es
Feedback
General Wingate Polytechnic college-Official channel

General Wingate Polytechnic college-Official channel

Ir al canal en Telegram

ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን። የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram General Wingate Polytechnic college-Official channel

El canal General Wingate Polytechnic college-Official channel (@wingetpolytechniccollege) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 12 311 suscriptores, ocupando la posición 16 473 en la categoría Educación y el puesto 2 743 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 12 311 suscriptores.

Según los últimos datos del 12 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -135, y en las últimas 24 horas de -3, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 48.55%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 12.86% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 979 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 584 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 42.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን። የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 13 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Educación.

12 311
Suscriptores
-324 horas
-167 días
-13530 días
Archivo de publicaciones
አርብ:- ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም   53ኛው የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀን በልዩ ልዩ ሁነት ተከበረ!!   53ኛው የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ቀን ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከነገው ዛፍ ፕሮጀክትና ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በልዩ ልዩ መርሐግብሮች ተከብሯል።   በዛሬው ዕለት ከኮሌጁ ግቢ በመነሳት መዳረሻውን ጉለሌ እጽዋት ማዕከል ያደረገ የ5 ኪሎ ሜትር ማራኪ የእግር ጉዞ የተካሄደ ሲሆን ይህ ጉዞ የአካባቢ ጥበቃን መልዕክት በስፋት ከማስተላለፍ ባለፈ የተሳታፊዎችን የአካል ጤንነት ለመጠበቅ እና ለማነቃቃት ትልቅ ፋይዳ ነበረው።   ከእግር ጉዞው ጎን ለጎን የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራም የተከናወነ ሲሆን በመርሐግብሩ ላይ ስለ ጉዞው ዓላማና የቀጣይ ስራ እንቅስቃሴ በዝግጅቱ አስተባባሪዎችና በባለሙያዎች ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡     በማብራሪያውም የዚህ እንቅስቃሴ ዋና ዓላማ "ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን የተተከሉትን በአግባቡ በመንከባከብ ዛፍ ሆነው ማየት፣ የአካባቢን የተፈጥሮ ሚዛን መጠበቅ እና ከዕፅዋት የሚገኙትን ልዩ ልዩ ገጸ-በረከቶች በአግባቡ መጠቀም ነው" ሲሉ አስገንዝበዋል።   በቀጣይም ኮሌጁ ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ትብብር በማጠናከር ተመሳሳይ የአካባቢ ጥበቃ የእግር ጉዞዎች እንደሚኖሩ፣ የችግኝ ተከላ መርሐግብሮች በስፋት እንደሚካሄዱ እና በተለይም ችግኞችን ከተተከሉ በኋላ የቅርብ ክትትልና እንክብካቤ የማድረጉ ስራ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል አቅጣጫ ተቀምጧል።   በተመሳሳይ ዜና በዓሉን ምክኒያት በማድረግ በትናንትናው ዕለት የአካባቢ ጥበቃን ፅንሰ ሀሳብ እና ወቅታዊ ጉዳዮችን መነሻ ያደረገ የፓናል ውይይት ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በኮሌጁ ተካሂዷል።     «የነገው ዛፍ» በአካባቢ ጥበቃ፣ በተፈጥሮ ሚዛን መጠበቅ እና በአረንጓዴ ልማት ላይ ትኩረት አድርጎ የሚንቀሳቀስ ተራማጅ የአካባቢ ጥበቃ ፕሮጀክት ሲሆን «ዛሬ የምንተክለው ችግኝ፣ የነገው ትልቅ ዛፍና የትውልድ ዋስትና ነው» የሚለውን መርህ በመያዝ፣ ትኩረቱን በችግኝ ተከላ ላይ ብቻ ሳይሆን በድህረ-ተከላ እንክብካቤ ላይ ያደረገ ፕሮጀክት ነው።     ድርጅቱ የያዘውን በጎ ራዕይ ከጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር ተቀናጅቶ በመስራት ዓላማውን ለማሳካት ስምምነት ተፈራርሞ እየሰራ ይገኛል፡፡       ‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››

🚨 አዲስ ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ! 🚨 የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመምህራንና ሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ማህበር ብቁ ባለሙያዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። 📌
🚨 አዲስ ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ! 🚨 የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመምህራንና ሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ማህበር ብቁ ባለሙያዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። 📌 የስራ መደቡ መጠሪያ:-  የሂሳብ ባለሙያ 👥 ብዛት:-  1 (አንድ) 🎓 የትምህርት ደረጃ:- በአካውንቲንግ ደረጃ 4 እና ከዚያ በላይ 💼 የስራ ልምድ:-  እስከ 2 ዓመት የስራ ልምድ 💻 ልዩ ክህሎት:-  መሰረታዊ የኮምፒውተር እውቀት፣  በኤክሴል (Excel) እና ፒችትሪ (Peachtree) የተግባር ልምድ ያለው/ያላት 💰 ደመወዝ:-  በስምምነት 📅 የማመልከቻ ጊዜ:-  ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ማመልከት ይችላሉ። 📍 የመመዝገቢያ ቦታ:-  ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ ውስጥበሚገኘው የህብረት ሥራ ማህበሩ ጽ/ቤት በአካል በመቅረብ መመዝገብ ይችላሉ። 📞 ለበለጠ መረጃ: 0946 61 24 47 ወይም 0965 65 69 81

📣 የወደፊት ስኬትዎን በክህሎት ያረጋግጡ! አዋጭና በገበያው ላይ እጅግ ተፈላጊ የሆኑ የአጫጭር ጊዜ ስልጠናዎች ጥሪ የወቅቱን የገበያ ፍላጎት ያገናዘበ፣ በተግባር የተደገፈ እና በአጭር ጊዜ ውስጥ ወ
📣 የወደፊት ስኬትዎን በክህሎት ያረጋግጡ!   አዋጭና በገበያው ላይ እጅግ ተፈላጊ የሆኑ የአጫጭር ጊዜ ስልጠናዎች ጥሪ   የወቅቱን የገበያ ፍላጎት ያገናዘበ፣ በተግባር የተደገፈ እና በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ስራ የሚያስገባ አስተማማኝ ክህሎት ማግኘት ይፈልጋሉ? እንግዲያውስ እኛ ጋር መፍትሄው አለ!   ኮሌጃችን በኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ  ዘርፍ (ራስዎን እና ተቋምዎን የሚቀይሩባቸውን እጅግ አዋጭ የስልጠና መስኮች ይዞላችሁ ቀርቧል።   1. ለዘመናዊ የመሰረተ-ልማት እና የሀይል አማራጮች የሕንፃ ላይ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታና ሶላር ሲስተም (Building Electrical Installation & Solar System)   2. ለኢንደስትሪና ለከፍተኛ ማሽነሪዎች የኢንደስትሪያል ሞተር ኮንትሮል እና ጀነሬተር ዝርጋታና ጥገና ኢንደስትሪያል አውቶሜሽን (Industrial Automation) - ኒውማቲክስ ሲስተምን ጨምሮ የሞተር ዋይንዲንግ (Motor Winding)   3. ለቴክኖሎጂ፣ ለደህንነት እና ለቤት ውስጥ እቃዎች CCTV ካሜራ ዝርጋታና ኮንፊግሬሽን (CCTV Installation & Configuration ሳተላይት ዲሽ ዝርጋታ፣ LED TV እና ሬሲቨር ጥገና የቤት ውስጥ እቃዎች ጥገና (Home Appliances Maintenance)     📌 እኛን ሲመርጡ? በተግባር (Practical) ላይ ያተኮረ ስልጠና ምቹ የስልጠና ክፍለ-ጊዜዎች ብቁ እና ልምድ ያላቸው አሰልጣኞች ስልጠናውን በጥራት ላጠናቀቁ የምስክር ወረቀት   🎯 ማሳሰቢያ: የስልጠናው ቦታ ውስን ስለሆነ ፈጥነው በመመዝገብ የዕድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ!   📞 ለበለጠ መረጃና ምዝገባ አድራሻ: -  ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስልክ ቁጥር: 0913143307 ወይም 0911105037   "ክህሎት ያነገበ ትውልድ — ለቀጣይ ብሩህ ተስፋ!"

የ16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት አውደ-ርዕይ በደመቀ ሁኔታ ተጠናቀቀ። 🇪🇹አዲስ አበባ | ሚያዝያ 28/2018 ዓ.ም🇪🇹 ላለፉት ቀናት በአራዳ ፓርክ "የቴክኖሎጂ ልህቀት ለአገር ብልጽግና" በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የቆየው 16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት አውደ-ርዕይና የፈጠራ ስራዎች ውድድር ዛሬ በደመቀ ስነ-ስርዓት ተጠናቋል። በማጠቃለያው ፕሮግራም ላይ ንግግር ያደረጉት አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ፤ የቴክኖሎጂ ታሪክ የኢኮኖሚ ልማት ታሪክ መሆኑን በጥልቀት በመተንተን፣ ባለፉት ቀናት የቀረቡት የፈጠራ ስራዎች የሀገሪቱን የልማት ተስፋና ተጨባጭ እንቅስቃሴ የሚያመላክቱ ናቸው ብለዋል። መንግስት የክህሎት መር የሥራ ስምሪትን እንደ ዋነኛ ፖሊሲ በመከተሉ፣ ወጣቶች ያላቸውን እምቅ አቅም በተግባር እንዲያሳዩና በ21ኛው ክፍለ ዘመን ራሳቸውን በእውቀት፣ በክህሎትና በስነ-ምግባር በማነጽ ለሀገራቸው ብልጽግና እንዲተጉ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አብራርተዋል። አክለውም፣ ወጣቶች የሥራን ክብር በመረዳትና ዲጂታል ክህሎታቸውን በማሳደግ የሀገር ግንባታ አካል እንዲሆኑና የጀመሩትን የፈጠራ ስራ ወደ ቢዝነስ በመቀየር ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ አደራ ብለዋል። የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሚደቅሳ ከበደ በበኩላቸው፣ የዘንድሮው አውደ-ርዕይ ቴክኖሎጂዎችን ለዕይታ ብቻ ከማቅረብ ባለፈ በቀጥታ ወደ ፋብሪኬሽን ኢንጂነሪንግ በማሸጋገር ለተጠቃሚው ተደራሽ እንዲሆኑ የሚያስችል አዲስ ስትራቴጂ የተተገበረበት መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የውጭ ምንዛሬን የሚያድኑ ተኪ ምርቶችን ማምረት እንደሚችሉ በተግባር ያረጋገጡበት መድረክ መሆኑን ጠቁመዋል። በዕለቱ በቴክኖሎጂ ፈጠራ፣ በዲጂታል  አይሲቲ ቴክኖሎጂዎች ፈጠራ፣ በፋሽን ዲዛይን ፤ በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር ከፍተኛ ውጤት እንዲሁም በ ስፖርት ዉድድር አሸናፊ በመሆን በደረጃ ለወጡት  የእውቅና እና የሽልማት ስነ-ስርዓት ተካሂዷል። የተጀመረው የቴክኖሎጂ ሽግግርና የምርት መተካት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለጽ የዝግጅቱ ፍጻሜ ሆኗል። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  👉 Tiktok https://www.tiktok.com/@bols20116?_t=ZM-8y9L28EOubG&_r=1 👉Facebook https://www.facebook.com/addisababatvetbureau 👉Telegram https://t.me/AABOLS 👉YouTube https://youtube.com/@bureauoflaborandskill?si=t9ZklwKzGx9rRyXf 👉website https://aabols.gov.et 👉ለቅሬታ፣ አስተያየትና ጥቆማ https://complain.aabols.gov.et 👉ለነፃ የስልክ ጥሪ 6524

                                                                                                  ሰኞ:- ሚያዚያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም 16ኛው ከተማ አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ዓውደ-ርዕይ በአራዳ ፓርክ ተከፈተ!! “የቴክኖሎጂ ልህቀት ለሀገር ብልጽግና!” በሚል መሪ ቃል ለተከታታይ ሦስት ቀናት የሚቆየው 16ኛው ከተማ አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ዓውደ-ርዕይ ዛሬ በአራዳ ፓርክ በድምቀት ተከፍቷል። ይህ ዓመታዊ ዓውደ-ርዕይ የብልፅግና ተምሳሌት የሆነችው አዲስ አበባ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያላትን ተወዳዳሪነት በተግባር የምታሳይበት መድረክ መሆኑ ተገልጿል። በዕለቱም የሚሰሩ እጆችና የሚፈጥሩ አዕምሮዎች ለሀገር ግንባታ ያላቸው መሠረታዊ ሚና ጎልቶ ታይቷል። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በቴክኖሎጂ ፈጠራ፣ ቴክኖሎጂን በመቅዳትና መልሶ በመጠቀም የዓለምን ፈጣን እድገት መቀላቀል መቻሏን የገለጹት የከተማው ከፍተኛ አመራሮች፣ በተለይም የውጭ ምንዛሪ እጥረትን የሚቀንሱ ተኪ ምርቶችን በማምረት ረገድ ትላልቅ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑን አብራርተዋል። በከተማዋ ፈጣን እድገት ውስጥ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ያላቸው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን፣ በቀጣይም ተቋማቱ ውጤታቸውን እንዲያሰፉ ጥሪ ቀርቧል። በተለይም የተለወጠ የሥራ ባህል መተግበር፣ የፈጠራ ስራዎችን ማጠናከር፣ የሀገሪቱን የልማት ፍላጎት የሚመጥኑ ብቁ ባለሙያዎችን ማፍራት ላይ ትኩረት እንዲደረግ አሳስበዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለቴክኒክና ሙያ ዘርፉ የሚያደርገውን ያልተቋረጠ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በድጋሚ አረጋግጧል። በመጨረሻም ይህን ደማቅ ዓውደ-ርዕይ በቅንጅት ላዘጋጁ የሥራ እና ክህሎት ቢሮ አመራሮች፣ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ አሰልጣኞች፣ ሠራተኞችና ሰልጣኞች ላበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ ምስጋና ቀርቦላቸዋል።        "በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"

የኢንዱስትሪ አብዮትና የሰው ልጅ ወደ ማሽንነት የተቀየረበት ጥቁር ዘመን። ከ140 ዓመታት በፊት የተከሰተው የኢንዱስትሪ አብዮት ለዓለም አዲስ የቴክኖሎጂ ብርሃን ይዞ የመጣ ቢመስልም፣ በስተጀርባው ግን በታሪክ የማይረሳ ሰብዓዊ ስቃይን አዝሎ ነበር። በወቅቱ የነበረው የካፒታሊዝም ሥርዓት ሰራተኛውን እንደ ሰው ሳይሆን እንደ አንዱ የፋብሪካ ማሽን ይቆጥረው ነበር። ሠራተኞች ከማለዳው 11 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 4 ሰዓት ድረስ ለ16 ሰዓታት ያለ እረፍት እንዲሠሩ ይገደዱ ነበር። በተለይም ሕፃናት በትምህርት ገበታ ፋንታ በፋብሪካ ጭስ ውስጥ እንዲታፈኑ መደረጋቸውና እናቶች ያለምንም የወሊድ ፈቃድ በቆሙበት እንዲወልዱ መገደዳቸው የዘመኑን እጅግ አሰቃቂ ገጽታ ያሳያል። ይህ "ጥቁር ህልም" የሰው ልጅ ሰብዓዊነት ክብር የወደቀበትና ጉልበት በግፍ የሚበዘበዝበት ወቅት ነበር። የቺካጎው ትግልና የመብት ማስከበር መስዋዕትነት ይህ መጠነ ሰፊ ግፍና በደል የወለደው መራራ ትግል በ1886 (እ.ኤ.አ) በቺካጎ ከተማ ፈነዳ። ሠራተኞች "እኛ ማሽን አይደለንም፣ ሰው ነን!" በሚል ጽኑ ድምፅ አደባባይ ወጡ። "8 ሰዓት ለሥራ፣ 8 ሰዓት ለዕረፍት፣ 8 ሰዓት ለእንቅልፍ" የሚለው ታሪካዊ ጥያቄ የዛሬው ዓለም አቀፍ የሥራ መመሪያ መሠረት ነው። ይሁን እንጂ ይህ ጥያቄ በቀላሉ አልተመለሰም፤ የሠራተኞች ደም ፈሷል፣ በጠመንጃ ጥይት ተቆልተዋል፣ ብዙዎችም በአደባባይ ተሰቅለዋል። ዛሬ የምናገኘው የሳምንት ዕረፍት፣ የወሊድ ፈቃድ፣ የትርፍ ሰዓት ክፍያና የሥራ ቦታ ደህንነት መብቶች በሙሉ በነዚያ ጀግኖች ደምና አጥንት የተገነቡ እንጂ በነፃ የተገኙ ስጦታዎች አይደሉም። የስራና ክህሎት ቢሮ ተልዕኮ፦ ሰብዓዊነትን የተላበሰ የስራ አካባቢ በኢትዮጵያም ሆነ በከተማችን አዲስ አበባ፣ የሥራና ክህሎት ቢሮ የተቋቋመው እነዚህን በደም የመጡ የሠራተኛ መብቶችን ለማስከበርና ለዜጎች ምቹ የሥራ ሁኔታን ለመፍጠር ነው። የቢሮው ተልዕኮ ዜጎች በክህሎት የበለፀጉና በሥራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ማብቃት ብቻ ሳይሆን፣ የሠራተኛውና የአሠሪው ግንኙነት በሕግና በሥርዓት እንዲመራ ማድረግ ነው። ቢሮው የሥራ ቦታ ደህንነትን በማረጋገጥ፣ ተገቢውን የሥራ ሰዓትና ክፍያ በመከታተል፣ እንዲሁም የኢንዱስትሪ ሰላምን በማስፈን የሠራተኛውን ሰብዓዊ ክብር የመጠበቅ ታሪካዊ አደራ አለበት። ይህም ትላንት በቺካጎ የተጀመረውን የፍትህ ትግል በዘመናዊና በተቋማዊ መንገድ የማስቀጠል ሥራ ነው። የክህሎት ልማት ለተሟላ የሠራተኛ ክብር በዛሬው ዘመን የሠራተኛው ቀን ሲከበር ከመብት ጥያቄ ባሻገር "ክህሎትን" ማሳደግ የክብር መገለጫ ሆኗል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ዜጎችን በቴክኒክና ሙያ በማሰልጠንና ብቁ በማድረግ፣ ሠራተኛው በጉልበቱ ብቻ ሳይሆን በዕውቀቱና በቴክኖሎጂ ታግዞ ራሱንና ሀገሩን እንዲለውጥ እየሠራ ይገኛል። ሚያዝያ 23 ስናከብር፣ በትላንትናው መስዋዕትነት የተገኘውን መብት እያከበርን፣ በዛሬው የክህሎት ልማት ደግሞ የሠራተኛውን ተወዳዳሪነትና ምርታማነት ለማረጋገጥ ቃል የምንገባበት ቀን ነው። የሠራተኛው ክብር የሚጠበቀው መብቱ ሲከበርና ለሥራው የሚመጥን ዕውቀትና ጥበብ ሲታጠቅ ብቻ በመሆኑ፣ ቢሮው ይህንን የተቀደሰ ዓላማ ከግብ ለማድረስ ሌት ተቀን ይተጋል። ለሀገር ሰራተኞች በሙሉ ክብር ይገባችኋል! መልካም የሰራተኞች ቀን! 🇪🇹 ሚያዝያ 23/2018 ዓ.ም 🇪🇹 <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://aabols.gov.et/qr.html

የሠራተኛው መብት መከበር ለኢንዱስትሪ ሰላምና ለምርታማነት መሠረት ነው! 🇪🇹 ሚያዝያ 23/2018 ዓ.ም 🇪🇹 በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ137ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ51ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም የላብ አደሮች ቀን (ሜይ ዴይ) አስመልክቶ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሠራተኛ ወሳኝ ቦርድ በኢንዱስትሪ ሰላምና በሠራተኞች ደህንነት ዙሪያ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጿል። በአሁኑ ወቅት በከተማችን አዲስ አበባ እየተስፋፉ የመጡት አምራች ኢንዱስትሪዎችና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ በማሳደግና የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ የላቀ ድርሻ እየተጫወቱ ይገኛሉ። ይሁን እንጂ እነዚህ ተቋማት ውጤታማና ምርታማ እንዲሆኑ በሥራ አካባቢ አስተማማኝ የደህንነትና የጤንነት ጥበቃ ሥርዓት መዘርጋት እንዲሁም የኢንዱስትሪ ሰላምን ማስፈን ለነገ የማይባል ተግባር መሆኑ ይታመናል። የዓለም የሠራተኞች ቀን ወይም ሜይ ዴይ በዓለም ዙሪያ መከበር የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ አካባቢ ሲሆን በተለይም በ1886 እ.ኤ.አ በቺካጎ የነበረው የሠራተኞች የሥራ ሰዓት እንዲቀነስና መብታቸው እንዲከበር ያደረጉትን ተጋድሎ የሚዘክር ነው። ይህ ታሪካዊ ክስተት በዓለም ዙሪያ ለሠራተኛው መብት መከበር፣ ለተሻለ የሥራ ሁኔታና ለሰብአዊ ክብር መከበር መሠረት በመጣል ዛሬ ለደረስንበት ዓለም አቀፍ የአሰሪና ሠራተኛ ሕጎች መፈጠር ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል። በሀገራችን ኢትዮጵያም ይህ በዓል ለ51ኛ ጊዜ መከበሩ  ሀገሪቱ በኢንዱስትሪ ልማትና በሠራተኛው መብት ጥበቃ ረገድ የሄደችበትን ረጅም ጉዞ የሚያሳይ ነው። ላለፉት አምስት አስርት ዓመታት የሠራተኛው መብት በሕግ እንዲጠበቅ፣ የማህበራት አደረጃጀት እንዲጠናከርና በአሰሪና ሠራተኛ መካከል በውይይት ላይ የተመሠረተ ግንኙነት እንዲሰፍን በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል። የዘንድሮው በዓል ደግሞ ምርታማነትን ከደህንነት ጋር በማቆራኘት አዲስ ምዕራፍ ለመጀመር ያለመ ነው። ይህንን ዓላማ ከግብ ለማድረስ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የሙያ ደህንነትና ጤንነት አጠባበቅ ፖሊሲዎችን እንዲሁም ተያያዥ ሕጎችንና መመሪያዎችን በአምራች ኢንዱስትሪዎችና በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ውስጥ ተግባራዊ እንዲሆኑ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። በተለይም በሥራ ቦታ ላይ የሚከሰቱ አለመግባባቶችን በሕጋዊ መንገድ ለመፍታትና የሰራተኛውን መብትና ደህንነት ለማስጠበቅ የአሰሪና ሰራተኛ ወሳኝ ቦርድ የፍትህ ሥርዓቱ ዋነኛ አካል ሆኖ በመንቀሳቀስ ላይ መሆኑ ተመልክቷል። ዘንድሮ “የሠራተኛው መብት መከበር ለኢንዱስትሪ ሰላምና ለምርታማነት መሠረት ነው!” በሚል መሪ ቃል ሚያዝያ 23 ቀን የሚከበረውን የሜይ ዴይ በዓል መነሻ በማድረግም እነዚህ የቁጥጥርና የድጋፍ ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሠራተኛ ወሳኝ ቦርድ ዳይሬክተር አቶ ካሳ ስዩም እንደገለጹት ቢሮው የሥራ ሁኔታ ቁጥጥር አገልግሎትን ይበልጥ ተደራሽ በማድረግ በየዓመቱ በአማካይ ከ12 ሺህ በላይ የሙያ ደህንነት አጠባበቅ ቁጥጥሮችን ያካሂዳል። ይህ ቁጥጥር በተለይ በርካታ ሠራተኛ በሚገኝባቸውና ከፍተኛ የአደጋ ስጋት ባለባቸው ኢንዱስትሪዎች ላይ ትኩረት የሚያደርግ ሲሆን በቁጥጥር ወቅት የሚታዩ ክፍተቶችን መሠረት በማድረግ ተቋማት አስፈላጊውን ማስተካከያ እንዲያደርጉ መመሪያና ትዕዛዝ ይሰጣል። ዳይሬክተሩ አክለውም የሥራ ላይ አደጋ ከደረሰ በኋላ ከሚከፈል ካሳ ይልቅ አደጋ እንዳይደርስ አስቀድሞ መከላከል ለሀገርም ሆነ ለድርጅቶች ትልቅ ትርጉም እንዳለው አስገንዝበዋል። ይህንን ክፍተት ለመሙላትና የዘንድሮውን የሜይ ዴይ በዓል መሪ ቃል በተግባር ለመተርጎም ቢሮው ለሴፍቲ ኮሚቴዎች፣ ለድርጅት ማኔጅመንት አካላትና ለሠራተኛ ማህበር አመራሮች ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል። በተለይም የግል መከላከያ መሣሪያዎች አቅርቦትና አጠቃቀምን፣ እንዲሁም የሥራ አካባቢ ልኬቶችን በአግባቡ ተግባራዊ በማድረግ አደጋዎችን ለመከላከል በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን አቶ ካሳ ስዩም አስረድተዋል። የአሰሪና ሠራተኛ ወሳኝ ቦርድ እንደ አንድ የፍትህ ተቋም በሥራ ቦታ ላይ የሚከሰቱ የጋራ የሥራ ክርክሮችን በሦስትዮሽ መድረክ በማስማማትና ውሳኔ በመስጠት የኢንዱስትሪ ሰላምን የማረጋገጥ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል። የዘንድሮው የሜይ ዴይ በዓል የሠራተኛው መብት መከበር ለኢንዱስትሪ ሰላምና ለምርታማነት ያለው ፋይዳ ጎልቶ የሚታይበት ሲሆን የአሰሪና ሠራተኛ ወሳኝ ቦርድም ይህንኑ መርህ መሠረት በማድረግ አደጋን በመከላከልና የፍትህ ሥርዓቱን በማጠናከር ረገድ የጀመረውን ውጤታማ ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል። የከተማዋን የኢኮኖሚ እድገት ዘላቂ ለማድረግም በየደረጃው የሚገኙ አሰሪዎችና ሠራተኞች ለሥራ አካባቢ ደህንነት ትኩረት በመስጠትና በጋራ በመሥራት ለምርታማነት መጨመር የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ ቀርቧል። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html

ረቡዕ:- ሚያዚያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም "ክህሎትን በቋንቋ፣ ሙያን በቴክኖሎጂ"፦ በጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተሰጠው ልዩ ስልጠና በስኬት ተጠናቀቀ!! በጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፣ በቻይናው ሻንዚ ፖሊቴክኒክ ዩኒቨርሲቲ እና በዓለም አቀፉ የቻይና ኮንስትራክሽን ኮሙኒኬሽን ካምፓኒ (CCCC) መካከል የተመሰረተው የሦስትዮሽ ትብብር፣ ለወጣቶች የክህሎት ልማት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር አሳይቷል። ለሳምንታት በቆየው ከፍተኛ ስልጠና ላይ ሲሳተፉ የቆዩ ከኮንስትራክሽንና ከኤሌክትሪክ ዲፓርትመንት የተመረጡ 73 ሰልጣኞች ዛሬ በድምቀት ተመርቀዋል። በፕሮግራሙ ላይ ክቡር ሚስተር ቼን ሃይ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር፣ ሚስተር ዌይ ቺያንግዩ በኢትዮጵያ የCCCC ጀነራል ማኔጀር፣ እንዲሁም ከሻንዚ ፖሊቴክኒክ ዩኒቨርሲቲ እና ከሲሲሲሲ (CCCC) የመጡ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን አባላት ተገኝተዋል። አምባሳደር ቼን ሃይ በዕለቱ እንደገለጹት ይህ ስልጠና በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን "የቴክኒክና ሙያ ዲፕሎማሲ" የሚያጠናክርና ኢትዮጵያ ለጀመረችው የኢንዱስትሪ ልማት ብቁ የሰው ኃይል የሚያፈራ ነው። ብለዋል፡፡ ስልጠናው ቻይንኛ ቋንቋና ሙዊ ክህሎት ላይ ያተኮረ ሲሆን ሰልጣኞችን ለዘመናዊው የሥራ ዓለም ዝግጁ ያደርጋቸዋል ተብሏል፡፡ ሰልጣኞቹ እንደ CCCC ባሉ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ውስጥ ሲገቡ በቀላሉ መግባባትና ቴክኖሎጂውን በፍጥነት መረዳት እንዲችሉ የቋንቋ ክህሎታቸውን የሚያዳብርላቸው ሲሆን በኮንስትራክሽንና በኤሌክትሪክ ዘርፎች ላይ የተሰጠው ይህ ስልጠና የሻንዚ ፖሊቴክኒክ ዩኒቨርሲቲን የላቀ ዕውቀትና የCCCCን ዘመናዊ የኢንዱስትሪ አሰራር ወደ ሰልጣኞቹ ለማሸጋገር ያለመ ነው ተብሏል፡፡ በሌላ በኩል የጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ መለሰ ይግዛው ይህ ስልጠና ኮሌጁ ከፕሮጀክት ተኮር ስራዎች ወጥቶ ወደ ስትራቴጂካዊ ዓለም አቀፍ አጋርነት መሸጋገሩን የሚያሳይ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ስልጠና እንደ መነሻ ተወስዶ ወደፊት በሚኖረው ትስስር ሻንዚ ፖሊቴክኒክ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የሥርዓተ-ትምህርት ድጋፉን በማስቀጠል ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ባለሙያዎችን ማፍራት የሚቀትል ሲሆን CCCC ለሰልጣኞች የሥራ ዕድልን በማመቻቸትና በግዙፍ ፕሮጀክቶች ላይ በማሳተፍ ተግባራዊ የክህሎት ሽግግርን ያረጋግጣል፡፡ በተመሳሳይ ጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የኢትዮጵያን የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የሚመራ የልህቀት ማዕከል ሆኖ ያገለግላል፡፡ CCCC በዓለም አቀፍ ደረጃ በFortune Global 500 ዝርዝር ውስጥ የሚገኝ፣ በመሠረተ ልማት ግንባታና በኢንጂነሪንግ ዘርፍ ግንባር ቀደም የሆነ ግዙፍ ካምፓኒ ሲሆን በኢትዮጵያ እንደ አዲስ-አዳማ ፈጣን መንገድ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ይታወቃል፡፡ ካምፓኒው አሁን ደግሞ ከግንባታው ጎን ለጎን ለሀገራችን ወጣቶች የክህሎትና የቴክኖሎጂ ሽግግር በማድረግ ረገድ ትልቅ አሻራውን እያሳረፈ ይገኛል። ‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››