uk
Feedback
🍂 ዲነል ኢስላም 🕌

🍂 ዲነል ኢስላም 🕌

Відкрити в Telegram

♡_ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራ ሰውን አጅር ያህል ያገኛል"(አመላካች የሰሪውን ምንዳ ያገኛል)ﷻ (ﷺ) « ከናንተም ወደ በጎ ነገር የሚጠሩ ፣ በመልካም ስራም የሚያዙ ከክፉ ነገርም የሚከለክሉ ሕዝቦች ይኑሩ ፣ ...» ቁርኣን[ 3:104 ] መወያያ ግሩፓችን ☞ @Dinel_islam_Group ✔ ሀሳብ አስተያየት ካሎት 👉 @DinelIslam1Bot 📩

Показати більше
9 696
Підписники
-224 гОдини
-487 днів
-22530 день

Триває завантаження даних...

Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
червень '26
червень '26
+38
в 0 каналах
травень '26
+10
в 2 каналах
Get PRO
квітень '26
+2
в 2 каналах
Get PRO
березень '26
+13
в 3 каналах
Get PRO
лютий '26
+9
в 0 каналах
Get PRO
січень '26
+19
в 3 каналах
Get PRO
грудень '25
+8
в 1 каналах
Get PRO
листопад '25
+8
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '25
+3
в 1 каналах
Get PRO
вересень '25
+2
в 1 каналах
Get PRO
серпень '25
+38
в 1 каналах
Get PRO
липень '25
+66
в 4 каналах
Get PRO
червень '25
+183
в 2 каналах
Get PRO
травень '25
+6
в 1 каналах
Get PRO
квітень '25
+3
в 4 каналах
Get PRO
березень '25
+640
в 3 каналах
Get PRO
лютий '25
+59
в 1 каналах
Get PRO
січень '25
+176
в 3 каналах
Get PRO
грудень '24
+137
в 0 каналах
Get PRO
листопад '24
+443
в 1 каналах
Get PRO
жовтень '24
+663
в 1 каналах
Get PRO
вересень '24
+673
в 3 каналах
Get PRO
серпень '24
+1 625
в 7 каналах
Get PRO
липень '24
+1 652
в 3 каналах
Get PRO
червень '24
+723
в 2 каналах
Get PRO
травень '24
+828
в 3 каналах
Get PRO
квітень '24
+1 010
в 2 каналах
Get PRO
березень '24
+949
в 3 каналах
Get PRO
лютий '24
+738
в 0 каналах
Get PRO
січень '24
+677
в 3 каналах
Get PRO
грудень '23
+659
в 2 каналах
Get PRO
листопад '23
+550
в 2 каналах
Get PRO
жовтень '23
+739
в 0 каналах
Get PRO
вересень '23
+170
в 0 каналах
Get PRO
серпень '23
+47
в 0 каналах
Get PRO
липень '23
+86
в 0 каналах
Get PRO
червень '23
+137
в 0 каналах
Get PRO
травень '23
+83
в 0 каналах
Get PRO
квітень '23
+76
в 0 каналах
Get PRO
березень '23
+90
в 0 каналах
Get PRO
лютий '23
+51
в 0 каналах
Get PRO
січень '23
+54
в 0 каналах
Get PRO
грудень '22
+83
в 0 каналах
Get PRO
листопад '22
+66
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '22
+77
в 0 каналах
Get PRO
вересень '22
+76
в 0 каналах
Get PRO
серпень '22
+65
в 0 каналах
Get PRO
липень '22
+66
в 0 каналах
Get PRO
червень '22
+33
в 0 каналах
Get PRO
травень '22
+11
в 0 каналах
Get PRO
квітень '22
+49
в 0 каналах
Get PRO
березень '22
+52
в 0 каналах
Get PRO
лютий '22
+11
в 0 каналах
Get PRO
січень '22
+113
в 0 каналах
Get PRO
грудень '21
+106
в 0 каналах
Get PRO
листопад '21
+194
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '21
+314
в 0 каналах
Get PRO
вересень '21
+1 052
в 0 каналах
Get PRO
серпень '21
+1 344
в 0 каналах
Get PRO
липень '21
+1 543
в 0 каналах
Get PRO
червень '21
+2 284
в 0 каналах
Get PRO
травень '21
+950
в 0 каналах
Get PRO
квітень '21
+2 476
в 0 каналах
Get PRO
березень '21
+1 393
в 0 каналах
Get PRO
лютий '21
+828
в 0 каналах
Get PRO
січень '21
+1 741
в 0 каналах
Дата
Залучення підписників
Згадування
Канали
26 червня+2
25 червня+4
24 червня0
23 червня+1
22 червня0
21 червня+3
20 червня+3
19 червня+2
18 червня+2
17 червня+2
16 червня0
15 червня+1
14 червня0
13 червня+2
12 червня+3
11 червня0
10 червня+5
09 червня+1
08 червня0
07 червня+2
06 червня+1
05 червня+2
04 червня+1
03 червня+1
02 червня0
01 червня0
Дописи каналу
ሁሉም ነገሮች ያልፋሉ ... ሁሉም ነገሮች ካለፉ በኋላ ግን ስላለፉበት መንገድ የአንድ ለአንድ ጥያቄና መልስ አለ ! ጀሀነም ሀቅ ነው ! ጀነትም !

2
ጭንቀትና ችግር ከአላህ ውጭ ማንም እንደሌለ ያስተምሩናል ❤️‍
310
3
የሰውን ውዴታ መፈለግ ማለቂያ የሌለው ድካም ነው፤ የአላህን ውዴታ መሻት ግን የሁሉ ነገር ማረፊያ ነው።አላህ ከወደደህ ዓለም በሙሉ እንዲወድህ ያደርጋል🤍
351
4
አላህዬ ከቻናሌ Leave የሚሉትን ቀልብ ስጣቸው 🤲🏼😕
356
5
እኛ በአላህ ፍቃድ ለናንተ ይሆናሉ የምንለውን ወደዚህ በመልቀቅ ለናንተ የተቻለውን እያደረግን አታግዙንም 🥺 👍ቻናላችንን ለሚወዱት ሼር ያድርጉ የአባላችን ቁጥር እንዲጨምር እናንተ ሼር React በማድረግ አበረታቱን 🥺 ! ✨ @Dinel_islam @Dinel_islam ✨
344
6
........ እንዳልተናገሩት ቃል ሸክም የለም ❤️‍🩹
386
7
✿ የቂያማ ቀን የሚሰጥህ መፅሀፍ ደራሲው አንተ ነህ
384
8
#ከዐሹራእ በአጭሩ ምን ተማርክ?" ብትሉኝ፤ የምላችሁ ነገር ቢኖር «አላህን የመያዝን ያህል ከባድ ፈተና የለም» የሚለውን ነው። ሰይድና ሙሳ እኮ ወደ ባሕሩ የገሰገሱት አላህን ብለው ነው፤ ከአላህ ውጭ ሌላ ምንም መተማመኛ አልነበራቸውም። ሰይድና ሑሰይንም ወደ ከርበላ ምድር ያመሩት አላህን ብለው ነው። በአላህ የተመካው ሰይድና ሙሳ ሕዝቦቹን ይዞ ባሕሩን ተሻገረ፤ ይህን ድል «የአላህ እዝነት» የምንለው ነው። እነዚያ የነቢዩ ቤተሰቦች አንድ በአንድ ያለቁባቸው ሰይድና ሑሰይን ግን በዚያ አስጨናቂ ክስተት ላይ እንዲህ አሉ፦ "አላህ ሆይ! ይህንን መከራ በእኛ ላይ የሚያቃልልን ብቸኛው ነገር፤ አንተ የምታየን መሆንህ ነው!" ይህ ደግሞ «የአላህ ፍጹም ፍትሕ» ነው። በእርግጥም ሁላችንም ያለነው በእርሱ እዝነትና በእርሱ ፍትህ መካከል ነው። ታላቁ ደራሲ ነጂብ ማሕፉዝ እንዳለው፦ «ብንድን በእዝነቱ ነው፣ ብንጠፋም በፍትሑ ነው!» በሁሉም ቀናት ከፍና ዝቅ በምንልበትም፣ በምንረበሽበትም፣ ደስ ባለንም ጊዜ ከእርሱ አያርቀን ♥
401
9
#የድል_ቀን አሹራ ቀን (ሙሀረም 10) ላይ የተከሰቱትን ታላላቅ መለኮታዊ ድሎች፦ * የነቢዩላህ ኣደም (ዐ.ሰ)፦ አላህ ንስሐቸውን የተቀበለውና ይቅርታ ያደረገላቸው በዚህ ቀን ነው። * የነቢዩላህ ኑህ (ዐ.ሰ)፦  ታላቁ የጥፋት ውሃ ጎርፍ አብቅቶ፣ እርሳቸውና አማኞች የነበሩበት መርከብ በ“ጁዲ” ተራራ ላይ በሰላም ያረፈችው በዚህ ዕለት ነው። * የነቢዩላህ ኢብራሂም (ዐ.ሰ)፦ ነቢዩላህ ኢብራሂም የተወለዱትም በዚህ ቀን ሲሆን፥ ከናምሩድ እሳት ውስጥ በተጣሉ ጊዜ አላህ እሳቱን ቀዝቃዛና ሰላም (በርደን ወሰላማ) አድርጎ ያዳናቸው በዚህ ዕለት ነው። * የነቢዩላህ ሙሳ (ዐ.ሰ)፦ ፈርዖንና ግፈኛው ሰራዊቱ በባህር ውስጥ የሰጠሙበት፣ ሙሳና የኢሥራኢል ልጆች ግን ባህሩ ተከፍሎላቸው በሰላም የተሻገሩበትና ከባርነት ነፃ የወጡበት ታላቁ የድል ቀን ነው። * የነቢዩላህ ዩሱፍ (ዐ.ሰ)፦ በወንድሞቻቸው ምቀኝነት ጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ ከተጣሉ በኋላ፣ ከአላህ በረከት ጋር ከጉድጓዱ የወጡበት እንዲሁም ከዓመታት በኋላ ከግብፅ እስር ቤት የተፈቱበት ቀን ነው። *የነቢዩላህ ያዕቆብ (ዐ.ሰ)፦ ከልጃቸው ከነቢዩ ዩሱፍ መለየት የተነሳ አልቅሰው ጠፍቶ የነበረው ዓይናቸው (ዕይታቸው) በአላህ ፈቃድ የተመለሰላቸውና ብርሃን ያገኙበት በዚህ ቀን ነው። * የነቢዩላህ አዩብ (ዐ.ሰ)፦ አላህ ሙሉ ጤንነታቸውንና ያጡትን ሀብት የመለሰላቸው በአሹራ ቀን ነው። * የነቢዩላህ ዩኑስ (ዐ.ሰ)፦ በአሳ ነባሪ ሆድ ውስጥ ሆነው ካደረጉት ጥልቅ ዚክርና መማጸን በኋላ፣ አላህ ከአሳው ሆድ በሰላም ያወጣቸውና ወደ ምድር የመለሳቸው በዚህ ዕለት ነው። * የነቢዩላህ ሱለይማን (ዐ.ሰ)፦ አላህ ለነቢዩ ሱለይማን ታላቅ የሆነውንና ማንኛውንም ፍጡር (ሰውን፣ ጂንንና ንፋስን) የሚገዛበትን ንግሥናና ስልጣን የለገሳቸው በዚህ ቀን ነው። *የነቢዩላህ ዳውድ (ዐ.ሰ)፦ አላህ ለነቢዩ ዳውድ ያደረገላቸውን ትልቅ ይቅርታና ወንጀላቸውን የማራቸው ዕለት። * የነቢዩላህ ዒሳ (ዐ.ሰ)፦ ጠላቶቻቸው ሊገድሏቸውና ሊሰቅሏቸው ባሴሩ ጊዜ፣ አላህ ከእነሱ ተንኮል ጠብቆ ወደ ሰማይ ያነሳቸው በዚህ ቀን ነው። * የነቢዩላህ እድሪስ (ዐ.ሰ)፦ አላህ በቁርኣን ውስጥ “ከፍተኛም ስፍራ አነሳነው” (መርየም፡ 57) በማለት የገለጸውና ነቢዩላህ እድሪስን ወደ አራተኛው ሰማይ ከፍ ያደረገበት ዕለት። * የነቢዩላህ ሹዐይብ (ዐ.ሰ)፦ ነቢዩላህ ሹዐይብ ለህዝቦቻቸው ጥመትና መከራ ካላቸው ከባድ ሀዘን የተነሳ አልቅሰው ዓይናቸው ጠፍቶ የነበረ ሲሆን፣ አላህ ሙሉ ዕይታቸውን የመለሰላቸው በዚህ ቀን ነው። * የነቢዩላህ ሁድ (ዐ.ሰ)፦ አላህ አመጸኞቹን የ“ዓድ” ህዝቦች በብርቱና አውዳሚ ንፋስ ባጠፋበት ወቅት፣ ነቢዩ ሁድንና አብረዋቸው የነበሩትን አማኞች ከጥፋት ያዳነበት ዕለት አሹራ ነው። * የነቢዩላህ ሷሊህ (ዐ.ሰ)፦ ታላቋ ግመል (የአላህ ተአምር) በድንጋይ ውስጥ የወጣችበት እንዲሁም ሰሙዶች ግመሏን ካረዱ በኋላ የመጣባቸውን የመብረቅና የጩኸት ቅጣት ተከትሎ ነቢዩ ሷሊህና ሙስሊሞች የዳኑት በዚህ ቀን ነው። * የነቢዩላህ ሎጥ (ዐ.ሰ)፦ የሰዶም (የሎጥ ህዝቦች) ከተማ ከመገልበጧና የድንጋይ ዝናብ ከመዝነቡ በፊት፣ አላህ ነቢዩ ሎጥንና ቤተሰቦቻቸውን ሌሊቱን በሰላም ያስወጣበትና ያዳነበት ዕለት እንደሆነ ይገለጻል። * የነቢዩ ሙሐመድ ﷺ፦  አላህ በቅዱስ ቁርዐን ሱራ ፈትህ (48:2) "አላህ ከወንጀልህ ያለፈውንና የሚመጣውንም ለአንተ ሊምርልህ፣ ጸጋውንም በአንተ ላይ ሊሞላልህ፣ ቀጥተኛውንም መንገድ ሊመራህ (ይህን ታላቅ ድል አጎናጸፈህ)።" በማለት የተናገረለትን ታላቅ የምህረትና የክብር አክሊል ለነቢያችን ﷺ ያረጋገጠበት ዕለት ነው። የተሰውፍ ሊቃውንት (መሻኢኾች) እንደገለጹት፣ አላህ ይህንን ዓለም በውጫዊ ነገሥታት ብቻ ሳይሆን በውስጣዊ አውሊያኦቹ (በመንፈሳዊ መዋቅር ወይም ዲዋን) ያስተዳድራታል። ይህ መዋቅር ደግሞ በየዓመቱ በአሹራ ሌሊትና ቀን ትልቅ ሽግግር ያደርጋል።
452
10
ዛሬ ... እኛም ከተጨነቅንበት ከፈራነው ሁሉ ነጃ እምንወጣበት ቀን ይሁንልን🤲 ያልተነፈሳችሁት በልቦቻችሁ አፍናችሁ እህህህ ካላችሁበት እስር የምትፈቱበት ቀን ይሁን🤲
430
11
365 ቀናት ወንጀል በጥቂት ሰአታት ፆም ይታበሳል✅ ነገ የአሹራ ፆም ነው መፆም እንዳንረሳ‼
512
12
ሶለዋቱሏሂ አለይከ ያ ሁሰይን ! ያ ኢማመል ሙስሊሚን! የሰይደ ሸባቢ አህሊል ጀናህ! አንተ የፅናት ተምሳሌት ! የሀቅና ባጢልም መለያ! አንተ የረሱሉ ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም ሽታ! አንተ እርሳቸው የሚንሰፈሰፉልህ የሚሳሱልህ የአይናቸው ማረፊያ ! የአላህ ሰላምም ሶላትም በአንተ ላይ ይስፈን! አንተና ቤተሰቦችን በከርበላእ በረሀ ላይ ከበው በገደሉ ፤ በተባበሩ ፤ በማለቃችሁ በተደሰቱ ፤ ግድያውን ለማድበስበስ በሄዱ ፤ በካዱህ በሁሉም ጠላቶችህ ላይ የአላህ እርግማን ይውረድባቸው! "ቁርአንና ቤተሰቤን ትቼላችሁ ሂጃለሁ እነርሱን ከተከተላችሁ አትጠሙም " ብለው አደራ የሰጡንን ብረሀኖቻችንን ለመቁረጥ ከርበላእ ላይ በተሰለፉ ሀይሎች ላይ የአላህ እርግማን ይውረድባቸው! ሁሰይን ሆይ አንተና ቤተሰቦችን በውሀ ጥም ቢያስጠሟችሁም ፤ በረሀብ አለንጋ ቢቀጧችሁም ፤ በሺዎች ከበው ቢጨፈጭፏችሁም የጀግንነት ተጋድሏቸው ህያው የሙእማኖች የፅናት ምልክት ሆኖ ይኖራል። አላህም ማጥራትን አጠራችሁ! የጀነት አለቃነትንም አጎናፀፋችሁ! በየሶላታችንም በናንተ ላይ ሶላትን እናወርድ ዘንዳ አላቃችሁ! ያውረደውን ቁርአንም ከናንተ ጋር አስተሳስሮ በውዱ ነብይ አንደበት አስነገረላችሁ! የሀቅና ባጢልም መለያ አደረጋችሁ! ከቤተሰብ ሁሉም እናንተ መረጣችሁ! ሶለዋቱሏሂ አላ አሊ በይቲ ረሱሊላህ! በርግጥ እናንተ ዱኒያን እንጅ ሌላ ምን አጣችሁ!
511
13
የየዚድ ቡችሎች በሰይዱና ሁሴን አሟሟት ላይ ብዙ ማስተባበያን ሲሰጡ እያየን እየታዘብን ነዉ! በመጀመሪያ ደረጃ እናንተን ላላደረገን አሏህ ሹክር እናቀርባለን ምክንያቱም ኢማም ኢብራሒም አነኸዒ እንዲይላሉ:- «ከሑሰይን ገዳዬች መካከል ብሆንና አሏህ ምሮኝንኳ ጀነት ብገባ የነብዬን ፊት ለማየት አፍር ነበር» እኛ ደሞ እናንተ በዘመናችን ዉስጥ በማየታችን አሏህን እና ነቢን ማየት እናፍራለን.. በመጀመሪያ ደረጃ የዚድን ነፃ ለምውጣት በምታረጉት ሂደት ሰይዱና ዐሊን ያለ ሰነድ እና ምስክር መወንጀላቸዉን ከ ሁሰይን ግድያ ጋ በማመሳሰል ለማስተባበል መሞከራችሁ ማንነታችሁን አጣርቶ ለመለየት በቂ ነዉ! 1,የዚድ ሁሰይንን ካላስገደለ ታድያ የእሳቸዉ ጭንቅላት ተቆርጦ እሱ ቤተ መንግሥት ድረስ እንደ ስጦታ ለሱ መቅረቡ ለምን አስፈለገ? በእስልምና ታሪክ መዛግብት (በተለይም በኢማም አል-ጠባሪ፣ በኢብኑ ከሲር እና በሌሎችም የታመኑ የታሪክ ምሁራን ዘንድ) እንደተመዘገበው፣ የሰይዲና ሁሴን (ረ.ዐ) አንገት በካርባላ ምድር ከተቀላ በኋላ በጦር ላይ ተሰክቶ ደማስቆ ወደሚገኘው የየዚድ ቤተመንግስት ተወስዷል። ​ይህ ክስተት በታሪክ ሰነዶች ላይ እንዴት እንደተገለጸ የሚከተሉትን ነጥቦች ማየት ይቻላል፦ የሁሴን የከበረ አንገት በሳህን ተቀምጦ በየዚድ ፊት በቀረበ ጊዜ፣ የዚድ በእጁ በነበረው በትር (ዱላ) የሰይዲና ሁሴንን ከንፈሮችና ጥርሶች እየነካካ ይጫወትበት እንደነበር በሰፊው ተዘግቧል። ​በወቅቱ በቤተመንግስቱ ውስጥ የነበሩ ታዋቂ ሰሃባዎች (ለምሳሌ አቡ በርዝ አል-አስለሚ) ይህንን ድርጊት ሲያዩ በከፍተኛ ቁጣ የዚድን እንዲህ በማለት ገስጸውታል፦ ​"በትርህን አንሳ! በአላህ እምላለሁ፣ ነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ይህንን ከንፈር ሲስሙት ብዙ ጊዜ አይቻለሁ። አንተ የዚድ ሆይ! በቂያማ ቀን ያንተ አማላጅ ኢብኑ ዚያድ ሲሆን፣ የዚህ መኳንንት (የሁሴን) አማላጅ ግን ነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ናቸው!" አሉት። ከዚያም አቡ በርዝ በንዴት ቤተመንግስቱን ጥለው ወጡ። ብዙ ማለት እኮ እንችል ነበር ግን....😭
404
14
Немає тексту...
356
15
#ዓሹራእ … አላህ የአደምን ተውበት የተቀበለበት፣ የኑህን መርከብ ያዳነበት እና ሙሳን ከአምባገነኑ ፊርዓውያን ነጻ ያወጣበት ቀን ነው። ለዚህም ምስጋና ይሆን ዘንድ ቀኑን መጾም ያለፈውን የአንድ ዓመት ወንጀል ያስምራል። በዚህ ዕለት በቤተሰብ ላይ ከተለገሰን ችሮታን ማስፋት ዓመቱን ሙሉ በረካ ያስገኛል። የተለያዩ በዘመናችን ያሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶችና ስልኮች ማኅበራዊ ሚድያ ያመጡትን የቤተሰብ መራራቅ በመተው፣ ቤትን በዚክርና በዱዓዎች ማሳመርና ለወላጆች መልካም መሆን ይገባል። #የኢማም_ሑሰይን (ረዲየላሁ ዓንሁ) ሸሂድ መሆን የነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የልጅ ልጅ የሆኑት ኢማም ሑሰይንና ቤተሰቦቻቸው በከረበላ ምድር በግፍ የተገደሉበት አሳዛኝ ዕለት ማለት ይኸው የዐሹራእ ዕለት ነው። በዚህች ኡማ (ሕዝበ ሙስሊም) ውስጥ በዚህች ዕለት ምን እንደተከሰተ ስናስተውል፤ የበደል፣ የጥጋበኝነት፣ የጥፋትና የጭቆና ኃይል የበላይነትን አግኝቶ ኢማም ሑሰይንና አብረዋቸው የነበሩ ሰባ የሚሆኑትን፣ ከእርሳቸው ጋር ለመሆን እንቢኝ ያሉ ሰዎችን እስኪገድሉ ድረስ። ከእነርሱም ጋር በርካታ ልጆቻቸው፣ ዘመዶቻቸውና ወዳጆቻቸው ያለቁበት ቀን እንደነበር ከታሪክ ገጽ ላይ እናገኛለን። የዚህ ዕለት ክስተትና መጥፎ ፍጻሜ ለዓለማቱ እምብርት ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ቀድሞ ተገልጦላቸው ነበር። እናታችን ኡሙ ሰለማህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ነቢዩን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሑሰይንን በጭናቸው ላይ አስቀምጠው ዓይኖቻቸው በእንባ ሲፈስ አየቻቸውና፦ 'የአላህ መልክተኛ ሆይ! የሚያስለቅስዎት ምንድን ነው?' ስትል ጠየቀቻቸው። እርሳቸውም፦ "ይህ ጂብሪል ነው፤ የእኔ ኡማ ከእኔ በኋላ ይህንን ልጄን እንደሚገድ^ሉት ነገረኝ፤ ከተገደለበት ስፍራ ከከረበላም አፈር አመጣልኝ' አሏት። እርሳቸውም አፈሩን አሳዩአት፤ እሷም ይዛው በጠርሙስ ውስጥ አስቀመጠችው።" የከረበላእ ክስተት ላይ ነበር ኡሙ ሰለማ ጉዳዩን አስታውላ ይህን ንግግራቸውን ያገናኘችው። የኢማም #ሑሰይን ጉዞ እና ምርጫ እነዚያ ውብ የኺላፋ ራሺዳ ዘመናት አልፈው የቂም፣ የቅናት፣ የሥልጣን ጥምና የሴራ ፈተናዎች በኡማው ላይ መጡ። ከኢራቅ ሕዝቦች (በኋላ ላይ የከዱትና የገደሉት) ደብዳቤዎችና መልእክቶች በደረሱት ጊዜ ሑሰይን (ረዲየላሁ ዐንሁ) ከመካ ወጣ እርሳቸውም፦ 'ከአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሰምቻለሁ፤ ከእኔ ቤተሰብ የሆነ አንድ ሰው በእርሱ ምክንያት ሐረም (የመካ ክልል) ይደፈራል፤ እኔ ያ ሰው መሆን አልፈልግም፣ ከሐረም ክልል መውጣቴ ለእኔ የተሻለ ነው' አሉ። እርሳቸው እንደሚገደሉና ሸሂድ (ሰማዕት) እንደሚሆኑ ያውቁ ነበር። እርሳቸውን ጨምሮ አብረዋቸው የነበሩ አንጋፋ ሰሐቦች የዚድን የተቃወሙትም ለነብዩ ኡመት የማይገባ መሪ በማለት ነበር። በከርበላ ኢማም ሑሰይንን ሊወ^ጋ የተዘጋጀው ጦር ሊዋጋቸው በመጣ ጊዜ ሑሰይን እንዲህ አሏቸው፦ 'ደብዳቤ የጻፋችሁልኝ ለዚህ ነበርን? ምን ሆናችኋል?' አሏቸው። እነርሱም፦ 'እኛ አንተን መግ^ደል እንጂ ሌላ አንፈልግም' አሉት። እርሳቸውም ሦስት አማራጮችን አቀረቡላቸው፦ 'ወይ የመጣሁበት እንድመለስ ተዉኝ፣ ወይም ወደ ገዢው የዚድ ዘንድ ወስዳችሁ በቀጥታ እንድንነጋገር አድርጉኝ፣ ካልሆነም ወደ አንዱ የድንበር ዘብ ስፍራ ሄጄ በአላህ መንገድ ላይ እንድዋጋ ፍቀዱልኝ' አሏቸው። እነርሱ ግን 'አንዱንም አንቀበልም!' አሉ። በዚህ ጊዜ ሑሰይን አብረዋቸው ለነበሩት ሰዎች፦ 'እነዚህ ሰዎች እኔን ብቻ ነው የሚፈልጉት፤ መሄድ የሚፈልግ ሰው አሁን ይሂድ' አሏቸው። ነገር ግን ታማኞቹና እውነተኛዎቹ ጓደኞቻቸው፦ 'በአላህ እንምላለን! ከነቢያችን የልጅ ልጅ አንለይም፤ ከአንተ ጋር እንገደላለን፣ ከአንተ ጋር እንሞታለን!' አሉ። እነዚያ ሰባ የሚያህሉ ሰዎች አንድ በአንድ ተገ^ደሉ።" ከተገ^ደሉት መካከል ትንሹ ልጃቸው ዓብዱላህ ኢብኑ ሑሰይን ይገኝበታል። ሑሰይን ሕፃኑን ውሃ ሊያጠጡት ሲያነሱት፣ አንድ ቀስት መጥቶ የሕፃኑን አንገት መታውና ሕፃኑ በእጃቸው ላይ ሞተ። #ሑሰይን በዚህ ጊዜ፦ "አላህ ሆይ! ይህንን መከራ በእኛ ላይ የሚያቃልልን ነገር ማለት አንተ የምታየን መሆንህ ነው!' አሉ።" የጠላት ጦር ውሃ ሲያስፈልገው ሑሰይን ካላቸው ውሃ እንዲጠጡ አዘው ነበር፤ ጠላቶቹ ግን ውሃውን በተቆጣጠሩ ጊዜ 'ሑሰይን ሆይ! በጥም ሙት እንጂ አንድ ጠብታ ውሃ አናጠጣህም!' አሏቸው። ከመላው ጦር የተረፈው አንድ ልጃቸው ዓሊ ኢብኑ ሑሰይን (ዘይነል ዓቢዲን) ብቻ ነበር። ሲገደልም ወደ ቅዱስ አስከሬኑ መጥተው ክቡር አካሉን ለመቀየር ፈረሶች በላዩ ላይ እንዲረግጡ አዘዝውም ነበር፡፡ ይህ ሁሉ ክስተት ለነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ቀድሞ ቀርቦላቸው ነበር፤ ነገር ግን አላህ የወሰነውን ቀደር እንዲቀይር አልለመኑም፤ ምክንያቱም እርሳቸው በአላህ ጥበብና ሑሰይን በአላህ ዘንድ ስለሚያገኘው ክብርና የጀነት ወጣቶች መሪ ስለመሆኑ ጠንቅቀው ያውቁ ነበር። ይህ ክስተት የዚህችን ዓለም ተራነትና በእውነት ላይ መጽናትን ያስተምረናል። ይህን ዕለት ማሰብ በራሱ የሚፈጥረው ሐዘን ከባድ ቢሆንም ውስጥን የሚደማ ነገር ቢኖረውም የአላህን ጥበብ በማሰብና የፈተና በራፍን ለመዝጋት በመማር የኢማም ሑሰይንን ጀግንነትና የተከተሉትን አብሮ የመዋደቅ ጽናት በማውሳት ብቻ ማለፉ ይበቃል ይመስለኛል። የኢማም ሑሰይን ወንድም ኢማም ሐሰን ቢን ዐለይ ለኡመቱ መዋሃድ ሥልጣናቸውን ለሙዓዊያ ሰጥተው የኩፋንና የሻምን ሕዝብ እንዳደረጉት ኹሉ በቤተሰቦቻቸው በረከት አላህ ዳግም ኡመቱን ያዋህድልን። አሚይንን
413
16
📍የዓሹራእ ቀን፡ የደስታ እንጂ የሐዘን ቀን አይደለም በዓሹራእ ቀን ለቤተሰብ ለየት ባለ መልኩ ሰፋ አድርጎ ማውጣት፣ ማንበሽበሽና እነሱን ማስደሰት፣ እንዲሁም ቀኑን መጾም በአራቱም የፊቅህ መዝሐቦች ሊቃውንት ስምምነት የተወደደ (ሙስተሐብ) ሱና ነው። ይህ የደስታ መገለጫ ነው እንጂ የሐዘን ምልክት፣ የለቅሶ ወይም የሐዘን መድረክ አይደለም። የዓሹራእ ቀን የደስታ እንጂ የሐዘን ቀን አይደለም! የነቢዩ (ﷺ) ፈለግ በስሜት የሚነቃነቅ ወይም በሐዘን የሚፈርስ አይደለም። ነቢዩን (ﷺ) የሚያስደስታቸው ነገር ቤተሰባቸውንም ያስደስታቸዋል፤ እንዲያውም እነርሱ የእርሳቸውን ሱና በመጠበቅና ሕያው በማድረግ ረገድ ከማንም በላይ ተገቢዎችና ከፍተኛ ትኩረት ሰጪዎች ናቸው። በሰይዳችን ኢማም ሑሰይን (ረዐ) ላይ የደረሰው ታላቅ በደልና አስከፊ ወንጀል፣ በእያንዳንዱ እውነተኛ አማኝ ልብ ውስጥ ጥልቅ ሐዘን የፈጠረ ነው። ይህ ሐዘንም በህይወት እስካለ ድረስ ከልቡ አይለይም። የሰይዳችን ሑሰይንን መገደል ያላሳዘነውና በደረሰበት መከራ ልቡ ያልተነካ ሰው፣ ልቡ የታመመ፣ ድርቀት ያለበትና ሊሰወር የማይችል የጥላቻ በሽታ ያደረበት ነው። ይሁን እንጂ ይህ እውነተኛ ሐዘን እንደ ቋሚ መፈክር መወሰድ የለበትም፤ እንዲሁም እንደ አንዳንድ አንጃዎችአ በየዓመቱ የሚታደስ የሐዘን ስርዓት ሊሆን አይገባውም። ሃይማኖታችን ደስታን የምናድስበት እንጂ ለቅሶንና ዋይታን የምናከርርበት አይደለም። በሸሪዓ የተፈቀደው ሐዘን ቦታው ልብ እንጂ ውጫዊ መድረኮች አይደሉም። መገለጫውም ክብር እንጂ ሁከትና ግርግር አይደለም ። ሰዪዱና አል-ሑሰይንን በእውነት የወደደ ሰው የአያቱን (የነቢዩን ﷺ) ሱና ይጠብቃል። እውነተኛ የመከራ መፅናኛና የልብ መድኃኒትም ያለው በዚህ ውስጥ ነው። 👉 የዓሹራእ ቀን፡ የደስታ እንጂ የሐዘን ቀን አይደለም። 👉 ዓሹራእ፡ በለጋስነት የምንታደስበት፣ በሱና የምንጽናናበት ቀን። 👉 የዓሹራእ እውነት፦ ከሐዘን ግርግር ይልቅ በሱና መጽናናት።
454
17
ዛሬ የተጀመረው የ #ዓሹራእ ጾም እንዲሁ ጾም ብቻ አይደለም። ዓሹራእ በሕይወታችን ሊቀየር አይችልም ብለን የምናስበውን ማንኛውም ነገር አላህ ሊቀይረው ቻይ እንደኾነ የምናስብበት ዕለት ነው። በጣም አስቸጋሪ ከሚባል ሕይወት ወደ ምርጥ ጅማሮ መቀየርን የምንዘክርበት ነው። ሰይድና ሙሳ ወደ ባሕሩ ሲገሰግሱ ተከታዮቻቸው "አረ ወዴት ነው የምንሄደው?" በሚል ስጋት ውስጥ ሳሉ ሰይድና ሙሳ ግን ከአላህ የተገባላቸውን የ መመራት ቃልኪዳን በልባቸው ይዘው ባህሩ ጋር ተጠጉ ባህሩም እርሳቸውንና ሕዝባቸውን ለማዳን ሰበብ ሲኾን ውሃው ልክ እንደ ትልቅ የተራራ ቋጥኝ ቀጥ ብሎ ቆመላቸው በውሃው መሀልም ደረቅ የብስን አገኝተው ተሻገሩ። አላሁ አክበር ♥ ይህን ፈትህና ስኬት ነው የምናስበው ♥ ዱንያዊና አኺራዊ ሐጃዎቻችን ብዙ ናቸው። በዚህ ቀን (ዓሹራእ) አይነት የተገኘውን አይነት ኃያል የኾነ ድል (ፈረጃ) ይረዝቀና።
459
18
ነቢዩላህ ሙሳ عليه السلام ከአንባገነኑ ፈርዖን ጋር ያደረጉት እልህ አስጨራሽ ግብግብ እየከበደ መጣ። በመጨረሻም ፊርዓውን ሙሳና ተከታዬቹን ሊዋጋ ሰራዊቱን አሰማራ፤ ነብዩላህ ሙሳም የአሹራ ቀን ላይ በአላህ ትዕዛዝ ህዝቦቻቸውን ይዘው ወደ ቀይ ባህር ጥግ ነጎዱ። የፈርዖን ሰራዊቶች ወደ ሙሳና ተከታዬቻቸው ሲቀርቡ የሙሳ ሷሂቦች ድንጋጤ እና ፍርሃት ወረሳቸው! .. "إنا لمدركون: እኛ የፈርዖን ሰዎች የሚደርሱብን ነን።» በማለት ጭንቀታቸውን ተናዘዙ። የዚህን ጊዜ ሙሳ ድንቅ መልስ መለሱ! በልጅነታቸው እናታቸው ጌታዋን ተወክላ ወንዝ ውስጥ የወረወረችው ልጅ፤ ፈቂር በኾኑበት (ምንም በሌላቸው ሰአት) ጌታቸውን ተማምነው ወደሱ ብቻ የተጣሩት ወጣት፤ እዚህ ቦታ ላይም አላህ ላይ ያላቸውን እምነት አሳዩ። እሱ ላይ ያላቸውን ፍፁም መተማመን አረጋገጡ። إِنَّ مَعِيَ رَبِّي سَيَهْدِينِ 🩵 (ሙሳ) «ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡ [ሱረቱል አሹዓራ: 63] ይህ መተማመንም ባህሩን እንዲከፍል አደረገው! ድል የነብዩላህ ሙሳ ሆነ። አንባገነኑ ፈርዖን'ም ህይወቱ አከተመች። ሰጠመ! ረሱለላህ ﷺ ወደ መዲና ሲገቡ አይሁዶች ይህንን ቀን ሲፆሙ ይመለከታሉ፤ ከዛም ለምን እንደሚፆሙ ሲጠይቋቸው ነብዩላህ ሙሳ ድል ያደረገበት እንደሆነ ነገሯቸው። ሸፊዒምﷺ: "ከነሱ በላይ እኛ ለሙሳ የቀረብን ነን።" በማለት የአሹራ ቀን፤ ከበፊቱ ያለውን እና የሚከተለውን መፆም እንደሚወደድ፤ ትሩፋቱም ትልቅ እንደሆነ አወጁ! 🩵 ያለፈው ዓመት ወንጀል የሚፋቅበት ሌላ እጣ! 😊 አሹራ ካስተማረኝ ነገር አንዱ አላህ ከኛ ጋር ነው ብለን ሙሉ እምነታችንን ስንሰጠው እና ስንተማመንበት ብዙ ድሎችን እንደሚሰጠን ነው። ሐቢበላህ ﷺ ከውዱ ጓደኛቸው ጋር ወደ መዲና በነበራቸው ጉዞ ላይ ሙሽሪኮች እየደረሱባቸው መሆኑን ሲያውቁ ጋሩ ሰውር የሚባል ጠባብ ዋሻ ውስጥ ገቡ! አባበክር በእባብ ከመነደፋቸው በላይ ሸፊዒ ﷺ አንድ ነገር እንዳይሆኑ ሰጉ፤ እንዳያዩን በሚል ፍርሃት ይንቀጠቀጡ ጀመር። የዚህን ጊዜ ውዱ መልዕክተኛው ﷺ ሷሂባቸውን አላህ ከነሱ ጋር እንደሆነ አበሸሩት! «ያ አባበክር! አትዘን አላህ ከኛ ጋር ነው።» አላቸው። ልክ ነብዩላህ ሙሳ ህዝባቸው በፍርሃት የፈርዖን ሰራዊቶች ሊደርሱብን ነው ሲሉ «ጌታዬ ከኔ ጋር ነው። በእርግጥ ይመራኛል!» ሲል ባህሩን እንደተከፈለላቸው ሁሉ ሸፊዒ ﷺ ለተጨናነቀው ጓደኛቸው «ላ ታህዘን ኢነላሃ ማዕና» ብለው ሲያረጋጉት በአላህ ጥበብ ምክንያት የሸረሪት ድር እንዲከልላቸው አደረገ። «ሁለቱም በዋሻው ሳሉ ለጓደኛው አትዘን አላህ ከእኛ ጋር ነውና ባለ ጊዜ አላህም መረጋጋትን በእርሱ ላይ አወረደ፡፡ ባላያችኋቸውም ሰራዊት አበረታው፡፡ የእነዚያንም የካዱትን ሰዎች ቃል ዝቅተኛ አደረገ፡፡ የአላህም ቃል ለእርሷ ከፍተኛ ናት፡፡ አላህም አሸናፊ ጥበበኛ ነው፡፡» [ሱረቱል ተውባ:40] የሚለው አያህ ወረደ። አሹራ! አላህ ላይ በኖረ ፍፁም ተወኩል የተሰጠ ድል! አላህ ከኔ ጋር ነው በሚል የኢማን ጥግ የተሰጠ ሽልማት ነው። አሹራ አሳዛኝ ክስተት የተከሰተበት ቀን'ም ነው። የሐቢበላህ ﷺ ተወዳጅ የልጅ ልጅ ሁሰይን ኢብን ዓሊይ ረሱሊ ﷺ በአንድ ወቅት «اللهم إني أُحبه فأَحبَّه، وأَحبَّ من يحبه» «አላህ ሆይ! ወድጄዋለው እና ውደደው፤ እሱንም የሚወዱትን ውደድ።» በማለት ፍቅራቸውን እና ስስታቸውን ይገልፁለት የነበረው እጅጉኑ የሚወዱት ሁሰይን ከርበላ ላይ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገ*ደሉበት ቀን'ም ነው። ሁሌም ሲታሰብ ህመም የሆነ ክስተት፣ ዘመናትን የተሻገረ ቁስል... የአላህ ቁ*ጣና እር*ግማን በኢማም ሁሰይን ገዳ*ዮችና መጥፎ አሳቢዮች ላይ ይውረድ 💔 አላህ በእርግጥ ከኛ ጋር ነው። እሱ ላይ የሚኖር ፅኑ እምነት ያድናል። በተዓምሩ ከጠላት ይከላከልልናል። ነቢዩላህ ሙሳ ተልዕኮው ሲሰጣቸው እና ተቀብለው ወደ ቀይ ባህር ሲተሙ መቼም ለጠላት የማይተዋቸው ጌታ ከጎናቸው እንደሆነ በጥልቅ ስላመኑ ነው። እኛስ አሹራ ምን አስተማረን? እኔ በበኩሌ ጌታችን በየትኛውም ከባድ ሁኔታ እንደማይተወን ተምሬያለሁ ምክንያቱም አላህ ሙሉ ውክልናውን ለሱ ከሚሰጡት ጋር ነውና። አላህ ከማን ጋር እንደሚሆን ቁርኣን ላይ ከተጠቀሱት የተወሰኑት: • إِنَّ اللَّهَ مَعَ الَّذِينَ اتَّقَوا وَّالَّذِينَ هُم مُّحْسِنُونَ : «አላህ ከእነዚያ ከሚፈሩትና ከእነዚያም እነሱ መልካም ሠሪዎች ከኾኑት ጋር ነውና፡፡» 🩵 • وَهُوَ مَعَكُمْ أَيْنَ مَا كُنتُمْ ۚ وَاللَّهُ بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ «እርሱም የትም ብትኾኑ ከእናንተ ጋር ነው፡፡ አላህም የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነው፡፡» • إِنَّ اللَّهَ مَعَ الصَّابِرِينَ «አላህ (በእርዳታው) ከታጋሾች ጋር ነውና፡፡» 🩵 • أَنَّ اللَّهَ مَعَ الْمُؤْمِنِينَ «አላህም ከምእምናን ጋር ነው፡፡» አሹራ ፆሙ ያለፈውን አመት ወንጀል የሚያስምር ቀን ነው። ሰይዲና ሁሰይን ኢብን ዓሊይ ላይ እንደተፈፀመው አሳዛኝ ክስተት የምናዝንበት እና የምናስበውም ቀን ጭምር ነው። ልክ ለረሱሊ ﷺ የበድር ጦርነት ድል እና ሐዘን የተቀላቀለበት ቀን እንደሆነው ሙሽሪኮች ላይ ድል ስላደረጉ ተደሰቱ፤ በተመሳሳይ ቀን ልጃቸው ሩቀያ ወደ አኺራ በመሻገርዋ ምክንያት ሐዘን ውስጥ ገቡ። የህይወት ፍልስፍና እንዲህ ነው። እኛም በነቢዩላህ ድል እንደምንደሰተው ሁሉ በረሱለላህ ውድ የልጅ ልጅ አሳዛኝ ግድ*ያ ደግሞ እናዝናለን። ድል እንዳለው ሁሉ ከባድ ሐዘን'ም ይኖራል! በበኩሌ አሹራ ያስተማረኝ ይህ ነው። መልካም የኢባዳ ጊዜ!😊
490
19
🌅ነገ ረቡዕን እና ሐሙስን የዓሹራ ፆም ናቸው መፆም እንዳትረሱ ሌላውንም እናስታውስ 😊 አመላካች የሰሪውን ምንዳ ያገኛል !
508
20
አቡ ዑስማን አን‐ነህዲይ እንዲህ ይላሉ: ‐ «[ሰለፎች] ሦስቱን ዐስሮች ያከብሩ ነበር: ‐ ⚀ ዐስሩን የመጨረሻ የረመዳን ቀናት፤ ⚁ የመጀመሪያዎቹን ዐስር የዙል‐ሒጃ ቀናት፤ ⚂ የሙሐረም ወርን የመጀመሪያ ዐስር ቀናት።» : ውዶቼ የዛሬ ውሎ ሙሐረም 8ኛው ቀን ነበር። ነገ ታሱዓእ ነው። የአላህ መልክተኛ [ሠለላሁ ዐለይሂ ወሰለም] በመጪው ዓመት በህይወት ካለሁ ከዐሹራእ በፊት እፆመዋለሁ ብለው ነይተውት የነበረው ቀን ነው። የፊታችን ሐሙስ ዐሹራእ ነው። እኛም እንጹም። ቤተሰቦቻችንንም እናስታውስ! ባረከላሁፊኩም!
507