በክርስቶስ ( in christ)
Відкрити в Telegram
በክርስቶስ ቴሌግራም ቻናል ውስጥ ክርስቶስ ማዕከል ያደረጉ መልዕክቶች ይተላለፋሉ ። @cgfsd
Показати більше1 564
Підписники
Немає даних24 години
+47 днів
+330 день
Архів дописів
1 564
Repost from በክርስቶስ ( in christ)
ቅዱስ ማቴዎስ እንደሚነግረኝ ጌታዬ ኢየሱስ ከመወለዱ ጀምሮ በኃያላን ሊቀላ የሚፈለግ ስደተኛ ተፈናቃይ ሕጻን ነበር። ከተፈናቀለበት ሲመለስም ወደቤቱ ሊመለስ ስላልቻለ በናዝሬት አደገ። በውሃ ተጠምቆ ሲወጣ ከሰማይ የተወደደ ልጅ መሆኑ ቢነገርለትም በገዛ ቀየው የተገፋ ማስጠንቀቂያው ትምህርቱ ልምምዱ ሁሉ ብዙ ንትርክ የሚያስነሳበት ዓይነት ነበር። ስልጣን አልነበረውም የሚያደርገውን ሁሉ በምን ስልጣን እንደሚያደርግ ማብራራት ይጠበቅበት ነበር። የሚበላውን ሌሎች የሚሰጡት ድኻ ነበር።
እርሱ ግን ለማስረዳት በሚከብድ ኃይል የተሞላ ነበር። በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ ወደምድረበዳ ሄዶ ለአርባ ቀናት ተርቦና ተጠምቶ፣ በሰይጣን ተፈትኖ ይመጣል። ሕሙማንን ሲነካ ይፈወሳሉ አጋንንት በፊቱ ይርዳሉ። እውነትም ኃያል በማለት የመጥምቁ ዮሐንስን ምስክርነት ለማጽናት እገደዳለሁ። ከማቴዎስ ገጾች ላይ ብቅ የሚለው በስደት የሚኖረው ተፈናቃዩና ጎዳና አዳሪው ኢየሱስ በአንዳች ኃይል የተሞላ የተስፋ ገንቦ ሆኖነው።
ብጹዕ ሆኖ በመንፈሱ ድኻ የመንግሥተ ሰማያት የእርሱ የሆነ የሚገባ ሌሎችን የሚያስገባ ድኻ የሚያዝን የሚጽናናና ሌሎችን አልቃሾች የሚያጽናና። የዋሕ በመስቀሉ ሞት ምድርን የሚወርስ ቀሊል ቀንበሩን ሌሎች ላይ አድርጎ ራሳቸውን ወደመካድ የሚመራ ልዝብ ልስልስ መሪ ዓለምን የሚያንበረክክ ጽኑ ፍቅር። ጽድቅን የሚራብ የሚጠማ የሞቱን ጽዋ ጨልጦ የራሱን ብቻ ሳይሆን የሌሎችን የጽድቅ ረሃብ የሚያረካ። ምህረትን የሚያደርግ ለጠላቶቹ የሚሞት በእግዚአብሔር አብ የትንሳዔን ምህረት የሚያገኝ፣ የትንሳዔን ምህረት የሚያስገኝ።ሰላምን የሚያወርድ ጨቋኞቹ እየሰቀሉት የሚመሰክሩለት እውነትም ይኽ ሰው የእግዚአብሔር ልጅ ነበር ማቴ27፥54 ። ስለጽድቅ ብሎ የተሰደደ ባለመንግሥት። እኔ ደካማዋ ላይ በረከትህ ይውረድብኝ ጌታዬ!
✍ ሳራ ከድር
1 564
ቅዱስ ማቴዎስ እንደሚነግረኝ ጌታዬ ኢየሱስ ከመወለዱ ጀምሮ በኃያላን ሊቀላ የሚፈለግ ስደተኛ ተፈናቃይ ሕጻን ነበር። ከተፈናቀለበት ሲመለስም ወደቤቱ ሊመለስ ስላልቻለ በናዝሬት አደገ። በውሃ ተጠምቆ ሲወጣ ከሰማይ የተወደደ ልጅ መሆኑ ቢነገርለትም በገዛ ቀየው የተገፋ ማስጠንቀቂያው ትምህርቱ ልምምዱ ሁሉ ብዙ ንትርክ የሚያስነሳበት ዓይነት ነበር። ስልጣን አልነበረውም የሚያደርገውን ሁሉ በምን ስልጣን እንደሚያደርግ ማብራራት ይጠበቅበት ነበር። የሚበላውን ሌሎች የሚሰጡት ድኻ ነበር።
እርሱ ግን ለማስረዳት በሚከብድ ኃይል የተሞላ ነበር። በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ ወደምድረበዳ ሄዶ ለአርባ ቀናት ተርቦና ተጠምቶ፣ በሰይጣን ተፈትኖ ይመጣል። ሕሙማንን ሲነካ ይፈወሳሉ አጋንንት በፊቱ ይርዳሉ። እውነትም ኃያል በማለት የመጥምቁ ዮሐንስን ምስክርነት ለማጽናት እገደዳለሁ። ከማቴዎስ ገጾች ላይ ብቅ የሚለው በስደት የሚኖረው ተፈናቃዩና ጎዳና አዳሪው ኢየሱስ በአንዳች ኃይል የተሞላ የተስፋ ገንቦ ሆኖነው።
ብጹዕ ሆኖ በመንፈሱ ድኻ የመንግሥተ ሰማያት የእርሱ የሆነ የሚገባ ሌሎችን የሚያስገባ ድኻ የሚያዝን የሚጽናናና ሌሎችን አልቃሾች የሚያጽናና። የዋሕ በመስቀሉ ሞት ምድርን የሚወርስ ቀሊል ቀንበሩን ሌሎች ላይ አድርጎ ራሳቸውን ወደመካድ የሚመራ ልዝብ ልስልስ መሪ ዓለምን የሚያንበረክክ ጽኑ ፍቅር። ጽድቅን የሚራብ የሚጠማ የሞቱን ጽዋ ጨልጦ የራሱን ብቻ ሳይሆን የሌሎችን የጽድቅ ረሃብ የሚያረካ። ምህረትን የሚያደርግ ለጠላቶቹ የሚሞት በእግዚአብሔር አብ የትንሳዔን ምህረት የሚያገኝ፣ የትንሳዔን ምህረት የሚያስገኝ።ሰላምን የሚያወርድ ጨቋኞቹ እየሰቀሉት የሚመሰክሩለት እውነትም ይኽ ሰው የእግዚአብሔር ልጅ ነበር ማቴ27፥54 ። ስለጽድቅ ብሎ የተሰደደ ባለመንግሥት። እኔ ደካማዋ ላይ በረከትህ ይውረድብኝ ጌታዬ!
✍ ሳራ ከድር
1 564
(የማቴዎስ ወንጌሉ ኢየሱስ)
በማቴዎስ ወንጌል መፅሃፍ ላይ የኢየሱስ ታሪክ ከእስራኤላዊያን ታሪክ ይመሳሰላል ። የኢየሱስ ታሪክ የሚተርከው የእስራኤላዊያን ታሪክ እያየ ይመስላል ። ለምሳሌ በአሜሪካን ታሪክ ውስጥ አብርሃም ሊንከንና ኬነዲ የሚባሉ ፕሬዝዳንቶች ነበር ። በሁለቱ ፕሬዝዳቶች መካከል መቶ አመት ልዩነት ነበር ። 100 አመት ልዩነት ቢመስልም የታሪክ መሳሳል አላቸው ። ፕሬዝዳንት የሆኑበት መንገድ ፣ አመራራቸው ፣ የሞቱበት መንገድ ብቻ ብዙ ነገራቸው ተመሳሳይነት አለው ። አንዱ ፕሬዝዳት አንዱን እየደገመው ይመስል ነበር ።
የኢየሱስ ታሪክ ከእስራኤል ህዝብ ጋር ተመሳሳይነት በማቴዎስ ወንጌል ። የእስራኤል ታሪክ ጅማሬ አብርሃም እንደነበር ይታወቃል ኢየሱስ የአብርሃም ልጅ ተብሎ ተጠርቷል(ማቴ1:1) ። ኢየሱስ ሲወለድ የተጠራበት ስም አማኑኤል (ማቴ1:23) ትርጉሙ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንደማለት ሲሆን ይሔ መጠሪያ ከእስራኤላዊያን መቅደስ ጋር ይመሳሰላል ፤ ምክኒያቱም በመቅደሱ እግዚአብሔር እንደ ህዝብ አብሮአቸው እንዳለ ይናገር ስለነበር ። ኢየሱስ እንደተወለደ በስደት ወደ ግብፅ ቤተሰቡ ሄዱ (ማቴ2:13) እስራኤላዊያን እንደ ህዝብ ወደ ግብፅ ዮሴፍን ጋር ያዕቆብ እየመራቸው ሄዱ በዛም ኖሩ ።
ኢየሱስ ከግብፅ ስደት ከቤተሰቡ ጋር ተመለሰ (ማቴ2:14-15) ፣ እስራኤላዊያንም 430 አመት በኋላ ከግብፅ ወጡ ። ኢየሱስ አገልግሎቱን ሲጀምር በመጥምቁ ዩሀንስ ተጠመቀ (ማቴ 3:13-17) እስራኤላዊያን ከግብፅ ሲወጡ በደረቅ መሬት በመሻገር ተጠመቁ (1ቆሮ10) ፣ ኢየሱስ አገልግሎቱን ከመጀመሩ በፊት 40ቀንና ሌሊት በምድረበዳ ቆየ(ማቴ3:1-14) እስራኤላውያን ከግብፅ ከወጡ በኋላ 40 አመት በምድረበዳ እየተጓዙ ቆዩ ፣ ኢየሱስ በምድረበዳ ቆይተታው መላዕክት ያገለግሉት ነበር(ማቴ3:11) እስራኤላዊያን በምድረበዳ ቆይታቸው መላዕክት ህጉ ሲሰጣቸው ሲመሯቸው ነበር ። ኢየሱስ ተራራ ላይ መወጥት የተራራው ስብከት የተባለው ትምህርት በማስተማር የህይወት መርህ አስተዋወወቀ (ማቴ5-7) ሙሴ ተራራ ላይ ለእስራኤላውያን የኪዳኑን መርህ ህግ በተራራው ላይ ተቀበለ ።
ይሔ የኢየሱስና የእስራኤል ታሪክ እያመሳሰለ ማቴዎስ የሚፅፍልን ምክኒያት መልዕክቱ ለእስራኤል የተፃፈ ለለነበር ። በእስራኤል ኪዳን እንዳለ ይታመን ስለነበር፤ ኢየሱስ ደግሞ ኪዳን የሚሰጥ አዲሱ ድነት ህይወት ያለበት እስራኤል እሱ ይለናል የማቴዎስ ወንጌል ፀሀፊ ።
1 564
ክርስትና መቃጠልም መረጋጋትም ነው ። ለጌታ ፍቅር መብሰክሰክ ፤ ለጌታ ፍቅር መስከን ። የጌታ ፍቅር ያቃጥላልም ያረጋጋልም ፣ ያብሰከስካልም ያሰክናልም ። አንድ ጎን ብቻ አይደለም ። ሁለቱም ጎን አስፈላጊ ናቸው ። ካልተብሰከሰከ ሰው በሃይል የመኖር አቅም አይኖረውም ፣ ካልሰከነ ደግሞ በማስተዋል መኖር አይችልም ። እያብሰከሰክ አስክነን፤ እያሰከን አብሰክስከን !
1 564
ኢየሱስ መክበር በሞቱ ብቻ አይደለም ፤ ይብሱንም መክበሩ ለሞቱ አዲስ ትርጓሜ ሰጠው ።
Death and blood inchrist Heavenly offering
@cgfsd
1 564
አማኞች ሆይ፣
ስለ እምነት ግድ የሚላችሁ ከሆነ ማድረግ የምትችሉት አንድ ነገር አለ፦ ቀጣዩ ትውልድ ማመን ጨርሶ እንዳያቆም፥ ጥያቄ መፍራት አቁሙ። ታሪክን አንብቡ፦ ጥያቄ መፍራት ኃይማኖቶችን አንኮታኩቷል!
Sara A.kedir
@cgfsd
1 564
እግዚአብሔር አማኝ አይደለም ማንም አያምንም ። ምክኒያቱም እምነት መደገፍ ነው ። እሱ ማንም ሊደገፍ አይችልም ። ይልቁንም እግዚአብሔር ታማኝ ነው ። ማስደገፍ ፣ መታመን ። ስለሚችል እሱ ታማኝ ነው ።
@cgfsd
1 564
ሰሞኑን አንድ በአንድ ቤተክርስቲያን ውስጥ የቲኔጀሮች ፕሮግራም ነበር ። እየተማሩ የነበረው ትምህርት ኢየሱስ ማን ነው? የሚል ነበር ። አንድ ጥያቄ ጠየቅናቸቸው እንዲህ በማለት " ኢየሱስን እንዴት ማወቅ ይቻላል ?
አንድ ልጅ እንደዚህ በማለት መለሰ " ኢየሱስን ለማወቅ ደቀመዝሙር (የክርስቶስ ተከታይ) መሆን ነው " ። በማለት ሰፊ የክርስትናን እውነት ለስለስ ብሎ መለሰ ።
@cgfsd
1 564
ሰኞ ሰኞ ከአንድ ሳምንት በኋላ live ፕሮግራም እንጀምራል ። በምን ጉዳዮች ላይ ብናጠና ፣ ብንማር ፣ ሰው ጋብዘን ብንጋገር የምትፈልጓቸውን ጉዳዮች mention አርጉልን comment ላይ ወይም inbox @filicross ትችላላችሁ ።
1 564
ለንጉሡ ታላቅ ድል ይሰጠዋል፤
ለቀባው ለዳዊትና ለዘሩ፣
ለዘላለም የማይለወጥ ፍቅሩን ያሳየዋል።
2 ሳሙኤል 22:51
አንዳንድ ጥቅስ ግን እያስተዋሉ ማንበብ እንዴት ያለ ነገር መሰላችሁ !
1 564
ከቤተክርስቲያን አባት መካከል የሆነው ባስልዮስ በቤተክርስቲያን ስለሚያገለግሏቸው ሰዎች ሲናገር በተለይ በድሆች አገልግሎት ዙሪያ
" እያንዳንዱ ወደ እኛ የሚመጣው ሰው ክርስቶስ በድንኳን ነው "
ሰለሞን አበበ(መጋቢ)
@cgfsd
