es
Feedback
🍂 ዲነል ኢስላም 🕌

🍂 ዲነል ኢስላም 🕌

Ir al canal en Telegram

♡_ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራ ሰውን አጅር ያህል ያገኛል"(አመላካች የሰሪውን ምንዳ ያገኛል)ﷻ (ﷺ) « ከናንተም ወደ በጎ ነገር የሚጠሩ ፣ በመልካም ስራም የሚያዙ ከክፉ ነገርም የሚከለክሉ ሕዝቦች ይኑሩ ፣ ...» ቁርኣን[ 3:104 ] መወያያ ግሩፓችን ☞ @Dinel_islam_Group ✔ ሀሳብ አስተያየት ካሎት 👉 @DinelIslam1Bot 📩

Mostrar mĂĄs
9 226
Suscriptores
-1124 horas
-667 dĂ­as
-23530 dĂ­as

Carga de datos en curso...

Atraer Suscriptores
septiembre '26
septiembre '26
+1
en 0 canales
agosto '26
+83
en 4 canales
Get PRO
julio '26
+98
en 1 canales
Get PRO
junio '26
+47
en 0 canales
Get PRO
mayo '26
+10
en 2 canales
Get PRO
abril '26
+2
en 2 canales
Get PRO
marzo '26
+13
en 3 canales
Get PRO
febrero '26
+9
en 0 canales
Get PRO
enero '26
+19
en 3 canales
Get PRO
diciembre '25
+8
en 1 canales
Get PRO
noviembre '25
+8
en 0 canales
Get PRO
octubre '25
+3
en 1 canales
Get PRO
septiembre '25
+2
en 1 canales
Get PRO
agosto '25
+38
en 1 canales
Get PRO
julio '25
+66
en 4 canales
Get PRO
junio '25
+183
en 2 canales
Get PRO
mayo '25
+6
en 1 canales
Get PRO
abril '25
+3
en 4 canales
Get PRO
marzo '25
+640
en 3 canales
Get PRO
febrero '25
+59
en 1 canales
Get PRO
enero '25
+176
en 3 canales
Get PRO
diciembre '24
+137
en 0 canales
Get PRO
noviembre '24
+443
en 1 canales
Get PRO
octubre '24
+663
en 1 canales
Get PRO
septiembre '24
+673
en 3 canales
Get PRO
agosto '24
+1 625
en 7 canales
Get PRO
julio '24
+1 652
en 3 canales
Get PRO
junio '24
+723
en 2 canales
Get PRO
mayo '24
+828
en 3 canales
Get PRO
abril '24
+1 010
en 2 canales
Get PRO
marzo '24
+949
en 3 canales
Get PRO
febrero '24
+738
en 0 canales
Get PRO
enero '24
+677
en 3 canales
Get PRO
diciembre '23
+659
en 2 canales
Get PRO
noviembre '23
+550
en 2 canales
Get PRO
octubre '23
+739
en 0 canales
Get PRO
septiembre '23
+170
en 0 canales
Get PRO
agosto '23
+47
en 0 canales
Get PRO
julio '23
+86
en 0 canales
Get PRO
junio '23
+137
en 0 canales
Get PRO
mayo '23
+83
en 0 canales
Get PRO
abril '23
+76
en 0 canales
Get PRO
marzo '23
+90
en 0 canales
Get PRO
febrero '23
+51
en 0 canales
Get PRO
enero '23
+54
en 0 canales
Get PRO
diciembre '22
+83
en 0 canales
Get PRO
noviembre '22
+66
en 0 canales
Get PRO
octubre '22
+77
en 0 canales
Get PRO
septiembre '22
+76
en 0 canales
Get PRO
agosto '22
+65
en 0 canales
Get PRO
julio '22
+66
en 0 canales
Get PRO
junio '22
+33
en 0 canales
Get PRO
mayo '22
+11
en 0 canales
Get PRO
abril '22
+49
en 0 canales
Get PRO
marzo '22
+52
en 0 canales
Get PRO
febrero '22
+11
en 0 canales
Get PRO
enero '22
+113
en 0 canales
Get PRO
diciembre '21
+106
en 0 canales
Get PRO
noviembre '21
+194
en 0 canales
Get PRO
octubre '21
+314
en 0 canales
Get PRO
septiembre '21
+1 052
en 0 canales
Get PRO
agosto '21
+1 344
en 0 canales
Get PRO
julio '21
+1 543
en 0 canales
Get PRO
junio '21
+2 284
en 0 canales
Get PRO
mayo '21
+950
en 0 canales
Get PRO
abril '21
+2 476
en 0 canales
Get PRO
marzo '21
+1 393
en 0 canales
Get PRO
febrero '21
+828
en 0 canales
Get PRO
enero '21
+1 741
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
03 septiembre0
02 septiembre+1
01 septiembre0
Publicaciones del Canal
ከነብዩ ﷺጋር ያለን ግንኙነት... https://t.me/Alimrancmc

2
ልብ በከበደች ግዜ መድሀኒቷ ዚክር ነው اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا محمد، وعلى آله وصحبه، ሀጃችን ሚወጣበት ሰለዋታችን መድሀኒት ሚሆንበት ሀቢባችንን ማየትን ምንወፈቅበ
ልብ በከበደች ግዜ መድሀኒቷ ዚክር ነው اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا محمد، وعلى آله وصحبه، ሀጃችን ሚወጣበት ሰለዋታችን መድሀኒት ሚሆንበት ሀቢባችንን ማየትን ምንወፈቅበት ምርጥ ኸሚስ አላህ ያርግልን
230
3
"ምርጥ ሚስት ማለት ስታያት የምትማርክህ ስታዛት የምትታዘዝህ አንተ ከቤት ስትርቅ ክብሯን እና ንብረትህን የምትጠብቅልህ የሆነችዋ ነች💝" ረሱልﷺ
261
4
..ከአንድ ወንድም ጋር የመግሪብ ሶላት ሰግደን እየወጣን ሳለ ስለ አንድ ጉዳይ አውርተን "ጥሩ ሃሳብ!" ተባብለን ቀጠሮ ይዘን ልንለያይ ስንል ሌላ ወንድም አስቆመንና ሃሳብን እንዴት መሬት ላይ ማውረድ እንዳለብን የራሱን ልምድ መሰረት አድርጎ 7 ነጥቦችን ይነግረን ጀመር... ከጠቀማችሁ ተከተሉኝ፦ 1/ በመጀመሪያ ደረጃ ጉዳዩ ሀላል ወይም ሐራም መሆኑን እለያለሁ። ሃላል ከሆነ 2/ በዚያ ጉዳይ ዙሪያ ያሉ ወንድሞችን/ሰዎችን ሹራ አደርጋለሁ 3/ በመቀጠልም ሶላተል ኢስቲኻራ(የምርጫ ሶላት) እሰግዳለሁ። ከዚያም ይህን ማስረጃ አጣቀሰ.. وَشَاوِرْهُمْ فِي الْأَمْرِ ۖ فَإِذَا عَزَمْتَ فَتَوَكَّلْ عَلَى اللَّهِ ۚ إِنَّ اللَّهَ يُحِبُّ الْمُتَوَكِّلِينَ <<..በነገሩም ሁሉ አማክራቸው፤ ቆራጥ ውሳኔ በወሰንክም ጊዜ በአላህ ላይ ተመካ፤ አላህ ተመኪዎችን ይወዳልና።" 4/ ሃጃው እንዲሳካ የወላጆችን ውዴታ ለማግኘትእሞክራለሁ። "እንደዚህ አይነት ሃጃ አለብኝ! በዱዓ አግዙኝ" ብዬ እናገራለሁ አሊያም አጅሩን ለእነሱ ነይቼ ሰደቃ እሰጣለሁ። ይህን ሳደርግ ሃየን ወመይተን(በህይወት ኖሩም አልኖሩም) ልዩነት አይኖረውም። 5/ ሃጃውን አላህ እንዲያሳካው በሚል ኒያ ሰደቃ አወጣለሁ። © በነዚህ Step መሰረት ስሄድ በአላህ ፍቃድ ሃጃው መሳካቱ አይቀርምና ሲሳካ በራስ መገረም(ዑጅብ)ውስጥ ላለመግባት 6/ ኢስቲግፋር አደርጋለሁ፦ «مَنْ لَزِمَ الاِسْتِغْفَارَ جَعَلَ اللَّهُ لَهُ مِنْ كُلِّ ضِيقٍ مَخْرَجًا ، وَمِنْ كُلِّ هَمٍّ فَرَجًا ، وَرَزَقَهُ مِنْ حَيْثُ لاَ يَحْتَسِبُ» «እስቲግፋርን (ምህረት መጠየቅን) አዘውትሮ የያዘ ሰው፤ አላህ ለእርሱ ከጨነቀው ነገር ሁሉ መውጫን፣ ከጭንቀቱም ሁሉ እፎይታን ያደርግለታል፤ ባላሰበበትም መንገድ ሲሳይን (ርዝቅን) ይሰጠዋል።» 7/ ሶላት ዓለ ነቢﷺ አበዛለሁ! ​«إِذًا تُكْفَى هَمَّكَ، وَيُغْفَرُ لَكَ ذَنْبُكَ» ታላቁ ሶሃባ ኡበይ ኢብኑ ካዕብ ለሰዪዳችንﷺ ትርፍ ኢባዳዬን በጠቅላላ ሶለዋት አደርጋለሁ! ሲላቸው ሰዪዳችንምﷺ፦ «እንግዲያውስ ጭንቀትህ ይወገድልሃል፤ ወንጀልህም ይማርልሃል» ባሉት መሰረት ሶለዋቴን አበዛለሁ። አለን! አላህ ይጨምርለት! እንደዚህ አይነት ወንድሞችን ያብዛልን!🤲 ምን አልባት ለሆነ ጊዜ ካስፈለገን Save አድርገን እንሞክር!💚 Tariq Jemil
460
5
አቅሙ እንዳለው እያወቀ ምንም ነገር መቀየር ካልቻለ ሰው በላይ ከባድ ጭንቀት የተሸከመ የለም❤️‍🩹
448
6
ጻጉሜ 1 ወንዶች የፈለጉበት ሔደው መውሊድ ከመሳተፍ የሚከለክላቸው የለም:: ከ በረከቱል ሀበሺያህ-Bereketul Habashiyah መውሊድ ውጪ:: ሴቶቹ ወንዶች ለኻዲምነትም ቢሆን ድርሽ እንዳትሉብን
ጻጉሜ 1 ወንዶች የፈለጉበት ሔደው መውሊድ ከመሳተፍ የሚከለክላቸው የለም:: ከ በረከቱል ሀበሺያህ-Bereketul Habashiyah መውሊድ ውጪ:: ሴቶቹ ወንዶች ለኻዲምነትም ቢሆን ድርሽ እንዳትሉብን ብለዋል:: ሙሒብ ሴቶችን በጠቅላላ ጋብዘዋል:: ካሜራ ክልክል መሆኑንም አዋጅ ብለዋል:: ለሴቶች ምቹ የሆነ መውሊድ ነው:: ሴቶች ሰብሰብ ብላቹ አርሒቡ ነብዬ በሉ 🥁👏 ﷺ አዲስ አበባ ያላችሁ ፍፁም እንዳያመልጣችሁ ⁉️
534
7
ስትወለድ ነፃ ሰው ነበረች። ህይወት ግን ለባርነት ማገደቻት። ባርነትን በሽያጭ ትጀምር ወይም በስጦታነት ተሰጥታ ግልፅ ታሪክ ባይኖርም ግን ከአብሲኒያ ተነሳታ ከአረቢያን ምድር ከተከበረው ከበኑ ሀሺም ጎሳ ከአብዱል ሙጠሊብ ቤት ገባች። የታሪክ እጣ ፈንታ አይታው፣ አውርታው ከማትጠግበው የምድር ዕንቁ የአላህ መልእክተኛ ﷺ ጋር እስኪያገናኛት ከሷ በፊት እንደነበሩት ከሷ ቡኋላም እንደመጡት ባሪያዎች ሁላ "ባሪያ" ተብላ ከመኖር ያልዘለለ ታሪክ ሊኖራት ነበር። የአብደላህ ሞት በሙሽሪቷ አሚናት ቤት የሀዘን ጥላን ሲያጠላ አይዞኝ ባይ አበሻሪዋ እሷው በረካ ራሷ ነበረች። ከእርግዝናዋ ማግስት እስከ ውልደት ቀን ስትንከባከባት ቆይታ፣ ያንን የጨረቃ ፍልቃቂ ውድ ነብይ ﷺ መወለድ ስታይ "ከጨረቃ የበለጠ ቆንጆ ልጅ ተወለደ"ስትል የብስራት ዜና አወጀች። አብዱላህ ሲሞቱ ነበረች፣ አሚና ስትሞት በአይኗ አይታለች፣ አብዱል ሙጠሊብ ሲሞቱም ነበረች፣ አቡጣሊብ ሲሞቱም አለች፣ ኸዲጃ ስታርፍ ነበረች፣ የአላህ መልእክተኛ ልጆቻቸውን በሞት ሲያጡም ነበረች። በዚህ ሁሉ ሀዘን ትከሻዋን ሰጥታ ሀዛናቸውን ያባሸረች እሷው ራሷ በረካ ነበረች። በአደራዋ ታምና ከውልደታቸው እስከሞታቸው ከጎናቸው ሆና ሲያዝኑ አዝና ሲደሰቱ ተደስታለች። በእጆቿ ያወለደቻቸው ነብይ ﷺ አድገው ሲዳሩም ነበረች። ደስታቸውን ያደመቀች፣ ትዳራቸውን ለመካደም ከጎጃቸው ዘልቃ የገባች፣ የአደራ ንግስት ነበረች። ብዙም አልቆየች፣ ውዱ ነብይና ﷺ ባለቤታቸው ኸዲጃ ነፃ ነሽ ብለው እንደ ባሪያ ሳይሆን እንደቤተሰብ አብራቸው እንድትኖር አደረጉ። ቡኋላም ለዑበይድ ኢብኑ ዘይድ ድረዋት የበኩር ልጇና የስሟ መጠሪያ የሆነውን አይመንን ወልዳ ታቀፈች። ከኢስላም መታወጅ በፊት ባለቤቷ ሞተ። እሷም ወደ ልጇ፣ ወደ ውዷ፣ ወደ ቤተሰቧ፣ ተመልሳ የአብራኳን ክፋይ ልጇን ታሳድግ ጀመር። ሰዎች አንድም ጥቁር ባሪያ የነበረች ሁለተኛም እድሜዋ መተለቁን ተከትሎ ሊያገቧት ፍላጎት አልነበራቸውም፣ አንዲት ቀን የአላህ መልእክተኛ ﷺ የጀነት እንስት መሆኗን እስኪያውጁ ድረስ። መልእክቱ ከጆሮዎ አልፎ ልቡ ድረስ የተሰማው ዘይድ ኢብኑ ሀሪሳ የመልእክተኛው የማደጎ ልጅ የኛዋን ሀበሻዋን በረካ አግብቶ ታዋቂውን የጦር መሪ ዑሳማ ኢብኑ ዘይድን ወለዱ። ኢስላም ከመታወጁ በፊት በድብቅ መልእክቱ ሲተላለፍ ከውልደታቸው ጀምሮ የምታውቃቸውን ታላቅ ሰው መልእክት ያለ ምንም ጥርጣሬ አሚን ብላ ተቀበለች። ለኢስላም ባሏን እና ልጇን ሰጥታለች፣ የሸሂድነትን ክብር በነሱ በኩል አይታለች። እሷም ባርነቷ የፈጠረባት የቤተሰብ እና የማንነት ክፍተት፣ የመልእክተኛው የሰይዳች ﷺ የቲምነት አጣምሯቸው እንደ ልጅ እና እናት ግንኙነታችወን አጠናከረው። በስጋና ደም ባይዛመዱም በፍቅር ገመድ ተገምደው እናትና ልጅ ሆኑ። ፍቅራቸውን ሲገልፁላት እናቴ በሚል ውብ ማዕረግ ነበር። ለሷ የነበራቸው ፍቅር ወደ ልጆቿም የተላለፈ ውብ ሃብቷ ነበር። ወገኖቿ በዝሆን ታግዘው ካዕባን ሊያፈርሱ ሲመጡ በቋንቋ እና በዘር በማይገናኟት አረቦች መሀል ሆና ተመልክታለች። እስልምና ከመነሻው አንስቶ በሰዎች መሀል ሲስፋፋ ተመልክታለች። እስልምና ባህር ተሻግሮ ከመጣችበት አቢሲኒያ ደርሶ ወገኖቿ፣ ደሞቿ፣ ቀለሞቿ፣ የእኛ አያቶች እስልምናን እንደተቀበሉ ሰምታለች። የጀነት በር፣ የነፃነቷ ሰበብ፣ ከማንም በፊት ልጄ ያለቻቸው፣ እናቴ እያሉ ያነገሷትን፣ የነብዮች ﷺ አለቃ በሞት ሲለዩዋት በሁለት መንገድ ተሰበረች። አንድም በፍቅር ሀረግ የተዛመደቻቸውን አይዞሽ ባይ፣ መስታወቷን፣ የነፃነት አባቷን፣ የሀይማኖት መሪዋን፣ የጀነት በሯን አሳጥቶ በብቸኝነት አለጋ ገረፋት። በሌላ በኩል ከፈጣሪዋ ይደርሳት የነበረው፣ ትሰማውና ትናፍቀው የነበረው፣ የመልካም ዜና ብስራትና የማስጠንቅቂያ መልእክት ዋህይ መቋረጡ ልቧን አደማው። መፅናኛዋ ብዙ ቢሆንም የልቧን አልሞላ አሏት። የወዳጇ የነብዩዋ ወዳጆች ሊዘይሯት ሲመጡ አቀባበሏም ሆነ አሽኛኘቷ በእንባ የታጀበ ነበር። ነገን በመናፈቅ በጀነት ከአላህ መልእክተኛ ዘንድ ለመሆን እየተመኘች ከአቢሲኒያ ምድር ያመጣት የህይወት መንገድ ከአረቢያ ምድር በመዲና ከደጋጎቹ ጎን አሳረፋት። እሷ ታሪክን ሙሉውን ያየች፣ የውልደቱ ብስራት ያወጀች፣ በሞቱ መርዶ የተሰበረች፣ ልጇና ባሏን በተግባር ለእርሱ ለውዷ ፊዳ ያለች፣ መወደድን በእናትነት ማዕረግ ያጣጣመች ድንቅ እንስት ነበረች። ወዲህም አያታችን መኩሪያና መጠሪያችን ሆነች። አላህ ውብ ስራዋን ይውደድላት🌸 #በረከቱል_ሀበሺያ #መውሊድ_1501
551
8
ሐጂዬ ቱፋ እርሶ ግን ትክክል የሚሰሩት መቼ ነዉ? ሁሌም ጥፋ ኧረ ተዉ አታሸማቁን አርፈዉ ቤቶት ቢቀመጡስ?? ወይኔ ኪሳራችን ሴትዮዋ ለራሷ እስከምትጨነቅ እኮ ነዉ ያቀፏት ግን ዒልም (ዕውቀት) እና ተቅዋ (አሏህን መፍራት) የሚለካው በትልልቅ ማዕረጎች ወይም በሕዝብ ፊት በሚደረግ ንግግር ሳይሆን፣ በሕይወት አጋጣሚዎች ሁሉ የሸሪዐን ድንበር በጥብቅ በመጠበቅ ነው!! ​በቪዲዮው ላይ እንደሚታየው፣ ራሳቸውን የሙስሊሙ ማህበረሰብ ተወካይ ወይም ታላቅ ዓሊም አድርገው የተቀመጡት ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ የህጠወጡ የመጅሊስ ፕሬዚደንት አጅነቢይ (ባዕድ) የሆነችን ሴት በእጅ ሰላምታ ሰጥተዉ ማቀፋቸው በሸሪዐው ዘንድ ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለውና ከአንድ የሃይማኖት መሪ የማይጠበቅ ትልቅ ስህተት ቀይ መስመር ነዉ🚫 አጅነቢይ ሴትን መንካት በአሏህ ዘንድ ከባድ ወንጀልና አካላዊ ቅጣትን የሚያስከትል ድርጊት ነው። ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦ ​«لَأَنْ يُطْعَنَ فِي رَأْسِ أَحَدِكُمْ بِمِخْيَطٍ مِنْ حَدِيدٍ خَيْرٌ لَهُ مِنْ أَنْ يَمَسَّ امْرَأَةً لا تَحِلُّ لَهُ» "ከእናንተ ከአንዱ ጭንቅላቱ ላይ በብረት መርፌ ቢወጋ አጅነቢ (ለእሱ ያልተፈቀደች) የሆነችን ሴት ከመንካት ይሻለዋል"። አጅነቢይ ሴትን መጨበጥ ወደ ትልቅ ጥፋት የሚወስድ የእጅ ወንጀል (ዚና) እንደሆነ ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም ሲናገሩ፦ ​«كُتِبَ عَلَى ابْنِ آدَمَ نَصِيبُهُ مِنَ الزِّنَى... فَالْيَدَانِ زِنَاهُمَا الْبَطْشُ» "በሰው ልጅ ላይ የዚና (የዝሙት) ዕድሉ ተጽፎበታል... የእጆች ዚና ደግሞ የማይፈቀድለትን(አጂነቢይ)መጨበጥ ነው"። ​ እውነተኛ የአሏህ ባሮችና ዑለሞቹ ከላይ የተጠቀሱትን ጥብቅ የሐዲስ ማስፈራሪያዎች በመፍራት፣ ከሴቶች ጋር በሚሆኑበት አጋጣሚ ሁሉ ዓይኖቻቸውን ይከልክላሉ፣ አንገታቸውን ይደፋሉ እንጂ እጃቸውን አይዘረጉም። ​ስለሆነም፣ ማንኛውም አካል በየተቋሙ ወይም በየስልጣኑ ማዕረግ ቢቀመጥ እንኳን፣ የነቢዩን ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም መንገድና የሐዲሱን ድንጋጌ ጥሶ አጅነቢይ ሴትን መጨበጥም ሆነ ማቀፍ በትክክለኛው የኢስላም ሚዛን ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው ትልቅ ስህተት ነው። AI ነዉ የሚሉ መንጋዎችም አይጠፉ እኮ ደግሞ እዚህ መጥተዉ!! Maida Ahmed ቪድዮ እዚህ ተመልከቱ https://www.facebook.com/share/r/198d363Aw6/
498
9
ሰውን...መናፈቅ: ማዘን: መውደድ: ማመን: መቅረብ: መጠየቅ: ያቆማችሁ ከመሰላችሁ እራሳችሁን አጥብቃችሁ ፍሩት::🩶💔
453
10
አወይ ፍቅር! ረሱለላህም ﷺ እንባው የራህመት እንጂ አላህ ልጃቸውን ስለወሰደ እያማረሩ እንዳልሆነ በመንገር አፅናኗት። አስባችሁታል የእሳቸው ህልፈት እንዴት ሊያደርጋት እንደሚችል? ከእሳቸው መራቅ የማትፈልገው፤ ልጅነቷን እሳቸውን በማሳደግና በመንከባከብ ያሳለፈችው፤ ይህንን ምድር ከተቀላቀሉበት ጊዜ ጀምሮ ወደ አላህ እስከተጓዙበት ድረስ ከጎናቸው ያልተለየችው ምርጥ ሴት ከነፍሷ አስበልጣ የምትወዳቸውን እና የምትሳሳላቸውን ነብይ ﷺ ስታጣ፤ የዐይን ማረፊያዋ ከጎኗ ሲለዩ ተጫዋቿ በረካ ዝምተኛ ሆነች ይላሉ። መጫወት፤ መቀለድ አቆመች። የምትወዳቸውን ሰዎች በማጣት ውስጥ የኖረችው ኡሙ አይመን የሰይደል ውጁድﷺ ላይ ግን ጠናባት! አሳመማት። የፍቅር ነገር ከባድ ነውና። የናፍቆት ነገር ከባድ ነው! ❤️‍🩹 የሰይዲና አባበክርና ኡመርን ኺላፋ መመልከት ችላለች። ከሸፊዒﷺ ህልፈት በኃላ አባበክርና ኡመር ሊዘይሯት ወደቤቷ ይሄዳሉ። እንዳየቻቸውም በከፍተኛው ታለቅሳለች። እነርሱም ረሱለላህን አስታውሳ እያለቀሰች እንደሆነ ስለገመቱ: «ያ ኡሙ አይመን አታልቅሺ! እላይ ያለው ጉርብትና እዚህ ካለው የተሻለ ነው።» ይሏታል። አፍቃሪዋ በረካም እንዲህ ብላ ትመልሳለች: «አሁን የሄዱበት ስፍራ ከዚህ የተሻለ እንደሆነ አውቃለሁ፤ እኔን ያስለቀሰኝ ግን ከሰማይ የሚመጣው ወህይ በመቋረጡ ምክንያት ነው።» ብላ አለች። መልሷን ሲሰሙ ሁለቱም አብረዋት ማልቀስ ጀመሩ። 😭 ሰይዲና ኡመር መስጂዳቸው ውስጥ ከተ*ገደሉ ከሐያ ቀን በኃላ የሐበሻዋ እንቁ በረካ'ም ወደ አኺራ ተሸጋገረች። በቂዕ ላይም ተቀበረች። ኢብን አሳኪር እንዲህ ይላሉ: «ኡሙ አይመንን የቀበርናት ከረሱለላህﷺ ቀብር ትይዪ ባለው ቦታ ላይ ነበር።» በማለት የቀብሯን ቦታ እንኳን ምን ያህል እንደተጨነቁበት እና ለሸፊዒ ቅርብ ለማድረግ እንደሞከሩ እንመለከታለን። ሱብሓነላህ! ... ረዲየላሁ አንሃ ያ በረካ! ፈለግሽን የምንከተል ያድርገን። 💚 N.B: ከአመት በፊት በመልዕክተኛው ዙሪያ የነበሩ ሴቶች የሚል Booklet አዘጋጅቼ ነበር። እርሱ ላይ የዑሙ አይመንንም የሌሎች ሰሐቢያቶችን ታሪክ ማግኘት ትችላላችሁ። 📙سير أعلام النبلاء: جزء ٢، صفحة ٢٢٤، أم أيمن
552
11
«ከውልደታቸው እስከ ህልፈታቸው» ኡሙ አይመን: በረካ_ቢንት_ثዕለባ 💚 አብዱላህ ኢብን አብዱልሙጠሊብ ሲቲ አሚና'ን ሲያገቡ ባሪያዎች ከሚሸጡበት ንግድ ቦታ ከሐበሻ የመጣችውን የ13 አመቷን በረካ ቢንት ثዕለባ'ን ቤት ውስጥ ባለው ስራ ላይ አሚነትን እንድታግዛት ይገዟታል። አብደላህ ለንግድ ወደ ሻም ሲወጣም ከአሚና ጎን የነበረችው በረካ ነበረች። አሚነት የረሱለላህን መልካም ዜና በህልሟ ስትመለከት ለበረካ ነገረቻት። ምን እንደምታስብ'ም ጠየቀቻት። በረካም፡ «የተባረከ ልጅ እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለውም።» በማለት አባሸረቻት! ከሻም የሚመጡ ቅፍለቶችን ዜና አጣርታ ለአሚነት የምትነግራትም እቺው የሐበሻ እንቁ ነበረች። የአብዱላህን ማረፍ ከነገረቻት በኋላም አሚነት'ን መንከባከቧን ይበልጥ ጨመረች። አሽረፈል ኸልቅ ሲወለዱም ከአሚና ጎን የነበረችው፤ የዓለሙ ብርሓን ወደ ምድር ሲመጡ መጀመሪያ የተቀበለቻቸው የኛዋ በረካ ነበረች። ሐቢበላህንﷺ በልጅነታቸው እንደ እናት ከተንከባከበቻቸው ምርጥ ሴቶች መካከል ነች። ሲቲ አሚነት የሞት አፋፍ ላይ የደረሰች ሰዓት'ም ከጎኗ የነበረችው እሷ ነበረች። እናታቸው አሚነት በደከመ አንደበቷ ልጇ'ን ልክ እንደ እናት ሆና እንድትንከባከበው፤ በህይወቱ እንዳያዝን፤ ከጎኑ እንዳትለይ አደራ ብላት ያለፈችውም ለሐበሻዊቷ በረካ ነበር። ረሱል ﷺ ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ደግሞ አብዱልሙጠሊብ'ንም አጧቸው። በዚህ ሁሉ ክስተታቸው ውስጥ ከጎናቸው የማትለየው በረካ ነበረች። ረሱሉ ﷺ እናታችን ኸዲጃ'ን ካገቧት በኃላ በረካን ለኸዲጃ: "هي أمي بعد أمي" : «ከእናቴ በኃላ እናቴ ነች።» ብለው አስተዋወቋታል። ረሱሉ'ምﷺ በረካን ከባርነት ነፃ ስላደረጓት የግል ህይወቷን መኖር እንደምትችል ሊነግሯት እንዲህ አሏት፡ «ያ ኡማ! እኔ አሁን አግብቻለሁ፤ ልጅነትሽን ለኔ ስትይ መስዋዕት አድርገሻል። አሁን አንቺም ማግባት አለብሽ።» አሏት። የከውኑን ጀምበር በመኻደምና በመንከባከብ ህይወቷን ማሳለፍ የምትፈልገው በረካ ግን አሻፈረኝ አለች። እናታችን ኸዲጃ'ም «እኔ ምርጥ ሰው አስተዋውቅሻለሁ፤ የሰርግሽን'ም ወጪ እኔ እችላለሁ።» አለቻት። በተደጋጋሚ ሲጠይቋት ግን ጥያቄውን ተቀበለች። ዑበይድ ኢብን ዘይድ የሚባል የኸዝረጅ ጎሳ ሰው'ን ዳሯት። አይመን የሚባል ልጅም ወለደች። በዚህም ምክንያት ኡሙ አይመን የሚል ስያሜን አገኘች። 💚 ረሱለላህ ﷺ ወህዩ ሳይወርድላቸው በፊት የኡሙ አይመን ባል አረፈ። ኡሙ አይመን'ም ልጇ አይመንን ይዛ ወደ ረሱሉ ተመለሰች። ሸፊዑና ወህዩ እንደወረደላቸውም ከእናታችን ኸዲጃ ቀጥሎ እስልምናን የተቀበለች ሴት ሆነች። እርሳቸው የኡሙ አይመን ድጋሚ አለማግባት አሁንም ያሳስባቸው ጀመር። አንድ ቀን ሰሐቦችን ሰብስበው እንዲህ በማለት ጥሪ አደረጉ: «من سره أن يتزوج امرأة من أهل الجنة فليتزوج أم أيمن» «ከጀነት የሆነችን ሴት ማግባት የሚሻ ሰው ኡሙ አይመንን ያግባ።» ብለው አሉ! 💚 በረካ እድሜዋ ገፍቷል፤ ከሚታወቅ ቤተሰብ አልመጣችም። ሰሐቦች ግን ግቡ ጀነት የሆነ'ን ነገር ላይ ሁሉ ተሽቀዳዳሚዎች ነበሩና የ 20 አመት ታናሿ የሆነው የረሱለላህ ተወዳጅ ዘይድ ኢብን ሃሪሳ ይህንን ውድ ጥሪ ተቀበለ። ከዘይድ ጋር'ም ተጣመሩ። ኡሙ አይመን እድሜዋ በጣም ገፍቶ ስለነበር ልጅ ታገኛለች ተብሎ ባልታሰበበት ሁኔታ ላይ በአላህ ፍቃድ በረሱሉﷺ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ የሆነውን ዑሳማ ኢብን ዘይድን አገኘች። ሒጅራ መጣ፤ ይህን ሰዓት ኡሙ አይመን እድሜዋ ወደ 70 ይጠጋ ነበር ይላሉ። ወደ መዲና ባደረገችው ጉዞ ላይ'ም ድንቅ ነገር ተከስቶ ነበር። ልክ ሸፊዒﷺ ከባልደረባቸው አባበክር ጋር ሲጓዙ በረሐብ ምክንያት የሚበላ ነገር ለመጠየቅ ወደ ኡሙ ማዕበድ ቤት እንደዘለቁት፤ ኡሙ አይመንም በመንገዷ ላይ በውሃ ጥም ምክንያት ልትሞት እንደነበር ትናገራለች። «እጅግ ደካክሞኝ ፀሐዩ በሚጠልቅበት ሰአት ከጭንቅላቴ በላይ ከሰማይ የሆነ ውሃ መጣልኝ። ጥሜን እስክቆርጥ ድረስ ከውሃው ጠጣሁኝ። ቀሪውን ያቀዘቅዘኝ ዘንድ ሰውነቴ ላይ አፈሰስኩት። ከዛ ቀን አንስቶ በጣም ሞቃታማ በሆነ ጊዜ እፆማለሁ፤ ፀሐዩ በበረታ ጊዜም ጠዋፍ አደርጋለሁ አንድም ጊዜ ግን ጥም አስቸግሮኝ አያውቅም።» በማለት አላህ የዋለላትን ኒዕማ ትነግረናለች። 💚 ወደ መዲና ስትዘልቅ እግሯ ውሃ ቋጥሮ፤ ፊትዋም በአቧራ ተሸፍኖ ነበር። ረሱሊ እንደ እናታቸው የሆነችውን ታላቅ ሴት በዚህ ሁኔታ ሲመለከቱ «ያ ኡማ! አንቺ በእርግጥ በጀነት ቦታ አለሽ።» በማለት ደረጃዋን አረጋገጡላት አነስ ኢብን ማሊክ: «ኡሙ አይመን ረሱሉﷺ በተካፈሉበት እያንዳንዱ ዘመቻ ላይ ተሳትፋለች። በእያንዳንዱ አንቅስቃሴ አይኗ ከእሳቸው ላይ አይነቀልም ነበር።» በማለት የእናትነት ባህሪዋን ይገልፃል። የኡሁድ ዘመቻ ላይ በዚያ ከባድ ሰዓትም ከረሱለላህﷺ ጎን ከነበሩ እንቁ ባልደረቦች መካከል ነበረች። ጎራዴ በማንሳት ከነፍሷ በላይ የምትወዳቸውን ነብይﷺ ለመከላከል ፊት ተሰልፋለች! 💚 ረሱሊﷺ ሲመለከቷት: «ሃዚሂ በቂየቱ አህሊ በይቲ» ይሉ ነበር። በእሳቸው ዘንድ የነበራት ደረጃ ይህ ነው የሚባል አይደለም። በየቀኑ ይዘይሯት ነበር። አንድ ቀን ረሱለላህﷺ እንደ ሌላው ጊዜ ሊዘይሯት ወደ ቤቷ ጎራ አሉ። «ያ ኡማ! እንዴት ነሽ?» ብለውም ጠየቋት። እሷም: «የአንቱ ሪሳላ(መልዕክት) ደህና እስከሆነ ድረስ እኔ ደህና ነኝ።» ብላ መለሰችላቸው። ምላሿ፥ «በእርጅና ምክንያት ሰውነቴ ደክሟል፤ እንደ ድሮው እንደፈለግኩ እየተንቀሳቀስኩ አይደለም።» አልነበረም። የፍቅር ነገር የሚገርም እኮ ነው 💚 ኡሙ አይመን ረሱለላህ ﷺ መዲና ከገቡ በኃላም እንደ እናት ሳትንከባከባቸው፤ ምግብ እየበሉ ነው አይደለም የሚለውን ሳትመለከት ቀናቶች አልፈው አያውቁም። አነስ ኢብን ማሊክ ባስተላለፉት ታሪክ ላይ እንዲህ ይላሉ: «አንድ ቀን ረሱለላህ ﷺ ኡሙ አይመን ቤት ሲሄዱ፤ ቤት ያፈራውን ምግብ አቀረበችላቸው። እሳቸው ግን ለእራሷ የምትበላው አይኖራትም ብለው ስለሚያስቡ በልቻለሁ ይሏት ነበር። እሷም እንደ እናት በግድ እንዲበሉ ይዛቸው ታጎርሳቸው ነበር።» በማለት ውብ የሆነውን ትስስራቸውን ይዘግብልናል። አላህ አላህ ሐበሻ ጉድ ይዛለች! 🥰💚 ኡሙ አይመን ረሱለላህን ﷺ ፈገግ ከሚያሰኙ ሴቶች መካከልም ነበረች። ከሐበሻ እንደመምጣቷ ዐረበኛዋ የሚሰባበርበት እና ማለት የምትፈልገውን ትርጉም የሚቀይርበት ሁኔታ ነበር። "ሰላሙላህ አለይኩም" ለማለት "ሰላም- ላ- አለይኩም" ስትላቸው ሸፊዒﷺ ፈገግ ይሉና "አስ-ሰላም" ብቻ በዪኝ አትጨናነቂ ይሏት ነበር። ዘመቻዎች ላይም ሰሐቦችን በቃላቶቿ ለማበርታት ትሞክር ነበርና የሑነይን ዘመቻ ላይ: «ثበተሏሁ አቅዳመኩም» እንደማለት «ሰበተሏሁ አቅዳመኩም።» ስትል ረሱለሏህ ወደ በረካ ዞር ብለው እንደተሳሳተች በፈገግታ ይነግሯታል! አብረዋት መቃለድን ያዘወትሩ ነበር። የኛዋ ኡሙ አይመን የረሱለላህﷺ ምቾት ነበረች። ✨💚 ነቢየላህﷺ የሚወዱትን ልጃቸውን ኢብራሒም'ን ያጡ ጊዜ ስቅስቅ ብለው ሲያለቅሱ እሷም አብራቸው እጅጉኑ ማልቀስ ጀመረች። ረሱለላህ ከእድሜዋ ጋርም የኡሙ አይመን ሁኔታ ስለሚያሳስባቸው ወደሷ ዞረው: «ያ ኡሙ አይመን! ለምንድነው የምታለቅሺው?!» አሏት። አፍቃሪያቸው በረካ'ም «እርሶ እያለቀሱ እየተመለከትኩ እንዴት አላለቅስም?» ብላ መለሰች። አደራ አለባታ! የእናታቸው አሚና አደራ። በህይወታቸው ውስጥ ሐዘን እንዳይነካቸው የበኩሏን ለማድረግ ቃል የገባችበት አደራ! ...
510
12
አሕመዲን ጀበል የመጅሊሱን ፕሬዝዳንት "ተሳስተዋል" ማለቱ የሚደነቅ ነው። እንደሚታወቀው ጀበሉ የፕሬዝዳንቱ ማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ ነው። አንድ አማካሪ ÷ አለቃው ስህተት እንደፈጸመ መናገሩ በአገራችን ከስንት አንዴ የምናየው ክስተት ነው። ይህ ለሌሎች ቤተ-እምነቶች አርአያ መሆን የሚችል ድንቅ ተግባር ነው። በነገራችን ላይ አባባ ሐጂ ባሌ የሄዱት የአካባቢውን ወጣቶች መከላከያ ሰራዊትን እንዲቀላቀሉ ለመገፋፋት እያሉ ሲጽፉ የነበሩ አሉ። ይህ ግን ውሸት ነው። በዚሁ አጋጣሚ ለመግለጽ ያህል ነው። ወደ አሕመዲን ጽሑፍ ስንመለስ ፤ የመጅሊሱ ፕሬዝዳንት "ወልይ" የሚል ቃል የወጣቸው ፤ በሶፍ ዑመር ዋሻ እድሳትና ልማት በመደሰታቸው ነው ብሏል። የአሕመዲን ጀበል ትንታኔ "አባባ ሐጂ ጠ/ሚሩን ወልይ ለማለት ያበቋቸው የሶፍ ዑመርን ዋሻ ከተደበቀበት በማውጣት አድሰው ለዓለም ስላሳዩ መሆኑን ይናገራል። ➤ በመጀመሪያ ደረጃ ሶፍ ዑመር ዋሻ በዩኔስኮ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ቀድሞውንም ኖሮ የተገኘ እንጂ የተደበቀ ዋሻ አልነበረም። በዩኔስኮ ዓለም አቀፍ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ የገባው ደግሞ በኢህአዴግ አገዛዝ ዘመን ፤ በ2004 ዓ.ም ነው። ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ ወደ ሥልጣን ከመምጣታቸው ስድስት ዓመት በፊት መሆኑ ነው። ስለዚህ! ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ጠ/ሚሩ ዋሻውን ከተደበቀበት አውጥቶ ለዓለም አሳይቷል የሚለው ንግግራቸው ሙሉ ለሙሉ ስህተት ነው። ልብ-በሉ! ጠ/ሚሩ በመጅሊሱ ፕሬዝዳንት አንደበት "ወሊይ" ለመባል ያበቃቸው ሶፍ ዑመር ዋሻን ከተደበቀበት አውጥተው ለዓለም በማሳየታቸው እንደሆነ ከንግግራቸው መረዳት ይቻላል። የአባባ ሐጂ ኢብራሂም ስህተት የሚጀምረው እዚህ ጋር ነው። ሶፍ ዑመር ዋሻ የተገኘው ከዐቢይ አገዛዝ ዘመን በፊት እንደሆነ ከላይ ጠቅሻለሁ። ስገምት በጉብኝት ወቅት አስጎብኚው (tour guide) የተሳሳተ ታሪካዊ መረጃ ሳይሰጣቸው አይቀርም። ➤ እንደው ለክርክር ያህል ታሪካዊውና ውቡ ዋሻ በዐቢይ አገዛዝ ዘመን ተገኘ እንበል። በብልጽግና አገዛዝ ዘመን መገኘቱ ፤ ዐቢይን በወሊይነት ለመወሰፍ ያበቃን? አሁን ላይ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ ሶፍ ዑመርን በሚያምር መልኩ እያደሱት ይገኛሉ። ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ እየጣሩ ነው። "ታላቅ ልማት" አድርገን እንውሰድላቸው። አንድ መሪ ታላቅ የሆነን ልማት ስላበረከተ "ወሊይነት" ይሰጠዋል? በቁርዓን ለወሊይነት መስፍርቱ ኢማንና ተቅዋ እንደሆነ የሚጠፋው ያለ አይመስለኝም። ከመች ጀምሮ ነው "ልማት" ማበርከት ለወሊይነት መስፈርት የሆነው? አሕመዲን ጀበል የአባባ ሐጂን ስህተት ለማቃለልና በደስታ ስካር የተነገረ እንደሆነ ለማደባበስ አንድ ሐዲስ መምዘዙን በመጣጥፉ ገልጿል። But ጀበሉ ከአጠቃላይ ጽሑፉ መንፈስ ጋር የሚጋጭ ትንታኔ እያቀረበ መሆኑን የዘነጋው ይመስላል። ራሱ በመጣጥፉ ላይ እንዲህ ብሏል :- "የመንግስትን የልማት ስራዎች ማድነቅ እንዳለ ሆኖ፤ እንደ ‘ነብይ’ እና ‘ወልይ’ ያሉ ጥልቅ እምነታዊ ፅንሰ-ሀሳቦችንና መንፈሳዊ ማዕረጎችን ለፖለቲካ ውዳሴ መጠቀም ፈጽሞ ተገቢ አይደለም።" በአንድ በኩል የመጅሊሱ ፕሬዝዳንት ንግግር ለፖለቲካ ውዳሴ የቀረበ እንደሆነ እየገለጸ ፤ በሌላ በኩል የአባባ ሐጂ ስህተት ምንጩ "የበረታ ደስታ" ነው ማለት ምን ለማለት ይሁን? ለፖለቲካ ውዳሴ የቀረበን ሙገሳ ፤ በደስታ ብዛት የወጣቸው ቃል ነው ብሎ መበየን እርስ'በርሱ አይጋጭም? ከመዘዘው ሐዲስ እንደምናየው ፤ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) አንድ ባሪያ በተውበት ወደ እርሱ ሲመለስ የሚደሰትበትን መጠን ለመግለጽ የሰጡት ምሳሌ እናገኛለን። "ከእናንተ አንዱ ምግብና መጠጡን የጫነችበት ግመሉ ምድረ በዳ ላይ ጠፍታበት፣ ፍለጋ ደክሞትና ተስፋ ቆርጦ የአንድ ዛፍ ጥላ ስር ተኝቶ ሳለ፣ ድንገት ከነጭነቷ አጠገቡ ቆማ ሲያገኛት ከሚሰማው ደስታ በላይ ነው" በማለት ይገልጹታል። እንዲሁም ሰውየው ከደስታው ብዛት የተነሳ ልጓሟን እንደያዘ ‘አላህ ሆይ! አንተ ባሪያዬ ነህ፤ እኔም ጌታህ ነኝ!’ አለ፤ ከደስታው ከደስታው ብርቱነት የተነሳም አንደበቱ ተሳሳተ ብለዋል ረሱል (ሰዐወ). ➤ ይህ ሐዲስ ግን "ነቢይና ወሊይን" አማርጠው ለተናገሩት አባባ ሐጂ የሚበጅ መከራከሪያ አይመስለኝም። ከጅምሩ በደስታ የሚያሰክርስ ምን ተገኝቶ ነው? መቼም የሶፍ ዑመር እድሳት አትሉኝማ?😁 ሀቁ ግን ወዲህ ነው። የመጅሊሱ ፕሬዝዳንት ንግግር ለፖለቲካ ውዳሴ የቀረበ መንፈሳዊ ሙገሳ እንጂ በደስታ ስካር ያወጡት ቃል ፈጽሞ አይደለም። ቃላትን መርጠው "ነቢይ እንዳልለው ... " እያሉ የተናገሩ ናቸው። አማርጠውና አስበውበት እንደሆነ ግልጽ ነው። "የስህተታቸው ምንጭ በኔ መረዳት ደስታ ነው" የሚለው የጀበሉ መከራከሪያ ፍጹም ስህተትና ያልተገባ ንጽጽር ነው። የሶፍ ዑመር ልማትና እድሳት ማየታቸው በደስታ የሚያስፈነድቅም ÷ የሚያሰክርም አይደለም። ይህ ለእሳቸው ክብረ-ነክ መከራከሪያ ነው። ያም ሆነ ይህ የአባባ ሐጂ ንግግር ሙስሊሙን ህብረተሰብ ያሳዘነ ሆኖ አልፏል። ደስ የሚለው ነገር ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በሚባል መልኩ ንግግራቸውን አውግዟል። ተችቷል። ይህ የዑማው መለያ ነጸብራቅ ሆኖ መቀጠል አለበት። ይልመድብን ለማለት ያህል ነው
455
13
ወልያ (وَلِيَّة)! የአዲስ አበባ ቁጥብ 💔
ወልያ (وَلِيَّة)! የአዲስ አበባ ቁጥብ 💔
506
14
በሻሻው ወሊይ 🙂
በሻሻው ወሊይ 🙂
544
15
ኧረ 🤦‍♀️ 😂😂😂😂
ኧረ 🤦‍♀️ 😂😂😂😂
542
16
ከነቢ ሙሐመድ صلى الله عليه وآله وسلم ጋር መላኢካው ጂብሪልን እንኳ አናወዳድርም:: ነቢ ሙሐመድን صلى الله عليه وسلم ለማወዳደር ቀርቶ ለማወደስ ውዱእ አድርገንም የማይቻል ነው:: በየቤታችን ለልጆቻችን ስም ስናወጣ ሙሐመድ ብለን ስናበቃ በምንቆጣቸው ወቅት የሚያገለግል ሌላ ስም እንጨምርላቸዋለን ወይም እጥፍ እናደርገዋለን:: ሙሐመድ የሚል ስም የያዘን ልጅን መቆጣት እንኳ ከባድ ነው:: የነቢያችንን صلى الله عليه وعلى ክብር ልብህ ውስጥ ሲቀል ልብህን ፈትሽ::
563
17
እኛ አያገባንም በአንተ ሂወት ነገር ግን የማትሰሩትን አትቀባጥሩ ለማለት ነዉ?!! ፎቶ ሐራም ነዉ ብለዉ ፈትዋ ይሰጡና የፎቶ ተነሺዎች አለቃ ሆነዉ እናያቸዋለን! ኒቃብ መልበስ ዋጂብ(ግዴታ) ነዉ ይሉ
እኛ አያገባንም በአንተ ሂወት ነገር ግን የማትሰሩትን አትቀባጥሩ ለማለት ነዉ?!! ፎቶ ሐራም ነዉ ብለዉ ፈትዋ ይሰጡና የፎቶ ተነሺዎች አለቃ ሆነዉ እናያቸዋለን! ኒቃብ መልበስ ዋጂብ(ግዴታ) ነዉ ይሉና ልክ 5 ወቅት ሶላት እንደመስገድና ረመዷን ፆም እንደመፆም ማለት ነዉ ዋጂብ ነዉ ሲሉን ነገር ግን የራሳቸዉ ሚስቶችና እህቶች ሱና የሆነዉን ኒቃብ ሊለብሱ ቀርቶ ሸሪዓህ ዋጂብ ያደረገባቸዉን ዐዉራቸዉን(ከፊትና ከመዳፋቸዉ ዉጭ) ያለዉን ሰዉነታቸዉን ገላልጠዉና በሜካፕ ለዚያዉም በአርቲፊሻል ጥፍር ተኳኩለዉ ብቅ ይላሉ!!! ወልዒያዙቢላሂ ተዓላ!! እናንተም ሆናችሁ የዉሀብያ አስተምህሮት ወሏሂ ኢስላምን አይወክልም!! ኢስላም ከእናንተ የፀዳ ነዉ አልሐምዱሊላህ። የዉ*ሀ*ብያ አለም ዓቀፉ ኡስጣዝ ሁሱ ሚስትና ሰርጉ። የሚታሸቅበትም ቪድዮ ደርሶኛል ይለቀቅ!??
575
18
አቤት ሀዲስ አመዛዘዝ ፣ አቤት አሳሳብ😔 አሁን ላይ ግልጽና እልም ያለ ስህተት እየታየ፣ በማይሆን ሐዲስና የተዛባ ትንተና እየደገፉ ፤ የሐይማኖትና የሞራል ልክና ስህተትን የመለየት አቅማችንን ዜሮ
አቤት ሀዲስ አመዛዘዝ ፣ አቤት አሳሳብ😔 አሁን ላይ ግልጽና እልም ያለ ስህተት እየታየ፣ በማይሆን ሐዲስና የተዛባ ትንተና እየደገፉ ፤ የሐይማኖትና የሞራል ልክና ስህተትን የመለየት አቅማችንን ዜሮ አርገው ለደጃል ፓስ ሊያረጉን ነው ቆርጠው የተነሱት😭
559
19
የተከበሩ ሀጅ ሀጂ ኢብራሂም የተናገሩትን የሆኑ የሰሜን ሸይኽ ተናግረውት ቢሆን ኖሮ አመዲን ጀበል የሚጽፋቸው ተከታታይ ጽሑፎች:- - ጠምጣሚ ካድሬና አጠማጠሙ - ወልይና ጫት አቃቃሙ - ማኅበረ ቅዱሳንና ወልይነት - ጴ^ንጤና ነብይነት - የኢዩ ጩፋ ደረሳዎች - የዳንሳ አዳናሾች - የወልዮችና የደብተራዎች ደብተር ሲገለጥ - ኒፋ^ቅና ሙና-ፊቆች በመጅሊስ ግቢ ውስጥ የሚሉ ብዙ ጽሑፎችን እናይ ነበር:
539
20
33 መስጂድ ቁ^ማር አስይዘው በር አስገንጥለው የምእመኑን ብር ወለድ በነጻ ብለው እየገ^ነጠሉ ያሉ የብር ባሪያዎች ዶክተር ዐብይን ወደ ነብይነት ዝቅ ማድረጋቸው የሆነ ችግር ሳይኖር አይቀርም:: ከዚ
33 መስጂድ ቁ^ማር አስይዘው በር አስገንጥለው የምእመኑን ብር ወለድ በነጻ ብለው እየገ^ነጠሉ ያሉ የብር ባሪያዎች ዶክተር ዐብይን ወደ ነብይነት ዝቅ ማድረጋቸው የሆነ ችግር ሳይኖር አይቀርም:: ከዚህ በፊት አደም ካሚል "ዶክተር ዐብይ የሰጡንን ዕድል ነቢ ሙሳ ነቢ ዒሳና ነቢ ሙሐመድ ቢመጡ የማናገኘው ነው" ብሎ ተሸማቀን ቆየን:: ሀጅ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ዶክተር ዐብይ የነብይነት ደረጃ ቢደርሱም ከነቢ ሙሐመድ በሗላ ሌላ ነብይ ስለሌለ ወልይ ነው ብለዋል:: እንዴት ለዶክተር ዐብይ ይሰጡት የነበረውን ክብር በዚህ ደረጃ ዝቅ እንዳደረጉ አልገባኝም:: ከሦስት ነብይ በላይ ነው ያሉትን ሰው ዛሬ ተራ ወልይ ማድረጋቸው ፖለቲካዊ አንድምታው ብዙ ነው:: ቶሎ አርመው ከአምስቱ ታላላቅ ነቢያት "ኡሉልዐዝም" በላይ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል:: አመዲን ጀበል ነቢ ሙሐመድ ሰለምቴ ናቸው ብሎ ምእመኑ ቅምም ሳይለው አልፎ የለ? ያስተባበለበት መንገድ ደግሞ ይብስ ይሰቀጥጣል:: ጀነት በብር እንጂ በዱዓና በሶላት እንደማይገኝ በሚዲያ የለፈፉ በዚህም የሚኮሩ ሰዎች ዛሬ ላይ እንዴት ጠቅላይ ሚኒስትሩን ወደ ተራ ወልይነት ያወርዱታል? መንግሥት ጋር ያልተመቻቸው ነገር አለ:: አያያዛችሁን ጠንከር አድርጉ:: ___ አላሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዐላ ሰዪዲና ወነቢዪና ሙሐመድ ወዓላ አሊሂ ወአስሃቢሂ via Hassen Injamo
661