es
Feedback
🍂 ዲነል ኢስላም 🕌

🍂 ዲነል ኢስላም 🕌

Ir al canal en Telegram

♡_ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራ ሰውን አጅር ያህል ያገኛል"(አመላካች የሰሪውን ምንዳ ያገኛል)ﷻ (ﷺ) « ከናንተም ወደ በጎ ነገር የሚጠሩ ፣ በመልካም ስራም የሚያዙ ከክፉ ነገርም የሚከለክሉ ሕዝቦች ይኑሩ ፣ ...» ቁርኣን[ 3:104 ] መወያያ ግሩፓችን ☞ @Dinel_islam_Group ✔ ሀሳብ አስተያየት ካሎት 👉 @DinelIslam1Bot 📩

Mostrar mĂĄs
9 709
Suscriptores
-324 horas
-437 dĂ­as
-23330 dĂ­as

Carga de datos en curso...

Atraer Suscriptores
junio '26
junio '26
+32
en 0 canales
mayo '26
+10
en 2 canales
Get PRO
abril '26
+2
en 2 canales
Get PRO
marzo '26
+13
en 3 canales
Get PRO
febrero '26
+9
en 0 canales
Get PRO
enero '26
+19
en 3 canales
Get PRO
diciembre '25
+8
en 1 canales
Get PRO
noviembre '25
+8
en 0 canales
Get PRO
octubre '25
+3
en 1 canales
Get PRO
septiembre '25
+2
en 1 canales
Get PRO
agosto '25
+38
en 1 canales
Get PRO
julio '25
+66
en 4 canales
Get PRO
junio '25
+183
en 2 canales
Get PRO
mayo '25
+6
en 1 canales
Get PRO
abril '25
+3
en 4 canales
Get PRO
marzo '25
+640
en 3 canales
Get PRO
febrero '25
+59
en 1 canales
Get PRO
enero '25
+176
en 3 canales
Get PRO
diciembre '24
+137
en 0 canales
Get PRO
noviembre '24
+443
en 1 canales
Get PRO
octubre '24
+663
en 1 canales
Get PRO
septiembre '24
+673
en 3 canales
Get PRO
agosto '24
+1 625
en 7 canales
Get PRO
julio '24
+1 652
en 3 canales
Get PRO
junio '24
+723
en 2 canales
Get PRO
mayo '24
+828
en 3 canales
Get PRO
abril '24
+1 010
en 2 canales
Get PRO
marzo '24
+949
en 3 canales
Get PRO
febrero '24
+738
en 0 canales
Get PRO
enero '24
+677
en 3 canales
Get PRO
diciembre '23
+659
en 2 canales
Get PRO
noviembre '23
+550
en 2 canales
Get PRO
octubre '23
+739
en 0 canales
Get PRO
septiembre '23
+170
en 0 canales
Get PRO
agosto '23
+47
en 0 canales
Get PRO
julio '23
+86
en 0 canales
Get PRO
junio '23
+137
en 0 canales
Get PRO
mayo '23
+83
en 0 canales
Get PRO
abril '23
+76
en 0 canales
Get PRO
marzo '23
+90
en 0 canales
Get PRO
febrero '23
+51
en 0 canales
Get PRO
enero '23
+54
en 0 canales
Get PRO
diciembre '22
+83
en 0 canales
Get PRO
noviembre '22
+66
en 0 canales
Get PRO
octubre '22
+77
en 0 canales
Get PRO
septiembre '22
+76
en 0 canales
Get PRO
agosto '22
+65
en 0 canales
Get PRO
julio '22
+66
en 0 canales
Get PRO
junio '22
+33
en 0 canales
Get PRO
mayo '22
+11
en 0 canales
Get PRO
abril '22
+49
en 0 canales
Get PRO
marzo '22
+52
en 0 canales
Get PRO
febrero '22
+11
en 0 canales
Get PRO
enero '22
+113
en 0 canales
Get PRO
diciembre '21
+106
en 0 canales
Get PRO
noviembre '21
+194
en 0 canales
Get PRO
octubre '21
+314
en 0 canales
Get PRO
septiembre '21
+1 052
en 0 canales
Get PRO
agosto '21
+1 344
en 0 canales
Get PRO
julio '21
+1 543
en 0 canales
Get PRO
junio '21
+2 284
en 0 canales
Get PRO
mayo '21
+950
en 0 canales
Get PRO
abril '21
+2 476
en 0 canales
Get PRO
marzo '21
+1 393
en 0 canales
Get PRO
febrero '21
+828
en 0 canales
Get PRO
enero '21
+1 741
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
24 junio0
23 junio+1
22 junio0
21 junio+3
20 junio+3
19 junio+2
18 junio+2
17 junio+2
16 junio0
15 junio+1
14 junio0
13 junio+2
12 junio+3
11 junio0
10 junio+5
09 junio+1
08 junio0
07 junio+2
06 junio+1
05 junio+2
04 junio+1
03 junio+1
02 junio0
01 junio0
Publicaciones del Canal
📍የዓሹራእ ቀን፡ የደስታ እንጂ የሐዘን ቀን አይደለም በዓሹራእ ቀን ለቤተሰብ ለየት ባለ መልኩ ሰፋ አድርጎ ማውጣት፣ ማንበሽበሽና እነሱን ማስደሰት፣ እንዲሁም ቀኑን መጾም በአራቱም የፊቅህ መዝሐቦች ሊቃውንት ስምምነት የተወደደ (ሙስተሐብ) ሱና ነው። ይህ የደስታ መገለጫ ነው እንጂ የሐዘን ምልክት፣ የለቅሶ ወይም የሐዘን መድረክ አይደለም። የዓሹራእ ቀን የደስታ እንጂ የሐዘን ቀን አይደለም! የነቢዩ (ﷺ) ፈለግ በስሜት የሚነቃነቅ ወይም በሐዘን የሚፈርስ አይደለም። ነቢዩን (ﷺ) የሚያስደስታቸው ነገር ቤተሰባቸውንም ያስደስታቸዋል፤ እንዲያውም እነርሱ የእርሳቸውን ሱና በመጠበቅና ሕያው በማድረግ ረገድ ከማንም በላይ ተገቢዎችና ከፍተኛ ትኩረት ሰጪዎች ናቸው። በሰይዳችን ኢማም ሑሰይን (ረዐ) ላይ የደረሰው ታላቅ በደልና አስከፊ ወንጀል፣ በእያንዳንዱ እውነተኛ አማኝ ልብ ውስጥ ጥልቅ ሐዘን የፈጠረ ነው። ይህ ሐዘንም በህይወት እስካለ ድረስ ከልቡ አይለይም። የሰይዳችን ሑሰይንን መገደል ያላሳዘነውና በደረሰበት መከራ ልቡ ያልተነካ ሰው፣ ልቡ የታመመ፣ ድርቀት ያለበትና ሊሰወር የማይችል የጥላቻ በሽታ ያደረበት ነው። ይሁን እንጂ ይህ እውነተኛ ሐዘን እንደ ቋሚ መፈክር መወሰድ የለበትም፤ እንዲሁም እንደ አንዳንድ አንጃዎችአ በየዓመቱ የሚታደስ የሐዘን ስርዓት ሊሆን አይገባውም። ሃይማኖታችን ደስታን የምናድስበት እንጂ ለቅሶንና ዋይታን የምናከርርበት አይደለም። በሸሪዓ የተፈቀደው ሐዘን ቦታው ልብ እንጂ ውጫዊ መድረኮች አይደሉም። መገለጫውም ክብር እንጂ ሁከትና ግርግር አይደለም ። ሰዪዱና አል-ሑሰይንን በእውነት የወደደ ሰው የአያቱን (የነቢዩን ﷺ) ሱና ይጠብቃል። እውነተኛ የመከራ መፅናኛና የልብ መድኃኒትም ያለው በዚህ ውስጥ ነው። 👉 የዓሹራእ ቀን፡ የደስታ እንጂ የሐዘን ቀን አይደለም። 👉 ዓሹራእ፡ በለጋስነት የምንታደስበት፣ በሱና የምንጽናናበት ቀን። 👉 የዓሹራእ እውነት፦ ከሐዘን ግርግር ይልቅ በሱና መጽናናት።

2
ዛሬ የተጀመረው የ #ዓሹራእ ጾም እንዲሁ ጾም ብቻ አይደለም። ዓሹራእ በሕይወታችን ሊቀየር አይችልም ብለን የምናስበውን ማንኛውም ነገር አላህ ሊቀይረው ቻይ እንደኾነ የምናስብበት ዕለት ነው። በጣም አስቸጋሪ ከሚባል ሕይወት ወደ ምርጥ ጅማሮ መቀየርን የምንዘክርበት ነው። ሰይድና ሙሳ ወደ ባሕሩ ሲገሰግሱ ተከታዮቻቸው "አረ ወዴት ነው የምንሄደው?" በሚል ስጋት ውስጥ ሳሉ ሰይድና ሙሳ ግን ከአላህ የተገባላቸውን የ መመራት ቃልኪዳን በልባቸው ይዘው ባህሩ ጋር ተጠጉ ባህሩም እርሳቸውንና ሕዝባቸውን ለማዳን ሰበብ ሲኾን ውሃው ልክ እንደ ትልቅ የተራራ ቋጥኝ ቀጥ ብሎ ቆመላቸው በውሃው መሀልም ደረቅ የብስን አገኝተው ተሻገሩ። አላሁ አክበር ♥ ይህን ፈትህና ስኬት ነው የምናስበው ♥ ዱንያዊና አኺራዊ ሐጃዎቻችን ብዙ ናቸው። በዚህ ቀን (ዓሹራእ) አይነት የተገኘውን አይነት ኃያል የኾነ ድል (ፈረጃ) ይረዝቀና።
127
3
ነቢዩላህ ሙሳ عليه السلام ከአንባገነኑ ፈርዖን ጋር ያደረጉት እልህ አስጨራሽ ግብግብ እየከበደ መጣ። በመጨረሻም ፊርዓውን ሙሳና ተከታዬቹን ሊዋጋ ሰራዊቱን አሰማራ፤ ነብዩላህ ሙሳም የአሹራ ቀን ላይ በአላህ ትዕዛዝ ህዝቦቻቸውን ይዘው ወደ ቀይ ባህር ጥግ ነጎዱ። የፈርዖን ሰራዊቶች ወደ ሙሳና ተከታዬቻቸው ሲቀርቡ የሙሳ ሷሂቦች ድንጋጤ እና ፍርሃት ወረሳቸው! .. "إنا لمدركون: እኛ የፈርዖን ሰዎች የሚደርሱብን ነን።» በማለት ጭንቀታቸውን ተናዘዙ። የዚህን ጊዜ ሙሳ ድንቅ መልስ መለሱ! በልጅነታቸው እናታቸው ጌታዋን ተወክላ ወንዝ ውስጥ የወረወረችው ልጅ፤ ፈቂር በኾኑበት (ምንም በሌላቸው ሰአት) ጌታቸውን ተማምነው ወደሱ ብቻ የተጣሩት ወጣት፤ እዚህ ቦታ ላይም አላህ ላይ ያላቸውን እምነት አሳዩ። እሱ ላይ ያላቸውን ፍፁም መተማመን አረጋገጡ። إِنَّ مَعِيَ رَبِّي سَيَهْدِينِ 🩵 (ሙሳ) «ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡ [ሱረቱል አሹዓራ: 63] ይህ መተማመንም ባህሩን እንዲከፍል አደረገው! ድል የነብዩላህ ሙሳ ሆነ። አንባገነኑ ፈርዖን'ም ህይወቱ አከተመች። ሰጠመ! ረሱለላህ ﷺ ወደ መዲና ሲገቡ አይሁዶች ይህንን ቀን ሲፆሙ ይመለከታሉ፤ ከዛም ለምን እንደሚፆሙ ሲጠይቋቸው ነብዩላህ ሙሳ ድል ያደረገበት እንደሆነ ነገሯቸው። ሸፊዒምﷺ: "ከነሱ በላይ እኛ ለሙሳ የቀረብን ነን።" በማለት የአሹራ ቀን፤ ከበፊቱ ያለውን እና የሚከተለውን መፆም እንደሚወደድ፤ ትሩፋቱም ትልቅ እንደሆነ አወጁ! 🩵 ያለፈው ዓመት ወንጀል የሚፋቅበት ሌላ እጣ! 😊 አሹራ ካስተማረኝ ነገር አንዱ አላህ ከኛ ጋር ነው ብለን ሙሉ እምነታችንን ስንሰጠው እና ስንተማመንበት ብዙ ድሎችን እንደሚሰጠን ነው። ሐቢበላህ ﷺ ከውዱ ጓደኛቸው ጋር ወደ መዲና በነበራቸው ጉዞ ላይ ሙሽሪኮች እየደረሱባቸው መሆኑን ሲያውቁ ጋሩ ሰውር የሚባል ጠባብ ዋሻ ውስጥ ገቡ! አባበክር በእባብ ከመነደፋቸው በላይ ሸፊዒ ﷺ አንድ ነገር እንዳይሆኑ ሰጉ፤ እንዳያዩን በሚል ፍርሃት ይንቀጠቀጡ ጀመር። የዚህን ጊዜ ውዱ መልዕክተኛው ﷺ ሷሂባቸውን አላህ ከነሱ ጋር እንደሆነ አበሸሩት! «ያ አባበክር! አትዘን አላህ ከኛ ጋር ነው።» አላቸው። ልክ ነብዩላህ ሙሳ ህዝባቸው በፍርሃት የፈርዖን ሰራዊቶች ሊደርሱብን ነው ሲሉ «ጌታዬ ከኔ ጋር ነው። በእርግጥ ይመራኛል!» ሲል ባህሩን እንደተከፈለላቸው ሁሉ ሸፊዒ ﷺ ለተጨናነቀው ጓደኛቸው «ላ ታህዘን ኢነላሃ ማዕና» ብለው ሲያረጋጉት በአላህ ጥበብ ምክንያት የሸረሪት ድር እንዲከልላቸው አደረገ። «ሁለቱም በዋሻው ሳሉ ለጓደኛው አትዘን አላህ ከእኛ ጋር ነውና ባለ ጊዜ አላህም መረጋጋትን በእርሱ ላይ አወረደ፡፡ ባላያችኋቸውም ሰራዊት አበረታው፡፡ የእነዚያንም የካዱትን ሰዎች ቃል ዝቅተኛ አደረገ፡፡ የአላህም ቃል ለእርሷ ከፍተኛ ናት፡፡ አላህም አሸናፊ ጥበበኛ ነው፡፡» [ሱረቱል ተውባ:40] የሚለው አያህ ወረደ። አሹራ! አላህ ላይ በኖረ ፍፁም ተወኩል የተሰጠ ድል! አላህ ከኔ ጋር ነው በሚል የኢማን ጥግ የተሰጠ ሽልማት ነው። አሹራ አሳዛኝ ክስተት የተከሰተበት ቀን'ም ነው። የሐቢበላህ ﷺ ተወዳጅ የልጅ ልጅ ሁሰይን ኢብን ዓሊይ ረሱሊ ﷺ በአንድ ወቅት «اللهم إني أُحبه فأَحبَّه، وأَحبَّ من يحبه» «አላህ ሆይ! ወድጄዋለው እና ውደደው፤ እሱንም የሚወዱትን ውደድ።» በማለት ፍቅራቸውን እና ስስታቸውን ይገልፁለት የነበረው እጅጉኑ የሚወዱት ሁሰይን ከርበላ ላይ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገ*ደሉበት ቀን'ም ነው። ሁሌም ሲታሰብ ህመም የሆነ ክስተት፣ ዘመናትን የተሻገረ ቁስል... የአላህ ቁ*ጣና እር*ግማን በኢማም ሁሰይን ገዳ*ዮችና መጥፎ አሳቢዮች ላይ ይውረድ 💔 አላህ በእርግጥ ከኛ ጋር ነው። እሱ ላይ የሚኖር ፅኑ እምነት ያድናል። በተዓምሩ ከጠላት ይከላከልልናል። ነቢዩላህ ሙሳ ተልዕኮው ሲሰጣቸው እና ተቀብለው ወደ ቀይ ባህር ሲተሙ መቼም ለጠላት የማይተዋቸው ጌታ ከጎናቸው እንደሆነ በጥልቅ ስላመኑ ነው። እኛስ አሹራ ምን አስተማረን? እኔ በበኩሌ ጌታችን በየትኛውም ከባድ ሁኔታ እንደማይተወን ተምሬያለሁ ምክንያቱም አላህ ሙሉ ውክልናውን ለሱ ከሚሰጡት ጋር ነውና። አላህ ከማን ጋር እንደሚሆን ቁርኣን ላይ ከተጠቀሱት የተወሰኑት: • إِنَّ اللَّهَ مَعَ الَّذِينَ اتَّقَوا وَّالَّذِينَ هُم مُّحْسِنُونَ : «አላህ ከእነዚያ ከሚፈሩትና ከእነዚያም እነሱ መልካም ሠሪዎች ከኾኑት ጋር ነውና፡፡» 🩵 • وَهُوَ مَعَكُمْ أَيْنَ مَا كُنتُمْ ۚ وَاللَّهُ بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ «እርሱም የትም ብትኾኑ ከእናንተ ጋር ነው፡፡ አላህም የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነው፡፡» • إِنَّ اللَّهَ مَعَ الصَّابِرِينَ «አላህ (በእርዳታው) ከታጋሾች ጋር ነውና፡፡» 🩵 • أَنَّ اللَّهَ مَعَ الْمُؤْمِنِينَ «አላህም ከምእምናን ጋር ነው፡፡» አሹራ ፆሙ ያለፈውን አመት ወንጀል የሚያስምር ቀን ነው። ሰይዲና ሁሰይን ኢብን ዓሊይ ላይ እንደተፈፀመው አሳዛኝ ክስተት የምናዝንበት እና የምናስበውም ቀን ጭምር ነው። ልክ ለረሱሊ ﷺ የበድር ጦርነት ድል እና ሐዘን የተቀላቀለበት ቀን እንደሆነው ሙሽሪኮች ላይ ድል ስላደረጉ ተደሰቱ፤ በተመሳሳይ ቀን ልጃቸው ሩቀያ ወደ አኺራ በመሻገርዋ ምክንያት ሐዘን ውስጥ ገቡ። የህይወት ፍልስፍና እንዲህ ነው። እኛም በነቢዩላህ ድል እንደምንደሰተው ሁሉ በረሱለላህ ውድ የልጅ ልጅ አሳዛኝ ግድ*ያ ደግሞ እናዝናለን። ድል እንዳለው ሁሉ ከባድ ሐዘን'ም ይኖራል! በበኩሌ አሹራ ያስተማረኝ ይህ ነው። መልካም የኢባዳ ጊዜ!😊
182
4
🌅ነገ ረቡዕን እና ሐሙስን የዓሹራ ፆም ናቸው መፆም እንዳትረሱ ሌላውንም እናስታውስ 😊 አመላካች የሰሪውን ምንዳ ያገኛል !
318
5
አቡ ዑስማን አን‐ነህዲይ እንዲህ ይላሉ: ‐ «[ሰለፎች] ሦስቱን ዐስሮች ያከብሩ ነበር: ‐ ⚀ ዐስሩን የመጨረሻ የረመዳን ቀናት፤ ⚁ የመጀመሪያዎቹን ዐስር የዙል‐ሒጃ ቀናት፤ ⚂ የሙሐረም ወርን የመጀመሪያ ዐስር ቀናት።» : ውዶቼ የዛሬ ውሎ ሙሐረም 8ኛው ቀን ነበር። ነገ ታሱዓእ ነው። የአላህ መልክተኛ [ሠለላሁ ዐለይሂ ወሰለም] በመጪው ዓመት በህይወት ካለሁ ከዐሹራእ በፊት እፆመዋለሁ ብለው ነይተውት የነበረው ቀን ነው። የፊታችን ሐሙስ ዐሹራእ ነው። እኛም እንጹም። ቤተሰቦቻችንንም እናስታውስ! ባረከላሁፊኩም!
314
6
''አንተን ከማገባ ምናለ ኢብሊስን ባገባሁ ኖሮ'' አለች ባልየው በእርጋታ መለሰላት «የኔ ፍቅር! እህት ወንድሟን ታገባ ዘንድ ሸሪዐው አይፈቅድም»🚶
426
7
ኢማም አል ገዛሊ (ቀደሰላሁ ሲረሁ) እንዲሁ "ኢሕያኡ ዑሉሚድ-ዲን") ላይ በዓሹራ ቀን ለቤተሰብ ማስፋፋት (ተውሲዓህ) በረከት እንዳለው ከሰለፎች (ከቀደምት ሊቃውንት) የተነገሩ ልምዶችን በመጥቀስ ተግባሩ መልካም መሆኑን ያጸድቃሉ። ነገ ዘጠነኛው ዕለት ነው፤ ከነገ ወዲያ ዐሥረኛው (ዓሹራእ) ነው። አላህ ጾም ከተጠቀሙት ያድርገና ♥
481
8
#ዓሹራእ የአላህ ወር ሙሐረም እና የዓሹራእ ቀን ዓሹራእ የሙሐረም ወር ዐሥረኛው ቀን ነው፤ አላህ ለዚህ ቀን ልዩ ክብር አለው፣ ቀኑን በመጾምም አላህ ለይቶ የሚሰጠው ትልቅ ትርፍ አለ፣ የአላህ መልክተኛም ﷺ በእሱ ላይ አበረታትተዋል። አላህ ሙሳንና ሕዝባቸውን ያዳነበት፣ ፈርዖንንና ሕዝቡን ያሰጠመበት ቀን ነው፤ ሙሳ ለአላህ ምስጋና ለማቅረብ ጾመውታል፣ ከዚያም ነቢዩ ﷺ ጾመውታል፣ እንዲጾምም አዘዋል፤ ኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ ዓንሁ) እንደዘገቡት እንዲህ ብለዋል፦ ‹‹ የአላህ መልክተኛ ﷺ ወደ መዲና በመጡ ጊዜ አይሁዶች የዐሹራን ቀን ሲጾሙ አገኟቸው፣ ስለዚያም ክስተት ተጠየቁ፤ እነሱም፦ ይህ አላህ ሙሳንና የእስራኤልን ልጆች በፈርዖን ላይ ድል ያቀዳጀበት ቀን ነው፤ እኛም ቀኑን ለማክበር እንጾመዋለን አሉ። የአላህ መልክተኛም ﷺ፦ ‹‹ እኛ ከእናንተ ይልቅ ለሙሳ እንገባዋለን›› አሉና እንዲጾም አዘዙ፡፡ ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል በሙስሊም ዘገባ ላይ ደግሞ፦ ‹‹ሙሳ ለአላህ ምስጋና ለማቅረብ ጾመውታል፣ እኛም እንጾመዋለን...›› ተብሎ መጥቷል። ነቢዩ ﷺ የአሹራን ቀን በመጾም ረገድ አራት ደረጃዎች (ሁኔታዎች) ነበሯቸው ለጣኢፉል መዓሪፍ 96-102 ላይ የተቀመጠውን ያንብቡ፡ የመጀመሪያው ሁኔታ፦ መካ እያሉ ይጾሙት ነበር፣ ነገር ግን ሰዎችን እንዲጾሙ አያዙም ነበር፤ በቡኻሪና ሙስሊም ዘገባ መሠረት ዓኢሻ (ረዲየላሁ ዓንሁ ) እንዲህ ብለዋል፦ ‹‹ዓሹራእ ቁረይሾች በጃሂሊያ ዘመን የሚጾሙት ቀን ነበር፣ ነቢዩም ﷺ ይጾሙት ነበር፤ ወደ መዲና በመጡ ጊዜ ጾሙት፣ ሰዎችንም እንዲጾሙት አዘዙ፤ የረመዳን ወር ግዴታ በወረደ ጊዜ ረመዳን የሚጾመው ሆነ፣ የዓሹራእን ጾም ተዉት፤ የፈለገ ሰው ይጾመዋል፣ የፈለገ ሰው ያፈጥራል›› ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል። በቡኻሪ ዘገባ ላይ ደግሞ፦ የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዲህ አሉ።፦ ‹‹የፈለገ ይጹም፣ የፈለገ ያፍጥር፡፡›› ሁለተኛው ሁኔታ፦ ነቢዩ ﷺ ወደ መዲና በመጡ ጊዜ የመጽሐፉ ባለቤቶች (አይሁዶች) ቀኑን ሲጾሙና ሲያከብሩት ባዩ ጊዜ ባልታዘዙበት ነገር ላይ እነሱን መግጠም ይወዱ ስለነበር ጾሙት፣ ሰዎችንም እንዲጾሙት አዘዙ፣ ትእዛዙንም አጠነከሩት፣ አልፎ ተርፎም ሕፃናቶቻቸውንም እንዲያስጾሙ ሰዎችን ያበረታቱ ነበር። ሦስተኛው ሁኔታ፦ የረመዳን ወር ጾም ግዴታ በተደረገ ጊዜ፣ ነቢዩ ﷺ ባልደረቦቻቸውን የዓሹራን ቀን እንዲጾሙ ማዘዛቸውን ተዉ፤ ሙስሊም በሶሒሐቸው ላይ እንደዘገቡት ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ ‹‹ ዓሹራእ ከአላህ ቀናት አንዱ ቀን ነው፤ የፈለገ ይጹመው፣ የፈለገ ይተወው፡፡›› በሌላ የሙስሊም ዘገባ ደግሞ፦ ‹‹ ከእናንተ መካከል መጾም የሚወድ ሰው ይጹመው፣ ያልፈለገ ሰው ደግሞ ይተወው።›› አራተኛው ሁኔታ፦ ነቢዩ ﷺ በሕይወታቸው መጨረሻ ላይ ቀኑን ለብቻው ላለመጾም ወሰኑ፣ ይልቁንም የመጽሐፉን ባለቤቶች ለመቃረን (ለመለየት) ዘጠነኛውን ቀን (ታሲዓእ) አብረው ለመጾም አሰቡ፤ ኢብኑ ዐባስ (ረ.ዐ) እንደዘገቡት እንዲህ ብለዋል፦ የአላህ መልክተኛ ﷺ ዓሹራእን በጾሙና እንዲጾም ባዘዙ ጊዜ፦ የአላህ መልክተኛ ሆይ! እሱ እኮ አይሁዶችና ክርስቲያኖች የሚያከብሩት ቀን ነው! አሏቸው። የአላህ መልክተኛም ﷺ፦ ‹‹የሚቀጥለው ዓመት ሲመጣ በአላህ ፈቃድ ዘጠነኛውን ቀን እንጾማለን›› አሉ። ነገር ግን የሚቀጥለው ዓመት ሳይመጣ የአላህ መልክተኛ ﷺ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡›› ሙስሊም ዘግበውታል። የዓሹራእ ቀን ጾም ትርፍን በተመለከተ አቡ ቀታዳህ (ረዲየላሁ ዓንሁ) በዘገቡት የነቢዩ ﷺ ሐዲስ ላይ ተገልጿል፣ በእሱ ውስጥ እንዲህ ብለዋል፦ የአላህ መልክተኛ ﷺ ስለ ዓሹራእ ቀን ጾም ተጠየቁ? እርሳቸውም እንዲህ አሉ፦ ‹‹ያለፈውን ዓመት ወንጀል ያስምራል ብዬ አላህ ላይ እከጅላለሁ፡፡››ሙስሊም ዘግበውታል አንድ ሙስሊም ዐሥረኛውን ቀን ብቻውን ቢጾም ምንም እንኳ ከፊል ሊቃውንት ቢጠሉትም ያለምንም ጥርጣሬ ይህንን ታላቅ ምንዳ ያገኛል፤ ዘጠነኛውን ቀን አብሮ ቢጨምር ግን ምንዳው የላቀ ይሆናል። ኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ ዓንሁ) እንደዘገቡት ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ ‹‹ እስከሚቀጥለው ዓመት ከኖርኩ በእርግጥ ዘጠነኛውን ቀን እጾማለሁ፡፡›› ከእሱ በፊት አንድ ቀን እና ከእሱ በኋላ አንድ ቀን፣ ወይም ከእሱ በፊት ወይም ከእሱ በኋላ መጾምን በተመለከተ የመጡት ሐዲሶች ወደ ነቢዩ ﷺ መድረሳቸው (ረፍዓቸው) አልተረጋገጠም፤ እንደሚታወቀው እምነታዊ ተግባራት (ዒባዳዎች) በመረጃ ላይ የተገደቡ (ተውቂፊያህ) ናቸው፣ ያለ መረጃ ሊሰሩ አይገባም፤ ነገር ግን በዚህ ዙሪያ በመጡት ዘገባዎች መጽናናት ይቻላል፤ ከእነዚህ መረጃዎች መካከል ከፊሉ በኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ላይ መቆማቸው (መውቁፍ መሆናቸው) ተረጋግጧል፤ በዚህም ምክንያት ዓሹራእንና ከእሱ በፊት አንድ ቀን እንዲሁም ከእሱ በኋላ አንድ ቀን ለሚጾም፣ ወይም በዓሹራእ ጾም ብቻ ተወስኖ ከእሱ በኋላ አንድ ቀን ብቻ ለሚጾም ሰው ላይ ወቀሳ አይደረግበትም። በዓሹራ ቀን የነቢዩ ﷺ የልጅ ልጅ የሆኑት #የኢማም_ሑሰይን እና የቤተሰቦቻቸው በካርባላ ምድር በሰማዕትነት መውደቅን ማውሳት ተሰዉፉ ዘንድ ትልቅ ቦታ አለው። ለአላህ መልእክተኛ ﷺ ቤተሰቦች (አህሉል በይት) ያላቸው ፍቅር የእምነታቸው አካል ነው ብለው ያምናሉ። ስለዚህ #በዓሹራእ ቀን የኢማም ሑሰይንን ታሪክ ማውሳት፣ የደረሰባቸውን መከራ ማስታወስ እና ለነፍሳቸው ዱዓ እና ሰለዋት ማድረግን እንደ በጎ ተግባር ይታያል፡፡ ይሁን እንጂ የኢማም ሑሰይንን ሰማዕትነት ሲያወሱ ድንበር እንደተላለፉት #ሺዓዎች ጉንጭን መምታት፣ ልብስን መቅደድ፣ በሰንሰለት ራስን መግረፍ እና ከመጠን ያለፈ ዋይታና ልቅሶን አይቀበሉም፤ እነዚህን ተግባራት የሸሪዓ ጥሰት አድርገውም ይመለከታሉ። በምትኩ ቀኑን በቁርኣን ኽትም፣ በዚክር፣ በሰለዋት እና በሰላማዊ መንፈሳዊ ጉባኤዎች (መጃሊሶ) የሑሰይንን ጽናትና መስዋዕትነት በማውሳት ያሳልፋሉ። በዓሹራ ቀን ለቤተሰብ የተሻለ #ምግብ ማቅረብ፣ ስጦታ መስጠትና ወጪን #ማስፋፋት (ተውሲዓህ) በእነዚህ መሻኢኾች ዘንድ የተወደደ (ሙስተሐብ) ተግባር ነው። ለዚህ ተግባር የሚከተለውን የነቢዩ ﷺ ሐዲስ እንደ መረጃ ይጠቅሳሉ፦ «በዓሹራእ ቀን ለቤተሰቡ (በወጪ/በምግብ) ያሰፋ ሰው፣ አላህ በዓመቱ ሙሉ ላይ ያስፋለታል።» (ጦባራኒና በይሃቂ የዘገቡት) ይህ ሐዲስ በአንዳንድ ሊቃውንቶች ዘንድ "ደካማ" (ዶዒፍ) ተብሎ ውድቅ ቢደረግም፣ እንደ ኢማም አል-ገዛሊ እና ሸይኽ ዐብዱልቃዲር ጂይላኒ መሰል ያሉ የጥንት የሱፊያ ሊቃውንቶች ዘንድ ግን ሐዲሱ በጥሩ ሥነ ምግባርና በበጎ ፈቃድ ሥራዎች (ፈዷኢሉል-አዕማል) ስር ስለሚካተት ሊሠራበት እንደሚገባ ያስተምራሉ። ይህንን ቀን አላህ ለፍጡራኑ ሲሳይንና በረከትን የሚቸርበት ዕለት አድርገው ስለሚመለከቱትም ለቤተሰብና ለድሆች ምግብ ማቅረብ (ሶደቃህ መስጠት) በዓመቱ ውስጥ የሲሳይ በረከትን ያስገኛል ብለው ያምናሉ። ኢማም ዐብዱልቃዲር ጂይላኒ (ቀደሰላሁ ሲረሁ) በ"አል-ጉንያህ" በተሰኘው ኪታባቸው ላይ እንዲህ ብለዋል፡ "በዓሹራእ ቀን ሰዎችን መመገብ፣ ለቅን አማኞች ማዕድ ማዘጋጀት እና ለቤተሰብ ወጪን ማስፋፋት የተወደደ ተግባር ነው። በዚህ ቀን አንድን ድሃ የመገበ ሰው፣ የዓለምን ድሆች ሁሉ እንደመገበ ይቆጠራል።"
455
9
ነፍስ ሁሉ ሞትን ቀማሽ ናት፡፡ ምንዳዎቻችሁንም የምትሞሉት በትንሣኤ ቀን ብቻ ነው፡፡ ከእሳትም የተራቀና ገነትን የተገባ ሰው በእርግጥ ምኞቱን አገኘ፡፡ ቅርቢቱም ሕይወት የመታለያ መሳሪያ እንጅ ሌላ
ነፍስ ሁሉ ሞትን ቀማሽ ናት፡፡ ምንዳዎቻችሁንም የምትሞሉት በትንሣኤ ቀን ብቻ ነው፡፡ ከእሳትም የተራቀና ገነትን የተገባ ሰው በእርግጥ ምኞቱን አገኘ፡፡ ቅርቢቱም ሕይወት የመታለያ መሳሪያ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡ كُلُّ نَفْسٍۢ ذَآئِقَةُ ٱلْمَوْتِ ۗ وَإِنَّمَا تُوَفَّوْنَ أُجُورَكُمْ يَوْمَ ٱلْقِيَٰمَةِ ۖ فَمَن زُحْزِحَ عَنِ ٱلنَّارِ وَأُدْخِلَ ٱلْجَنَّةَ فَقَدْ فَازَ ۗ وَمَا ٱلْحَيَوٰةُ ٱلدُّنْيَآ إِلَّا مَتَٰعُ ٱلْغُرُورِ
374
10
"አንተ የምስጋናና የልግስና ሁሉ መገኛ ሆይ! ተስፋዬ በቸርነትህ ላይ ተንጠልጥሏል። አላህ ሆይ! ተስፋውን ባንተ ያሰረን ሰው አታሳፍር፤ ወዳንተ የተዘረጋችን እጅ ባዶ አትመልስ፤ በአንተ እውቀት የተከበረችን ነፍስም አታዋርድ።" : ይህ የአንድ የዐረብ ዘላን ዱዓ በጣም ጥልቅ የሆነ የኢማን መልእክት ይዟል። ‐ "ተስፋዬ በቸርነትህ ላይ ተንጠልጥሏል" ማለት፣ ሰውዬው በራሱ ጉልበት፣ በሀብቱ ወይም በሰዎች ላይ ሳይሆን በአላህ ቸርነት ላይ ብቻ ተስፋውን አድርጓል ማለት ነው። ‐ "ወደ አንተ የተዘረጋችን እጅ ባዶ አትመልስ" ማለት፣ ዱዓ አድራጊውን ከቸርነትህ ሳታጎድል ምላሽ ስጠው፤ ልመናውን አትንፈገው ማለት ነው። ‐ "በአንተ እውቀት የተከበረችን ነፍስ አታዋርድ" ማለት፣ አንተን ያወቀ፣ ወደ አንተ የቀረበ እና በአንተ የተከበረ ልብ እንዳይዋረድና እንዳይጣል እጠይቅሃለሁ ማለት ነው። 🔴 አሚን!
403
11
(ሙሐረም 10 — ዓሹራ) ================= በወርሃ ሙሐረም ባስርተኛዋ ቀን የገድልና የድል የፈውስም የተውበት በታላቅ‒ታላላቅ‒ታሪክ ታተመበት። ከዚያኛው መጀምር እሰከኔው ዘመኔ ኩታ ገጠም ነብሯል የዓሹራው ቅኔ። ያውም በታላቆች በነቢያት ህይወት የሆነውን ሰምተን ከቶ እንዴት ላይደንቀን ተመሳሳይ ገድል በተመሳሳይ ቀን የአደምን ተውበት ሲቀበል ረሕማኑ ከጥፋቱ ውኃ ኑሕ ነጃ ሲሆኑ አዩብም ከሕመም ታግሰው ሲድኑ ዓሹራ ነው ቀኑ። ዩሱፍ ከየዕቁብ ጋር የተገናኙበት ኢብራሂም ከእሳቱ ዩኑስ ከዓሳ ሆድ አማን የወጡበት ፊርዐውኑ ሰምጦ፣ ሙሳ የዳኑበት እለቱን ለማወቅ ታሪክ ሲበረበር መገን መገጣጠም፣ ዓሹራ ላይ ነበር። ግንስ ደግሞ ቀዷው፣ ያሏህ መሻት ሆኖ በሙሐረም 10 ፥ በዚህ ባሹራው ቀን ክሱት ተከስቷል፣ ሕመሙ ማይለቀን ለክሱቱ ግዝፈት፣ ላይ ታቹ ተናውጧል ሁነት ተገላብጧል፣ ኮከብ በቀን ወጧል ፍጥረት በየ ዘይቤው ፥ እዝኑን ይፋ ገልጧል የጀነት ወጣቶች አንድኛው አለቃ የፋጢመት ሽታ፣ የሐይደር ድማማ የረሱል የልጅ ልጅ፣ ያህለል በይቱ ግርማ ሸሂድ ሆነው ሲያርፉ፣ በከርበላዕ መሬት ሰይዲ ሑሰይኑ፣ የነቢ ረይሓኑ ዓሹራ ነበረ፣ የዛን ለትም ቀኑ። Ustaz Seid Ahmed
382
12
ሀጅ ላይ ኒሻን, ዋንጫና ሜዳሊያ መሸለም ብርቅ አይደለም:: የቀድሞ መጅሊስ በአመራርም በድርጅትም ደረጃ የሀጅ አፈጻጸም ላይ ኒሻን የተሸለሙበት, ቤተመንግሥት ንጉሦቹ ጋር ገብተው የተስተናገዱበት ሰነ+1
ሀጅ ላይ ኒሻን, ዋንጫና ሜዳሊያ መሸለም ብርቅ አይደለም:: የቀድሞ መጅሊስ በአመራርም በድርጅትም ደረጃ የሀጅ አፈጻጸም ላይ ኒሻን የተሸለሙበት, ቤተመንግሥት ንጉሦቹ ጋር ገብተው የተስተናገዱበት ሰነዶችም ፎቶዎች አሉ:: ሙተሦዊፉ በዝምታ ነው የሚሠራው:: መስጂድ ሲሠራም ጸጥ ነው:: አይጮኽም አያስጮኽም:: በወሃbው በኩል መስጂዶችን በመደዳ ሲያስፈርሱም ጭምር የገጽታ ግንባታ ልገንባ ይላሉ:: ትንሽዬ እንቁላል ለመጣል እንደምታስካካ ዶሮ ሀገሩን በጩኸት ያናውጣሉ:: የአሁኖቹ መጅ^ሊዞች ኒሻም መሸለም ብርቅ ሆኖባቸው ነው መሰለኝ ከአየር መንገድ እስከ ሸራተን ምንጣፍ አንጥፉልን እያሉ ናቸው:: 2007/2008 ላይ የተሸለሙት ከፍተኛ ኒሻን እንጀምርና እያየን እንግባ ወይስ መስጂድ አስፈራሽ መጅሊሶች <<ጅ^ብ የማያውቁት ሀገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ >> ግርግራቸውን እንዳናበላሽ ይሸልሉ? Via Hassen Injamo
496
13
እነዛ እስልምናን የተሳደቡ ስፔናዊያን የሚመኩበት ልጃቸው በሱጁድ ለስድባቸው ምላሽ ሰቷል ❤️ ወደ ከፍታ የሚመራክ ብቸኛው ዝቅታ ለአለማቱ ጌታ አላህ ሱጁድ 🥰 #እግርኳስ #ያማል #ሱጁድ
እነዛ እስልምናን የተሳደቡ ስፔናዊያን የሚመኩበት ልጃቸው በሱጁድ ለስድባቸው ምላሽ ሰቷል ❤️ ወደ ከፍታ የሚመራክ ብቸኛው ዝቅታ ለአለማቱ ጌታ አላህ ሱጁድ 🥰 #እግርኳስ #ያማል #ሱጁድ
485
14
ትክክለኛ መልሱ ይኸው 😁
ትክክለኛ መልሱ ይኸው 😁
482
15
መልሱ ልናገር? ትንሽ ሞክሩ
478
16
ሞክሩ እስኪ 😊 ❓መስኮት ላይ ከውጪ በኩል ብረቱ እንዲህ ወጣ ተደርጎ የሚሰራው ለምንድነው?
ሞክሩ እስኪ 😊 ❓መስኮት ላይ ከውጪ በኩል ብረቱ እንዲህ ወጣ ተደርጎ የሚሰራው ለምንድነው?
506
17
«አላህን የማያስታውስ ልብ፣ መስኮት የሌለው ጨለማ ቤት ነው። ከሰማይ ጋር ያልተገናኘች ነፍስ፣ ምድር ላይ ባለ ጌጥ ብትሞላም ደብዛዛ ናት። የማይጠፋ ሕይወት ከፈለግህ፣ ምላስህን የሚያወራ ሙስባሓ አድርግ፤ ትንፋሽህን ሰላት ያድርግ፤ እርምጃዎችህንም ወደ ብርሃን የሚመራ ጉዞ አድርግ። ዚክር የነፍስ ሕይወት ነው፤ ዚክርን የረሳ ሰው ሥጋ ብቻ ይዞ እንደሚኖር፣ ነፍስ የሌለው ሕያው ሬሳ ነው።» ሸምስ ተብሪዚ
530
18
ሰላት ስንቆም የእግሮቻችን ጣቶቸ ወደ ቂብላ መዞራቸው የሚወደድ ሱና ነውና እያጣመምን ባንቆም መልካም ነው። ሰላት ላይ ስንቆም ወደ ቂብላ ነው። ቂብላ ፎከስ (ትኩረት) የምናደርግበት ነው። ቂብላን ስናስብ ነገሮችን ኹሉ ጥለን ወደርሱ መሰብሰብን (ሓዲር መኾንን) ይሰጠናል። ቂብላ ሙሉ ለሙሉ ወደርሱ መዞርን ይጠቁማል ♥
582
19
የዛሬው መጨነቅ የነገው መሳቅ ምክንያት ሊሆን ይችላል እናም ታገሱ።
563
20
«ከቀደር ጋር መከራከርህን እስካልተውክ ድረስ፣ ከንቱ ልፋትና ድካምህ አይቆምም። ነገር ግን፣ ‘ጌታዬ ሆይ፣ ባንተ ላይ ተስፋዬን ጥያለሁ። ጉዳዬንም ለአንተ አስረክቤያለሁ’ በምትልበት ቅጽበት፣ ሁሉም ነገር ይረጋጋል፤ ልብህም ሰላም ያገኛል፤ ሊሆን አይችልም ብለህ ያሰብከው እንኳን ወደ ቀና መንገድ ይመለሳል።»
690