Mujib Amino Z islam
📈 Аналитический обзор Telegram-канала Mujib Amino Z islam
Канал Mujib Amino Z islam (@mujibbinislam) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 14 536 подписчиков, занимая 5 980 место в категории Религия и духовность и 2 329 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 14 536 подписчиков.
Согласно последним данным от 13 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -79, а за последние 24 часа — -9, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 28.98%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 10.83% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 213 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 575 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 11.
📝 Описание и контентная политика
Описание канала не предоставлено.
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 14 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 14 июля | 0 | |||
| 13 июля | 0 | |||
| 12 июля | +1 | |||
| 11 июля | 0 | |||
| 10 июля | 0 | |||
| 09 июля | 0 | |||
| 08 июля | 0 | |||
| 07 июля | +2 | |||
| 06 июля | +2 | |||
| 05 июля | 0 | |||
| 04 июля | +2 | |||
| 03 июля | +2 | |||
| 02 июля | +9 | |||
| 01 июля | +7 |
| 2 | በሀገራዊ ምክክራችን ዋዜማ ኢትዮጵያ በምክክር ለምታረጋግጠው አንድነትና ዘላቂ የሰላም ጉዞ ጥበብ ቀስመናል:: ዶር Abiy Ahmed Ali(የኢ/ፌ/ዲ/ሪ ጠ/ሚ)
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
ዛሬ በታሪካዊው የሀገራዊ ምክክራችን ዋዜማ፣ የኢትዮጵያ ታላቅ ወዳጅ የሆኑትን ክቡር ኦሊሴጉን ኦባሳንጆን በጽሕፈት ቤቴ ተቀብያለሁ። በመጪው ሀገራዊ ምክክር ዙሪያ ለመወያየት እንዲሁም ከዚህ ቀደም ካከናወኗቸው ተግባራት ጥበብ ለመቅሰም ችለናል፤ በተለይም የቢያፍራን የሰላም ሂደት በመምራት ያካበቱትን ልምድ አጋርተውናል። ይህም ኢትዮጵያ በምክክር ለምታረጋግጠው አንድነትና ዘላቂ የሰላም ጉዞ ላይ ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ ነው።
ኢትዮጵያ ለሚያበረክቱት አስተዋፅኦ ሁልጊዜም የላቀ ምስጋናዋን ታቀርባለች! | 670 |
| 3 | Нет текста... | 618 |
| 4 | በሀገራዊ ምክክር ላይ የኢስላምና ሙስሊም ጠልነት ጉዳይ በሚገባ ተነስቶ መፍትሄ ሊሰጠው ይገባል‼️
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
ሙስሊም ተማሪዎች በትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚደርስባቸው ስልታዊ ጫና እና እንደ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባሉ ትላልቅ ተቋማት ውስጥ ጭምር ዛሬ ድረስ ሙስሊም ሴቶች በማንነታቸውና በሂጃባቸው ምክንያት የሥራ ዕድል መከልከላቸው የመዋቅራዊ መድልዎ ግልጽ ማሳያ ነው።
ተቋማቱ ሙስሊሙን ማህበረሰብ እንደ ደንበኛና አገልግሎት ተቀባይ በደስታ እየተቀበሉ፣ እንደ ሠራተኛ ግን በየትኛውም የሥራ መደብ ማንነቱን ገፍተው ለማግለል ራሳቸው የጻፏቸውን መመሪያዎች እንደ ሰበብ ይጠቀማሉ። ይህ ዓይነቱ ድርብ ስታንዳርድ ኢስላም ጠልነት የወለደው እንጂ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል?
እነኝህ ከኢስላም ጠልነት የመነጩ ጭቆናና መድሎዎችን ሕዝበ ሙስሊሙ እያስተናገደ የዘለቀው ስለመብት እንጂ ከጥላቻ በመነሳት በተለያዩ መልኩ በደል የሚፈጽሙትን የሚቀጣ ህግ የለም።በተደጋጋሚ ወደ ፍርድ ቤት ያመሩ ጉዳዮች ብይናቸው "መብታችሁ ነው።ይህን ማድረግ አይችሉም" በሚል ላይ የሚወሰን ነው።ብይኑ ሆነ ብሎ ከጥላቻ የተነሳ ያን ሁሉ በደልና ጭቆና ያደረሱ አካላትን በዝምታ ይልፋል። ምክንያቱም የኢስላም ጠልነትን የሚከለክል ህግ ባለመኖሩ ኢስላምና ሙስሊም ጠሎቹ በድርጊታቸው የመቀጠል እድል አገኙ። በመሆኑም በሀገራዊ ምክክር ላይ የኢስላምና ሙስሊም ጠልነት ጉዳይ በሚገባ ተነስቶ መፍትሄ ሊሰጠው ይገባል።
መፍትሄው ምንድነው?
📶📶📶📶📶📶📶
መፍትሄውን ተግባራዊ ለማድረግ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በሲቪክ ማህበራትና በዲጂታል ሚዲያ ተደራጅቶ መብቱን በንቃትና በህጋዊ መንገድ ማስከበር ይኖርበታል። የአስተሳሰብ ለውጥ ለማምጣትም በትምህርት ስርአቱና በታሪክ መጽሀፍት ውስጥ የተዛቡ ውክላናዎችን የሚያስተካክሉ ስልታዊ ይዘቶችን ማካተት ወሳኝ እርምጃ ነው። በስተመጨረሻም፣ ይህንን ስር የሰደደ ጥላቻ በህግ መዋጋት የዜጎችን እኩልነት በማረጋገጥ የፍትሃዊነት ሜዳውን ሙሉ በሙሉ ያስተካክላል።
1) ኢስላም ጠልነት በኢትዮጵያ ዉስጥ ከጥንት ጀምሮ በአስተሳሰብ፥በአሰራር፥ በፖሊሲ፥ በታሪክ ትርክት፥በኢማጅኔሽን፥ በአሰራር፥ወዘተ በሚገለጽ በኢትዮጵያ ዉስጥ እንደነበር በግልጽ መተማመን ላይ እንዲደረስ ማድረግ።
2) ኢስላም ጠልነት በሙስሊሞች ዘርፈ ብዙ ችግሮችንና የመብት ጥሰቶችን፥መገለሎችንና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ብዙ ጉዳት እየፈጠረ መሆኑን በተጨባጭ ማስረጃ መተማመን ላይ መድረስ።
3) የየትኛውም የመንግስት መዋቅር፣ ሕዝባዊ እና ማህበሰባዊ ተቋማት አሰራር፥ፖሊሲዎችና ባለድርሻዎች ከሙስሊም ጠልነት ነጻ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ሕግና ስርዓት በመዘርጋት ከኢስላም ጥላቻ የጸዳ ሕዝብና መንግስት መኖሩን ማረጋገጥ።
4) ሙስሊሙ በትምህርት፣በሥራ በቅጥር ፣ግልጋሎትን በሚያገኝበት ወቅትና ባጠቃላይ በአደባባይ ህይወቱ መድልዎ እንዳያጋጥመው ማድረግ፡፡ ሃይማኖት ተኮር የመብት ጥሰቶችን ለመከላከል ጥሰቱን በሚፈጽሙት አካላት ላይ ቅጣት የሚያሳልፍና ለመብቱ ጥበቃ ለማድረግ የሙስሊም ጠልነት ልዩ ድጋጌ ማስወጣት።
5) ሙስሊሙ አናሳ ሆኖ በሚኖርበትና በየትኛውም አካባቢ ባለው የግል ሕይወት ከትንኮሳ፣ ከዘለፋና ከጥቃት የተጠበቀ እንዲሆን ማስቻል።
6) ሙስሊሙ በታሪክ ድርሳናት፣ በኪነ-ጥበብ ስፍራዎች፣ በኦፊሴላዊ ንግግሮች (ወዘተ) (misrepresent) አለመሆኑን ማረጋገጥ።
7) እንደሀገርና ሕዝብ ሙስሊም-ጠል ዘይቤያዊና ባህላዊ አባባሎችን መዋጋት።
😎 ሙስሊም-ጠልነትን በህገ-መንግስት እውቅና እዲሰጠው ማድረግ።
9) ሙስሊሞችን ከሃይማኖት ዝንባሌያቸው በመነሳት “ጨዋ”፣ “ነባር”፣ “ ጥሩ’’ ወይንም “አክራሪ”፣ “ፀንፈኛ” ወዘተ በማለት ፈርጆ የማሸማቀቅን አካሄድ ማስቀረት።
10) የእስልምና ጥላቻ ክልከላን በሕግ ማስቆም ማለት የጨዋታ ሜዳውን ወደ አጥቂዎቹ ማዞር እንደሆነ ማሳመን ያስፈልጋል። | 678 |
| 5 | ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን።
የንጹሀን ና የሃይማኖት አባቶችን ግ*ድያ በጽኑ እንቃወማለን!
የባቲው ሸይኽና የሀገር ሽማግሌ የሆኑት ሸይኽ የህያ ይማም በፅንፈኛ ታጣቂዎች መገ*ደላቸዉ ታውቋል::
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
በአማራ ክልል ባቲ ወረዳ የሀገር ሽማግሌ ፤ የሃይማኖት አባት ፤ ሰላምን በማስፈን እና ማህበረሰቡን በፍቅርና በመቻቻል በማገልገል ይታወቁ የነበሩት የተከበሩ ሸይኽ የህያ ይማም በክልሉ በሚንቀሳቀሰዉ ፅንፈኛ ቡድን በግፍ መገ*ደላቸው ተሰምቷል::
በቅርቡ እንኳ ሰኔ 20/10/18 እለተ ቅዳሜ ምሽት ላይ
በአማራ ክልል ዳንግላ ከተማ ቀበሌ 02 አደም የ 4 ልጆች አባት የነበሩና የኹጥባ መስጂድ ኢማም የሆኑትን ሸይኽ ሱፍያን አደም በግፍ መሰዋታቸዉ የምናስታውሰው መራራ እዉነት ነዉ::
ፅንፈኛና የሃይማኖት አባቶችን መግ*ደል ስራው ያደረገው የሽብር ቡድን በዛሬዉ እለት በባቲ ማህበረሰብ ዘንድ ከሃይማኖት አባትነት ባለፈ በማሸማገል ፤ እርቅና ህዝቡን ወደአንድነት በመጥራት አባት የነበሩትን ሸይኽ የህያ ይማምን በግፍ ሕይወታቸዉን ቀጥፏል::
መንግስት የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ማረጋገጥ ቅድሚያ ሊሰጠዉ የሚገባ ተግባር በማድረግ እንዲሰራ እየጠየቅን ፤ ማህበረሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር የፅንፈኞችን ህልም ሊያመክን እንደሚገባ እንገልፃለን::
ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን።
አላህ (ሱ.ወ) ለክቡር ሸይኽ የህያ ይማም ሰፊ ምሕረቱን ያድርግላቸው ፤ ወንጀላቸውን ይማር ፤ ጀነተል ፊርደውስን ያውርሳቸው ለቤተሰቦቻቸውና ለሚወዷቸው ሁሉ ሰብርና መጽናናትን ይስጥ።
አሚን🤲 | 1 822 |
| 6 | Нет текста... | 2 111 |
| 7 | ሙስሊሙ ማኅበረሰብ በቢሮክራሲው ውስጥ ያለውን ተመጣጣኝ ውክልና የማረጋገጥ ጥያቄ ሊመለስ ይገባል!!!
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
እኩልና ተመጣጣኝ የቢሮክራሲ ውክልናን በሀገሪቱ የማረጋገጥ ጉዳይ በትክክል መሬት ላይ ወርዶ ሊተገበር ይገባል:: በሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ላይ ተሳታፊ ሙስሊሞችም ሆነ የሌላ እምነት ተከታይ ወገኖቻችን ስለሀገሪቷ ቀጣይ እጣፈንታ ስለፍትህ ስለእኩልነት ስትሉ እነኚህ የዘመናት ጥያቄ እንዲመለሱ እንድትተጉ እንገልፃለን:-
በአንድ ሀገር ውስጥ ፍትሃዊ አገልግሎት፣ የትምህርትና የመንግስት ተቋማት ሀገርን የመምሰል ደረጃቸው በዚያ ሀገር ውስጥ ከታች አንደኛ ደረጃ ትምህርት ጀምሮ እስከ ላይኛው የፌዴራል መንግስት መዋቅሮች ድረስ ለሁሉም ዜጎች ክፍት የሆኑና ሁሉም ዜጎች ሊደርሱበት የሚችሉ መሆኑን ማሳያ ነው፡፡
በሌላ በኩል ወካይ ያልሆነ የፌዴራል ቢሮክራሲ፣ ወካይ ያልሆነ የትምህርት ስርዓት፣ የቅጥር መስፈርት እና ሚዛናዊ ያልሆኑ የተቋማትና የሀገር መሪዎች ስብጥር ማግለልን ያሳያል፡፡ በመሆኑም ይህንን ለመቀየር አቅምን ማዕከል ማድረጉ እንደተጠበቀ ሆኖ ወካይ ቢሮክራሲ ሊኖረን ይገባል፡፡
በተጨማሪም የፌዴራል ቢሮክራሲውን የማመጣጠን ሥራው በተለምዶ እንደሚሞከረው ብሔሮችን ብቻ ታሳቢ ካደረገ ለዘመናት የዘለቀውን የሙስሊሙን በመንግስት ተቋማት ውስጥ ያለውን የማገልገል እና የመወከል እድል እጦት ለተጨማሪ ዘመናት ያስቀጥለዋል፡፡ ስለዚህም በመንግስት በኩል ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት በብሔራዊ ምክክሩ ቁልፍ አጀንዳ ሆኖ መፍትሄ ሊሰጠው ይገባል፡፡
በሀገሪቱ የለውጥ ውይይቶች ውስጥ አንዳንዶች የብሔር፣ የጾታ ወይም የአካል ጉዳተኞችን እኩልነትና ተጠቃሚነት ለማረም ፍላጎት ሲያሳዩ፤ ጥያቄው ወደ ሃይማኖታዊ ፍትሐዊነትና እኩልነት ሲመጣ ግን ሆን ብለው የመዝለል (የማለፍ) አዝማሚያ ያሳያሉ። ይህ ዓይነቱ አካሄድ ለዘመናት በበላይነት ተጠቃሚ ከነበሩት ወገኖች የሚመነጭ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስና በከፍተኛ የመንግሥት የሥልጣን እርከኖች ላይ ካላቸው ተገቢ ያልሆነ ድርሻ ላይ ቅነሳ እንዳይመጣ ከመስጋት የሚመነጭ ነው።
እንዲያውም አንዳንዶች ይህንን ሕገ-መንግሥታዊ የእኩልነትና የፍትሐዊ ተመጣጣኝ ውክልና ጥያቄን “የጽንፈኝነት” ወይም “የሌላ አጀንዳ” አድርገው ለመፈረጅ ይሞክራሉ። ይህ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ሕጋዊና ፍትሐዊ ጥያቄዎች ለማፈንና ለማስማማት የሚደረግ ስልታዊ አካሄድ (Strategies of silencing) በመሆኑ፣ ይህንን ለማረም የሚከተሉት እርምጃዎች መወሰድ አለባቸው፦
1) የሙስሊሙ ማኅበረሰብ በቢሮክራሲው ውስጥ ያለውን ተመጣጣኝ ውክልና የማረጋገጥ ጥያቄ የዴሞክራሲ፣ የዜግነት መብት እና የፍትሐዊነት ጥያቄ እንጂ ከማንኛውም የፖለቲካ አጀንዳ ጋር እንደማይገናኝ በመረዳት ግልጽ መፍትሄ ማስቀመጥ ይገባል።
2) የሀገሪቱን ተቋማት “ሀገርን የመምሰል” (Representative Bureaucracy) ሂደት ከብሔር ስብጥር ባለፈ፣ ሃይማኖታዊ ስብጥርን ጭምር ፍትሐዊ በሆነ መልኩ ያካተተ እንዲሆን ማድረግ።
3) ፍትሐዊ ውክልናን ለመጠየቅ የሚደረጉ ሕዝባዊና ምሁራዊ እንቅስቃሴዎችን በጽንፈኝነት የመፈረጅን አድሏዊ አዝማሚያ አልያም መሰል ጥያቄዎች እንዳይነሱ እርስ በእርስ በማጋጨትና ተከታታይ የመጥመጃ አጀንዳዎችን በመስጠት ህዝበ ሙስሊሙን እሳት በማጥፋት ላይ በመጥመድ ጉዳይ እንዲያበቃ የእኩልነት፣የተገቢ ዉክልናና የእኩል ተጠቃሚነት ጉዳይ በሕግና በግልጽ መድረኮች መታገል። | 1 980 |
| 8 | Нет текста... | 1 874 |
| 9 | የአካታችነት ና የብዝኅነት ጉድለቶች
በሀገራዊ ምክክር ላይ ለምትሳተፉ ሙስሊሞች በሙሉ!
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
ሚዲያ፥ ስነ-ጥበብ፥ መድረኮችና የእንግዳ አቀባበል ዝግጅቶች በተመለከተ የሀገሪቱን የብዝሃነት እውነታ ባማከለ መልኩ እንዲሆን ከሀሳብ ጀምሮ መሬት ላይ እንዲተገበር እድትሰሩ ስለማሳወቅ:-
⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕
በእነዚህ ዘርፎች ውስጥ የሚንጸባረቁ ምስሎች፣ አለባበሶች እና አቀራረቦች የሀገሪቱን የብዝሃነት እውነታ በትክክል መወከል ይኖርባቸዋል። ይሁን እንጂ በተግባር የሚታዩ የአካታችነት ጉድለቶች፣ በተለይም የሙስሊሙን ማኅበረሰብ እሴቶችና መገለጫዎች ያገለሉ ወይም ያደበዘዙ አቀራረቦች ሊታረሙና ሥርዓት ሊበጅላቸው ይገባል።
1) በመንግስታዊ ሚዲያዎች ላይ የሚቀርቡ አለባበሶችና መገለጫዎች ሁሉንም የወከሉ አይደሉም፡፡ በሀገሪቱ ይፋዊ ሚዲያዎች ላይ በሚቀርቡ የዜናና ሌሎች ዝግጅቶች ላይ ኢስላማዊ አለባበስ ለብሶ ማቅረብ የተከለከለ ነው፡፡ በመሰል ሁኔታ ላይ ኢስላማዊ አለባበስ እንዳይታይ መከልከል ማለት ኢስላማዊ የማንነት መገለጫን ከህዝብ እይታ የመደበቅ ስራ በመሆኑ ይህ ተወግዶ አካታች መሆን አለበት።
2) ሁሉን ዓቀፍ ሊሆኑ የሚገባቸው ብሔራዊ መድረኮች በሚዘጋጁበት እና በሚመሩበት ወቅት የመድረኩ ጀርባ የሚገነባባቸው ቅርፃ ቅርፆችና ስዕሎች፣ የመድረክ መሪዎች የሚለብሷቸው አልባሳት እና በዓላትን ለመግለፅ የሚጠቀሙባቸው አገላለፆች ወዘተ አካታችነት የጎደላቸው በመሆናቸው እነዚህን ለማረም እና ለማረቅ ተገቢ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ እንዲዘጋጅላቸው ማስቻል።
3) ከውጭ ሀገር እንግዶች ወደ ሀገራችን በሚገቡበት ወቅት የሙስሊሙንም እሴቶች ጎላ አድርገው የሚያቀርቡ አቀባበሎችና አለባበሶች እንዲኖሩ ማድረግ።
4) የኢትዮጵያ እየተባሉ የሚቀርቡ ኪነ-ጥበቦችና ስነ-ጥበቦች በአብዛኛው ሙስሊሞችን የዘነጉ አልያም ተገቢ ባልሆነ መልኩ የሳሉ በመሆናቸው በፍትሃዊነትና በአካታችነት መርህ ሊታረሙ ይገባል። | 1 860 |
| 10 | Нет текста... | 1 669 |
| 11 | Haala kanaan uffannaan Islaamummaa akka hin mul'anne dhorkuun agarsiiftuu eenyummaa Islaamummaa ija uummataa jalaa dhoksuu waan ta'eef, kun dhabamee hunda-ammataa ta'uu qaba.
2) Sagantaaleen biyyoolessaa hunda-ammataa ta'uu qaban yeroo qophaa'anii fi durfamanitti, bocawwan fi fakkiiwwan dugda-duuba (background) jiran, uffannaan dhiheessitoota sagantaa fi jechamoonni ayyaanota ibsuuf itti fayyadaman kkf hunda-ammataa waan hin taaneef, kanneen sirreessuuf seera dhimma kanaan wal qabatu uumuun barbaachisaa dha.
3) Keessummoonni alaa yeroo gara biyya keenyaa dhufanitti, duudhaalee hawaasa Musliimaas haala kanaan mul'isuun simannaa fi uffannaan sun akka jiraatu gochuu.
4) Kineensawwan (Aartii fi Iskiitii) kan Itiyoophiyaa jedhamanii dhiyaatan baay'een isaanii hawaasa Musliimaa kan dagatan ykn haala sirrii hin taaneen kan dhiheessan waan ta'aniif, qajeeltoo haqaa fi hunda-ammataa ta'een sirreeffamuu qabu.
#ኢትዮጵያ
#ሙስሊሞች
#ኢስላም
#ሀገራዊ_ምክክር
#የሙስሊሞች_ጥያቄዎች
#ኢትዮጵያዊነት
#የጋራ_መፍትሄ
#ፍትህና_እኩልነት
#የኢትዮጵያ_ሙስሊሞች
#ብሄራዊ_ውይይት
#መብትና_ግዴታ
#የሃይማኖት_እኩልነት
#MariBiyyoolessaa
#GaaffiiMuslimootaa
#MariifiNagaa
#EenyummaaFiMirga
#HaqaaFiWalqixxummaa
#MuslimootaItoophiyaa
#FurmaataWaliinii
#SagaleeMuslimootaa
#Tokkummaa
#NationalDialogueEthiopia
#EthiopianMuslims
#NationalConsensus
#ሀገራዊምክክር
#religiousequality | 1 641 |
| 12 | ሕዝባዊ ስፍራዎች፣ የከተማ እና መንደሮች ስያሜ
✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅
Moggaasa Iddoowwan Hawaasaa, Magaalotaa fi Gandootaa
📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶
በአንድ ባለብዙ-ባህል እና ልዩ ልዩ እምነቶች ባሉባት ሀገር ውስጥ፣ የሕዝብ መገልገያ ቦታዎች እና የስያሜዎች አሰጣጥ ሥርዓት ማኅበራዊ ትስስርን ለመገንባት ወይም ለማላላት ከፍተኛ ሚና አላቸው። ሕዝባዊ ስፍራዎች (Public Spheres) የሁሉም ዜጋ የጋራ መገለጫዎች በመሆናቸው፣ የእነዚህ ስፍራዎች ስያሜና አጠቃቀም ፍትሐዊነትን፣ አካታችነትን እና የሕገ-መንግሥቱን የሴኩላሪዝም (የመንግሥትና የሃይማኖት መለያየት) መርህ የተከተለ መሆን ይኖርበታል።
እና ምን ይሁን?
📶📶📶📶
1) ማናቸውም ህዝባዊ ስፍራዎች (Public Sphere) ስያሜዎች እና መጠሪያዎች ከማንኛውም ሃይማኖታዊ መገለጫዎች ነፃ መሆን አለባቸው። ስለሆነም የቦታ ስያሜዎች እና መጠሪያዎች ለድርድር ከመቅረባቸው በፊት የሃገሪቷ ህገ መንግስት አካል የሆነውን የሃይማኖት እና የመንግስትን መለያየት መሠረት ያደረገ አካሄድ መከተሉ ብዙ ጉዳዮችን ሊያቀል ይችላል።
2) ማንኛውም የሕዝብ መገልገያ ስፍራዎች (Public Sphere)፣ አደባባዮች፣ መንገዶች፣ እንዲሁም የመንግስትና የሕዝብ ተቋማት (እንደ ሆስፒታሎች፣ ባንኮች፣ የትምህርት ተቋማት ወዘተ) ሴኩላር መሆን አለባቸው፡፡ ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ማንኛውም ስያሜና አጠራር በሃገሪቱ ያለውን የሃይማኖት ስብጥር ፍትሃዊ በሆነ መንገድ (equitable) የሚያንፀባርቅ እንዲሆን ማስቻል ይገባል።
ሚዲያ፥ ስነ-ጥበብ፥ መድረኮችና የእንግዳ አቀባበል ዝግጅቶች
⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕
በእነዚህ ዘርፎች ውስጥ የሚንጸባረቁ ምስሎች፣ አለባበሶች እና አቀራረቦች የሀገሪቱን የብዝሃነት እውነታ በትክክል መወከል ይኖርባቸዋል። ይሁን እንጂ በተግባር የሚታዩ የአካታችነት ጉድለቶች፣ በተለይም የሙስሊሙን ማኅበረሰብ እሴቶችና መገለጫዎች ያገለሉ ወይም ያደበዘዙ አቀራረቦች ሊታረሙና ሥርዓት ሊበጅላቸው ይገባል።
እና ምን ይሁን?
🔴🔴🔴🔴
1) በመንግስታዊ ሚዲያዎች ላይ የሚቀርቡ አለባበሶችና መገለጫዎች ሁሉንም የወከሉ አይደሉም፡፡ በሀገሪቱ ይፋዊ ሚዲያዎች ላይ በሚቀርቡ የዜናና ሌሎች ዝግጅቶች ላይ ኢስላማዊ አለባበስ ለብሶ ማቅረብ የተከለከለ ነው፡፡ በመሰል ሁኔታ ላይ ኢስላማዊ አለባበስ እንዳይታይ መከልከል ማለት ኢስላማዊ የማንነት መገለጫን ከህዝብ እይታ የመደበቅ ስራ በመሆኑ ይህ ተወግዶ አካታች መሆን አለበት።
2) ሁሉን ዓቀፍ ሊሆኑ የሚገባቸው ብሔራዊ መድረኮች በሚዘጋጁበት እና በሚመሩበት ወቅት የመድረኩ ጀርባ የሚገነባባቸው ቅርፃ ቅርፆችና ስዕሎች፣ የመድረክ መሪዎች የሚለብሷቸው አልባሳት እና በዓላትን ለመግለፅ የሚጠቀሙባቸው አገላለፆች ወዘተ አካታችነት የጎደላቸው በመሆናቸው እነዚህን ለማረም እና ለማረቅ ተገቢ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ እንዲዘጋጅላቸው ማስቻል።
3) ከውጭ ሀገር እንግዶች ወደ ሀገራችን በሚገቡበት ወቅት የሙስሊሙንም እሴቶች ጎላ አድርገው የሚያቀርቡ አቀባበሎችና አለባበሶች እንዲኖሩ ማድረግ።
4) የኢትዮጵያ እየተባሉ የሚቀርቡ ኪነ-ጥበቦችና ስነ-ጥበቦች በአብዛኛው ሙስሊሞችን የዘነጉ አልያም ተገቢ ባልሆነ መልኩ የሳሉ በመሆናቸው በፍትሃዊነትና በአካታችነት መርህ ሊታረሙ ይገባል።
Moggaasa Iddoowwan Hawaasaa, Magaalotaa fi Gandootaa
✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅
Biyya aadaa baay'ee fi amantiiwwan garaa garaa qabdu keessatti, sirni iddoowwan tajaajila uummataa fi moggaasa maqootaa hidhata hawaasummaa ijaaruu ykn diiguu keessatti gahee gudbaa qabu.
Iddoowwan uummataa (Public Spheres) agarsiiftuu waliinii lammiilee hundaa amantii fi sabummaa malee waan ta'aniif, moggaasni fi itti fayyadamni iddoowwan kanaa loogii kan hin qabne, hunda-ammataa fi qajeeltoo seera-mootummaa keessatti tumame kan seculaarizimii (adda ba'uu mootummaa fi amantii) hordofe ta'uu qaba.
Maaltu haa ta'u ree?
📶📶📶📶📶📶📶📶
1) Maqoonni fi moggaasni iddoowwan uummataa (Public Sphere) kamiyyuu agarsiiftuu amantii kamirraayyuu walaba ta'uu qabu. Kanaafuu, moggaasni maqaa bakkaa dhimma marii fi daldala siyaasaaf dhiyaachuu isaa dura, qajeeltoo adda ba'uu mootummaa fi amantii kan qaama seera-mootummaa biyyattii ta'e bu'uureffachuu isaa mirkaneessuun dhimmoota baay'ee salphisuu danda'a.
2) Iddoowwan tajaajila uummataa (Public Sphere) kamiyyuu, addabaabayyonni, daandiiwwan, akkasumas dhaabbanni mootummaa fi uummataa (kanneen akka hospitaalotaa, baankotaa, dhaabbata barnootaa fi kkf) seculaar (sekulaar) ta'uu qabu. Kun kan hin taane yoo ta'e garuu, moggaasni fi waamichi kamiyyuu madaallii amantii biyyattii keessa jiru haala loogii hin qabneen (equitable) kan calaqqisiisu ta'uu qaba.
Miidiyaa, Kileensa (Aartii), Sirnoota fi Qophiiwwan Keessummoota Simachuu
⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕
Fakkiiwwan, uffannaan fi dhiheenyiwwan dameewwan kanaan calaqqisifaman dhugaa fi baay'ina (diversity) biyyattii haala sirriin bakka bu'uu qabu. Ta'us garuu, hanqinni hunda-ammataa ta'uu (inclusivity) muuxannoo keessatti mul'atu, keessumattuu dhiheenyiwwan duudhaalee fi eenyummaa hawaasa Musliimaa hanqisan ykn dhoksan sirreeffamanii sirna uumamuu qaba.
Maaltu haa ta'u ree?
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
1) Miidiyaalee mootummaa keessatti uffannaan fi agarsiistuuwwan dhiyaatan kan hunda bakka bu'an miti. Miidiyaalee dhimma addaa (official) biyyattii keessatti oddeeffannoo fi qophiiwwan biroo dhiyaatan irratti uffannaa Islaamummaa uffatanii dhiyaachuun dhorkamaa dha. | 1 807 |
| 13 | አፋልጉኝ
ስም-ኢዘዲን ላሎ
ትውልድና እድገቱ ወራቤ ከተማ አስተዳደር፣አልከሶ ቀበሌ፣
አቶ ኢዘዲን ላሎ በአጋጣሚ ባደረበት የአእምሮ ህመም ምክንያት ከቤት አምልጦ የጠፋ ሲሆን፣በአሁን ሰዓት ያሉበትን ቦታ ለማወቅ ቤተሰብ በከፍተኛ ጭንቀት ላይ ይገኛል።
የለበሰው ልብስ እና መለያ ምልክት
ጥቁር ሸሚዝ፣ ቡኒ (ቡነማ) ሱሪ በባዶ እግሩ ነው ልዩ ምልክት:በእጁ ላይ ካቴና ታስሯል።
ወንድማችንን ያየ ወይም ያለበትን ቦታ የሚያውቅ ሰው እባክዎትን ለአላህ/ለፈጣሪ ብለው ከታች ባለው የስልክ ቁጥር በመደወል ለቤተሰቦቹ ጥቆማ እንዲሰጡ በትህትና እንጠይቃለን።
ፈላጊ ወንድሙ:ጁዋር ስራጅ
ስልክ ቁጥር: 📱 0910882887
| 561 |
| 14 | አፋልጉን
ስም-አህምዲን ኡመር
ከዳለቲ ኑር መስጂድ በቀን 2/11/2018 ቀን 11 ሰዓት አከባቢ ከቤት እንደወጣ አልተመለሰም።
ከታች በምስሉ ላይ የምትመለከቱትን አህመዲን ዑመርን ያያችሁ ወይንም ያለበትን የምታውቁ በተቀመጡት ስልክ ቁጥሮች እንድታሳዉቁን በአላህ ስም እንጠይቃለን፦
📲0986 26 13 58
📲0935 54 07 72
📲0939 47 60 82 | 2 096 |
| 15 | አፋልጉኝ
ስም ቢላል ኸሊል ያሲን
ከ 1 አመት በፊት /ታህሳስ 8/4/2017 ስራ ከሚሰራበት መርካቶ አከባቢ ቁርስ ልብላ ብሎ በግምት ከረፋዱ 5:00 ሰዓት ላይ እንደወጣ ፤ ሊመለስ አልቻለም።
እናት በልጃቸዉ መጥፋት ሀዘን ላይ ወድቀዉ ሁሌም ሲያለቅሱ ይዉላሉ።
እባካችሁ በምስሉ ላይ የምትመለከቱትን ወንድማችንን ቢላል ኸሊልን ያያችሁ ወይንም ያለበትን የምታዉቁ ከታች በተቀመጡት ስልክ ቁጥሮች አሳዉቁን፦
📲0920 54 33 33
📲 0911 76 71 70 | 2 599 |
| 16 | የኢትዮጵያውያን ሙስሊም ጀግኖች መዝከር በሁሉም ልጆቿ መስዋዕትነት የቆመች ኩሩ ሀገር - ኢትዮጵያ
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
በአንድ አካባቢና ባህል ውስጥ ብቻ የታጠረው የሀገር ጀግኖች ሙገሳና በተለያዩ ሀገራዊ ሁነቶች የመዘከር አካሄድ ሀገራችንን በሙሉ ምስሏ ስለማይገልፃት በብሔራዊ ምክክሩ ሊከለስ ይገባል፡፡ በአብዛኛው የሀገር ጀግኖች አሰያየም ትርክት ሌሎች ህዝቦች ጀግኖቻቸውን እንዳያውቁ፣ እንዳያስተዋውቁ፣ በተለያዩ ሁነቶች እንዳይወክሉ እንቅፋት ሆኗል።
በአንድ ወገን የበላይነት ላይ ብቻ የተመሰረተው የጀግኖች አሰያየም ሂደት ተከልሶ፣ እነዚህ የኢትዮጵያውያን ሙስሊም ጀግኖች እና የባህል ምልክቶች ተገቢውን ብሔራዊ እውቅና ማግኘታቸው፣ ኢትዮጵያ በእውነትም የሁሉም ህዝቦቿ የጋራ እሴትና በሁሉም ልጆቿ መስዋዕትነት የቆመች ኩሩ ሀገር መሆኗን በተሟላ ምስል ለማሳየት ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
NB-በኢትዮጵያ አራት ሺህ ሰዎች የሚሳተፉበት ሀገራዊ ምክክር ሊካሄድ ጥቂት ቀናቶች ቀርተውታል። በዚህ ሂደት ተሳታፊ የሚሆኑ ሙስሊሞች ሁሉ በንቃትና በብቃት በኢትዮጵያ የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ጥያቄዎችና አጀንዳዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ ሊያደርጉ ይገባል። ስለሆነም፣ በዚህ ሀገራዊ ምክክር ላይ ይህ በብሔራዊ ደረጃ የሚታየው የታሪክ አሻራዎችን የመደበቅ አካሄድ ተረትቶ፣ እነዚህ በዓለም የተመሰገኑ የኢትዮጵያ ሙስሊም ጀግኖች በሀገራቸውም የመንግስት እውቅና አግኝተው ስማቸው በትላልቅ ብሔራዊ ተቋማት ላይ ሊሰየም ይገባል። | 2 522 |
| 17 | ወንድማችንን አፋልጉን
ስም- ሃያቱ ኢማሙ አህመድ
ከ5 አመታት በፊት ይኖርበት ከነበረዉ አዳማ ቀበሌ 11 ለስራ በሚል ወደድሬደዋ እንደወጣ ዛሬም ድረስ አልተመለሰም።
እባካችሁ ወንድማችንን ያያችሁ ወይንም ያለበትን የምታውቁ ከታች በተቀመጡት ስልክ ቁጥሮች አሳዉቁን ይላሉ ፈላጊ ቤተሰቦቹ፦
ፌሩዝ አብደላ
📲+251921893689
ሙና አብደላ
📲+251911038544 | 2 129 |
| 18 | ተከታታይ ጽሁፎች ስለሚለጠፉ በንቃት እንድታነቡ ፣ለሚሳታፉትም እንድታደርሱ!
ሀገራዊ ምክክሩና ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች
💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢
Marii Biyoolessaa fi Muslimoota Itoophiyaa
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
በኢትዮጵያ አራት ሺህ ሰዎች የሚሳተፉበት ሀገራዊ ምክክር ሊካሄድ ጥቂት ቀናቶች ቀርተውታል። በዚህ ሂደት ተሳታፊ የሚሆኑ ሙስሊሞች ሁሉ በንቃትና በብቃት በኢትዮጵያ የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ጥያቄዎችና አጀንዳዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ ሊያደርጉ ይገባል። ሰሞኑን በዚህ የፌስቡክ ገፅ በርካታ ተከታታይ ጽሁፎች ስለሚለጠፉ በንቃት እንድታነቡ ፣ለሚሳታፉትም እንድታደርሱ እጋብዛለሁ መልካም ንባብ።
Ahmedin Jebel-አሕመዲን ጀበል | 2 559 |
| 19 | Нет текста... | 2 663 |
| 20 | አንድ ሕይወት አለፈ፤ አንድ ቤተሰብ ግን አሁንም የእኛን እጅ ይፈልጋል!
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
ወንድማችን ዘይኔ ፈድሉ በአፋልጉኝ ማስታወቂያ በዚሁ የማሕበራዊ ሚዲያ ሲፈለግ ሰንብቶ- ሕይወቱ አልፎ መገኘቱ ይታወቃል። በሰዎች የጭካኔ ተግባር ለመፈፀሙ ደረቱ አከባቢ በስለት የተወጋበት አስክሬን አካሉ ምስክር ነዉ። የወንጀል ዝርዝሩን የከተማዉ የፖሊስ ኮምሽን በዝርዝር እንደሚያቀርብ ተስፋ አለን።
ወንድማችንን በድንገት በማጣታችን የተሰማን ሀዘን በቃላት የሚገለጽ አይደለም። ይህ ክስተት አንድን ቤተሰብ ብቻ ሳይሆን ጓደኞቹን፣ ዘመዶቹንና ማህበረሰባችንን በሙሉ ያሳዘነ ነው። ከዚህ አሳዛኝ ክስተት በኋላ የቀሩት ባለቤቱና ገና ያልተወለደው ልጅ ከሁላችንም ድጋፍና አብሮነት ይፈልጋሉ።
ዛሬ የምንሰጠው የገንዘብ ድጋፍ ቁጥር ብቻ አይደለም፤ ለዚህ ቤተሰብ “ብቻችሁን አይደላችሁም” የሚል የተስፋ መልእክት ነው። ትንሽም ቢሆን ከልብ የተሰጠ እገዛ በእነሱ ሕይወት ትልቅ ለውጥ ሊያመጣ ይችላል።
እናት ሆና ልጇን ለመቀበል የምትጠባበቅ ሴት በዚህ አስከፊ ሁኔታ ውስጥ የምትገኝ መሆኗን ስናስብ ልባችን ይነካል። ያ ሕፃን ወደ ዓለም ሲመጣ የአባቱን ፍቅር ባያገኝም፣ የማህበረሰቡን ፍቅርና ድጋፍ እንዲያገኝ የማድረግ ኃላፊነት የሁላችንም ነው።
ስለዚህ እያንዳንዳችን የበኩላችንን እናበርክት። ብዙ ሰዎች በጥቂቱም ቢሆን ቢያበረክቱ ትልቅ ድጋፍ ይፈጠራል። የምንሰጠው እርዳታ ለዚህ ቤተሰብ የዛሬን ችግር ለማቃለል ብቻ ሳይሆን ለነገውም ተስፋ የሚሆን መሠረት ይሆናል።
የወንድማችን ስርዓተ ቀብር በዛሬዉ እለት ቱሉዲምቱ በሚገኘዉ የሙስሊም መካነ መቃብር ቤተሰቦች ፣ ጏደኞቹና ወዳጆቹ በተገኙበት ተፈፅሟል:: ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን አላህ ማረፊያዉን ጀነተል ፊርደውስ ያድርገዉ:: አሚን! 🤲🏽 ለባለቤቱና ለቤተሰቡ በሙሉ አሏህ(ሱ.ወ) መጽናናትን ይሰጣቸው:: 🤲🏽 | 2 604 |
