Tikvah-University
📈 Аналитический обзор Telegram-канала Tikvah-University
Канал Tikvah-University (@tikvahuniversity) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 382 360 подписчиков, занимая 115 место в категории Образование и 13 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 382 360 подписчиков.
Согласно последним данным от 05 сентября, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 11 670, а за последние 24 часа — 415, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 18.79%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 11.24% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 71 832 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 42 996 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 191.
📝 Описание и контентная политика
Описание канала не предоставлено.
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 06 сентября, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Образование.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 06 сентября | 0 | |||
| 05 сентября | +415 | |||
| 04 сентября | +259 | |||
| 03 сентября | +618 | |||
| 02 сентября | +310 | |||
| 01 сентября | +731 |
| 2 | #ተጨማሪ
ጳጉሜን 02 እና 03/2018 ዓ.ም የሚሰጠውን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (UAT) ለመውሰድ የመፈተኛ ማዕከላችሁን አምቦ ዩኒቨርሲቲ የመረጣችሁ ፈተናው የሚሰጥበት ማዕከል በሀቻሉ ሁንዴሳ ካምፓስ መሆኑ ተገልጿል።
በተመሳሳይ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲን በፈተና ማዕከልነት የመረጣችሁ፣ ፈተናው በፖሊ ካምፓስ የሚሰጥ መሆኑ ተመላክቷል።
@tikvahuniversity | 752 |
| 3 | #AAU #UAT
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም በመደበኛ መርሐግብር የቅድመ-ምረቃ ትምህርት ለመከታተል ላመለከታችሁ የቅድመ-ምረቃ የመግቢያ ፈተና (UAT) ጳጉሜን 02 እና 03/2018 ዓ.ም ይሰጣል።
ፈተናው በተጠቀሱት ቀናት በሦስት ፈረቃ ማለትም ፈረቃ 1: ጠዋት ከ2:30-5:00 ፈረቃ 2: ረፋድ ከ5:30-8:00 ፈረቃ 3: ከሰዓት ከ8:30-11:00 የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል።
መርሐግብሩን እዚህ በጥንቃቄ ይመልከቱ። የመፈተኛ ማዕከልዎን የመፈተኛ ሰዓትዎን በደንብ ይመልከቱ።
🔔 ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ፣ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ እና ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲን ለፈተና ማዕከልነት የመረጣችሁ አመልካቾች ወደ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል የተዘዋወራችሁ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ለፈተና ማዕከል የመረጡ ማየት የተሳናቸው አመልካቾችች በሙሉ ዋናው ግቢ በሚገኘው የአካል ጉዳተኞች ማዕከል ላብ 1 ማክሰኞ ጳጉሜን 03/2018 ዓ.ም በፈረቃ 3 ፈተናቸውን የሚወስዱ መሆኑ ተገልጿል፡፡
@tikvahuniversity | 33 916 |
| 4 | የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በተለያዩ የጤና ሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 252 የጤና ባለሙያዎች አስመርቋል።
ተመራቂዎቹ በሕክምና ዶክትሬት፣ በነርሲንግ፣ በሕክምና ላቦራቶሪ ሳይንስ፣ በስፔሻሊቲ፣ በሰብ-ስፔሻሊቲ እና በማኅበረሰበ ጤና ማስተርስ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
ኮሌጁ በዛሬው 9ኛ ዙር የምርቃት ስነ-ስርዓት፣ በነርሲንግ እና በሕክምና ላቦራቶሪ ሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ አስመርቋል።
ኮሌጁ በአኔስቴዢያ እና በክሪቲካል ኬር ሜዲሲን ስፔሻሊቲ እንዲሁም በዩሮጋይኔኮሎጂ ሰብ-ስፔሻሊቲ ለመጀመሪያ ጊዜ ተማራዎችን አስመርቋል።
በሕክምና ዶክትሬት ትምህርት CGPA 3.90 ውጤት ያስመዘገበው ዶ/ር ይርጋለም መሐመድ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል።
ኮሌጁ የቅድመ-ምረቃ የሕክምና ዶክትሬት ስልጠና፣ ስፔሻሊቲ እና ሰብስፔሻሊቲን ጨምሮ በ21 ፕሮግራሞች የሕክምና ትምህርት በመስጠት ላይ ይገኛል።
@tikvahuniversity | 42 253 |
| 5 | #ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ
የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ላይ ነው❗️
BSc Fields of Study:
→ Doctor of Medicine
→ Doctor of Dental Medicine
→ Bachelor of Dental Science
→ Nursing
TVET Programs:
→ Dental Therapy
→ Nursing
→ Medical Laboratory
→ Pharmacy
→ Radiography
⭐️ የ CPD ማዕከል አገልግሎት!
☎️ 0913398780 / 0911596059
አድራሻ፦
CMC አደባባይ ከፀሐይ ሪል እስቴት ጀርባ ከ ICMC ጠቅላላ ሆስፒታል አጠገብ
📍 Addis Ababa, CMC Square, Behind Tsehay Real Estate, next to ICMC General Hospital
Facebook: https://www.facebook.com/Lorcanmedicalcollege
Tiktok: https://www.tiktok.com/@lorcan.medical.co | 35 756 |
| 6 | #NGATResult
ነሐሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት ተለቋል።
ውጤትዎን ለማየት 👇
https://result.ethernet.edu.et
ሊንኩን ከተጫኑ በኋላ 'NGAT Results' ላይ 'View Results' የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ።
@tikvahuniversity | 42 812 |
| 7 | የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2019 ዓ.ም ቅበላ የመግቢያ ፈተና ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል።
ወደ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለመሔድ ከላይ በምስሉ የተገለፁትን አራት የትራንስፖርት አቅጣጫ አማራጭ መንገዶች ይጠቀሙ።
@tikvahuniversity | 39 753 |
| 8 | 🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ!
► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ
► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው
► የኮሪያ ሆስፒታል እህት ኩባንያ
15ኛ ዙር የህክምና ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን!
🎓 ኮሌጃችን ያስተማራቸውን ተማሪዎች በሙሉ የብቃት ምዘና ፈተና ማሳለፍ ችሏል!
ለማመልከት 👇
https://maps.app.goo.gl/oxRezU99L2DqnngD6
አድራሻ፦
አዲስ አባባ፣ ገርጂ ኮሪያ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ሬጅስትራር ቢሮ
የምዝገባ ጊዜ 👇
እስከ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ድረስ። አሁኑኑ ይመዝገቡ!
☎️ 0116395020
ድረ-ገጽ፦ www.mmc-edu.net
Facebook: https://web.facebook.com/MMCmedcollege/
#MyungsungMedicalCollege | 34 433 |
| 9 | 🌻 የአዲስ ዓመት 25% ቅናሽ ከነሐሴ 27/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም🌻
12ኛ ዙር የኢንቴሪየር ዲዛይን (Interior Design) ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን!
👉 AutoCAD, Revit, እና 3D Max ሶፍትዌሮችን በአንድ ላይ
👉 በተጨማሪ በተግባር በወርክሾፕ የሚሰጥ
የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ደራርቱ ህንፃ 5ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com
Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute | 34 542 |
| 10 | የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2019 ዓ.ም ቅበላ የመግቢያ ፈተና ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም ይሰጣል።
በ2019 ዓ.ም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በአፕላይድ ሳይንስ እና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች የመግቢያ ፈተና ለመፈተን በኦንላይን የተመዘገባችሁ አመልካቾች የመግቢያ ፈተና ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ተገልጿል።
በመሆኑም ያመለከታችሁ በሙሉ በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ በአካል በመቅረብ መፈተን የምትችሉ መሆኑን ዩኒቨርሲቲዎቹ አሳውቀዋል።
ተፈታኞች በዕለቱ ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያዎች መገኘት ይጠበቅባችኋል። የሞባይል ስልክ እንዲሁም ማንኛውም ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችን ይዞ ወደ ፈተና ጣቢያ መግባት የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል፡፡
አመልካቾች ለፈተና ስትቀርቡ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤት፣ የአድሚሽን ካርድ እና የምዝገባ ማረጋገጫ ኮፒ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
የመግቢያ ፈተናውን የሚያልፉ አመልካቾች በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በሚደረገው የዩኒቨርሲቲ ምደባ ውስጥ አይካተቱም፡፡
@tikvahuniversity | 50 394 |
| 11 | የ Anesthesia ሙያ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የተግባር ፈተና ጳጉሜን 03/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡
ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ Anesthesia ሙያ በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ በነሐሴ 2018 ዓ.ም የፅሑፍ ፈተና ያለፋችሁና የተግባር ፈተና (OSCE) ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ፤ ፈተናው ጳጉሜን 03/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
ተፈታኝ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ መከታተል ይኖርባቸዋል ተብሏል።
ተፈታኞች በፈተናው ዕለት ማንነታቸውን የሚገልፅ ብሔራዊ መታወቂያ መያዝ ይኖርባቸዋል የተባለ ሲሆን፣ ምንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ (ስልክ፣ የእጅ ሰዓት፣ መነጽር (የተረጋገጠ የዕይታ ችግር ከሌለ በስተቀር) ይዞ መግባት አይፈቀድም፡፡
ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲሔድ ሲስተሙ የሚሰጠውን QR Code ያለው የፈተና መግቢያ ስሊፕ መያዝ ይጠበቅበታል፡፡
(ተመዛኞች የመረጣችሁትን የፈተና ጣቢያ እዚህ ይመልከቱ፡፡)
@tikvahuniversity | 53 612 |
| 12 | #Pioneer_College
🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ
የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️
ከትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዕውቅና ባገኘንባቸው የዲግሪ ፕሮግራሞች፦
► የሕክምና ዶክትሬት
► የጥርስ ሕክምና ዶክትሬት
► ፋርማሲ
► ሜዴካል ላብራቶሪ ሳይንስ
🔔 ምዝገባ ጀምረናል!
በጤናው መስክ ተወዳደሪ ሆኖ ለመገኘት ካሰቡ አሁኑኑ ፓዩኒዬር ኮሌጅ ይመዝገቡ!
አድራሻ
ከጀርመን አደባባይ ወደ ለቡ መብራት በሚሰደው መንገድ
☎️ 0902442244 / 0902443344
www.pioneercollege.edu.et | 51 190 |
| 13 | ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የሰባት የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ውጤታቸው በስህተት Disqualified እንደተባለባቸው በመግለፅ፣ የዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር ጽ/ቤት ለትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ማሳወቁን ገልጿል።
ሰባቱም ተማሪዎች ለአገልግሎቱ ማመልከት ስለሚገባቸው፣ ተማሪዎቹ ቅሬታቸውን እንዲያቀርቡ መረጃው እንዲደርሳቸው ጠይቋል፡፡
ተማሪዎቹ (3 የማኅበራዊ ሳይንስ እና 4 የተፈጥሮ ሳይንስ) ፈተናቸውን በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል የወሰዱ ናቸው።
(ጥር 11, 2022 የተከፈተና 18,853 ተከታዮች ያሉት የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር የቴሌግራም ገጽ ትናንት ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ያጋራው መረጃ ከላይ ተያይዟል።)
በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ፈተናቸውን የወሰዱና ውጤታቸው Disqualified የተባለባቸው እጅግ በርካታ ተማሪዎች ቅሬታቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ። በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የተገለፀው አይነት መሠል ግድፈት ሊኖር ስለሚችል ዩኒቨርሲቲዎች በድጋሜ የሪሚዲያል ተፈታኞችን ውጤት እንዲያዩ ይጠየቃሉ።
@tikvahuniversity | 52 948 |
| 14 | የመውጫ ፈተና አፈጻጸም በከፍተኛ ትምህርት ተቋም
መንግሥት በመውጫ ፈተና ምክንያት ከዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ወጪ መጋራት በሁለት ዓመት ብቻ 8 ቢሊዮን ብር ማጣቱን አንድ ጥናት አሳየ፡፡
የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን አጠናቀውና የመውጫ ፈተና ወስደው ያላለፉና ሰርተፍኬት ባለማግኘታቸው ምክንያት በኮንትራትም ሆነ በቋሚ መቀጠር ካልቻሉ ተማሪዎች፣ መንግሥት በሁለት ዓመት ብቻ ያገኝ የነበረውን ስምንት ቢሊዮን ብር እንዳጣ አንድ ጥናት አረጋገጠ፡፡
መንግሥት የተጠቀሰውን ያህል ገንዘብ እንዳጣ የተገለፀው፤ ትምህርት ሚኒስቴር ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን፣ ከአሪዞና ዩኒቨርሲቲ እና ከሽያሾኔ ተቋም ጋር በመተባበር ባዘጋጀው አውደ ጥናት ላይ ነው፡፡
የመውጫ ፈተና በከፍተኛ ትምህርት ተቋም ውስጥ ያለው አፈጻጸም፣ የታዩ ችግሮች እና የወደፊት መፍትሔ ምን ሊሆን እንደሚገባ ትኩረት ያደረገ ጥናት በመድረኩ ላይ ቀርቧል፡፡
ጥናቱን ያደረገው ቡድን ከአዲስ አበባ፣ ከሐዋሳ እና ከጅማ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም ከትምህርት ሚኒስቴር የተውጣጡ አባላት ያሉት መሆኑን፣ ጥናቱን ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ምርምር ማዕከል አባል አብርሃም ቱሉ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡
በ2016 እና 2017 ዓ.ም. የመውጫ ፈተና ከሰጡ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ከ128,000 በላይ ተማሪዎች መውደቃቸውንና ከተፈተኑት ውስጥ ከ52.7 ከመቶ በላይ የሚሆኑት ደግሞ ማለፋቸው በጥናቱ ተመላክቷል፡፡
የግል የትምህርት ተቋማት ደግሞ 14.8 በመቶ ብቻ ተማሪዎች ማለፋቸውን፣ በዚህም ትልቁ የመውደቅ ምጣኔ የተመዘገበው በግል የትምህርት ተቋማት መሆኑን ጥናቱ አሳይቷል፡፡ ሦስት የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በምንም ዓይነት የትምህርት ፕሮግራም ተማሪዎችን አለማሳለፋቸው በመረጃ መረጋገጡን የጥናቱ አቅራቢ ተናግረዋል፡፡
በአጠቃላይ በሁለት ዓመታት ውስጥ የተመዘገበው የማለፍ ምጣኔ 33.1 በመቶ ሲሆን፣ 66.9 በመቶ የሚሆነው ደግሞ የመውደቅ ምጣኔ መሆኑን በጥናቱ ግኝት መካተቱ ተገልጿል፡፡ በመሆኑም የመውጫ ፈተና አልፈው ተቀጥረው ቢሆን በሁለት ዓመት ውስጥ በትንሹ መንግሥት ከወጪ መጋራት ያገኝ የነበረው ከስምንት ቢሊዮን ብር በላይ መመለስ እንዳልቻሉ ተገልጿል፡፡
ተማሪዎቹ የሚማሩት ትምህርት በመጀመሪያ ምርጫቸው ከሆነ የማለፍ ምጣኔያቸው ከፍተኛ መሆኑን ለአብነትም የጤና፣ የኢንጅነሪንግና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የማለፍ ምጣኔ ከፍተኛ እንደሆነ፣ በተቃራኒው የማኅበራዊ ሳይንስ፣ የቢዝነስና የትምህርት ፕሮግራም ተማሪዎች የማለፍ ምጣኔ ዝቅተኛ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
64 በመቶ የሚሆኑት የመውጫ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎች ሰርተፍኬት ስለሌላቸው በጊዜያዊነትም ሆነ በቋሚነት መቀጠር እንዳልቻሉ፣ በዚህ ምክንያት ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ መግባት በቤተሰብ፣ በአካባቢና በጓደኛ የማሸማቀቅ ሁኔታ በልጆቹ ላይ እንደሚደርስ፣ ከ94 በመቶ በላይ የሚሆኑት ደግሞ በቤተሰብ ላይ ጥገኛ እንዲሆኑ ምክንያት መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ጥናቱ በተመለከታቸው ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች በአብዛኛው ምንም ዓይነት የመውጫ ፈተና በሁሉም የትምህርት ፕሮግራሞች የመስጠት ሁኔታ እንደማይታይና ከዚያ ይልቅ በተመረጡ ፕሮግራሞች ላይ ብቻ ተግባራዊ አንደሚደረግ አቅራቢው አስረድተዋል፡፡
በመሆኑም ኢትዮጵያ ብቻ በሁሉም የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ የመውጫ ፈተና ተግባራዊ ማድረግ የጀመረች አገር መሆኗንና፣ ትምህርት ሚኒስቴርም ወደ እዚህ ሁኔታ የገባው ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተመርቀው የሚወጡ ተማሪዎች ለሥራ ቅጥር ብቁ ባለመሆናቸው፣ ይህን ያስከተለውን የትምህርት ጥራት ለማሻሻል ኃላፊነቱን በመውሰዱን ነው ብለዋል፡፡
6,ዐ3ዐ ተማሪዎች በጥናቱ መሳተፋቸውንና ከእነዚህ ውስጥ 1,38ዐ የሚሆኑት ከአንድ እስከ አምስት ጊዜ የወደቁ መሆናቸውን እንዲሁም 78 የመንግሥት እና የግል ተቋማት፣ 13 የመንግሥት እና ሰባት የግል፣ በአጠቃላይ 20 ዩኒቨርሲቲዎች በጥናቱ መካተታቸው ተገልጿል፡፡ #ሪፖርተር
@tikvahuniversity | 46 652 |
| 15 | Нет текста... | 37 653 |
| 16 | #ጥናት
በሀገር አቀፍ ደረጃ የተካሔደ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በሚያገኙት አገልግሎት የሚሰማቸው እርካታ ዝቅተኛ መሆኑን አሳየ፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት ከተለያዩ ተቋማት በተውጣጡ አጥኚዎች የተሠራው ጥናቱ፤ በ2017 እና በ2018 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በሚሰጡ አገልግሎቶች መምህራን፣ ተማሪዎች፣ የአስተዳደር ሠራተኞች እና ማህበረሰቡ ምን ያህል ደስተኛ ናቸው የሚለውን ለማወቅ ነው፡፡
በጥናቱ በ2017 ዓ..ም የተሻለ ደረጃ ላይ የነበሩ፣ በ2018 ዝቅ ማለታቸው የታየ ሲሆን፣ በተቃራኒው ባለፈው ዓመት ዝቅተኛ ደረጃ ላይ የነበሩት በዚህ ዓመት መሻሻል ማሳየታቸውን ጥናቱ ጠቁሟል፡፡
በጥናቱ 47ቱም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የተካተቱ ሲሆን፣ ከ16 ሺህ በላይ ተማሪዎች፣ ከ16 ሺህ በላይ መምህራን፣ ከ4 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ሠራተኞች እና 4 ሺህ የሚሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች (በአጠቃላይ 61,431 ሰዎች) በጥናቱ ውስጥ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የጥናቱ ዋና ዋና ትኩረቶች
● የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የአገልግሎት እርካታ
● የዩኒቨርሲቲ መምህራን አገልግሎት አሰጣጥ
● በዩኒቨርሲቲዎች የአስተዳደር ሠራተኞች እርካታ
● ዩኒቨርሲቲዎች በአካባቢው ማኅበረሰብ ዘንድ በሚሰጡት አገልግሎት እርካታ
ከ47ቱ ዩኒቨርሲቲዎች በተማሪዎች የአገልግሎት እርካታ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዝ፣ ኦዳ ቡልቱም እና ወልድያ ዩኒቨርሲቲዎች ተከታዮቹን ደረጃዎች አጊኝተዋል፡፡
በተቃራኒው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች አገልግሎት ደስተኛ አለመሆን ቀዳሚ ሲሆን፣ መቐለ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲዎች ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል፡፡
ሸገር ኤፍኤም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተ/ፕሬዝዳንትን ስለጥናቱ ግኝት የጠየቀ ሲሆን፣ "ለጊዜው መልስ መስጠት እንደማይችሉ" ነግረውታል፡፡
ከ47ቱ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል በመምህራን "የተሻለ አገልግሎት ይሰጣል" ተብሎ በጥናቱ በቀዳሚነት የተለየው ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ቀዳሚው ሲሆን፣ ቀብሪደሃር እና ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲዎች ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል፡፡
በእነዚህ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚያስተምሩ መምህራን ለመምህራን በሚሰጠው አገልግሎት ጥሩ እርካታ እንዳላቸው ጥናቱ ጠቅሷል፡፡
መቐለ ዩኒቨርሲቲ ዝቅተኛ የመምህራን እርካታ ያለበት ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ጥናቱ ያሳየ ሲሆን፣ ዋቸሞ እና ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲዎች ተከታዮቹን ደረጃዎች ይይዛሉ፡፡
በዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ሠራተኞች እርካታ ኦዳ ቡልቱም፣ ቀብሪደሃር እና ሰላሌ ዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ እርካታ የተመዘገበባቸው ሲሆኑ፤ መቐለ፣ ደብረ ማርቆስ እና መቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ ዝቅተኛ የአስተዳደር ሠራተኞች እርካታ የተጠቀሰባቸው ናቸው፡፡
ሐራማያ፣ ዓዲግራት እና ወልድያ ዩኒቨርሲቲዎች በአካባቢው ማኅበረሰብ ዘንድ በሚሰጡት አገልግሎት ከፍተኛ እርካታ ከተመዘገበባቸው መካከል ሲሆኑ፤ ዲላ፣ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እና ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በአካባቢው ማኅበረሰብ ዝቅተኛ የእርካታ ደረጃ ከተመዘገበባቸው መካከል ቀዳሚዎቹ መሆናቸውን ጥናቱ ጠቅሷል፡፡
ተማሪዎች በማደሪያ እና በመመገቢያ ስፍራዎች ላይ ከፍተኛ ቅሬታ እንዳላቸው የሚገልፀው ጥናቱ፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንም በደሞዝና ጥቅማ ጥቅም ደስተኛ እንዳልሆኑ ጥናቱ አመላክቷል፡፡ #ShegerFM
@tikvahuniversity | 42 659 |
| 17 | Нет текста... | 36 722 |
| 18 | የሴጅ አርቲስተሪ ፕሮጀክት ቀን
እሑድ ጳጉሜ 01/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 02:00 እስከ ምሽቱ 12፡00 ሰዓት
በሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በክረምቱ ለሁለት ወራት በፕሮግራሚንግ እና ኮዲንግ፣ በመሰረታዊ ኮምፒውተር እና ቋንቋ ትምህርቶች ሲሰለጥኑ የቆዩ ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ተማሪ ልጆች የመጨረሻ መመረቂያ ፕሮጀክታቸውን ያቀርባሉ።
የእነዚህን ተመራቂ ተማሪዎቻችንን የምረቃ ስራዎች በፒያሣ ኤልያና ሆቴል በሚገኝው ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ተገኝተው እንዲያዩ እና አስተያየትዎን እንዲያካፍሉን ጋብዘንዎታል።
የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ደራርቱ ህንፃ 5ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com
Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute | 38 753 |
| 19 | 🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ!
► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ
► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው
► የኮሪያ ሆስፒታል እህት ኩባንያ
15ኛ ዙር የህክምና ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን!
🎓 ኮሌጃችን ያስተማራቸውን ተማሪዎች በሙሉ የብቃት ምዘና ፈተና ማሳለፍ ችሏል!
ለማመልከት 👇
https://maps.app.goo.gl/oxRezU99L2DqnngD6
አድራሻ፦
አዲስ አባባ፣ ገርጂ ኮሪያ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ሬጅስትራር ቢሮ
የምዝገባ ጊዜ 👇
እስከ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ድረስ። አሁኑኑ ይመዝገቡ!
☎️ 0116395020
ድረ-ገጽ፦ www.mmc-edu.net
Facebook: https://web.facebook.com/MMCmedcollege/
#MyungsungMedicalCollege | 45 333 |
| 20 | የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግር በመጠናቀቁ አዲስ ፕሬዝዳንት ለመሾም የውድድር ማስታወቂያ በቅርቡ ይወጣል፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግር ጊዜው በማብቃቱ አዲስ ፕሬዝዳንት ለመሾም የሚያስችለውን የውድድር ማስታወቂያ ለማውጣት የመጨረሻ ዝግጅት ላይ እንደሚገኝ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ ለሸገር ኤፍኤም ተናግረዋል፡፡
የውድድር ማስታወቂያው በቅርብ ቀናት እንደሚወጣ ሚኒስትር ዴኤታው ገልፀዋል።
ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ከነሐሴ 24/2015 ዓ.ም ጀምሮ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡
በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ውሳኔ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ የሆነው ሐምሌ 28/ 2015 ዓ.ም እንደነበር አይዘነጋም፡፡
@tikvahuniversity | 57 803 |
