Mujib Amino Z islam
📈 Telegram kanali Mujib Amino Z islam analitikasi
Mujib Amino Z islam (@mujibbinislam) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 14 557 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 984-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 323-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 14 557 obunachiga ega bo‘ldi.
09 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -81 ga, so‘nggi 24 soatda esa -1 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 27.65% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 9.79% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 026 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 426 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 17 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Kanal uchun tavsif kiritilmagan.
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 10 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 10 Iyul | 0 | |||
| 09 Iyul | 0 | |||
| 08 Iyul | 0 | |||
| 07 Iyul | +2 | |||
| 06 Iyul | +2 | |||
| 05 Iyul | 0 | |||
| 04 Iyul | +2 | |||
| 03 Iyul | +2 | |||
| 02 Iyul | +9 | |||
| 01 Iyul | +7 |
| 2 | ወንድማችንን አፋልጉን
ስም- ሃያቱ ኢማሙ አህመድ
ከ5 አመታት በፊት ይኖርበት ከነበረዉ አዳማ ቀበሌ 11 ለስራ በሚል ወደድሬደዋ እንደወጣ ዛሬም ድረስ አልተመለሰም።
እባካችሁ ወንድማችንን ያያችሁ ወይንም ያለበትን የምታውቁ ከታች በተቀመጡት ስልክ ቁጥሮች አሳዉቁን ይላሉ ፈላጊ ቤተሰቦቹ፦
ፌሩዝ አብደላ
📲+251921893689
ሙና አብደላ
📲+251911038544 | 957 |
| 3 | ተከታታይ ጽሁፎች ስለሚለጠፉ በንቃት እንድታነቡ ፣ለሚሳታፉትም እንድታደርሱ!
ሀገራዊ ምክክሩና ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች
💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢
Marii Biyoolessaa fi Muslimoota Itoophiyaa
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
በኢትዮጵያ አራት ሺህ ሰዎች የሚሳተፉበት ሀገራዊ ምክክር ሊካሄድ ጥቂት ቀናቶች ቀርተውታል። በዚህ ሂደት ተሳታፊ የሚሆኑ ሙስሊሞች ሁሉ በንቃትና በብቃት በኢትዮጵያ የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ጥያቄዎችና አጀንዳዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ ሊያደርጉ ይገባል። ሰሞኑን በዚህ የፌስቡክ ገፅ በርካታ ተከታታይ ጽሁፎች ስለሚለጠፉ በንቃት እንድታነቡ ፣ለሚሳታፉትም እንድታደርሱ እጋብዛለሁ መልካም ንባብ።
Ahmedin Jebel-አሕመዲን ጀበል | 1 111 |
| 4 | Matn yo'q... | 1 670 |
| 5 | አንድ ሕይወት አለፈ፤ አንድ ቤተሰብ ግን አሁንም የእኛን እጅ ይፈልጋል!
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
ወንድማችን ዘይኔ ፈድሉ በአፋልጉኝ ማስታወቂያ በዚሁ የማሕበራዊ ሚዲያ ሲፈለግ ሰንብቶ- ሕይወቱ አልፎ መገኘቱ ይታወቃል። በሰዎች የጭካኔ ተግባር ለመፈፀሙ ደረቱ አከባቢ በስለት የተወጋበት አስክሬን አካሉ ምስክር ነዉ። የወንጀል ዝርዝሩን የከተማዉ የፖሊስ ኮምሽን በዝርዝር እንደሚያቀርብ ተስፋ አለን።
ወንድማችንን በድንገት በማጣታችን የተሰማን ሀዘን በቃላት የሚገለጽ አይደለም። ይህ ክስተት አንድን ቤተሰብ ብቻ ሳይሆን ጓደኞቹን፣ ዘመዶቹንና ማህበረሰባችንን በሙሉ ያሳዘነ ነው። ከዚህ አሳዛኝ ክስተት በኋላ የቀሩት ባለቤቱና ገና ያልተወለደው ልጅ ከሁላችንም ድጋፍና አብሮነት ይፈልጋሉ።
ዛሬ የምንሰጠው የገንዘብ ድጋፍ ቁጥር ብቻ አይደለም፤ ለዚህ ቤተሰብ “ብቻችሁን አይደላችሁም” የሚል የተስፋ መልእክት ነው። ትንሽም ቢሆን ከልብ የተሰጠ እገዛ በእነሱ ሕይወት ትልቅ ለውጥ ሊያመጣ ይችላል።
እናት ሆና ልጇን ለመቀበል የምትጠባበቅ ሴት በዚህ አስከፊ ሁኔታ ውስጥ የምትገኝ መሆኗን ስናስብ ልባችን ይነካል። ያ ሕፃን ወደ ዓለም ሲመጣ የአባቱን ፍቅር ባያገኝም፣ የማህበረሰቡን ፍቅርና ድጋፍ እንዲያገኝ የማድረግ ኃላፊነት የሁላችንም ነው።
ስለዚህ እያንዳንዳችን የበኩላችንን እናበርክት። ብዙ ሰዎች በጥቂቱም ቢሆን ቢያበረክቱ ትልቅ ድጋፍ ይፈጠራል። የምንሰጠው እርዳታ ለዚህ ቤተሰብ የዛሬን ችግር ለማቃለል ብቻ ሳይሆን ለነገውም ተስፋ የሚሆን መሠረት ይሆናል።
የወንድማችን ስርዓተ ቀብር በዛሬዉ እለት ቱሉዲምቱ በሚገኘዉ የሙስሊም መካነ መቃብር ቤተሰቦች ፣ ጏደኞቹና ወዳጆቹ በተገኙበት ተፈፅሟል:: ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን አላህ ማረፊያዉን ጀነተል ፊርደውስ ያድርገዉ:: አሚን! 🤲🏽 ለባለቤቱና ለቤተሰቡ በሙሉ አሏህ(ሱ.ወ) መጽናናትን ይሰጣቸው:: 🤲🏽 | 1 661 |
| 6 | ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን
ወንድማችን ዘይኔ ፈድሉ ተገድሎ አስክሬኑ በጫካ ውስጥ ተገኝቷል!
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
ከቀናት በፊት ወንድማችን ዘይኔ ፈድሉ ከቤት እንደወጣ ሳይመለስ መቅረቱን በመግለጽ የአፋልጉኝ ማስታወቂያ አጋርተን ነበር።
ሆኖም በሚያሳዝን ሁኔታ በዛሬዉ እለት አስክሬኑ በአዲስ አበባ ከተማ ከቡልቡላ ወደኮዬ ፈጬ በሚወስደዉ አዲሱ መንገድ ጫካ ዉስጥ ሕይወቱ አልፎ ተገኝቷል።
ወንድማችን ዘይኔ በመልካም ባህሪው የሚታወቅ፤ በአከባቢዉ ማህበረሰብ የሚወደድ ወጣት የነበረ ሲሆን ሕይወቱ በዚህ መልኩ ማለፉ አስደንጋጭ ክስተት ሆኗል። ባለቤቱ ነፍሰጡር መሆኗና እርሱ በሚሰራዉ ስራ መተዳደራችዉ ቤተሰቡ ላይ ከባድ ሀዘን ፈጥሯል።
ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን
አላህ ጀነተልፊርደውስን እንዲያጎናፅፈዉ፣ ቀብሩንም የጀነት ጨፌ እንዲያደርግለት፤ ለቤተሰቦቹም መጽናናትን እንመኛለን።
አሚን 🤲 | 2 526 |
| 7 | 💫ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም
🎙አቅራቢ: ኡስታዝ ማህሙድ ሀሰን
🔥ርዕስ : ወጣትነት እና ትርፍ ጊዜ
📅ቀን:እሁድ 28/10/2018
🕰ሰዓት :የዙሁር ሰላት እንደተሰገደ
አድራሻ: 🕌አብነት ከፍ ብሎ በሚገኘው ዑመር ኢብኑል ኸጣብ(26)መስጂድ
📌 አቡ አል-ዓታሂያ እንዲህ ይላሉ ፡
«ወጣትነት፣ ባዶ ጊዜ እና ብዙ ሀብት ለሰው እጅግ የሚያበላሹ ናቸው» | 3 625 |
| 8 | አልሀምድሊላህ : ከቤተሰቦቹ ጋር ተገናኝቷል | 3 842 |
| 9 | የአፋልጉኝ ማስታወቂያ‼
ወንድማችን ዐብዱልሃዲ ኸይረዲን ኑሪ በ19/10/2018 አንፎ ደንበል መስጂድ አካባቢ ከሚገኘው ቤታቸው እንደወጡ አልተመለሱም ። አቶ ዐብዱልሃዲ ኸይረዲን የልጆች አባት እና የቤተሰብ አስተዳዳሪ ነው። ቤተሰብ በጣም ጭንቀት ላይ ስለሆነ ያየ ወይም ያለበትን የሚያውቅ ቢያሳውቀን ወሮታ ከፋይ ነን ይላሉ ቤተሰቦቹ
ስልክ: 0911235477። | 3 681 |
| 10 | Matn yo'q... | 4 254 |
| 11 | Matn yo'q... | 3 686 |
| 12 | የንጹሐን ደም ምንም ዓላማ አያጸድቀውም
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
Mujib Amino
ሃይማኖት የሰላም፣ የእርቅ፣ የፍቅር እና የሰብዓዊነት እሴቶችን የሚያስተምር ተቋም ነው። እነዚህን እሴቶች የሚያስተምሩ የሃይማኖት መሪዎችን በጥይት ማጥቃት ወይም መግደል ደግሞ በአንድ ግለሰብ ላይ ብቻ የተፈጸመ ጥቃት ሳይሆን፣ በሰላም፣ በሃይማኖት ነፃነት እና በማህበረሰብ አንድነት ላይ የተቃጣ ጥቃት ነው።
የፅንፈኝነት ዋና መለያው ልዩነትን አለመቀበል፣ ሃሳብን በኃይል ለማስገደድ መሞከር እና ፍርሃትን እንደ መሣሪያ መጠቀም ነው። የሃይማኖት አባትን ዒላማ ማድረግም የዚህ አስተሳሰብ አደገኛ መገለጫ ነው፤ ምክንያቱም ዓላማው አንድን ሰው መጉዳት ብቻ ሳይሆን ሰፊ ማህበረሰብን በፍርሃት እና በውጥረት ውስጥ ማስገባት ሊሆን ይችላል።
ማንኛውም ዓላማ የሰውን ሕይወት ከመከበር በላይ ሊቆም አይችልም። ንጹሐንን መግደል በማንም አካል ቢፈጸም ሊወገዝ የሚገባ ወንጀል ነው። የንጹሐን ደም ምንም ዓላማ አያጸድቀውም፤ የሚያስከትለው ሀዘን፣ ፍርሃት እና ተጨማሪ ግጭት ብቻ ነው። ዘላቂ መፍትሔ የሚገኘው በሕግ የበላይነት፣ በፍትሕ እና በሰላማዊ ውይይት እንጂ በጥይት አይደለም።
በማንኛውም ፖለቲካዊ፣ ሃይማኖታዊ፣ ወይም በሌላ ምክንያት ንጹሐንን ማጥቃት ወይም መግደል ፈጽሞ ሊያፀቅ አይችልም። የሚነገር ዓላማ ምንም ያህል ትልቅ ቢመስልም፣ የሰው ደም በላዩ ሲፈስ ሞራላዊ እና ሕጋዊ ተቀባይነቱን ያጣል።
ፅንፈኛ ከሀሳብ ተሻግሮ በተግባር ወደ ግድያ፣ ወደ ማስፈራራት እና ወደ ማኅበረሰብ መከፋፈል ሲያመራ የሚጎዱት በአብዛኛው ንጹሐን ዜጎች ናቸው። ታጣቂ ቡድኖችም ሆኑ ሌሎች ኃይል የሚጠቀሙ አካላት የሲቪል ሰዎችን ኢላማ ማድረግ በሕግም ሆነ በሰብዓዊ እሴት ተቀባይነት የለውም።
በአማራ ክልል ዳንግላ ከተማ ቀበሌ 02 በሚገኘው የኹጥባ መስጂድ ኢማም ሸይኽ ሱፍያን አደም የ 4 ልጅ አባት የነበሩና በማህበረሰቡ ዘንድ ክቡርና ወጣቶችን በመልካም ስነ ምግባር በማነፅ የሚታወቁ
የነበሩ የሃይማኖት መሪ በትላንትናዉ እለት ሰኔ 20/10/18 እለተ ቅዳሜ ምሽት ላይ የዒሻ ሶላታቸዉ ምዕመናኑ በማሰገድ ሲወጡ በአማራ ክልል ስር እየሰደደ የመጣዉ ፅንፈኝነትና የሽብር ግብረ ኀይል በጥይት በመምታት ግድያ ፈፅሟል::
ፋኖ ተብሎ የሚጠራዉ ፅንፈኛና ሙስሊም ጠል ቡድን በዚሁ ክልል ና በተለያዩ አከባቢዎች በርካታ ነዋሪዎችን እምነታቸዉን ምክንያት በማድረግ ብቻ እንግልትና ግድያ በተደጋጋሚ ፈፅሟል:: በጥቂት ጊዜያት ዉስጥ ብቻ እንደማሳያ:-
ሸይኽ መሐመድ ነጃው በአማራ ክልል በጎንደር ከተማ ፒያሳ ቀበሌ 11 በሚገኘው ሼህ መሐመድ ደሴ መስጂድ ላይ ኢማም ፅንፈኛዉና ባለሽብር ካባዉ ፋኖ ሚያዚያ 18 ቀን 2014 ገድ*ሏቸዋል::
በአማራ ክልል ጎንደር ዙሪያ ወረዳ እንፍራንዝ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሚያዚያ 10 እና 11 ቀን 2016 በፅንፈኛዉ ፋኖ ምክንያት የሸይኽ ኢብራሂም መህሊ የሃይማኖት እውቀት ማዕከል ላይ ሙዓዚኑን ጨምሮ 4 የሃይማኖት ትምህርት ተማሪዎች ተሰዉተዋል::
ሸይኽ ሲራጅ አብድሬ በአማራ ክልል ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ደንቢያ ወረዳ አየንባ ቀበሌ ውስጥ የመስጂድ ኢማም ግንቦት 10 ቀን 2016 የመግሪብ ሶላትን አሰግደው ሲወጡ፣ በፅንፈኞቹ ፋኖዎች ህይወታቸዉ አልፏል::
ሸይኽ ጀማል ከማል ኢሳ በደቡብ ወሎ ዞን፣ ቦረና ወረዳ፣ መካነ ሰላም ከተማ ቀበሌ 2 ውስጥ የሚገኘው አንጋፋው የኑር ሃጂ ነስሩ መስጂድ ኢማም የነበሩ ሲሆን
መስከረም 23 ቀን 2018 ዓ.ል በፋኖ ታጣቂዎች በተሰነዘረ አሰቃቂ ጥቃት መስጂድ ውስጥ እያሉ በግፍ በጥይት ተመትተው ተገድለዋል።•••ወዘተ የሽብር ዶሴዎች!
ፅንፈኝነት የሚሸነፈው በቁጣ ወይም በበቀል ሳይሆን፣ በፍትሕ፣ በጠንካራ ተቋማት እና በሕግ የበላይነት መሆኑን በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል። ስለዚህ መንግሥት በግልጽና በተጠያቂነት ሕግን ማስከበር ሲኖርበት፣ ማኅበረሰቡም ለሰላም፣ ለመቻቻል እና ለፍትሕ በመቆም የበኩሉን ኃላፊነት ሊወጣ ይገባል። ይህ ነው የአመፅና የፅንፈኝነት ዑደትን ለማስቆም ዘላቂ መንገድ የሚሆነዉ::
ከዚህ ጎን ለጎን የጥቃቱ ተደጋጋሚ ሰለባ የሆነዉ ሙስሊም ማህበረሰቡ ራሱን ፋኖ ብሎ የሚጠራዉን ፅንፈኛና ፀረ ኢስላም ቡድን ከበፊቱ በተሻለ ሁኔታ ነቅቶና ተደራጅቶ እንዲታገል ፣ የእርስ በእርስ ግንኙነቱንና ማህበራዊ ሕይወቱን በአንድነት ገመድ ማስተሳሰር ፣ ለነገ የማይባል የዛሬ ስራችንና ትግበራችን ሊሆን ይገባል::
በዚሁ አጋጣሚ ይሕ ፅንፈኛ ቡድን የማህበረሰብን አንድነት ለመናድና የዘመናት አብሮ የመኖር እሴትን ለማፈራረስና ለመበጠስ ሲል የአንድንት እምነት ተቋም መገለጫዎችና ቃላትን በመጠቀም ጠበቃ ና አገልጋይ በመምሰል ዉዥንብ ቢፈጥርም እዉነታዉ ግን ቆምኩለት የሚለዉን የእምነት ተቋም የሃይማኖት አባቶችን ጭምር በግፍ የሚገድል በመሆኑ የዚህ ሽብር እንቅስቃሴ ባለቤት ቡድኑ እንጂ ሃይማኖቶችና ተቋማቱ እንዳልሆኑ ልንገነዘብ ይገባል:: በእርግጥ አንዳንድ መምህራን ተብዬዎች ቀን የሰላም ባንዲራ ምሽት ላይ ጦርነት መጎሰም ስራቸዉ ያደረጉ ከፅንፈኛዉ ሃይልጋር አብረው የሚሰሩ መኖራቸዉ አያጠራጥርም:: እንዲያም ሆኖ እምነቱን የማይወክሉ ተርብ ናቸው::
ኢማማችንን አላህ ይዘንላቸው። ማረፊያቸውንም ጀነት ያድርግልን:: አሚን 🤲
Abiy Ahmed Ali
FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
Ethiopian Federal Police
Prosperity Party - ብልፅግና
Amhara Prosperity Party /APP/ | 3 483 |
| 13 | አፋልጉን
ከታች በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ህጻን ሙሀመድ ሁሴን ይባላል::
ትላንት ሰኔ 20/2018 እለተ ቅዳሜ በግምት ከቀኑ
8:00 ሰዓት አከባቢ ኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከ ወረዳ 10 ልዩ ቦታው መብራት ሀይል ተብሎ በሚጠራዉ በሚኖርበት ስፍራከልጆች ጋር እየተጫወተ እንደነበርና ቤተሰቦቹ ፓሊስ ጣቢያም የሕክምና ተቋማትም ጭምር ሲፈለጉት ማግኘት አልቻሉም::
ህፃን ሙሀመድ ሁሴን ያያችሁ ወይንም ያለበትን የምታዉቁ እባካችሁ ከታች በተቀመጡት ስልክ ቁጥሮች አሳዉቁን ያላሉ ቤተሰቦቹ:-
📲091 310 1614
📲 0911622758 | 3 446 |
| 14 | ይህ የክረምት የዑምራ ፓኬጅ እንዳያልፋችሁ!
በ150ሺ ብር ሙሉ የዑምራ ፓኬጅ
* ቪዛና የደርሶ መልስ ቲኬት
* ለ2ቱም ሀረሞች ቅርብ የሆኑ ጥራታቸውን የጠበቁ ሆቴሎች
* ሙሉ የትራንስፖርት ወጪ
* በመካና በመዲና የታሪካዊ ቦታዎች ጉብኝት
* የዑምራ አደራረግ ቅድመ ስልጠና እና የልምድ ልውውጦች
* ሾፒንግ ያካተተ ፓኬጅ
-------------
0967237373
ይደውሉ | 4 319 |
| 15 | በአገራችን ድምጽ አልባው የትዳር ገዳይ
/ትምህርት ሰጪ በመሆኑ: ይሕን አጭር ፁሁፍ ጋብዣለሁ/
ትዳር በሁለት ሰዎች የሚጀምር ቢሆንም፣ በአገራችን ብዙ ጊዜ በብዙ ሰዎች የሚመራ ሆኗል። ይህም ለብዙ ቤተሰቦች መፍረስ፣ ለልጆች መበተን እና ለማኅበረሰባችን በጣም ከባድ ማኅበራዊ ቁስል ሆኗል። ባልና ሚስት በፍቅር ተዋውቀው፣ በተስፋ ተጋብተው አዲስ ሕይወት ይጀምራሉ። በሠርጋቸው ቀን ስለ ደስታ፣ ስለ ፍቅር፣ ስለ ልጆች እና ስለ ወደፊት ሕይወታቸው ያልማሉ። ነገር ግን ከተጋቡ በኋላ ትዳራቸው በራሳቸው እጅ እንዲመራ ከመተው ይልቅ ቀስ በቀስ ወደ ወላጆች፣ ወደ እህቶች፣ ወደ ወንድሞች እና ወደ ሌሎች ዘመዶች እጅ ይገባል።
መጀመሪያ ምክር በሚመስል ነገር ይጀምራል። "እንዲህ አድርጉ።" "እንዲያ አታድርጉ።" "ልጃችን እንዲህ አይደረግበትም።" "እኛ የምናውቀው ይሻላል።" ከዚያ ግን ምክር ወደ ቁጥጥር ይቀየራል። ቁጥጥሩም ወደ ጣልቃ ገብነት ያድጋል። በመጨረሻም ባልና ሚስት የራሳቸውን ሕይወት ለመወሰን የማይችሉ ሰዎች ይሆናሉ።
በብዙ ቤቶች ውስጥ ችግሩ በባልና ሚስት መካከል አይደለም። ችግሩ የሚፈጠረው ከቤቱ ውጭ ነው። ባል ለሚስቱ የነበረውን ቅሬታ ለእናቱ ይናገራል። ሚስትም ለቤተሰቦቿ ትናገራለች። ከዚያም ሁለቱ ችግሩን ለመፍታት ከመቀመጥ ይልቅ የየራሳቸውን ወገን ማሰባሰብ ይጀምራሉ።
በዚህ ጊዜ ትዳሩ ከፍቅር ወደ ውድድር ይቀየራል። ከመግባባት ወደ ወገንተኝነት ይሄዳል። ከመደማመጥ ወደ መከሳሰስ ይለወጣል።
የሚያሳዝነው ግን በዚህ ግጭት ውስጥ የማይናገሩት ልጆች ናቸው። በየምሽቱ የእናትና የአባት ጭቅጭቅ የሚሰሙ ልጆች፣ አንድ ቀን አባት ከቤት ሲወጣ የሚያዩ ልጆች፣ በፍቺ መካከል የሚጎዱ ልጆች ማንንም አይከሱም፤ ግን ቁስሉን ዕድሜ ልካቸውን ይሸከማሉ። ብዙ ጊዜ ትዳር ሲፈርስ ሰዎች ባልን ወይም ሚስትን ይወቅሳሉ። ነገር ግን እውነቱ አንዳንድ ጊዜ ትዳሩን የገደለው ሰው በውስጡ ሳይሆን በዙሪያው የነበረ ሰው ነው። ወላጆች ልጆቻቸውን መውደድ አለባቸው። ዘመዶች መደገፍ አለባቸው። ጓደኞችም መርዳት አለባቸው። ነገር ግን ትዳርን መምራት ያለባቸው ባልና ሚስት ብቻ ናቸው።
ትዳር የቤተሰብ ፕሮጀክት አይደለም። ትዳር የዘመዶች ኮሚቴ አይደለም። ትዳር የሁለት ሰዎች ቃል ኪዳን ነው። በአገራችን የትዳር መፍረስን ለመቀነስ የመጀመሪያው መፍትሄ ባልና ሚስት ችግራቸውን በራሳቸው መፍታት መማር ነው። ወላጆች መካሪ እንጂ አስተዳዳሪ መሆን የለባቸውም። ዘመዶች ደጋፊ እንጂ ዳኛ መሆን የለባቸውም። ቤት የሚገነባው በፍቅር ነው። የሚፈርሰው ግን ብዙ ጊዜ በከመጠን በላይ በሆነ ጣልቃ ገብነት ነው። ዛሬ የምናድነው አንድ ትዳር ከሆነ፣ ነገ የምናድነው አንድ ትውልድ ይሆናል። | 6 427 |
| 16 | የተዛባዉ ትርክት ሲጋለጥ:-👇
https://youtu.be/_Be1OtgHSGY?si=OyP-6tLTxWjC-WAL | 4 989 |
| 17 | አሜን ከማለት ውጪ ምን ይባላል?
ኢማም አሕመድ ኢብን ኢብራሂም አልጋዚ | 6 500 |
| 18 | ተፈላጊ- አህመድ ሽኩር
እድሜ- 16
ነዋሪነቱ ጉሬጌ ዞን ጌቶ ወረዳ ልዩ ስሙ ቀቡል
በቀን 29/9/18 ጠዋት ከቤት እንደወጣ አልተመለሰም።
ተፈላጊ አህመድ ሽኩርን ያየ ወይንም ያለበትን የሚያዉቅ ከታች በተቀመጡት ስልክ ቁጥሮች እንድታሳውቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፦
📲0923 75 40 04
📲0925 75 61 79 | 6 096 |
| 19 | Matn yo'q... | 6 065 |
| 20 | ለሀሰተኞች ህመም ይሆን ዘንድ ሼር ይደረግ!
እዉነታዉን ሁሉም ይወቅ! ሁሉም ይረዳ!
በአርሲ ዞን 2 የክርስትና እና 1 የእስልምና ተከታይ ናቸው የተገደሉት-ኢሰመኮ
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ በተፈጸመ ጥቃት የሦስት ሲቪል ሰዎች ሕይወት ማለፉን ኢሰመኮ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች መገደል በተጨማሪ ከ2 ሺሕ 650 በላይ የሚገመቱ የአካባቢው ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገልጿል።
ኮሚሽኑ ግንቦት 23 እና 24 ቀን 2018 የተፈጸመውን ይህንን ጥቃት በተመለከተ ባካሄደው ክትትልና ምርመራ፤ ጥቃቱ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ በሚጠራውና “በተለምዶ ኦነግ ሸኔ” በሚባለው ታጣቂ ቡድን መፈጸሙን ጠቁሟል።
በዚህም የሰው ሕይወት መጥፋቱን፣ መፈናቀል፣ የንብረት ውድመት እና ቃጠሎ መድረሱን ከዐይን እማኞች፣ ከተጎጂዎች፣ ከቤተሰቦቻቸውና ከመንግሥት አካላት ባሰባሰበው መረጃ ማረጋገጡን ገልጿል።
ኢሰመኮ ከደቂቃዎች በፊት ባወጣው መግለጫ፣ በአሰኮ ወረዳ ደለተ ጫፋ ቀበሌ አካባቢ ከግንቦት 22 ቀን 2018 . ጀምሮ የታጣቂዎች እንቅስቃሴ በመስተዋሉ የአካባቢው ሚሊሻዎችና የኦሮሚያ ጸረ ሽምቅ ውጊያ ፖሊስ አባላት በስፍራው ተሰማርተው ነበር ብሏል።
በዚህም ሳቢያ በታጣቂ ቡድኑ እና በጸጥታ አካላቱ መካከል ግጭት የተፈጠረ ሲሆን፣ ግጭቱን ተከትሎ ታጣቂ ቡድኑ በሰነዘረው ጥቃት ከአካባቢው መሸሽ ያልቻሉት ኃይሉ ንጉሴ እና ሰሙ አባይነህ የተባሉ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንዲሁም በአካባቢው ከብቶች በመጠበቅ ላይ የነበረ ባቶ ሰፈኖ የተባለ የእስልምና እምነት ተከታይ በድምሩ የሦስት ንጹሐን ዜጎች ሕይወት አልፏል።
ከሰው ሕይወት መጥፋት በተጨማሪ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ የመኖሪያ ቤቶችና የንግድ መደብሮች ላይ በመደዳ ዘረፋና ቃጠሎ መፈጸሙን ኮሚሽኑ በምርመራው አረጋግጧል።
በዚሁ ጥቃት የጠለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን መቃጠሉን፣ የቢዮ ቡጡሌ የሼክ ሙስተፋ መስጅድ አጥር ላይ ጉዳት መድረሱን እና የደለተ ጫፋ ጤና ጣቢያ መዘረፉን የገለጸው ኢሰመኮ፣ በሽርካ፣ በአሰኮ፣ በአንቆሎ ዋቤ፣ ጉና እና መርቲ ወረዳዎች ላይ መሰል ጥቃቶች ዳግም እንዳይከሰቱ በተለያዩ ጊዜያት ማሳሰቡን አስታውሷል።
በአሁኑ ወቅት በጥቃቶቹ ምክንያት ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ነዋሪዎች በመንግሥትና በአጋር አካላት በቂ የአስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ እንዲቀርብና በዘላቂነት የሚቋቋሙበት ሁኔታ እንዲመቻች ኮሚሽኑ አሳስቧል።
ይዘቱ በአግባቡ ሳይረጋገጥ የሚሰነዘሩ ፍረጃዎችና ቅስቀሳዎች ተጨማሪ ግጭት ሊቀሰቅሱ ስለሚችሉ ማናቸውም ተቋማትና ግለሰቦች ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ጥሪ ያቀረበው ኮሚሽኑ፣ ጉዳዩን አስመልክቶ ዝርዝር የምርመራ ሪፖርት በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ በዜጎች ላይ በደረሰው ሞትና ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ኃዘን ገልጸው፣ የተፈጸሙት የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች እጅግ አሳሳቢ መሆናቸውን አስረድተዋል።
ዋና ኮሚሽነሩ መንግሥት ሁኔታውን ለማረጋጋት የጀመራቸውን ጥረቶች በማጠናከር በአስቸኳይ ተጨማሪ የጸጥታ ኃይሎችን እንዲያሰማራ፣ የነዋሪዎችን በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደኅንነትና የንብረት መብቶች እንዲያስጠብቅ ጠይቀዋል። | 4 795 |
