cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Tikvah-University

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
231 154
Suscriptores
+35324 horas
+8 2857 días
+15 30430 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

#ETA የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ2015 ዓ.ም እና በ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ወስደው ያለፉ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎችን ዝርዝር እንዲልኩ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን አሳስቧል። ተቋማቱ ፈቃድ በተሰጣችሁ የትምህርት መስኮች፣ የትምህርት ደረጃ፣ መርሐግብር እና ካምፓስ ያስመረቋቸውንና ከዚህ በፊት ያልተላኩ የተመረቁ ተማሪዎች መረጃንም እንዲልኩ ተብሏል። በዚህም መረጃዎቹን እስከ ሰኔ 30/2016 ዓ.ም በሶፍት እና በሀርድ ኮፒ እንድትልኩ ባለሥልጣኑ አሳስቧል። የተመራቂ ተማሪዎችን ዝርዝር መረጃ መላኪያ ቅፅ ለውጥ ማድረጉን ባለሥልጣኑ ገልጿል። (አዲሱ መረጃ መላኪያ ቅፅ ከላይ ተያይዟል።) @tikvahuniversity
Mostrar todo...
Active and graduate UG and PG student datasheet.xlsx0.22 KB
👍 31👎 4 4
Photo unavailableShow in Telegram
#DillaUniversity ዲላ ዩኒቨርሲቲ በቡና ሳይንስና ኢኮኖሚክስ የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ ያስመርቃል። ዩኒቨርሲቲው ነገ ሰኔ 27/2016 ዓ.ም የተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት ያካሒዳል። ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ 2,800 በላይ ተማሪዎችን የሚያስመርቅ ሲሆን፤ በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ 127 ተማሪዎች ይገሀኙበታል፡፡ @tikvahuniversity
Mostrar todo...
👍 9
Photo unavailableShow in Telegram
24ኛ ዙር የግራፊክስ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኢዲቲንግ፣ ሞሽን ግራፊክስ እና ዲጂታል ማርኬቲንግ ስልጠና ሰኞ ሐምሌ 01/2016 ዓ.ም ይጀምራል።  👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና 👉 ከ50 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት 👉 የሥራ ላይ ስልጠና የተመቻቸለት 👉 Advanced Graphics + Video Editing + Motion Graphics + Digital Marketing በአንድ ላይ ☎️    0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 3ኛ ፎቅ Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
Mostrar todo...
👍 8
Photo unavailableShow in Telegram
የግል የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ውጤት መቼ ይፋ ይሆናል? የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የ2016 ዓ.ም ዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ውጤት ሰኔ 21/2016 ዓ.ም ይፋ መደረጉ ይታወቃል። የመውጫ ፈተናውን የወሰዱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ውጤት እስካሁን ይፋ አልተደረገም። ይህንንም ተከትሎ የግል ተፈታኞች በርካታ ጥያቄዎችን ለቲክቫህ አድርሰዋል። በጉዳዩ ዙሪያ በትምህርት ሚኒስቴር የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልገሎት ዴስክን ጠይቀናል። "ከግል ተፈታኞች ውጤት ጋር በተያያዘ ያልተጠናቀቁ ነገሮች በመኖራቸው ውጤቱ ይፋ አለመደረጉን" የዴስኩ ኃላፊ እዮብ አየነው (ዶ/ር) ለቲክቫህ ተናግረዋል። "ቀሪ መጠናቀቅ ያለባቸው ጉዳዮች እንዳለቁ የግል ተፈታኞች የመውጫ ፈተና ውጤት ይፋ ይደረጋል" ብለዋል። የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ማኅበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ ገበየሁ በበኩላቸው፤ "ከግል ተፈታኞች አጠቃላይ መረጃ እና ክፍያ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ሲጠናቀቁ ውጤቱ በቀጣይ ቀናት እንደሚለቀቅ" ለቲክቫህ ተናግረዋል። ማኅበሩ 178 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በአባልነት ይዟል፡፡ ዘንድሮ 124 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን የመውጫ ፈተና ማስፈተናቸው ይታወቃል። @tikvahuniversity
Mostrar todo...
👍 161👎 48 13😢 7🙏 4😱 3
Photo unavailableShow in Telegram
በሁለቱም ቅርንጫፎቻችን (ሜክሲኮ እና መገናኛ) እንዲሁም በኦንላይን በምንሰጣቸው ስልጠናዎች ከሁሉም ላይ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ አድርገናል! አሁኑኑ ይመዝገቡና ትልቅ ለውጥ ወደሚያመጡበት ተቋም ይቀላቀሉ! ከትምህርትና ስልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን ሙሉ ዕውቅና ካለው ሰርተፊኬት ጋር! የብዙ ዓመት ልምድ እና ብቃት ባላቸዉ አሰልጣኞች! 🎯 Graphics Design 🎯 Video Editing 🎯 Digital Marketing 🎯 Adobe photoshop 🎯 Website Design 🎯 Programming Language 🎯 Interior Design 🎯 Database 🎯 Basic Computer 🎯 Accounting Softwares 🎯 SPSS & STATA 🎯 MS-Project 🎯  Foreign & Local Languages አድራሻ፦ ቁ. 1. መገናኛ መተባበር ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ. 419 (ሊፍት ይጠቀሙ) ቁ. 2. ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ (ትንሹ ኬኬር) 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ. 639 ሁለተኛውን ሊፍት ይጠቀሙ ☎️ 0910317675 / 0991929303 / 0991929304 Telegram: t.me/topinstitutes
Mostrar todo...
👍 20 8
#SalaleUniversity ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 1,197 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡ ተመራቂዎቹ በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው። @tikvahuniversity
Mostrar todo...
👍 74 11🙏 2
#RayaUniversity ራያ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 497 ተማሪዎች አስመረቀ። ከተመራቂዎቹ መካከል 141 ተማሪዎች በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ሲሆን፤ ቀሪዎቹ 356 ደግሞ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች ናቸው፡፡ በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታና የራያ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ፤ የፌዴራል መንግሥት የዩኒቨርሲቲውን አቅም ማጎልበት የሚያስችል ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጉን ተናግረዋል። @tikvahuniversity
Mostrar todo...
👍 49 7😢 4👎 1
#WallagaUniversity ወለጋ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ 2,300 በላይ ተማሪዎች አስመርቋል። ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ነቀምቴ ከተማ በሚገኘው ዋናው ግቢ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ 2,335 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡ ተመራቂዎቹ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ ስልጠናቸውን የተከታተሉ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ @tikvahuniversity
Mostrar todo...
👍 33👎 2 2
Photo unavailableShow in Telegram
#DebreTaborUniversity ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያስተማራቸውን 544 ተማሪዎች አስመርቋል። የዩኒቨርሲቲው 11ኛ ዙር ተመራቂዎች፣ በቅድመ እና በድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው። ተመራቂዎቹ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ከ92 በመቶ በላይ በማምጣት ለምረቃ መብቃታቸውን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት አነጋግረኝ ጋሻው (ዶ/ር) ተናግረዋል። @tikvahuniversity
Mostrar todo...
👍 39👎 7 6
Photo unavailableShow in Telegram
#BahirDarUniversity ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ግዜ ከወሰዱ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች መካከል 93.3 በመቶ ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማስመዝገባቸውን ገልጿል። @tikvahuniversity
Mostrar todo...
👍 46 10👏 3
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.