በክርስቶስ ( in christ)
Відкрити в Telegram
በክርስቶስ ቴሌግራም ቻናል ውስጥ ክርስቶስ ማዕከል ያደረጉ መልዕክቶች ይተላለፋሉ ። @cgfsd
Показати більше1 553
Підписники
+324 години
+207 днів
+3630 день
Архів дописів
1 552
ክርስቶስን ጌታ አድርጋችሁ በልባችሁ ቀድሱት። እናንተ ስላላችሁ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ሁል ጊዜ የተዘጋጃችሁ ሁኑ፤ ነገር ግን ይህን ሁሉ በትሕትናና በአክብሮት አድርጉት፤
1 ጴጥሮስ 3:15
1 552
አስር ልጆቿንና ባሏን በጦርነት ያጣች የትግራይ እናት በአንድ ቪዲዮ ተመለከትኩ ፤ ሀዘኗን መቋቋም አቅቷት መናገር ስትቸገር። ምን ያህል ጦርነት አስከፊ እንደሆነ ፀያፍ ተግባር እንደሆነ ግልፅ ነው ። አሁንም የጦርነት ቅስቀሳ አለ እያሉ እናቶች ሲያለቅሱ ልጆቻቸውን ስደት ሲልኩ ማየት እጅግ ያማል። ትግራይ የመሄድ እድል ባይገጥመኝም እዛም ዘመድ ባይኖረኝም እንኳን ከጓደኞቻችን ፣ ከማህበራዊ ሚዲያ፣ በእየ ከተማው ተሰደው የሚመጡን ወጣቶችና አዛውንቶች ስይ ምን ያህል ጉዳዩ አስከፊ እንደሆነ መረዳት እችላለሁ።
ግን ለምን ? ከትናንት ስሕተቶች የማንማረው ይህን ህዝብ ልናፅናናው ከጎን ልንቆም ይገባል ። መፅናናት ያስፈልጋቸዋል! ስለ ሰው ለማዘን ለመጨነቅ የግድ ከእኛ ዘር ሀረግ መሆን የለበትም ለክርስቲያን ባልንጀራው ያገኘው የሰው ልጅ በጠቅላላ እንጂ የዘር ሀረጉ ብቻ አይደለም ።ጦርነት እንዲቆም ፣ እናቶችና አባቶች እንዲፅናኑ ፣ ልጆች በሰላም እንዲኖሩ የመፀለይ ግዴታ አለብን ። እግዚአብሔር ሆይ በቃ በለን 😭 ህዝብን አስብ ። እንፀልይ !😭😭
1 552
(አጭሩና ረጅሙ መዝጊያ)
በአዲስ ኪዳን መጽሐፍት መካከል ከፍተኛ ውዝግብ ከሚያስነሱ ክፍሎች መካከል የማርቆር ወንጌል መዝጊያ አንዱ ነው ። ክርክሩ የማርቆስ ወንጌል የሚያበቃው ምዕራፍ 16 ቁጥር 8 ላይ ነው ወይስ ምዕራፍ 16 ቁጥር 20 ላይ ነው ማለቂያው የሚል የቆየ የሙግት ሀሳብ አለ ። 16:8 የሚሉት አጭሩ መዝጊያ በመባል ሲጠሩ 16:20 ደግሞ ረጅሙ መዝጊያ በመባል ይታወቃሉ ።
አጭሩ መዝጊያ የሚያምኑ መነሻ የሆናቸው የተወሰኑ የድሮ የመፀሃፍ ቅዱስ ማንስክሪፕት ቅጂዎች ላይ እስከ ቁጥር ስምንት ድረስ ብቻ መገኘቱ ነው ። በተለይ ከ3ተኛና 4ተኛ ክፍለ ዘመን በኋላ በርካታ ቅጂዎች ይገኛሉ ፤ከእነዚህም ውስጥ ከአንድ ሺ ከሚበልጡ ቅጂ ውስጥ ሶስት ቅጂ ላይ የማርቆስ 16:8 ድረስ ብቻ ሲሆን ከቁጥር 9-20 አይገኝም ። እነዚህም ቅጂዎች :- ቫቲካነስ ኮዴክስና ሲናይቲከስ ኮዴክስ ይገኙበታል ። በእነዚህ ቅጂዎች ላይ የማርቆስ 16:8 በኋላ ያሉ ቁጥሮች የለም ። በአንድኛው ባዶ ቦታ በሌላኛው ተራርቆ በተፃፉ ፊደላት ምክኒያት ባዶ ቦታውን ወደ ሉቃስ ወንጌል የሚያስገባ መሸጋገሪያ በመሆን ተቀምጧል። በእነዚህ ክስተት ምክኒያት የማርቆስ ወንጌል 16:9-20 ያለው ሀሳብ የተጨመረ በቀድሞ ኦሪጂናል ጥቅቅል መፀሃፍ ውስጥ የለም የሚል መላምት መበራከት ቀጥሏል ። ከዛም ከቁጥር 9-20 ያለው ስነፅሁፋዊ ይዘቱም ከሌሎቹ ማርቆስ ወንጌል መፀሃፍ ጋር የተለየ ነው የሚል ውስጣዊ ሙግትም ይሰነዝራሉ ። ብለው አንዳንድ አስተምሮዎች ከ9-20 ያለው ከሙሉ የመፀሃፍ ቅዱስ ትምህርት እንደሚጋጭ ያምናሉ በተለይም መርዝ ብትጠጡ አይገላችሁም ፣ እባብ ብትጨብጡ የሚለው ጥቅስ በመምዘዝ ከክርስትና ትምህርት ይጋጫል የሚል እይታ አላቸው ፤ ነገር ግን ይህ እይታ ውሃ የማያነሳ ነው የሁልጊዜ አስገዳጅ ሁኖ አልቀረብም ፣ ከዛም ከተልዕኮ አንፃር የተጠቀሰም በመሆኑ ተአምራዊ መልክ ሊኖር እንደሚችል ማሰብ ያስፈልጋል ። ከዛም በመቀጠል በታሪካዊ ማስረጃ በመጥቀስ የቤተክርስቲያን ታሪክ አባት ተደርጎ በሚቆጠረው አውሳብዮስ የለም እንዳሉ በመጥቀስ ይነሳል አውሳብዮስ የማርቆስ 16:9-20 ያነሱት የተጨመረ ነው ከማለት አንፃር ሳይሆን ከሌሎች የወንጌላት መፀሃፍ ጋር ትንሳኤውን እንደማይጋጭ ግልፅ ከማድረግ አንፃር ነው ።
አጭሩ መዝጊያ 16:8 ልክ ያልሆነበት ሌላኛው አግባብ ማርቆስ ቁጥር 8 የጨረሰው ሆን ብሎ(intentionally ) የሚል ሀሳብ ያነሳሉ ( book from perspective on ending mark )። ይህ ሀሳብ አሳማኝ ሊሆን የሚችለው ከአንድ ነገር ጎን ብቻ ሊሆን ይችላል የማርቆስ ወንጌል አፃፃፍ ጥድፊያ የተሞላ እንደመሆኑ መጠን በቶሎ የማርቆስ ወንጌል ፀሃፍ ዘግተት ሊሆን ይችላል ። ምን አልባት እንደ አንድ ሙግት ነው ግን በቂ አይደለም ። ምክኒያቱም የማርቆስ ወንጌል ከጴጥሮስ ስብከት ተመሳሳይነት አለው በተለይም የሐዋሪያት ስራ ላይ ጴጥሮስ ለቆርነሌዎስ የሰበው ስብከት ውስጥ ማርቆስ ወንጌል ጋር የይዘት መመሳሰል ሊኖረው ይችላል ። እንደተባለው ማርቆስ ወንጌሉን ከጴጥሮስ ሰምቶ ወይም በጴጥሮስ ንድፍ ከፃፈ ፤ ጴጥሮስ ደግሞ በስብከቱ ውስጥ የክርስቶስ ትንሳኤ በተደጋጋሚ ያነሳል አልፎ ተርፎ አይን እማኝ እንደሆነ ግልፅ ነው ። ስለዚህ ከትንሳኤ በኋላ ያለው ክስተት ትዕዛዝ ሊነሳ ያስፈልጋል ። ከማርቆስ ወንጌል አመጣጥ አንፃር በጥድፊያ የተሞላና ስለማገልገል ሲነሳ ስለተመለከት በቀደሙት ምዕራፍ በመጨረሻው ላይ ተልዕኮን የሚያክል አደራ ያለበት የአገልግሎት ትዕዛዝ የማያሳይ ከሆነ አሁንም ከፅሁፍ ውስጣዊ ባህሪ አንፃር ይጋጫል ። በቁጥር ስምንት የሚያልቅ ከሆነ ትንሳኤውን እንደ መልካም ዜና ማየት ይከብዳል ምክኒያቱ በብዥታ ስለሚያልቅ ።
አሳማኝ የሆነው የማርቆስ መዝጊያ ረጅሙ ነው ። በቁጥር 20 የሚያልቀው ነው ። ከውስጣዊውም ፣ ከውጫዊም ፣ ከታሪካዊ ማስረጃ ብንመለከት አሳማኙ ረጅሙ መዝጊያ ነው ። በእርግጥ በሶስቱ ቅፆች ከቁጥር 8 በኋላ አለመገኘቱ ጥርጣሬ ቢያስነሳም በሌሎች በሺ የሚቆጠሩ መጣጥፎች ላይ መገኘቱ በርካታ መረጃ እንዳለ ያሳያል( እውነት ለሁሉ ገፅ የማርቆስ ወንጌል 16:9-20 ትክክለኝነት) ። በቤተክርስቲያን አባቶች ከሶስቱ ቅጂዎች በፊት ከቁጥር 9 እስከ 20 ያለው ጠቅሰው በማስተማራቸውና በመፃፋቸው ምን ያህል ማርቆስ 16:9-20 የመፀሃፍ ቅዱሳችን አካል እንደሆነ ማረጋገጫ ይሆናል ።
@cgfsd
1 552
ሐዋሪያው ጳውሎስ የክርስቶስን የፍቅር ጥልቀት ፣ ስፋት፣ ርዝመት ተናግሮ ከመታወቅ ያልፋል እያለ ይሔን ታላቅ ፍቅር ለማወቅ መንገዱ ብሎ የሚጠቁመው መንገድ አብረን፣ በጋራ በአንድነት፣ በህብረት፣ የቅዱሳን አንድነት ይላል። ፍቅሩን ታላቅ ነው ብሎ በግላዊ መንገድ ብቻ እንድንለማመደው አይጠቁመንም በጋራ በህብረት ይለናል ። ፍቅር በራሱ ግላዊነት አይታይበትም ። ሰው ብቻውን መሸከም የማይችለው ከእሱ የከበደ ሽክም ቢገጥመው ብቻውን አይሸከምም ይልቅ ሸክሙን የሚያግዘው ሌላ ሰው ይፈልጋል አብሮት እንዲሸከም ያደርጋል ፤ የእግዚአብሔር ፍቅር ከእኛ አቅም በላይ በመሆኑ መፍትሔው በጋራ ለማወቅ መጣጣር ነው ፣ በጋራም ቢታወቅ አይደለም ነገር ግን በመያያዝ ውስጥ ፍቅሩን ማጣጣም ስለሚኖር ነው ።
የእግዚአብሔርን ፍቅር በትክክል ለመለማመድ ትክክለኛ ቦታ ለጳውሎስ በጋራ አብረን እንጂ ለብቻ አያወጣም። ይሔ ፍቅር በስላሴ መካከል የነበር ነው ። በአብ በወልድ ፣ በመንፈስ ቅዱስ መካከል የነበረ የህብረት ግንኙነት ነው ። በስላሴ መካከል ያየነው ፍቅር በራሱ ህብረታዊነት አለበት ። ስለዚህ የእግዚአብሔርን ፍቅር ለመለማመድ ትክክለኛው ስፍራ ህብረት ነው ።
አስቴር አበበ በአንድ የመዝሙር Track ላይ እግዚአብሔር ፍቅር ነው የሚል ሀሳብ ትዘምራለች ነገር ግን የእግዚአብሔርን ፍቅር የምታብራራው በአማኞች የህብረት ህይወት ውስጥ ያለ የምንለማመመደው ጉዳይ የእርስ በእርስ ግንኙነታችን አድርጋ ነው ። እግዚአብሔር ፍቅር ነው በማለት እንዲህ ትላለች
"የሌላውን እርቃን ተባብረን ስንሸፍን
ሞገስ አለ ከላይ የሚለቀቅልን በመያያዛችን
ፍቅር ነው ፍቅር እግዚአብሔር ፍቅር
እኛም ተጠርተናል እሱን እንድንመስል
የክርስቶስ ፍቅር ስፋቱ፣ ርዝመቱ፣ ከፍታውና ጥልቀቱ ምን ያህል እንደሆነ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር የመገንዘብ ኀይልን እንድታገኙ ነው።
ኤፌሶን 3:18
@cgfsd
1 552
እፍራው ወይስ እንውደደው?
በተደጋጋሚ ሲነገር የምንሰማው ትምህርተ ስላሴ ከባድ እንደሆነ ነው ። እርግጥ ነው በሰው መረዳት ልክ የሆነ አይደለም ። ስለ ስላሴ የሚነገር አባባል አለ " ስላሴን በሙላት ማወቅ አይምሮን ያሳጣል ስላሴን አለማወቅ ደግሞ ህይወት ያሳጣል " ። ስላሴን ተረድተነው የማንጨርሰው ቢሆንም ለመረዳት ፣ ለማወቅ ፣ ለመገንዘብ ከመፈለግ ወደኋላ ማለት የለብንም ። የስላሴን ትምህርት ውስብስ ብቻ እያደረግነው ከሄድን ትምህርቱን እየፈራነው ከአክብሮት ፍርሃት ይልቅ የዕውቀት መራቀቅ ብቻ እያደረግነው እንሄዳለን ። ይልቅ ከአክብሮት አንፃር እየፈራነው የስላሴን አስተምሮውን መውደድ ያስፈልጋል። ብዙ ሰው ጋር ስላሴ ትምህርት ከባድ የሚለው አስተሳሰሰብ ስላሴን ለማወቅ ፍላጎት እንዳይኖር እያደረገ ይገኛል። የስላሴን ትምህርት መፍራት ያለብን ከአክብሮት አንፃር እንጂ ከማወቅ ወይም ለማወቅ ከመፈለግ መሆን የለበትም። የስላሴን አስተምሮ መወደድ ያሻናል ።
@cgfsd
1 552
#የናዝሬቱ
ኢየሱስ ምን ያህል የሰው ልጅ ወገን እንደሆነ ከሚያስረዱን መጠሪያዎቹ መካከል የናዝሬቱ ኢየሱስ እየተባለ የተጠራበት መጠሪያ ነው ። የናዝሬቱ ኢየሱስ ማለት የተለየ በማዕረግ የሚገኝ ስም አይነት አይደለም ። የአንድ የአካባቢ መንደር መጠሪያ ነው። የናዝሬቱ ኢየሱስ ሲባል በአካባቢ ስም መለያ ተደርጎ እየተጠራ ነው ። ምሳሌ ጳውሎስ የጠርሴስ ሰው ነው ፤ የጠርሴሱ ሳውል ቢባል በአካባቢው ስም ለመለያነት ከሌሎች ስም እየተለየበት ነው ። ናዝሬት ኢየሱስ ያደገበት መንደር በመሆኑ በዛው ስም መለያ ተደረጎ ተሰጠው ። በአካባቢው ስም እንደ መለያ ሲጠራ ይሔም የሚያሳየው ምን ያህል ወደ ሰው አለም እንደቀረበ ፤ የሰው ወገን በምን ያህል እንደሆነ ነው ። በሰው ቋንቋ ፣ በሰው አኗኗር ፣ በሰው መንደር ፣ በፍፁም ሰውነት ሲገለጥ ሲጠራ የሰው ልጅ ወገንና እንደ ኾነ ምስክርነቱ ነው ። የናዝሬቱ ኢየሱስ
1 552
በማህበራዊ ሚዲያ ያየነው ክስተት ነበር ። አንድ በሌላ ቤተ-እምነት ያለ ሰው ወደ አንድ ከተማ በመሄድ የወንጌል ስርጭት የወጡትን ጥያቄ ይጠይቃል ከዛም መሃል አንዷ እንደዚህ በማለት መለሰች ። " ክርስቶስ ስንት ባህሪ አለው ? እሷም መልሳ " በእርግጥ ብዙ ባህሪ አለው" ..ብላ መዘርዘር .......አንድ ገጠር በመሄድ ወንጌል የሚሰብክ ወዳጃችን እንደነገረን ቤተክርስቲያን ውስጥ ስላሴን አብራሩ ሲባሉ ' ሶስት ክርስቶስ' እያሉ ማብራሪያ ይሰጣሉ። ታዲያ እንደ ወንጌላዊያን አማኞች ዶክትሪን መማር ያለብን አይመስላችሁም ? ፍትህ ለንፁህ ዶክትሪን✊
1 552
በመሪነት አገልግሎት ያለ አንድ ወንድም ነበር ፤ እሱም ሰፋ ያለን ሰአት ወስዶ በተደጋጋሚ ሲፀልይና የእግዚአብሔር ቃል ያጠናል። እኛም ከተለማመድነው የፀሎት የበለጠ ረዘም ያለ ሰአት የሚወስድ የፀሎት ልምምድ እንዳለው አስተውለን። ምንድን ነው ዋነኛ የፀሎት ትጋትህ ምክኒያት ? ብለን ስጠይቀው እንዲህ መለሰልን " የምመራው ይህ ህዝብ እግዚአብሔር ማን ነው ? ብሎ ቢጠይቀ ምን ብዬ መልሳለሁ ? መልስ እንዳይታጣብኝ ነው ።
@cgfsd
1 552
Problem of evil እከይ ወይም በምድር ላይ ሆነ በህይወታችን ላይ የሚመጥብን ክፉ ነገሮች እንደ ሰውም እንደ ምድር ላይ ነዋሪም ለምን የሚል ጥያቄ እናነሳለን ( የህመም ጉዳዩች ፣ የተፈጥሮ አደጋ ፣ ሞት ፣ ስቃይ ፣ ጭካኔ ...ብዙ ብዙ )። የማቴዎስ ወንጌል በተራራው ስብከት ላይ problem of evil ለምን እንደዚህ ሆነ ብሎ ከማብራራት ይልቅ መፍትሔው ላይ ትኩረት ያደርጋል ። መፍትሔውም የእግዚአብሔር መንግስት መገለጥ ነው ይለናል ። የእግዚአብሔር መንግስት መገለጥ ደግሞ እንደ ማቴዎስ ወንጌል ሁለት አይነት መልክ አለው ። የመጣና የሚመጣ መንግስት ነው ። የእግዚአብሔር መንግስት መጥቷል ንጉሱ መሲህ በመምጣቱ አገዛዙ መንግስቱ በዚህ ምድር ይፋዊ በሆነ መንገድ መጥቷል፤ ደግሞ ንጉሱ ክርስቶስ ኢየሱስ በዳግም መምጣቱ ሁሉን ሊገዛ ይመጣል መንግስቱም በፍፅምና ይመጣል ። የእግዚአብሔር መንግስት የመጣና የሚመጣ ነው ።
በአሁን በመምጣቱ ለሰው መንፈሳዊ ነፃነት በመስጠት ፣ የህይወት ለወጥ በማድረግ ፣ የጨለማው መንግስትን በመግለጥ፣ እውነተኛ ሰላም በማቀናጀት ፣ ፅድቅ በቤተክርስቲያን በኩል ለአለም በማስተዋወቅ፣ በማፅናናት ፣ ፍቅር በመስጠት problem of evil እየገለጠና አቅም እያሳጣ አለ ። በሙላት ሲመጣ ደግሞ ክፋት ፈፅሞ ይጠፋል ይደመሰሳል ። ያኔ መልስ ያጣንለት ለምን እንደዚህ ሆነ እየተባለ የሚነሱ የለምን ጥያቄ በመንግስቱ በሙላት መገለጥ ውስጥ ግሩም መልስ ያገኛል ። የእግዚአብሔር መንግስት አሁን በመካከላችን መኖሩ በመገኘቱ በማፅናናትና ህይወትን በማካፈል መልስ እየሰጠን ሲሆን በሙላት ወደፊት መምጣቱ ደግሞ ፈፅሞ መልስ ይሰጠናል ። መፍትሔው የእግዚአብሔር መንግስት ነው ።
@cgfsd
1 552
የእግዚአብሔር መንፈስ መፀሃፍ ላይ የተወሰነ እይታ
የእግዚአብሔር መንፈስ የተሰኘው መፀሃፍ በተገኝ ሙሉጌታ የተፃፈ ነው ። መፀሃፉ የሚያጠነጥነው ነገረ መንፈስ ቅዱስ በዘመናት ውስጥ ያለው ምልከታ ያስረዳል። መፀሃፋ ታሪካዊ ነገረ መንፈስ ቅዱስ በመሆኑ ሚዛናዊነት ለየትኛው ቤተ-እምነት የማዳላት አዝማሚያ አይታይበት ። ይህም የመፀሃፉ ጥሩ ጉን ተደርጎ መወሰደ ይገባዋል። በልፋት እንደተሰራ ሰፊ ዝግጅት ለመኖሩ አቀራረቡና ብዛትና ወገንተኝነት የሌላቸው ዋቢ መፃሕፍት ብዛት ያስታውቃል ።
መፀሃፉ ነገረ መንፈስ ቅዱስ ላይ የተነሱን ጥያቄዎችና ሙግቶችን በማንሳት ይጀምራል ከዛም መፀሃፍ ቅዱሳዊ ነገረ መንፈስ ቅዱሳዊ እይታ በብሉይም ሆነ በአዲስ ኪዳን ያሉት ያብብራራል ። በብሉይ ኪዳንና በአዲስ ኪዳን መካከል የነበረውን የሁለተኛ ቤተመቅደስ ዘመን በማንሳት የቁምራን ማህበረስብ ፣ ጁዲዝም ምልከታን ፣ ሙት ባህር ጥቅልል በማንሳት የአዲስ ኪዳን ዘመን ይሻገራል ይሔ የተሻለ ታሪካዊ እውነት እንዲኖረን መሰረት ይጥላል ። የአዲስ ኪዳን መፀሃፍት ለማብራራት ከተመሳሳይ ወንጌል ሲነሳ ከማርቆስ ወንጌል በመነሳት (markan priority ) የተጠቀመ ሲሆን በመቀጠል ከዩሀንስ ወንጌል በፊት luke-act መጠቀሙ ሉቃስ የታሪክ ሰው ብቻ ነው ወይስ ስነመለኮትም የሚለውን ክርክር ሳያነሳ በተሻለ የወጥነት ምልከታ እንድናይ ያግዛል ። ሐዋሪያት ስራን ከታሪክ መፀሃፍ ባለፈ መንፈስ ቅዱስ በተልዕኮ መነፀር ለማየት ይጋብዛል ።
የመፀሃፍ ቅዱስ ማብራራቱን ወደ አበው ዘመን በመሻገር የቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ የነበሩን ነገረ መንፈስ ቅዱሳዊ ምልከታዎችን ፣ ኑፋቄዎች ረጅም ሽፋን ይሰጠዋል ። ይህ ደግሞ የአበው ዘመን ላይ binary መልክ አለ ወይ ለሚለው መስመር የወጣ ጥያቄ የተሻለ ሀሳቦችን በማጥራት ለሚነሱ ውዝግ ለስለስ ያለ ግልፅነት ያስጨብጣል ። የምስራቁንና የምዕራቡ ቤተክርስቲያን ልዩነት በግልፅ ማነፃፀሩ ትኩረት ከየት መጀመር እንዳለበት ለማሳየት ጥሯል ከተግባራዊ ህይወት አንፃር። ከዛሞ የተሐድሶን ዘመን በመምጣት በሉተር ፣ ዝዌንጊሊ ፣ ካልቪን በኩል የተነሳውን የነገረ መንፈስ ቅዱስ በንፅፅር ከቤተክርስቲያን ዘመን ያስቀምጠዋል ።ድህረ ዘመናዊነት ዘመን ድረስ ያሉትን የአብርሆት አስተሳሰቦችን ምን አይነት ጫና እንዳላቸው ይጠቁመናል ።
የጴንጤቆስጣዊያን ታሪክና ተፅዕኖ በስርአት ከተደገፉ ማስረጃዎችና ለብቻተው አንድ ምዕራፍ በመስጠት በሌሎች ቤተ-እምነት የመጣውን ተፅዕኖ አለማቀፋዊ ይዘት ይሰጠዋል ። በተለይም የጴንጤቆስጤዊነትና ካሪዝማቲክስ እንቅስቃሴን ድንበር በማበጀት ለየብቻ ይተነትናቸዋል ፤ የሁለቱ ይዘትና ቅርፅ በብዙዎች ግርታትን የሚጭር መሆኑ ገለፃ መደረጉ ትልቅ አስተዋፆን ያመጣል ። የካርዝማቲክስ እንቅስቃሴ ለኢኩሚኒካል አንድነት ያደረገውን በረከት
(ካቶሊክ፣አንግሊካን ፣ ሉትራን) መጠቀሱ የመፍትሔው አካል ያረገዋል ።
የአፍሪካን ነገረ መንፈስ ቅዱስ መልካቸው እንዴት እንዲህ ሊመጡ እንደቻለ በተቻለ መጠን ለማብራራት መሞከሩ በልዩነት የራሳችን መልክ እንድገነዘብ የሚያስችል ነው ። ከፍረጃና ከእውነታ ከራቀ ሃሳባዊ ከመሆን ምን ላይ ነበረን የሚለውን በአፍሪካዊ ነገረ መንፈስ ቅዱስ እውነታ ውስጥ ያስገነዝበናል ። ምንስ መስራት እንዳለብን ይጠቁማል!ድህረ ዘመናዊነት ይዞብን የተደቀነውን ዘመናዊውን ነገረ መንፈስ ቅዱስ ከታሪካዊውና ከመፀሃፍ ቅዱሳዊ ነገረ መንፈስ ቅዱስ ከባህል ጋር አጣጥመን አውዳዊ እናርገው የሚል የተሰራውን እንጠብቅ ደግሞ እንስራ የሚል ሸክም ያለበት ጥሪ ያቀርብልናል ።
በተለይም መንፈስ ቅዱስ ከፀጋ ስጦታ ፣ ከልምምድ ፣ ከዶክትሪን ፣ በቤተክርስቲያን ሲገደብ በመፀሃፉ ስለማህበራዊ ፍትህ፣ ስለድሆችም ጭምር ነው በማለት ይሞግታል ። መንፈስ ቅዱስ ለማህበረሰቡ በፍትህ ፣ በርህራሄ ይደርሳል (public sprit) በማለት ቤተ-እምነታዊ ባለፈ ለሁሉ የተገባ እንደሆነ ይሞግተናል ። ቀጥሎም ከፍጥረት ጋር ያለው ግንኙነት በማንሳት በዓለም የሚያገባው በስራ ላይ ያለም ነው የሚል የሰፋን እይታ ይጭርናል ። መፀሃፉ የቤት-ስራ ሰጥቶን የሚያጠናቅቀው ። ነገረ መንፈስ ቅዱስ ያልሰራነው ብዙ ጎኖች እንደሆኑ ይነግረናል ። እንደ ምክረ ሀሳብ ያቀረበልንም ጉዳይ ለዘመናዊ አሁናዊ አለም መፍትሔው ነገረ መንፈስ ቅዱስ ነው ። እንዲሁም የአንድነት ድምፅ ይዞ ልንሰራው የሚገባው ግልፅ ስራ እንደሚያሻን በመጠቆም ያጠናቅቃል።
የተወሰኑ ቢሻሻሉ የምላቸው ትንሽ እይታዎቼ የመፀሃፉ ፎንት ከተለመደው የተለቀ ይመስላል ምቾት አይሰጥም ፣ የቤተክርስቲያን ታሪክ ተነስቶ የተብራራት መንገድ ግሩም ነው ነገር ግን ስርፀት የመሰለ የምስራቁንና የምዕራቡን ቤተክርስቲያን መካከል አንገብጋቢ ጉዳይ ሰፋ ያለ ሽፋንና የሙግት ነጥቦች ከዚህ በላይ ቢጨመርበት ፣ ታሪካዊ ነገረ መንፈስ ቅዱስ ሀሳቦችን እይታ ተኮር ገለፃ ከሚደረግ ሙግታዊ በሆነ መንገድ ትረካው ቢደገፍ አንባቢውን ከዚህ በበለጠ ለፍለጋ ያነሳሳዋል ፣ contemporary ስራ ላይ የነበሩን አለም አቀፋዊ ክፍተቶች ከመስመር የወጡን ነገረ መንፈስ ቅዱሳዊ ስራዎች ታሪካዊ እንደመሆኑ ቢነሱ ለምሳሌ ጀምስ ደን በተደጋጋሚ እንደ ዋቢ ተጠቅሷል ነገር ግን አንዳንዱ የእሱን እይታዎች ለአንባቢ ቢቀመጥ ታሪካዊ ሚዛን ይጠበቃል አንባቢውም ይጠበቃል ።
ለቤተክርስቲያን ጠቃሚ የሆነ ስራ እንደሆነ ምንም ጥርጥር የለውም ። በተገኘበት ይነበብ !
@cgfsd
1 552
ተመሳሳይ ወንጌላትን(ማቴዎስ፣ ማርቆስና ሉቃስ) ስናነብ ወይም ስናጠና አንዱን የወንጌል መፀሃፍ ከሌላው ጋር በማስተያየት ማንበብ ወይም ማጥናት ጥሩ አማራጭ ሊሆን ይችላል ። በሶስቱ ወንጌላት ውስጥ የታሪክ ፣ የአተራረክ፣ የተአምራት ፣ የትምህርት መመሳሰል ይታይባቸዋል ።በስፋት የሚታመነው ማቴዎስ ወንጌል በመመልከት መነሻ በማድረግ ማርቆስና ማቴዎስ እንደፃፉት ይናገራሉ ፤ ሌሎች ደግሞ የማርቆስ ወንጌል ቀደም ተብሎ ተፅፎ ማቴዎስና ሉቃስ አንደመነሻ እንደተጠቀሙበት ይናገራሉ ። ይሔ የሚያሳየው መለያየትም ቢኖር በተመሳሳይ ወንጌላት ላይ የመሳሳል ይዘት እንዳለ ነው። የተፃፉበት አፃፃፍ መንገድ ቢለያይም እንኳን ተመሳሳይነት አላቸው ። ስለዚህ ወንጌላት በስርአት በጥልቀት ለማንበብና ለማጥናት ስንነሳ የተመሳሳይ ወንጌላትን መፀሃፍት እርስ በእርስ እያመሳከሩ ማንበብ በጣም ወሳኝ መንገድ ነው ። የመፀሃፍ ቅዱሱ የመጀመሪያው ኮመንተሪ ራሱ መፀሃፍ ቅዱስ የሚባለው ለዚህ ነው ።
@cgfsd
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
