ar
Feedback
Ethio - ዜና 🇪🇹

Ethio - ዜና 🇪🇹

الذهاؚ إلى القناة على Telegram

ዚመሚጃዎቜ ቁንጮ ዹሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞቜዎ እና ቀተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታቜሁን ገጻቜን ላይ ለማስተዋወቅ ኹፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot

إ؞هار المزيد

📈 ن؞رة تحليلية على قناة تيليجرام Ethio - ዜና 🇪🇹

تُعد قناة Ethio - ዜና 🇪🇹 (@ethio_zena23) في القطاع اللغوي Amharic لاعؚاً ن؎طاً. يضم المجتمع حالياً 104 475 م؎تركاً، محتلاً المرتؚة 72 في ف؊ة صور والمرتؚة 285 في منطقة Ethiopia.

📊 م؀؎رات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في МевіЎПЌП، حقق الم؎روع نمواً سريعاً وجمع 104 475 م؎تركاً.

ؚحسؚ آخر الؚيانات ؚتاريخ 01 أغسطس, 2026، تحاف؞ القناة على ن؎اط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء ؚمقدار -2 616، وفي آخر 24 ساعة ؚمقدار -70، مع ؚقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يؚلغ متوسط تفاعل الجمهور 3.21‎%. وخلال أول 24 ساعة من الن؎ر يحصد المحتوى عادةً 2.29‎% من ردود الفعل نسؚةً إلى إجمالي الم؎تركين.
  • وصول المن؎ورات: يحصل كل من؎ور على متوسط 3 358 م؎اهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 398 م؎اهدة.
  • التفاعلات والاستجاؚة: يتفاعل الجمهور ؚانت؞ام؛ متوسط التفاعلات لكل من؎ور يؚلغ 24.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف الم؀لف القناة ؚأنها مساحة للتعؚير عن الآراء الذاتية:
“ዚመሚጃዎቜ ቁንጮ ዹሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞቜዎ እና ቀተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታቜሁን ገጻቜን ላይ ለማስተዋወቅ ኹፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot”

ؚفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث الؚيانات ؚتاريخ 02 أغسطس, 2026) تحاف؞ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُ؞هر التحليلات تفاعلاً ن؎طاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن ف؊ة صور.

104 475
الم؎تركون
-7024 ساعات
-6387 أيام
-2 61630 أيام
أر؎يف الم؎اركات
ዹ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጀት ይፋ ሆነ። በአማራ ክልል ዹ2018 ዚትምህርት ዘመን ዹ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጀት ይፋ ሆኗል።ኚሰኔ 3-5/2018 ዓ.ም ዹተሰጠውን ዹ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ
ዹ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጀት ይፋ ሆነ። በአማራ ክልል ዹ2018 ዚትምህርት ዘመን ዹ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጀት ይፋ ሆኗል።ኚሰኔ 3-5/2018 ዓ.ም ዹተሰጠውን ዹ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና 173,699 ተማሪዎቜ ውስደው ነበር። ፈተናውን ኚወሰዱት ተማሪዎቜ መካኚልም 135,003 (77.72%) ተማሪዎቜ 50% እና በላይ ውጀት አስመዝግበዋል። ተማሪዎቜም ውጀታ቞ውን https://amhara.ministry.et/#/result ዹሚለውን አድራሻ በመፃፍ ፀ በሚመጣው ቅጜ ላይ  ዚተማሪ መለያ ቁጥር (Registration Number) እና ስም በአማርኛ በማስገባት ፀ ዉጀት ይመልኚቱ (Check your result) ዹሚለውን ቁልፍ በመጫን ማዚት ይቜላሉ፡፡ በተጚማሪም @emacs_ministry_result_qmt_bot  ላይ መመልኚት ይቜላሉ። ተማሪዎቜ ማንኛውም ኚውጀት ጋር ዚተያያዘ ቅሬታ ካላ቞ው https://amhara.ministry.et/#/complaint ላይ በመግባት ቅሬታ቞ው ማቅሚብ እንደሚቜሉ ዹክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል። 2018 ዓ.ም ዹ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጀት ነገ ይፋ ይደሹጋል ተብሏል።

"ወደ አራት ኪሎ እንመለሳለን" ዹሚለውን ቅዠት በአስ቞ኳይ ማቆም ይገበዋል❗❗ "ግጭቱን ማንና መቌ እንደጀመሚው ለማወቅ አስቀድሞ ተዘጋጅቶ ዚወጣውን ዚኋላቀሩ ቡድን መግለጫ ኚመስማት ይልቅ፣ ገለልተኛ አካላት ዚሚያደርጉትን ዚሳተላይት ክትትልና ዚክትትሉን ውጀት መጠበቅ ተገቢ ነው"— ስምሚት ፓርቲ❗ ​በቀድሞ ዚህወሓት አመራሮቜ ዹተመሰሹተው ስምሚት ፓርቲ፣ ዚትግራይ ሕዝብ ዹማይፈልገውና ዹማይመኘው አዲስ ወታደራዊ ግጭት መኚሰቱን አስታወቀ። ፓርቲው ባወጣው መግለጫ፣ አሁን ዹተኹፈተው ጊርነት በውጭ ኃይሎቜ ፍላጎትና እቅድ ዚሚመራ መሆኑን በመጥቀስ ዚሁኔታው ምስጢር አስቀድሞ ዚታወቀ በመሆኑ እንቅስቃሎው ሳይስፋፋ ዚሚኚሜፍ እንደሆነና ዹዚህ አላስፈላጊ ግጭት ዋና ሰለባ እዚሆነ ያለው ዚትግራይ ወጣት መሆኑ ዚሚያሳዝን ነው ብሏል። ​ፓርቲው አክሎም፣ ቡድኑ ዚፕሪቶሪያውን ዹሰላም ውል በመጣስና ዚጊዜያዊ አስተዳደሩን ሥልጣን በኃይል ገልብጊ ህገ-ወጥ አስተዳደር ኹመሠሹተ በኋላ፣ አሁን ደግሞ "ግዛታዊ አንድነትን ማስኚበር" በሚል ሜፋን በውጭ ኃይሎቜ ተመክቶ አዲስ ጊርነት ደግሷል ሲል ኚሷል። ቀደም ሲል ሲካሄዱ ዚነበሩ ዚዛቻና ዚትምክህት መግለጫዎቜም ቡድኑ ለጊርነት ዹነበሹውን ኹፍተኛ ፍላጎት ዚሚያሳዩ በቂ ማስሚጃዎቜ እንደሆኑ አመልክቷል። ​በሌላ በኩል ዚፓርቲው መሪ አቶ ጌታ቞ው ሚዳ ለትግራይ ሠራዊት አመራሮቜና አባላት ባስተላለፉት መልዕክት፣ አመራሮቹ ዚተሻለ ወታደራዊ እውቀት አላቾው ተብሎ ስለሚታመን ለሕዝቡ ዹሚጠቅም ዹበሰለ ውሳኔ መወሰን እንደነበሚባ቞ው አስገንዝበዋል። ዚትግራይን ሕዝብ አንድነት በማበላሞትና በውጭ አካላት ተመክቶ ዹሚደሹግ ፎኚራ ሕዝብን ወደ ኹፋ አደጋ ኚመክተት ውጪ ዚሚያመጣው ለውጥ ዹለም ያሉት አቶ ጌታ቞ው፣ በግዳጅ ወጣቱን በመመልመል "ወደ አራት ኪሎ እንመለሳለን" ዹሚለውን ቅዠት በአስ቞ኳይ ማቆም እንደሚገባ ገልጞዋል። ​አቶ ጌታ቞ው አክለውም፣ ለሠራዊቱ አባላት ሊያሳስባ቞ው ዚሚገባው በጣት ዚሚቆጠሩ ወንጀለኞቜ ህልውና ሳይሆን ዚትግራይ ሕዝብ ሰላምና ህልውና በመሆኑ በሕይወታ቞ውና በአካላ቞ው ላይ ዚሚጫወቱ አካላትን "ይበቃል" ሊሏቾው እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። ዚሕዝቡ ዹመኖርና አለመኖር ህልውና ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ ብቻ ሊመለስ እንደሚቜል በመጠቆም፣ በሃውልቲ ዹመሾገው ቡድን ዚዲፕሎማሲ በሮቜን ዘግቶና ኹውጭ አካላት በሚጠበቅ እርዳታ ተመክቶ ሁኔታዎቜን ካበላሞ በኋላ "ዓለም ስማኝ" ማለቱ ዚአስተዋይነት ማነስን ዚሚያሳይ ነው ሲሉ ኮንነዋል።

“በብር ደመወዝ ዹሚኹፈላቾው ሰዎቜ ገቢያ቞ው እጅግ ቀንሷል”ፊ ዚቀድሞው ዹዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዹ #ኢትዮጵያ ዚምንዛሬ ሪፎርም ድህነትን አባብሷል አሉ ዚቀድሞው ዹዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዎቪድ ማልፓ
“በብር ደመወዝ ዹሚኹፈላቾው ሰዎቜ ገቢያ቞ው እጅግ ቀንሷል”ፊ ዚቀድሞው ዹዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዹ #ኢትዮጵያ ዚምንዛሬ ሪፎርም ድህነትን አባብሷል አሉ ዚቀድሞው ዹዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዎቪድ ማልፓስ ዚኢትዮጵያ ብር መዳኚም እና ዹውጭ ምንዛሬ ማሻሻያዎቜ ድህነትን በኹፍተኛ ሁኔታ ማባባሳ቞ውን በመግለጜፀ በብር ደመወዝ ዹሚኹፈላቾው ሰዎቜ «ገቢያ቞ው እጅግ ቀንሷል» ሲሉ ተናግሚዋል። በተቃራኒው ጥቂት ቡድኖቜ ዹውጭ ምንዛሬን እና ዹሀገር ውስጥ ብድርን በልዩ ሁኔታ ማግኘት በመቻላ቞ው ተጠቃሚ መሆናቾውን ጠቁመዋል። ማልፓስፀ ስታንሊ ፊሾር መታሰቢያ በተሰኘ መድሚክ ላይ ባቀሚቡት ዚፖሊሲ ጥናት ላይ ኢትዮጵያን በዋና ምሳሌነት ዹተጠቀሙ ሲሆን፥ ሀገሪቱ ዚእርሻ መሬት፣ ዚተፈጥሮ ሀብት፣ ዚውኃ፣ ተስማሚ ዹአዹር ንብሚት እና ዹሰው ኃይል አቅም ያላት በመሆኗ «ትልቅ ዚእድገት አቅም» ያላት ሀገር እንደሆነቜ ገልጞዋል። ዹዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ውስጥ ወደ 200 ዹሚጠጉ ፕሮጀክቶቜን በገንዘብ መደገፉንና 43ቱ አሁንም በሂደት ላይ እንደሚገኙ ዚጠቆሙት ማልፓስፀ ሆኖም ዚሀገሪቱ ዚነፍስ ወኹፍ ገቢ አሁንም 1,100 ዶላር አካባቢ በመሆኑ «ኚዓለም ደሃ ሀገራት አንዷ» አድርጓታል ብለዋል።

ትርፍ አንጀት ምንድን ነው? በተለምዶ ትርፍ አንጀት እዚተባለ ዚሚጠራው ቜግር ዹሚኹሰተው አፔንዲክስ (ትርፍ አንጀት) ሚባለው ትንሜ ዚአንጀት አካል ሲያብጥ ወይም ሲቆጣ ነው። ይህ ቜግር በፍጥነት ካል
ትርፍ አንጀት ምንድን ነው? በተለምዶ ትርፍ አንጀት እዚተባለ ዚሚጠራው ቜግር  ዹሚኹሰተው አፔንዲክስ (ትርፍ አንጀት) ሚባለው ትንሜ ዚአንጀት አካል ሲያብጥ ወይም ሲቆጣ ነው። ይህ ቜግር በፍጥነት ካልታኚሙ ሊፈነዳ እና አደገኛ ኢንፌክሜን ሊያስኚትል ይቜላል። ዚትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ምንድን ነው? ዚትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ትርፍ አንጀት ለማስወገድ ዹሚደሹግ ቀዶ ጥገና ሲሆን ለትርፍ አንጀት ቜግር በጣም ዹተለመደው ሕክምና ነው። ቀዶ ሕክምናው በክፍት (open) መንገድ ወይም በላፓሮስኮፒ ሊሰራ ይቜላል። 🚚 ዚትርፍ አንጀት አደገኛ ምልክቶቜ፡ 👉 ኚታቜ በቀኝ በኩል ባለው ዚሆድ ክፍል ላይ ድንገተኛ እና ኚባድ ህመም ፣ 🔹ማቅለሜለሜ እና ማስታወክ ፣ 🔹ትኩሳት እና ብርድ ብርድ ማለት፣ 🔹 ዚምግብ ፍላጎት ማጣት እና 🔹 በእንቅስቃሎ ዚሚባባስ ህመም ሲኖር በፍጥነት ወደ ህክምና መሄድ ያስፈልጋል። ✹ ዚትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ለምን ያስፈልጋል? ✅ ትርፍ አንጀት እንዳይፈነዳ እና ✅ ኚባድ ኢንፌክሜን እንዳይፈጠር እንዲሁም ✅ በፍጥነት ለማገገም ይህ ቀዶ ህክምና ያስፈልጋል። ኚቀዶ ጥገናው በኋላ ምን ማድሚግ ያስፈልጋል? 🔹 በቀላሉ ሊፈጩ ዚሚቜሉ ምግቊቜን መመገብ፣ 🔹 ሹጋ ያለ እንቅስቃሎ ማድሚግ፣ 🔹 እሚፍት ማድሚግ እና 🔹 ውሃ በደንብ መጠጣት ቶሎ ለማገገም ይሚዳል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23

ዚጊርነት ውጀት አስኚፊ ነው‌ ዛሬ በሞሚሪና ዹተፈፀመው እልቂት ዘግናኝ ነው። ዚህወሓት አርሚ 70 ታጣቂዎቜ በሞሚሪና ግንባር ወደ ሁመራ ለመግባት ጥቃት ዚፈፀሙት ኚታቜ ዚተዘሚዘሩትን ሎጀስቲክ፣ዚሰው
+1
ዚጊርነት ውጀት አስኚፊ ነው‌ ዛሬ በሞሚሪና ዹተፈፀመው እልቂት ዘግናኝ ነው። ዚህወሓት አርሚ 70 ታጣቂዎቜ በሞሚሪና ግንባር ወደ ሁመራ ለመግባት ጥቃት ዚፈፀሙት ኚታቜ ዚተዘሚዘሩትን ሎጀስቲክ፣ዚሰው ሀይል እና መሳሪያ በመያዝ ነው። - ዙ-23       03 በፓትሮል ዚተጫነ - 107 ሮኬት   01 - ኮርኔት        02 - ሞርታር-120  01 - ሞርታር-82    01 - ሞርታር (ልዩ)  02 [በምርመራ ላይ ነው] - ድሜቃ          09 - ዚድሜቃ ሆ/እግር  01 - RPG            06 - ብሬን             54 - ስናይፐር          05 - ክላሜ            1347 - ሬድዮ            183 - ኊራል    02 - ፓትሮል  02 - ጄኔሬተር 02 ይህንን ጥቃት ተኚትሎ በአካባቢው ዹሚገኘው መኚላኚያ ሰራዊት በወሰደው ዹአፀፋ ጥቃት:- - ዹተማሹኹ   01 ሻለቃ አዛዥ - ዹተማሹኹ  141 ታጣቂ እና ዚተለያዚ ዚአመራር - ዹተገደለ እና ዹቆሰለ 1000+ መሆናቾውን ዚአዩዘሀበሻ ምንጮቜ አሚጋግጠዋል። ዚተለያዩ ትጥቆቜ፣ ዹሕክምና ቁሳቁስ፣ ተተኳሟቜ፣ ዚደሚት ትጥቆቜ፣ መድኃኒቶቜ፣ ዚመኪና መለዋወጫ፣ ነዳጅ ዘይትን ጚምሮ ዚጥይት ዎፖዎቜ በቁጥጥር ስር ዹዋሉ ሲሆን ሞሚሪና እና  አካባቢው ሙሉ ለሙሉ በመኚላኚያ ቁጥጥር ስር መሆኑ ተሚጋግጧል። በዚሁ በቃ ይበለን።

አሳዛኝ ነው‌ በሞሚሪና አቅጣጫ ዚህወሓት አርሚ 70 በመኚላኚያ ሰራዊት ላይ ጥቃት መፈፀማቾውን ተኚትሎ መኚላኚያ ሰራዊት በሜካናይዝድ ጩር ዹአፀፋ ምላሜ እዚሰጠ ይገኛል። አንድ ዹአርሚ 70 አባል 'ኑ ቁስለኛ እናንሳ' ሲል ይሰማል። ጊርነት ይብቃ🕊🕊🕊

ተራዝሟል‌ በመዲናዋ ዚመኖሪያ ቀት አኚራይ ተኚራይ ውል እድሳት ጊዜ ተራዘመ። ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚመኖሪያ ቀት አኚራይ ተኚራይ ውል እድሳት እስኚ ነሐሮ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ተራዝሟል
ተራዝሟል‌ በመዲናዋ ዚመኖሪያ ቀት አኚራይ ተኚራይ ውል እድሳት ጊዜ ተራዘመ። ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚመኖሪያ ቀት አኚራይ ተኚራይ ውል እድሳት እስኚ ነሐሮ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ተራዝሟል፡፡ ኹተማ አስተዳደሩ እስኚ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲካሄድ አስታውቆት ዹነበሹውን ዚቀት ኪራይ ውል እድሳት ነው እስኚ ነሐሮ 30 ቀን 2018 ያራዘመው፡፡ ዹኹተማ አስተዳደሩ ዚዜጎቜን ዚኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ ዚሚስተዋሉ ሕገ ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮቜን በዘላቂነት ለመግታት ዚቀት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11 ነጥብ 5 በመቶ እንዲሆን መወሰኑ ይታወቃል፡፡ ይህንን ተኚትሎ በመላው ኹተማዋ ዹሚገኙ ዹግል መኖሪያ ቀቶቜ ዚአኚራይ ተኚራይ ዹውል እድሳት ምዝገባ ጊዜ እስኚ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ዹነበሹው እስኚ ነሐሮ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድሚስ መራዘሙን ቢሮው አስታውቋል። ዹውል እድሳት ጊዜው በሕብሚተሰቡ ጥያቄ መሰሚት ዚተራዘመ ሲሆን ÷  ይህም ነዋሪው ያለምንም መጹናነቅ እንዲዋዋል ያስቜላል፡፡ ነዋሪው በሁሉም ክ/ኹተማ ቀቶቜ አስተዳደር ጜ/ቀት ፀ በዚወሚዳው በተዘጋጁ ዹውል ቊታዎቜ እና በሁሉም ክ/ኹተማ አዲስ መሶብ ዚአንድ ማዕኹል አገልግሎት አስፈላጊውን መሹጃ በመያዝ አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚቜል መገለጹን ዚቢሮው መሹጃ አመልክቷል፡፡

ሰበር ዜና በኢትዮ ሱዳን ድንበር መጠነ ሰፊ ውጊያ ተኚፈተ፡፡ ውጊያ ኚማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ዹተቀሰቀሰ ሲሆንፀ ኚበሚኞት እስኚ ሞሚሪና ዚኚባድ መሳሪያ ድምጜ በስፋት እንደሚሰማ ምንጮቜ አሹጋግጠዋል
ሰበር ዜና በኢትዮ ሱዳን ድንበር መጠነ ሰፊ ውጊያ ተኚፈተ፡፡ ውጊያ ኚማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ዹተቀሰቀሰ ሲሆንፀ ኚበሚኞት እስኚ ሞሚሪና ዚኚባድ መሳሪያ ድምጜ በስፋት እንደሚሰማ ምንጮቜ አሚጋግጠዋል፡፡

በምዕራብ ትግራይ "አዲስ ግጭት መቀሰቀሱን" ዚትግራይ ባለሥልጣናት ገለጹ! ዚትግራይ ባለሥልጣናት ዚኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት በምዕራብ ትግራይ “አዲስ ወታደራዊ ጥቃት ኚፍቷል” ሲሉ ኚሰሱ። ግጭቱ ቅዳ
በምዕራብ ትግራይ "አዲስ ግጭት መቀሰቀሱን" ዚትግራይ ባለሥልጣናት ገለጹ! ዚትግራይ ባለሥልጣናት ዚኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት በምዕራብ ትግራይ “አዲስ ወታደራዊ ጥቃት ኚፍቷል” ሲሉ ኚሰሱ። ግጭቱ ቅዳሜ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ማለዳ በምዕራብ ትግራይ ዞን በሞሚሪና አቅጣጫ መጀመሩን ገልጞዋል። ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ዚሚመራው ዹክልሉ አስተዳደር ዛሬ á‰£á‹ˆáŒ£á‹ መግለጫ፥ á‹šáŒá‹°áˆ«áˆ መንግሥት በምዕራብ ትግራይ ዞን «ግልጜ ጊርነት ኚፍቷል» ሲል በመክሰስ ኹክልሉ ጋር ዹቆዹውን ፍጥጫ አባብሶታል ብሏል። «በትግራይ ሕዝብ ላይ ሲያካሂድ ዹቆዹውን አጠቃላይ እገዳ እና ኚበባ፥ እንዲሁም በድሮን እና በውክልና ዚትጥቅ ኃይሎቜ ዹሚፈጾሙ ጥቃቶቜን በማባባስ ዚብልፅግናው ሥርዓት ግልጜ ጊርነት ኚፍቷል» ሲል መግለጫው ገልጿል። በትግራይ ባለሥልጣናት ዹቀሹበው ይህ ክስ በፌደራል መንግሥቱ እና በክልሉ አስተዳደር መካኚል ለወራት ሲካሄድ ዹቆዹውን ዚፖለቲካ እና ዚወታደራዊ ውጥሚት ተኹተሎ ዚመጣ ነው። መግለጫው እ.ኀ.አ. በ2022 ዚፕሪቶሪያው ዚግጭት ማቆም ስምምነት ኹተፈሹመ ወዲህ ዚፌደራል መንግሥት «ዚተለያዩ ሎራዎቜን፣ እገዳዎቜን፣ ኚበባዎቜን እና ወታደራዊ ዝግጅቶቜን» ሲያካሂድ ቆይቷል ሲል ዹኹሰሰ ቢሆንም ማስሚጃ ግን አላቀሚበም።

በአሜሪካ ጥገኝነት ጠያቂዎቜ ያለ ቃለ-መጠይቅ ወደ ፍርድ ቀት ዚሚላኩበት መመሪያ ጞደቀ። ዚትራምፕ አስተዳደር በሀገሪቱ ጥገኝነት ዹጠዹቁ ስደተኞቜን ዚሚመለኚት አዲስ መመሪያ አውጥቷል። ይህን ተኚትሎ በርካታ ጥገኝነት ጠያቂዎቜ ጉዳያ቞ው ሳይሰማ ቀጥታ ሊባሚሩ ዚሚቜሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል። አዲሱ አሰራር ኹ1.4 ሚሊዮን በላይ ዚተኚማቹ ዚጥገኝነት ማመልኚቻዎቜን ለማቃለል ዚታሰበ ነው ተብሏል። ቀደም ሲል ዹነበሹው አሰራር አመልካ቟ቜ መጀመሪያ ጉዳያ቞ውን ለኢሚግሬሜን ኩፊሰር አቅርበው ጥያቄያ቞ው ውድቅ ኹተደሹገ ብቻ ወደ ፍርድ ቀት እንዲመሩ ዚሚያደርግ ነበር። በአዲሱ መመሪያ በርካታ ዚጥገኝነት አመልካ቟ቜ ኚኢሚግሬሜን ኊፊሰሮቜ ጋር ዹሚደሹገውን ዚመጀመሪያ ደሹጃ ቃለ-መጠይቅ ሳያደርጉ ጉዳያ቞ው በቀጥታ ወደ ፍርድ ቀት ሊመራ ይቜላል። 444,724 ያህል መዝገቊቜን ይነካል ዚተባለው ይህ ውሳኔ ዹሕግ ባለሙያዎቜና ዚኢሚግሬሜን ተኚራካሪዎቜ አሰራሩ ዚስደተኞቜን ዚመሰማትና ዚፍትህ ዚማግኘት መብት ዚሚጎዳና ውሳኔዎቜን በማፋጠን ሰዎቜን በፍጥነት ለማባሚር ያለመ ነው በማለት ተቜተውታል። በሌላ በኩል ፥ ዚአሜሪካ መንግሥት በሀገሪቱ በሚማሩ ዹውጭ ሀገር ተማሪዎቜ ላይ እስኚ 100,000 ዶላር ዚሚደርስ አዲስ ክፍያ ለመጣል ማቀዱ ተሰምቷል። ዚታቀደው እርምጃ በተለይ ትምህርታ቞ውን አጠናቀው በአሜሪካ ለመቆዚት ለሚፈልጉ ዓለም አቀፍ ተማሪዎቜ ፈተና ሊሆን እንደሚቜል ተገልጿል። መንግሥት እርምጃው ዚቪዛ አጠቃቀምን ለማጥበቅና ዹሀገር ውስጥ ዚሥራ ገበያን ለመጠበቅ ያለመ መሆኑን ሲገልጜ፣ ተቃዋሚዎቜ ግን ዹውጭ ተማሪዎቜ ለአሜሪካ ዚትምህርትና ቮክኖሎጂ ዘርፍ ያላ቞ውን አስተዋፅኊ ሊጎዳ ይቜላል በማለት ስጋታ቞ውን ገልጞዋል። ዚትራምፕ አስተዳደር ኚስደተኞቜ ጋር በተያያዝ እጅግ ጠንካራ እርምጃዎቜን እዚወሰደ መሆኑ ተደጋግሞ መገለጹ ይታወሳል።

አሊኮ ዳንጎ቎ ኚሃብታ቞ው ሲሶውን ለበጎ አድራጎት ድርጅት ሊያውሉት ነው። ዚአፍሪካ ቁጥር አንድ ባለሀብት ዚሆኑት ናይጄሪያዊው ቢሊዚነር አሊኮ ዳንጎ቎፣ ኚሀብታ቞ው ውስጥ አንድ ሊስተኛውን (35 ቢሊዮን
አሊኮ ዳንጎ቎ ኚሃብታ቞ው ሲሶውን ለበጎ አድራጎት ድርጅት ሊያውሉት ነው። ዚአፍሪካ ቁጥር አንድ ባለሀብት ዚሆኑት ናይጄሪያዊው ቢሊዚነር አሊኮ ዳንጎ቎፣ ኚሀብታ቞ው ውስጥ አንድ ሊስተኛውን (35 ቢሊዮን ዶላር ዚሚደርስ) ኃብታ቞ውን ለበጎ አድራጎት ሥራዎቜ ሊለግሱ መሆኑ ተገልጿል። ልጃቾው ፋጢማ ዳንጎ቎ በቅርቡ ኚብሉምበርግ ጋር በነበራት ቃለ-መጠይቅ ድጋፉን በስማ቞ው በተቋቋመው ፋውንዎሜን በኩል ለበጎ አድራጎት ሥራዎቜ እንደሚያውሉት ይፋ አድርጋለቜ።

አሐዱ ራዲዮ እና አርትስ ቲቪ ማስጠንቀቂያ ተሰጣ቞ው ዚኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለሁለቱ ሚዲያዎቜ ዚመጚሚሻ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን አስታውቋል። አሐዱ ኀፍ ኀም 94.3 እና አርትስ ቎ሌቪዥን
+1
አሐዱ ራዲዮ እና አርትስ ቲቪ ማስጠንቀቂያ ተሰጣ቞ው ዚኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለሁለቱ ሚዲያዎቜ ዚመጚሚሻ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን አስታውቋል። አሐዱ ኀፍ ኀም 94.3 እና አርትስ ቎ሌቪዥን ዚመጚሚሻ ማስጠንቀቂያ ዚተሰጣ቞ው፣ "ውል ዚገቡበትን ዚይዘት ግዎታዎቜ በመተላለፍ፣ ለተኚታታይ ጊዜ ያልተሚጋገጠ፣ ሚዛናዊ ያልሆነ እንዲሁም ዚሕዝብን ጥቅም ዚሚጎዳ መሹጃ በማሰራጚታ቞ው" ነው ተብሏል። ባለሥልጣን መስሪያ ቀቱ ኚሬድዮ እና ኚ቎ሌቪዥን ጣቢያዎቹ ኃላፊዎቜ ጋር "ተደጋጋሚ ዹህግና ዚሙያ ጥሰቶቜ" መፈጾማቾውን በተመለኚተ፣ ወይይት ቢደሚግም "ጉልህ ለውጥ ሳይታይ በመቅሚቱ" ማስጠንቀቂያ መስጠቱን አስታውቀዋል፡፡

ጥቆማ‌ ምንም ውሞት አልተቀላቀለበትም!! በትኩሱ ስለወቅታዊ ጉዳይ ፈጣን እና ታማኝ መሹጃ ለማግኘት ይሄንን ቻናል ዝምብላቹህ ተቀላቀሉ!! 👇👇👇 https://t.me/seledadotio https
ጥቆማ‌ ምንም ውሞት አልተቀላቀለበትም!! በትኩሱ ስለወቅታዊ ጉዳይ ፈጣን እና ታማኝ መሹጃ ለማግኘት ይሄንን  ቻናል ዝምብላቹህ ተቀላቀሉ!! 👇👇👇 https://t.me/seledadotio https://t.me/seledadotio

ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ኹነገ ጀምሮ ኹጎንደር ሁመራ ቋሚ በሚራ ይጀምራል ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ኹነገ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ኹጎንደር ወደ ሁመራ ቋሚ ዚበሚራ አገልግሎት ይጀመራል አ
ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ኹነገ ጀምሮ ኹጎንደር ሁመራ ቋሚ በሚራ ይጀምራል ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ኹነገ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ኹጎንደር ወደ ሁመራ ቋሚ ዚበሚራ አገልግሎት ይጀመራል አለ፡፡ በዚህም መሰሚት ዘወትር ቅዳሜ ኹጎንደር ወደ ሁመራ እንዲሁም ዘወትር ሰኞ ኚሁመራ ወደ ጎንደር ዚበሚራ አገልግሎት ይሰጣል። ዹሀገር ውስጥ በሚራ መዳሚሻዎቜን በማስፋት ሕዝብን ለማገልገል እንደሚራ ዹገለጾው አዹር መንገዱ ይህ ዚበሚራ አገልግሎት መጀመር ማኅበራዊ ግንኙነትን ኹፍ ያደርጋል ብሏል።

ዹ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጀት ይፋ ሆነ!! ​በኊሮሚያ ክልል ዹ1ኛ ደሹጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ዹ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ሰኔ 08 - 09/2018 ዓ.ም ተሰጥቶ ዹነበሹ ሲሆን፣ ዛሬ ዚተማሪዎቜ ውጀ
ዹ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጀት ይፋ ሆነ!! ​በኊሮሚያ ክልል ዹ1ኛ ደሹጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ዹ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ሰኔ 08 - 09/2018 ዓ.ም ተሰጥቶ ዹነበሹ ሲሆን፣ ዛሬ ዚተማሪዎቜ ውጀት ይፋ ሆኗል። ​👉 ዚማለፊያ ነጥብ 50% እና ኚዚያ በላይ እንዲሆን ተወስኗል። ​👉 ፈተናውን ኚተቀመጡ 517,209 ተማሪዎቜ ውስጥ ዚማለፊያ ነጥብ (50% እና ኚዚያ በላይ) በማስመዝገብ ወደ ሚቀጥለው ክፍል ዚተሞጋገሩት 464,839 (89.9%) ተማሪዎቜ መሆናቾው ታውቋል። ​ኚተፈተኑት ተማሪዎቜ መካኚል፡ 📍 ወንድ 267,307 ውስጥ 91.2% እና 📍 ሎት 249,902 ውስጥ 88.4% አልፈዋል። ​በዚሁ መሠሚት ውጀት ለማዚት ኹዚህ በታቜ ዹቀሹበውን ሊንክ በመክፈትፀ ዹመፈተኛ ቁጥርዎን (Registration Number) ማስገባትፀ ቀጥሎም ዚመጀመሪያ ስምዎን በማስገባት ውጀትዎን መመልኚት ትቜላላቜሁ።👇 ​ሊንክ፩ https://oromia6.ministry.et

በግል ትምህርት ቀቶቜ ዚክፍያ ጭማሪና ዚምዝገባ አሰራር ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እዚተደሚገ ነው፡- ዚአዲስ አበባ ትምህርትና ሥልጠና ቁጥጥር ባለስልጣን በ2019 ዓመተ ምህሚት ዚትምህርት ዘመን በግል ትምህ
በግል ትምህርት ቀቶቜ ዚክፍያ ጭማሪና ዚምዝገባ አሰራር ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እዚተደሚገ ነው፡- ዚአዲስ አበባ ትምህርትና ሥልጠና ቁጥጥር ባለስልጣን በ2019 ዓመተ ምህሚት ዚትምህርት ዘመን በግል ትምህርት ቀቶቜ በሚካሄደው ዚተማሪዎቜ ምዝገባ፣ ዚክፍያ ጭማሪና ዚግብዓት ጥያቄ ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እዚተካሄደ መሆኑን በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አስታወቀ:: ባለፉት ዓመታት ዹግል ትምህርት ቀቶቜ በወርሃዊ ክፍያ፣ በምዝገባ፣ በዩኒፎርም እንዲሁም በዓይነት በሚጠይቋቾው እንደ ሳሙና እና ሶፍት ባሉ ቁሳቁሶቜ ምክንያት በወላጆቜ ዘንድ ሰፊ ቅሬታ ሲነሳ መቆዚቱ ይታወሳል፡፡

ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት ይቀጥሉ ‌ - ዚአሜሪካ ሎኔት ዚአሜሪካ ዹህግ መወሰኛ ምክር ቀት (ዹላይኛው ምክር ቀት፣ ሎኔት)ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ ዚመውሰድ ስልጣና቞ው
ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት ይቀጥሉ ‌ - ዚአሜሪካ ሎኔት ዚአሜሪካ ዹህግ መወሰኛ ምክር ቀት (ዹላይኛው ምክር ቀት፣ ሎኔት)ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ ዚመውሰድ ስልጣና቞ውን ለማገድ ዹቀሹበውን ዚውሳኔ ሃሳብ በ 49 ለ 50 በሆነ በጠበበ ዚድምፅ ልዩነት  ውድቅ አደሚገ። ​በሮናተር ኪርስተን ጊሊብራንድ ዹቀሹበው ይህ ጥያቄ፣ ኮንግሚሱ ዚጊርነት አዋጅ ሳያወጣ ዚአሜሪካ ጩር በኢራን ውስጥ ዚሚያደርገውን ወታደራዊ እንቅስቃሎ እንዲያቆም ዹሚጠይቅ ነበር። ​ውሳኔው ውድቅ መደሹጉን ተኚተሎ፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በቀጣናው ላይ ያላ቞ው ወታደራዊ እርምጃ ዚመውሰድ ሙሉ ስልጣን እንደተጠበቀ ይቆያል። ​በድምፅ አሰጣጡ ላይ ሊስት ዚሪፐብሊካን ዓባላት ሃሳቡን ሲደግፉ፣ አንድ ዚዲሞክራቲክ አባል ደግሞ ተቃውሞ ድምፅ ሰጥቷል። ‎

ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት ይቀጥሉ ‌ - ዚአሜሪካ ሎኔት ዚአሜሪካ ዹህግ መወሰኛ ምክር ቀት (ዹላይኛው ምክር ቀት፣ ሎኔት)ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ ዚመውሰድ ስልጣና቞ው
ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት ይቀጥሉ ‌ - ዚአሜሪካ ሎኔት ዚአሜሪካ ዹህግ መወሰኛ ምክር ቀት (ዹላይኛው ምክር ቀት፣ ሎኔት)ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ ዚመውሰድ ስልጣና቞ውን ለማገድ ዹቀሹበውን ዚውሳኔ ሃሳብ በ 49 ለ 50 በሆነ በጠበበ ዚድምፅ ልዩነት  ውድቅ አደሚገ። ​በሮናተር ኪርስተን ጊሊብራንድ ዹቀሹበው ይህ ጥያቄ፣ ኮንግሚሱ ዚጊርነት አዋጅ ሳያወጣ ዚአሜሪካ ጩር በኢራን ውስጥ ዚሚያደርገውን ወታደራዊ እንቅስቃሎ እንዲያቆም ዹሚጠይቅ ነበር። ​ውሳኔው ውድቅ መደሹጉን ተኚተሎ፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በቀጣናው ላይ ያላ቞ው ወታደራዊ እርምጃ ዚመውሰድ ሙሉ ስልጣን እንደተጠበቀ ይቆያል። ​በድምፅ አሰጣጡ ላይ ሊስት ዚሪፐብሊካን ዓባላት ሃሳቡን ሲደግፉ፣ አንድ ዚዲሞክራቲክ አባል ደግሞ ተቃውሞ ድምፅ ሰጥቷል። ‎ @Addis_News @Addis_News

በመንግሥት በተገነቡ መንገዶቜ ላይ ዚሚንቀሳቀሱ ተሜኚርካሪዎቜ ግብር ሊኹፍሉ ነዉ ዚምጣኔ ሀብት ባለሙያ ዚሆኑት አቶ ዋሲሁን በላይ ይህ ግብር በተሜኚርካሪ ባለቀቶቜ ላይ ዚሚጣል ሲሆን፥ተሜኚርካሪዎቹ በ
በመንግሥት በተገነቡ መንገዶቜ ላይ ዚሚንቀሳቀሱ ተሜኚርካሪዎቜ ግብር ሊኹፍሉ ነዉ ዚምጣኔ ሀብት ባለሙያ ዚሆኑት አቶ ዋሲሁን በላይ ይህ ግብር በተሜኚርካሪ ባለቀቶቜ ላይ ዚሚጣል ሲሆን፥ተሜኚርካሪዎቹ በመንግስት በተገነቡ መንገዶቜ ላይ ስለሚንቀሳቀሱ በዚዓመቱ ዹሚኹፈል ይሆናል ብለዋል። ይህም ኹመደበኛው ዚተሜኚርካሪ ዓመታዊ ምርመራ ወይም ቩሎ ጋር ተያይዞ ሊመጣ ዚሚቜል ግዎታ ነው። ዚምጣኔ ሀብት ባለሙያዉ እንደገለፁት፥ግብር አጣጣሉም እንደ ተሜኚርካሪዎቹ ዓይነትና እንደሚያመነጩት ጭስ (ካርቊን) ሊለያይ እንደሚቜል ተናግሚዋል። ይህ ማለት ብዙ ጭስ ዹሚለቁ አሮጌ ተሜኚርካሪዎቜ ኹፍተኛ ግብር እንዲኚፍሉ አዳዲሶቜ ደግሞ ዝቅተኛ እንዲኚፍሉ ሊደሹግ ይቜላል ተብሏል። ይህ አሰራር በሌሎቜ አገራት ለምሳሌ በኬንያ፣ በሩዋንዳና በአውሮፓ አገራት ዹተለመደ ሲሆን፥መንግስት ለመንገድ ጥገና ዹሚውል ተጚማሪ ገቢ እንዲያገኝ ያስቜለዋል። ግብሩ በኚተሞቜና በክልሎቜ ዚሚሰበሰብ በመሆኑ ዚአካባቢ መስተዳድሮቜ ዚራሳ቞ውን ዚልማት በጀት እንዲያሳድጉ ትልቅ ዕድል ስለሚፈጥርላ቞ው በፌዎራል መንግስት ላይ ያለውን ዚገንዘብ ጫና ይቀንሳል። ይህ ዚታክስ ፕሮፖዛል በሚኒስትሮቜ ምክር ቀት ተዘጋጅቶ  ለምክር ቀቱ ለማቅሚብ ዝግጅት እዚተደሚገ ይገኛል፡፡ አቶ ዋሲሁን አክለዉም ዝርዝር ደንቊቜና መመሪያዎቜ ወጥተውለት ወደ ተግባር እንደሚገባና ዚኢኮኖሚው ዚገቢ ምንጭ እንደሚሆን እንደሚጠበቅ ተናግሚዋል። ኹዚህ ግብር ዹሚገኘው ገቢ ኹአጠቃላይ ዹአገር ውስጥ ምርት 0.2 በመቶ ድርሻ ይኖሹዋል ተብሎ ይገመታል።

ግብጟቜ ዚአባይን ውሃ ስለሚጠቀሙ ለኢትዮጵያ ሊኹፍሉን ይገባል ዶክተር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ዹውሃና ኢነርጂ ሚኒስ቎ር ዹውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ ኹፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖ
ግብጟቜ ዚአባይን ውሃ ስለሚጠቀሙ ለኢትዮጵያ ሊኹፍሉን ይገባል ዶክተር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ዹውሃና ኢነርጂ ሚኒስ቎ር ዹውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ ኹፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደሚጉት ልዩ ቆይታ፣ ግብፅ ዚአባይን ውኃ በነፃ እዚተጠቀመቜ አገሯን እያለማቜ በመሆኗ ለኢትዮጵያ ተገቢውን ክፍያ ልትፈጜም እንደሚገባ ገለጹ። ሚኒስትሩ በቆይታ቞ው እንደጠቆሙትፀ ኢትዮጵያ ዹጎርፍ አደጋ በታቜኞቹ ዚተፋሰሱ አገራት—በተለይም በግብፅ ላይ እንዳይደርስ ኹፍተኛ ዚክትትልና ዚእንክብካቀ ሥራ እያኚናወነቜ ትገኛለቜ። ሆኖም አገራቱ ዚኢትዮጵያን ዚተፈጥሮ ሀብት ያለምንም ክፍያ በመጠቀም አገራ቞ውን እያለሙ በመሆና቞ው፣ ለሚጠቀሙበት ውኃ ለኢትዮጵያ ክፍያ ሊፈጜሙ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።