es
Feedback
የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ

የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ

Ir al canal en Telegram

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته ውድ የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ይህ ቻናል የተከፈተው በሰመራ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀምዓ የሚሰጡ ትምህርቶች፣መልዕክቶች የሚሰራጭበት ቻናል ነው በዚህ ቻናል ማንኛውንም ሙስሊም ተማሪዎች ወደ ቻናሉ በመጋበዝ ተጠቃሚ ያድርጉ የመጋበዣ ሊንክ 👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/sumuslim_jemaa

Mostrar más
1 196
Suscriptores
-224 horas
+67 días
+1730 días
Archivo de publicaciones
እኔ የአላህን መልዕክተኛ ﷺ ከራሴ በላይ እወዳቸዋለሁ፤ ነገር ግን የመውሊድን በዓል አላከብርም። በዚህም አቋሜ እኔ በሁሉም የመልእክተኛው ባልደረቦች (ሶሐቦች)፣ በታቢዒዮቹ የዲን መሪዎች፣ እና በአራቱ አኢማዎችና የእስልምና ታላላቅ መሪዎች ጎን ነኝ። ​አንተ በዓሉን የምታከብረው ሰው ሆይ! ​እስኪ በጌታህ ይሁንብህ! ከምርጥ ትውልዶች (ከሰለፎች) መካከል ከየትኛው ኢማም ሰልፍ ነህ? በፍጹም ልታገኝ አትችልም! ​ከምርጥ ትውልዶች በኋላ የመጣን አንድ ሰው እንኳን ብትጠቅስልኝና እኔም በእሱ ጎን መሆንህን ብቀበልህ፤ እስኪ በጌታህ ይሁንብህ ንገረኝ፦ እሱ እኔ ባለሁበት ጎን ካሉት (ከምርጡ ትውልድ) ሰዎች ከአንዱ ጋር ይስተካከላልን? ​ይልቁንም ንገረኝ፤ ከኋለኞቹ ትውልድ የብዙዎቹ ስብስብ ከአንዱ ሶሐቢይ ጋር ይስተካከላልን? ​እናንተ ሰዎች ሆይ! አስተውሉ፤ አስተንትኑ። ዋጋ በሌለው የቃላት ጌጣጌጥ አትሸወዱ፤ ያልተገራ ስሜትም ዓይናችሁን አይጋርዳችሁ፤ ከእውነት በኩል ምንም የማይጠቅምን ከማህበረሰቡ የወረሳችሁት ልማድ እስረኛ አትሁኑ! ሸይኽ ሱለይማን አር- ሩሐይሊ (حفظه الله) https://t.me/durusuabihizam https://t.me/durusuabihizam

ሸውካኒይ እና መውሊድ (ወሳኝ ነጥቦች የተዳሰሱበት) ~ ሙሐመድ ብኑ ዐሊ አሽ-ሸውካኒይ በ1250 ሂ. የሞቱ ታላቅ የመናዊ ዓሊም ናቸው፡፡ በሰፊው የሚታወቁ ስለሆኑ እሳቸውን በማስተዋወቅ ረጅሙን ፅሑፌን ይበልጥ ማስረዘም አልሻም፡፡ ሸውካኒይ መውሊድ ላይ እጅግ የሰላ ትችት ሰንዝረዋል፡፡ ዛሬ በተደጋጋሚ ከምንሰማቸው መውሊድ ተኮር ጥያቄዎች ውስጥ የተወሰኑትን በመምዘዝ በሸውካኒይ ንግግር ምላሽ እሰጣለሁ፡፡ ሙሉ ንግግራቸውን መመልከት የፈለገ ሰው “አልፈትሑ ረባኒይ ሚን ፈታዋ አልኢማሚ ሸውካኒይ” በተሰኘው የፈትዋ መድብላቸው ውስጥ ሁለተኛውን ጥራዝ ከገፅ 1087 - 1101 ድረስ መመልከት ይችላል፡፡ (ፅሑፉ ስለ ረዘመ ዐረብኛውን ማካተት አልቻልኩም፡፡) 1. መውሊድ የሸሪዐ መነሻ አለውን? ሸውካኒይ፡- “እስካሁን ድረስ ከቁርኣንም፣ ከሱናም፣ ከኢጅማዕም፣ ከቂያስም (ንፅፅራዊ ምልከታም) መሰረት እንዳለው የሚያመላክት መረጃ አላገኘሁለትም፡፡” [ገፅ፡ 2/1087] 2. መውሊድን ሰለፎች ያውቁታል? ሸውካኒይ፡- “እንዲያውም ከዘመናት ሁሉ ምርጡ በሆነው (የሶሐቦች) ዘመንም፣ ከነሱ ቀጥሎ በነበሩትም፣ ቀጥሎ በነበሩትም (ዘመን) እንዳልነበር ሙስሊሞች ወጥ አቋም ይዘዋል (ኢጅማዕ አድርገዋል፡፡)” [ገፅ፡ 2/1087] 3. ቢድዐ በመሆኑ ላይ ልዩነት አለ? ሸውካኒይ፡- “ቢድዐ በመሆኑ ላይ ከሙስሊሞች አንድ እንኳን የተቃወመ የለም፡፡” [ገፅ፡ 2/1088] “ይሄ ነገር ቢድዐ በመሆኑ ላይ ከሁሉም ሙስሊሞች ኢጅማዕ እንዳለበት አረጋግጠንልሃል፡፡” [ገፅ፡ 2/1091] 4. መውሊድን በሚደግፉ መሻይኾች ማስፈራራት ያዋጣል? ሸውካኒይ፡- “በምርጡ ነብይ ﷺ የማያሻማ ምስክርነት ቢድዐ ሁሉ ጥመት እንደሆነ ተነግሮ ሳለ የመውሊድን ቢድዐ መሆን ካመነ በኋላ ይፈቀዳል የሚል ሰው የተናገረው ከንፁሁ ሸሪዐ ጋር የሚፃረር ንግግር ነው፡፡ ያለ አንድ ተጨባጭ እውቀታዊ መነሻ ቢድዐን ወደተለያዩ ክፍሎች ለከፈለ ሰው በጭፍን ከመከተል ያለፈ ነገርም የለውም፡፡ የትኛውንም አቋም ይቻላል የሚልን ሰው ይህንን ቢድዐ በተለየ የሚመለከት ማስረጃ ካቀረበ በኋላ እንጂ አንቀበለውም፡፡ … እንጂ ‘እከሌ እንዲህ አለ’፣ ‘እከሌ እንዲህ አይነት ኪታብ አዘጋጅቷል’ የሚል ባዶ ንግግር ፋይዳ የለውም፡፡ ሐቅ ከየትኛውም አካል ይበልጣልና፡፡” [ገፅ፡ 2/1088 - 1089] “ከነሱ (ከፈቃጆቹ) ውስጥ ቢድዐነቱን አምኖ መጥፎ ነገር ካልተቆራኘው በሚል መስፈርት የፈቀደው አለ፡፡ ምንም ማስረጃ ግን አላመጣም፡፡” [ገፅ፡ 2/1094] ኢብኑ ሐጀር እንዳደረገው የዓሹራን ፆም ማስረጃ ማድረግ፣ ወይም ሲዩጢ እንዳደረገው ከነብይነት በኋላ ለራሳቸው ዐቂቃ ማውጣታቸውን መመርኮዝ ቢድዐን የማፅናት ፍቅር እንዲህ አይነት ነገር ላይ እንደሚጥል ከሚያሳዩ አስገራሚ ነገሮች ውስጥ ነው፡፡ [ገፅ፡ 1095] 5. መውሊድ የብዙሃን ሙስሊሞች ድጋፍ ነበረውን? ሸውካኒይ፡- “በሰዎች ንግግሮች ላይ የምንመረኮዝ ከሆንና የእንቶ ፈንቶ ጅራቶችን የምንጨብጥ ከሆንን መታወቅ ያለበት ነገር ቢኖር ‘ይፈቀዳል’ ባዮቹ ከሙስሊሞች በአቋም ያፈነገጡ ናቸው፡፡ …” [ገፅ፡ 2/1087-1089] “ሲጨመቅ የመውሊድ ፈቃጆች ከከልካዮቹ አንፃር ሲታዩ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ለዚያውም እነሱም ቢሆኑ ምግብ ለማብላትና ለዚክር ካልሆነ በስተቀር እንደማይቻል ተስማምተዋል፡፡” [ገፅ፡ 1095 – 1099] (አስተውሉ! ይህ እንግዲህ በሸውካኒ ዘመን ነው፡፡ የሞቱት በ1250 ሂ. ሲሆን ሁለት መቶ አመት ሊሞላቸው ጥቂት ነው የቀራቸው፡፡ ሱፊያ ደፋር ነውና የዛሬን የመውሊድ ጨፋሪዎች በመመልከት ሸውካኒን “ውሸታም ነው” እንዳይሉ እሰጋለሁ፡፡) 6. መውሊድ እንዴት ተስፋፋ? ሸውካኒይ፡- “ግና ቢድዐን በማፅናትም ሆነ በማጥፋት ላይ ንጉሳን ተፅእኖ አላቸው፡፡ ይህንን ቢድዐ (በሱኒው ዓለም ውስጥ) የፈጠረው ያ ንጉስ (ሙዞፈር) ሲሆን ኢብኑ ዲሕያ ደግሞ ‘አተንዊር ፊ መውሊዲል በሺር ነዚር’ የተሰኘ ኪታብ በማዘጋጀት አግዞታል፡፡ ሰውየው በዘገባ እውቀት ላይ የጠለቀ ከመሆኑም ጋር በዚህ ኪታቡ ግን ግልፅ ማስረጃ አላቀረበም፡፡ ለዚህ ስራው - ኢብኑ ኸሊካን እንደጠቀሱት - አንድ ሺህ ዲናር በንጉሱ መሸለሙ ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ የዱንያ ፍቅር ከዚህም በላይ ያደርሳል፡፡” [ገፅ፡ 2/1091] “የቢድዐ ስርጭት ከእሳት ስርጭት የፈጠነ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ መውሊድ፡፡ ምክንያቱም የመሃይማን ነፍሶች ጥግ የደረሰ መናፈቅን ይናፍቁታልና፡፡ በተለይ ደግሞ ከምሁራን፣ ከክቡራንና መሪዎች በርከት ያለ ሰው ከተካፈለበት በኋላ ይሄ ቢድዐ ወሳኝ ከሆኑ ሱናዎች ይመስላቸዋል፡፡ … እንደ መውሊድና አምሳያዎቹ ያሉ ለሐራም ነገሮች የሚያመቻቹ የጥፋት መዳረሻዎች መሃይሞች ፈጥነው እንደሚገቡባቸው አያጠራጥርም፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ በዒልም፣ በክብርና በስልጣን ዝና ያለው ሰው መካፈል ሲታከልበት ሐራም ነገሮችን እንደ ፈጣሪ ትእዛዛት ሲፈፅሙ፣ በድንቁርናና በጥመት ሸለቆች ውስጥ ገብተው ሲዘባርቁ፣ “የተከበሩ እከሌ፣ እከሌ፣ እከሌ፣… ተገኝተዋል” እያሉ ከተቃውሞ ሲያመልጡ የባሰ ይሆናል፡፡ መሃይሙ ህዝብ ይቅርና አንዱ በዒልም ፍለጋ ላይ ገኖ የወጣ ሰው አንዳንድ የኢጅቲሃድ እውቀቶችን ለመማር ከፊቴ ተቀምጦ ነበር፡፡ በዚህ ወር ከተከናወኑ መውሊዶች ውስጥ በአንዱ አዳር ላይ እንደተካፈለ ሲነግረኝ ተቃወምኩት፡፡ አንገሸገሸኝ፡፡ በዚህን ጊዜ ‘ሰዪዲ እከሌ፣ እከሌ፣ እከሌ፣… ተካፍለዋልኮ’ አለኝ፡፡ በነዚህ ታዋቂ ሰዎች ፊት የነበረውን አፈፃፀም ስጠይቀው እንዲህ አለኝ፡- ‘እነዚያ ታዋቂ ሰዎች እየዘፈኑና እያዳመጡ መንዙማውን አንድ ዱርየ አነበበ፡፡ ከዚያም አንዱ ልክ ከእስር የተነሳ ይመስል አፈፍ ብሎ ተነስቶ “መርሐባ ያ ኑረ ዐይኒ፣ መርሐባ” (እንኳን መጣህ ያይኔ ብርሃን እንኳን መጣህ!) ሲል ታዳሚው በመላ ታዋቂዎቹን ጨምሮ ተከትለውት ቆሙ፡፡ እነሱ በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉ ቆሞ ማጓራት ያዘ፡፡ አንዱ ታዳሚ ደክሞት ቢቀመጥ ከታዋቂዎቹ ውስጥ አንዱ ንዴቱ ከፊቱ ላይ እየታየ ‘ተነስ! ጨዋታኮ አይደለም!’ ብሎ ጮኸበት፡፡ ቃል በቃል! የአላህ መልእክተኛ ﷺ በዚያች ሰዓት ከነሱ ዘንድ እንደደረሱ ጭራሽ አይጠራጠሩም፡፡ ከዚያም ተጨባበጡ፡፡ ከመሀይማን ከፊሎቹ በእጆቻቸው ሽቶ በመያዝ በፍጥነት ቀቡ፣ ተቀቡ፡፡ ልክ የሳቸውን ﷺ መገኘት ለመጠቀም፡፡’ ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን! የዲን ክብር የት ገባ?! ይህም ከጠፋ አይናፋርነት፣ ግብረ ገብነት፣ ህሊና የት ገባ?” [ገፅ፡ 2/1089 - 91] 7. መውሊድን የነብዩ ﷺ ቤተሰቦች ይደግፉታል? መውሊድን የሚያከብሩ ሰዎች “ከኛ በላይ ነብዩን ﷺ የሚወድ ላሳር!” የሚሉ ናቸው፡፡ እውነት ለመናገር የነብዩ ﷺ ዘሮች ሙእሚኖች ከሆኑ ለነብዩ ﷺ ያላቸው ፍቅር ልዩ ነው፡፡ መውሊዱ የፍቅር መገለጫ ቢሆን ኖሮ ከማንም ቀድመው ባከበሩት ነበር፡፡ ግን ከነሱ የተገኘው መውሊድን ማክበር፣ ማስከበር፣ ለሱ ሽንጥን ገትሮ መሟገት ነውን? ሸውካኒይ፡- “ከነብዩ ﷺ ንፁሕ ቤተሰብም ይሁን ከተከታዮቻቸው ይህ ነገር እንደሚፈቀድ የተናገረ አንድም ፊደል አላገኘንም፡፡ እንዲያውም ይህቺ ቢድዐ ከተከሰተች ጀምሮ ወደ ጥፋቶች ከሚያሻግሩ አስቀያሚ መዳረሻዎች አንዷ እንደሆነች ንግግሮቻቸው ከሞላ ጎደል ተስማምተዋል፡፡” [ገፅ፡ 1089]

ትርፍ ጊዜ አጥፊ ነው አእምሮ ከዓላማ፣ ከሀሳብ ወይም ከሚማርከው ፍላጎት ባዶ በሚሆንበት ጊዜ፣ ወደ ምስቅልቅል አደባባይ ይለወጣል፡ በውስጡም ጥቃቅን ነገሮች ይጋነናሉ፣ በከንቱ ነገሮች ውስጥ ይጠፋል፣ እንዲሁም ጉልበት በማይገባቸው ጉዳዮች ላይ ይባክናል.. ኢብኑል ቀይም (አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ ብለዋል፡-
"ነፍስህ በሀቅ ካልጠመድካት፣ በባጢል ታጠምድሃለች።"

በሕፃንነትህ ጊዜ ስትታመም ዶክተሩ
"ምን ያምሃል?"
ብሎ ይጠይቅሃል! አንተ ግን ወደ እናትህ ትመለከታለህ፤ እሷም በአንተ ፈንታ ትመልሳለች።ምክንያቱም አንተ የሚሰማህን ነገር እሷም እንደምታውቀው ስለምትረዳ ነው። ስለዚህ ስታድግ አትዘንጋት።

🎉 بَارَكَ اللَّهُ لَكُمَا وَبَارَكَ عَلَيْكُمَا وَجَمَعَ بَيْنَكُمَا فِي خَيْرٍ የ2015 ተመራቂ የሆነው ወንድማችን የላጤነትን ሕይወትን በማጠናቀቅ ወደ ተከበረው የትዳር ዓለም የሚያደርገውንጉዞ ሀ ብሎ በመጀመር ላይ ነው:: ዛሬም ከእነዚህ 2015 ተመራቂ ተማሪወች  መካከል አንዱ የሆነው ወንድማችን ቃሲም  አህመድ ይህንን የተቀደሰ መንገድ ተቀላቅሏል ‎ ‎ወንድማችን በ 2015 ከ biology ትምህርት ክፍል congra ብለን እንዳስመረቅነው ሁሉ ዛሬም በሠርጉ ዕለት  ከላጤነት ሂወት እንኳን ወደ እዚህ ወደ ተከበረ የትዳር አለም well come ብለናል ወንድማችን  ትዳራችሁ ዱኒያን አልፎ እስከ ጀነት እንዲያረግላችሁ ወደ እዚህ የተባረከ አለም ለወፈቀህ ጌታችንን እንማፀነው አለን ‎ ‎ ‎ ‎አህባቦች የእኛም ተራ እስኪደርሰን ባረከላሁ እንበል ያ ረብ እኛንም በእዝነት በድጋሜ ሀቢቢ بَارَكَ اللَّهُ لَكُمَا وَبَارَكَ عَلَيْكُمَا وَجَمَعَ بَيْنَكُمَا فِي خَيْرٍ .......

" لا تستوحش في طريقك من قلة السالكين ولا تغتر بكثرة الهالكين "

በቂርዓት ስም ኢኽቲላጥ ቢስሚላህ አልሃምዱሊላህ በዘመናችን ብዙ ሚያስገርሙ ክስተቶችን እያየን ነው ሰው ቁርአን ሃዲስን ይዞ ስሜቱን ሲከተል ደግሞ እጅግ የሚደንቅ ተግባር ነው። ምክንያቱም አላህን ካወቀ(ከቀራ)ሰው ምንጠብቀው አላህ ከማይወደው ነገር መራቅን ነው። ነገር ግን ብዙዎቻችን እንደታዘብነው ቁርአንና ሃዲስን እናስተምራለን ብለው አንድ ቤት ላይ ሴትና ወንድን አስገብተው ሚያስተምሩ(ኡስታዞችን)እያየን ነው። አስቡት ወጣት ናቸው ሴትና ወንድ ባንድ ክላስ ላይ ሁኖ ምን አይነት ቂርአት ነው ሚቀራው።? ይሄ ግልፅ የሆነ ስሜትን መከተል እንጂ ልክ እንዳልሆነ ጃሂል ሰው እንኳ አይጠፋውም። የሚገርመው እነዚህ ሰዎች(ኡስታዞች)ምንም በቂ ምክንያት የላቸውም ለየ ብቻ የማያስተምሩበት ነገር ግን ነፍስያ እንዲህ አይነት ነገር ስለምትወድ ነፍስያቸውን እየተከተሉ ይገኛሉ። ያወቅነው ልንተገብረው እንጂ አውቀዋል ለመባል አይደለም። ምን አልባትም ይሄን ፁሁፍ ከምታነቡት ውስጥ በዚህ ተግባር(ማቅራትም መቅራቱም)ላይ ልትኖሩ ትችላላችሁ። ስሙ ነብያችን ምን እንዳሉ አይደለም አንድ ቤት(መድረሳ)ላይ ሴትና ወንድ አድርገው ማቅራትን ሊፈቅዱ የመስጅዱን የግቢ በር እንኳ የሴት ለብቻ የወንድ ለብቻ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። አስቡት አንድ ካላስ ውስጥ ለመቀመጥ አይደለም ለመውጣትና ለመግባት እንኳ እንዳይቀላቀሉና እንዳይተያዩ ነው ጥንቃቄ እንዲደረግ እንደተናገሩት። ስለዚህ ነብያችን ያስተማሩትን ዲን ለመማርና ለማስተማር ከሆነ ንያችን ሸሪዓው ባልፈቀደበት መንገድ መሆን የለበትምና አላህን እንፍራ። እንዲህ አይነት ነገር እየተስፋፋም ይገኛል የሚማሩትም ልጆች የተሻለ ግንዛቤ እያላችው አካሄዱ ልክ እንዳልሆነ እየተረዱም ግን መናገር አይፈልጉም። ምክንያቱም አንደኛ ከኛ የበለጠ ኡስታዞቹ ያውቃሉ ችግር ቢኖረው በዚህ መልኩ አያስተምርም ነበር ብለው ያስባሉ ግን ይሄም ስህተት ነው ምክንያቱም እንደኛ ሰው ናቸው ይሳሳታሉ። ሁለተኛ ነፍስያም ይሄንን ነገር ተወደዋለች ሴትና ወንድ መቀላቀሉን ነገር ግን ወላሂ ሚያሳፍር ተግባር ነው። ያውም ራሳቸውን እንደሱና ሰው ከሚያይ ጀመዓ ይሄ ተግባር በጭራሽ አይጠበቅም። እንመለስ ወደ አላህ የቂርአት አላማው አላህን ለመፍራት እንጂ እሱን ለማመፅ አይደለም። ስለዚህ በመጀመሪያ በዚህ መንገድ ምታስተምሩ ኡስታዞች አላህን እንፍራ እላለሁ። እንዲሁም በዚህ መንገድ ምትቀሩ እህት ወንድሞች ከቻላችሁ ይሄን አካሄድ ልክ እንዳልሆነ ተናግራችሁ ሴትና ወንድ አንድ ቤት ላይ መሆኑ እንዲስተካከል አድርጉ። ለዚህ ነገር ኡስታዞቹ ፍቃደኛ ካልሆኑ ከዚህ መንገድ ከመቅራት ርቃችሁ ሌላ በሱናው መንገድ የሚያቀሩ ኡስታዞችን ፈልጋችሁ ቅሩ። የሚገርመው በቅርቡ አንድ እህት ይሄን ትምህርት ስትማር ነበርና አቋረጠችው ኡስታዙም ለምን ያቋረጥሽው ብሎ ሲጥይቃት በነበረው የቂርአት አካሄድ እንደነበር ስነግረው ኡስታዙም ስህተት መሆኑ አልጠፋውም የመለሰላትም መልስ በቂ ገንዘብ የለኝምና ለሁለት ከፍየ ማስተማር አልችልም አሁንም ማገኘው ገንዘብ ትንሽ ነው ብሎ ነው የመለሰላት። አስቡት ለሚያገኘው ትንሽ ገንዘብ ብሎ ሃቁን እያወቀ ሱናውን እያፈረሰ ነው። ሌላም ቦታ እንደዚሁ አንድ እህት እንዲህ ባለ አካሄድ ቂርአን እንደሚቀቱ ነግራኝ ደረሳዎች ለኡስታዙ ልክ እንዳልሆነ በመናገር እንዲስተካከል አድርገዋል። ስለዚህ አቅሪውም ቀሪውም አላህን ሊፈራ ይገባል። ምትቀሩም ልጆች ከምን አይነት ኡስታዝ ነው እውቀት እየወሰድከ ያለው ሚለውን ልታስቡበት ይገባል። በዚህ መንገድ ምትቀሩም ልጆች ካሉት ተማሪዎችጋ ተመካክራችሁ ለኡስታዙ የቂርአት አካሄዱ እንዲስተካከል ተናገሩ። ከኛ ሚጠበቀው ሃቁን በጥበብ ማስታወስ ነው ኡስታዝ ነውና ብለን ዝም ልንል አይገባም። "ንያችን ማማሩ ብቻ በቂ አይደለም አካሄዳችንም መስተካከል አለበት።" ወላሁ አዓለም መልዕክቱን ሁላችንም በተለያዩ መንገዶች ሼር እናድርገው። አላህ ሚወደውን ይመራበታል። ©ወንድማችሁ ሙሂዲን ሰኢድ በዝሙት አንዘምን ቴሌግራም

"‌اللَّهُمَّ ‌صَلِّ ‌عَلَى ‌مُحَمَّدٍ ‌وَعَلَى ‌آلِ ‌مُحَمَّدٍ، ‌كما ‌صليت ‌على ‌إبراهيم، وعلى آل إبراهيم، إنك حميد مجيد، اللَّهُمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كما باركت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم، إنك حميد مجيد"

ለማንኛውም የበኑ ኡመያ መስለም ከነብዩ ﷺ እና ከኸሊፋዎቻቸው ዘንድ የሚጠረጠር አልነበረም። ሂንድን በተመለከተም መስለሟን ነብዩ ﷺ ከተቀበሏት በኋላ እኛ በጥርጣሬ የምናይበት ምንም አይነት ቀዳዳ የለም። ለሐምዛ እኛ ከነብዩ ﷺ በላይ ተቆርቋሪዎች አይደለንም። ያለ አንድ መረጃ የሰዎችን ያውም የሶሐቦችን እስልምና ጥያቄ ውስጥ መክተት የባለ ^ጌዎች ስራ ነው። የሚገርመው ሐምዛን በማስ7ደል እና ጉበቱን በማኘክ ሂንድን የሚያብጠለጥሉ አካላት በቀጥታ ግድያውን የፈፀመውን ወሕሺይን ግን ሲዘምቱበት እና እስልምናውን ጥያቄ ውስጥ ሲያስገቡ አይታዩም። ስለዚህ ሂንድም በመስለሟ የተነሳ ከነብዩ ﷺ ምርጥ ሶሐብያት ሆናለች ማለት ነው። ስለሆነም ለሶሐቦች አክብሮት እንዲኖረን የተነገረን ትምህርት ሂንድንም ያካትታል። ሶሐቦችን በክፉ እንዳናነሳ የተሰጠን ማሳሰቢያም እንዲሁ ሂንድንም ይመለከታል። ደግሞም እፈሩ! አቡ ሉእሉአ ማለት ከነብዩ ﷺ በኋላ የኡማው ሁለተኛ ታላቅ ሰው የሆኑትን ኸሊፋው ዑመርን፣ ሱብሒ ሶላት እያሰገዱ በነበሩበት በመርዛማ ስለት ወግቶ የ7ደለ ነው። ይሄ ሰውዬ እሳት አምላኪ መጁሲ ሙሽሪክ ነው። ሺዐዎች ዘንድ ግን ትልቅ የአላህ ወሊይ ነው። ዑመርን መግደሉን ትልቅ ገድል በማድረግ የተንጣለለ መታሰቢያ ዶሪሕ ገንብተውለታል። ለዚያራም ይመላለሱበታል። መግቢያው ላይም አቡበክርን፣ ዑመርንና ዑሥማንን የሚራገም ፅሁፍ በደማቁ አስፍረዋል። እነዚህ የጥመት ቋቶች እና የነዚህ እርጉሞች ደጋፊዎቻቸው ነጋ ጠባ በኑ ኡመያን ሲያብጠለጥሉ ማየት የሚደንቅ ነው። እንጥፍጣፊ ሞራል ቢኖራቸው ኖሮ በዚህ ልክ ርክስ፣ ቁሽሽ ያሉ ፍጥረቶችና የነሱ ደጋፊ ጭፍራዎች ስለ በኑ ኡመያ የማውራት ሞራል አይኖራቸውም ነበር። = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

እውን ሂንድ የሐምዛን ጉበት አኝካለችን? ~ ሂንድ ቢንቱ ዑትባህ የአቡ ሱፍያን ባለቤት፣ የሙዓዊየህ እናት ነች። ከመስለሟ በፊት የሐምዛን ጉበት አውጥታ አኝካለኝ በሚል ክስ ዛሬም ድረስ ትብጠለጠላለች። በሺዐዎች በተዘጋጀው አር-ሪሳላህ ፊልም ውስጥ ሂንድን እጅግ ጋጠ ወጥ አድርጎ የሚያሳይ በርከት ያለ ክፍል አለ። በርግጥ ይሄ ከሺዐ የማይጠበቅ አይደለም። ለአቡበክርና ለዑመር ያልተመለሱ ጠማሞች ለሂንድ ይመለሳሉ ተብሎ አይጠበቅም። የነብዩ ﷺ አጎት የሆኑት የአላህ አንበሳ ሐምዛ ብኑ ዐብዲል ሙጦሊብ ረዲየላሁ ዐንሁ የኡሑድ ጦርነት ጊዜ በሐበሻዊው ወሕሺይ መገ - ደላቸው የሚታወቅ ነው። ከዚያም ሆዳቸው ተቀዶ አካላቸው ተቆራርጦ ነውረኛ ተግባር ተፈፅሞባቸዋል። ታሪኩ እዚህ ድረስ ትክክለኛ መረጃ የመጣበት ነው። ከዚህ ውጭ ግን እንዲህ የሚል ዘገባ አለ። "ሂንድ ሆዱን ቀዳ ጉበቱን በማውጣት አኘከችው። ልትውጠው ግን አልቻለችም። የአላህ መልክተኛ ﷺ ሲያዩት 'ከእሱ በልታለት ይሆን?' ብለው ጠየቁ። 'አልበላችም' ሲሏቸው 'አላህ የሐምዛን አንድም ክፍል ወደ ጀሃነም እሳት እንዲገባ አይፈቅድም' አሉ።" [ሙስነድ አሕመድ፡ 4414] ይህንን ዘገባ መነሻ በማድረግ ሂንድን ዛሬም ድረስ ክፉኛ የሚያንቋሽሹ ሰዎች አሉ። ሺዐዎች እንኳ ከዚህም የከፋ ብዙ ነገር ስላላቸው ምንም ቢሉ አይደንቅም። የሚገርመው በነሱ ቅጥፈት ተመርዘው ዛሬም ሂንድን የሚኮንኑ ሰዎች ሁኔታ ነው። ይሄ አካሄድ ስሜትን በሸሪዐ ልጓም አለመቆጣጠር ነው። ሐምዛ ላይ የተፈፀመው ድርጊት እጅግ በጣም የሚያም መሆኑ ግልፅ ነው። ነገር ግን ለሐምዛ ያለን ቁጭትና መቆርቆር መነሻው ኢስላም ከሆነ ኢስላማዊ ህግጋትን ሰው እየመረጥን ልንጥስ አይገባም። በዚህ ክስ ሂንድን የሚያወግዝ አካል ቢያንስ ሁለት መሰረታዊ ነጥቦችን ጥሷል። #አንደኛው፦ ባልተጨበጠ ዘገባ ላይ ተመርኩዞ ነው ውግዘት ውስጥ የገባው። ታሪኩ የተላለፈበት ሰነድ ከ0ፋን፣ ከሐማድ፣ ከዐጧእ ብኑ ሳኢብ፣ ከሸዕቢይ፣ ከኢብኑ መስዑድ የሚል ነው። ደረጃው ለማስረጃ የሚበቃ ጥንካሬ የሌለው ደካማ ዘገባ ነው። እንዴት እንደሆነ እንመልከት፦ 1. ሸዕቢይ ከኢብኑ መስዑድ አልሰማም። አቡ ሓቲም፣ ዳረቁጥኒይ፣ ሓኪም እና ኢብኑ ሐጀር ይህንን አስረግጠው ተናግረዋል። [አልመራሲል፣ ኢብኑ አቢ ሓቲም ፡ ቁ. 591] [ጃሚዑ ተሕሲል ሊአሕካሚል መራሲል፣ አልዐላኢይ፡ 204] [መዕሪፈቱ ዑሉሚል ሐዲሥ፡ 111] [ተህዚቡ ተህዚብ: 7/419] 2. ዐጧእ ብኑ ሳኢብ ኢኽቲላጥ (የሒፍዝ መደባለቅ) የገጠመው ሰው ነው። ይህንን ኢብኑ መዒን፣ ቡኻሪ፣ ዒጅሊ፣ ኢብኑ ዐዲይ፣ ኢብኑ ቀጧን፣ ኢብኑ ከሢር፣ ኢብኑ ሐጀር ገልፀውታል። [አት-ታሪኹል ከቢር፡ 6/465] [አሥ-ሢቃት፣ ዒጅሊ፡ 332] [አልካሚል፡ 7/72] [ተቅሪቡ ተህዚብ፣ ኢብኑ ሐጀር፡ 1/391] [አድ-ዱዐፋኡል ከቢር፡ 3/398] [አልቢዳያ ወንኒሃያ፡ 5/430] [ተህዚቡ ተህዚብ: 7/207] ይሄም የዘገባውን ዋጋ ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ሌላ ድክመት ነው። የሚከተሉት ሙሐዲሦች ደግሞ ታሪኩ ደካማ እንደሆነ በቀጥታ የገለፁ ናቸው፦ 1ኛ፦ ኢብኑ ከሢር [አልቢዳያ ወንኒሃያ፡ 5/430] 2ኛ፦ አልሐይሠሚ 3ኛ፦ አልአልባኒይ [ፊቅሁ ሲራ፡ 279-280] ታሪኩን ሶሒሕ ወይም ሐሰን በማለት ዋጋ ለመስጠት በሞከሩት አሕመድ ሻኪርና አርነኡጥ ላይ ዘለግ ያለ አጥጋቢ ምላሽ የተሰጠበትን ትንታኔ መመልከት የፈለገ إزاحة الغمة في بيان ضعف قصة أكل هند من كبد حمزة የተሰኘውን ጥናት መመልከት ይችላል። #ሁለተኛው መሰረታዊ የዘገባው ችግር፦ ከሰነድ ባለፈ መልእክቱ ራሱ ፍፁም የተሳሳተ መሆኑ ነው። ዘገባው ላይ ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል የሚል አለበት:- “አላህ የሐምዛን አንድም ክፍል ወደ ጀሃነም እሳት እንዲገባ አይፈቅድም።” ይሄ ማለት ሂንድ የእሳት ነች ማለት ነው። ይሄ የተሳሳተ ነው። ሶሒሕ አይደለም እንጂ ሂንድ ድርጊቱን መፈፀሟ ቢረጋገጥ እንኳ ይሄ ተግባር ከመስለሟ በፊት የተፈፀመ ነው። መስለሟ በአስተማማኝ ሰነድ ተረጋግጧል። [ቡኻሪ፡ 3825] [ሙስሊም፡ 1714] በተለያዩ ሐዲሦች እንደተረጋገጠው ኢስላም የቀደመን ወንጀል ሁሉ ያብሳል። ይህ ከሆነ ድርጊቱን ለመፈጸሟ በቂ መረጃ የለም እንጂ ቢኖርስ ከመስለሟ በፊት በነበረ ጉዳይ እንዴት የእሳት ትሆናለች? ይሄ ከመሰረታዊ የኢስላም አስተምህሮት ጋር የሚቃረን ነው። በርካታ የምንወዳቸው ሶሐቦችኮ ከመስለማቸው በፊት ሺርክን ጨምሮ ብዙ ከባባድ ወንጀሎችን ፈፅመዋል። ልክ እነዚያ ከመስለማቸው በፊት በተፈፀመ ወንጀል እንደማይወቀሱት ሂንድም ከመስለሟ በፊት በተፈፀመ ድርጊት አትወቀስም። ልክ የሐምዛ ገዳይ የሆነውን ወሕሺይን ከመስለሙ በፊት በፈፀመው ድርጊት ከሰለመ በኋላ እንደማንወቅሰው ማለት ነው። ጌታችን እንዲህ ማለቱ ይታወስ፦ {قُلۡ یَـٰعِبَادِیَ ٱلَّذِینَ أَسۡرَفُوا۟ عَلَىٰۤ أَنفُسِهِمۡ لَا تَقۡنَطُوا۟ مِن رَّحۡمَةِ ٱللَّهِۚ إِنَّ ٱللَّهَ یَغۡفِرُ ٱلذُّنُوبَ جَمِیعًاۚ إِنَّهُۥ هُوَ ٱلۡغَفُورُ ٱلرَّحِیمُ} "በላቸው 'እናንተ በነፍሶቻችሁ ላይ ድንበር ያለፋችሁ ባሮቼ ሆይ! ከአላህ እዝነት ተስፋ አትቁረጡ፡፡ አላህ ኃጢኣቶችን በመላ ይምራልና፡፡ እነሆ እርሱ መሓሪው አዛኙ ነውና፡፡" [አዝ-ዙመር: 53] ይህንን ከመሰሉ ሰፋፊ የአላህ የእዝነት አዋጆች ውስጥ ሂንድን ለይተን ልናወጣ ነውን? ለራሳችን ልንፈራ ይገባል። በሌላም ቦታ ጌታችን አላህ ሺርክ የሚፈፅሙ፣ ነፍስ የሚያጠፉ፣ ዝሙት የሚፈፅሙ ሰዎች አሳማሚ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው በዛተበት ላይ ተውበት የሚያደርጉትን ግን እንዲህ ሲል እንደሚምራቸው ገልጿል:- {إِلَّا مَن تَابَ وَءَامَنَ وَعَمِلَ عَمَلࣰا صَـٰلِحࣰا فَأُو۟لَـٰۤىِٕكَ یُبَدِّلُ ٱللَّهُ سَیِّـَٔاتِهِمۡ حَسَنَـٰتࣲۗ وَكَانَ ٱللَّهُ غَفُورࣰا رَّحِیمࣰا} "ተፀፅቶ የተመለሰና ያመነ መልካምንም ሥራ የሠራ ሰው ብቻ ሲቀር፡፡ እነዚያም አላህ መጥፎ ሥራዎቻቸውን በመልካም ሥራዎች ይለውጣል፡፡ አላህም እጅግ መሓሪ አዛኝ ነው።" [አል-ፉርቃን፡ 70] ታዲያ ሂንድን ከሰለመችም በኋላ ከነዚህ የአላህ የተስፋ ቃል ውጭ ልናደርጋት ይቻላል ወይ? አደብ ሊኖረን ይገባል። ሁሉንም ሶሐቦች አላህ መልካም ስራዎቻቸውን ይውደድላቸው። ከመስለሟ በፊት በተፈጠረ ክስተት ማብጠልጠል ለምን አስፈለገ? ምክንያቱ ወዲህ ነው። እነዚህ ባ -ለጌዎች የአቡ ሱፍያንንም፣ የሂንድንም መስለም አይቀበሉም። ሺዐዎች እና እነሱን በጥመት የተከተሉ እንደ ሰይድ ቁጥብ ያሉ የኢኽዋን አፈንጋጮች ዘንድ የበኑ ኡመያ ቤተሰቦች ኢስላምንና የነብዩን ﷺ ቤተሰቦች ለመበቀል ነው የሰለሙ የመሰሉት እንጂ ኢማን ወደ ልባቸው አልገባም። በዚህ ደረጃ የነብዩን ﷺ ሶሐቦች ከእስልምና እያስወጡ እያከ^ ፈሩ ለዘብተኛና ሚዛናዊ መስለው ሲተውኑ ስቅም አይላቸውም።

🎤ለተማሪዎች እና ለትውልድ የሚሆን የዑለሞች የማንቂያ ደውል ምክር 👉እነዚህ በአገራችን ውስጥ በአዲስ አበባ የሺዓን አስተምህሮት እያስፋፉ የሚገኙ አንጃዎች ናቸው ።ወንድሞች እና እህቶች ልንጠነቀቅ ይገባል ! ​ታላላቅ የሱና ዑለማዎች ወጣቱ ትውልድ እራሱንና እምነቱን ከዚህ አደጋ እንዲጠብቅ የሚከተሉትን ወርቃማ ምክሮች ይለግሳሉ፦ ​ሀ. ትክክለኛውን የዓቂዳ (የእምነት) እውቀት መቅሰም ​የሺዓን ተንኮል ለመከላከል ትልቁ መሣሪያ ተውሂድንና የሰለፎችን (የቀደምት ደጎች) ዓቂዳ በሚገባ መማር ነው። ጨለማን ለማጥፋት ብርሃን እንደሚያስፈልገው ሁሉ፣ ስሕተትን ለማስወገድም ትክክለኛውን የሱና እውቀት መያዝ ግድ ይላል። ​ለ. የነብዩን ﷺ ባልደረቦች (ሶሓባዎችን) ማክበርና ለነሱም መከላከል ​የሺዓዎች ትልቁ ተንኮል የነብዩን ﷺ ሶሓባዎች (በተለይም አቡበክርን፣ ዑመርንና ዓኢሻን - ረዲየላሁ ዐንሁም) መሳደብና ማግለል ነው። ዑለማዎች እንደሚሉት፡ ​"ሶሓባዎችን መተቸት ማለት ዲኑን ለማፍረስ መሞከር ማለት ነው፤ ምክንያቱም ዲኑ ለእኛ የደረሰን በእነሱ በኩል ነውና።" ስለዚህ የሶሓባዎችን ታሪክና ደረጃ በሚገባ መማርና ማስተማር ያስፈልጋል። ​ሐ. እውቀትን ከታመኑ የሱና ዑለማዎች ብቻ መውሰድ ​በየማህበራዊ ሚዲያው (ቲክቶክ፣ ቴሌግራም፣ ዩቲዩብ) ላይ የሚለቀቁ ማራኪ የሚመስሉ ግን መርዛማ የሆኑ ስብከቶችን ከመስማት መቆጠብ። ነብዩ ﷺ እና ሰለፎች እንዳስተማሩት ዲንን ከማን እንደምንቀበል ማየት አለብን። ካልታወቁና ጥርጣሬ ካለባቸው አካላት እውቀት መቅሰም የተከለከለ ነው። ​መ. በቡድንና በልዩ ልዩ ስሞች ከመከፋፈል መራቅ ​ አላህ በቁርዓን ላይ እንዳዘዘው በአላህ ገመድ ስር መሰብሰብና እርስ በእርስ መተጋገዝ ይገባል።

🎓 بِسْمِ اللهِ الرَّحْمَنِ الرَّحِيمِ 🎓 سَمَرَ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ 축 18ኛው ዙር ምረቃ — እንኳን ደስ አላቹህ! 🌙✨ አልሀምዱሊላህ! የሰመራ ዩኒቨርስቲ 18ኛ ዙር ምረቃ በጥሩ ሁኔታ ተካሂዷል ። ዓመታትን በትጋት፣ በሥነ ምግባር፣ እና በእምነት ጉዞዋቸውን ያጠናቀቁ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን — مَبْرُوك، أَلْف مَبْرُوك!              🏆  እንኳን ደስ አላቹህ — የዋንጫ ተሸላሚዎች 🥇 አጠቃላይ Overall Trophy Winner ወንድማችን ዶ/ር መሀመድ ሀሰን ገመዳ 📚 ቬተርነሪ ሜድሲን | CGPA: 3.96 ከሙሉው ተመራቂ ተማሪዎች  አንደኛ በመሆን አጠናቋል!     ماشاءالله، بارك الله فيك             🥇 Overall Women's Trophy Winner እህታችን ሀስና ኢብራሒም አብደላ 📚 ፐብሊክ ሄልዝ ኦፊሰር | CGPA: 3.82 ከሁሉም ሴት ተመራቂዎች ተወዳድራ አንደኛ በመሆን አጠናቃለች ! ماشاءالله، بارك الله فيها قَالَ رَسُولُ اللهِ ﷺ: "مَنْ سَلَكَ طَرِيقًا يَلْتَمِسُ فِيهِ عِلْمًا، سَهَّلَ اللهُ لَهُ طَرِيقًا إِلَى الْجَنَّةِ" "ዕውቀትን ፍለጋ የተጓዙ ሰው ሁሉ — አላህ ወደ ጀነት መንገዳቸውን ያቀልላቸዋል።" ወደ ፊትም በዲናቹህ እንድትበረቱ ፣ማህበረሰባችሁን በሀቅ እንድታገለግሉ፣ ሁሌም የአላህን ቁርአንና የነብዩን ሐዲስ ከሁሉም በፊት ተቀዳሚ እንድታደርጉ የሰመራ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ምኞቱን ያሳውቃል። وَفَّقَكُمُ اللهُ جَمِيعًا                            አላህ ሁላችንንም ይጠብቀን! 🤲 — ሰመራ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ (SUMSG)

💎 { ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا ت
💎 { ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ }      💎   ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ  💎 🤲 اللهم صلي على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم في العالمين إنك حميد مجيد... 🕌 ከጁሙዓ ቀን ሱናዎች     🚿   ገላን መታጠብ     🖇 ጥፍርን መቁረጥ     👕 ጥሩ ልብስ መልበስ     ⚱️ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች ብቻ)      🥢  መፋቂያ መጠቀም    🕰  በጊዜ ወደመስጂድ መሄድ    🕌  ወደ መስጂድ ሲሔዱ በተቻለ መጠን           በእግር መጓዝ    🔸ኢማሙ ሚንበር ላይ እስኪወጣ ባለው ሰዐት የሱና ሰላትን መስገድ (አልነፍል አልሙጥለቅ)    👉  በነብዩ - ﷺ - ላይ ሰለዋት ማብዛት    📖   ሱረቱል ከህፍን መቅራት 🦻ኹጥባን በጥሞና ማዳመጥ    🤲 ዱዓ ተቀባይነት ያለበትን ሰአት መጠባበቅ ⚡️ሌላ ሰው ቢያወራም ዝም በል አለማለት ⚡️በተጨማሪ አርፍደው ከመጡ የሰው ትከሻ ላይ እየተረማመዱ ሶፍ ውስጥ ከመግባት መቆጠብ :: ===================

በያመቱ ሙሐረም አስርን እየጠበቁ አካላቸውን በስለት እየተለተሉ፣ ጥቁር ለብሰው "ሑሴን" እያሉ ሙሾ የሚያወርዱት ሺዐዎች የታላቁን ኸሊፋ፣ የዑመር ብኑል ኸጧብ 7ዳይ ለሆነው ለአቡ ሉእሉአ የጀግና መታ
በያመቱ ሙሐረም አስርን እየጠበቁ አካላቸውን በስለት እየተለተሉ፣ ጥቁር ለብሰው "ሑሴን" እያሉ ሙሾ የሚያወርዱት ሺዐዎች የታላቁን ኸሊፋ፣ የዑመር ብኑል ኸጧብ 7ዳይ ለሆነው ለአቡ ሉእሉአ የጀግና መታሰቢያ የገነቡ ናቸው። "አቡ ሉእሉአ አልመጁሲ ማለት ዑመር ብኑል ኸጧብን የሱብሕ ሶላት እያሰገዱ እያሉ በመርዛማ ሰይፍ የ7ደላቸው ሙሽሪክ ነው። በእለቱ ከዑመር በተጨማሪ ወደ ሰባት ሶሐቦችን የ7ደለ ሲሆን ሌሎች በርካቶችንም አቁስሏል። የተያያዘው ምስል ኢራን ውስጥ የሚገኝ የአቡ ሉእሉአ ዶሪሕ መግቢያ በር ነው። ቀብሩ ላይ ትልቅ ቤት ገንብተው ይዘይሩታል፣ ይመላለሱበታል። አቡ ሉእሉአ አልመጁሲ የመጁሳ (እሳት አምልኮ) ሃይማኖት ተከታይ የነበረ ቢሆንም ኢራኖች ዘንድ ትልቅ የአላህ ወሊይ ነው። ለዑመር ያላቸው ጥላቻ ነው በዚህ ርቀት የወሰዳቸው። ዑመርን በየ ሶላታቸው የሚራገሙ፣ ጣዖት ነው የሚሉ፣ እሱ ብቻ ሳይሆን ለሱ "ረዲየላሁ ዐንሁ" እያለ ዱዓ የሚያደርግም ሙሽሪክ እንጂ ሙስሊም አይደለም የሚሉ እነዚህ መጁሳዎች ለመጁሲው ግን ማስታወሻ ዶሪሕ አቁመውለታል። ታላቁን ኸሊፋ ዑመርን አውግዞ፣ ለሙሽሪኩ አቡ ሉእሉአ አልመጁሲ ሀውልት የሚያቆም የሺዐ እምነት በሑሰይን ሞት ዓመት እየጠበቀ የሚያላዝነው ለሑሰይን ተቆርቆሮ አይደለም። በሱ ተንጠላጥሎ ሌሎችን ለመንካት ነው። = የቴሌግራም ቻናል :- https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

የ2018 ,18 ዙር ተመራቂዎች በከፍተኛ መዕረግ የተመረቁ ሙስሊም ተማሪዎች 🎓Congrats ... ሀስና ኢብራሒም ከሰመራ ዩኒቨርስቲ የዋንጫ ተሸላሚ ! ! !    እየሞከሩ ያሉት እርሷን እና መሰሎቿን በስኬት ላይ ላለማየት ቢሆንም ችግሩን ሁሉ ተቋቁመው ዋንጫም እየተሸለሙ ነው። ጥረታቸው ኒቃብን አስታኳ ሙስሊም ተማሪዎችን ከሁለንተናዊ ስኬት ማደናቀፍ ቢሆንም ሀስና እና መሰሎቿ ግን ጩኸታቸውን ሳይሰሙ መድረስ ካለባቸው ደርሰው እያሳዩ ነው።   ሀስና ኢብራሒም በPublic Health Department የከፍተኛ ማዕረግ ተሸላሚ ከመሆን ባሻገር ከHealth and Medicine College የሜዳልያ ተሸላሚ እንዲሁም ከሁሉም ተመራቂ ሴት ተማሪዎች የላቀ ውጤት በማምጣት የዋንጫ ተሸላሚ ሆናለች።   እንደለበሰች ተምራለች   እንደለበሰች ትማራለች   እንደለበሰች ትመረቃለች   እንደለበሰች ከማዕረግ ከዋንጫ ትደርሳለች 🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉

​📢 ደዉራህ በሎጊያ ከተማ (አንሷር መስጂድ) ​📚 የሪሳላዋ ስም: الطريق إلى السلفية ("አጥ-ጦሪቁ ኢለ ሰለፊያህ") ​📖 የሪሳላዋን ፒዲኤፍ (PDF) ለማግኘት: 👉 https://t.me/durusuabihizam/3771 ​📅 የሚሰጥበት ቀንና ሰዓት: አርብ እና ቅዳሜ ከመግሪብ ሶላት በኋላ ​📍 የደርሱ ቦታ: ሎጊያ — አንሷር መስጂድ ​📱 ደርሱ የሚተላለፍበት የቴሌግራም ቻናል: 👉 https://t.me/durusuabihizam

እንኳን ደስ አላችሁ ውድ ተማሪዎቻችን! 🎊 📍 Samara University Muslim Students Jemea ዛሬ የምርቃት ቀናችሁ በመሆኑ ከልብ እንኳን ደስ አላችሁ። ይህ ስኬት የእናንተን ትጋት፣ የቤተሰቦቻችሁ ድጋፍ እና የአላህ ረድኤት ውጤት ነው። 🤲 አላህ ለዚህ ትልቅ ቀን በሠላም እንዳደረሳችሁ እንደረዳችሁ፣ ወደፊትም በሕይወታችሁ ሁሉ ላይ ስኬት፣ በረከት እና መልካም መንገድ ይስጣችሁ። 🌙 ዲናችሁን የሚጠቅም እውቀት እንዲሰጣችሁ፣ ራሳችሁንና ማህበረሰባችሁን የሚጠቅም ሰዎች እንድትሆኑ አላህ ይወፍቃችሁ። ✔️እንኳን አደረሳችሁ🌿 ✔️Unkaq ruffa teenih🌿 ✔️BAGA NAGAYAAN GEESSAN 🌿 ✔️

#exit_exam ውጤት ማያ ዌብሳይቱ መስራት ጀምሯል ታማኝ እና ፈጣን መረጃ ሁልጊዜም አንደኛ🏆 https://result.ethernet.edu.et/usernamepage