fa
Feedback
ያሬዳውያን

ያሬዳውያን

رفتن به کانال در Telegram

የየበዓላቱ ስርአተ #ዋዜማ ፤ #ማኅሌት ፤ #ወረብ ከ፯ ቀናት በፊት እንዲሁም የየሳምንቱ መዝሙራት እና ምስባክ በጽሑፍ እና በድምጽ የሚቀርቡበት ቻናል ነው #ሁሉም_ነገር_ስለ_ማኅሌት ለማስታወቂያ እና ለማንኛውም ጥያቄ ከፈለጉን አለን በዚህ ያናግሩን 👉 @Yaredawi_admin እናመሰግናለን

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ያሬዳውያን

کانال ያሬዳውያን (@eotcmahlet) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 124 121 مشترک است و جایگاه 248 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 239 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 124 121 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 18 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 2 738 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -18 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 12.74% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.91% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 15 807 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 9 812 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 46 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የየበዓላቱ ስርአተ #ዋዜማ ፤ #ማኅሌት ፤ #ወረብ ከ፯ ቀናት በፊት እንዲሁም የየሳምንቱ መዝሙራት እና ምስባክ በጽሑፍ እና በድምጽ የሚቀርቡበት ቻናል ነው #ሁሉም_ነገር_ስለ_ማኅሌት ለማስታወቂያ እና ለማንኛውም ጥያቄ ከፈለጉን አለን በዚህ ያናግሩን 👉 @Yaredawi_admin እናመሰግናለን

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 19 سپتامبر, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

124 121
مشترکین
-1824 ساعت
+1897 روز
+2 73830 روز
آرشیو پست ها
ሰላም ያሬዳውያን ቅዳሴ በዜማ ከመጀመሪያው ጀምሮ ይፈልጋሉ? እንግዲያው ቅዳሴ የሚለውን በመጫን ማግኘት ይችላሉ ከፈለጉ ይችን ጠቅ 👉 ቅዳሴ

+1
mahlete tsige 1.pdf7.53 MB

ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ያላስተማረቸውን እንዳስተማረች ያላለችውን እንደተናገረች ተደረጎ ትምህርት የሚሰጥበት ነገር አንዱ የቅዱሳን ቃልኪዳን ነው ጥንቃቄ ከሚያስፈልጋቸው ትምህርቶች መካከል አንደኛው ነው ። ስለ ቅዱሳን ቃልኪዳን የተዘጋጀ ጽሑፍ አለ፤ስለ ቅዱሳን ቃልኪዳን ሲነሳ ጥያቄ የላችሁም ? መጠየቅ ይቻላል... ስለ ተዘጋጀው ጽሑፍ ቅዱሳን ቃልኪዳን ምትለዋን በመጫን ያንብቡ ለማንበብ ይችን ጠቅ👉 ቅዱሳን ቃልኪዳን

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 መዝሙር እኩት አንተ ከመስረም ፱ - ፲፭ 🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊 (በ፭/ር) እኩት አንተ ወስቡሕ ስምከ ፤ ወዓቢይ ኃይልከ ፤ ዘተአርፍ በአርያም ወትሴባሕ በትሑታን ፤ ዘአንተ ሠራዕከ ሰንበተ ለዕረፍት ፤ ወወሀብከ ሲሳየ ዘበጽድቅ ለኵሉ ፤ እግዚኦ ባርክ ፍሬሃ ለምድር ፤ መሐሪ ወጻድቅ መኑ ከማከ ፤ ዘታርኁ ክረምተ በጸጋከ ፤ ማ ፦ ነፍስ ድኅንት ወነፍስ ርኅብት ፤ እንተ ጸግበት ተአኵተከ ። አመላለስ፦ ነፍስ ድኅንት ወነፍስ ርኅብት/፪/ እንተ ጸግበት ተአኵተከ/፬/ 🇪🇹👇👇👇👇👇👇🇪🇹 👉@EOTCmahlet👈 👉@EOTCmahlet👈 👉@EOTCmahlet👈 🇪🇹👆👆👆👆👆👆🇪🇹 @EOTCmahlet # Join & share

መልክአ-ሥዕል-በዜማ.m4a14.34 MB

መልክአ ሥዕል

ውድ ያሬዳውያን የመጀመሪያ ቻሌንጃችሁ እንሆ ተዘጋጅቷል፣ የያዛችሁት ጥሩ ለጀማሪዎች ግን ይህ የምታዩት በዓሉን የሚነካ መልክዓ ሥላሴ ወይም ገባሬ ኩሉ ዓለም ከተባለ በኃላ የሚባል ነው በስልክ እያዩ
ውድ ያሬዳውያን የመጀመሪያ ቻሌንጃችሁ እንሆ ተዘጋጅቷል፣ የያዛችሁት ጥሩ ለጀማሪዎች ግን ይህ የምታዩት በዓሉን የሚነካ መልክዓ ሥላሴ ወይም ገባሬ ኩሉ ዓለም ከተባለ በኃላ የሚባል ነው በስልክ እያዩ ማለት የለም 😉 ሁላችሁም በቃል ሸምድዱ ሙሉ ነግሥ በዚህ መሠረት በቻሌንጅ ይሰጣል ከነ ዜማው በቃል ይያዛል ማለት ነው 🙂 #challenge_3 እንሆ share 👉 @EOTCmahlet

ምል ይቤሎሙ ኢየሱስHA.m4a3.54 MB

#ሊቀ #ካህናት #ኢየሱስ #ክርስቶስ 1) ራሱ መሥዋእት አቅራቢ 2) ራሱ መሥዋእት 3) ራሱ መሥዋእት ተቀባይ ነገረ ሥላሴን አለማወቅ ነገረ ሥጋዌ ላይ እንድትስት ያደርግሀል። ሥላሴን በአካል ሦስት በባሕርይ አንድ እንላለን። አንዲት ባሕርይ ደግሞ ሦስት ከዊን አላት። ስለዚህ አዳም በሳተ ጊዜ በኋላ አዳምን ለማዳን የአዳምን ሥጋ የተዋሐደው ወልድ ነው። ይህም ሲሆን ወልድ በተለየ አካሉ አካለ ሥጋን ገንዘቡ አደረገ። ሥጋን ገንዘብ ያደረገ በተለየ አካሉ ወልድ ነው። ቅዱስ ቄርሎስ እንቲኣሁ ለቃል ኮነ ለሥጋ ወእንቲኣሁ ለሥጋ ኮነ ለቃል ያለው። አስተውል ወንድማለም እንቲኣሁ ለልብ ኮነ ለሥጋ ወእንቲኣሁ ለሥጋ ኮነ ለልብ አላለም። አብ ሰውን አልሆነምና። በተለየ አካሉ ሰው የሆነ ወልድ ነው። ከሁለት አካል አንድ አካል ማለት አካለ ወልድ አንድ፣ አካለ ሥጋ ሁለት ነው። እኒህ በተዋሕዶ በተዓቅቦ አንድ መሆን ነው።ሊቁ እስመ ተዋሕዶ አእተታ ለምንታዌ ተዋሕዶ ሁለትነትን አጥፍቷልና ይላል። ከተዋሕዶ በኋላ የቃል የሥጋ እያልን የምንለየው ነገር የለም። የቃል የሆነው ሁሉ የሥጋ የሥጋ የሆነው ሁሉ የቃል ሆኗልና። ምን ማለት ነው። ሥጋ ውሱንነቱን ሳይለቅ መላ። በአንድ ቦታ መሆኑን ሳይለቅ በሁሉ ቦታ ሆነ። ቃል ምልዐቱን ሳይለቅ በድንግል ማኅፀን ተወሰነ። ሥጋ ሐማሚነቱን ሳይለቅ ኢሐማሚ ሆነ። ቃል ኢሐማሚነቱን ሳይለቅ ሐማሚ ሆነ። ሥጋ ግዙፍነቱን ሳይለቅ ረቀቀ ስለዚህም በተዘጋ ቤት ገባ። ከድንግል ማኅፀን ተወለደ። ቃል ረቂቅነቱን ሳይለቅ ገዘፈ ስለዚህም በድንግል ማኅፀን ተወሰነ። ቅዱስ ኤፍሬም ድንግል ወለደቶ ለገባሪሃ ወውእቱኒ ፈጠረ ወላዲቶ እንዳለ። ፈጣሪ እናቱን ፈጠረ ድንግል ደግሞ ፈጣሪዋን ወለደችው። እንግዲህ የአካል ተዋሕዶ እንዲህ ነው። ። የባሕርይ ተዋሕዶስ እንዴት ነው? ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ እንላለን። ባሕርየ ሥላሴ አንዲት ናት። ስለዚህ ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ስንል ባሕርየ ሥላሴ ሰው ሆነች ወደማለት አያመራም ወይ የሚል ብዙ ጊዜ ጥያቄ ይነሳል። የዚህም መልሱ ባሕርየ ሥላሴ በቃል ከዊን ሰው ሆነች ይባላል እንጂ በልብ ከዊን ወይም በእስትንፋስነት ከዊን ስላልሆነ አያሰኝም። ስለዚህ ወልድ በተለየ ባልተለየ ባሕርዩ ሰው ሆነ። በተለየ በቃል ከዊኑ ከአሐቲ ባሕርይ ሳይለይ ሰው ሆነ። ለኩነት እንደ አካል ተሌልዮ አይነገርም። ሁልጊዜም ኩነታት ተገናዝቦ እንጂ ተፈልጦ የለባቸውምና። ። ይህንን ካልን መሥዋእት የሆነው ማን ነው ከተባለ። ከሦስቱ አካላት ወልድ በተዋሐደው ሥጋ ነው። አብ መሥዋእት ሆነ መንፈስ ቅዱስ መሥዋእት ሆነ አንልም። በመስቀል ተሰቅሎ መሥዋእት የሆነ በተለየ ወልድ ነው። እንጂ አብና መንፈስ ቅዱስ አልተሰቀሉም። አብ ልቡ መንፈስ ቅዱስ እስትንፋሱ የሆነ ቃል በሥጋ ተሰቀለ እንላለን እንጂ። የምንቀበለው ሥጋ ወደሙም ሥጋ ወልደ እግዚአብሔር ነው። እንጂ አብና መንፈስ ቅዱስ ሥጋን ስላልለበሱ የአብን ወይም የመንፈስ ቅዱስን ሥጋ አይደለም። ይህን ስንል ግን መረሳት የሌለበት ነገር አለ። በጊዜ ተዋሕዶ ሥጋ ቃልን ሆኗል። ስለዚህም ሥጋ በቃል የአብ ቃሉ የመንፈስ ቅዱስ ቃሉ ሆኗል። አብ በቃል የሥጋ ልቡ ሆኗል። መንፈስ ቅዱስ በቃል የሥጋ እስትንፋሱ ሆኗል።ቃል ልብን ወደመሆን አይለወጥም። ቃል ቃል ነው። በሦስትነቱ ርባዔ በአንድነቱ ምንታዌ የሌለበት ልዑል እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን ያሉት ሊቃውንት ይህንን ያጎላል። መሥዋእት የሆነው በተዋሐደው ሥጋ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ይህም አንድ ጊዜ በመስቀል ላይ የተደረገ ነው። ። በጊዜ መስቀል መሥዋእት አቅራቢ ሊቀ ካህናትም ወልድ ነው። ወልድ ሊቀ ካህናት መባሉ ሰው በመሆኑ ነው። አብ እና መንፈስ ቅዱስ ሰው አልሆኑም። ስለዚህ በተለየ አካሉ ለአዳም ቤዛ ሆኖ መሥዋእትን ያቀረበው ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ትልቁ ጥያቄ ወደማን አቀረበ የሚለው ነው። መልሱም ወደራሱ ወደ አብ ወደ መንፈስ ቅዱስ ነው። አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አንድ ፈቃድ አንድ ሥልጣን አንዲት ስምረት አንዲት ክሂል አላቸው። ስለዚህ መሥዋእት ተቀባይነት የሦስቱም አንዲት ግብረ ባሕርይ ስለሆነ መሥዋእት ተቀባይነት ለሥላሴ ይሰጣል ማለት ነው። ክርስቶስ ያደረገውን የማዳን ሥራ ዝቅ ማድረግ አይገባም። ስለዚህ ወልድ በመስቀል ተሰቅሎ ከራሱ ጋር ከአብ ጋር ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አስታረቀን እንላለን። ። በተለየ የምንቀበለው ቁርባን የክርስቶስን ሥጋና ደም ነው። ለዚህ ሥጋና ደም ደግሞ አብ ልቡ መንፈስ ቅዱስ እስትንፋሱ ነው።ለዚያም ነው ነፍስ የተለየው መለኮት የተዋሐደው የምንለው። ስለዚህ በተለየ የክርስቶስን ሥጋና ደም ስንቀበል የምናገኘው ድኅነት እና ጸጋ ግን የአብን የወልድን የመንፈስ ቅዱስን ነው። ማዳን መፍጠር የመሳሰሉ ቃላት ሦስቱ አካላት በአንዲት ግብረ ባሕርይ የሚያደርጉት እንጂ በተለየ ለአንዱ አካል የሚሰጥ አይደለም። ። ለቡ (አስተውል) በብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህናቱ መሥዋእት ሊያቀርብ ወደ ደብተራ ሲገባ።መጀመርያ እርሱ ራሱም ከኃጢኣት ንጹሕ ስላልነበረ። ለራሱም ወደ እግዚአብሔር መሥዋእት ካቀረበ በኋላ ነበር። እንደገና መሥዋእቱ ይቀርብ የነበረው በየዓመቱ በየጊዜው ነበር። ክርስቶስን ሊቀ ካህናት ስንለው ግን ከዚህ በተለየ ነው። ምክንያቱም እርሱ ንጹሐ ባሕርይ አምላክ ስለሆነ ምንም ምን በደል የለበትም።ወኮነ ሰብአ ዘእንበለ ኃጢኣት ባሕቲታ እንዲል። ስለዚህ መሥዋእቱን ያቀረበው ለራሱ እጠቀም ብሎ ክብርን ሽቶ አይደለም። እርሱ በባሕርይው ክቡር ነውና። መሥዋእቱን ያቀረበውም መሥዋእቱን የሚቀበል ከእርሱ በላይ ላለ ከእርሱ ለሚበልጥ ሌላ አካል አይደለም። መሥዋእት ተቀባይ (ተወካፌ መሥዋእት) ራሱ ወልድ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ነው እንጂ። ያስታረቀን ከራሱ ጋር ነው።መሥዋእቱም የተሰዋው አንድ ጊዜ በመስቀል ነው። አንድ ጊዜ በመስቀል የቀረበውን መሥዋእት እስከ እለተ ምጽአት እየፈተትን ንሥሐ ገብተን እንቀበለዋለን። እርሱም ድኅነተ ሥጋ ወነፍስ ይሰጠናል። ይቀድሰናል። ስለዚህ ንሥሓ ገብተን ክብር ሥጋውን ክቡር ደሙን ለመቀበል እግዚአብሔር በቸርነቱ ይርዳን። ። ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን። ።

+8
ዚቅ ዘመስቀል-1631514657033.mp33.50 MB

ዓመተ ወንጌላዊ ወንጌላውያን 4 ናቸው።ወንጌልን ለ4 ተካፍለው እንደጻፉት ሁሉ።ዘመናትንም ለ4 ተካፍለው ይመግቡታል።ስለዚህ በሚቀጥለው ዓመት ዘመኑ ዘመነ ማን ነው የሚለውን ለማወቅ ስንፈልግ ዓመተ ዓለሙን ለ4 አካፍለን                ቀሪው 1 ከሆነ ዘመነ ማቴዎስ                ቀሪው 2 ከሆነ ዘመነ ማርቆስ                ቀሪው 3 ከሆነ ዘመነ ሉቃስ                ያለ ቀሪ ከተካፈለ ዘመነ ዮሐንስ ነው።                             መደብና ወንበር ስንል ምን ማለታችን ነው? መባጃ ሐመርና ተውሳክ ስንል ምን ማለታችን ነው? የአጽዋማትና በዓላት አወጣጥ ማወቅ ይፈልጋሉ? ኢየአርግና ኢይወርድ ስንል ምን ማለታችን ነው? ሠርቃት/አሥርቆት ሲባልስ? ስለ ብርሃናትና ነፋሳት አፈጣጠር ምን ያህል ያውቃሉ? ዓመተ ሰማዕታት ምን ማለት ይመስላቹሀል? ስለ ኬክሮስና ኬንትሮስ ምን ያህል እውቀት አሎት? ስለ ባሕረ ሀሳብ ማወቅ ከፈለጉ ...ቻናሉን ይቀላቀሉ ይችን ተጫኑና አዳምጡ 👉 ባሕረ ሐሳብ መግቢያ

ሰባቱ መንጦላይት ወዴት ተጋረዱ ሰባቱ መብራቶች ወዴት ተሰናዱ ታናሽ ሙሽራ ነሽ የአሥራ አምስት ዓመት በአንቺ ላይ ሲፈጸም እንግዳ ሥርዓት አንዴ እየታጠቀ አንዴም እየፈታ ገብርኤል ሲያበስርሽ በፍጹም ሰላምታ ይኩነኒ ብለሽ ስትቀበይው መለኮት እንዴት ነው የተዋሐደው ይህን ባሰብኩ ቁጥር ልቤ ይመሰጣል ከዚህ በላይ ፍቅርስ እንዴት ይገለጣል አዝ = = = = = ሁሉን የሚወስን ባንቺ ተወሰነ ከሦስቱ አካል አንዱ ቃልም ሥጋ ሆነ ስፋት እና ጥበት ሰማይ እና ምድር ባንቺ ተገናኙ ገባሪና ግብር ይህን ባሰብኩ ቁጥር ልቤ ይመሰጣል ከዚህ በላይ ፍቅርስ እንዴት ይገለጣል አዝ = = = = = እንዴት ቢመርጥሽ ነው እንዴት ቢያከብርሽ ትናንት እና ዛሬን ያገናኘብሽ ምልዐትና ወሰን ግዝፈትና ርቀት ባንቺ ተዋሐዱ ፈጣሪና ፍጥረት ይህን ባሰብኩ ቁጥር ልቤ ይመሰጣል ከዚህ በላይ ፍቅርስ እንዴት ይገለጣል አዝ = = = = = ምስጢር ሊመረምር ይወጣል ኀሊና ያልፋል ይሻገራል ከሰማይ ደመና ነገር ግን አይችልም ምንም ቢገሠግሥ በመሰወሪያው ቀኝ ከልጅሽም ሊደርስ ስለዚህ አቅቶት ደክሞት ይመለሳል መልክዐ ውዳሴሽን በአድናቆት ያደርሳል | በዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሀኑ

ከልጅዎ ጋር አጥና ብሎ መጨቃጨቅ ሰልችቶዎታል? ትምህርትን እንዲረዱት ና እንዲወዱት ማድረግ ሲቻል ከልጅዎ ጋር ዘወትር አጥና አታጥና ብሎ መጨቃጨቅ ትርፋ ድካም ና ልጅዎ ትምህርትን የበለጠ እንዲጠላው
ከልጅዎ ጋር አጥና ብሎ መጨቃጨቅ ሰልችቶዎታል? ትምህርትን እንዲረዱት ና እንዲወዱት ማድረግ ሲቻል ከልጅዎ ጋር ዘወትር አጥና አታጥና ብሎ መጨቃጨቅ ትርፋ ድካም ና ልጅዎ ትምህርትን የበለጠ እንዲጠላው ማድረግ ብቻ ነው። አብዛኞቹ ዓለምን የቀየሩ ሳይንቲስቶች በአንድ ወቅት ደካማ ና ሰነፍ የተባሉ ነበሩ🤷 ነገረ ግን አቅማቸውን እንዲጠቀሙ በረዷቸው የግል መምህሮቻቸው በኩል አለምን ጉድ ያስባሉ ሰዎች መሆን ቻሉ።
የኛም ልጆች ይህን ታራክ ለመድገም የሚፈልጉት ትንሽ እገዛ ቢሆንስ?🤔
የረሳነው 1 ነገር የመጀመሪያ ቀን ጥናት 100% ነጻ ነው። በመጀመሪያ ቀን ከልጅዎት ጋር ስለ ፍላጎታቸው ና ስለሚስማማቸው የጥናት ሁኔታ ቀለል ባለ መልኩ ከተነጋገርን በኋላ በቀጣይ ቀን ጥናቱ ይጀምራል። ለተጨማሪ መረጃ : 0980793179 ወይም በቴሌግራም @AhaduTutors 2019ን የሚኮሩበትን ውሳኔ ለልጅዎ በመወሰን ይጀምሩ🥰

የሊቃውንት አምላክ ነፍሳቸውን በገነት ያኑርልን

መጋቤ አእላፍ የኔታ ሄኖክ ወልደ ሚካኤል የተወለዱት እና የተማሩት በዋግ አውራጃ ዛሮታ ተክለ ሐይማኖት ሲሆን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሰፊ አገልግሎት በሚሰጠው በአቋቋም ት
መጋቤ አእላፍ የኔታ ሄኖክ ወልደ ሚካኤል የተወለዱት እና የተማሩት በዋግ አውራጃ ዛሮታ ተክለ ሐይማኖት ሲሆን  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሰፊ አገልግሎት በሚሰጠው በአቋቋም ትምህርት ላይ ሰፊ አሻራ ያኖሩ እንደሆኑ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ይነገራል። @zkretemari @zkretemari ከታላቁ መምህር ክፍሌ ወልደ ጻድቅ ወንበሩን ተረክበው እስከ 1997 ዓ.ም በርካታ ሊቃውንትን ቃለ በረከት ሰጥተው ፣ መምህር አድርገው ለቤተ ክርስቲያናችን ያስረከቡት መጋቤ አእላፍ ሄኖክ ወልደ ሚካኤል ዝክረ ቃል ፣ መዳልወ አልባብ ፣ መልክአ ጉባኤና ሌሎችም ለማኅሌቱ አገልግሎት የሚያስፈልጉ መጻሕፍትን ያሳተሙ ሲሆን በረከታቸው ይደርብንና  መስከረም 7 ቀን 1997 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። ከ 1997 ዓ.ም ጀምሮ በእሳቸው እግር በመተካት መጋቤ አእላፍ የኔታ ክቡር ጥላሁን የምስክር ጉባኤ መምህር በመሆን በርካታ ሊቃውንትን እያፈሩ ይገኛል። @zkretemari @zkretemari ለጓደኞቻችሁ አጋሩ

🌸 ዐዲስ የግእዝ ቋንቋ መጽሐፍ 🌸 ከዚኽ ቀደም ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ፩ እና ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ፪ የተባሉ የግእዝ ቋንቋ መማሪያ መጻሕፍት በመ/ር ግዛቸው ደጀኑ አዘጋጅነት ቀርበዋል። አኹን ደግሞ "
+3
🌸 ዐዲስ የግእዝ ቋንቋ መጽሐፍ 🌸 ከዚኽ ቀደም ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ፩ እና ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ፪ የተባሉ የግእዝ ቋንቋ መማሪያ መጻሕፍት በመ/ር ግዛቸው ደጀኑ አዘጋጅነት ቀርበዋል። አኹን ደግሞ "ዝርዝር ግሶች በመዝሙረ ዳዊት" የተሰኘ 546 ገጾች ያሉት ዐዲስ የግእዝ ቋንቋ መማሪያ መጽሐፍ ተዘጋጅቶ ለአንባብያን በገበያ ላይ ውሏል። ይኽ መጽሐፍ፦ ▪️ ከየአርእስተ ግሶች እና ከአዕማድ       የተውጣጡ ግሶች ይገኙበታል። ▪️ ከ1800 በላይ በንኡስ ርባታ የረቡ       የዋህ ግሶችን ይዟል። ▪️ ከ14,400 በላይ ዝርዝር ግሶች       ከዐማርኛ ትርጕማቸው ጋራ ቀርበዋል። ▪️ የእያንዳንዱ ግስ የአንቀጽ ዐይነት፣       እና የንባብ ዐይነት ከበቂ ማብራሪያ ጋራ       ተካቶበታል። ▪️ ከ418 በላይ ማስረጃዎችን ከመዝሙረ       ዳዊት ያካተተ ልዩ መጽሐፍ ነው። ▬▬▬▬▬ 📚 መጽሐፉን፦ አራት ኪሎ፣ ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ሕንጻ በልዩ መጻሕፍት መደብር (+251901175520) እና በሌሎች መጻሕፍት መደብሮች ያጉኙታል። ለተጨማሪ መረጃ፦ ☎️ +251911727529 ( ኤልያስ) ▬▬▬▬▬ የግእዝን ቋንቋ መማር ከፈለጉ፦ ◦ በቴሌግራም   @geezachew16 ◦ በዩቲዩብ https://www.youtube.com/@geezinberiket 🌸 ዐዲስ የግእዝ ቋንቋ መጽሐፍ 🌸

ዮምሰ ለእሊአየ አበርህ በመስቀልየ ትርጉም፡ ዛሬ ግን ለወገኖቼ በመሰቀሌ/በመስቀሌ አበራላቸዋለሁ

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ስርዓተ ደመራ ዘመስቀል 🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊 ከሁሉ አስቀድሞ ጸሎት ከተደረሰ በኃላ ዲያቆን መስቀሉን ይዞ ምስባክ ይስበክ @EOTCmahlet ይ.ዲ @EOTCmahlet ወወሀብኮሙ ትእምርተ ለእለ ይፈርሁከ፣ ከመ ያምሥጡ እምገጸ ቅሥት፣ ወይድኅኑ ፍቁራኒከ። መዝ ፶፱፤፬ ወንጌል ከተነበበ በኃላ @EOTCmahlet እስመ ለዓለም መስቀል አብርሃ በከዋክብት አሠርገወ ሰማየ፤ እምኲሉሰ ፀሐየ አርአየ፤ መስቀል አብርሃ በከዋክብት አሠርገወ ሰማየ። @EOTCmahlet ✝✝✝ አንገርጋሪ 🕊🕊🕊 ይቤሎሙ ኢየሱስ ለአይሁድ እመኑ ብየ፤ወእመኑ በአቡየ፤ ዮምሰ ለእሊአየ፤አበርሕ በመስቀልየ @EOTCmahlet @EOTCmahlet 🌼🌼🌼🌼🌼 ስርአተ ምልጣን፦ ⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️ መሪ-ሃሌ ሉያ ተመሪ-ሃሌ ሉያ መሪ- ይቤሎሙ ኢየሱስ ተመሪ- ይቤሎሙ ኢየሱስ መሪ- ለአይሁድ ተመሪ-ለአይሁድ መሪ- እመኑ ብየ ተመሪ- እመኑ ብየ መሪ- ወእመኑ በአቡየ ተመሪ- ወእመኑ በአቡየ መሪ- ዮምሰ ለእሊአየ ተመሪ- ዮምሰ ለእሊአየ መሪ- አበርሕ በመስቀልየ ተመሪ- አበርሕ በመስቀልየ @EOTCmahlet ከዚህ በኃላ "ሃሌ ሉያ" ብሎ ዝማሜውን ይዘምማሉ፤ ንሺው ጋር በመሄድ ለሁለት ረዘም ባለ ዜማ ይመራራሉ መሪ- እመኑ ብየ ተመሪ- እመኑ ብየ መሪ- ወእመኑ በአቡየ ተመሪ- ወእመኑ በአቡየ መሪ- ዮምሰ ለእሊአየ ተመሪ- ዮምሰ ለእሊአየ @EOTCmahlet በዝማሜ ሁሉም - አበርሕ በመስቀልየ ሁለተኛ ሰው ከንሺው ጀምሮ ያነሳል እመኑ ብየ፤ወእመኑ በአቡየ፤ ዮምሰ ለእሊአየ በዝማሜ ሁሉም - አበርሕ በመስቀልየ @EOTCmahlet ሶስተኛ ሰው አሁንም እንዲሁ ንሺውን ያነሳል በመቀጠል  "ዮምሰ ለእሊአየ አበርሕ በመስቀልየ "  የሚለው በዝማሜ ተብሎ ከጽናጽል ና ከከበሮ ጋር ይቀርባል @EOTCmahlet አባባሉም፦ በጽፋት የከበሮ አመታት ፩ ጊዜ ዮምሰ ለእሊአየ አበርሕ በመስቀልየ ከዚያ በቁርቋሮ እና በጽፋት ዮምሰ ለእሊአየ....     ፩ዴ በቁርቋሮ ዮምሰ ለእሊአየ....    ፩ዴ በጽፋት አበርሕ በመስቀልየ....     ፩ዴ በቁርቋሮ አበርሕ በመስቀልየ....    ፩ዴ በጽፋት @EOTCmahlet አመላለስ አባባል ፦ ዮምሰ ለእሊአየ /፪ ጊዜ/ አበርሕ በመስቀልየ አበርሕ በመስቀልየ /፪ ጊዜ/ አመላለሱ ተብሎ እንዳለቀ በጽፋት የከበሮ አመታት እመኑ ብየ፤ወእመኑ በአቡየ፤ ዮምሰ ለእሊአየአበርሕ በመስቀልየ ዝግ አባባል እመኑ ብየ እመኑ ብየ ወእመኑ በአቡየ እመኑ ብየ ዮምሰ ለእሊአየ አበርሕ በመስቀልየ ከዚ በኃላ በጽፋት ፦ ይቤሎሙ ኢየሱስ ለአይሁድ እመኑ ብየ፤ወእመኑ በአቡየ፤ ዮምሰ ለእሊአየ፤አበርሕ በመስቀልየ ወረቡ እዚጋ ይባላል፦ "ይቤሎሙ ኢየሱስ"/፪/ ለአይሁድ/፪/ እመኑ ብየ ወእመኑ በአቡየ አበርሕ በመስቀልየ ለእሊአየ/፪/ በቁም አባባል፦ ዮምሰ ለእሊአየ፤አበርሕ በመስቀልየ እስመ ለዓለሙን በቁም በመረግድ እንዲሁም በጽፋት ይሉትና ወረቡን አንስተው ስርዓቱን ይፈጽማሉ 🇪🇹🌼🌼🌼🌼🌼🌼🇪🇹 🌼 @EOTCmahlet 🌼                 🌼 @EOTCmahlet 🌼 🌼 @EOTCmahlet 🌼 🇪🇹🌼🌼🌼🌼🌼🌼🇪🇹       @EOTCmahlet   #ይቀላቀሉ & #ለወዳጅዎ_ሼር_ያርጉ

በቅርቡ tiktok live ላይ መምህር እያሱ የብርሃናተ ዓለም የአቋቋሙ ሊቅ እና ትሁቱ መምህራችን ማኅሌተ ጽጌ ዜማ ጥናት አለን ቀን እና ሰአቱን እናሳውቃለን
በቅርቡ tiktok live ላይ መምህር እያሱ የብርሃናተ ዓለም የአቋቋሙ ሊቅ እና ትሁቱ መምህራችን ማኅሌተ ጽጌ ዜማ ጥናት አለን ቀን እና ሰአቱን እናሳውቃለን

ያሬዳውያን - آمار و تحلیل کانال تلگرام @eotcmahlet