በክርስቶስ ( in christ)
رفتن به کانال در Telegram
በክርስቶስ ቴሌግራም ቻናል ውስጥ ክርስቶስ ማዕከል ያደረጉ መልዕክቶች ይተላለፋሉ ። @cgfsd
نمایش بیشتر1 640
مشترکین
-124 ساعت
-27 روز
+8630 روز
آرشیو پست ها
1 640
በድጋሚ እላለኹ፤
100 ዓመት ባልሞላ ዕድሜ፣ ከ15 ጊዜ በላይ አሰቃቂ የርስ በርስ ጦርነት አድርገናል። ታድያ እኛ ነን፣ "እግዚአብሔርን የምንፈራ" ሕዝቦች?!
ዲያቆን አቤኔዘር ተክሉ
@cgfsd
1 640
አብርሃም ባያውቀን፣
እስራኤልም ባያስታውሰን እንኳ፣
አንተ እኮ አባታችን ነህ፤
እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ አባታችን ነህ፤
ከጥንትም ቢሆን ስምህ “ቤዛችን” ነው።
ኢሳይያስ 63:16
1 640
በመሠረቱ ማንበብን ከክርስቲያኖች መካከል ማጥፋት ከባድ ይመስለኛል ። ለምን ? የእግዚአብሔር መገለጥ እንኳን የተሰጠን በታላቁ መጽሐፍ በኩል ነውና ። ሕዝበ እግዚአብሔር " የመጽሐፍ ሕዝብ" እንደ መባል ታሪኩና ሕይወቱ ከንባብ ጋር የተቆራኘ ነው ።
(ሰለሞን አበበ ገብረመድህን፣ የተቆረሱ ነፍሶች ገፅ 280)
1 640
+9
ሰሞን የእኛና የኢየሱስ ልጅነት ልጅነት ልዩነት አለው ወይስ እንዴት እንመልከተው የሚለው ። ረጅም ማብራሪያ
ከዶክተር ሳምሶን ጥላሁን
ብታነቡት ብዙ የምትጠቀሙት ጽሁፍ ነው ።
1 640
ጁስቲን የተባለ ሊቅ የንጽሕና ምልክቱ ምን እንደ ሆነ ሲያትት " የንጽህና ምልክቱ :- ከተደሰቱት ጋር መደሰት፣ ካዘኑት ጋር ማዘን ፣ ከታመሙት ጋር መታመም ፣ከኋጥአንም ጋር የኋጥያትን አስጨናቂነት እያሰቡ መጸጸት ፣ መከራን ከሚቀበሉት ጋር አብሮ መሳተፍ ፣ ማንንም ሰው አለመንቀፍ፣ እንዲሁም ፣ በራስ ንጹሕ አእምሮ ኹሉንም ሰው ፣ መልካምና ቅዱስ አድርጎ ማየት ነው ። " ይላል ።
ገፅ 21
(ዲ/ን ዩሐንስ ጌታቸው ፣ ኦርቶዶክሳዊ ነገረ ሥላሴ ፣ የመጀመሪያ ዕትም መጋቢት 2018
መንፈሳዊ ንጽህና ፣ የልብ ንጽህና ፣የህይወት ንጽህና ሀጢያት ከመስራት ካለመስራት ጋር ብቻ አይያያዝም ፤ አንዱ ነገር ቢሆንም እሱ ከዛ ባለፈ ደግሞ ከሌሎችም ጋር ያለን መተሳሰብ ነው ንጽህና ። ንጽህና ለራስ ንጹህ ሁኖ መቆም ብቻ አይደለም ። ሌሎች ጋር አብሮ ንጹህ ሁኖ መቆም ነው ። ከደከሙት ጋር መደጋገፍ ፣ ካዘኑት፣ ካለቀሱት ፣ ከተቸገሩት ጋር አብሮ ችግሮችን እየተጋሩ የሚኖር ሰው እሱ መጽሃፍ ቅዱሳዊ ንጹህ ።
1 640
ወጣቶች እንዲያነቡ 1 ሰው 2 መጽሃት ስጦታ ቢሰጠን 🤲 ። ተንቀሳቃሰ library ይኖረናል ። ለቸርች ወጣቶች ያላችሁን መጽሃፍ 🙏 አዲስ አበባ ያላችሁ በተለይ ። inbox @filicross
1 640
😁 ኢየሱስ ሳይመጣ ቶሎ ቶሎ ብለን bible challenge ጀምረን መፀሃፍ ቅዱሳችን እናብብ ማለት አንዱ እንጁን አውጥቶ ጌታ ሲመጣ ግን ጥቅስ ይጠይቀናል እንዴ? በአቤት ይሔ ትወልድ 😁😁
@cgfsd
1 640
ከቀዳሚ አንባቢያን መካከል👇
መጽሐፉን አንብቤ ጨርሻለሁ። የተፈጥሮ የጽሑፍ ክህሎት ያለው ደራሲ ነው። የቃላት አመራረጡ ለአንባቢው ስዕል ይስላል፣ ሁኔታውንም በቀላሉ በሕሊናህ እንዲታይ ያደርጋል። ደራሲውን በሥራው ላበረታታው እወዳለሁ፤ የተሰጠው እና ጥሩ comunicarse (ሀሳብ አስተላላፊ) በመሆኑም ጽሑፉን እንዲቀጥልበት ማበረታታት እፈልጋለሁ።
#አብሰክስከን
1 640
Repost from Bibliophagos
መቼስ መፅሐፍ መጻፍ እና ማሳተም ፅንስ ከመገላገል ያነሰ ደስታ አይኖረውም። ወንድማችን ፊሊሞን ነጋ(@ownkin)ጌታ ረድቶት የመጀመሪያ መፅሐፉን ሊያሳትም ነው ። በመፅሐፉም ላይ ደቀመዝሙርነት ፣ የመስቀል ማዕከልነት ፣ ለወንጌል ያለ መቃጠል እንዲሁም በርካታ ጠቃሚ ሀሳቦች በቆንጆ አማርኛ ተሞሽረው ቀርበዋል ። ፀሀፊው ለመፅሀፍ ቅዱስ ጥግት ያለ ፤ ጤናማ ስንመለኮትን የሚያራምድ ፤ ለቤተክርስቲያን ሸክም ያለው ፤ ተልዕኮ እና ደቀመዛሙርነት ጩኸቱ የሆነ ፤ በክርስቶስ መስቀል የተብሰከሰከ መልካም ምስክርነት ያለው አገልጋይ ነው ። በፀሎትም ሆነ በቻላችሁት ነገር ከአጠገቡ እንድትቆሙ እንዲሁም ለገቢያ በሚወጣበት ጊዜ መፅሐፋን በመግዛት እንድታተርፉ የአክብሮት ጥሪዬን አቀርባለው ።
1 640
''አብሰክስከን'' የሥነ-መለኮትን ጥልቀት ከእረኛዊ ልብ እና ርህራሄ ጋር አዋህዶ የያዘ፣ የወጣቱን ትውልድ መንፈሳዊ ጥማትና የቤተክርስቲያንን ወቅታዊ ጥሪ በትክክል የተረዳ ድንቅ ጥራዝ ነው። ወንድማችን ፊልሞን ነጋ ክርስቶስንና የመስቀሉን እውነት በማዕከልነት አቁሞ፣ ትውልዱ ከላይ ላይ መንፈሳዊነት ወጥቶ በጌታ ፊት እንዲብሰከሰክ ያቀረበው ጥሪ እጅግ ወቅታዊ ነው። እያንዳንዱ አማኝ፣ አገልጋይና የነገዋ ቤተክርስቲያን ተስፋ የሆነ ወጣት ሊያነበው የሚገባ ወቅታዊ የመንፈስ ቅዱስ ጥሪ ነው!"
እስራኤል ቴዎድሮስ
(የቃሉ አስተማሪ )
