ru
Feedback
General Wingate Polytechnic college-Official channel

General Wingate Polytechnic college-Official channel

Открыть в Telegram

ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን። የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала General Wingate Polytechnic college-Official channel

Канал General Wingate Polytechnic college-Official channel (@wingetpolytechniccollege) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 12 294 подписчиков, занимая 16 116 место в категории Образование и 2 714 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 12 294 подписчиков.

Согласно последним данным от 28 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 14, а за последние 24 часа — 0, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 41.60%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.03% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 5 114 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 971 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 19.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን። የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 29 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Образование.

12 294
Подписчики
Нет данных24 часа
+187 дней
+1430 день
Архив постов
ማስታወቂያ ለነባር ተሻጋሪ ሰልጣኞች በሙሉ! ውድ የ2018 ዓ.ም ተሻጋሪ (ነባር) የመደበኛ (የቀን፣ የማታ እና የዊኬንድ) ፕሮግራም ሰልጣኞቻችን!! አካዳሚክ ኮሚሽን ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት ከነሐሴ
ማስታወቂያ   ለነባር ተሻጋሪ ሰልጣኞች በሙሉ!   ውድ የ2018 ዓ.ም ተሻጋሪ (ነባር) የመደበኛ (የቀን፣ የማታ እና የዊኬንድ) ፕሮግራም ሰልጣኞቻችን!! አካዳሚክ ኮሚሽን ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት ከነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 3 ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ የክረምት እረፍት ጊዜ መሆኑን በደስታ እናሳውቃለን።   ቀጣዩ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ምዝገባ የሚካሄደው ከመስከረም 4 ቀን 2019 ዓ.ም ጀምሮ መሆኑን አውቃችሁ ተገቢውን ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።   ጥብቅ ማሳሰቢያዎች፡-  ያላጠናቀቃችሁትን ኮርስ /ስልጠና እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንድታጠናቅቁ፣  የትብብር ስልጠና (Cooperative Training) ውጤታችሁን ለስልጠና ክፍላችሁ እንድታስገቡ፣  በየደረጃው ያለውን የስልጠና ውጤታችሁን በየስልጠና ክፍላችሁ በአካል በመቅረብ እንድታረጋግጡ እናሳውቃለን።   �� ልዩ ማሳሰቢያ ለእጩ ተመራቂዎች፡- ይህ ማስታወቂያ የ2018 ዓ.ም ተመራቂ ሰልጣኞችን አይመለከትም። እጩ ተመራቂ ሰልጣኞች ለምረቃ የሚያስፈልጉ ቅድመ-ሁኔታዎችን እና ሂደቶችን እያሟላችሁ የምረቃ ቀናችሁን በትዕግስት እንድትጠባበቁ ኮሌጁ በአክብሮት ያሳውቃል።    የኮሌጁ የስልጠና እና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን ቢሮ

ሰኞ:- ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም   ⚽️  የኮሌጁ አሰልጣኞች የክረምት እግር ኳስ ውድድር በድምቀት ተከፈተ! የአይሲቲ ዲፓርትመንት ደግሞ የጎል ናዳ አዘነበ!   በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተዘጋጀው የአሰልጣኞች የክረምት ስፖርታዊ የእግር ኳስ ውድድር በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀመረ። የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ባገኘበት ማግስት የተጀመረው ይህ የአሰልጣኞች ውድድር ስድስት የተለያዩ ዲፓርትመንቶችን የሚወክሉ ቡድኖች እየተሳተፉ ይገኛሉ።   በዚህ ውድድር አውቶሞቲቭ ዲፓርትመንት (Turbo Striker)፣ ጀነራል መካኒክስ /GM/ ( Iron Man)፣ አይሲቲ ዲፓርትመንት (Wingate Best)፣ አግሮ ቢዝነስ (ከተማ ግብርና እና የቢዝነስ)፣ ኤሌክትሪክና ሰርቬይንግ እና ኮንስትራክሽን (ኮንስትራክሽንና ውድ ወርክ)  ባከተተ ምድብ ተከፍሎ የሚካሄድ ሲሆን የደረጃና የፍጻሜውን የዋንጫ ጨዋታ ጨምሮ በአጠቃላይ 10 የእግር ኳስ ግጥሚያዎች ይስተናገዳሉ።   የምድብ ጨዋታው ሲጠናቀቅ ሶስተኛ የሚወጡት ቡድኖች የሚሰናበቱ ሲሆን፤ ከየምድቡ አንደኛ እና ሁለተኛ የሚወጡት አራት ቡድኖች ወደ ቀጣይ ዙር ጨዋታ ያልፋሉ። አሸናፊውን ለመለየትም የአንደኛው ምድብ አሸናፊ ከሌላኛው ምድብ ሁለተኛ ጋር ይፋለማል።   በዛረው የመክፈቻው ጨዋታ ላይ ሁለት ምድቦች ግጥሚ ያደረጉ ሲሆን መጀመሪያ ላይ አውቶሞቲቭ (Turbo Striker) ከ ጀነራል መካኒክስ (Iron Man) ጋር ተፋልመዋል፡፡    በዚህ ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች እጅግ ማራኪ የሆነ የማጥቃት እና የመከላከል ብቃት ያሳዩ ሲሆን እስከ እረፍት  ሰዓት ድረስ ባደረጉት ጠንካራ ፉክክር ጨዋታው ያለ ምንም ግብ ተጠናቆ ከእረፍት መልስ ሁለቱም ቡድኖች አቻ የሚያደርጋቸው አንድ አንድ ግብ በማስቆጠር 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ነጥብ ተካፍለዋል።   በሁለተኛው ጨዋታ ደግሞ አይሲቲ ዲፓርትመንት (Wingate Best) ከ ኮንስትራክሽን ጋር የተደረገ ሲሆን አይሲቲ ዲፓርትመንት ኮንስትራክሽንን 11 ለ 5 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት በማሸነፍ አስገራሚ የበላይነቱን አሳይቷል።    አይሲቲ ዲፓርትመንት ወደ ተቃራኒ የግብ ክልል በተደጋጋሚ በማምራት በርካታ ግቦችን አከታትሎ በማስቆጠር ድንቅ አጨዋወት ሲያሳይ ኮንስትራክሽን ዲፓርትመንቶች ደግሞ በአቅም የተፈተኑበትና አንድ ደርዘን የሚጠጉ ግቦችን ያስተናገዱበት ፈታኝ ጨዋታ ሆኖ አልፏል።   የኮሌጁ የክረምት ስፖርታዊ ውድድር በእግር ኳስ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን የሰራተኞችን የእርስ በእርስ ግንኙነት እና ጤንነት ለማጎልበት ታስቦ የመረብ ኳስ እና የጠረጴዛ ቴኒስ ጨዋታዎችም ጭምር  ይካሄዳሉ።   ውድድሩን በአሸናፊነት ለሚያጠናቅቁ ቡድኖች የዋንጫ ሽልማት እንደሚበረከት አዘጋጅ ኮሚቴው የገለጸ ሲሆን የዛሬው የመክፈቻ ቀን እጅግ የተሳካና የተመልካችን ቀልብ የሳበ በመሆኑ በቀጣይም ይህ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።    "በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"

🌿 ለኮሌጁ ማህበረሰብ በሙሉ! 🌿   🌳 አረንጓዴ አሻራችንን በጋራ እናኑር! 🌳 ዛፍ መትከል ህይወትን ማለምለም፣ ትውልድን ማሻገር ነው! ኮሌጃችን አካባቢውን አረንጓዴ በማልበስ የተፈጥሮ ውበቱን ለመጠበቅና አየር ንብረቱን ለማሻሻል ደማቅ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አዘጋጅቷል።   በዚህም ሁላችንም በአንድነት በመቆም ለኮሌጃችንም ሆነ ለሃገራችን የሚጠቅም ዘላቂ አሻራን እናሳርፍ!   የመርሃ ግብሩ ዝርዝር መረጃ፡- 📍 ቦታ፡- በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቅጥር ግቢ 📅 ቀን፡- ነገ፣ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ⏰ ሰዓት፡- ከጧቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ   ውድ የኮሌጃችን ማህበረሰብ (አሰልጣኞች፣ ሰራተኞች እና ሰልጣኞች) እርስዎም የዚህ በጎ ዓላማ አካል በመሆን የኮሌጃችንን ግቢ በተለያዩ ውብ ችግኞች ለማስዋብ በነቂስ ወጥተው አሻራዎን እንዲያሳርፉ በታላቅ አክብሮት ተጋብዘዋል!   አካባቢያችንን እንንከባከብ፤ ለትውልድ የሚተርፍ አረንጓዴ አሻራ እናኑር! 🌍

🌿 ለኮሌጁ ማህበረሰብ በሙሉ! 🌿   🌳 አረንጓዴ አሻራችንን በጋራ እናኑር! 🌳 ዛፍ መትከል ህይወትን ማለምለም፣ ትውልድን ማሻገር ነው! ኮሌጃችን አካባቢውን አረንጓዴ በማልበስ የተፈጥሮ ውበቱን ለመጠበቅና አየር ንብረቱን ለማሻሻል ደማቅ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አዘጋጅቷል። በዚህም ሁላችንም በአንድነት በመቆም ለኮሌጃችንም ሆነ ለሃገራችን የሚጠቅም ዘላቂ አሻራን እናሳርፍ! የመርሃ ግብሩ ዝርዝር መረጃ፡- 📍 ቦታ፡- በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቅጥር ግቢ 📅 ቀን፡- ነገ፣ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ⏰ ሰዓት፡- ከጧቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ ውድ የኮሌጃችን ማህበረሰብ (አሰልጣኞች፣ ሰራተኞች እና ሰልጣኞች) እርስዎም የዚህ በጎ ዓላማ አካል በመሆን የኮሌጃችንን ግቢ በተለያዩ ውብ ችግኞች ለማስዋብ በነቂስ ወጥተው አሻራዎን እንዲያሳርፉ በታላቅ አክብሮት ተጋብዘዋል! አካባቢያችንን እንንከባከብ፤ ለትውልድ የሚተርፍ አረንጓዴ አሻራ እናኑር! 🌍💚

አስደሳች እድል ለ Cisco (ሲስኮ) ኔትዎርኪንግ/ICT ስልጠና ፈላጊዎች፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለውን(የአሜሪካ Cisco ት/ቤት )የሲስኮ ኔትወርኪንግ ስልጠና ለመስጠት ሙሉ ፍቃድ ያለው
አስደሳች እድል ለ Cisco (ሲስኮ) ኔትዎርኪንግ/ICT ስልጠና ፈላጊዎች፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለውን(የአሜሪካ Cisco ት/ቤት )የሲስኮ ኔትወርኪንግ  ስልጠና ለመስጠት ሙሉ ፍቃድ ያለው እናም  የሲስኮ ኔትዎርኪንግ  ማሰልጠኛ ማዕከል  የሆነው አንጋፋው ኮሌጃችን ጄነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዘርፉ ብቃታቸውን ባረጋገጡ  እና (Certified) ሰርቲፋይድ በሆኑ አሰልጣኞች አማካኝነት በገበያው እጅግ ተፈላጊ የሆኑ ስልጠናዎችን ለመስጠት ምዝገባ መጀመሩን በደስታ ይገልፃል። የሚሰጡ ኮርሶች፡- IT Essentials CCNA   ልዩ ዕድሎች! ለማንኛውም ኮርስ ሲመዘገቡ የሚከተሉትን ኮርሶች በነፃ ያገኛሉ:: 1. Introduction to Cybersecurity 2. Introduction to Modern AI 3. Python Essentials 4. Digital Awareness ማሳሰቢያ፡- o   ለሁሉም ኮርሶች ሰርተፊኬት ይሰጣል። o  ክፍያ የሚፈፀምበት አካውንት ቁትር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000328857468 መመዝገቢያ ቦታ፡- o   ነባሩ ህንፃ ላይ ባንድራ መስቀያ ፊት ለፊት በሚገኘው የማታ ተከታታይ ትምህርት ማስተባበሪ ቢሮ ለበለጠ መረጃ፡- 0911717635 | 0911196315 | 0944767038 ይደውሉልን።

📢 የሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ! 📢 በተመጣጣኝ ዋጋ የተለያዩ ያገለገሉ ነገር ግን በጥሩ ይዞታ ላይ የሚገኙ የቤት እና የግንባታ ዕቃዎችን መግዛት ይፈልጋሉ? እንግዲያውስ ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ
📢 የሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ! 📢   በተመጣጣኝ ዋጋ የተለያዩ ያገለገሉ ነገር ግን በጥሩ ይዞታ ላይ የሚገኙ የቤት እና የግንባታ ዕቃዎችን መግዛት ይፈልጋሉ? እንግዲያውስ ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ያዘጋጀው ልዩ የሽያጭ ጨረታ ለእርስዎ ነው!   🛠 በጨረታው የቀረቡ ዕቃዎች፡- ·        ተነቃይ የጣሪያ ቆርቆሮዎች ·        የእንጨት በሮች እና መስኮቶች ·        ሙሉ ጣውላዎች እና እንጨቶች ·        የኪችን ካቢኔት (ከነ ዕቃ ማጠቢያው) እና ቁምሳጥኖች ·        ፍርግርግ የብረት መስኮቶች   📅 ዋና ዋና የጨረታው ዝርዝሮች፡- ·        የእይታ እና መወዳደሪያ ጊዜ፡- ተጫራቾች ከ ሐምሌ 03/11/2018 እስከ ሐምሌ 09/11/2018 ዓ.ም ድረስ ኮሌጁ ግቢ ውስጥ (ብሎክ 10 የንብረት አስተዳደር ቢሮ) በአካል በመገኘት ዕቃዎቹን በማየት የጨረታ ሰነድ መሙላት ይችላሉ። ·        የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond)፡- 29,800 ብር (ሃያ ዘጠኝ ሺህ ስምንት መቶ ብር) ·        ጨረታው የሚዘጋበት እና የሚከፈትበት ቀን፡- ሐምሌ 09/11/2018 ዓ.ም ጧት 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ዕለት 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል።   ⚠️ ማሳሰቢያ፡- አሸናፊው አካል በ5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ክፍያውን በመፈጸም እና ቦታውን በማፅዳት ዕቃዎቹን ማንሳት ይኖርበታል።   📍 አድራሻ፡-   ዊንጌት አደባባይ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን አጠገብ።  📞 ለበለጠ መረጃ፡- 011 2 73 96 35 ይደውሉ!    ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

🌟 የስራ ቅጥር ማስታወቂያ!🌟 በስልጠና እና ማማከር አገልግሎት ዘርፍ ቀዳሚ የሆነውና ከአንጋፋው ጀነራል ዊንጌት ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በተለያዩ ሙያዎች የአጫጭር ጊዜ ስልጠና በትብብር እየሰጠ የሚገኘው ዩኒቨርሳል የስልጠና፣ የትምህርት እና የማማከር አገልግሎት ድርጅት የልዩ ልዩ ዘርፍ ባለሙያ የሆናችሁ ኑ አብረን እንስራ ብሏችኋል! 🚀 ድርጅቱ እውቀትን ከክህሎት ጋር በማቀናጀት ለግለሰቦችና ለተቋማት ስኬት ብቁ በሆኑ ባለሙያዎች የታገዘና ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት መስጠቱን እየገለፀ ተቋሙ አሁን ላይ ንቁ እና በዘርፉ ውጤታማ የሆኑ ባለሙያዎችን አወዳድሮ በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል። 📚 የትምህርት መስክ፦ ስራ አመራር፣ አካውንቲንግ፣ ማርኬቲንግ፣ ኮምፒውተር ሳይንስ፣ ግራፊክ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኤዲቲንግ፣ ፕሮጀክት ማኔጅመንት፣  የሰው ኃይል አስተዳደር፣ እንግሊዝኛ ቋንቋ፣ ሒሳብ፣ ፊዚክስ፣ ኬሚስትሪ፣ ባዮሎጂ፣ ኢንጅነሪንግ፣ ጤና፣ ሳይኮሎጅ፣ ሶሲዮሎጅ፣ ህግ፣ ኢኮኖሚክስ 🎓 የትምህርት ደረጃ፦ ፒኤችዲ | ማስተርስ | ባችለር ዲግሪ | ደረጃ IV + COC 💼 የስራ ልምድ፦ ዜሮ አመት (ተዛማጅ ልምድ ቅድሚያ ይሰጣል) ✅ የቅጥር ሁኔታ፦ በቋሚነት የስራ መደቦች👇 🎬 1. Advanced Video & Photo Editing አሰልጣኝ – ብዛት፡ 3 🎨 2. Advanced Graphic Design አሰልጣኝ – ብዛት፡ 2 📊 3. Modern & Peachtree Accounting አሰልጣኝ – ብዛት፡ 2 📱 4. Digital Marketing አሰልጣኝ – ብዛት፡ 1 👨‍💼 5. Leadership & Management Skills አሰልጣኝ – ብዛት፡ 2 📈 6. Research Methodology & Advanced SPSS አሰልጣኝ – ብዛት፡ 1 🗣️ 7. English Language Skills አሰልጣኝ – ብዛት፡ 2 📝 8. Exit, GAT & COC Exam አሰልጣኝ – ብዛት፡ 2 💻 9. Basic Computer Skills አሰልጣኝ – ብዛት፡ 3 👨‍🏫 10.  አስጠኝ:- (በሁሉም ትምህርት) 📋 11. ሲኒየር የፕሮጀክት ባለሞያ – ብዛት፡ 2 📩 እንዴት ማመልከት ይቻላል? መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች የትምህርት እና የስራ ልምድ ማስረጃችሁን በአንድ Pdf በሚከተለው የኢሜል አድራሻ ብቻ እንድትልኩ እናሳስባለን፦ 📧 Email፦ universaltraining11@gmail.com ⚠️ ጠቃሚ ማሳሰቢያ፦ • ማመልከቻ የምንቀበለው በኢሜል ብቻ ነው። • ለፅሁፍ እና ለቃለ-መጠይቅ ፈተና የምንጠራው ብቁ የሆኑ አመልካቾችን ብቻ ይሆናል። የስራ ኃላፊነቶችስልጠናዎችን ማቀድ፦ የስልጠና ተሳታፊዎችን ወይም ቡድኑን ፍላጎት በመለየት አጫጭር እና የረዥም ጊዜ የስልጠና እቅዶችን ያዘጋጃሉ። ✅ክህሎትና ስልቶችን ማስተማር፦ ተሳታፊዎች ተገቢውን እውቀት፣ ስነ-ልቦና እና አካላዊ ብቃት እንዲያዳብሩ የሚያስችሉ ተግባራዊና ቲዎሬቲካል ትምህርቶችን ይሰጣሉ። ✅ክትትልና ግምገማ ማድረግ፦ እያንዳንዱ ሰልጣኝ ወይም ቡድን እያሳየ ያለውን ለውጥ በየጊዜው በመከታተል ድክመቶች ላይ ምክርና እርምት ይሰጣሉ። ✅የስራ አፈፃፀም መለካት፦ በስልጠናው መጨረሻ የሚጠበቀውን ውጤት መሰረት በማድረግ የተሰጠውን ስልጠና ውጤታማነት ይመዝናሉ። ✅ተነሳሽነት መፍጠር፦ ሰልጣኞች በራስ መተማመናቸውን እንዲገነቡ እና ለተግባራዊ ውጤታቸው አዎንታዊ አስተሳሰብ እንዲኖራቸው የማበረታታት ስራዎችን ይሰራሉ። 🔗 ለበለጠ መረጃ፦👇 🌐 ቴሌግራም 👉 https://t.me/WWETC1  👉 https://t.me/WWETC1 ኑ አብረን! ኑ ትውልድ እናቅና! ዩኒቨርሳል የስልጠና እና ማማከር አገልግሎት ኢንስቲትዩት🌎 ለእውቀትና ለክህሎት ማደግ በትጋት እንሰራለን! ❤️👍

🚀 የስራ እድልዎን የሚቀይር አዲስ የስልጠና ጥሪ! 🚀 ለአጫጭር ጊዜ ስልጠና ፈላጊዎች በሙሉ፤ አንጋፋው ጀኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከዩኒቨርሳል የስልጠና እና ስራ አመራር ማማከር አገልግሎት ጋር በመተባበር የሚሰጠው የ3ኛው ዙር ስልጠና በደመቀ ሁኔታ ቀጥሏል! 🔥 እርስዎም የገበያ ፍላጎትን መሰረት ያደረጉ ስልጠናዎቻችንን በመውሰድ ብቁና ተወዳዳሪ ይሁኑ። 📚 የምንሰጣቸው ስልጠናዎች፦ 🎨 ለፈጠራ ባለሙያዎች (Creative Arts)   • Advanced Video Editing 🎬   • Advanced Photoshop 📸   • Advanced Graphic Design 🎨 📊 ለሂሳብና ቢዝነስ ባለሙያዎች (Business & Finance)   • Modern Peachtree Accounting 📉   • Leadership & Management Skills 👔 🔍 ጥናትና ምርምር (Research)   • Research Methodology & Advanced SPSS 📊 🗣️ ቋንቋና ቴክኖሎጂ (Language & Tech)   • English Language Skills 💬   • Basic Computer Skills 💻 💼 የማማከር አገልግሎት (Consultancy)   • የፕሮጀክት አዋጭነት ጥናት (Feasibility Study) 📝   • የፕሮጀክት ፕሮፖዛል (Project Proposal) 📑 🌟 አሁኑኑ ይደውሉ፤ ይመዝገቡ! 📞 ስልክ ቁጥር፦   👉 0933884400   👉 0911972393 📱 የቴሌግራም አድራሻችን፦   👉 https://t.me/WWETC1 ከልብ እናመሰግናለን!❤ ለእውቀትና ለክህሎት ማደግ በትጋት እንሰራለን! 👍❤

ረቡዕ:- ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ኮሌጁ ከ1,800 በላይ ለሚሆኑ ተመራቂ ሰልጣኞች ለሀገር አቀፍ የብቃት ምዘና የሚያበቃ ሞዴል ፈተና መስጠት ጀመረ!!   ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 ዓ.ም ተመራቂ ሰልጣኞችን ለሀገር አቀፍ የሙያ ብቃት ምዘና (CoC) ብቁ የሚያደርገውን ተቋማዊ የሞዴል ምዘና በዛሬው ዕለት በይፋ መስጠት ጀመረ።   ፈተናው ሰልጣኞች ወደ ስራ ዓለም ከመቀላቀላቸው በፊት ክህሎታቸውን የሚፈትሹበት ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑ ተገልጿል።   በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ የተዘጋጀው ይህ ምዘና በ11 ዲፓርትመንቶች እና በ25 የሙያ ዘርፎች ስልጠናቸውን ላጠናቀቁ 1,876 ዕጩ ምሩቃን እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን በዚህ ምዘና 691 ወንድ እና 1,185 ሴት ተመራቂ ሰልጣኞች ይሳተፋሉ።   ተመራቂዎቹ ከሚመዘኑበት አጠቃላይ ውጤት ውስጥ 30% የፅንሰ ሀሳብ (Theory) ምዘና በበይነ-መረብ (Online) እየተሰጠ ሲሆን 70%ቱ ደግሞ የተግባር (Practical) ምዘና  በስልጠና ወርክሾፓቸው  እየተመዘኑ ነው።   "የዚህ ተቋማዊ ሞዴል ዋነኛ ግብ ተመራቂዎቻችን ለሀገር አቀፉ የብቃት ምዘና ማዕከል ከመቅረባቸው በፊት ያላቸውን እውቀትና ክህሎት ለመፈተሽ እና ክፍተቶቻቸውን ለይቶ ለማረም ነው"  ያሉት በኮሌጁ የስልጠና እና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን የሆኑት አቶ ጄበሳ ሙላቱ ናቸው።   ምክትል ዲኑ አክለውም ሰልጣኞች በስራ ገበያው ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ብቃታቸውን ከፍ ለማድረግ በሚረዱ አምስት የተለያዩ ዘርፎች የልል ክህሎት (Soft Skills) ስልጠናዎች ከምዘናው ጎን ለጎን እየተሰጣቸው መሆኑን አብራርተዋል።   በዛሬው ዕለት የኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ፣ የሆቴልና ሆስፒታሊቲ፣ የሰርቬይንግና ድራፍቲንግ፣ የውድ ወርክ እንዲሁም የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) ሞዴል ምዘናዎች የተሰጡ ሲሆን ቀሪዎቹ በ5 ቀናት ውስጥ ተጠናቀው ሁሉም ተመራቂዎች ለዋናው ፈተና ዝግጁ እንደሚሆኑ ታውቋል።   በተያያዘ ዜና ሁሉም የበጀት ዓመቱ ተመራቂዎች የኮሌጁን የውስጥ ብቃት ምዘና ማለፋቸውም ተጠቁሟል። "በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"

📣 2ኛው ዙር ምዝገባ ተጀምሯል፤ ስልጠናውም ሐምሌ 6 ቀን 2018 ይጀምራል! ስለሆነም አዋጭና በገበያው ላይ እጅግ ተፈላጊ የሆኑ የአጫጭር ጊዜ ስልጠናዎች ጥሪ እንሆ! ኮሌጃችን በኤሌክትሪካል ኤሌክ
📣 2ኛው ዙር ምዝገባ ተጀምሯል፤ ስልጠናውም ሐምሌ 6 ቀን 2018 ይጀምራል!   ስለሆነም አዋጭና በገበያው ላይ እጅግ ተፈላጊ የሆኑ የአጫጭር ጊዜ ስልጠናዎች ጥሪ እንሆ!   ኮሌጃችን በኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ  ዘርፍ ራስዎን እና ተቋምዎን የሚቀይሩባቸውን እጅግ አዋጭ የስልጠና መስኮች ይዞላችሁ ቀርቧል።   1. ለዘመናዊ የመሰረተ-ልማት እና የሀይል አማራጮች የሕንፃ ላይ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታና ሶላር ሲስተም (Building Electrical Installation & Solar System)   2. ለኢንደስትሪና ለከፍተኛ ማሽነሪዎች የኢንደስትሪያል ሞተር ኮንትሮል እና ጀነሬተር ዝርጋታና ጥገና ኢንደስትሪያል አውቶሜሽን (Industrial Automation)  ኒውማቲክስ ሲስተምን ጨምሮ የሞተር ዋይንዲንግ (Motor Winding)   3. ለቴክኖሎጂ፣ ለደህንነት እና ለቤት ውስጥ እቃዎች CCTV ካሜራ ዝርጋታና ኮንፊግሬሽን (CCTV Installation & Configuration) ሳተላይት ዲሽ ዝርጋታ፣ LED TV እና ሬሲቨር ጥገና የቤት ውስጥ እቃዎች ጥገና (Home Appliances Maintenance)   📌 እኛን ሲመርጡ? በተግባር (Practical) ላይ ያተኮረ ስልጠና ምቹ የስልጠና ክፍለ-ጊዜዎች ብቁ እና ልምድ ያላቸው አሰልጣኞች ስልጠናውን በጥራት ላጠናቀቁ የምስክር ወረቀት   🎯 ማሳሰቢያ: የስልጠናው ቦታ ውስን ስለሆነ ፈጥነው በመመዝገብ የዕድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ!   📞 ለበለጠ መረጃና ምዝገባ አድራሻ: -  ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስልክ ቁጥር: 0913143307 ወይም 0911105037   "ክህሎት ያነገበ ትውልድ — ለቀጣይ ብሩህ ተስፋ!"

እሁድ:- ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ኮሌጁ የተሟላ አገልግሎትን ያካተተ ስልጠና የሰጠበትን ቆይታ በስኬት አጠናቀቀ!! አንጋፋው ጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከቦንጋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለመጡ አሰል
+7
እሁድ:- ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም   ኮሌጁ የተሟላ አገልግሎትን ያካተተ ስልጠና የሰጠበትን ቆይታ በስኬት አጠናቀቀ!!   አንጋፋው ጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከቦንጋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለመጡ አሰልጣኞች ሲሰጥ የነበረውን የ10 ቀናት የተጠናከረ የአሉሚኒየም ስራዎች አፕሊኬሽን (Aluminum Works Applications Skill Training) ክህሎት ስልጠና በስኬት በማጠናቀቅ የምስክር ወረቀት አበረከተ።   በኮሌጁ የማታ ተከታታይ ትምህርት እና የአጫጭር ስልጠና ማስተባበሪያ እንዲሁም በሜታል ማኑፋክቸሪንግ ዲፓርትመንት ትብብር የተዘጋጀው ይህ ስልጠና ከሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም) ድረስ ለ10 ተከታታይ ቀናት ተሰጥቷል።   ስልጠናው የቦንጋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኞች (Trainers) በዘርፉ ያላቸውን የተግባር ክህሎትና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በማሳደግ በተቋማቸው የላቀ የስልጠና ጥራት እንዲያረጋገጡ ያለመ ነው። በስልጠናው ማጠቃለያ መርሃ ግብርም ክህሎታቸውን ላዳበሩ 9 አሰልጣኞች የስልጠና ተሳትፎ የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።   ‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››

እሁድ:- ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም   ኮሌጁ የተሟላ አገልግሎትን ያካተተ ስልጠና የሰጠበትን ቆይታ በስኬት አጠናቀቀ!!   አንጋፋው ጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከቦንጋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለመጡ አሰልጣኞች ሲሰጥ የነበረውን የ10 ቀናት የተጠናከረ የአሉሚኒየም ስራዎች አፕሊኬሽን (Aluminum Works Applications Skill Training) ክህሎት ስልጠና በስኬት በማጠናቀቅ የምስክር ወረቀት አበረከተ።   በኮሌጁ የማታ ተከታታይ ትምህርት እና የአጫጭር ስልጠና ማስተባበሪያ እንዲሁም በሜታል ማኑፋክቸሪንግ ዲፓርትመንት ትብብር የተዘጋጀው ይህ ስልጠና ከሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም) ድረስ ለ10 ተከታታይ ቀናት ተሰጥቷል።   ስልጠናው የቦንጋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኞች (Trainers) በዘርፉ ያላቸውን የተግባር ክህሎትና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በማሳደግ በተቋማቸው የላቀ የስልጠና ጥራት እንዲያረጋገጡ ያለመ ነው። በስልጠናው ማጠቃለያ መርሃ ግብርም ክህሎታቸውን ላዳበሩ 9 አሰልጣኞች የስልጠና ተሳትፎ የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።   ‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››

ለጣሊያን ሀገር የሥራ ዕድል የምዝገባ ጥሪ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በገባው የሁለትዮሽ ስምምነት መሰረት በህጋዊ የውጪ ሀገር ሥራ ስምሪት ፕሮግራም በጣሊያን ሀገር በሆቴልና መስተንግዶ (Hospitality) ዘርፍ የሰው ኃይል ይፈለጋል። የዜጎችን መብት፣ ደህንነት እና ጥቅም በማስጠበቅ ህጋዊ በሆነ መንገድ ወደ ጣሊያን ሄደው መስራት የሚፈልጉ አመልካቾች እንዲያመለክቱ እናሳውቃለን። 🏨 የሥራ መደቦች፦ 🔹ጸሐፊ(Commis de Rang / F&B Server) – 19 ቦታዎች 🔹 የፅዳት ሰራተኛ (Room Attendant / Housekeeping) – 20 ቦታዎች 🔹 ረዳት ሼፍ (Commis Chef) – 13 ቦታዎች 🔹 የእቃ አጣቢ (Kitchen Steward / Dishwasher) – 11 ቦታዎች 🔹 የወለል ረዳት (Floor Porter / Houseperson) – 3 ቦታዎች 🔹 የቢሮ አስተናጋጅ (Front Office Agent / Receptionist) – 4 ቦታዎች 🔹 የጥገና ቴክኒሺያን (Maintenance Technician) – 1 ቦታ 🔹 የስፓ ቴራፒስት / የማሳጅ ባለሙያ (Spa Therapist / Masseuse) – 1 ቦታ 📌 የማመልከቻ መስፈርቶች ✅ ከስራው ጋር ተያያዥ የስራ ልምድ ያላቸው ተመራጭ ናቸው። ✅ ለአብዛኛዎቹ የስራ መደቦች የእንግሊዝኛ እና/ወይም የጣሊያንኛ ቋንቋ እውቀት ያስፈልጋል። ✅ ለአንዳንድ የሙያ መደቦች ተዛማጅ የሙያ ማረጋገጫ ወይም የሆቴል እና መስተንግዶ ትምህርት ተመራጭ ነው። 📅 የሥራ ቆይታ አብዛኛዎቹ የስራ መደቦች ለ2026/2027 የክረምት የቱሪዝም ወቅት የሚቀጠሩ ሲሆን፣ አንዳንድ የስራ መደቦች ዓመቱን ሙሉ ወይም በበጋና በክረምት ወቅት የሚሰሩ ናቸው። ✅ ለመመዝገብ 1.Labor ID ካሎት በተሰጠው የማመልከቻ ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ያመልክቱ። 2.Labor ID ከሌሎት የሚከተሉትን ሂደቶች ይከተሉ፦ 1. በ lmis.gov.et ይመዝገቡ። በአቅራቢያዎ ባለ የአንድ ማዕከል (ወረዳ ወይም ቀበሌ) በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ ይስጡ እና የሰራተኛነት መለያ ቁጥር (Labor ID) ይያዙ። 1. Labor ID ካገኙ በኋላ በተሰጠው የማመልከቻ ማስፈንጠሪያ https://forms.lmis.gov.et/italy-hotel/ገብተው መረጃዎትን በትክክል ሞልተው ያመልክቱ። ማሳሰቢያ • ምዝገባም ሆነ ስምሪቲ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ ብቻ የሚከናወን ሲሆን ሚኒስቴሩ ለየትኛውም አካል ውክልናም ሆነ ፈቃድ አለመስጠቱን እንገልፃለን። • ምንም አይነት ክፍያም የለውም

አስደሳች እድል ለ Cisco (ሲስኮ)ኔትዎርኪንግ/ICT ስልጠና ፈላጊዎች፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለውን(የአሜሪካ Cisco ት/ቤት )የሲስኮ ኔትወርኪንግ ስልጠና ለመስጠት ሙሉ ፍቃድ ያለው እ
አስደሳች እድል ለ Cisco (ሲስኮ)ኔትዎርኪንግ/ICT ስልጠና ፈላጊዎች፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለውን(የአሜሪካ Cisco ት/ቤት )የሲስኮ ኔትወርኪንግ  ስልጠና ለመስጠት ሙሉ ፍቃድ ያለው እናም  የሲስኮ ኔትዎርኪንግ  ማሰልጠኛ ማዕከል  የሆነው አንጋፋው ኮሌጃችን ጄነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣ በዘርፉ ብቃታቸውን ባረጋገጡ  እና (Certified)ሰርቲፋይድ በሆኑ አሰልጣኞች አማካኝነት በገበያው እጅግ ተፈላጊ የሆኑ ስልጠናዎችን ለመስጠት ምዝገባ መጀመሩን በደስታ ይገልፃል። የሚሰጡ ኮርሶች፡- IT Essentials CCNA   ልዩ ዕድሎች! ለማንኛውም ኮርስ ሲመዘገቡ የሚከተሉትን ኮርሶች በነፃ ያገኛሉ:: F Introduction to Cybersecurity F Introduction to Modern AI F Python Essentials F Digital Awareness ማሳሰቢያ፡- o   ለሁሉም ኮርሶች ሰርተፊኬት ይሰጣል። መመዝገቢያ ቦታ፡- o   አስተዳደር ህንፃ፣ 2ኛ ፎቅ፣ ቢሮ ቁጥር 208 ለበለጠ መረጃ፡- 0911717635 | 0911196315 | 0944767038 ይደውሉልን።

ሰኞ:- ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም የCOC ምዘና ውጤትን ለማሻሻል የዊንጌት ክላስተር ኮሌጆችና የትምህርትና ስልጠና ቁጥጥር ባለስልጣኑ በቅንጅት ሊሰሩ ተስማሙ፡፡ የጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን
+5
ሰኞ:- ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም   የCOC ምዘና ውጤትን ለማሻሻል የዊንጌት ክላስተር ኮሌጆችና የትምህርትና ስልጠና ቁጥጥር ባለስልጣኑ በቅንጅት ሊሰሩ ተስማሙ፡፡   የጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን ጨምሮ በዊንጌት ክላስተር ስር የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች እና የትምህርትና ስልጠና ቁጥጥር ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች የብሔራዊ የሙያ ብቃት ምዘና (COC) ውጤትን ለማሻሻል የሚያስችል የጋራ የውይይት መድረክ አካሄዱ።   መድረኩ የ2017 ዓ.ም. የተመራቂ ሰልጣኞችን የብሔራዊ ምዘና አፈጻጸም ሪፖርት ለመገምገምና የ2018 ዓ.ም. የምዘና ሂደትን በተሻለ ውጤት ለማስፈጸም ያለመ ነው።   በዚሁ የውይይት መድረክ ላይ በዊንጌት ክላስተር ስር የሚገኙት የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣ የደጃዝማች ገረሱ ዱኪ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ እና የኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ዋና ዲኖችና እና የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲኖች ተሳትፈዋል። በተጨማሪም ከአዲስ ከተማ፣ ከኮልፌ፣ ከአራዳ፣ ከጉለሌ እና ከልደታ ክፍለ ከተሞች የተወጣጡ የትምህርትና ስልጠና ቁጥጥር ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የስራ ኃላፊዎች በጋራ መክረዋል።   በዕለቱ የውይይት ሰነዱን ያቀረቡት የሰልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን ቢሮ የስልጠና ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አየለ ብርሃኑ ሲሆኑ በሰነዳቸውም የሰልጣኞችን የመብቃት ምጣኔ እና የታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በዝርዝር አቅርበዋል።   ብሔራዊ ምዘና የሰልጣኞችን የሙያ ብቃት የሚያረጋግጥ ወሳኝ ሂደት መሆኑ በመድረኩ ላይ የተገለጸ ሲሆን በቀጣይ ሂደቱ የሚሳተፉ ሁሉም አካላት በቅንጅት፣ በኃላፊነትና በተጠያቂነት በመስራት የ2018 ዓ.ም. የምዘና ውጤትን ከፍ ማድረግ እንደሚገባቸው አቅጣጫ ተቀምጧል። መድረኩ ሲጠናቀቅም ሁሉም ተሳታፊ አካላት በጋራ በመስራት ክፍተቶችን ለመሙላት የ2018 ዓ.ም

የጨረታ ማስታወቂያ ጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በግቢው ውስጥ የሚገኙና ያገለገሉ የግንባታ ቁሳቁሶችን በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል። የሚሸጡ ቁሳቁሶች ዝርዝር 1. ተነቃይ የጣራ ቆርቆሮ 2.
የጨረታ ማስታወቂያ ጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በግቢው ውስጥ የሚገኙና ያገለገሉ የግንባታ ቁሳቁሶችን በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል። የሚሸጡ ቁሳቁሶች ዝርዝር 1. ተነቃይ የጣራ ቆርቆሮ 2. ያገለገለ ቦሮንዳዮ ቆርቆሮ 3. ያገለገለ ሽክላ 4. ያገለገለ የብረት በር 5. ያገለገለ የእንጨት በር ለጨረታ ተሳታፊዎች የሚሰጡ መመሪያዎች የቦታ ጉብኝት፦ ተጫራቾች ከመወዳደራቸው በፊት ቁሳቁሶቹ ያሉበትን ሁኔታ በአካል በመገኘት መመልከት ይጠበቅባቸዋል። የጨረታ ሰነድ መውሰጃ፦ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከኮሌጁ የንብረት አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ከ12/10/2018 ዓ.ም እስከ 18/10/2018 ዓ.ም ድረስ መውሰድ ይችላሉ። ጨረታው የሚከፈትበት ቀን፦ ጨረታው በዚሁ ዕለት ማለትም በ18/10/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በ4:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። የጨረታ ማስከበሪያ፦ አሸናፊ የሆነ አካል በ5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ክፍያውን ፈጽሞ ንብረቱን ማንሳት አለበት። እያንዳንዱ ተጫራች ለጨረታ ማስከበሪያ (CPO) 1,100 ብር (አንድ ሺህ አንድ መቶ ብር) በጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ስም ማቅረብ ይኖርበታል። ተጨማሪ መረጃ፦ ለጨረታው ተወዳዳሪ ያልሆኑ ወይም ያልተሟላ ሰነድ ያቀረቡ ተጫራቾች ከጨረታው ውጪ ይሆናሉ። ኮሌጁ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። አድራሻ፦ ዊንጌት አደባባይ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን አጠገብ ስልክ ቁጥር፦ 011 2 73 96 35 ጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ