EB Media
Відкрити в Telegram
👉መዝናኛ 👉ዜና 🗣 Our YouTube Channel https://youtube.com/@ebmedia123?si=3Zgov2sCJcx1Qla4
Показати більше1 496
Підписники
-224 години
-27 днів
+4430 день
Архів дописів
1 496
በሕይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በአውሮፕላን የተሳፈረ ሰውዬ የበረራ አስተናጋጇ በሰጠችው ጥቆማ መሰረት የአውሮፕላኑ መጸዳጃ ቤት ውስጥ መጠቀም ይጀምራል ታዲያ በመሃል አንዲት ቀይ ማብሪያና ማጥፊያ የምትመስል ነገር ያይና ነካ ያደርጋታል።
በዚህ ቅፅበት አውሮፕላኑ በሃይል መንገጫገጭና ወደ ጎን ማጋደል ይጀመራል ሰውዬውም ደንግጦ ወይኔ ሳላውቅ የማይነካ ነገር ነክቼ ሕዝብ ጨረስኩኝ ብሎ በነካት ቀይ ነገር ይጸጸታል ከጥቂት ቆይታ በኃላ ግን መንገጫገጩ ይቆምና ጨርሶ ከመጸዳጃ ቤት ይወጣል።
ሁሉም ሰው "አንተ የማትረባ! ጨርሰኸን ነበር እኮ!" ብሎ ይጮህብኛል ብሎ ቢጠብቅም ዞር ብሎ ያየው ሰው እንኳን አልነበረም።
መቀመጫው ላይ እንደደረሰም አጠገቡ የተቀመጠውን ሰው ቀስ ብሎ እየተሳቀቀ "ይቅርታ የማይነካ ነገር ነክቼ ጨርሻቹ ነበር አይደል?" ይለዋል ሰውዬውም "አረ በፍጹም እንደዛ እንዳታስብ! ይህን ያህል ጥንቃቄ የሚፈልጉ ነገሮች እኮ መፀዳጃ ቤት ውስጥ አይደረጉም ካፒቴኑ ያለበት ክፍል ውስጥ ነው ያሉት። አጋጣሚ ነው ትንሽ የአየሩ ሁኔታ አስቸጋሪ ስለሆነ ነው አውሮፕላኑ የተንገራገጨው" ይለዋል።
ብዙ ጊዜ ሰዎች እንደዚህ ያስባሉ የሆነች ነገር ነክተው ሕይወትህን የሚያንገጫግጩ እና መጨረሻህን የሚወስኑ ይመስላቸዋል የረሱት ነገር ቢኖር ይህን ያክል ጥንቃቄ የሚፈልገው ነገር እነሱ አጠገብ ሳይሆን የሕይወትህ ካፒቴን ጋር እንዳለ ነው።
እንደዛማ ባይሆን ኖሮ ቀይዋን ነገር እየጠቀጠቁ ሕይወታችንን መንገጫገጭ ብቻ ያደርጉት ነበር ምስጋና ለካፒቴኑ ፈጣሪ ይሁንና እንደዚህ አይነት ጥንቃቄ የሚፈልጉ ነገሮችን በሱ እጅ ብቻ እንዲገኙ አድርጓቸዋል።
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
1 496
💔😭 እንዲህ ያለ ፍቅር ዛሬም አለ?
12 ዓመታት ሙሉ አንድም ቃል ሳይናገር የኖረውን ባለቤቷን በፍቅርና በትዕግስት ተንከባክባለች። 18 ዓመታት መከራ፣ እንባ እና ፈተና ውስጥ ብትሆንም ተስፋዋን አልቆረጠችም። ❤️🙏
1 496
እገታ ተፈፀመ‼️
በዛሬው ዕለት ሰኔ 6/2018 ዓ.ም ጠዋት በምስራቅ አርሲ ከአቦምሳ ከተማ ወደ አስኮ እየመጣ ያለ አንድ ቅጥቅጥ የህዝብ ማመላለሻ ሙሉ ተሳፋሪዎችን ከቀኑ 6:00 ላይ ባለፈው ጥቃት የፈፀሙት የሸኔ ታጣቂዎች እግተዉ ይዘው መሄዳቸውን የአካባቢው የአይን እማኞች ለአዩዘሀበሻ ገልፀዋል።
እገታው የተፈፀመው ከከተማው ጥቂት ኪሎሜትር እርቀት ላይ ሲሆን የፀጥታ ሀይሎች እዛው አከባቢ ነበሩ ብለዋል።
ከሁለት ሳምንት በፊት በዚህ አካባቢ በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ጥቃት መፈፀሙ የሚታወስ ነው።
1 496
ስለዚህ ሌሎች ወገኖችም ሊያሸንፉ የሚችሉበት ዕድል ስለነበረ ውጤቱ አስቀድሞ የተወሰነ አልነበረም። ተቃዋሚዎች ብቻ እንዲወዳደሩ ዕድል መስጠትን የፖለቲካ ምህዳሩን ከማስፋት አንጻር ነው የምመለከተው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ/ም
1 496
"ምክር ቤቱን የማሞቅ የማቀዝቀዝ ወይም ልክ ልካቸውን ነገራቸው ለመባል ሳይሆን ችግሮች ከመሰረቱ እንዲፈቱ የሚያደርግ እንቅስቃሴ አደርጋለሁ ! " - አቶ ጣሂር ሙሐመድ
📌 " እጩ ያላቀረበው [ብልጽግና ፓርቲ] በተለየ ሁኔታ ምህዳሩን ለማስፋት የተደረገ ጥረት ነው ብዬ ነው የምወስደው ! "
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው 24 ውጤቶች መሠረት፤ በአማራ ክልል በጎንደር ዙሪያ 4 ምርጫ ክልል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) እጩ የሆኑት አቶ ጣሂር ሙሐመድ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወንበር ማሸነፋቸው መገለጹ ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም የምርጫ ውጤቱን በማስመልከት ከአቶ ጣሂር ጋር አጭር ቆይታ አድርጓል።
🎤 ጋዜጠኛ፦ ጣሂር መሐመድ ማን ናቸው? የት ተወለዱ፣ የት ተማሩ ?
👤 አቶ ጣሂር መሐመድ ፦ ተወልጄ ያደኩት በጎንደር ዙሪያ ወረዳ እንፍራንዝ የምትባለው ከተማ ላይ ነው። የመጀመሪያ ዲግሪዬን በወሎ ዩኒቨርሲቲ በቋንቋ እና ስነ-ጽሁፍ፣ ሁለተኛ ዲግሪዬን ደግሞ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በፖለቲካል ሳይንስ እና አለም አቀፍ ግንኙነት አግኝቻለሁ።
በተለያዩ የግል ሚዲያዎች እና በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) በጋዜጠኝነት ሰርቻለሁ። በአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ሆኜም ለረጅም አመታት ሰርቻለሁ።
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ ሆኜ ለሶስት አመታት አገልግያለሁ።
🎤 ጋዜጠኛ፦ የ7ኛው ሀገራዊ የምርጫ ሂደት በእርስዎ እና በፓርቲዎ አንጻር እንዴት ይገመገማል? እንዴት አዩት?
👤 አቶ ጣሂር መሐመድ፦ የዘንድሮው ምርጫ እጅግ በርካታ እና ውስብስብ በሆኑ ሀገራዊ እውነታዎች ውስጥ የተከናወነ ነው። ይህ ዓይነቱ የፖለቲካ ውጥረት በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ወቅትም የነበረ ቢሆንም፣ በወቅቱ ግጭቱ በዋነኝነት በትግራይ ክልል ላይ የተወሰነ ስለነበር በቀሪው የሀገሪቱ ክፍል ተንቀሳቅሶ የምርጫ ቅስቀሳ ለማድረግ የተሻለ ዕድል ፈጥሮ ነበር። ግጭቱ የጠነከረውም ምርጫው ተጠናቆ መንግስት ምስረታ በተከናወነበት ወቅት ነበር።
በዚያ መሃል በነበረው አንጻራዊ ሰላም ቢያንስ እኛ በአማራ ክልል በቂ እንቅስቃሴና ተሳትፎ ማድረግ ችለን ነበር። የዘንድሮው ምርጫ ግን በርካታ የሀገር ውስጥ ውስብስብ ችግሮች የሰፈኑበት በመሆኑ "ይሄ ምርጫ ይደረግ ይሆን?" ያሉም አሉ፣ ጊዜውን ጠብቆ ስለመደረጉም ጥርጣሬ የነበራቸው አካላቶች ነበሩ።
እኛም እንደ ፓርቲ ያለውን ውስብስብ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት፣ እንቅስቃሴያችንን በተወሰኑ ቦታዎች ላይ አድርገናል። በየቦታው ምርጫውን የሚቃወሙ እና በትጥቅ ትግል ችግሮቻችንን እንፈታለን ብለው የተነሱ አካላት ሂደቱ እንዳይሳካ ፍላጎት ነበራቸው።
ይህ ትንሽ ብቻ ሳይሆን መደበኛ የምርጫ ስራዎችን እንዳንሰራ አድርጎናል። በተለይ ከማህበረሰቡ ጋር በቀጥታ ተገናኝተን እንቅስቃሴዎችን እንዳናደርግ ፈታኝ ሆኖብን ነበር።
እንደዚህ አይነት ሁኔታዎችን ተቋቁሞ ህዝቡ ካርድ አውጥቶ መርጧል። ሂደቱ የራሱ የሆነ ውስንነት ሊኖረው ይችላል። ግን መንግስት ለማጽናት የሚሆን ፕሮሰስ ተካሂዷል ብዬ ነው የማምነው።
🎤 ጋዜጠኛ፦ በተወዳደሩበት የምርጫ ክልል እርስዎ ተንቀሳቅሰው ከህዝቡ ጋር ተገናኝተው የተለያዩ ቅስቀሳዎችን አድርገው ነበር ?
👤 አቶ ጣሂር መሐመድ፦ አዎ፣ እንፍራዝ ከተማ ላይ በአካል ለሦስት ጊዜ በመሄድ ከተፅዕኖ ፈጣሪ ሰዎች እና ከማህበረሰቡ መሪዎች ጋር በመሆን የምረጡኝ ቅስቀሳ አድርጌያለሁ። ከህዝቡ ጋርም ለመገናኘት ሞክሬያለሁ። በአንጻሩ ከዚህ በፊት እንደነበሩት አይነት ድባብ ባይኖረውም ጥረቶች ግን አድርጌያለሁ።
🎤 ጋዜጠኛ፦ በተወዳደሩበት የምርጫ ክልል ህዝቡን ወክለው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ አግኝተዋል እና ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ወደዚህ ምክር ቤት የሚገቡት፤ ምንድነው እቅድዎ?
👤 አቶ ጣሂር መሐመድ፦ የመረጠኝ ማኅበረሰብ በርካታ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ያሉበት፣ ወጣቶች በበቂ ሁኔታ የስራ ዕድል ሊፈጠርላቸው የሚገባ፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ ችግር፣ የመሰረተ ልማት ጥያቄ ያላቸው ናቸው። ምን አይነት ችግሮች እንዳሉበት አውቃለሁ። ይህን የመቅረፍ የመጀመሪያው እቅዴ ነው።
ሁለተኛ በሚኖረኝ የፓርላማ ቆይታ በአንድ በኩል ድምፅ በመሆን በክልሉ እና በሀገራችን ያሉትን ዋና የፖለቲካና የኢኮኖሚ ችግሮችን እንዲፈቱ ማድረግ ነው። መንግስት ለሚባለው አስፈጻሚው አካል የህዝባችንን ችግሮች ማስታወስ፣ የማስረዳት እና የማግባባት ስራ የመስራት እቅድ አለኝ።
ምክር ቤቱን የማሞቅ የማቀዝቀዝ ወይም "ልክ ልካቸውን ነገራቸው" ለመባል ሳይሆን ችግሮች ከመሰረቱ እንዲፈቱ የሚያደርግ እንቅስቃሴ አደርጋለሁ። የአጋዥነት ሚና እንቅስቃሴ ማድረግ ሌላው እቅዴ ነው።
🎤 ጋዜጠኛ፦ የአማራ ክልል የፀጥታ ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻሎች እያሳየ አይደለም። ትልቅ ኃላፊነት ይዞ እንደሚሄድ የህዝብ ተወካይ ክልሉን ወደ ቀደመ ሰላሙ ለመመለስ ያለዎት አቋም ምንድን ነው?
👤 አቶ ጣሂር መሐመድ፦ መንግስት ከተለያዩ ታጣቂ ኃይሎች ጋር ለመግባባትና ችግሩ በውይይት እንዲፈታ የጀመራቸውና ለድርድር ክፍት የሆነባቸው ጥረቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አደርጋለሁ።
በጦር መሣሪያ ጥያቄዬን እፈታለሁ የሚሉና እስካሁን ወደ ሂደቱ ያልገቡ የፖለቲካና የትጥቅ ኃይሎችን እምነት በሚጥሉበትና የጋራ መተማመን ባለበት መንገድ ወደ ድርድርና መግባባት የማምጣቱን ጥረት በከፍተኛ ሁኔታ አጠናክራለሁ።
ህዝቡ ካርድ አውጥቶ ሲመርጥ ዋናው መልዕክቱ "ህይወቴና ደህንነቴ ይጠበቅልኝ" የሚል በመሆኑ፣ ከመንግስት የሚጠበቀውን የህዝብን ሰላም እና ደህንነት በምንም አይነት ዋጋ (At any cost) የማስጠበቅ ስራን በግልም ሆነ በቡድን (በምክር ቤት አባልነቱ) የማስፈጸም፣ የማገዝ እና በመንግስት ላይ ጫና የመፍጠር ጽኑ አቋም አለኝ።
🎤 ጋዜጠኛ፦ የምርጫ ቦርድ ውጤት ይፋ ባደረገበት ወቅት እርስዎ በተወዳደሩበት ክልል ብልጽግና ፓርቲ እጩ አለማቅረቡ እንደ ጥያቄ ተነስቷል፤ የእርስዎ አስተያየት ምንድነው?
👤 አቶ ጣሂር መሐመድ፦ ይህን ጉዳይ ሌሎች አጋነው እንደሚመለከቱት አልመለከተውም። የሀገራችን የዲሞክራሲ ሂደት ገና በእጅጉ የሚቀረው ነው። ብልጽግና ገዥ ፓርቲ ነው። የፋይናንስ አቅምና የሰው ኃይሉ በመላው ሀገሪቱ ተንቀሳቅሶ የመወዳደር እና እጩ አቅርቦ ድምፅ የማግኘት አስተማማኝ ሁኔታ እንዳለው በራሱ ከገመገመ በኋላ፣ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት ሲል በተወሰኑ ክልሎች ውድድር ውስጥ አለመግባቱን እኔ በበጎ ጎኑ ነው የምወስደው።
በእርግጥ የዚህ ሀገር ፖለቲካ ግምትና ጥርጣሬ የሚታወቅ ነው፤ "እገሌ ነው የለቀቀው፣ እገሌ ነው የመጣው" ይባላል። ገዥው ፓርቲ እዚህ ብቻ ሳይሆን በሌሎችም በርካታ አካባቢዎች ራሱን አግልሏል።
በቀሪዎቹ ቦታዎች ያገኘሁት ውጤት ይበቃኛል፣ ለሌሎች ዕድል ልስጥ ብሎ እንዳሰበ ነው የምረዳው። በዚህም የተነሳ የተሻለ የሃሳብ ዓይነትና ብዝሃነት ያለው የሕዝብ ተወካይ እንዲመረጥ ማድረጉ ጠቃሚ ነው። ይህ ተነሳሽነት ወደፊትም ሥርዓቱ እንዲያድግና እንዲሻሻል በቀጣይም መለመድ ያለበት አካሄድ ነው።
ነገር ግን ይህ ውድድር በተለየ መልኩ ለጣሂር ወይም ለተወሰነ ግለሰብ ተብሎ የተመቻቸ አይደለም። አራት ፓርቲዎች በተለያየ ቦታ ተወዳድረው ተፎካካሪዎች መጥተዋል።
1 496
+2
በዓለም ላይ በርካታ ተከታታይ ያለው ዝነኛው የቲክቶክ ፈጣሪ ኻቢ ሌም ዛሬ አሜሪካ እንደደረሰ በቁጥጥር ስር መዋሉና ወደ መጣበት አገር ሊመለስ (ሊባረር) እንደሆነ እየተሰማ ነው።
የጉዞው ዓላማ የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን የሚያደርጋቸውን የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች በሙሉ በቀጥታ ስርጭት (Stream) በማስተላለፍ በአገሩ ያሉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ደጋፊዎች ጨዋታውን በቀጥታ እንዲከታተሉ ለማድረግ ነበር። ሆኖም ግን፣ አሜሪካ ኤርፖርት እንደደረሰ የመግቢያ ቪዛ ተከልክሏል።
ከጀርባው ያለው እውነታ ምንድን ነው?
በአሁኑ ሰዓት የአሜሪካ የኢሚግሬሽን ባለስልጣናት (ICE) በቱሪስት ቪዛ (Tourist Visa) ወደ አገር ውስጥ ገብተው የማህበራዊ ሚዲያ ይዘቶችን በመስራት ገቢ የሚያመነጩ (የሚከፈላቸው) የውጭ አገር ኢንፍሉዌንሰሮችን ጥብቅ ቁጥጥር እያደረጉ ይገኛሉ። የኻቢ ሌም ጉዳይም ከዚህ የቪዛ ህግ መጣስ ጋር የተያያዘ እንደሆነ እየተገለጸ ነው።
ኻቢ ሌም ከዚህ ቀደም በ2025 ተመሳሳይ የቪዛ ጊዜ ማለፍ (Overstay) ችግር አጋጥሞት እንደነበር ይታወሳል። አሁን ላይ ባለስልጣናቱ ዛሬ ምሽት ወደ አገሩ ለመመለስ እያዘጋጁት እንደሆነ ተነግሯል።
ሚሊዮን የሴኔጋል ደጋፊዎችን ያስቆጨው ይህ ውሳኔ እና የአሜሪካ አዲሱ ጥብቅ የቪዛ ፖሊሲ በሶሻል ሚዲያ ላይ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኗል!
Ebrahim Yezid
1 496
+2
ዛሬ የእሱ ቀን ነው የቀነኒ ኬኛ!
#maleda : ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም፤ የኢትዮጵያ ሰማይ በጀግንነት ዜማ የሚደምቅበት፣ የዓለም አትሌቲክስ ታሪክ ለአንዱ ታላቅ ንጉሥ አንገቱን ደፍቶ ክብር የሚሰጥበት ዕለት ነው።
ዛሬ የእሱ ቀን ነው የቀነኒ ኬኛ!
ይህ ታሪክ ሰሪ ጀግና ዛሬ 44ኛ ዓመት የልደት በዓሉን ያከብራል። ቀነኒሳ በቀለ ማለት ለኢትዮጵያውያን ከሩጫ አትሌትነት በላይ ነው፤ እሱ የፅናት፣ የቁጭት፣ የእልህ እና የማይበገረው የኢትዮጵያዊነት መንፈስ ሕያው ተምሳሌት ነው።
ቀነኒ ኬኛ!ኢትዮጵያ እንኳን ተወለድክላት!
መልካም 44ኛው የልደት ጀግናችን!
1 496
🚨💔 አሳዛኝ ዘገባ ከሊቢያ!
በሊቢያ የሚገኙ አንዳንድ አፍሪካውያን ስደተኞች በሃይማኖታቸው ምክንያት ለእንግልትና ለጥቃት እየተጋለጡ መሆናቸውን የሚያሳዩ ቪዲዮዎች በማኅበራዊ ሚዲያ ተሰራጭተዋል።
በቪዲዮው ላይ መስቀል ያደረጉ ስደተኞች በሰዎች ተከበው ሲደበደቡ፣ ሲዋረዱ እና የአንገት ሐብላቸው በኃይል ሲቀማ የሚያሳይ ምስል ይታያል። ይህ ድርጊት በብዙ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ዘንድ ቁጣን ቀስቅሷል።
📰 እንደ DW እና JaafarTalk ዘገባ ከሆነ፣ የሊቢያ ብሔራዊ የሰብአዊ መብት ተቋም ድርጊቱን በጽኑ አውግዞ ተጠያቂዎቹ ተለይተው ለፍርድ እንዲቀርቡ ጠይቋል።
⚠️ እስካሁን ድረስ ከሊቢያ ባለሥልጣናት በኩል ስለ ጉዳዩ ይፋዊ መግለጫ አልተሰጠም ተብሏል።
💔 ሰው በሃይማኖቱ፣ በዘሩ ወይም በማንነቱ ምክንያት መዋረድና መጠቃት በማንኛውም ቦታ ተቀባይነት ሊኖረው አይገባም።
👇 ሙሉ ቪዲዮውን ለመመልከት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇
👉 https://t.me/EBMedia123
🙏 SHARE እና JOIN በማድረግ ጓደኞችዎን ያሳውቁ!
#ሊቢያ #ስደተኞች #ክርስቲያኖች #ሰብአዊመብት #DW #JaafarTalk #Libya #HumanRights
1 496
አፍሪካዊያን መደጋገፍ ሲገባቸዉ ከእኛ ተቃራኒ መሆናቸዉን ማየት በጣም ያማል ሲል የደቡብ አፍሪካዉ ግብ
ጠባቂ ተናገረ
የደቡብ አፍሪካው አምበል ሮንዌን ዊሊያምስ ከሜክሲኮ ጋር በነበራቸዉ ጨዋታ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ሜክሲኮን በመደገፋቸዉ ማዘኑን ገልጿል።
"በየትኛውም የአለም ዋንጫ አፍሪካውያን አብዛኛውን ጊዜ የአፍሪካ ሀገራትን ይደግፋሉ።ሆኖም ግን እኛ ላይ ብዙ አፍሪካውያን ከደቡብ አፍሪካ ይልቅ ሜክሲኮን ሲያበረታቱ ማየት በጣም ያማል" ብሏል።
ግብጠባቂዉ "ሁሉንም ነገር ለሀገራችን ሰጥተናል ከጨዋታው በኋላ ግን አምብተናል" ብሏል።
"ይህ ወቅት አፍሪካ በአንድነት በመቆም፣ መደጋገፍና መተሳሰር የምትችልበት ወቅት ነው" ሲልም አክሏል።
ሆኖም አብዛኛው የአፍሪካዊያን የእግርኳስ ተመልካች ግን ምሽቱን ለሜክሲኮ ነበር ድጋፉን ያሳየዉ። ለዚህም ደግሞ የደቡብ አፍሪካውያን የመጤ ጠል እንቅስቃሴ ጥቁር አፍሪካውያን ሀገራችንን ለቅቀዉ ይዉጡ ማለት በመጀመራቸዉ ነዉ። ደቡብ አፍሪካዊያን ሌሎች አፍሪካዊያን የስራ እድሎቻችን ይዘዋል በሚል ዋነኛ ምክኒያት ነዉ ይዉጡልን ሲሉ የከረሙት። በዚህም አብዛኛው የአፍሪካ ክፍል በደቡብ አፍሪካውያን ላይ ቂም ሳይዝ አልቀረም። ሽንፈታቸውንም እንደ ድል እየተደሰቱበት ነዉ።
(ዳጉ ስፖርት)
1 496
አሳዛኝ መረጃ💔
የአርቲስቷ አሳዛኙ ዜና እረፍት😭
በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽና በራስ ቴአትር እንዲሁም በህጻናትና ወጣቶች ቴአትር ቤት ለረጅም ዓመታት በተዋናይነት ስታገለግል የቆየችው አርቲስት ሰላማዊት ደስታ በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቷ ይታወሳል፡፡ አርቲስቷ ለረጅም ጊዜያት ታማ በህክምና ስትረዳ የቆየች ሲሆን እንደ መንግስት ቅጥር አርቲስትነቷ ደሞዟ ህክምናውን ለመከታታል በቂ ስላልነበረ የሰዎችን እጅ ለማየት ተገዳ እንደነበር የቅርብ ጓደኞቿ ይናገራሉ፡፡
አርቲስቷ ሰላማዊት ደስታ ለረጀም ዓመታት አብሯት የቆየ በሽታ ሳቢያ አልጋ ከያዘች በርካታ ጊዜያት የሆናት ሲሆን ከአንድ ኣመት በፊት ደግሞ የቀኝ ጡቷ መቆረጡን የቅርብ ሰዎች ይናገራሉ፡፡ በዚህም ሳቢያ በሽታው እያመረቀዘባት የተሻለ ህክምና ለማግኘት የህዝቡንና የአርቲስቱን ድጋፋ በተደጋጋሚ ብትጠይቅም ሰሚ እንዳላገኘችና በባዶ ቤት እረፍቷ መሰማቱ ታውቋል፡፡
በአርቲስቷ አሟሟት ምክንያትም በኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች በኩል ከፍተኛ የተባለ አለመግባባት ነግሷል፡፡ በጣም ጥቂት ባለሙያዎች ብቻ ከአርቲስቷ ጎን እስከ መጨረሻው ነበሩ የተባለ ሲሆን፤የተቀሩት ግን ሞቷን ለማርዳት ብቻ ቀደሚዎች ነበሩ ተብሏል፡፡
የአርቲስት ሰላማዊት ህልፈት ግንቦት 21/2018 ዓ.ም በተሰማ ጊዜ ግን በህመሟ እና በችግሯ ጊዜ አብረዋት ያልነበሩት የሙያ አጋሮቿ በፌስቡክ ማዘናቸውን ለመግጽ ግን የቀደማቸው አልነበረም፡፡ ይህ ሁኔታቸውም ብዙዎችን አስቆጥቷል፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ አርቲስት ሰላማዊት ካረፈች በኋላ የተወሰኑ የሙያ ጓደኞቿ የመታሰቢያ ዝግጅት በማለት ሰሞኑን አንድ ፕሮግራም ልማቅረብ ሽር ጉድ እያሉ መሆኑ ታውቋል፡፡
ለመሆኑ ለአርቲስት ሰላማዊት ደስታ ምደረግ የነበረበት ድጋፍና የአርቲስቱን ዝምታ እንዴት አያችሁት? አስተያየት ስጡበት?
©ዋልያ ሚዲያ
1 496
🚨 ሰበር ዜና (BREAKING): ኢሎን ማስክ የዓለም መጀመሪያው ትሪሊየነር ሆነ ተብሏል 💰🚀
SpaceX በታሪክ የተመዘገበ የ75 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት (IPO) ከሰበሰበ በኋላ፣ ኩባንያው በገበያ ላይ መጀመር ሲጀምር የኢሎን ማስክ የሀብት መጠን ከ1.1 ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደደረሰ ተነግሯል። 📈
ይህም ማስክን በራሱ የተለየ የኢኮኖሚ ደረጃ ላይ አድርጎታል ተብሏል።
🚗 ከTesla ያለው ድርሻ እና ሌሎች ኢንቨስትመንቶቹ ጋር በመደመር፣ አጠቃላይ የሀብቱ መጠን ወደ 1.1 ትሪሊዮን ዶላር ደርሷል ተብሏል።
🛰️ በSpaceX ውስጥ ብቻ ያለው ድርሻ ወደ 690 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል ተብሎ ይገመታል።
👨💼 ይህ እንዲሁ ለሺዎች የSpaceX ሰራተኞች የኩባንያ ድርሻ ስላላቸው ታላቅ የህይወት ለውጥ እንደሚያመጣ ተገልጿል።
🌍 ኢንቨስተሮች ከTesla ስኬት በኋላ ማስክ በጠፈር ኢንዱስትሪ እና በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ደግሞ ተመሳሳይ እድገት እንደሚያሳይ በጣም እየተወደዱ ነው።
💭 ምን ታስባላችሁ?
በእውነት አንድ ሰው ይህን ያህል ሀብት መያዝ የዓለምን ኢኮኖሚ ሚዛን ይቀይራል ብለው ታስባላችሁ?
#ElonMusk #SpaceX #Tesla #BreakingNews #Economy #TechNews
1 496
🚀💰 ታሪካዊ የሀብት ክስተት እንደ ሀሳብ!
ኢሎን ማስክ የቴክኖሎጂ እና የስፔስ ኢንዱስትሪ ዓለምን በአስደናቂ ፍጥነት እየቀየረ ያለ ሰው ነው።
Tesla 🚗 እና SpaceX 🛰️ እንደ ኩባንያዎቹ በገበያ ላይ ያላቸው ተፅዕኖ በዓለም የሚታወቅ ነው።
📈 ባለሀብት መጠኑ በዓለም ከፍተኛ ቦታ ላይ ቢገኝም፣ “ትሪሊየነር ሆነ” የሚለው መረጃ ግን እስካሁን በተረጋገጠ መልኩ አልተመረጠም።
🌌 ነገር ግን የSpaceX የሳተላይት ኢንተርኔት (Starlink)፣ የAI ቴክኖሎጂ እና የጠፈር ምርምር ፕሮጀክቶች ወደፊት የዓለምን ቴክኖሎጂ ሊቀይሩ ይችላሉ።
💭 ጥያቄ፡
እንደዚህ ዓይነት ሀብት እና ቴክኖሎጂ በእውነት የዓለምን የኢኮኖሚ ሚዛን ሊቀይር ይችላል ብለው ታስባላችሁ?
👇 አስተያየታችሁን አጋሩ!
👇 ለበለጠ መረጃ የኢቢ ሚዲያ ቴሌግራም ቻናልን ይቀላቀሉ። https://t.me/EBMedia123�
🔄 Share | 📢 Join | 👍 Follow
#TechNews #ElonMusk #SpaceX #Tesla #FutureTech #Innovation
1 496
🚀💰 ታሪካዊ የሀብት ክስተት እንደ ሀሳብ!
ኢሎን ማስክ የቴክኖሎጂ እና የስፔስ ኢንዱስትሪ ዓለምን በአስደናቂ ፍጥነት እየቀየረ ያለ ሰው ነው።
Tesla 🚗 እና SpaceX 🛰️ እንደ ኩባንያዎቹ በገበያ ላይ ያላቸው ተፅዕኖ በዓለም የሚታወቅ ነው።
📈 ባለሀብት መጠኑ በዓለም ከፍተኛ ቦታ ላይ ቢገኝም፣ “ትሪሊየነር ሆነ” የሚለው መረጃ ግን እስካሁን በተረጋገጠ መልኩ አልተመረጠም።
🌌 ነገር ግን የSpaceX የሳተላይት ኢንተርኔት (Starlink)፣ የAI ቴክኖሎጂ እና የጠፈር ምርምር ፕሮጀክቶች ወደፊት የዓለምን ቴክኖሎጂ ሊቀይሩ ይችላሉ።
💭 ጥያቄ፡
እንደዚህ ዓይነት ሀብት እና ቴክኖሎጂ በእውነት የዓለምን የኢኮኖሚ ሚዛን ሊቀይር ይችላል ብለው ታስባላችሁ?
👇 አስተያየታችሁን አጋሩ!
👇 ለበለጠ መረጃ የኢቢ ሚዲያ ቴሌግራም ቻናልን ይቀላቀሉ። https://t.me/EBMedia123�
🔄 Share | 📢 Join | 👍 Follow
#TechNews #ElonMusk #SpaceX #Tesla #FutureTech #Innovation
1 496
ሰበር ዜና
ኢራን የዓለም ዋንጫን አመሰችው!
የ2026 ፊፋ ዓለም ዋንጫ ውድድር በሳይበር ጥቃት ስጋት ስር መውደቁ ተነግሯል።
ራሱን “Handala” ብሎ የሚጠራ የጠላፊዎች ቡድን፣ የFBI ድሮኖችን መጥለፉን በመግለጽ የዓለም ዋንጫውን ተሳታፊ ሀገራት እን እና ደጋፊዎችን በቀጥታ ማስፈራራቱ ተዘግቧል።
በዚህ ምክንያት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የቡድኑን አባላት ለመለየት የሚረዳ መረጃ ለሚያቀርብ ሰው እስከ 10 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ማቅረቡ ተገልጿል።
1 496
በእውነት ተፀፅቻለሁ‼️" አርቲስት አስጌ ዴንዳሾ
አርቲስት አስገኘዉ ከሰሞኑ ከአርሲ ኦርቶዶክሳዉያን ጋር ተያይዞ በተገኘበት የስታዲየሙ ኮንሰርት በብዙዎች የገጠመዉን ተቃዉሞ ተከትሎ በፌስቡክ ገፁ የሚከተለዉን የይቅርታ መልዕክት አጋርቷል
👇👇👇
"ወዳጅ ወገኖቼ…
🫵🏽ባለቀሳችሁበት ቦታ ሳቃችሁ ይሰማ!!
🫵🏽ፈጣሪ የተሰበረውን ልባችሁን ጠግኖ ህመማችሁን ያስረሳ!! 🙌💔
🫵🏽በቃችሁ ይበላችሁ!!
🫵🏽ደስታ መቅደሳችሁን ፡ ቤታችሁን ይሙላው!!💕
ግና ግን…
ከ’ናንት ጫማ ወጥታችሁ ፡ በ’ኔ ጫማ አስቡኝ ፤
አትጥሉኝ አትግፉኝ ፡ ወደ እቅፋችሁ ሳቡኝ ፤
አቅጄ ያረኩኝ አንዳች የለም’ና ፡ እስኪ አፉ በሉኝ።🙏🏽❤️
አመሰግናለሁ ፤ እወዳችኋለውም።"
1 496
በፌስቡክ እና በሌሎች የሜታ (Meta) አገልግሎቶች ላይ መስተጓጎል አጋጠመ!
ዛሬ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. (June 12, 2026) በዓለም ዙሪያ የሚገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የፌስቡክ፣ የኢንስታግራም እና የሜሴንጀር ተጠቃሚዎች ከፍተኛ የአገልግሎት መቋረጥ እያጋጠማቸው መሆኑን ሪፖርት እያደረጉ ይገኛሉ።
ምን ተከሰተ?
ብዙሃኑ ተጠቃሚዎች ከበይነ-መረብ አካውንቶቻቸው በራሱ ጊዜ Log out እየሆኑባቸው ሲሆን፥ ተመልሰው ለመግባት በሚሞክሩበት ወቅትም የሚከተሉትን የስህተት መልዕክቶች እያዩ መሆናቸውን ገልጸዋል፦
- Something went wrong” የሆነ የተሳሳተ ነገር ተከስቷል) *Query error” (የጥያቄ ስህተት) ከተለመደው የፌስቡክ መተግበሪያ በተጨማሪ የ Messenger እና የInstagram አገልግሎቶችም ተመሳሳይ እክል እንደገጠማቸው ታውቋል።
ምን ማድረግ ይኖርብዎታል? ችግሩ ከእርስዎ ስልክ ወይም የኢንተርኔት ግንኙነት ጋር የተያያዘ ሳይሆን ከራሱ ከሜታ (Meta) ሰርቨር የመነጨ በመሆኑ፦
1. አይደናገጡ፦አካውንቴ ተጠለፈ (Hack ተደረገ) ብለው እንዳይሰጉ።
2. ይጠብቁ፦የሜታ የቴክኒክ ባለሙያዎች ችግሩን ቀርፈው አገልግሎቱን ወደ ነበረበት እስኪመልሱ ድረስ በትዕግስት መጠበቅ ብልህነት ነው።
1 496
🚗💸 56,000 ብር ለታርጋ?
ጋዜጠኛ ሉላ የአዲሱን የተሽከርካሪ ሰሌዳ ዋጋ በመተቸት፣ በአሜሪካ፣ አውስትራሊያ እና እንግሊዝ የሰሌዳ ዋጋ ከዚህ በእጅጉ ዝቅተኛ መሆኑን ገልጻለች።
“መኪና ያለው ሁሉ ሀብታም ነው ተብሎ መገመት ስህተት ነው” በማለትም ውሳኔው በዜጎች ላይ ከባድ የኢኮኖሚ ጫና እንደሚፈጥር አስጠንቅቃለች።
❓እርስዎ 56,000 ብር ለአዲስ ታርጋ መክፈል ተገቢ ነው ብለው ያስባሉ?
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
