ru
Feedback
የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ

የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ

Открыть в Telegram

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته ውድ የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ይህ ቻናል የተከፈተው በሰመራ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀምዓ የሚሰጡ ትምህርቶች፣መልዕክቶች የሚሰራጭበት ቻናል ነው በዚህ ቻናል ማንኛውንም ሙስሊም ተማሪዎች ወደ ቻናሉ በመጋበዝ ተጠቃሚ ያድርጉ የመጋበዣ ሊንክ 👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/sumuslim_jemaa

Больше
1 212
Подписчики
+124 часа
+47 дней
+2330 дней
Архив постов
📌 የሸሪዓዊ ሂጃብ 3 ዋና ዋና መስፈርቶች 🎥 በዶ/ር ሸይኽ ዐብዱስ-ሰላም አሽ-ሹወይዒር አንዲት ሙስሊም እህት የምትለብሰው ሂጃብ በኢስላም ሸሪዓ ተቀባይነት እንዲኖረው የሚያስፈልጉ 3 መሠረታዊ መስፈርቶች፦ 1️⃣ ዐውራን ሙሉ በሙሉ መሸፈን፦ ልብሱ መሸፈን ያለበትን የሰውነት አካል በሙሉ የሚሸፍን መሆን አለበት። 2️⃣ ሰፊ ሆኖ የሰውነትን ቅርፅ የሚያሳይ (ጠባቅ) አለመሆን፦ • የሰውነትን እያንዳንዱን ቅርፅና አካል ለይቶ የሚያሳይ ጥብቅ ያለ ልብስ (ተፍሲል የሚያደርግ) ለብሶ መውጣት አካልን እንደ መሸፈን አይቆጠርም። • የሰውነትን አጠቃላይ ግዙፍነት ወይም መጠን ብቻ የሚያሳይ (ተጅሲም) ግን የማይቀረውን(አስገዳጅ የሆነውን) ያህል የሚታለፍ/ይቅር የሚባል ነው (ለምሳሌ የራስ ቅርፅ)። 3️⃣ ስስ አለመሆን፦ ልብሱ ከውስጥ ያለውን የሰውነት አካል የሚያሳይ ስስ መሆን የለበትም። 💡 መልእክት፦ የሰውነትን ቅርፅ ለይቶ የሚያሳይ ጥብቅ ልብስ ለብሶ መውጣት በሸሪዓ መሸፈን ተብሎ አይጠራም፤ ይልቁንም ለብሰው እንደተራቆቱ(كاسيات عاريات) ይቆጠራል።

#UPDATE የ2019 የ 12 ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሰኔ28-ሐምሌ 9 እንደሚሰጥ ተገለጸ ከጥር14-24 "exit and ngat exam የትምህርት ሚንስትር አጠቃላይ የአመት ካላንደር ከላይ ተያይዟል @alluexams

ህፃን ራህመትን እንታደጋት ! - ለ DDUMSJ ተማሪዎቻችን የቀረበ የእርዳታ ጥሪ ! . ጀመዓችንን ከ 2013-2015 ለ ሶስት አመታት በአሚርነት ያገለገለች ፤ብሎም በሹራ አባልነት ለብዙ አመታት ያ
+1
ህፃን ራህመትን እንታደጋት ! - ለ DDUMSJ ተማሪዎቻችን የቀረበ የእርዳታ ጥሪ ! . ጀመዓችንን ከ 2013-2015  ለ ሶስት አመታት በአሚርነት ያገለገለች ፤ብሎም በሹራ አባልነት ለብዙ አመታት ያገለገለችው እህታችን አሁን ላይ እገዛችሁን ትሻለች ። . እህታችን በቅርቡ የመጀመሪያ ልጇን አላህ ሰጥቷት የነበረ ቢሆንም ፤  በልብ ህመም የተነሳ ህፃኗ ተገቢውን ህክምና ካላገኘች  ከ 2 ሳምንትታት  ያልዘለለ ጊዜ እንደቀራት የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ገልፆላታል ! . ከሀገር ውጪ ተገቢውን ህክምና ካገኘች መዳን እንደምትችል እና የተሻለ ተስፋ እንዳላት በህክምና ባለሙያዎች ተነግሮናል ። . ለህክምናው ብቻ የሚያስፈልገው ወጪ ከ 3 ሚሊየን ብር በላይ በመሆኑ ቤተሰቦቿ ጭንቀት ውስጥ ገብተዋል ። . ከአላህ በታች እኛም እህታችንን ከጭንቀት ለማውጣት የእኛ አስርም መቶም ብር ወጋ አላትና የአቅማችንን እንረባረብላት ስንል በአላህ ስም እንጠይቃለን። ይህንን አካውንት ተጠቀሙ 1000139136164   hamid mohammed ለበለጠ መረጃ +251924585748 +251994247701

🎤አሰላሙአለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ ውድ የሠመራ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች  ጀመዓ! 👉እንደሚታወቀው ግቢ የመግቢያችን ቀን እየደረሰ ስለሆነ ኩፖን የወሰዳቹህ የጀመዓ ልጆች ኩፖኑን እንድትሸጡ እያልን ለማስታወስ እንወዳለን።                     አላህ ኸይር ጀዛዐችሁን ይክፈላቹህ!🤲🤲 💵በአካውንት ለሚያስገቡ ... . 1000 724 605 797     CBE 240 374 706               Abyssinia 10000 5203 0001       Hijra 006758 6120 101      zam zam screen sheet እዳይረሳ እሺ።        የሠመራ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች  ጀመዓ!🕌🕌🕌

السلام عليكم ورحمة وبركاته አስደሳች ዜና ለዕውቀት ፈላጊዎች በሙሉ እነሆ ከዛሬ ማለትም 04/13/2018 ዓ,ል  ጀምሮ በአፋር ክልል በሎግያ ከተማ በአንሷር መስጂድ ለተከታታይ ቀናት የሚቆይ  የደውራ ፕሮግራም መኖሩን ስናበስራችሁ በታላቅ ደስታ ነው። በደውራው ላይ የምትቀራዋ ሪሳላ: 📚  منكرات شائعة في المجتمعات يجب الحذر منها للشيخ ابي عبد الله محمد بن حزام الفضلي  البعداني የደረሱ አቅራቢ: أستاذ دكتور حسين علي ድርሱ የሚሰጥበት ቦታ: ሎግያ አንሷር መስጂድ ሰዓት: ከመጝሪብ በኃላ መልእክቱን ሸር በማድረግ ተደራሽ እናድርገው። ማስታወሻ: ኪታብ የሌላችሁ ወንድሞች ኪታብ ኡስታዝ ሙሀመድ ሰዒድ ጋር አለ።

የ “ዘመን መለወጫ” ኮተቶች ~ ኢትዮጵያ በምትከተለው ክርስቲያናዊው የዘመን አቆጣጠር መሰረት አዲስ አመት ሊገባ የያዝነው አመት እየተጠናቀቀ ነው። በያመቱ በዚህ ሰሞን የሚፈፀሙ ከሃይማኖታችን ጋር የማይሄዱ በርካታ ነገሮ አሉ። ከነዚህም ውስጥ:- 1. ድግምትና ጥንቆላ፦ በሃገራችን የተለያዩ አካባቢዎች ነሐሴ ሊጠናቀቅ ሲል በየጠንቋዩ ቤት የሚልከሰከሱት ብዙ ናቸው። ከዚያም አምስቱ ወይም ስድስቱ የጳጉሜ ቀናት መንገዶች በድግምት ስራዎች ይሞላሉ። በነዚህ ቀናት ማልዶ የወጣ ሰው እንዲረግጣቸው/ እንዲራመዳቸው ታስቦ በጎረቤት መተላለፊያ እና ህዝብ በሚያዘወትራቸው መንገዶች ላይ የሞቱ ፍየሎች፣ ዶሮዎች፣ ድመቶች፣ ጥንቸሎች ወዘተ ታርደው ይጣላሉ። በደም የተነከሩ ሳንቲሞች፣ ብሮች፣ ጌጣ ጌጦች፣ የተለያዩ ቁሳቁሶች እዚህም እዚያም ወድቀው ይታያሉ። * ጥንቆላና ድግምት ከኢስላም የሚያስወጡ ከባባድ ወንጀሎች ናቸው፡፡ وَاتَّبَعُوا مَا تَتْلُو الشَّيَاطِينُ عَلَى مُلْكِ سُلَيْمَانَ وَمَا كَفَرَ سُلَيْمَانُ وَلَكِنَّ الشَّيَاطِينَ كَفَرُوا يُعَلِّمُونَ النَّاسَ السِّحْرَ “በሱለይማን ዘመነ-መንግስት ሸይ ^ጧኖች የሚያነቡትንም (ድግምት) ተከተሉ። ሱለይማን ግን አልካደም (ድግምተኛ አልነበረምና።) ግና ሸይ^ጧኖች ሰዎችን ድግምት የሚያስተምሩ ሲሆኑ ካዱ።” [አል-በቀራህ፡ 102] ነብዩም ﷺ {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ በሚናገረው ያመነ፣ በሙሐመድ ላይ በወረደው ክዷል} ብለዋል። [አስ-ሶሒሐህ፡ 3387] * ደጋሚዎችና ከነሱ ዘንድ የሚመላለሱ ሰዎች መቼም ቢሆን ስኬት የላቸውም። ጌታችን “ድግምተኛም በመጣበት ስፍራ ሁሉ አይቀናውም” ብሏል። [ጦሃ፡ 69] * ጠንቋይና ደጋሚ ዘንድ የሚሄድ ሰው የተነገረውን ባያምን እንኳን ከባድ ቅጣት ይከተለዋል። ነብዩ ﷺ {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ ስለሆነ ነገር የጠየቀው የአርባ ቀን ሶላቱ ተቀባይነት የለውም} ብለዋል። [ሙስሊም፡ 5957] 2. ሎሚ መምጠጥ እና ፌጦ መብላት:- በአንዳንድ አካባቢዎች ከድግምትና ጥንቆላ ለመጠበቅ በማሰብ ወላጆች ልጆቻቸውን ጳጉሜ ላይ ሎሚና ፌጦ ይመግባሉ። ድግምትና ጥንቆላ ሸይ^ ጧናዊ ተግባራት ናቸው። መጥጠበቂያ መንገዶቹ አዝካር፣ አየቱል ኩርሲይ፣ ሱረቱል ኢኽላስን (ቁል ሁወላሁ አሐድ)፣ ሙዐዊዘተይን (ቁል አዑዙ ቢረቢል ፈለቅ፣ ቁል አዑዙ ቢረቢናስ) ከሶላት በኋላ እና ጧትና ማታ መቅራት፣ እንዲሁም ከሱረቱል በቀራ የመጨረሻዎቹን ሁለት አንቀፆች መቅራት፣ ሩቅያ ማድረግ ናቸው። አጉል እምነት ላይ የተመሰረቱ ሰበቦችን መጠቀም ከሺርክ ነው። በተረፈ የተጣለ የድግምት ስራ ቢያጋጥመን ምንም መደናገጥ አያስፈልግም። በአላህ ላይ ጠንካራ እምነት ማሳደር (ተወኩል) ቀዳሚው መከላከያ መንገድ ነው። አጉል መጨናነቅ ለችግር ይዳርጋል። ከዚያም የድግምት ስራውን ሙዐዊዘተይን በመቅራት ማስወገድ ነው (ማቃጠል፣ መቆራረጥ ወይም ቆፍሮ መቅበር)። 3. የጳጉሜ ዱዓእ የሚል ቢድዐ:- በአንዳንድ አካባቢዎች የጳጉሜ ዱዓእ “መቅቡል ነው” (ተቀባይነት ያለው ነው) የሚል እምነት አለ። ይሄ አጉል እምነት ነው። በጣም የሚገርመው ለዱዓእ የሚጣዱት እስልምናን ያውቃሉ ሰዎችን ያስተምራሉ የሚባሉት ሰዎች መሆናቸው ነው። ነብዩ ﷺ “አላህ እውቀትን ከባሪያዎቹ መንጠቅን አይነጥቅም። ይልቁንም ዑለማዎችን በመውሰድ (በመግደል) እውቀትን ይወስዳል። ከዚያም ዓሊም እስከማይቀር ድረስ። በዚያኔ ሰዎች መሀይማንን መሪዎች አድርገው ይይዛሉ። ሲጠየቁም ያለ እውቀት ፈትዋ ይሰጣሉ። በዚህም ይጠማሉ፣ ያጠማሉም” ብለዋል። [ሶሒሕ አልቡኻሪይ፡ 100] [ሶሒሕ ሙስሊም፡ 2673] 4. የጳጉሜ ጸበል (ጥምቀት)፦ ጳጉሜ 3 ቀን በኦርቶዶክስ ክርስትና የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ በዓል ነው ይላሉ። በዚህ ዕለት "የሰማይ ደጆች ይከፈታሉ፣ ዝናቡም የበረከትና የፈውስ ውሃ ሆኖ ይወርዳል" ተብሎ ይታመናል። በዚህም የተነሳ ሕዝቡ ሕፃናትን ጨምሮ ከሰማይ የሚወርደውን ዝናብ (የጳጉሜን ዝናብ) እንደ ጸበል በመቁጠር ሰውነታቸውን ይጠመቁበታል። ሙስሊሞች ከንደዚህ ዓይነት እምነቶችና ተግባራት ሊርቁ ይገባል። 5. እንቁጣጣሽ ማክበር:- ሌላኛው የ “ዘመን መለወጫን” ተከትሎ የሚፈፀመው ጥፋት መስከረም አንድን ወይም እንቁጣጣሽን ማክበር ነው። ዕለቱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት መሠረት "ቅዱስ ዮሐንስ" በመባል የሚጠራ ሲሆን፣ የመጥምቁ ዮሐንስ መታሰቢያ እና የቅዱሳን አበው መታሰቢያ ይደረግበታል። በቤተክርስቲያን ደረጃ የማህሌት፣ የቅዳሴ እና የምስጋና ሥርዓት ይፈጸምበታል። ​በተጨማሪም የበዓሉ ስም (እንቁጣጣሽ የሚለው) ከንግሥተ ሳባ እና ከንጉሥ ሰሎሞን አፈ ታሪክ ጋር ይያያዛል። ንግሥተ ሳባ ከኢየሩሳሌም ስትመለስ መኳንንቶቿ "እንቁ ለጣጣሽ" (ለጌጥሽ ይሁን) በማለት በዕንቁ ስለተቀበሏት ይህ ስም እንደወጣ ይነገራል። አቆጣጠሩ ሀገራዊ እንጂ እምነታዊ መሰረት እንደሌለው ሊያሳምኑ የሚሞክሩ ሰዎች አሉ። ነገሩ ግልፅ ቢሆንም ድንገት የሚሰወራቸው ካሉ ለማስታወስ ያህል:- * አቆጣጠሩ ከግብፅ ኮፕቲክ ቤተክርስቲያን የተቀዳ ነው። * አመቱ ሲፃፍ መጨረሻ ላይ “ዓመተ ምህረት” የሚባለውም ክርስቲያናዊ ስለሆነ ነው። * የነብዩ ዒሳን (ሰላም በሳቸው ላይ ይስፈንና) መወለድ መሰረት ያደረገ እንደሆነ የሚታመን ነው። * በእለቱም የሚፈፀሙት የተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶችም በዓሉ ክርስቲያናዊ እንደሆነ በሚገባ አጉልተው ያሳያሉ፦ - የዋዜማ ጸሎትና ማኅሌት፦ በበዓሉ ዋዜማ (ጳጉሜን 5 ወይም 6) ሌሊቱን ሙሉ በቤተክርስቲያን ልዩ የቅዱስ ዮሐንስ ማኅሌትና ጸሎት ይቆማል። - የቅዳሴ ሥነ-ሥርዓት፦ በዕለቱ ጠዋት ምዕመናን አዲስ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተክርስቲያን በመሄድ በቅዳሴና በዕለቱ ትምህርተ ወንጌል ላይ ይሳተፋሉ። - ዘመነ ዮሐንስን መቀበል፦ በቤተክርስቲያን ዘመን መለወጫን አስመልክቶ ልዩ ጸሎት ይደረጋል፤ የወንጌላዊው ዘመንም (ዘመነ ማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስ ወይም ዮሐንስ) ይታወጃል። “እንኳን ከዘመነ ማቲዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ፣ ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ፣ ... አደረሳችሁ” ማለታቸው አቆጣጠሩና በዓሉ ሃይማኖታዊ መሆናቸውን አጉልተው የሚያሳዩ ነጥቦች ናቸው፡፡ ይህንን ስንል የሚጎረብጣቸው አሉ። እኛ'ኮ የኛን ዒድ አብራችሁን ካላከበራችሁ አላልንም። ይልቁንም የኛን እምነታዊ መገለጫ ካላንፀባረቃችሁ ብሎ ሌሎችን መወረፍ አክራሪነት ነው። እምነታችን የሌሎች ህዝቦች #መለያ በሆኑ እምነቶችና ልማዶች መመሳሰልን አይፈቅድም። ነብያችን ﷺ “በሰዎች የተመሳሰለ ከነሱው ነው” ብለዋል። (ኢብኑ ሙነወር፣ 18/11/1436) = የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

Repost from Tikvah-University
#RemedialResult በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ተለቋል። https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Remedial Ex
#RemedialResult በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ተለቋል። https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Remedial Examination ከሚለው ስር View Results የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ። ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና 53,620 ተፈታኞች መውሰዳቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወሳል። @tikvahuniversity

እኔ የአላህን መልዕክተኛ ﷺ ከራሴ በላይ እወዳቸዋለሁ፤ ነገር ግን የመውሊድን በዓል አላከብርም። በዚህም አቋሜ እኔ በሁሉም የመልእክተኛው ባልደረቦች (ሶሐቦች)፣ በታቢዒዮቹ የዲን መሪዎች፣ እና በአራቱ አኢማዎችና የእስልምና ታላላቅ መሪዎች ጎን ነኝ። ​አንተ በዓሉን የምታከብረው ሰው ሆይ! ​እስኪ በጌታህ ይሁንብህ! ከምርጥ ትውልዶች (ከሰለፎች) መካከል ከየትኛው ኢማም ሰልፍ ነህ? በፍጹም ልታገኝ አትችልም! ​ከምርጥ ትውልዶች በኋላ የመጣን አንድ ሰው እንኳን ብትጠቅስልኝና እኔም በእሱ ጎን መሆንህን ብቀበልህ፤ እስኪ በጌታህ ይሁንብህ ንገረኝ፦ እሱ እኔ ባለሁበት ጎን ካሉት (ከምርጡ ትውልድ) ሰዎች ከአንዱ ጋር ይስተካከላልን? ​ይልቁንም ንገረኝ፤ ከኋለኞቹ ትውልድ የብዙዎቹ ስብስብ ከአንዱ ሶሐቢይ ጋር ይስተካከላልን? ​እናንተ ሰዎች ሆይ! አስተውሉ፤ አስተንትኑ። ዋጋ በሌለው የቃላት ጌጣጌጥ አትሸወዱ፤ ያልተገራ ስሜትም ዓይናችሁን አይጋርዳችሁ፤ ከእውነት በኩል ምንም የማይጠቅምን ከማህበረሰቡ የወረሳችሁት ልማድ እስረኛ አትሁኑ! ሸይኽ ሱለይማን አር- ሩሐይሊ (حفظه الله) https://t.me/durusuabihizam https://t.me/durusuabihizam

ሸውካኒይ እና መውሊድ (ወሳኝ ነጥቦች የተዳሰሱበት) ~ ሙሐመድ ብኑ ዐሊ አሽ-ሸውካኒይ በ1250 ሂ. የሞቱ ታላቅ የመናዊ ዓሊም ናቸው፡፡ በሰፊው የሚታወቁ ስለሆኑ እሳቸውን በማስተዋወቅ ረጅሙን ፅሑፌን ይበልጥ ማስረዘም አልሻም፡፡ ሸውካኒይ መውሊድ ላይ እጅግ የሰላ ትችት ሰንዝረዋል፡፡ ዛሬ በተደጋጋሚ ከምንሰማቸው መውሊድ ተኮር ጥያቄዎች ውስጥ የተወሰኑትን በመምዘዝ በሸውካኒይ ንግግር ምላሽ እሰጣለሁ፡፡ ሙሉ ንግግራቸውን መመልከት የፈለገ ሰው “አልፈትሑ ረባኒይ ሚን ፈታዋ አልኢማሚ ሸውካኒይ” በተሰኘው የፈትዋ መድብላቸው ውስጥ ሁለተኛውን ጥራዝ ከገፅ 1087 - 1101 ድረስ መመልከት ይችላል፡፡ (ፅሑፉ ስለ ረዘመ ዐረብኛውን ማካተት አልቻልኩም፡፡) 1. መውሊድ የሸሪዐ መነሻ አለውን? ሸውካኒይ፡- “እስካሁን ድረስ ከቁርኣንም፣ ከሱናም፣ ከኢጅማዕም፣ ከቂያስም (ንፅፅራዊ ምልከታም) መሰረት እንዳለው የሚያመላክት መረጃ አላገኘሁለትም፡፡” [ገፅ፡ 2/1087] 2. መውሊድን ሰለፎች ያውቁታል? ሸውካኒይ፡- “እንዲያውም ከዘመናት ሁሉ ምርጡ በሆነው (የሶሐቦች) ዘመንም፣ ከነሱ ቀጥሎ በነበሩትም፣ ቀጥሎ በነበሩትም (ዘመን) እንዳልነበር ሙስሊሞች ወጥ አቋም ይዘዋል (ኢጅማዕ አድርገዋል፡፡)” [ገፅ፡ 2/1087] 3. ቢድዐ በመሆኑ ላይ ልዩነት አለ? ሸውካኒይ፡- “ቢድዐ በመሆኑ ላይ ከሙስሊሞች አንድ እንኳን የተቃወመ የለም፡፡” [ገፅ፡ 2/1088] “ይሄ ነገር ቢድዐ በመሆኑ ላይ ከሁሉም ሙስሊሞች ኢጅማዕ እንዳለበት አረጋግጠንልሃል፡፡” [ገፅ፡ 2/1091] 4. መውሊድን በሚደግፉ መሻይኾች ማስፈራራት ያዋጣል? ሸውካኒይ፡- “በምርጡ ነብይ ﷺ የማያሻማ ምስክርነት ቢድዐ ሁሉ ጥመት እንደሆነ ተነግሮ ሳለ የመውሊድን ቢድዐ መሆን ካመነ በኋላ ይፈቀዳል የሚል ሰው የተናገረው ከንፁሁ ሸሪዐ ጋር የሚፃረር ንግግር ነው፡፡ ያለ አንድ ተጨባጭ እውቀታዊ መነሻ ቢድዐን ወደተለያዩ ክፍሎች ለከፈለ ሰው በጭፍን ከመከተል ያለፈ ነገርም የለውም፡፡ የትኛውንም አቋም ይቻላል የሚልን ሰው ይህንን ቢድዐ በተለየ የሚመለከት ማስረጃ ካቀረበ በኋላ እንጂ አንቀበለውም፡፡ … እንጂ ‘እከሌ እንዲህ አለ’፣ ‘እከሌ እንዲህ አይነት ኪታብ አዘጋጅቷል’ የሚል ባዶ ንግግር ፋይዳ የለውም፡፡ ሐቅ ከየትኛውም አካል ይበልጣልና፡፡” [ገፅ፡ 2/1088 - 1089] “ከነሱ (ከፈቃጆቹ) ውስጥ ቢድዐነቱን አምኖ መጥፎ ነገር ካልተቆራኘው በሚል መስፈርት የፈቀደው አለ፡፡ ምንም ማስረጃ ግን አላመጣም፡፡” [ገፅ፡ 2/1094] ኢብኑ ሐጀር እንዳደረገው የዓሹራን ፆም ማስረጃ ማድረግ፣ ወይም ሲዩጢ እንዳደረገው ከነብይነት በኋላ ለራሳቸው ዐቂቃ ማውጣታቸውን መመርኮዝ ቢድዐን የማፅናት ፍቅር እንዲህ አይነት ነገር ላይ እንደሚጥል ከሚያሳዩ አስገራሚ ነገሮች ውስጥ ነው፡፡ [ገፅ፡ 1095] 5. መውሊድ የብዙሃን ሙስሊሞች ድጋፍ ነበረውን? ሸውካኒይ፡- “በሰዎች ንግግሮች ላይ የምንመረኮዝ ከሆንና የእንቶ ፈንቶ ጅራቶችን የምንጨብጥ ከሆንን መታወቅ ያለበት ነገር ቢኖር ‘ይፈቀዳል’ ባዮቹ ከሙስሊሞች በአቋም ያፈነገጡ ናቸው፡፡ …” [ገፅ፡ 2/1087-1089] “ሲጨመቅ የመውሊድ ፈቃጆች ከከልካዮቹ አንፃር ሲታዩ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ለዚያውም እነሱም ቢሆኑ ምግብ ለማብላትና ለዚክር ካልሆነ በስተቀር እንደማይቻል ተስማምተዋል፡፡” [ገፅ፡ 1095 – 1099] (አስተውሉ! ይህ እንግዲህ በሸውካኒ ዘመን ነው፡፡ የሞቱት በ1250 ሂ. ሲሆን ሁለት መቶ አመት ሊሞላቸው ጥቂት ነው የቀራቸው፡፡ ሱፊያ ደፋር ነውና የዛሬን የመውሊድ ጨፋሪዎች በመመልከት ሸውካኒን “ውሸታም ነው” እንዳይሉ እሰጋለሁ፡፡) 6. መውሊድ እንዴት ተስፋፋ? ሸውካኒይ፡- “ግና ቢድዐን በማፅናትም ሆነ በማጥፋት ላይ ንጉሳን ተፅእኖ አላቸው፡፡ ይህንን ቢድዐ (በሱኒው ዓለም ውስጥ) የፈጠረው ያ ንጉስ (ሙዞፈር) ሲሆን ኢብኑ ዲሕያ ደግሞ ‘አተንዊር ፊ መውሊዲል በሺር ነዚር’ የተሰኘ ኪታብ በማዘጋጀት አግዞታል፡፡ ሰውየው በዘገባ እውቀት ላይ የጠለቀ ከመሆኑም ጋር በዚህ ኪታቡ ግን ግልፅ ማስረጃ አላቀረበም፡፡ ለዚህ ስራው - ኢብኑ ኸሊካን እንደጠቀሱት - አንድ ሺህ ዲናር በንጉሱ መሸለሙ ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ የዱንያ ፍቅር ከዚህም በላይ ያደርሳል፡፡” [ገፅ፡ 2/1091] “የቢድዐ ስርጭት ከእሳት ስርጭት የፈጠነ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ መውሊድ፡፡ ምክንያቱም የመሃይማን ነፍሶች ጥግ የደረሰ መናፈቅን ይናፍቁታልና፡፡ በተለይ ደግሞ ከምሁራን፣ ከክቡራንና መሪዎች በርከት ያለ ሰው ከተካፈለበት በኋላ ይሄ ቢድዐ ወሳኝ ከሆኑ ሱናዎች ይመስላቸዋል፡፡ … እንደ መውሊድና አምሳያዎቹ ያሉ ለሐራም ነገሮች የሚያመቻቹ የጥፋት መዳረሻዎች መሃይሞች ፈጥነው እንደሚገቡባቸው አያጠራጥርም፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ በዒልም፣ በክብርና በስልጣን ዝና ያለው ሰው መካፈል ሲታከልበት ሐራም ነገሮችን እንደ ፈጣሪ ትእዛዛት ሲፈፅሙ፣ በድንቁርናና በጥመት ሸለቆች ውስጥ ገብተው ሲዘባርቁ፣ “የተከበሩ እከሌ፣ እከሌ፣ እከሌ፣… ተገኝተዋል” እያሉ ከተቃውሞ ሲያመልጡ የባሰ ይሆናል፡፡ መሃይሙ ህዝብ ይቅርና አንዱ በዒልም ፍለጋ ላይ ገኖ የወጣ ሰው አንዳንድ የኢጅቲሃድ እውቀቶችን ለመማር ከፊቴ ተቀምጦ ነበር፡፡ በዚህ ወር ከተከናወኑ መውሊዶች ውስጥ በአንዱ አዳር ላይ እንደተካፈለ ሲነግረኝ ተቃወምኩት፡፡ አንገሸገሸኝ፡፡ በዚህን ጊዜ ‘ሰዪዲ እከሌ፣ እከሌ፣ እከሌ፣… ተካፍለዋልኮ’ አለኝ፡፡ በነዚህ ታዋቂ ሰዎች ፊት የነበረውን አፈፃፀም ስጠይቀው እንዲህ አለኝ፡- ‘እነዚያ ታዋቂ ሰዎች እየዘፈኑና እያዳመጡ መንዙማውን አንድ ዱርየ አነበበ፡፡ ከዚያም አንዱ ልክ ከእስር የተነሳ ይመስል አፈፍ ብሎ ተነስቶ “መርሐባ ያ ኑረ ዐይኒ፣ መርሐባ” (እንኳን መጣህ ያይኔ ብርሃን እንኳን መጣህ!) ሲል ታዳሚው በመላ ታዋቂዎቹን ጨምሮ ተከትለውት ቆሙ፡፡ እነሱ በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉ ቆሞ ማጓራት ያዘ፡፡ አንዱ ታዳሚ ደክሞት ቢቀመጥ ከታዋቂዎቹ ውስጥ አንዱ ንዴቱ ከፊቱ ላይ እየታየ ‘ተነስ! ጨዋታኮ አይደለም!’ ብሎ ጮኸበት፡፡ ቃል በቃል! የአላህ መልእክተኛ ﷺ በዚያች ሰዓት ከነሱ ዘንድ እንደደረሱ ጭራሽ አይጠራጠሩም፡፡ ከዚያም ተጨባበጡ፡፡ ከመሀይማን ከፊሎቹ በእጆቻቸው ሽቶ በመያዝ በፍጥነት ቀቡ፣ ተቀቡ፡፡ ልክ የሳቸውን ﷺ መገኘት ለመጠቀም፡፡’ ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን! የዲን ክብር የት ገባ?! ይህም ከጠፋ አይናፋርነት፣ ግብረ ገብነት፣ ህሊና የት ገባ?” [ገፅ፡ 2/1089 - 91] 7. መውሊድን የነብዩ ﷺ ቤተሰቦች ይደግፉታል? መውሊድን የሚያከብሩ ሰዎች “ከኛ በላይ ነብዩን ﷺ የሚወድ ላሳር!” የሚሉ ናቸው፡፡ እውነት ለመናገር የነብዩ ﷺ ዘሮች ሙእሚኖች ከሆኑ ለነብዩ ﷺ ያላቸው ፍቅር ልዩ ነው፡፡ መውሊዱ የፍቅር መገለጫ ቢሆን ኖሮ ከማንም ቀድመው ባከበሩት ነበር፡፡ ግን ከነሱ የተገኘው መውሊድን ማክበር፣ ማስከበር፣ ለሱ ሽንጥን ገትሮ መሟገት ነውን? ሸውካኒይ፡- “ከነብዩ ﷺ ንፁሕ ቤተሰብም ይሁን ከተከታዮቻቸው ይህ ነገር እንደሚፈቀድ የተናገረ አንድም ፊደል አላገኘንም፡፡ እንዲያውም ይህቺ ቢድዐ ከተከሰተች ጀምሮ ወደ ጥፋቶች ከሚያሻግሩ አስቀያሚ መዳረሻዎች አንዷ እንደሆነች ንግግሮቻቸው ከሞላ ጎደል ተስማምተዋል፡፡” [ገፅ፡ 1089]