡ ዋዜማ" የሥዕል አውደርዕይ እዚህ ትርዒት ላይ ተገኝቼ፣ በከተማ ዝመና ውስጥ የማንነትንና የትዝታን ትርጉም የሚፈትሹ ስራዎችን ተመልክቻለሁ። የጥበብ ስራዎ
+9
የ ሥዓሊ እና መምህር ኃይሉ ክፍሌ "ተገማች፡ ዋዜማ" የሥዕል አውደርዕይ እዚህ ትርዒት ላይ ተገኝቼ፣ በከተማ ዝመና ውስጥ የማንነትንና የትዝታን ትርጉም የሚፈትሹ ስራዎችን ተመልክቻለሁ። የጥበብ ስራዎቹ የሚጠቀሟቸው ቁሶችና የሚያነሷቸው ሰብአዊ ጥያቄዎች ቆም ብሎ ለማሰብ ትልቅ እድል ይሰጣሉ። የለውጥ ሂደቱ ወዴት እየወሰደን ነው? የጋራ ትዝታችንን እያካተትን ነው ወይስ እየረሳን? እነዚህንና መሰል ጥያቄዎችን የሚመልስ ድንቅ ትርዒት ነው። እድሉ ያላችሁ እንዳያመልጣችሁ! 📍 እስከ ግንቦት 24 ድረስ ክፍት ነው @Seiloch #Hailukifle #artExhibition.

ሰው ብቻ አይደለሽም! Sirak Wondemu እናትነት ዓለምን አምጦ መውለድ ነው። በምጥ ጣር ተይዞ ለሚቃትት ነፍስ የውልደት እልልታን በከንፈሩ ሰማይ ይዞ እንደሚዞር ደመና ነው። ሰው እውነትን መፃፊያ ጠመኔ ሲሆን እናት የጠመኔው መዳረሻ ሰፊ ሰሌዳ ናት። ትሁንልህ መወደሻ ተብላ በባርኮት የተሰጠች ስጦታ! በግምባሯ መስመር ላይ ዘመን ፅፋለች። በመዳፏ ስር ሕይወት ወልዳለች። ሽብሽብ ቆዳዋ እድሜን ዘምሯል። ዳሳሽ ጣቶቿ ቀንን ፈክሯል። ሰው ብቻ አይደለችም! በወዟ ጠፈፍ ከራሰ የሻሿ ጨርቅ የበለጠ የዓለም ታሪክ የለም። ጊዜና የሕይወት ዑደት አዳውረው በጥቁር ጸጉሯ መሀል እንደበተኑት የሽበት ተክል ያህል መቆዘሚያ ሀሳብ አልነበረም። እማማ ንፁህ ፈገግታሽ የንግስ ቀን ነው። የእሺታ ደጅሽ የዓለም ብርሃን ነው። ሁሉን ቻይ ልብሽ ዕፁብ ተምሳሌት ... በጊዜ ጣይ ፊት የማይሞት አይነት ፤ ነው። ኩርፊያሽ ውስጥ እንደነገሩ የወለድሽው ልጅ ፈገግታሽ ያጫውተኛል። የውሸት ተኮሳትረሽ ከሸበሸብሽው የግምባርሽ መስመር ላይ መጥምቁ ዮሐንስ እየሱስን ባጠመቀበት ቅፅበት ትከሻው ላይ ያረፈችውን ፀዓዳ እርግብ እመለከታለሁ። አለሀሳብ መከደን ካማረው መንታ ዓይኖችሽ ውስጥ ፍቅር ጠምቃለሁ። ሰው ይርበኛል። ተስፋ ጠምጄ... እምነት አርሳለሁ! እማማ ልጄ ሰው ሆነልኝ ዩኒቨርስቲ ገባልኝ ብለሽ ግማሽ ደስታ ግማሽ ሀዘን ሆነሽ የሸኘሽኝ ቀን ትምህርትን ለዘላለም ረገምኩ። ከእነዚያ ብርሃናማ ዓይኖች ብርቅ ... ከህመም ፈዋሽ ጠረኖችሽ ብሸሽ ... ከሞት መላሽ ዳሳሽ ጣቶችሽ ብሰደድ ፤ ማወቅ የገሀነም ፀሎት ሆነብኝ። ክረምቱ መጥቶ ጉያሽ ውስጥ ሽሽግ እንድል አርጩሜ ቆርጠሽ በጋውን አባሪልኝ። ኮስተር ብለሽ ሀምሌን ጥሪው። ነሀሴም ይምጣ! አንቺ ከተቆጣሽ ሁሉም ቀና ይሆናል! እማማ እምባ አርግዞ በስስት የሚያየኝ ክርትት አይኖችሽ እንዴት ናቸው? ዛሬም ለመንገደኛ እንዳዘኑ ነው? ለነፍሰጡር ላም እንደተንሰፈሰፉ ነው? በቅርሻቴ ያረጠብኩት ጀርባሽ ... ዓለሜን የተሸከመው ጫንቃሽ ዛሬም ከመቻሉ አልተፈታም? እኔማ እነሱን ለማየት ለመንካት በስንት ቀናትና ወራቶች ደረት ላይ ተሳብኩ! ሺህ ናፍቆት ከፊቴ ሺህ ጉጉት ከኋላዬ አጅቦኝ በርሽ ለመቆም ተሳልኩ! ለስንት ንጋቶች ለፈፍኩ! ሰው ብቻ አይደለሽም። ብትይኝም አላምንሽም! ሞገስሽ ልክ እንደታቦት ነው። ቁጣሽ ሀገር ያርማል። የወደቀ ቀዬን አንስቶ በውል ያቆማል። ዝምታሽ እንደፍርድ ቀን ይጨንቃል። ይጠባል። ሳቅሽ እንደእሸት ባቄላ ታኝኮ አይጠገብም። መርቀሽ የሳምሽኝ ግንባሬ ዛሬም በብርሃን እንደታጀበ ነው። ኑርልኝ ብለሽ የመረቅሽኝ ምርቃት እኔ ካልሰለቸኝ ከሞት እንደሚታደገኝ ቃል ገብቶልኛል። እማዬ ከእንግዲህ ይራባል ብለሽ አትስጊ! ይልቅ የስጋት በርሽን ዝጊ! ያኔ በጨቅላነቴ ዘመኔ እንደወፍ ልጅ ከአፍሽ ነጥቄ የጎረስኩት እስከ እለተ ሞቴ ከአንጀቴ ይኖራል። አምሳያ የሌለው ውዴታሽ ሞትን ማምለጫዬ ነው። የአንቺ ትካዜ የሀገር መፍረስ ነው። ያ ልዝብ ቃልሽ የንጋት ቀን ነው። ሰው ብቻ አይደለሽም! በነጠላሽ ጫፍ የሰው ልጅ ቋንቋ የማይገልፀው የእረፍት ዋኔ - በመቀነትሽ ስር ያልታየ ያልተሰማ ስውር ቅኔ ተቋጥሯል። ከአንቺ ጋር አይደለም አስር ሀያዬን ሰባ ሰማኒያዬን መሰንበት እፈልጋለሁ። እማ አንቺ ወዳጅ የለሽም ወዳጅሽ እኔ ነኝ። እኔም የአንቺን ያህል ግምት ሰጥቶ የሚቀበለኝ ወዳጅ የለኝም። ወዳጄ አንቺ ነሽ! ቀሚስሽን በለጋ ጣቶቼ ጨብጬ የቆምኩባቸው የጎረቤት ቡና ቅፅበቶች አይረሱኝም። ገበያ ሄደሽ እስክትመለሺ መንገድ መንገዱን እያየሁ ጉበን ታቅፌ የተኮራመትኩባቸው ወቅቶች አይኔ ላይ ናቸው። አባቴ ነጥቆሽ ዓመት ከዓይንና ድምፅሽ ርቄ የተመለስኩ ቀን ዘማች በህይወት ተርፎ እንደመጣልሽ ሁሉ በስስት ያነባሽው ዕምባ አንቺ ብትፈቅጂ ወንዝ ሆኖ ይወስደኝ ነበር። ሰውነትን የለካሁብሽ ፤ የፍቅርን ትርጉም የሰፈርኩብሽ ፤ ትናንትን ፣ ዛሬንና ነገን የመዘንኩብሽ ሚዛኔ ነሽ። ሳቅሽ ውሎ ሳይገባ እንዳይመሽ እፀልያለሁ። ስጋትሽ ስጋት በልቶት ሳይጠፋ ዘመን እንዳያልፍ እፈልጋለሁ። በትከሻሽ ላይ ቆሜ ጎበዝ ተብያለሁ። አንድ የናፍቆትሽ ዘለላ አንገቴ ላይ ቢታሰር ይዞኝ ጥልቅ እንደሚወርድ ግን የተረዳኝ የለም። አድጌ አንቺን ረሳለሁ? ቤት ይኖረኛል? እሸሽሻለሁ? አመመኝ ብትይ እረጋጋለሁ? ልቤ ይሰክናል? እኔ'ንጃ ! ልጅ ሆኜ አጎቴ ሞቶ በሀዘን ቅስምሽ ስብር ሲል ፤ ማቅ ስትለብሺ እግዜር ከትምህርት ቤታችን ዳገት በላይ ያለ እየመሰለኝ ሄጄ «አንተ አትችልም እናቴ ትሁን! » ብዬ መኮሳተር ያምረኛል። ሰፈር ሰው ሞቶ ለቅሶ ስትሄጂ መንደርተኛው እርር ሲል ... ምርር ብሎ እምባውን በጉንጩ በራፍ ሲደፋ ያ አባባሌ እውነት ሆኖ እታዘባለሁ። « በቃ እሱ አይችልም እናቴ ትሁን! » እላለሁ በልቤ። እዝነት እንደሌለው ሁሉ ፤ ምህረትን እንደማያውቅ ዝንጉ አባት ፍፁምነቱን እንድጠራጠር ያደረገኝ ፍቅርሽ ነው። ለሁሉም ነገር ሆደ ባሻ የሚሆነው አዛኝ አንጀትሽ ነው። አንቺ እኮ እግዜርን ብትሆኚ የሰፈራችን ሰዎች በሙሉ ማሪያም ቤተክርስቲያን እንዳሉ ዛፎች ሰማይ ጠቀስ እንደሆኑ ይሸብቱ ነበር። እማማ እርጅና በአንቺ ላይ ስልጣን እንዳይኖረው የአንቺን ቁጣ ኮርጄ እቆጣዋለሁ። ሞት በሰፈርሽ እንዳያልፍ በርሽ ላይ አያ-ጅቦ እንዳለ ነግሬ አስፈራራዋለሁ። እማማዬ ቃል የእምነት እዳ ነው ይላል ፀጋዬ። ቃል የእምነት ዕዳ መሆኑን የተረዳሁት ግን በአንቺ ነው። ዛሬም በሰው ሀገር ሆኜ የተቆላ ቡና ሲሸተኝ ትዝ ትይኛለሽ። ትኩስ ሽሮ ሲሸተኝ ፤ ጠይም ፈገግታም እናት ስመለከት ዓይኔ በእምባ ይሞላል። ማን ያውቃል ዛሬም ህፃን ልጅ ሲጮህ ትደነግጫለሽ አይደል? በሌለሁበት ቀዬ ተጋደሉ ሲሉሽ እግርሽን ብርክ ብርክ ይልሻል አይደል? እማዬ ጌሾ ያልወቀጠልሽ እጄን እጠላዋለሁ። ስታዢኝ በእምቢታ የሰበቅኳቸውን ትከሻዎቼን እጠየፋቸዋለሁ። ለእነዚያ ጊዜ ... ለእነዚያ ወቅቶች መዳፍሽ ስር ፊቴን ቀብሬ ማልቀስ እፈልጋለሁ። ስትገርፊኝ ያኮረፍኩባቸውን ቀኖች ባገኛቸው እንደልጅነቴ ድንጋይ ወርውሬባቸው ሮጣለሁ። ማጀትሽ በጥጋብ ይሙላ! ... ሰላምሽ እንደአሸን ይፍላ! የጦር ቃል ጆሮው ይደፈን ... በደጅሽ ፍቅር ይሸመን! ማሳሽ ላይ አዝዕርት ይብቀል! ... ይመር ሰማዩ እንደምንጭ ይጥለል። አዛኝ ነሽና መርቂኝ አለሁ... ክፉሽን ከቶ አልስማ ሳለሁ! ገብያሽን ጥጋብ ይውረሰው አይጉደል ዘመኑን ሙሉ... የተኳረፈም ይታረቅ ሁሉ! አካል ነሽና ለምድሩ ለሰው... ስሁት ደስታሽን ቀን ይደግሰው! ብቻ እማማ አንቺ ሰው ብቻ አይደለሽም ፤ እግዜር ነሽ ለልጅሽ ... ሚዛን ነሽ ለምድሩ.. ባርኮት ነሽ ለሰማይ አድባር ነሽ አውጋር ነሽ የኔ አድባር። መላዕክ ነሽ ልዩ ሰው! የአጥቢያ ዳኛ የአንቺን ያህል ፍትሕ አያውቅም! ውብ አዝማሪ ከእሽሩሩሽ የተሻለ ዜማ አይደርስም። በዓይኖችሽ ስር የፀነስሽው የተስፋ እምባ ለመኖሬ ለመዳኼ ሆኗል መባ! አለው ዋጋ! አለው ፀጋ። አስራቴ ነሽ ጃኖ ጥለት... ወደር የለሽ የሰው ቁመት። ብቻ ብቻ . . . አንቺ ሰው ብቻ አይደለሽም... ብትይኝም አላምንሽም። . . . መልካም የእናቶች ቀን ❤

ሶምሶማ የአጫጭር ልቦለዶች መጽሐፍ -በጃፋር መጽሐፍት መደብር(ለገሀር) -አብዱ book delivery (ፒያሳ) - +251994886247 ሰለሞን አራት ኪሎ ያገኙታል።@sirakoo @wegoch @wegoch @wegoch

ADDIS ABABA — FOR SUDAN Voices From Sudan On April 21, join us for a powerful evening where film, music, and community come t
ADDIS ABABA — FOR SUDAN Voices From Sudan On April 21, join us for a powerful evening where film, music, and community come together to mark the 3rd anniversary of the Sudan war. The night opens with a special live performance by The Tana Quintet by Hazim Alshafei, bringing the rhythm, soul, and resilience of Sudan to life—followed by a screening of the acclaimed film Khartoum. ✨ Free Entrance This is more than a screening. It’s a gathering. It’s a shared moment. It’s solidarity in action. Expect a full house, a powerful atmosphere, and a night that will stay with you. 📅 Tuseday, April 21, 2026 📍 Bata Complex 22, around Golagul 🕠 5:30 PM Bring your friends. Be present. Stand with Sudan. #Khartoum #Sudan #AddisAbaba #InDeepCultures #FilmScreening #LiveMusic #1960Films #AddisCinemaClub

📌 በሀዋሳ ከተማ አዲስ የስነ-ጥበብ ትምህርት ቤት የምዝገባ ጥሪ! ጥበብን ለሚወዱ እና ተሰጥኦአቸውን ማሳደግ ለሚፈልጉ ሁሉ ታላቅ እድል! በሀዋሳ ከተማ ከዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር አዲስ የስነ-ጥበብ (ስዕል) ትምህርት ቤት ስራ ሊጀምር ዝግጅቱን አጠናቋል። 🎨 ለምን ይመዘገባሉ? • በዘርፉ ብቁ በሆኑ ባለሙያዎች የታገዘ ስልጠና ለማግኘት። • ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በተቀናጀ መልኩ እውቀትን ለማዳበር። • የፈጠራ ስራዎትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር። 🌟 የእርስዎ ድርሻ፦ ጥበብ የሀገር መገለጫ ናት! ይህ መልዕክት እንዲደርሳቸው የሚገባቸው ወጣቶች እና ፍላጎቱ ያላቸው ግለሰቦች እንዲያውቁት በማጋራት (Share በማድረግ) ማህበራዊ ሀላፊነትዎን ይወጡ። ምዝገባው ተጀምሯል!👇👇 link ይጫኑ https://tally.so/r/D4Jjrl.

ፖስታዬንና ክርታሴን አንጠልጥዬ እንትና በሰጠኝ አድራሻ ታክሲ ይዤ አዲስአባ አስራምስት ቀን ያህል ቆይተን ለመመለስ ሁለት ቀኖች ሲቀረን ሄድኩ። ስድስት ኪሎ አፍንጮ በር አካባቢ ነበር። በር ሳንኳኳ የከፈቱልኝ ጥምጥም ያደረጉ፤ ፂማቸውን የተላጩ፣ ሽበት ጣል ጣል ያደረገበት ገፅ ያላቸው መልከ መልካም ጠይም ሽማግሌ ነበሩ፡፡ መምጣቴን ቀደም ብዬ ስልክ ደውዬ ነግሬአቸው ስለነበር፣ በስሜ ጠርተው በትህትና እንድገባ ጋበዙኝ፡፡ ቤት ውስጥ እሳቸውና ፊታቸው ብቻ እስኪቀር የተከናነበ ሌላ ሴት ነበሩ፡፡ ገና እንደተቀመጥኩ ራት በልቼ (ማታ ላይ ነበር የደረስኩት) እንድሄድ ሲጠይቁኝ፣ በሥነስርዓት ተከላክዬ ፖስታውንና እቃቸውን በእጃቸው ሰጠኋቸው። ስለ ልጃቸው ጤንነት ከጠየቁኝ በኋላ፤ የሚያበረታታቸውን መልስ ሰጥቼ ከተቀመጥኩበት ስነሳ፣ አንድ የሚያጫውቱኝ ነገር ስላለ በጥሞና እንድሰማቸው አግባቡኝና ተመልሼ በመመቻቸት ተቀመጥሁ። «እግዚአብሄር አንድ ነው፣ አየህ፤ ስሙን ሰዎች ይለያዩታል እንጂ አላህ ብትል፣ እግዚአብሄር ብትል አንድ ነው። ቅድመ አያቴ እስላም ነበሩ። ልጃቸው ክርስቲያን አገባና ከዚያ በኋላ ክርስትናው ቤታችን ገባ። የድሮ ሰዎች ናቸው። ለምን? በለኝ አላህ በለው እግዜር በለው ያው ነው። ልጄ ሆላንድ የቤተክርስቲያን አመራር ይሠራል ሲባል ሰምቼአለሁ፣ እሱም አንዴ ሰላም ሊል ደውሎ አጫውቶኛል። ልክ ነው? (‘ኧረ የማይገባበት ቦታ የለም’) አንድ ነገር ልንገርህ፤ እኔ ወደ ቅድመ አያቶቼ ሐይማኖት ተመልሼአለሁ» ግድግዳ ላይ በመስታወት ውስጥ ሆኖ የተሰቀለ ዳንቴል የመሰለ የዐረብኛ ነገር የተፃፈበት ነገር አሳዩኝ፡፡ «ዐረብኛውን ባላውቀውም አላህ ከሰዎች ጋር በሚገባቸው ቋንቋ ይናገራል፡፡ ነቢዩም እንዲህ ነው የሚያስተምሩት፤ ስማቸው ይባረክና፡፡ ግን ልጄ እንዲከፋው አልፈልግም፡፡ ‛አባቱም እናቱም ሰለሙ' ተብሎ ቢሰማ ያዝናል፣ ይበሳጫል፡፡ (ኧረ ካሽ ካገኘ ግድ የለውም)፡፡ ግን እዚያም ስገዱ ነው፣ እዚህም ስገዱ ነው። 'አለማየሁ' የተባለ ስሜን ‛አብዱላሂ' አሰኝቼአለሁ፡፡ የሰፈር ሰው ገና አለማየሁ' ነው የሚለኝ፡፡ ክፋት የለውም፡፡ እንዲህ ያደረግነው ለጥቅም አይደለም፡፡ ለእሱ ነው። ለእምነቱ ነው። ታዲያ ከልጄ ጋር ተገናኝታችሁ ድንገት ወሬ ቢነሳ መነሳቱ መቼም አይቀር፣ እንደ ሰለምኩ አትንገረው፡፡ ይኼን ቃል ግባልኝ፡፡ ያለዛሬ አይቼህ አላውቅም፡፡ መቼም ታምነህ የተላክህ ሰው ስለሆንክ፣ ብትግባቡ ነው መቼም (‛ከቴም ተግባባን') ቢሰማ ችግርይኖረዋል? እንጃ እንግዲህ ባትነግረው ባታወራው ግን ይመረጣል፡፡ እንዳይሳትህ ብዬ ነው» ሴትዮዋ/ባለቤታቸው ከእኛ ራቅ ብለው በጋቢያቸው ተሸፋፍነው ታስረው የተቀመጡ መስለዋል፡፡ ቃል አውጥተው አይንገሩኝ እንጂ ከአስተያየታቸው፣ ከአንገት አደፋፋቸው እየተለማመጡኝ እንደሆነ ይገባኛል፡፡ ለሰውዬው ከአፌ ቃል እንደማይወጣኝ፣ በተፈጥሮዬ (ምናልባት ስወለድ ጀምሮ ወይም ከእናቴ ሆድ ጀምሮ ለሐይማኖት ግድ እንደሌለኝ፤ እንደውም እሳቸው ያሉት የእግዜር መመሳሰል ትልቁ እውነት እንደ ሆነ አንስቼ) ሳይሆን አይቀርም ሚስጢር ቀርቃሪ በመሆኔ ትንፍሽ እንደማልል፣ አንዲት ቃል ከአፌ ጠብ እንደማትል ቃሌን ሰጠኋቸው፡፡ ክርስቶስን ጠርተው መረቁኝ፡፡ ከተቀመጡበትም ተነስተው ትከሻዬ ላይ ሳሙኝ፡፡ ሲሰናበቱኝና ሲሸኙኝ ሽማግሌው ዐይኖች ውስጥ ሊሸፍኑት ያልቻሉት ወፍራም እፍረት ነበር፡፡ ለመቅደስ ይሄን ሁሉ አልነገርኳትም፡፡ *** By | አዳም ረታ/ 📖 ይመያመ @wegoch @wegoch @paappii

የሳሪሱ ወጣት እና የቱርኳ Player ------------------------------------- ምነው ባላወቅኳት ያልኩበት ጊዜ ነበር...! at that time She gave me a Trauma. የደግነት ማስኳን አጥልቃ ነገር ግን የክ-ፋት ሀሳቧንም በውስጧ ሰቅዛ ተለሳልሳ ስትቀርበኝ ምን ነበር አይኔን የጋረደው..? 😁 . . እንዴት ልታሳየኝ የፈቀደችውን ብቻ ተመለከትኩላት..? ልትደብቅ የሞከረችውን ማንነት እንዴት ማየት አቃተኝ..? ወቅቱ 2014 ዓ.ም ነው። ወርሀ መጋቢት። ክስተቱ ዛሬ ድፍን አራት አመት ሞላው። በአንዲት የቢሾፍቱ ቆንጆ የተታለልኩበት ሁኔታ እና አጋጣሚ ተፈጥሮ ነበር። አጃጃለችኝ። አሞኘችኝ። አጭበ-ረበረችኝ። አወጫበረችኝ። የምትኖረው ቱርክ ነው። በወቅቱ Turkey መኖር ከጀመረች 3 አመታትን ያህል አስቆጥራለች። የተዋወቅነው በ Facebook ነው። Long Distance Relationship መሆኑ ነው እንግዲህ። ከ Messanger ወደ Telegram ባደገው የስልክ ልውውጣችን - በየቀኑ ለሰአታት በ Video call እናወራ ነበር። አስታውሳለሁ የሆነ ሰአት ላይ እንዲሁ በ Telegram - Video call አውርተን ስንጨርስና መጨረሻ ላይ ቻው ስንባባል - ስልኩን "አንተ ዝጋው..አንቺ ዝጊው..አንተ ዝጋው.." ተባብለን እናውቃለን። ከአንዴም ብዙ ጊዜ። Straight 5 ሰአት ያህል በስልክ የምናወራበትም ጊዜም ነበር። . እንደ እኔ እንደ እኔ ይህ ፍቅር የሚባለው ነገር መጃጃል ነው የሚመስለኝ።It is all Imagination. Glazing a person without any valid reason. There is no reason to glaze someone like that. ይህ ጉዳይ በሳይንሳዊው ዓለም Limerence ወይም ደግሞ Halo Effect ተብሎ ይጠራል። አንድ ሰው ሲያፈቅር አንጎሉ ውስጥ የሚረጩት Dopamine እና Oxytocin ልክ እንደ እ-ፅ ናቸው። እነዚህ ኬሚካሎች ሲበዙ ደግሞ... የወደድነውን ሰው ድክመት እንዳናይ ያደርገናል፣ የማይረቡ ነገሮችን እንደ ትልቅ ቁምነገር እንድንቆጥር ያደርገናል፣ በዚህ ሰዓት የምንወስነው ውሳኔ Logic የለውም። . ለማንኛውም.. የባለታሪካችንን ስም R እንበለው። R እሳት ነች ፤ ዛሬ ላይ ሁሉም ነገር አልፎ ሳስበው አድናቂዋ ነኝ። እንዴት እንዳወጫበረችኝ ሳጤነው በራሴ ሽምቅቅ እላለሁ። ቢሾፍቱ ተወልዳና አድጋ የመሀል ከተማ ልጅ [ የአዲስአበባ ልጅ ] ለዛውም የሳሪስ ልጅ ላይ ድራማ የሰራች እሳት ናት። መጀመርያ ከእኔ ጋር የፍቅር ግንኙነት ስትጀምር ሌላ ያላለቀ ግንኙነት ላይ እያለች ነው። እኔ ይህንን አላውቅም ነበር። መጨረሻ ላይ ነው የደረስኩበት። መጀመርያውኑ ፍቅረኛ እያላት ለምን ከእኔ ጋር መሆን ፈለገች..? . ከእኔ ጋር እንደተዋወቅን እንዲሁም ለረጅም ጊዜ [ ለ 4 ወር ያህል ] in Contact እያለን የበፊት ፍቅረኛዋን ሙሉ ለሙሉ አልተወችውም። በሳምንት 1ዴ ወይም 2ቴ እየደወለች ታወራዋለች። ከእኔ በፊት የነበረውን ልጅ ከመተዋወቋ በፊት ደግሞ ሌላ ፍቅረኛ ነበራት - unfortunately ያንንም አልተወችውም። ከዛ በፊትም ሌላ ፍቅረኛ ነበራት - ያንንም አልተወችውም። ሁላችንንም አልተወችንም። እንደ የቤት አውቶሞቢል [ የቤት መኪና ] በአንድ ጊዜ 4 ሰው አሳፍራ ነበር ስትጓዝ የነበረው። ልጅቷ Multi-tasking ትችላለች። በአንድ እጇ ለኔ ቴክስት እየፃፈች፣ በሌላኛው እጇ ደግሞ ከሌላው ጋር ቪዲዮ ኮል ታደርጋለች። 4 መኪና በአንድ ጊዜ የምትነዳ Formula 1 ድራይቨር ናት። ይሄን ሁሉ መጨረሻ ላይ ነው የማውቀው። ከአንድ ወንድ ጋር ሆና - ወደ ሌላ ወንድ። እኔን አስምጣ ወደ ሌላ - ያኛውንም አስምጣ ወደ ሌላ - ይሄኛውንም አስምጣ ወደ ሌላ። She is a player type of sh-it. . በአንድ ጊዜ አራት ወንዶችን እንደ ቼዝ ጠጠር እያገላበጠች ስታጫውት አንዱ ለሌላው እንቅፋት እንዳይሆን ያደረገችው Scheduling የሚገርም ነበር። እኔ ስልኩን "አንቺ ዝጊው.. አንተ ዝጋው" እየተባባልኩ በቪዲዮ ኮል ስሟገት፣ እሷ ግን ለካ በሌላ ስልኳ ሌላኛውን "አንተ ዝጋው.." እያለችው ነበር። ፍቅር ሳይሆን ለካ የኔትወርክ መጨናነቅ ውስጥ ነበርኩ..😁 በነገራችን ላይ.. እኔ በጣም ጠንቃቃ ነኝ። እንደ እኔ ተጠራጣሪ ሰው አልነበረም / አሁንም የለም። ማንንም አላምንም። መጨረሻ ላይ ይሄ ባህሪዬ ወይም ጥርጣሬዬ [ my Gut felling ] ነው እውነታው ላይ እንድደርስ ያደረገኝ። እኔ ጥላዬንም አላምንም። እሷን ግን እንዴት ላምናት እንደቻልኩና - ሙሉ ሀሳቤን እንደሰጠኋት ሳስብ ይገርመኛል። እንኳን ክፉ ድርጊት ሊያደርግ ያሰበን ሰው ይቅርና ያላሰበን ሰው ራሱ የምጠራጠር አይነት ሰው ነኝ። . ልባችሁ የሆነ ነገር ሲነግራችሁ አትናቁት። ልባችሁ የሚነግራችሁን አትናቁ። እኔ ተጠራጣሪው የሳሪስ ልጅ፣ በውበቷ ምክንያት እውነታው ተጋርዶብኝ Gut Fellingኤን አላዳመጥኩም ነበር። ቆንጆ ፊትና የተረጋጋ አንደበት ሁልጊዜም ቅንነትን አይወክሉም። አንዳንዴ እጅግ Calculated የሆነ አቀራረብ ከጀርባው የተቆፈረ ጥልቅ ጉድጓድ እንዳለው ማወቅ ነበረብኝ። እኔ ተጠራጣሪ ነኝ እያልኩ ግን የእኔ Gut feeling የሚሰጠኝን ምልክት ውበቷ ሸፍኖብኝ ነበር። ጥርጣሬ መጥፎ አይደለም። መጠርጠር ማለት ነፍስህ ራስህን እንድታድን የምትሰጥህ Alarm ማለት ነው። Infact በመጀመርያዎቹ ሳምንታት ያሳየችኝ እጅግ Calculated የሆነ - እንዲሁም የተጠና አቀራረብ አውሮኝ ነበር። . በውበቷ አሻፍዳኝ፣ በምላሷ አታላኝ የገባሁበት የ 6 ወር የፍቅር ህይወት በመጠኑም ቢሆን Scar ጥሎብኝ አልፏል። ፍቅር እውር ነው ይላሉ። እኔ ግን ሽፍድናዬ ነው ያሳወረኝ እላለሁ። ልጅቷ ቆንጆ ናት። በተለምዶ ቀይ የምንለው ወይም Light skinned የሆነው የቆዳ ቀለሟ - እንዲሁም ሰላም ተስፋዬን የሚመስለው መልኳ - ጨዋ ጨዋ የምትጫወተው ነገር - ምሁር ምሁር አንባቢ አንባቢ የሚያደርጋት ነገር - ይሄ ሁሉ ተደማምሮ አስምጣኝ ነበር። በኋላ ላይ ግን ሁሉንም ነገር ስደርስበት እኔ ብቻ አይደለሁም የተጣላኋት። እያንዳንዱ ስታወራቸው የነበሩ ወንዶችን ሰብስቤ እስካሁን እየተጫወተችብን እንደሆነ ነግሬያቸው አስረድቻቸው እነሱም አይንሽን ለአፈር ብለው ተለይተዋታል። . ታዲያ በመጨረሻ ሁሉንም መኪናዎች በአንድ ጊዜ ለማሽከርከር የሞከረችው Formula 1 ድራይቨራችን፣ በራሷ ስህተት Crash አደረገች። እያንዳንዱን ተሳፋሪ / ተበዳይ ሰብስቤ እውነታውን ሳስረዳቸው፣ ለካ ሁላችንም በአንድ ቃል ተገዝተን፣ በአንድ መስመር ስንታለል የነበርን ምስኪኖች ነን። ፍቅር እውር አይደለም ፤ ፍቅር አስተዋይ ነው ፤ እውር የሚያደርገን ግን የምናየው ውበት ሳያንስ የምንመኘው ህልም ነው። ዛሬ ላይ ሆኜ ሳስበው ግን ይሄ ራሱ አንድ ትልቅ ትምህርት ነው። አሁን የገዛ ጥላዬንም ቢሆን ፋይዳ መታወቂያ / National ID ካላሳየኝ አላምነውም..! 😁 By Fraol Habesha @wegoch @wegoch @paappii

የተወደዳችሁ የወግ ብቻ ቻናል አባላት ነገ በወመዘክር ጊቢ ተገኝታችሁ መጽሐፌን ትመርቁልኝ ዘንድ ልባዊ ግብዣዬ ነው!!
የተወደዳችሁ የወግ ብቻ ቻናል አባላት ነገ በወመዘክር ጊቢ ተገኝታችሁ መጽሐፌን ትመርቁልኝ ዘንድ ልባዊ ግብዣዬ ነው!!

ከአንዲት ቆንጅዬ ልጅ ጋ ነበርኩ። መኪና ውስጥ ነበርን ፒዛ እየጋበዝኳት አስተናጋጁ ሲያልፍ በእጄ ቢል እንዲያመጣልኝ ነገርኩት ቢል ይዞ መጣ እያየኝ ከፊት ከኃላ ኪሴ አውጣጥቼ ሂሳብ ከፈልኩ ... ሄደ .... መልስ መጠበቅ ጀመርኩ አልመጣም ጠበኩት አልመጣም ተበሳጭቼ ክላክስ አስጮህኩ (ሱሰኛ ይመስላል ፣ የቀረውን ገንዘብ ለማስቀረት አስቦ ነው ፣ ጉርሻ በፍቃደኝነት የሚሰጥ እንጂ በብልጠት የሚዘገን አይደለም ፣ ሲቆይብን ሰልችቶን እንድንሄድ ነው ) ያስጮኩትን ክላክስ ሰምቶ መጣ "መልስ ስጠን እንጂ ጌታው "አልኩት "የሰጠኸኝ ስድስት መቶ ነው ሂሳቡ ደሞ ስድስት መቶ ሰላሳ አምስት ብር ነው "አለኝ ( ስበረብር ስላየኝ የለው ይሆናል በማለት ተሳቆ ነው እንዳልገረጣ ይጎላል ያላለው ) ከሌለህ ብዬ ነው አይነት ፊት አሳየኝ ። አንዳንድ አድራጎት የሚያገዝፈው አደራረጉ ነው ። ይቅርታ ቢሉን በደንብ ስላላስተዋልኩት ነበር። በጣም አመሰግናለሁ አልኩት እንደገና ኪሴን በርብሬ ድፍን ሁለት መቶ ብር ሰጠሁት እንዲመጣልኝ እንዳልቸኮልኩ እንዲሄድልኝ ቸኮልኩ መልስ ሊያመጣልኝ ሄደ ሳይነግሩን ለዋሉልን እየነገርን መዋል ነውር ነው አይደል ? ሳይመጣብኝ ሄድኩኝ ። By Adhanom Mitiku @wegoch @wegoch @paappii

ያች ከልታማ ወለተ ስላሴ ናት አሉ እንደዛሬው ሁዳዴ ፆም ሊገባ ሲል እሁድ ማታ ቅበላ ተብሎ ድስት ሙሉ ወጥ ተሰርቶ ሲዛቅ አምሽቶ ትንሽ ተርፎባቸው አደረ። በበነጋታው ፆሙ ገብቶ እቃ ልታጥብና የፆም ምግብ ልትሰራ ስትል ያደረውን ስጋ ወጥ ለመድፋት አንዤቷ አልችል አለ።እንጀራዋን እጥፍ አርጋ ድስቱን ጠራርጋ በልታ በሳምንቱ ንስሃ ገባችና ስግደት ታዘዘላት። ይችው ሴትዮ ደግሞ ፆሙን ፆማ ጨርሳ ፋሲካ እሁድ ሊሆን ቅዳሜ ማታ ዶሮ ሰርታ አሻቦውን ለመቅመስ ብላ እንጀራዋን መዥረጥ አድርጋ አንዱን ክንፍ አቀላጠፈችው። በበነጋው ለንሰሐ አባቷ ድጋሚ ተሳሳትኩኝኮ ብላ ሀፅያቷን ስትነግራቸው አባ ግራ ገብቷቸው እንዲህ አሏት:-ምነው ወለተ ስላሴ ይሄንን ፆም አላስገባ አላስወጣ አልሽው? እና ይሄንን ያረጀ ወግ ለምን አወጋኋችሁ መሰላችሁ ምነው ግን ፆሙን አላስገባ አላስወጣ አላችሁት? ሊገባ ሲልም ዳንኪራ፣ዝሙት እና ስጋ ሊወጣ ሲልም ዳንኪራ፣ዝሙት እና ስጋ እስኪ ቢያንስ ወይ በመግቢያው ወይ በመውጫው በኩል ሰከን ብላችሁ አስተናግዱት! By koan Ad @wegoch @wegoch @paappii

ሳሯን . . . ----------- አንድ ድሮ መቀለ መካነ ኢየሱስ ቤ/ክርስቲያን አንድ "ገበሬ ነኝ" ይሉን የነበሩ ከአድዋ? ይመጡ የነበሩ አባት ስለ ዕምነት የነገሩን ምሳሌ አለች። ሰውዬው ተንሸራተው ወድቀው ከገደል አፋፍ ላይ ተንጠልጥለዋል። ወደገደሉ ከመውደቅ ያዳነቻቸው አንዲት ገደሉ አፋፍ ላይ የበቀለች ሳር ነች። እሷን ይዘው ጥቂት እንደቆዩ እጃቸው ዛለ። ሊወድቁ ሆነ። ይሄኔ ድምፅ አውጥተው ፀለዩ። "ጌታ ሆይ አድነኝ!" ይሄኔ መልዓክ ብቅ አለና ሰውዬውን "በአምላክህ አዳኝነት ካመንክ ላድንህ ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልኬ የመጣሁ ነኝ!" ይላቸዋል። ሰውዬውም "ታዲያ ምን ትጠብቃለህ፣ አምናለሁ! አድነኝ!" ይላሉ። መልዓኩም "መጀመሪያ የያዝካትን ሳር ልቀቅና!" አላቸው። * * * ሳሯን አስለቅቀኝ 🤲 By gemechu merera fana @wegoch @wegoch @paappii

የክብራን ገብርኤል መናኝ ገጠመኝ በዕለታት በአንዱ ቀን ከኪዳን ፀሎት በኋላ ንፋስ ለመቀበል ወደ ሀይቅ ዳርቻ አመሩ፡፡ ተፈጥሮን ያስተውሉ ጀመር፡፡ ሀይቁ፣ ንፋሱ፣ አዕዋፋት፣ በሀይቁ ዳርቻና በደኑ ጥግ የሚራወጡት አርጃኖዎች ብዙ ናቸው፡፡ ጠላቂ አዕዋፋት ሰምጠው ቆይተው የዕለት ምግባቸውን ራሳቸውን ወደ ፈጣሪ አንጋጠው አንገታቸውን ቀጥ አድርገው የዕለት ምግባቸውን ወደ ሆዳቸው ያወራርዳሉ፤ ሁሉም የአቅሙን ይጥራል፣ የመጠኑን ያገኛል፣ ይመገባል፤ ትርፍ ማግበስበስ የለም፤ የአቅምን የድርሻን ብቻ፡፡ በዚህ ትዕይንት መካከል አንድ ንሥር ከገዳሙ ረጅም ዛፍ ጫፉ ላይ ተቀምጦ በንሥር ዓይኖቹ የዓሣዎችን እንቅስቃሴ በንቃት ያማትራል፤ በድንገት በተመለከተው ትልቅ ዓሣ ጓጉቶ ተወርውሮ ወደ ሀይቁ ወረደ፡፡ እንደ ሰንጢ የሾሉ ጥፍሮቹን ከመቅፅበት በዓሣው ገላ /ጐን/ ላይ ሰገሠገ፡፡ የተለመደው ድርጊት ከዚህ በኋላ ረጃጅም ክንፎቹን እያማታ ወደ ላይ መነሣትና ወደ ረጅሙ ዛፍ አልያም ወደ ሀይቁ ዳርቻ በርሮ የዕለቱን ሢሣይ ማጣጣም ነበር፡፡ በዕለቱ መነኩሴው የተመለከቱት ግን አስገራሚ ነበር፡፡ ንሥሩ አድኖ የያዘው ዓሣ እጅግ ትልቅ ከመሆኑ የተነሣ ተሸክሞ መብረር አልቻለም፡፡ ጥፍሮቹ ጫፋቸው ላይ ቆልመም ያሉና እንደ ሜንጦ ያሉ ስለነበር ከዓሣው ለማላቀቅም አልቻለም፡፡ መጨረሻ ክንፎቹን አማትቶ ሲደክመው ሀይቁ ላይ ተመልሶ አረፈ፡፡ ዓሣው ነፍስ ዘራና ወደ ሀይቁ ንሥሩን ይዞት ሰጠመ፡፡ የንሥሩ እጣ ፈንታ መሞት እንደነበር ግልፅ ነው፣ እርግጥ ዓሣውም ከጐኑ የተሰካውን ጥፍር ባለቤት ትልቅ ንሥርን ያህል ተሸክሞ መኖር አይችልም፡፡ ሁለቱም አዳኝና ታዳኝ እጣ ፈንታቸው ሞትና ለሌላ አውሬ ሢሣይ መሆን ነው፡፡ መነኩሴው ባዩት ትዕይንት ተመስጠው ለራሣቸው “ለዐይን የሚያስጎመጅ ሁሉ አይበላም፤ ምናልባት ሞት ያለውም በሚያሰጎመጅ ነገር ውስጥ ይሆናል” አሉ፡፡ ነገሩ እስከ አሁን ድረስ እንደሚደንቃቸውም አጫወቱኝ፡፡ @wegoch @wegoch @paappii By Alemayehu wassie