uk
Feedback
ያሬዳውያን

ያሬዳውያን

Відкрити в Telegram

የየበዓላቱ ስርአተ #ዋዜማ ፤ #ማኅሌት ፤ #ወረብ ከ፯ ቀናት በፊት እንዲሁም የየሳምንቱ መዝሙራት እና ምስባክ በጽሑፍ እና በድምጽ የሚቀርቡበት ቻናል ነው #ሁሉም_ነገር_ስለ_ማኅሌት ለማስታወቂያ እና ለማንኛውም ጥያቄ ከፈለጉን አለን በዚህ ያናግሩን 👉 @Yaredawi_admin እናመሰግናለን

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу ያሬዳውያን

Канал ያሬዳውያን (@eotcmahlet) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 113 138 підписників, посідаючи 306 місце в категорії Релігія і духовність та 251 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 113 138 підписників.

За останніми даними від 02 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 1 606, а за останні 24 години на -9, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 12.87%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 7.35% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 14 557 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 8 315 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 50.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
የየበዓላቱ ስርአተ #ዋዜማ ፤ #ማኅሌት ፤ #ወረብ ከ፯ ቀናት በፊት እንዲሁም የየሳምንቱ መዝሙራት እና ምስባክ በጽሑፍ እና በድምጽ የሚቀርቡበት ቻናል ነው #ሁሉም_ነገር_ስለ_ማኅሌት ለማስታወቂያ እና ለማንኛውም ጥያቄ ከፈለጉን አለን በዚህ ያናግሩን 👉 @Yaredawi_admin እናመሰግናለን

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 03 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

113 138
Підписники
-924 години
+5667 днів
+1 60630 день
Архів дописів
መልክዐ አቡነ ሀብተማርያም።.pdf1.37 MB

የሞተው ይልቁንም ከሙታን በተነሣው በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው ! ምን ማለት ነው ?

🌹አርያም🌹
ልዩ Online የአብነት ጉባኤ ቤት❯
በሀገር ውስጥ እና በተለያዩ የዓለም ክፍላት የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያን የጊዜ ና የቦታ ርቀት ሳይገድብዎ የኢ.ኦ.ተ.ቤተ-ክርስቲያን የአብነት ት/ቶችን የሚያስተምር Telegram Channel ስለሆነ ቤተሰብ ይሁኑ ይማሩ ልጆቾንም በማስተማር ለትውልድም ያስተላልፉ 🙏🙏🙏 እነሆ ከ''አአትብ ጀምሮ እስከ ሚፈልጉት ት/ት ድረስ በቻናሉ በመመዝገብ ተማሩ ➩ ውዳሴ ማርያም ➩ አንቀጸ ብርሃን ➩ መልክዐ ማርያምና ኢየሱስ ➩ መዝሙረ ዳዊት ➩ መልዕክተ ዮሐንስ ና ወንጌል(ሐዲስ ኪዳን) ንባባት ➩ ዜማ (ምዕራፍ : ጾመ ድጓ) ➩ ቅዳሴና ሰዓታት ዘደብረ ዓባይ (ለምዕመናን ተሰጥኦ) ➩ ቅኔ ምራታ(ሙሉ ቤት) ➩ አቋቋም ዘተክሌ(በታች ቤት) ➩ ዝማሬ መዋሥዕት ➩ ልሳነ ግእዝ ➩ባሕረ ሐሳብ...ወ.ዘ.ተርፈ.... ይህ የዘመነ ክረምት ገጸበረከት ነው እንዳያመልጥዎ በተለይ በቅዳሴ: ሰዓታት: ማኅሌት መሳተፍና ከካህናቱ ና ሊቃውንቱ ጋር ቃለ እግዚአብሔርን ለማለት ጠቃሚ ነው
ልዩ የክረምት የልጆች የት/ት ሰሌዳ ስላዘጋጀን ልጆትን በመንፈሳዊ እውቀት ያበልጽጉ🙏
መመዝገቢያ ቀን ስለሆነ እንዳያመልጣቹ🙏🙏🙏 ለበለጠ መረጃ 📱 0947458537 0989165434 ➢ @JonasM27 @Nah2129

ርእስ : በምን ደስ ላሰኝህ በምን ደስ ላሰኝ ጌታዬ ሆይ በምን ደስ ላሰኝ አምላኬ ሆይ አለምና ሞላው ያንተ አይደለም ወይ የፈጠርከው ሁሉ ያንተ አይደለም ወይ ++++++++  አዝማች ++++++++++++          ኪሩቤል ሱራፌል ቅዱስ ስሉስ ያሉህ           መላዕክት በራማ የሚያመሰኑህ           ድንቅ መካር አምላክ ኤልሻዳይ ነህና       ትንቢያ ነኝ ምን ልስጥህ ምንስ አለኝና (2) ++++++++ አዝማች  ++++++++++++ ቅዱሱን  መሰዋዕት ልዑል ስለ ሚወድ ምን ይዤ ልምጣና በአምላኬ ፊት ልስገድ ወደ ላይ በሰማይ ወደ ታች በጥልቀት  አምላኬ የት አለ የማትገኝበት ++++++ አዝማች +++++++++         በኪዳን በፀሎት ቅዳሴ ሰዓታት         አንተ የሰጠኸኝ የመንፈስ ቅዱስ ሀብት         መልሰን ወዳንተ ብንሰጥ ምን አለ          ተወው ጉዳችንን ስስታችን ይኸው (2) +++++++    አዝማች    ++++++++++ ሀብትና ንብረቴ ጉልበቴስ ምንድነው ጤናዬ የሰጠኝ ከአንተ በቀር ማነው በሰጠኸኝ እድሜ በሒወት ዘመኔ ከገላዬስ ቢሆን የትኛው ነው የኔ ከአካላቴስ ቢሆን የትኛው ነው የኔ

​                      ሰዋስወ ግእዝ ​ (ክፍል አንድ) ​ሀ. ሰዋስው ማለት፡ "አሰውሰወ" (መሰላል አደረገ/መሰላል ሠራ) ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ነው። ትርጉሙም መሰላል፣ ድልድይ፣ መሸጋገሪያ፣ መመላለሻ ማለት ነው። ​"አንድ ሰው በመሰላል  አማካኝነት ከታች ወደ ላይ እንደሚወጣና ከላይም ወደ ታች እንደሚወርድ ሁሉ፤ አንድ ተማሪም በሰዋስው አማካኝነት በመጀመሪያ ፊደላትን አጥንቶ፣ ቃላትን ሰብስቦ፣  (አረፍተ ነገር) ይመሠርታል። በዚያም አማካኝነት ወደ ጥልቅ የትርጓሜ መጻሕፍት፣ ምስጢርን የመረዳት፣ ዕውቀትን የመቅሰምና ቋንቋውን የመቆጣጠር ደረጃ ይደርሳል።" ይህ የቃሉ ቀጥተኛ ትርጉም ነው። ​ለ. ተግባራዊ ትርጉሙ፡ ሰዋስው ማለት የአንድ ቋንቋ መዋቅራዊ ሕጎችና ሥርዓቶች ማለት ነው። "ሰዋስወ ግእዝ" ሲባልም የግእዝ ቋንቋ ሕግ፣ ሥርዓት፣ አካሄድ፣ አነባበብ፣ አጻጻፍ፣ አነጋገር፣ አገባብ፣ አዋጅና ቅምር ማለት ነው። በአጠቃላይ የቅኔና የግእዝ ትምህርት ሁሉ ሰዋስው ተብሎ ይጠራል። ​ሰዋስው በሁለት ይከፈላል፤ እነርሱም ዘር እና ነባር ናቸው። ​፩. ዘር ​ዘር የተባለበት ምክንያት በምሳሌነት ነው።  አንድ የዘር ፍሬ ተዘርቶ፣ በቅሎ፣ ቅርንጫፍ አውጥቶ ብዙ ፍሬ እንደሚያፈራ፤ በሰዋስወ ግእዝም "ዘር" የተባለው ቃል ልክ እንደ ዘር መነሻ ሆኖ፣ በራሱ ልዩ አረባብና አካሄድ ብዙ ቃላትን ስለሚያፈራና ስለሚወልድ ነው። ይህም የሁሉም አንቀጾችና ቃላት ምንጭ፣ ሥርና እናት ነው። ​፪. ነባር  ​ነባር ማለት ተቀማጭ፣ የማይንቀሳቀስ ማለት ነው። ልክ እንደ ዘር አዳዲስ ቃላትን መውለድ  የማይችል (ጸንቶ የሚኖር) ማለት ነው። ይህ ደግሞ በአምስት ይከፈላል፦ የሰው ስም፣ የሀገር ስም፣ አንቀጽ፣ አገባብ እና ሰዋስው (ወይም ብትን ሰዋስው)። ​የሰው ስም፦ እንደ ሙሴ፣ ኤልያስ ያሉ። ​የሀገር ስም፦ እንደ ኢትዮጵያ፣ ኬብሮን ያሉ። ​አገባብ፦ እንደ እስመ ፣ እንዘ ፣ ከመ ያሉ። ​አንቀጽ፦ እንደ ቦ (አለ)፣ አልቦ (የለም)፣ ውእቱ (እርሱ/ነው)፣ አኮ (አይደለም) ያሉ። ​ሰዋስው (ብትን ሰዋስው)፦ እንደ ዖም ፣ ኮከብ ያሉ። ​የዘር ምደባዎች ​ዘር በተለያዩ ክፍሎች ይከፈላል፤ እነርሱም ጥሬ ዘር፣ ዘመድ ዘር፣ ሳቢ ዘር፣ ባዕድ ዘር፣ አንቀጽ ወዘተ ናቸው። ​፩. ጥሬ ዘር፦ ከመጀመሪያው አንቀጽ (ግስ) ጋር የተያያዘ ሁኔታን ወይም ነገርን የሚገልጽ ትርጉም ያለው ሲሆን፣ ተጨማሪ ፊደል ሳይጨምር መጨረሻው ፊደል ራብዕ (4ኛ)፣ወይም ሓምስ (5ኛ) ወይም ሳብዕ (7ኛ) ፊደል ያደርጋል። ​ምሳሌ፦ ሥጋ ከተሠገወ፣ ሉዓሌ (ከተልዕለ)መሰንቆ (ከሰንቀወ)። ​፪. ዘመድ ዘር፦ በትርጉሙ ከመጀመሪያው አንቀጽ ጋር የተያያዘ ሆኖ፣ በፊደል አወቃቀሩም ከመጀመሪያው አንቀጽ የማይወጣ፤ ነገር ግን የመጨረሻው ፊደል በሳልስ (3ኛ) ወይም በሳድስ (6ኛ) ፊደል የሚያልቅ ነው። ​ምሳሌ፦ ክብር (ከከበረ)፣ ፍቅር (ከአፍቀረ)፣ ሐሊብ (ከሐለበ)፣ ነቢብ (ከነበበ)፣ ቀዳሚ (ከቀደመ)። ​፫. ሳቢ ዘር፦ ዘሮችን ተናቦና ሳይናበብ የሚስብ መድረሻው ፊደል በሳድስ  (6ኛ) ፊደል በት ብቻ የሚያልቅ፣ የመጨረሻው ፊደል ተከታይም ግእዝ (1ኛ) ፊደል የሚያርግ ነው። ​ምሳሌ፦ ቅትለት (ከቀተለ)፣ ጥሕረት (ከጥሕረ)፣ ሢመት (ከሤመ)፣ ሑረት (ከሖረ)፣ ምጽአት (ከመጽአ)። ​፬. ባዕድ ዘር ፦ ከመጀመሪያው አንቀጽ (ግስ) ጋር በትርጉም የተያያዘ ሆኖ፣ ነገር ግን ከመጀመሪያው አንቀጽ ውጪ የሆነ ባዕድ  ፊደል በመጀመሪያው ላይ የሚጨምር ነው። መጨረሻውም በሳድስ (6ኛ) ይጠናቀቃል። በመጀመሪያው ላይ የሚጨመሩት ፊደላትም መ፣ ተ፣ አ ናቸው። ​ምሳሌ፦ መንበር (ከነበረ)፣ ተግባር (ከገብረ)፣ አስካል (ከሰከለ)። ​፭. አንቀጽ፦ አንቀጽ ማለት "በር" ማለት ነው። በር የአንድ ቤት መግቢያና መውጫ እንደሆነ ሁሉ፣ ይህ ደግሞ የቃላት መግቢያና መውጫ ነው። ​ጥንታውያን የቅኔ ሊቃውንት ከዘር ወደ አንቀጽ ይገሱት (ያወርዱት) ነበር፤ ከእነርሱ በኋላ የተነሱ ሊቃውንት ግን ከአንቀጽ ወደ ዘር መገሰስን (ማርባትን) ጀምረዋል። ምክንያቱም አንቀጽ ማለት በር ማለት ስለሆነ፣ የአንድ ቤት በር ካልተከፈተ በውስጥ ያለው እቃ እንደማይታይ ሁሉ፤ ልክ እንደዚያም በበር የተመሰለው አንቀጽ  ሲከፈት (ሲረባ)፣ ዘር ከአንቀጽ ተለይቶ ስለሚታወቅ  ከአንቀጽ ወደ ዘር ገሰውታል። ​ምሳሌ፦ "ቀተለ"، "ቀደሰ"، "ቆመ"، "ሤመ"። ​አንቀጽ ቀዳማይ፣ ካልኣይ፣ ሳልሳይ እየተባለ ይረባል/ይዘረዘራል። ዓቢያን አንቀጾች ሦስት ናቸው፤ እነርሱም፡ ሓላፊ አንቀጽ (ቀዳማይ)፣ ትንቢት አንቀጽ (ካልኣይ)፣ እና ትእዛዝ አንቀጽ (ሳልሳይ) ናቸው። ዓቢያን የተባሉበት ምክንያትም  ስበው ስለሚያስሩ ነው። ​፩. ሓላፊ አንቀጽ (ግስ)፦ ይህ አንቀጽ ሓላፊ ወይም ያለፈ አንቀጽ የተባለው፣ ባለፈው ጊዜ ስለተፈጸመ ድርጊት ወይም ስለተሠራ ሥራ ስለሚገልጽና ስለሚያመላክት ነው። ​ምሳሌ፦ "ቃል ሥጋ ኮነ" (ቃል ሥጋ ሆነ)። ማብራሪያ፦ "ቃል ሥጋ ሆነ" ሲል ድርጊቱ ተፈጽሞ ማለፉን ያሳያል። ​፪. ትንቢት አንቀጽ፦ ይህ አንቀጽ ትንቢት ተብሎ የተሰየመበት ምክንያት ወደፊት ስለሚፈጸም ነገር ስለሚገልጽ ነው። ነገር ግን በግእዝ ቋንቋ ለብቻው የቆመ የ"አሁን" (ህሉው) አንቀጽ ስለሌለ፣ ይህ የትንቢት አንቀጽ ለአሁን (አሁን ለሚደረግ) ነገር መግለጫም ተገቢውን አገልግሎት ይሰጣል። ​ምሳሌ ፩ (የወደፊቱን ሲገልጽ)፦ "ክርስቶስ ይመጽእ በስብሐት" (ክርስቶስ በክብር በምስጋና ይመጣል)። ​ምሳሌ ፪ (የአሁኑን ሲገልጽ)፦ "እግዚአብሔር ይነብር በሰማይ" (እግዚአብሔር በሰማይ ይኖራል)። ​፫. ትእዛዝ አንቀጽ፦ ይህ አንቀጽ አንድ አካል አንድ ተግባር እንዲፈጽም የሚሰጥ ቀጥተኛ ትእዛዝ ነው። ​ምሳሌ፦ "ወሶበ ርእይዎ ሊቃነ ካህናት ወወዓልያኒሆሙ ከልሑ ወይቤሉ ስቅሎ ስቅሎ" (የካህናት አለቆችና ጠባቂዎቻቸው ባዩት ጊዜ "ስቀለው! ስቀለው!" እያሉ ጮኹ)። ​"ባዕ ውስተ ፍሥሓሁ ለእግዚእከ" (ወደ ጌታህ ደስታ ግባ)። ​✍️ መምህር ኣቤሜሌክ በሥርዓት ተመዝግበው መማር የሚፈልጉ በሚከተለው ቁጥር ያግኙኝ፦ +251980021323

​1.መሰረታዊ ሰዋስው 2.ምስጢረ ቅኔ 3.አዋጅ፤እርባቅምር፤አገባብ፤መንገዲ ቅኔ 4.መጽናዕቲ ግዕዝ ​"አጥርዮታ ለጥበብ ይትበደር እምወርቅ ወአጥርዮታ ለአእምሮ ይኄይስ እምብሩር" ምሳ16.15 https
​1.መሰረታዊ ሰዋስው 2.ምስጢረ ቅኔ 3.አዋጅ፤እርባቅምር፤አገባብ፤መንገዲ ቅኔ 4.መጽናዕቲ ግዕዝ ​"አጥርዮታ ለጥበብ ይትበደር እምወርቅ ወአጥርዮታ ለአእምሮ ይኄይስ እምብሩር"  ምሳ16.15 https://t.me/MemhirRobelGeezandQene

የሰኔ መድኃኔዓለም ማኅሌት ነገ ይጠብቁን ዛሬን ማኅሌት ለምትቆሙ የቅዱስ ገብርኤል ወዳጆች መልካም አገልግሎት

በዚህ ክረምት ልጅዎ ትምህርቱን እንዲያጠናክር እና ለቀጣይ ዓመት ዝግጁ እንዲሆን ይፈልጋሉ? ⏳ ጊዜው አሁን ነው! የክረምቱን እረፍትን ለትምህርት ማጠናከሪያ ይጠቀሙበት። ቀንዲል ✨ ከልጅዎ ጋር በመሆ
በዚህ ክረምት ልጅዎ ትምህርቱን እንዲያጠናክር እና ለቀጣይ ዓመት ዝግጁ እንዲሆን ይፈልጋሉ? ⏳ ጊዜው አሁን ነው! የክረምቱን እረፍትን ለትምህርት ማጠናከሪያ ይጠቀሙበት። ቀንዲል ✨ ከልጅዎ ጋር በመሆን ድክመቶችን እናስተካክላለን እንዲሁም ጥንካሬዎችን እናሳድጋለን! ከKG – 12ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች በልምድ የታገዙ አስጠኚዎችን እናቀርባለን። 📌 ክረምቱን ከእኛ ጋር ያሳልፉ ✅ ለ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ልዩ ዝግጅት ✅ የቤት ለቤት አገልግሎት (ሴት/ወንድ አስጠኚ) ✅ በተመጣጣኝ ዋጋ እኛን ለማግኘት 📲 +251935235078 ይደውሉ!

ሥርዓተ ማኅሌት አመ ፳ወ፮ ለሰኔ ቅዳሴ ቤቱ ለገብርኤል ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፤ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፤ በአሐቲ ቃል። ለገባሬ ኵሉ ሰላም ለአብ ገባሬ ኵሉ ዓለም፤ለወልድ ሰላም ወለመንፈስ ቅዱስ ሰላም፤ለማርያም ሰላም ወለመላእክት ሰላም፤ሰላም ለነቢያት ወለሐዋርያት ሰላም፤ለሠማዕታት ሰላም ወለጻድቃን ሰላም። ዚቅ፦ ሃሌ ሉያ ለአብ ወአዕባነ ወርቅ ተሐንፀት መካኑ፤ሃሌ ሉያ ለወልድ ምሥጢረ ሥላሴ ነጸረ በዓይኑ፤ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ፤ተቃሞቶ መዋግድ ስዕኑ፤መዓዛ ኂሩቱ ከመ ርኄ አፈው ይጼኑ፤ለገብርኤል እመዓር ይጥዕም ልሳኑ። ነግሥ፦ ሰላም ዕብል ገብርኤል ግሩም፤በዲበ አዕላፍ ስዩም፤ለአውር ረዳኢ እምቅንዓተ ሰይጣን ርጉም፤ሶበ ፈጸመ ሐኒፀታ በአዕባነ ባሕርይ መድምም፤ቤተ ክርስቲያኑ ተቀደሰት በኔቅሎን ዮም። ዚቅ፦ ወፈጺሞ ንጉሥ ሐኒፀ ቤቱ ለእግዚአብሔር፤ሰገዳ በብረኪሁ ወእደዊሁኒ ውስተ ሰማይ አልዓለ፤ጸለለ ወመልዓ ስብሐተ እግዚአብሔር፤ውስተ ዝንቱ ቤት። መልክአ ገብርኤል፦ ሰላም ለአዕዳዊከ ወለመዛርኢከ ክልዔቱ፤ዘአስተዋደዶሙ ቅድመ እግዚአብሔር በመለኮቱ፤ገብርኤል አንተ ሐዋርያ ክርስቶስ ወወላዲቱ፤አዕርገኒ እምግበ ደይን ዘኢይጠፍእ እሳቱ፤ወዕፄሁ ትጉህ ዘንዋም አልቦቱ። ዚቅ፦ ዳንኤልኒ ይቤ በውስተ ኦሪት፤ምድር ሠናይት ወአኮ ከመ ምድረ ግብፅ፤ምድር ሠናይት እንተ ዘልፈ ይሔውፃ እግዚአብሔር፤እምዓመት እስከ ርእሰ ዓውደ ዓመት፤ምድር ሠናይት ወአኮ ከመ ምድረ ግብፅ፤ያዕቆብኒ ይቤ፤ርኢኩ ሰዋስወ ዘሰማይ ዝየ ይትሐነፅ ቤተ እግዚአብሔር፤ሐነፀ መቅደሶ በአርያም ዳዊትኒ ይቤ፤ዛቲ ይእቲ ምዕራፍየ ለዓለም ዝየ አኃድር እስመ ኃረይክዋ፤ሐነፀ መቅደሶ በአርያም፤ክነፈ ርግብ በብሩር ዘግቡር፤ወገበዋቲሃኒ በሐመልማለ ወርቅ፤ሥርጉት አረፋቲሃ ለቤተ ክርስቲያን በዕንቈ ሰንፔር ወበጳዝዮን፤ሥርጉት አረፋቲሃ ለቤተ ክርስቲያን፤በከርከዴን ወበመረግድ፤ሥርጉት አረፋቲሃ ለቤተ ክርስቲያን፤ሥርጉት በከርከዴን ወበመረግድ፤በአስማተ ፲ቱ ወ፭ቱ ነቢያት፤ሥርጉት አረፋቲሃ ለቤተ ክርስቲያን፤ሥርጉት በከርከዴን ወበመረግድ፤በአስማተ ፲ቱ ወ፪ ሐዋርያት፤ሥርጉት በከርከዴን ወበመረግድ፤አረፋቲሃ ለቤተ ክርስቲያን ሐፁር የዓውዳ ወጽጌ ረዳ ብእሲ ተወልደ በውስቴታ፤ንጉሠ ፳ኤል አልቦ ማኅለቅት ለመንግሥቱ፤ንጉሠ ፳ኤል አልቦ ማኅለቅት ለመንግሥቱ፤ንጉሠ ፳ኤል፤ህየ ማኅደሩ ለልዑል፤ንጉሠ ፳ኤል አልቦ ማኅለቅት ለመንግሥቱ፤መድኃኔ ዓለም እግዚአብሔር ኃደረ ላዕሌሃ ኪያሃ ዘሠምረ ሀገረ። ወረብ፦ ገብርኤልኒ ይቤ ዛቲ ይእቲ ምዕራፍየ ለዓለም ዛቲ ይእቲ/፪ ዝየ አኃድር "እስመ ኃረይክዋ"/፪/፪/ መልክአ ገብርኤል፦ ሰላም ለሕሊናከ ዘየአምር የብቦ፤መሌሊተ ሥጋዕ ኵሉ በባሕርይከ ዘአልቦ፤መልአከ አድኅኖ ገብርኤል አውጽአኒ እምተመንድቦ፤አመ ነፍሐ በላዕሌየ እሳተ መቅሰፍት ላሕቦ፤ኪያየ ጸልል በአክናፍ ዘገቦ። ዚቅ፦ በምድረ ጽዮን ኢይኩን ሐከክ፤ወበገራኅታ ኢይብቁል ሦክ፤ጸሊ ኀበ አምላክ ራጉኤል መልዓክ፤ዓውደ ዓመት ከመ ይትባረክ። ወረብ፦ በደብረ በደብረ ምሕረት ኢይኩን ሐከክ/፪/ ጸሊ ኀበ አምላክ ገብርኤል መልአክ ከመ ይትባረክ ዝንቱ ክረምት/፪/ ዓዲ ወረብ፦ "ጸሊ ኀበ አምላክ"/፪/ገብርኤል መልአክ/፪/ ከመ ይትባረክ ዝንቱ ክረምት/፪/"ጸሊ ኀበ አምላክ"/፪/ገብርኤል መልአክ/፪/ መልክአ ገብርኤል፦ ሰላም ለአዕጋሪከ በጽንፈ ኤፍራጥስ እለ ቆሙ፤ቅድመ ብእሴ ፍትወት ዳንኤል ለብልጣሶር ውላጤ ስሙ፤ገብርኤል አንተ ናዛዜ ኅዙናን ዘእምቀዲሙ፤ወሚጠተ ሕዝብ እለ ውስተ ባቢሎን ሐሙ፤ለዝኩ ነቢይ ነገርኮ በሕልሙ። ዚቅ፦ መንበሩ በእሳት ክሉል ወማኅደሩ በማይ ጥፉር፤ወዲበ ተድባበ ቤቱ ኅንባበ ማይ ዘኢይትከዓዉ፤ወእመንበሩ ይወጽእ ፀዓዕ፤ከመ ርስነ እሳት ውስጡ ብርሃን ዓቢይ ውስቴቱ፤ከመ ቀስተ ደመና ዘክረምት መብረቅ ዓውዱ። ወረብ፦ ወዲበ ተድባበ ቤቱ ለሊቀ መላእክት/፪/ ኅንባበ ማይ/፪/ዘኢይትከዓዉ/፪/ መልክአ ገብርኤል ዘካልዑ፦ እንዘ አኃሥሥ እግዚኦ በረከተከ ብዙኀ፤ዘአቅረብኩ ለከ ስብሐተ ማኅሌት አምኃ፤ተወከፈኒ ሊቅየ ገብርኤል መልአከ ፍሥሐ፤ከመ ሠምረ ወተወከክፈ መስዋዕተ አቤል ንጹሐ፤እግዚአብሔር አምላክ ለምሕረት አቡሃ። ዚቅ፦ ተወከፍ ጸሎቶሙ ለአግብርቲከ ወለአዕማቲከ፤እለ ጻመዉ ወመጽዑ ጽርሐ መቅደስከ፤ኀበ የኃድር ኃይለ ስብሐቲከ። ወረብ፦ ተወከፍ ፀሎቶሙ ለአግብርቲከ ወለአዕማቲከ ሊቀ መላእክት[፪] እለ ፃመዉ ወመጽዑ "ጽርሐ መቅደስከ"/፪/ሊቀ መላእክት[፪] መልክአ ማርያም፦ ሰላም ለአጽፋረ እግርኪ ዘኢፈቀዳ ለሥርጋዌ፤ጥምዓታተ ሕምር ምድራዌ፤ማርያም ድንግል ሐውልተ ስምዕ ዘወልደ ነዌ፤ሡቅኒ እምትንታኔ ወባልሕኒ እምአርዌ፤ላዕለ እምየ ዘአምጽአ ደዌ። ዚቅ፦ ሐውልተ ስምዕ ዘኢያሱ ፀምር ዘጌዴዎን፤ሙዳየ ዕፍረት ወቀርነ ቅብዕ ዘሳሙኤል። አመላለስ ፦ ሐውልተ ስምዕ ዘኢያሱ/፬/ ዘጌዴዎን ፀምር/፬/ ምልጣን፦ ተቀደሲ ወንስዒ ሃይለ ኦ ቤተ እግዚአብሔር፤እስመ ናሁ ንጉሥኪ በጽሐ ዘያበርህ ለኪ በኃይሉ፤ለዛቲ ቤት ሣረራ አብ ቀዲሙ ለዛቲ ቤት፤ሐነጻ ወልድ ለዛቲ ቤት፤ወፈጸማ መንፈስ ቅዱስ። ወረብ፦ ተቀደሲ ወንሥኢ ኃይል ኦ ደብረ ምሕረት/፪/ እስመ ናሁ ንጉሥኪ በጽሐ ንጉሥኪ ዘያበርህ በኃይሉ ፋሲለደስ/፪/ እስመ ለዓለም በጾም ወበጸሎት ይሠረይ ኃጢአት፤ጾም ተውህበት ለንሥሐ፤እስመ ለሊሁ መድኃኒነ ጾመ፤በጾም ሙሴኒ ጾመ በደብረ ሲና፤ወተናገሮ እግዚአብሔር በዓምደ ደመና በጾም፤በጾም ወኢያሱኒ በጾም ድኅነ፤በገባዖን ፀሐየ ዓቀመ፤በጾም ዕዝራኒ ጾመ በገዳም፤ወርእያ በገዳም ለቤተ ክርስቲያን፤በጾም ወበጸሎት ይሠረይ ኃጢአት፤ርእዩ ዕበያ ለጾም። አመላለስ ዘእስመ ለዓለም በጾም ወበጸሎት ይሠረይ ኃጢአት/፪/ ርዕዩ ዕበያ ለጾም/፪/ ወረብ ዘእስመ ለዓለም፦ ወኢያሱኒ በጾም ድኅነ በገባዖን ፀሐየ አቀመ/፪/ ዕዝራኒ ጾመ በገዳም ወርእያ ለቤተ ክርስቲያን/፪/

photo content

💠💠💠💠💠💠 መዝሙር ዘሰንበት ✨✨✨✨✨✨ በ፪ ሀሌታ- ሃሌ ሃሌ ሉያ ደምፀ እገሪሁ ለዝናም፤ ሶበ ይገስስ ዝናመ ይፀግቡ ርኁባን፤ ደምፀ እገሪሁ ለዝናም ሶበ ይዘንም ዝናም ይትፌሥሑ ነዳያን ፤ደምፀ እገሪሁ ለዝናም ወሠርዓ ሠንበተ ለሰብዐ ዕረፍተ፤ ማ፦ ደምፀ እገሪሁ ለዝናም፤ ደምፀ እገሪሁ ለዝናም አመላለስ፦ ደምፀ እገሪሁ ለዝናም/2/ ደምፀ እገሪሁ ለዝናም/4/ 🇪🇹👇👇👇👇👇🇪🇹 👉@EOTCmahlet👈 👉@EOTCmahlet👈 👉@EOTCmahlet👈 🇪🇹👆👆👆👆👆👆🇪🇹 @EOTCmahlet #ይቀላቀሉ & #ለወዳጅዎ_ሼር_ያርጉ

አቋቋም👳‍♂👳‍♂👳‍♂👳‍♂👳‍♂👳‍♂👳‍♂👳‍♂👳‍♂ አቋቋም ትምህርት ይህንን ዘር በተለያዩ ዓይነቶች ይዘርዝራል፤ በዝማሜ፣በቁም፣ በመረግድ እና በጽፋት ብሎ ተከፍሎ ይሰጣል። እንዲሁም አቋቋም ለመጀመር ከበዓል ወቅት ጀምሮ ይቻላል፣ በተለይም በጎንደር በዓታ የሚጀመረው የሚከተሉት ናቸው፦ 1 ከመስከረም ዮሐንስ እስከ ጳጉሜን – ክብረ በዓል አቋቋም 2 ከመስከረም ዮሐንስ ... እስከ ጳጉሜን መዝሙር አቋቋም 3 ከመስከረም ... እስከ ነሐሴ መጨረሻ – ወረኃ በዓላት አቋቋም 4 አርባዕት አቋቋም 5 ቅኔ አቋቋም 6 ኪዳን ሰላሞች አቋቋም 7 ሠለስት አቋቋም 8 ሰሎሞን ምቅናይና ግናይ አቋቋም 9 መኃትው አቋቋም እነዚህ ከላይ የምታዩት አቋቋም ትምህቶች  በተጨማሪ ከታች ያሉትን ስንል ምን ማለታችን ነው? አመል -? ጠንቅቅ - ? ለቡ - ? ተመልከት አቅና - ? ኢትርገጥ/አይረግጥም/ጠቅልል - ? ተወራራሽ - ? ማሳረፍ/አሳርፍ - ? አንሣ -? ዕጠፍአጥፍ-? ሠረገላ -? ከዚህ መሠረት ከሆነው ዜማ ከአአትብ ጀምሮ ሁሉም መሠረታዊ የአብነት ት/ት ተማሩ አለ ኑ ተማሩ እየተባላችሁ ነው ያሬዳውያን አቋቋምን መማር ከፈለጉ በደንብ ለማስተምር የተዘጋጀ ጉባኤ ቤት እናስተዋውቆ አርያም ዜማ ቤት ይሰኛሉ፣ በመጀመሪያ የአቋቋም ትምህርት መማር ለመጀመር እንደ “ጥሬ እቃ” የሚሆነው ከር ይኖራል፡፡ ይህ ጥሬ እቃ የተባለው የድጓ ዘር ወይም ዜማ ነው፡፡ በአቋቋም ቤት ይህን ዜማ እንደ “ዘር” በመጠራት ይታወቃል፣ ምክንያቱም ዜማ ለአቋቋም መሠረት ስለሆነ ነው::

የሰኔ 30 በዓለ ልደቱ ለዮሐንስ መጥምቅ ማኅሌት ከነ ወረቡ ተለቋል እኮ ደረሳችሁ?👀 ካልደረሳችሁ ዮሐንስ ምትለዋን ተጫኑ ለማግኘት 👉 ዮሐንስ

በዚህ ክረምት ልጅዎ ትምህርቱን እንዲያጠናክር እና ለቀጣይ ዓመት ዝግጁ እንዲሆን ይፈልጋሉ? ⏳ ጊዜው አሁን ነው! የክረምቱን እረፍትን ለትምህርት ማጠናከሪያ ይጠቀሙበት። ቀንዲል ✨ ከልጅዎ ጋር በመሆ
በዚህ ክረምት ልጅዎ ትምህርቱን እንዲያጠናክር እና ለቀጣይ ዓመት ዝግጁ እንዲሆን ይፈልጋሉ? ⏳ ጊዜው አሁን ነው! የክረምቱን እረፍትን ለትምህርት ማጠናከሪያ ይጠቀሙበት። ቀንዲል ✨ ከልጅዎ ጋር በመሆን ድክመቶችን እናስተካክላለን እንዲሁም ጥንካሬዎችን እናሳድጋለን! ከKG – 12ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች በልምድ የታገዙ አስጠኚዎችን እናቀርባለን። 📌 ክረምቱን ከእኛ ጋር ያሳልፉ ✅ ለ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ልዩ ዝግጅት ✅ የቤት ለቤት አገልግሎት (ሴት/ወንድ አስጠኚ) ✅ በተመጣጣኝ ዋጋ እኛን ለማግኘት 📲 +251935235078 ይደውሉ!

አቋቋም መማር ለምትፈልጉ በቅርቡ የምስራች አለን ጠብቁን

✞✞✞ ቅኔ ✞✞✞ "ቅኔ"  "ቀነየ" ገዛ አስገዛ ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጓሜውም አዕምሮን ለቅኔ ምስጢር አስገዝቶ አዲስ ምስጥር ማፍለቅ ሲሆን ይሄንንም ገላጩ መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡       ቅኔ በእኛ በባለታሪኮቹ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ብቻ ያለ ድንቅ እና ረቂቅ ሀብታችን ነው ፡፡    ቅኔ የአንድን ሰው የማሰብ ችሎታን ወይም ለሰው መለኪያነት በድሮ ጊዜ ያገለግል ነበር ፡፡ ይህ ማለትም አንድን ሰው ለመገመት የአዕምሮውን ብስለት እና ርቀት ለማወቅ ቅኔውን ብቻ መስማት በቂ ነበር ማለት ነው፡፡ በረከታቸው ይደርብን እና ፪ኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ቅኔ አዋቂ ነበሩ እና አንድን የቤተ ክህነት ትምህርት የተማረን ሰው ለመቅጠር ቅኔን እንደ አንድ መስፈርት አድርገው ፈትነው ነበር የሚቀጥሩት የሰውንም ብስለት እና ጥሬነት በቅኔው ይረዱ ነበር ይባላል፡፡   ሌላው ቅኔ የራሱ የሆነ ስርዐት እና ሕግ ያለው ሰዋሰው የጠነቀቀ በሰምና ወርቅ የተጠቀለለ የስድነት ፀባይ የሌለው ሲሰሙት ለጆሮ የሚጥም ዜማ ልክ ያለው ቤት , ሐረግ ያለው ሲሆን ለፈጣሪ ለቅዱሳን , ለጻድቃን ,ለሰማዕታት ምስጋና ማቅረቢያ ነው፡፡          ሌላው ቅኔ በየቀኑ ከአዕምሮ የምናፈልቀው ሁሌ አዲስ ምስጋና ዛሬ የተባለ ለነገ የማይደገም ሁሌ አዲስ ምስጋና ነው ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ "ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር ሐዲሰ ስብሐት" ባለው መሰረት ሁሌ አዲስ የሆነ ምስጋና ነው፡፡ በኦንላይን የምንሰጣቸው ትምህርቶች ➡️ንባብ፦ ከዘወትር ጸሎት ጀምሮ ➡️ግእዝ፦ ከፊደል ጀምሮ ➡️የዘመን አቆጣጠር/ባሕረ ሐሳብ ➡️ቅኔ፦ ከጉባኤ ቃና ጀምሮ የክረምት ትምህርት ለልጅዎ የሚያወርሱት ልዩ ቅርስ እውቀት ትምህርት ነው በዚህ ክረምት ደግሞ ጳውሎስ ኦንላይን ቅኔ ቤት ሰፊ የትምህርት ዝግጅት አድርጎ ማስተማር ጀምሯል ሳይረፍድ ይመዝገቡ❗ ለመማር ቴሌግራም @pawli37 Phone +251915642585 ዋና ቻናላችን ❤️❤️❤️❤️ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/GeezPoetry ✅✅✅✅✅✅❤️ ➡️አዲስ አበባ ያላችኹ ኮተቤ መሳለሚያ ማርያም አካባቢ እየመጣችኹ በአካል ተማሩ ✝መርሐ ግብራችን ➡️ቅዳሜና እሑድ ✅ከጠዋቱ 3:00-10:00 ➡️ከሰኞ እስከ ዐርብ ✅ከቀኑ 11:30 እስከ ምሽቱ 1:30

✨አረሳት ኢትዮጵያን አረሳት ኢትዮጵያን በእርፈ መስቀል አባ ተክለ ሀይማኖት ሰባኪ ወንጌል የእግዚአብሔር ሰው ነው ተወዳጅ በሰማይ የተረማመደ በፅድቅ አደባባይ አዝማች ፈውስና ፀሎቱ ቃሉ የተሰማ ወንጌል የሰበከ በገጠር ከተማ የኢቲሳው ኮከብ የደብረ አስቦቱ ለወንጌል ተዋጋች ንፅህት ህይወቱ አዝማች ፋናው እስከ ዛሬ ሲያበራ የኖረው የኢቲሳው አባት ፍስሀ ፅዮን ነው እግዚአርያ እናቱ ማህፀነ ብሩክ ወለደች ኮከብን ሲዖልን የሚያውክ አዝማች ዲያብሎስ እስካሁን ስሙ ሲጠራበት ሲገረፍ ይኖራል በእሳት ሰንሰለት አዲስ ሀዋርያ የኢትዮጲያ አባት ደጋና ቆላውን በመስቀል ባረካት አዝማች ምንጩና ፏፏቴው ተራራው ቅዱስ ነው የአባታችን መስቀል ፀሎት ስለነካው የተራመደበት የዳሰሰው ሁሉ ድውይ ይፈውሳል ሳር እና ቅጠሉ

ውድ የዝማሬ ዳዊት ቤተሰቦቻችን የእናታችን ቤት ለፍጻሜ እንዲበቃ እገዛችሁን እንሻለን ይህች የምታዩዋት በወላይታ ሀገረ ስብከት በኪንዶ ወረዳ በዛሮ ማ/ስ/ቅ/ሥላሴ ቤተክርስቲያን ሥር የምትተዳድረው የ
+2
ውድ የዝማሬ ዳዊት ቤተሰቦቻችን የእናታችን ቤት ለፍጻሜ እንዲበቃ እገዛችሁን እንሻለን ይህች የምታዩዋት በወላይታ ሀገረ ስብከት በኪንዶ ወረዳ በዛሮ ማ/ስ/ቅ/ሥላሴ ቤተክርስቲያን ሥር የምትተዳድረው የጋላ በዓታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያንን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በጥቅምት ወር 2019 ዓ/ም ለፍጻሜ እንድናበቃት የናንተን የቤተክርስቲያን ልጆቻችንን እገዛ እንፈልጋለን ። ስለዚህም ውድ ክርስቲያኖች በቁስ ወይንም በባንክ አካውንት የምትችሉትን በማድረግ አብራችሁን እንድትሆኑ በእናታችን ስም በአክብሮት እንጠይቃችኋለን የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶች 1) ፟ለኮርኒስ ፦ ኮንፎርሳቶ 50 ፍሬ ፡ ሞራሌ 12 እስር ፡ ጨርቅ 3 ጣቃ ፡ ሻሪሬ 100 ፍሬ 2) ቀለም 25 ጋሎን ፡ 3) መንበር 1 4) ምንጣፍ 5) ሲሚንቶ 20 ኩንታል 6) የመብራት ሹቦ 2.5 ( 2 ጥቅልል ) 7) ሚስማር 4 ፋኮ 8) አልባሳት 9) መጎናጸፊያ ከነ ቀጸላው 10) የሰንበት አልባሳት እና ልዩ ልዩ ቁሳቁሶች የሚያስፈልጉን ስለሆነ የምትችሉትን እንድታግዙን ለሌሎችም በማጋራት እንዲደርስ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃችኋለን ። የንግድ ባንክ አካውንት 1000379054138 « ወደ ተራራው ውጡ እንጨትንም አምጡ ቤቱንም ሥሩ፤ እኔም በእርሱ ደስ ይለኛል እመሰገንማለሁ ይላል እግዚአብሔር።» (ሐጌ 1፡8) የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷ እና ምልጃዋ አይለያችሁ ። እግዚአብሔር በቸረነቱ ይጠብቃችሁ ።