uk
Feedback
General Wingate Polytechnic college-Official channel

General Wingate Polytechnic college-Official channel

Відкрити в Telegram

ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን። የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу General Wingate Polytechnic college-Official channel

Канал General Wingate Polytechnic college-Official channel (@wingetpolytechniccollege) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 12 374 підписників, посідаючи 15 980 місце в категорії Освіта та 2 722 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 12 374 підписників.

За останніми даними від 30 серпня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 62, а за останні 24 години на 14, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 44.19%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 17.15% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 461 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 119 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 51.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን። የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 31 серпня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Освіта.

12 374
Підписники
+1424 години
+707 днів
+6230 день
Архів дописів
ሐሙስ:- ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ∙ም   በፋዌ (FAWE) እና ማስተርካርድ ፋውንዴሽን ዓመታዊ ጉባኤ ላይ የኮሌጁ አሰልጣኝና ሰልጣኝ እውቅና ተበረከተላቸው፡፡   ኮሌጃችን በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል (AICC) በተካሄደው የፋዌ (FAWE) እና ማስተር ካርድ ፋውንዴሽን 2ኛ ምዕራፍ የ2026 ዓመታዊ የሰልጣኞች ጉባኤ ላይ በዛሬው ዕለት ተሳትፏል።   የአፍሪካ ሴት የትምህርት ባለሙያዎች ፎረም (FAWE) ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር የሚተገብረው ይህ የትምህርትና ስልጠና ድጋፍ ፕሮግራም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተተገበረባቸው ሁለት ተቋማት አንዱ ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሲሆን በአሁኑ ወቅት 59 የኮሌጁ ሰልጣኞች የዚህ ፕሮግራም ተጠቃሚ ናቸው።   በጉባኤው ላይ "የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞችን የተቅጣሪነት እና የስራ ፈጠራ እድሎች ማጠናከር" (Strengthening Employability and Entrepreneurship Pathways for TVET Students) በሚል ርዕስ የፓናል ውይይት የተካሄ ሲሆን በውይይቱ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ከማስተርካርድ ፋውንዴሽን፣ ከፋዌ፣ ከኢንዱስትሪው ዘርፍ እና ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የተውጣጡ አመራሮች ተሳትፈዋል።    ውይይቱ ሰልጣኞችን ከገበያው ፍላጎት ጋር የሚጣጣም ክህሎት በማስጨበጥ፣ የኢንዱስትሪ ትስስርን በማስፋት እና ለግል ስራ ፈጠራ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ዙሪያ ያተኮረ ነበር።   ከዕለቱ መርሃ-ግብር ክንዋኔዎች መካከል አንዱ የእውቅና እና ሽልማት ስነ-ስርዓት ሲሆን በዚህም በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በላቀ ስራ ሰልጣኞችን በማብቃትና በመደገፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱት የኮሌጁ የፊዚኮ-ኬሚካል አሰልጣኝ ወ/ሮ ጸሐይ አህመድ የታብሌት ሽልማት ሲበረከትላቸው በተመሳሳይ ከተቋማችን ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገበቺው ሰልጣኝ ሀና ቢራራ የስማርት ፎን ማበረታቻ ተሰጥቷታል፡፡     ፋዌ (FAWE) ከማስተርካርድ ፋውንዴሽን በሚያገኘው የገንዘብ ድጋፍ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በአማራ፣ በኦሮሚያና ሲዳማ ክልሎች በሚገኙ 6 ፖሊ ቴክኒኮች ላይ እየሰራ ያለ ድርጅት ነው፡፡     "በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"

ቅዳሜ:- ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ∙ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ!! የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ መደረጉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። በዘመኑ ፈተናውን ለ
+1
ቅዳሜ:- ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ∙ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ!! የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ መደረጉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። በዘመኑ ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡ 563 ሺህ 960 ተማሪዎች መካከል 550 ሺህ 210 ተማሪዎች ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 12.8 በመቶ (70 ሺህ 544 ተማሪዎች) 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ በማምጣት ማለፍ ችለዋል። 50ከመቶ እና ከዚያ በላይ ካመጡ ተማሪዎች መካከል በተፈጥሮ ሳይንስ 16.5 በመቶ እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ 8.33 በመቶ ናቸው። የተመዘገቡ ከፍተኛ ውጤቶችን በተመለከተ ተፈጥሮ ሳይንስ በወንድ 591.6 ከ 600 እና በሴት 583 ከ 600 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ በወንድ 576.2 እና በሴት 569.1 ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንደገለጹት የዘንድሮው ውጤት ከባለፉት ዓመታት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ በመሆኑ የሚቀበሉት የሬሚዲያል ተማሪዎች ቁጥር የሚቀንስ ሲሆን የመቁረጫ ነጥቡ ወደፊት የሚገለጽ ይሆናል። ተማሪዎች ውጤታቸውን ከሰኞ ጠዋት ወይም ማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መመልከት የሚችሉ ሲሆን ቅሬታ ያላቸው ተማሪዎችም ለ5 እና 6 ቀናት ቅሬታ ማቅረብ ይችላሉም ተብሏል። የብሔራዊ ፈተና ውጤት መለቀቁን ተከትሎ ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅም የስራና ክህሎት ሚኒስቴር በሚቆርጠው የመግቢያ ነጥብ መሠረት የ2019 ዓ.ም አዲስ ሰልጣኞችን ለመቀበል ሙሉ ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል። ኮሌጁ በ12 ዲፓርትመንቶች እና 30 በሚደርሱ የሙያ መስኮች በቀን፣ በማታ እና በቅዳሜና እሁድ መርሃ ግብሮች ለማሰልጠን ሰብዓዊና ቁሳዊ ግብዓቶችን በማሟላት አዲስ ሰልጣኞችን ለመቀበል ዝግጁ ነው። "በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"

ሐሙስ:- ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ∙ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ!! የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ መደረጉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። በዘመኑ ፈተናውን ለ
+1
ሐሙስ:- ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ∙ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ!! የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ መደረጉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። በዘመኑ ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡ 563 ሺህ 960 ተማሪዎች መካከል 550 ሺህ 210 ተማሪዎች ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 12.8 በመቶ (70 ሺህ 544 ተማሪዎች) 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ በማምጣት ማለፍ ችለዋል። 50ከመቶ እና ከዚያ በላይ ካመጡ ተማሪዎች መካከል በተፈጥሮ ሳይንስ 16.5 በመቶ እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ 8.33 በመቶ ናቸው። የተመዘገቡ ከፍተኛ ውጤቶችን በተመለከተ ተፈጥሮ ሳይንስ በወንድ 591.6 ከ 600 እና በሴት 583 ከ 600 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ በወንድ 576.2 እና በሴት 569.1 ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንደገለጹት የዘንድሮው ውጤት ከባለፉት ዓመታት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ በመሆኑ የሚቀበሉት የሬሚዲያል ተማሪዎች ቁጥር የሚቀንስ ሲሆን የመቁረጫ ነጥቡ ወደፊት የሚገለጽ ይሆናል። ተማሪዎች ውጤታቸውን ከሰኞ ጠዋት ወይም ማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መመልከት የሚችሉ ሲሆን ቅሬታ ያላቸው ተማሪዎችም ለ5 እና 6 ቀናት ቅሬታ ማቅረብ ይችላሉም ተብሏል። የብሔራዊ ፈተና ውጤት መለቀቁን ተከትሎ ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅም የስራና ክህሎት ሚኒስቴር በሚቆርጠው የመግቢያ ነጥብ መሠረት የ2019 ዓ.ም አዲስ ሰልጣኞችን ለመቀበል ሙሉ ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል። ኮሌጁ በ12 ዲፓርትመንቶች እና 30 በሚደርሱ የሙያ መስኮች በቀን፣ በማታ እና በቅዳሜና እሁድ መርሃ ግብሮች ለማሰልጠን ሰብዓዊና ቁሳዊ ግብዓቶችን በማሟላት አዲስ ሰልጣኞችን ለመቀበል ዝግጁ ነው። "በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"

ሐሙስ:- ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ∙ም አንጸባራቂ ድል ለጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ!! አንጋፋውና በክህሎት ስልጠና ዘርፍ ግንባር ቀደም የሆነው ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 በጀት ዓመት ባስመዘገበው የላቀ አፈፃፀም በከተማ አቀፍ ደረጃ የ2ኛ ደረጃን  ድል ተቀዳጅቷል። ኮሌጁ ይህንን ትልቅ ስኬት ያረጋገጠው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ሥር በሚገኙ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች መካከል በተካሄደው ምዘና ነው። በቢሮው በተካሄደው የ2018 በጀት ዓመት የግብ ተኮር (KPI) እና የቁልፍ ተግባራት አፈፃፀም ምዘና መሠረት ኮሌጃችን 94.26% ከፍተኛ ውጤት ማምጣት ችሏል። ይህ ምዘና የተቋማትን የመማር ማስተማር ጥራት፣ የአሰራር ቅልጥፍና፣ የተገልጋይ እርካታን እንዲሁም በተቋማዊ አቅም ግንባታ የተከናወኑ ዐበይት ተግባራትን በሚገባ የፈተሸ ሲሆን ኮሌጁ በሁሉም መለኪያዎች ልቆ መገኘት ችሏል። ኮሌጁ ባስመዘገበው በዚህ የላቀ አፈጻጸም  የዕውቅናና ሽልማት የምስክር ወረቀት የተሰጠው ሲሆን ይህ ክብር የተቋሙ አመራሮች፣ አሰልጣኝና የአስተዳደር ሠራተኞች ዓመቱን ሙሉ ላሳዩት ያላሰለሰ ጥረት፣ ቁርጠኝነት እና ጠንካራ የቡድን መንፈስ የተሰጠ እውነተኛ ማሳያ ነው። ይህ አሸናፊነት ኮሌጁ ለጥራት ማረጋገጥ ስርዓት የሚሰጠውን ከፍተኛ ትኩረትና ተቋማዊ አሰራሩን ለማዘመን እያደረገ ያለውን ስኬታማ ጉዞ በጉልህ የሚያንፀባርቅ ነው። የኮሌጁ ማህበረሰብ በዚህ በተገኘው ስኬት በመኩራት በቀጣይ የ2019 በጀት ዓመት ከዚህም ላቀ ደረጃ ለመድረስና የ1ኛ ደረጃ አሸናፊነትን ለመቀዳጀት በበለጠ ተነሳሽነት ዝግጅቱን ጀምሯል። ለዚህ ታላቅ ስኬት መገኘት ከፍተኛ አስተዋፅዖ ላበረከታችሁ የኮሌጃችን ቤተሰቦች በሙሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታችንን እያስተላለፍን በቀጣይ የጀመርነውን የላቀ አፈፃፀም አጠናክረን እንድንቀጥል ጥሪያችንን እናቀርባለን። "በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"

ኢትዮጵያ በአፍሪካ መድረክ ላይ! 🇪🇹🌍 PICE በASEB 2026 የTOP 5 የመጨረሻ ተወዳዳሪዎች ውስጥ መመረጡን በደስታ እንገልጻለን። ይህ የሽልማት ውድድር ብቻ አይደለም። ይህ የኢትዮጵያን የ
ኢትዮጵያ በአፍሪካ መድረክ ላይ! 🇪🇹🌍 PICE በASEB 2026 የTOP 5 የመጨረሻ ተወዳዳሪዎች ውስጥ መመረጡን በደስታ እንገልጻለን። ይህ የሽልማት ውድድር ብቻ አይደለም። ይህ የኢትዮጵያን የፈጠራ፣ የቴክኒክ ክህሎት፣ የሥራ ፈጠራ እና የምርታማነት አቅም ለአፍሪካ የምናሳይበት እድል ነው። 🗳️ ለPICE ድምጽዎን ይስጡ! 🙏 ይምረጡ 📲 ያጋሩ 👥 ጓደኞችዎን ያሳትፉ 🌍 የኢትዮጵያን ድምፅ በአፍሪካ ያሰሙ! አንድ ድምፅ። አንድ ድምጽ ማሰማት። አንድ የአፍሪካ ተፅዕኖ። 🇪🇹🌍 VOTE ON;- https://www.asebs.com/finalists/productivity-improvement-center-of-excellence-coworking-space

ሐሙስ:- ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ∙ም   የጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን ድህረ-EASTRIP ፕሮጀክት ዘላቂነት የሚያረጋግጥ የምክክር መድረክ ተካሄደ!!   የEASTRIP ፕሮጀክት መጠናቀቅን ተከትሎ የጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን ሁለንተናዊ የለውጥ ጉዞ ለማስቀጠል የሚያስችል የዘላቂነት ማስተር ፕላን ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሄደ።   በዚህ መድረክ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ በከተማ አስተዳደሩ ስር የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ዲኖች፣ የኢንዱስትሪ ተወካዮች  ተሳትፈዋል።    የምክክር መድረኩ ዋና ዓላማ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ተቋማት ከፕሮጀክት ጥገኝነት በመውጣት ራሳቸውን ችለው መቀጠል እንዲችሉና ከፕሮጀክት ድጋፍ ወደ መንግሥትና የግል ዘርፍ አጋርነት (PPP) የሚሸጋገርበትን ስልታዊ አቅጣጫ ማስቀመጥ እንደሆነ ተገልጿል።   በግምገማው ወቅት ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ኮሌጁ ራሱን ችሎ መቀጠል እንዲችል የውስጥ የገቢ አቅሙን የሚያሳድግበት ስልታዊ አቅጣጫዎች የተቀመጡ ሲሆን ሌሎች ኮሌጆችም የጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን መልካም ተሞክሮ በመውሰድ ለውጥ ለማምጣት ትልቅ መነቃቃት ሊፈጥሩ እንደሚገባ ተመላክቷል።   በአሁኑ ወቅት በአጋርነት ከጀነራል ዊንጌት ጋር አብሮ ለመሥራት ፍላጎት አሳይተው ወደ ሥራ የገቡ በርካታ አካላት መኖራቸውንና በቀጣይም አብረው ለመሥራት አቅደው በዝግጅት ላይ ያሉ በርካቶች መሆናቸው ተገልጿል።   ከጋራ ውይይቱ በተጨማሪ በተካሄዱ ተናጠል ስብሰባዎች የቢሮው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና የኮሌጅ ዲኖች በግልና መንግሥት አጋርነት (PPP) አተገባበር ዙሪያ ትኩረት አድርገው የመከሩ ሲሆን በተመሳሳይ መልኩ የአድቫይዘሪ ቦርድ አባላት በበኩላቸው የነበራቸውን የሥራ እንቅስቃሴና አፈፃፀም ገምግመው በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት አድርገዋል።   የመድረኩ ተሳታፊዎች ፕሮጀክቱ ለሀገሪቱ ብቁና የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት ያለውን ከፍተኛ ፋይዳ በማድነቅ በቀሪው የፕሮጀክት የሥራ ጊዜ የሚከናወኑ ተግባራት በግልጽ ዕቅድና መሪ አቅጣጫ እንዲመሩ በጋራ ስምምነት ላይ ደርሰዋል። በተለይም በኮሌጆችና በኢንዱስትሪዎች መካከል ያለው ቅንጅትና ትስስር ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ የቀረበ ሲሆን ውይይቱ የኮሌጆችን ዘላቂ እድገት ለማረጋገጥ ትልቅ መሠረት የጣለ እንደነበር ተጠቁሟል።   "በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"

ማክሰኞ:- ሐምሌ  28 ቀን 2018 ዓ.ም     የኮንስትራክሽን ዲፓርትመንት በድምቀት የተጠናቀቀው የጀነራል ዊንጌት የክረምት እግር ኳስ ውድድር ሻምፒዮን ሆነ!   በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሲካሄድ የቆየው የአሰልጣኞች የክረምት ስፖርታዊ የእግር ኳስ ውድድር እጅግ ማራኪ እና ፉክክር በታከለበት የፍፃሜ ጨዋታ በዛሬው ዕለት በድምቀት ተጠናቋል። በጉጉት ሲጠበቅ በነበረው የዋንጫ ጨዋታ የኮንስትራክሽን ዲፓርትመንትን ድንቅ ብቃት በማሳየት የዘንድሮው የዋንጫ አሸናፊ መሆን ችሏል።   ለፍፃሜው ደርሰው ዋንጫውን ለማንሳት የተፋለሙት አይሲቲ ዲፓርትመንት (Wingate Best) እና ኮንስትራክሽን ዲፓርትመንት ያደረጉት ጨዋታ በእግር ኳስ አፍቃሪዎች ዘንድ ከፍተኛ አድናቆትን ያተረፈ ነበር። ከጨዋታው በፊት ለዋንጫው ሰፊ ቅድመ ግምት ተሰጥቷቸው የነበሩት የአይሲቲ ዲፓርትመንት ተጫዋቾች የጨዋታ የበላይነት በመውሰድ የመጀመሪያውን ግብ ከመረብ ጋር ማዋሃድ ቢችሉም ኮንስትራክሽኖች በአጭር ጊዜ ውስጥ አቻ የሚያደርጋቸውን ግብ አግኝተዋል።   ከእረፍት መልስም ሁለቱም ቡድኖች በማጥቃት ላይ የተመሰረተ ጨዋታ በማሳየት ተጨማሪ ሁለት ሁለት ግቦችን አስቆጥረው መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ 3 ለ 3 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል። አይሲቲዎች በኳስ ቁጥጥሩ ብልጫ ወስደው ወደ ግብ ክልል በተደጋጋሚ በመድረስ ሙከራዎችን ቢያደርጉም የኮንስትራክሽኑን ግብ ጠባቂ ማለፍ እና ኳስ ከመረብ ማገናኘት አልተቻላቸውም።   አሸናፊውን ለመለየት በተሰጠው የፍፁም ቅጣት ምት የኮንስትራክሽን ዲፓርትመንት ግብ ጠባቂ የሆነው ዘካሪያስ ገብሬ የዕለቱ ኮከብ በመሆን አድምቋል! ዘካሪያስ ሁለት የአይሲቲ ቅጣት ምቶችን ድንቅ በሆነ ብቃት አምክኖ ቡድኑን ታድጓል። አይሲቲዎች በበኩላቸው የተሰጣቸውን ኳሶች መከላከል ባለመቻላቸው ኮንስትራክሽን ዲፓርትመንት በ2 የግብ ልዩነት በማሸነፍ የዋንጫው ባለቤት ሆኗል።   ከዋንጫው ጨዋታ አስቀድሞ የደረጃ ፍልሚያ የተካሄደ ሲሆን ጀነራል መካኒክስ /GM/ (Iron Man) ከአግሮ ቢዝነስ ጋር ባደረጉት ጨዋታ ጀነራል መካኒክስ ተጋጣሚውን 6 ለ 2 በሆነ ሰፊ ውጤት በማሸነፍ የ3ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል።   በውድድሩ መዝጊያ ስነ-ስርዓት ላይ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ ይዘው ላጠናቀቁት ዲፓርትመንቶች ደማቅ የሽልማት አሰጣጥ ስነ-ስርዓት ተካሂዶ የዘንድሮው የክረምት እግር ኳስ ውድድር በስኬት ተጠናቋል።    "በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"

ማስታወቂያ ለነባር ተሻጋሪ ሰልጣኞች በሙሉ! ውድ የ2018 ዓ.ም ተሻጋሪ (ነባር) የመደበኛ (የቀን፣ የማታ እና የዊኬንድ) ፕሮግራም ሰልጣኞቻችን!! አካዳሚክ ኮሚሽን ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት ከነሐሴ
ማስታወቂያ   ለነባር ተሻጋሪ ሰልጣኞች በሙሉ!   ውድ የ2018 ዓ.ም ተሻጋሪ (ነባር) የመደበኛ (የቀን፣ የማታ እና የዊኬንድ) ፕሮግራም ሰልጣኞቻችን!! አካዳሚክ ኮሚሽን ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት ከነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 3 ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ የክረምት እረፍት ጊዜ መሆኑን በደስታ እናሳውቃለን።   ቀጣዩ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ምዝገባ የሚካሄደው ከመስከረም 4 ቀን 2019 ዓ.ም ጀምሮ መሆኑን አውቃችሁ ተገቢውን ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።   ጥብቅ ማሳሰቢያዎች፡-  ያላጠናቀቃችሁትን ኮርስ /ስልጠና እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንድታጠናቅቁ፣  የትብብር ስልጠና (Cooperative Training) ውጤታችሁን ለስልጠና ክፍላችሁ እንድታስገቡ፣  በየደረጃው ያለውን የስልጠና ውጤታችሁን በየስልጠና ክፍላችሁ በአካል በመቅረብ እንድታረጋግጡ እናሳውቃለን።   �� ልዩ ማሳሰቢያ ለእጩ ተመራቂዎች፡- ይህ ማስታወቂያ የ2018 ዓ.ም ተመራቂ ሰልጣኞችን አይመለከትም። እጩ ተመራቂ ሰልጣኞች ለምረቃ የሚያስፈልጉ ቅድመ-ሁኔታዎችን እና ሂደቶችን እያሟላችሁ የምረቃ ቀናችሁን በትዕግስት እንድትጠባበቁ ኮሌጁ በአክብሮት ያሳውቃል።    የኮሌጁ የስልጠና እና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን ቢሮ

ሰኞ:- ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም   ⚽️  የኮሌጁ አሰልጣኞች የክረምት እግር ኳስ ውድድር በድምቀት ተከፈተ! የአይሲቲ ዲፓርትመንት ደግሞ የጎል ናዳ አዘነበ!   በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተዘጋጀው የአሰልጣኞች የክረምት ስፖርታዊ የእግር ኳስ ውድድር በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀመረ። የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ባገኘበት ማግስት የተጀመረው ይህ የአሰልጣኞች ውድድር ስድስት የተለያዩ ዲፓርትመንቶችን የሚወክሉ ቡድኖች እየተሳተፉ ይገኛሉ።   በዚህ ውድድር አውቶሞቲቭ ዲፓርትመንት (Turbo Striker)፣ ጀነራል መካኒክስ /GM/ ( Iron Man)፣ አይሲቲ ዲፓርትመንት (Wingate Best)፣ አግሮ ቢዝነስ (ከተማ ግብርና እና የቢዝነስ)፣ ኤሌክትሪክና ሰርቬይንግ እና ኮንስትራክሽን (ኮንስትራክሽንና ውድ ወርክ)  ባከተተ ምድብ ተከፍሎ የሚካሄድ ሲሆን የደረጃና የፍጻሜውን የዋንጫ ጨዋታ ጨምሮ በአጠቃላይ 10 የእግር ኳስ ግጥሚያዎች ይስተናገዳሉ።   የምድብ ጨዋታው ሲጠናቀቅ ሶስተኛ የሚወጡት ቡድኖች የሚሰናበቱ ሲሆን፤ ከየምድቡ አንደኛ እና ሁለተኛ የሚወጡት አራት ቡድኖች ወደ ቀጣይ ዙር ጨዋታ ያልፋሉ። አሸናፊውን ለመለየትም የአንደኛው ምድብ አሸናፊ ከሌላኛው ምድብ ሁለተኛ ጋር ይፋለማል።   በዛረው የመክፈቻው ጨዋታ ላይ ሁለት ምድቦች ግጥሚ ያደረጉ ሲሆን መጀመሪያ ላይ አውቶሞቲቭ (Turbo Striker) ከ ጀነራል መካኒክስ (Iron Man) ጋር ተፋልመዋል፡፡    በዚህ ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች እጅግ ማራኪ የሆነ የማጥቃት እና የመከላከል ብቃት ያሳዩ ሲሆን እስከ እረፍት  ሰዓት ድረስ ባደረጉት ጠንካራ ፉክክር ጨዋታው ያለ ምንም ግብ ተጠናቆ ከእረፍት መልስ ሁለቱም ቡድኖች አቻ የሚያደርጋቸው አንድ አንድ ግብ በማስቆጠር 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ነጥብ ተካፍለዋል።   በሁለተኛው ጨዋታ ደግሞ አይሲቲ ዲፓርትመንት (Wingate Best) ከ ኮንስትራክሽን ጋር የተደረገ ሲሆን አይሲቲ ዲፓርትመንት ኮንስትራክሽንን 11 ለ 5 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት በማሸነፍ አስገራሚ የበላይነቱን አሳይቷል።    አይሲቲ ዲፓርትመንት ወደ ተቃራኒ የግብ ክልል በተደጋጋሚ በማምራት በርካታ ግቦችን አከታትሎ በማስቆጠር ድንቅ አጨዋወት ሲያሳይ ኮንስትራክሽን ዲፓርትመንቶች ደግሞ በአቅም የተፈተኑበትና አንድ ደርዘን የሚጠጉ ግቦችን ያስተናገዱበት ፈታኝ ጨዋታ ሆኖ አልፏል።   የኮሌጁ የክረምት ስፖርታዊ ውድድር በእግር ኳስ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን የሰራተኞችን የእርስ በእርስ ግንኙነት እና ጤንነት ለማጎልበት ታስቦ የመረብ ኳስ እና የጠረጴዛ ቴኒስ ጨዋታዎችም ጭምር  ይካሄዳሉ።   ውድድሩን በአሸናፊነት ለሚያጠናቅቁ ቡድኖች የዋንጫ ሽልማት እንደሚበረከት አዘጋጅ ኮሚቴው የገለጸ ሲሆን የዛሬው የመክፈቻ ቀን እጅግ የተሳካና የተመልካችን ቀልብ የሳበ በመሆኑ በቀጣይም ይህ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።    "በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"

🌿 ለኮሌጁ ማህበረሰብ በሙሉ! 🌿   🌳 አረንጓዴ አሻራችንን በጋራ እናኑር! 🌳 ዛፍ መትከል ህይወትን ማለምለም፣ ትውልድን ማሻገር ነው! ኮሌጃችን አካባቢውን አረንጓዴ በማልበስ የተፈጥሮ ውበቱን ለመጠበቅና አየር ንብረቱን ለማሻሻል ደማቅ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አዘጋጅቷል።   በዚህም ሁላችንም በአንድነት በመቆም ለኮሌጃችንም ሆነ ለሃገራችን የሚጠቅም ዘላቂ አሻራን እናሳርፍ!   የመርሃ ግብሩ ዝርዝር መረጃ፡- 📍 ቦታ፡- በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቅጥር ግቢ 📅 ቀን፡- ነገ፣ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ⏰ ሰዓት፡- ከጧቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ   ውድ የኮሌጃችን ማህበረሰብ (አሰልጣኞች፣ ሰራተኞች እና ሰልጣኞች) እርስዎም የዚህ በጎ ዓላማ አካል በመሆን የኮሌጃችንን ግቢ በተለያዩ ውብ ችግኞች ለማስዋብ በነቂስ ወጥተው አሻራዎን እንዲያሳርፉ በታላቅ አክብሮት ተጋብዘዋል!   አካባቢያችንን እንንከባከብ፤ ለትውልድ የሚተርፍ አረንጓዴ አሻራ እናኑር! 🌍

🌿 ለኮሌጁ ማህበረሰብ በሙሉ! 🌿   🌳 አረንጓዴ አሻራችንን በጋራ እናኑር! 🌳 ዛፍ መትከል ህይወትን ማለምለም፣ ትውልድን ማሻገር ነው! ኮሌጃችን አካባቢውን አረንጓዴ በማልበስ የተፈጥሮ ውበቱን ለመጠበቅና አየር ንብረቱን ለማሻሻል ደማቅ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አዘጋጅቷል። በዚህም ሁላችንም በአንድነት በመቆም ለኮሌጃችንም ሆነ ለሃገራችን የሚጠቅም ዘላቂ አሻራን እናሳርፍ! የመርሃ ግብሩ ዝርዝር መረጃ፡- 📍 ቦታ፡- በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቅጥር ግቢ 📅 ቀን፡- ነገ፣ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ⏰ ሰዓት፡- ከጧቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ ውድ የኮሌጃችን ማህበረሰብ (አሰልጣኞች፣ ሰራተኞች እና ሰልጣኞች) እርስዎም የዚህ በጎ ዓላማ አካል በመሆን የኮሌጃችንን ግቢ በተለያዩ ውብ ችግኞች ለማስዋብ በነቂስ ወጥተው አሻራዎን እንዲያሳርፉ በታላቅ አክብሮት ተጋብዘዋል! አካባቢያችንን እንንከባከብ፤ ለትውልድ የሚተርፍ አረንጓዴ አሻራ እናኑር! 🌍💚

አስደሳች እድል ለ Cisco (ሲስኮ) ኔትዎርኪንግ/ICT ስልጠና ፈላጊዎች፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለውን(የአሜሪካ Cisco ት/ቤት )የሲስኮ ኔትወርኪንግ ስልጠና ለመስጠት ሙሉ ፍቃድ ያለው
አስደሳች እድል ለ Cisco (ሲስኮ) ኔትዎርኪንግ/ICT ስልጠና ፈላጊዎች፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለውን(የአሜሪካ Cisco ት/ቤት )የሲስኮ ኔትወርኪንግ  ስልጠና ለመስጠት ሙሉ ፍቃድ ያለው እናም  የሲስኮ ኔትዎርኪንግ  ማሰልጠኛ ማዕከል  የሆነው አንጋፋው ኮሌጃችን ጄነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዘርፉ ብቃታቸውን ባረጋገጡ  እና (Certified) ሰርቲፋይድ በሆኑ አሰልጣኞች አማካኝነት በገበያው እጅግ ተፈላጊ የሆኑ ስልጠናዎችን ለመስጠት ምዝገባ መጀመሩን በደስታ ይገልፃል። የሚሰጡ ኮርሶች፡- IT Essentials CCNA   ልዩ ዕድሎች! ለማንኛውም ኮርስ ሲመዘገቡ የሚከተሉትን ኮርሶች በነፃ ያገኛሉ:: 1. Introduction to Cybersecurity 2. Introduction to Modern AI 3. Python Essentials 4. Digital Awareness ማሳሰቢያ፡- o   ለሁሉም ኮርሶች ሰርተፊኬት ይሰጣል። o  ክፍያ የሚፈፀምበት አካውንት ቁትር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000328857468 መመዝገቢያ ቦታ፡- o   ነባሩ ህንፃ ላይ ባንድራ መስቀያ ፊት ለፊት በሚገኘው የማታ ተከታታይ ትምህርት ማስተባበሪ ቢሮ ለበለጠ መረጃ፡- 0911717635 | 0911196315 | 0944767038 ይደውሉልን።