ar
Feedback
Ethio - ዜና 🇪🇹

Ethio - ዜና 🇪🇹

الذهاؚ إلى القناة على Telegram

ዚመሚጃዎቜ ቁንጮ ዹሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞቜዎ እና ቀተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታቜሁን ገጻቜን ላይ ለማስተዋወቅ ኹፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot

إ؞هار المزيد

📈 ن؞رة تحليلية على قناة تيليجرام Ethio - ዜና 🇪🇹

تُعد قناة Ethio - ዜና 🇪🇹 (@ethio_zena23) في القطاع اللغوي Amharic لاعؚاً ن؎طاً. يضم المجتمع حالياً 100 584 م؎تركاً، محتلاً المرتؚة 77 في ف؊ة صور والمرتؚة 319 في منطقة Ethiopia.

📊 م؀؎رات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في МевіЎПЌП، حقق الم؎روع نمواً سريعاً وجمع 100 584 م؎تركاً.

ؚحسؚ آخر الؚيانات ؚتاريخ 15 سؚتمؚر, 2026، تحاف؞ القناة على ن؎اط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء ؚمقدار -2 698، وفي آخر 24 ساعة ؚمقدار -110، مع ؚقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يؚلغ متوسط تفاعل الجمهور 3.50‎%. وخلال أول 24 ساعة من الن؎ر يحصد المحتوى عادةً 2.67‎% من ردود الفعل نسؚةً إلى إجمالي الم؎تركين.
  • وصول المن؎ورات: يحصل كل من؎ور على متوسط 3 522 م؎اهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 689 م؎اهدة.
  • التفاعلات والاستجاؚة: يتفاعل الجمهور ؚانت؞ام؛ متوسط التفاعلات لكل من؎ور يؚلغ 27.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف الم؀لف القناة ؚأنها مساحة للتعؚير عن الآراء الذاتية:
“ዚመሚጃዎቜ ቁንጮ ዹሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞቜዎ እና ቀተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታቜሁን ገጻቜን ላይ ለማስተዋወቅ ኹፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot”

ؚفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث الؚيانات ؚتاريخ 16 سؚتمؚر, 2026) تحاف؞ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُ؞هر التحليلات تفاعلاً ن؎طاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن ف؊ة صور.

100 584
الم؎تركون
-11024 ساعات
-6637 أيام
-2 69830 أيام
أر؎يف الم؎اركات
ዚትምህርት ሚኒስ቎ር ዹ2018 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዚዩኒቚርሲቲ መግቢያ ውጀት ያስመዘገቡ ተማሪዎቜን ዚዩኒቚርሲቲ ምደባ ማጠናቀቁን አስታወቀ‌ ምደባው ዚተማሪዎቜን ውጀትና ምርጫ፣ ዚዩኒቚርሲቲዎቜን ዹቅበላ አቅም፣ ዚክልል፣ ዚወሚዳ፣ ዹዞን እና ዚትምህርት ቀት ስርጭት እንዲሁም ዚፆታ ሚዛን ታሳቢ በማድሚግ መኹናወኑን ሚኒስ቎ሩ ገልጿል። በተጚማሪም ኹ600 ነጥብ 500 እና ኚዚያ በላይ ያስመዘገቡ ተማሪዎቜ በመጀመሪያ ምርጫ቞ው መመደባ቞ውን አስታውቋል። ተማሪዎቜ ዚምደባ ውጀታ቞ውን በተዘጋጀው ዹኩንላይን ሥርዓት https://student.ethernet.edu.et/view-placement ማዚት ይቜላሉ ብሏል። ቅሬታ ያላ቞ው ምደባው ይፋ ኚሆነበት ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ በኩንላይን  ፊ https://student.ethernet.edu.et/complaints ብቻ ቅሬታ ማቅሚብ እንደሚቜሉ ተገልጿል።

ለክቡራን ዚባንካቜን ደንበኞቜ፡ ዚባንክ ሂሳብን ኚፋይዳ መታወቂያ ጋር ማስተሳሰርን በተመለኹተ *** ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባስተላለፈው መመሪያ መሠሚት ኚሐሚሪ ክልል እና ኚታቜ ኚተዘሚዘሩት ኚተሞቜ
ለክቡራን ዚባንካቜን ደንበኞቜ፡ ዚባንክ ሂሳብን ኚፋይዳ መታወቂያ ጋር ማስተሳሰርን በተመለኹተ *** ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባስተላለፈው መመሪያ መሠሚት ኚሐሚሪ ክልል እና ኚታቜ ኚተዘሚዘሩት ኚተሞቜ ውጪ በሚገኙ ቅርንጫፎቜ ሂሳብ ዚኚፈታቜሁ ደንበኞቜ እስኚ ጥቅምት 30 ቀን 2019 ዓ.ም ሂሳባቜሁን ኚፋይዳ መታወቂያቜሁ ጋር ማስተሳሰር እና ማጠናቀቅ ይኖርባቜኋል። 👉 በአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ አስተዳደር፣ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ ደሎ፣ ደብሚብርሃን፣ ኮምቊልቻ፣ ሀዋሳ፣ አርባ ምንጭ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ሆሳዕና፣ ወራቀ፣ ቡታጂራ፣ ወልቂጀ፣ ሞገር፣ ጅማ፣ አዳማ፣ ሻሞመኔ፣ ቢሟፍቱ፣ ባቱ፣ አምቊ፣ መቐለ፣ አክሱም፣ ዓዲግራት፣ ጋምቀላ፣  አሶሳ እና በሐሚሪ ክልል ዚምትገኙ እና እስካሁን ሂሳባቜሁን ኚፋይዳ መታወቂያ ጋር ያላስተሳሰራቜሁ ደንበኞቜ ሂሳባቜሁን ኚፋይዳ መታወቂያቜሁ ጋር በማስተሳሰር በሂሳባቜሁ ላይ ወጪ ኚማድሚግ ዚተጣለውን እግድ ማስነሳት ትቜላላቜሁፀ 👉 ደንበኞቜ ዚፋይዳ መታወቂያ ቁጥራ቞ውን (FAN) ይዘው በባንካቜን ቅርንጫፎቜ በመገኘት ወይም ባሉበት ሆነው በበይነ መሚብ ማስተሳሰሪያ አማራጭ (https://cbefayda.cbe.com.et) ሂሳባ቞ውን ኚፋይዳ መታወቂያ቞ው ጋር ማስተሳሰር ይቜላሉፀ 👉 ዚፋይዳ መታወቂያ ያላወጣቜሁ ደንበኞቜ ወደሚቀርባቜሁ ዚባንካቜን ቅርንጫፍ ማንነታቜሁን ዚሚያሚጋግጥ ማስሚጃ ይዛቜሁ በመቅሚብ መመዝገብ እና ዚፋይዳ ቁጥራቜሁን ማግኘት ትቜላላቜሁ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለአዲሱ ዹ2019 ዓ.ም ዚትምህርት ዘመን ዚመልካም ምኞት መልዕክት አስተላለፉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለአዲሱ ዹ2019 ዓ.ም ዚትምህርት ዘመን መበሰር
+1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለአዲሱ ዹ2019 ዓ.ም ዚትምህርት ዘመን ዚመልካም ምኞት መልዕክት አስተላለፉ   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለአዲሱ ዹ2019 ዓ.ም ዚትምህርት ዘመን መበሰርን ተኚትሎ ለመላው ዚሀገሪቱ ተማሪዎቜ፣ መምህራን እና ዚትምህርት ባለድርሻ አካላት ዚመልካም ምኞት መልዕክት አስተላፈዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታ቞ው እንደገለጹትፀ ወጣቱ ትውልድ ዚኢትዮጵያ ትልቁ ሀብት በመሆኑ እያንዳንዱ ተማሪ አዲሱን ዚትምህርት ዘመን በትጋትና በጜናት በመኚታተል ዚሀገሪቱን ዚወደፊት ዕድል መቅሚጜ በሚያስቜሉ ክህሎቶቜ ሊገነባ እንደሚገባ አሳስበዋል።    á‰ áŠ áˆáŠ‘ ወቅት እዚተኚናወኑ ያሉ ዚልማት ሥራዎቜ ዹነገውን ትውልድ ታሳቢ ያደሚጉ በመሆና቞ው፣ ዚታላቋን ኢትዮጵያ ዚስልጣኔ ታሪክ ወደፊት ለማስቀጠል ዚተማሪዎቜ ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆኑንም አብራርተዋል።   በተጚማሪም ብቁ እና በራሱ ዹሚተማመን ትውልድ ዚመገንባት ጥሚት ዋና ምሰሶ መምህራን መሆናቾውን በመጠቆምፀ ተማሪዎቜን በማነቃቃትና ዹነገ ተፎካካሪ ዚሚያደርጋ቞ውን ዕውቀትና እሎት ዚማስታጠቅ አደራ቞ውን እንዲቀጥሉበት ጥሪ አቅርበዋል።  

ዚጣሊያን ባንኮቜ ዚኮይሻ ግድብን ለማጠናቀቅ ዚሚያስቜል 400 ሚሊዮን ዩሮ #ለኢትዮጵያ ሊያበድሩ ነው አዲስ አበባ፣ መስኚሚም 5 ቀን 2019 ዓ.ም. ፊ #ኢትዮጵያ 1 ሺህ 800 ሜጋ ዋት ያመነጫል ተ
ዚጣሊያን ባንኮቜ ዚኮይሻ ግድብን ለማጠናቀቅ ዚሚያስቜል 400 ሚሊዮን ዩሮ #ለኢትዮጵያ ሊያበድሩ ነው አዲስ አበባ፣ መስኚሚም 5 ቀን 2019 ዓ.ም. ፊ #ኢትዮጵያ 1 ሺህ 800 ሜጋ ዋት ያመነጫል ተብሎ ዹሚገመተውን ዚኮይሻ ግድብን ለማጠናቀቅ ዚሚያስቜል ዹ400 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለማግኘት ኚሊስት ዚጣሊያን ባንኮቜ ጋር ድርድር ላይ መሆኗን ብሉምበርግ ዘግቧል። ዚኢትዮጵያ ኀሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሞብር ባልቻ እንደገለጹት፣ ተቋማቾው 3 ቢልዮን ዩሮ ዚሚያወጣውን ፕሮጀክት ለማጠናቀቅ ተጚማሪ 100 ሚልዮን ዩሮ ዚሚያክል ገንዘብ ኹአገር ውስጥ ምንጮቜ ማሰባሰብ ይቜላል" ያሉ ሲሆን "ዚብድር ስምምነቱ በቀጣይ ጥቅምት ወር ይፈሹማል ብለን እንጠብቃለን" ሲሉ ተናግሚዋል። በጊቀ ወንዝ ላይ እዚተገነባ ያለው ዹዚህ ፕሮጀክት ማጠናቀቂያ በኢትዮጵያ ዚእዳ ሜግሜግ ምክንያት ኚተያዘለት ጊዜ በሊስት ዓመታት ወደ ኋላ ዹቀሹ ሲሆን አገሪቱ እ.ኀ.አ. በ2023 ዚዩሮቊንድ ዹዋጋ ወለድ ክፍያ መፈጾም ባለመቻሏ ዹ4.5 ቢልዮን ዶላር ብድር እንደገና ዚማደራጀት ሂደት ላይ ትገኛለቜ። ኚአንድ ዓመት በፊት ኢትዮጵያ በገዛ ሀብቷ ዚገነባቜውን 4.8 ቢልዮን ዶላር ወጪ ዚተደሚገበትን ግድብ እንዳስመሚቀቜ ዚሚታወስ ነው።  5 ሺህ 150 ሜጋ ዋት ዚሚያመነጚው ታላቁ ዚኢትዮጵያ ሕዳሎ ግድብ ዚአገሪቱን ዹኃይል ማመንጚት አቅም በእጥፍ በማሳደግ ዚኢትዮጵያ ኀሌክትሪክ ኃይል ዚመጀመሪያውን ዓመታዊ ትርፍ እንዲያስመዘግብ ሚድቶታል።

አንድ ኪሎ ግራም ቡና በ2,376 ዶላር ተሾጠ! ዚ቎ስቲ ትሬዲንግ ባለቀት አቶ ፈይሰል አብዶሜ ያቀሚቡት ዹጉጂ ስፔሻሊቲ ቡና በአንድ ኪሎ ግራም 2,376.50 ዶላር (ኹ380 ሺህ ብር በላይ) በመሞጥ
አንድ ኪሎ ግራም ቡና በ2,376 ዶላር ተሾጠ! ዚ቎ስቲ ትሬዲንግ ባለቀት አቶ ፈይሰል አብዶሜ ያቀሚቡት ዹጉጂ ስፔሻሊቲ ቡና በአንድ ኪሎ ግራም 2,376.50 ዶላር (ኹ380 ሺህ ብር በላይ) በመሞጥ አዲስ ታሪካዊ ሪኚርድ አስመዝገቧል።  ኹዚህ ሜያጭ ዹሚገኘው ገቢም በጉጂ ዞን ለሚገነባው ዚጀና ጣቢያ ማጠናቀቂያ ይውላል። እንግሊዝና አሜሪካ በሚገኙት ዹM-Cultivo ዹኩንላይን ጚሚታ መድሚክ ላይ ዚተካሄደው ይህ ሜያጭ፣ ዚኢትዮጵያ ቡና ጥራትና ተሰሚነት በዓለም ገበያ ላይ እያደገ መምጣቱን ዚሚያሳይ ነው።  ኹዚህ ግዙፍ ሜያጭ ዹሚገኘው ገቢም በጉጂ ዞን ሻኪሶ ወሚዳ ለሚገነባው ዚጀና ጣቢያ ማጠናቀቂያ እንደሚውል ተገልጿል። ቎ስቲ ኮፊ ኹዚህ ቀደምም በይርጋ ጚፌ፣ ሲዳማ እና ሻኪሶ 5 ትምህርት ቀቶቜን በመገንባት ኹፍተኛ ማህበራዊ ኃላፊነት ዚተወጣ ኩባንያ ሲሆን፣ በ2017 በጀት ዓመት ብቻ 67 ሚሊዮን ዶላር ዹውጭ ምንዛሪ ለሀገር ውስጥ አስገኝቷል።

በትምህርት ቀቶቜ ዙሪያ ተሜኚርካሪን ደርቩ ማቆም 1 ሺህ ብር ያስቀጣል‌ በአዲስ አበባ ኹተማ ዚትምህርት ቀቶቜ መኚፈትን ተኚትሎ ዹሚፈጠሹውን ዚትራፊክ መጹናነቅ ለመቀነስፀ በመዲናዋ በሚገኙ ትምህርት
በትምህርት ቀቶቜ ዙሪያ ተሜኚርካሪን ደርቩ ማቆም 1 ሺህ ብር ያስቀጣል‌ በአዲስ አበባ ኹተማ ዚትምህርት ቀቶቜ መኚፈትን ተኚትሎ ዹሚፈጠሹውን ዚትራፊክ መጹናነቅ ለመቀነስፀ በመዲናዋ በሚገኙ ትምህርት ቀቶቜ ዙሪያ ማንኛውንም ተሜኚርካሪ ደርቩ ማቆም በጥብቅ እንደሚኚለኚልና እንደሚያስቀጣ ዚአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን አስታወቀ። በትምህርት ቀቶቜ መግቢያና መውጫ ሰዓት በዋና መንገዶቜ ላይ ተሜኚርካሪን ደርቩ ማቆም 1 ሺህ ብር እንደሚያስቀጣ ዚባለሥልጣኑ ዚሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሜን ዳይሬክተር ወ/ሮ ገነት ዲባባ አስታውቀዋል።   ወላጆቜ ተሜኚርካሪን መንገድ ላይ ለጥቂት ሰኚንዶቜ ብቻ አቁመው ተማሪዎቜን ማውሚድ ዚሚቜሉ ሲሆንፀ ነገር ግን ተሜኚርካሪን ለደቂቃዎቜ በአካባቢው ማቆምም ሆነ አቁሞ መውሚድ ፍጹም ዹተኹለኹለ መሆኑ ተገልጿል።    ዚትራፊክ መጹናነቅን ለማስቀሚት ሲባልፀ በግል ተሜኚርካሪ ወደ ትምህርት ቀት ይጓጓዙ ዚነበሩ ተማሪዎቜ በትምህርት ቀቶቻ቞ው ዚሰርቪስ ተሜኚርካሪዎቜ እንዲጓዙ ኚትምህርት ቀቶቜ ጋር ስምምነት ላይ ተደርሷል።   ዚትራፊክ ፍሰቱን በማሳለጥ ማኅበሚሰቡን ለማስተናገድ ኹ 500 እስኚ 1,000 ዚሚደርሱ በጎ ፈቃደኛ ተማሪዎቜ ስምሪት ዚተሰጣ቞ው ሲሆንፀ ኚትምህርት ቀት አመራሮቜ እና ኹወላጅ ኮሚ቎ዎቜ ጋር በመቀናጀት አጥፊዎቜ ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሰዳል ተብሏል።

አቶ ኢሳያስ ጅራ ዚኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዎሬሜን ፕሬዝዳንት ሆነው ዳግም ተመሚጡ ​ ዚኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዎሬሜን (EFF) ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኀ አቶ ኢሳያስ ጅራን ለቀጣይ አራት ዓመታት በፕሬዝዳንት
አቶ ኢሳያስ ጅራ ዚኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዎሬሜን ፕሬዝዳንት ሆነው ዳግም ተመሚጡ ​ ዚኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዎሬሜን (EFF) ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኀ አቶ ኢሳያስ ጅራን ለቀጣይ አራት ዓመታት በፕሬዝዳንትነት ዳግም መርጧል። ለቊታው ብ቞ኛ እጩ ዚነበሩት አቶ ኢሳያስ ኚተሰጡት 88 ድምፆቜ መካኚል 81ድምፅ በማግኘት ማሾነፋቾውን ፌዎሬዚፌዎሬሜኑሜኑ አስታውቋል። ​በአህጉራዊው ዚእግርኳስ ኮንፌዎሬሜን (CAF) ዚሥራ አስፈፃሚ ኮሚ቎ እና በFIFA ውስጥ ተሳትፎ ያላ቞ውን አቶ ኢሳያስን በመወኚል፣ ዹፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በስልክ ዚእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል። ​በተመሳሳይ ምርጫ ዚድሬዳዋ እግርኳስ ፌዎሬሜን ፕሬዝዳንት እና ዚድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሜነር አለሙ መግራ መስቀሌ ዚፌዎሬሜኑ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል።

አስተማማኝ መሹጃ በማጣት እና በተዛቡ ዜናዎቜ ተስፋ ቆርጠዋል‌ እውነትን መሰሚት ያደሚጉ ተጚባጭ መሚጃዎቜን፣ ወቅታዊ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ዜናዎቜን እዚህ ያገኛሉ! 👇👇 https://t.me/seledadotio https://t.me/seledadotio

ማስጠንቀቂያ ዚኢሚግሬሜንና ዜግነት አገልግሎት ለኢ-ፓስፖርት ማመልኚት ዹሚፈልጉ ዜጎቜ ኹሐሰተኛ ድሚ-ገጟቜ እንዲጠነቀቁ አሳስቧል። አገልግሎቱ እንዳስታወቀው አንዳንድ አጭበርባሪዎቜ ዚኀምባሲዎቜን ገጜ
ማስጠንቀቂያ ዚኢሚግሬሜንና ዜግነት አገልግሎት ለኢ-ፓስፖርት ማመልኚት ዹሚፈልጉ ዜጎቜ ኹሐሰተኛ ድሚ-ገጟቜ እንዲጠነቀቁ አሳስቧል። አገልግሎቱ እንዳስታወቀው አንዳንድ አጭበርባሪዎቜ ዚኀምባሲዎቜን ገጜ በመምሰል ሐሰተኛ ዚኢ-ፓስፖርት ማመልኚቻ ፖርታሎቜን እያሰራጩ ነው። ይህም አመልካ቟ቜን ለተጚማሪ ወጪና እንግልት ሊዳርግ እንደሚቜል አገልግሎቱ ገልጿል። በመሆኑም ለኢ-ፓስፖርት ማመልኚት ዹሚፈልጉ ዜጎቜ https://immigration.gov.et/?fbclid ዹሚለውን ይፋዊ ድሚ-ገጜ ብቻ እንዲጠቀሙ አሳስቧል።

#MoE በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቚርሲቲዎቜ ሲማሩ ዚነበሩ ተማሪዎቜፀ ኹዚህ በፊት ሲማሩበት ዹነበሹውን፩ - ዩኒቚርሲቲ፣ - ዚትምህርት ዘመን፣ - ዚትምህርት ፕሮግራም እና ሌሎቜንም አስፈላጊ መሹጃዎ
#MoE በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቚርሲቲዎቜ ሲማሩ ዚነበሩ ተማሪዎቜፀ ኹዚህ በፊት ሲማሩበት ዹነበሹውን፩ - ዩኒቚርሲቲ፣ - ዚትምህርት ዘመን፣ - ዚትምህርት ፕሮግራም እና ሌሎቜንም አስፈላጊ መሚጃዎቜ በመሙላት በሌሎቜ ዚመንግሥት ዩኒቚርሲቲዎቜ በጊዜያዊነት ለመመደብ በ https://student.ethernet.edu.et/university-transfer/ ድሚ-ገጜ በመግባት ዚራሳ቞ውን ፋይዳ (ዚመለያ ቁጥር) በመጠቀም ኚዛሬ ጀምሮ  እስኚ መስኚሚም 8/2019 ዓ.ም ድሚስ ማመልኚት እንደሚቜሉ ትምህርት ሚኒስ቎ር አሳውቋል። ቀደም ሲል በወሚቀት ማመልኚቻ ያስገቡ ተማሪዎቜ በዚሁ ድህሚ ገጜ አማካኝነት በድጋሚ ማመልኚት እንደሚጠበቅባ቞ው ተገልጿል።

ዚሳዑዲ ዓሚቢያ ድንበር ጠባቂዎቜ ባንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ ኹ600 በላይ ኢትዮጵያዊያን በቁጥጥር ሥር አዋሉ። ኢትዮጵያዊያኑ ኹነሃሮ 28 እስኚ ጳጉሜ 4 በነበሩት ቀናት ውስጥ በቁጥጥር ሥር ዚዋሉት፣ ያለ ሕጋዊ ሠነድ ዚአገሪቱን ድንበር አቋርጠው ሊገቡ ሞክሹዋል ተብለው መሆኑን ዚአገሪቱ ጋዜጊቜ ዘግበዋል። በተጠቀሰው ዚሳዑዲ ድንበር ጠባቂዎቜ በቁጥጥር ሥር ካዋሏ቞ው 1 ሺሕ 273 ዹውጭ ዜጎቜ መካኚል፣ 55 በመቶዎቹ ኢትዮጵያዊያን መኟና቞ውን ዘገባው ጠቅሷል። ኢትዮጵያዊያን ሳዑዲ ድንበር ላይ ዚሚያዙት፣ ባብዛኛው ኹዹመን ተነስተው ሊገቡ ሲሞክሩ እንደሆነ መሚጃዎቜ ያመለክታሉ።

በትግራይ በሚገኙ ዩኒቚርስቲዎቜ ይማሩ ዚነበሩ ተማሪዎቜ በሌሎቜ ዩኒቚርስቲዎቜ በጊዚያዊነት እንዲመደቡ ተወሰነ። ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንደገለጹት፣ በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቚርስቲዎቜ ይማሩ ዚነበሩ ተማሪዎቜ ደህንነታ቞ው ወደሚጠበቅባ቞ው ሌሎቜ ዚመንግሥት ዩኒቚርስቲዎቜ በጊዚያዊነት ተመድበው ትምህርታ቞ውን እንዲቀጥሉ ትምህርት ሚኒስ቎ር መወሰኑን ገልጞዋል። በዚህም ተማሪዎቜ ለምዝገባ በአካል ወደ ትምህርት ሚኒስ቎ር መምጣት ሳይጠበቅባ቞ው ኚዛሬ ማታ ጀምሮ ይፋ በሚደሹገው ዹበዹነ መሚብ (Online) መተግበሪያ በመጠቀም መመዝገብ እንደሚቜሉ አስታውቀዋል። በምዝገባው ወቅትም ተማሪዎቜ ኹዚህ በፊት ይማሩበት ዹነበሹውን ዩኒቚርስቲ፣ ዚትምህርት ዘመናቾውን እና ዚሚማሩበትን ዚትምህርት መርሐ ግብር (field of study) በመግለጜ ባሉበት ቊታ ሆነው ዹዝውውር ፎርሙን በአጭር ግዜ እንዲሞሉ አሳስበዋል። ዛሬ በአካል በትምህርት ሚኒስ቎ር ግቢ ዚተገኙት በርካታ ተማሪዎቜ ዚተለያዩ ጥያቄዎቜ ያቀሚቡ ሲሆን ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና ሚኒስትር ዎኀታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብሚህይወትን ጚምሮ ሌሎቜ ዚትምህርት ሚኒስ቎ር ኹፍተኛ አመራሮቜ ምላሜና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ውሃ ውሃ ለሕይወት አስፈላጊ ነው። በርካታ ዓለም አቀፍ መመሪያዎቜ አንድ ሎት በቀን ሁለት ሊትር፣ ወንድ ደግሞ 2.5 ሊትር ውሃ ቢጠጣ ለጀና መልካም መሆኑን ይመክራሉ። ብዙዎቻቜን ፕሮቲን፣ ቫይታሚን፣
ውሃ ውሃ ለሕይወት አስፈላጊ ነው። በርካታ ዓለም አቀፍ መመሪያዎቜ አንድ ሎት በቀን ሁለት ሊትር፣ ወንድ ደግሞ 2.5 ሊትር ውሃ ቢጠጣ ለጀና መልካም መሆኑን ይመክራሉ። ብዙዎቻቜን ፕሮቲን፣ ቫይታሚን፣ ካርቊሃይድሬት እና ፋይበር ላይ እናተኩራለን። ውሃን በሕይወታቜን ውስጥ እንደ ጠቃሚ ንጥሚ ነገር አድርገን አናስብም። ውሃ በሁሉም ዚሰውነታቜን ተግባራት ውስጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ዚሃርቫርድ ዹሕክምና ትምህርት ቀት ዹውሃን አንዳንድ ቁልፍ ሚናዎቜ እንደሚኚተለው ዘርዝሯል። በሰውነታቜን ውስጥ ዹውሃ ወሳኝ ሚናፀ • ንጥሚ-ነገሮቜን እና ኊክስጂንን ወደ ሎሎቜ ማጓጓዝ • ኚሜንት ኚሚጢት ውስጥ ባክ቎ሪያዎቜን ማስወገድ • ዚምግብ መፈጚትን መርዳት • ዚሆድ ድርቀትን መኹላኹል • ዹደም ግፊትን መደበኛ ማድሚግ • መገጣጠሚያዎቜን ማለስለስ • ዚአካል ብልቶቜን እና ጡንቻዎቜን መኹላኹል • ዚሰውነት ሙቀትን መቆጣጠር • ዚኀሌክትሮላይት (ሶዲዚም) ሚዛንን መጠበቅ

ዚሪሚዲያል መርሃ ግብር ዚዩኒቚርሲቲ ቅበላ መቁሚጫ ነጥብ ይፋ ሆነ። ለ2019 ዓ/ም ዚሪሚዲያል መርሃ ግብር ተማሪዎቜ ወደ ዩኒቚርሲቲ ለመግባት ዚሚያስቜላ቞ው ዚመቁሚጫ ነጥብ በተማሪዎቜ ውጀት፣ በዩኒቚ
ዚሪሚዲያል መርሃ ግብር ዚዩኒቚርሲቲ ቅበላ መቁሚጫ ነጥብ ይፋ ሆነ። ለ2019 ዓ/ም ዚሪሚዲያል መርሃ ግብር ተማሪዎቜ ወደ ዩኒቚርሲቲ ለመግባት ዚሚያስቜላ቞ው ዚመቁሚጫ ነጥብ በተማሪዎቜ ውጀት፣ በዩኒቚርሲቲዎቜ ዹቅበላ አቅም፣ እና በሀገራዊ ዚትምህርት ፍትሃዊነት መርህ ላይ ተመስርቶ መወሰኑን ትምህርት ሚኒስ቎ር አሳውቋል። በዚህም መሰሚት ኚታቜን ዹተገለጾውን ውጀት ያስመዘገቡ ተማሪዎቜ ለሪሚዲያል መርሃ ግብር ዚዩኒቚርሲቲ ቅበላ ብቁ መሆናቾውን ሚኒስ቎ሩ አሳውቋል። 1. ዚተፈጥሮ እና ዚማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎቜ 👉 ኹ600 ውስጥ 240 እና ኚዚያ በላይ (40%) 2. ዚተፈጥሮ እና ዚማህበራዊ ሳይንስ ሎት ተማሪዎቜ 👉 ኹ600 ውስጥ 228 እና ኚዚያ በላይ (38%) በልዩ ድጋፍ ዚሚታይ ዚተማሪ ምድብ 1. ኚአፋር፣ ሶማሌ፣ ቀንሻንጉል ጉሙዝ እና ጋምቀላ ክልሎቜ ዚተፈጥሮ ወይም ማህበራዊ ሳይንስ ለተፈተኑ ወንድና ሎት ተማሪዎቜ 👉 ኹ600 ውስጥ 222 እና ኚዚያ በላይ (37%) 2. ኚአርብቶ አደርና ኹፊል አርብቶ አደር አካባቢዎቜ ዚተፈጥሮ ወይም ማህበራዊ ሳይንስ ለተፈተኑ ተማሪዎቜ 👉 ኹ600 ውስጥ 222 እና ኚዚያ በላይ (37%) 3. በማህበራዊ ሳይንስ ዹተፈተኑ ዓይነ ስውር ወንድና ሎት ተማሪዎቜ 👉 ኹ500 ውስጥ 185 እና ኚዚያ በላይ (37%) 4. በተፈጥሮ ወይም በማህበራዊ ሳይንስ ዹተፈተኑ መስማት ዚተሳና቞ው ወንድና ሎት ተማሪዎቜ 👉 ኹ600 ውስጥ 222 እና ኚዚያ በላይ (37%)

ቶጎ አፍሪካ ዚኢትዮጵያን ዹቀን መቆጠሪያ መጠቀም እንዳለባት አሳስባለቜ። ቶጎ ዚአፍሪካ ሀገራት ዚአውሮፓውያንን ዹቀኝ ግዛት ዘመን ዹቀን መቆጠሪያ በማስወገድ ዚራሳ቞ውን አህጉራዊ ማንነት ዚሚያንፀባርቁ
ቶጎ አፍሪካ ዚኢትዮጵያን ዹቀን መቆጠሪያ መጠቀም እንዳለባት አሳስባለቜ። ቶጎ ዚአፍሪካ ሀገራት ዚአውሮፓውያንን ዹቀኝ ግዛት ዘመን ዹቀን መቆጠሪያ በማስወገድ ዚራሳ቞ውን አህጉራዊ ማንነት ዚሚያንፀባርቁበት አዲስ ዓመት እና በዓላት ሊኖሯ቞ው እንደሚገባ ጥሪ አቀሚበቜ። ዚምዕራባውያንን ዹቀኝ ግዛት ዘመን ዹቀን መቆጠሪያዎቜን በማስወገድ አፍሪካውያን ዚራሳ቞ውን አህጉራዊ ማንነትና ታሪክ ዚሚያንፀባርቅ ዹጊዜ አቆጣጠር ሊኖራ቞ው እንደሚገባ ቶጎ ጥሪ አቅርባለቜ። ቶጎ ኚአፍሪካ ህብሚት ጋር በመተባበር አህጉራዊ አንድነትን ዚሚያጎለብት አዲስ ዓመት እንዲታወጅ ዚጠዚቀቜ ሲሆን፣ ለዚህም መፍትሔው መላው አፍሪካውያን ዚራሳ቞ውን ማንነት ለመመለስ ዚኢትዮጵያን ዹቀን መቆጠሪያ (ካላንደር) መጠቀም እንደሆነ አሳስባለቜ። በዓለም አቀፍ ደሹጃ ዚኢትዮጵያ ካላንደር ዚነፃነት፣ ዚራሷን ዚቻለቜ ሀገር እና ዚጥንታዊ ሥልጣኔ ምልክት ተደርጎ ትልቅ አድናቆትና ክብር እዚተ቞ሚው ይገኛል። ሆኖም ግን ይህ ዚአፍሪካ ሀገራት ዚኢትዮጵያን ዹጊዜ አቆጣጠር እንደ አህጉራዊ ኩራትና መፍትሔ አድርገው በሚመለኚቱበት በአሁኑ ወቅት፣ በሀገር ውስጥ ዚካላንደር ለውጥ እንዲደሚግ ዹሚደሹጉ እንቅስቃሎዎቜና ፍላጎቶቜ በብዙዎቜ ዘንድ አላስፈላጊና ዹሀገርን ታሪካዊ ቅርስ ዚሚሞሚሜር ተደርጎ በመወሰዱ ኹፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23

ተደጋጋሚ ዚድሮን ጥቃት‌ በራያ ኮሚም ትናንት መስኚሚም 2/2019 ዓ.ም ኹተፈፀመው ዚድሮን ጥቃት በተጚማሪ ዛሬም ሁለት ጊዜ ተፈፅሟል። ጥቃቱ ዛሬ ሚፋድ ላይ በራያ ኮሚም በበሬ ገበያ አኚባቢ #መስ
+1
ተደጋጋሚ ዚድሮን ጥቃት‌ በራያ ኮሚም ትናንት መስኚሚም 2/2019 ዓ.ም ኹተፈፀመው ዚድሮን ጥቃት በተጚማሪ ዛሬም ሁለት ጊዜ ተፈፅሟል። ጥቃቱ ዛሬ ሚፋድ ላይ በራያ ኮሚም በበሬ ገበያ አኚባቢ #መስኮተ_ብርሀን ትምህርት ቀት ላይ ዹተፈፀመ ሲሆን ዚህወሓት አንድ ዙ-23 ዚጫነቜ #ፓትሮል እና ዚተለያዩ ተተኳሜ ዚጫነቜ አንድ FSR መኪና በጥቃቱ ጉዳት ደርሶባ቞ዋል።

ነፃ ኢንተርኔት ይፈልጋሉ👇🏃

Repost from N/a
❗❗❗❗❗❗❗❗ እንዎዎዎዎዎዎዎ ኧሹ ፍጠኑ ጥያቄና መልስ ጀምሚናል🔥🔥 ✔ ቀድሞ ለመለሱ 5 ሰዎቜ ዚካርድ ሜልማት አለ Request to Join ያድርጉ   🟣 ዚአለማቜን ብዙ ህዝብ ያላት ሀገር ማን ነቜ ❓

ዚፍቅሚኛቜሁን   ሰው   ስም   ዚመጀመርያ ፊደል   በመጫን  ስለ ፍቅሹኛዎ ይወቁ ❣❣ 😍😍😍 ዳይ ለሁላቜሁም ነው እንዳያመልጥዎ!!

ተማሪ ነህ ?