Tikvah-University
📈 Análisis del canal de Telegram Tikvah-University
El canal Tikvah-University (@tikvahuniversity) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 382 155 suscriptores, ocupando la posición 115 en la categoría Educación y el puesto 13 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 382 155 suscriptores.
Según los últimos datos del 04 septiembre, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 11 516, y en las últimas 24 horas de 259, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 18.87%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 11.44% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 72 061 visualizaciones. En el primer día suele acumular 43 678 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 194.
📝 Descripción y política de contenido
No se ha proporcionado la descripción del canal.
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 05 septiembre, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Educación.
Carga de datos en curso...
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 05 septiembre | +210 | |||
| 04 septiembre | +259 | |||
| 03 septiembre | +618 | |||
| 02 septiembre | +310 | |||
| 01 septiembre | +731 |
| 2 | የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2019 ዓ.ም ቅበላ የመግቢያ ፈተና ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል።
ወደ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለመሔድ ከላይ በምስሉ የተገለፁትን አራት የትራንስፖርት አቅጣጫ አማራጭ መንገዶች ይጠቀሙ።
@tikvahuniversity | 19 342 |
| 3 | 🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ!
► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ
► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው
► የኮሪያ ሆስፒታል እህት ኩባንያ
15ኛ ዙር የህክምና ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን!
🎓 ኮሌጃችን ያስተማራቸውን ተማሪዎች በሙሉ የብቃት ምዘና ፈተና ማሳለፍ ችሏል!
ለማመልከት 👇
https://maps.app.goo.gl/oxRezU99L2DqnngD6
አድራሻ፦
አዲስ አባባ፣ ገርጂ ኮሪያ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ሬጅስትራር ቢሮ
የምዝገባ ጊዜ 👇
እስከ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ድረስ። አሁኑኑ ይመዝገቡ!
☎️ 0116395020
ድረ-ገጽ፦ www.mmc-edu.net
Facebook: https://web.facebook.com/MMCmedcollege/
#MyungsungMedicalCollege | 15 977 |
| 4 | 🌻 የአዲስ ዓመት 25% ቅናሽ ከነሐሴ 27/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም🌻
12ኛ ዙር የኢንቴሪየር ዲዛይን (Interior Design) ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን!
👉 AutoCAD, Revit, እና 3D Max ሶፍትዌሮችን በአንድ ላይ
👉 በተጨማሪ በተግባር በወርክሾፕ የሚሰጥ
የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ደራርቱ ህንፃ 5ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com
Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute | 15 331 |
| 5 | የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2019 ዓ.ም ቅበላ የመግቢያ ፈተና ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም ይሰጣል።
በ2019 ዓ.ም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በአፕላይድ ሳይንስ እና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች የመግቢያ ፈተና ለመፈተን በኦንላይን የተመዘገባችሁ አመልካቾች የመግቢያ ፈተና ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ተገልጿል።
በመሆኑም ያመለከታችሁ በሙሉ በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ በአካል በመቅረብ መፈተን የምትችሉ መሆኑን ዩኒቨርሲቲዎቹ አሳውቀዋል።
ተፈታኞች በዕለቱ ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያዎች መገኘት ይጠበቅባችኋል። የሞባይል ስልክ እንዲሁም ማንኛውም ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችን ይዞ ወደ ፈተና ጣቢያ መግባት የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል፡፡
አመልካቾች ለፈተና ስትቀርቡ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤት፣ የአድሚሽን ካርድ እና የምዝገባ ማረጋገጫ ኮፒ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
የመግቢያ ፈተናውን የሚያልፉ አመልካቾች በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በሚደረገው የዩኒቨርሲቲ ምደባ ውስጥ አይካተቱም፡፡
@tikvahuniversity | 39 733 |
| 6 | የ Anesthesia ሙያ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የተግባር ፈተና ጳጉሜን 03/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡
ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ Anesthesia ሙያ በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ በነሐሴ 2018 ዓ.ም የፅሑፍ ፈተና ያለፋችሁና የተግባር ፈተና (OSCE) ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ፤ ፈተናው ጳጉሜን 03/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
ተፈታኝ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ መከታተል ይኖርባቸዋል ተብሏል።
ተፈታኞች በፈተናው ዕለት ማንነታቸውን የሚገልፅ ብሔራዊ መታወቂያ መያዝ ይኖርባቸዋል የተባለ ሲሆን፣ ምንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ (ስልክ፣ የእጅ ሰዓት፣ መነጽር (የተረጋገጠ የዕይታ ችግር ከሌለ በስተቀር) ይዞ መግባት አይፈቀድም፡፡
ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲሔድ ሲስተሙ የሚሰጠውን QR Code ያለው የፈተና መግቢያ ስሊፕ መያዝ ይጠበቅበታል፡፡
(ተመዛኞች የመረጣችሁትን የፈተና ጣቢያ እዚህ ይመልከቱ፡፡)
@tikvahuniversity | 47 487 |
| 7 | #Pioneer_College
🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ
የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️
ከትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዕውቅና ባገኘንባቸው የዲግሪ ፕሮግራሞች፦
► የሕክምና ዶክትሬት
► የጥርስ ሕክምና ዶክትሬት
► ፋርማሲ
► ሜዴካል ላብራቶሪ ሳይንስ
🔔 ምዝገባ ጀምረናል!
በጤናው መስክ ተወዳደሪ ሆኖ ለመገኘት ካሰቡ አሁኑኑ ፓዩኒዬር ኮሌጅ ይመዝገቡ!
አድራሻ
ከጀርመን አደባባይ ወደ ለቡ መብራት በሚሰደው መንገድ
☎️ 0902442244 / 0902443344
www.pioneercollege.edu.et | 43 003 |
| 8 | ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የሰባት የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ውጤታቸው በስህተት Disqualified እንደተባለባቸው በመግለፅ፣ የዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር ጽ/ቤት ለትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ማሳወቁን ገልጿል።
ሰባቱም ተማሪዎች ለአገልግሎቱ ማመልከት ስለሚገባቸው፣ ተማሪዎቹ ቅሬታቸውን እንዲያቀርቡ መረጃው እንዲደርሳቸው ጠይቋል፡፡
ተማሪዎቹ (3 የማኅበራዊ ሳይንስ እና 4 የተፈጥሮ ሳይንስ) ፈተናቸውን በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል የወሰዱ ናቸው።
(ጥር 11, 2022 የተከፈተና 18,853 ተከታዮች ያሉት የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር የቴሌግራም ገጽ ትናንት ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ያጋራው መረጃ ከላይ ተያይዟል።)
በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ፈተናቸውን የወሰዱና ውጤታቸው Disqualified የተባለባቸው እጅግ በርካታ ተማሪዎች ቅሬታቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ። በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የተገለፀው አይነት መሠል ግድፈት ሊኖር ስለሚችል ዩኒቨርሲቲዎች በድጋሜ የሪሚዲያል ተፈታኞችን ውጤት እንዲያዩ ይጠየቃሉ።
@tikvahuniversity | 47 171 |
| 9 | የመውጫ ፈተና አፈጻጸም በከፍተኛ ትምህርት ተቋም
መንግሥት በመውጫ ፈተና ምክንያት ከዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ወጪ መጋራት በሁለት ዓመት ብቻ 8 ቢሊዮን ብር ማጣቱን አንድ ጥናት አሳየ፡፡
የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን አጠናቀውና የመውጫ ፈተና ወስደው ያላለፉና ሰርተፍኬት ባለማግኘታቸው ምክንያት በኮንትራትም ሆነ በቋሚ መቀጠር ካልቻሉ ተማሪዎች፣ መንግሥት በሁለት ዓመት ብቻ ያገኝ የነበረውን ስምንት ቢሊዮን ብር እንዳጣ አንድ ጥናት አረጋገጠ፡፡
መንግሥት የተጠቀሰውን ያህል ገንዘብ እንዳጣ የተገለፀው፤ ትምህርት ሚኒስቴር ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን፣ ከአሪዞና ዩኒቨርሲቲ እና ከሽያሾኔ ተቋም ጋር በመተባበር ባዘጋጀው አውደ ጥናት ላይ ነው፡፡
የመውጫ ፈተና በከፍተኛ ትምህርት ተቋም ውስጥ ያለው አፈጻጸም፣ የታዩ ችግሮች እና የወደፊት መፍትሔ ምን ሊሆን እንደሚገባ ትኩረት ያደረገ ጥናት በመድረኩ ላይ ቀርቧል፡፡
ጥናቱን ያደረገው ቡድን ከአዲስ አበባ፣ ከሐዋሳ እና ከጅማ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም ከትምህርት ሚኒስቴር የተውጣጡ አባላት ያሉት መሆኑን፣ ጥናቱን ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ምርምር ማዕከል አባል አብርሃም ቱሉ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡
በ2016 እና 2017 ዓ.ም. የመውጫ ፈተና ከሰጡ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ከ128,000 በላይ ተማሪዎች መውደቃቸውንና ከተፈተኑት ውስጥ ከ52.7 ከመቶ በላይ የሚሆኑት ደግሞ ማለፋቸው በጥናቱ ተመላክቷል፡፡
የግል የትምህርት ተቋማት ደግሞ 14.8 በመቶ ብቻ ተማሪዎች ማለፋቸውን፣ በዚህም ትልቁ የመውደቅ ምጣኔ የተመዘገበው በግል የትምህርት ተቋማት መሆኑን ጥናቱ አሳይቷል፡፡ ሦስት የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በምንም ዓይነት የትምህርት ፕሮግራም ተማሪዎችን አለማሳለፋቸው በመረጃ መረጋገጡን የጥናቱ አቅራቢ ተናግረዋል፡፡
በአጠቃላይ በሁለት ዓመታት ውስጥ የተመዘገበው የማለፍ ምጣኔ 33.1 በመቶ ሲሆን፣ 66.9 በመቶ የሚሆነው ደግሞ የመውደቅ ምጣኔ መሆኑን በጥናቱ ግኝት መካተቱ ተገልጿል፡፡ በመሆኑም የመውጫ ፈተና አልፈው ተቀጥረው ቢሆን በሁለት ዓመት ውስጥ በትንሹ መንግሥት ከወጪ መጋራት ያገኝ የነበረው ከስምንት ቢሊዮን ብር በላይ መመለስ እንዳልቻሉ ተገልጿል፡፡
ተማሪዎቹ የሚማሩት ትምህርት በመጀመሪያ ምርጫቸው ከሆነ የማለፍ ምጣኔያቸው ከፍተኛ መሆኑን ለአብነትም የጤና፣ የኢንጅነሪንግና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የማለፍ ምጣኔ ከፍተኛ እንደሆነ፣ በተቃራኒው የማኅበራዊ ሳይንስ፣ የቢዝነስና የትምህርት ፕሮግራም ተማሪዎች የማለፍ ምጣኔ ዝቅተኛ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
64 በመቶ የሚሆኑት የመውጫ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎች ሰርተፍኬት ስለሌላቸው በጊዜያዊነትም ሆነ በቋሚነት መቀጠር እንዳልቻሉ፣ በዚህ ምክንያት ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ መግባት በቤተሰብ፣ በአካባቢና በጓደኛ የማሸማቀቅ ሁኔታ በልጆቹ ላይ እንደሚደርስ፣ ከ94 በመቶ በላይ የሚሆኑት ደግሞ በቤተሰብ ላይ ጥገኛ እንዲሆኑ ምክንያት መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ጥናቱ በተመለከታቸው ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች በአብዛኛው ምንም ዓይነት የመውጫ ፈተና በሁሉም የትምህርት ፕሮግራሞች የመስጠት ሁኔታ እንደማይታይና ከዚያ ይልቅ በተመረጡ ፕሮግራሞች ላይ ብቻ ተግባራዊ አንደሚደረግ አቅራቢው አስረድተዋል፡፡
በመሆኑም ኢትዮጵያ ብቻ በሁሉም የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ የመውጫ ፈተና ተግባራዊ ማድረግ የጀመረች አገር መሆኗንና፣ ትምህርት ሚኒስቴርም ወደ እዚህ ሁኔታ የገባው ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተመርቀው የሚወጡ ተማሪዎች ለሥራ ቅጥር ብቁ ባለመሆናቸው፣ ይህን ያስከተለውን የትምህርት ጥራት ለማሻሻል ኃላፊነቱን በመውሰዱን ነው ብለዋል፡፡
6,ዐ3ዐ ተማሪዎች በጥናቱ መሳተፋቸውንና ከእነዚህ ውስጥ 1,38ዐ የሚሆኑት ከአንድ እስከ አምስት ጊዜ የወደቁ መሆናቸውን እንዲሁም 78 የመንግሥት እና የግል ተቋማት፣ 13 የመንግሥት እና ሰባት የግል፣ በአጠቃላይ 20 ዩኒቨርሲቲዎች በጥናቱ መካተታቸው ተገልጿል፡፡ #ሪፖርተር
@tikvahuniversity | 41 905 |
| 10 | Sin texto... | 33 150 |
| 11 | #ጥናት
በሀገር አቀፍ ደረጃ የተካሔደ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በሚያገኙት አገልግሎት የሚሰማቸው እርካታ ዝቅተኛ መሆኑን አሳየ፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት ከተለያዩ ተቋማት በተውጣጡ አጥኚዎች የተሠራው ጥናቱ፤ በ2017 እና በ2018 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በሚሰጡ አገልግሎቶች መምህራን፣ ተማሪዎች፣ የአስተዳደር ሠራተኞች እና ማህበረሰቡ ምን ያህል ደስተኛ ናቸው የሚለውን ለማወቅ ነው፡፡
በጥናቱ በ2017 ዓ..ም የተሻለ ደረጃ ላይ የነበሩ፣ በ2018 ዝቅ ማለታቸው የታየ ሲሆን፣ በተቃራኒው ባለፈው ዓመት ዝቅተኛ ደረጃ ላይ የነበሩት በዚህ ዓመት መሻሻል ማሳየታቸውን ጥናቱ ጠቁሟል፡፡
በጥናቱ 47ቱም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የተካተቱ ሲሆን፣ ከ16 ሺህ በላይ ተማሪዎች፣ ከ16 ሺህ በላይ መምህራን፣ ከ4 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ሠራተኞች እና 4 ሺህ የሚሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች (በአጠቃላይ 61,431 ሰዎች) በጥናቱ ውስጥ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የጥናቱ ዋና ዋና ትኩረቶች
● የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የአገልግሎት እርካታ
● የዩኒቨርሲቲ መምህራን አገልግሎት አሰጣጥ
● በዩኒቨርሲቲዎች የአስተዳደር ሠራተኞች እርካታ
● ዩኒቨርሲቲዎች በአካባቢው ማኅበረሰብ ዘንድ በሚሰጡት አገልግሎት እርካታ
ከ47ቱ ዩኒቨርሲቲዎች በተማሪዎች የአገልግሎት እርካታ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዝ፣ ኦዳ ቡልቱም እና ወልድያ ዩኒቨርሲቲዎች ተከታዮቹን ደረጃዎች አጊኝተዋል፡፡
በተቃራኒው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች አገልግሎት ደስተኛ አለመሆን ቀዳሚ ሲሆን፣ መቐለ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲዎች ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል፡፡
ሸገር ኤፍኤም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተ/ፕሬዝዳንትን ስለጥናቱ ግኝት የጠየቀ ሲሆን፣ "ለጊዜው መልስ መስጠት እንደማይችሉ" ነግረውታል፡፡
ከ47ቱ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል በመምህራን "የተሻለ አገልግሎት ይሰጣል" ተብሎ በጥናቱ በቀዳሚነት የተለየው ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ቀዳሚው ሲሆን፣ ቀብሪደሃር እና ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲዎች ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል፡፡
በእነዚህ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚያስተምሩ መምህራን ለመምህራን በሚሰጠው አገልግሎት ጥሩ እርካታ እንዳላቸው ጥናቱ ጠቅሷል፡፡
መቐለ ዩኒቨርሲቲ ዝቅተኛ የመምህራን እርካታ ያለበት ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ጥናቱ ያሳየ ሲሆን፣ ዋቸሞ እና ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲዎች ተከታዮቹን ደረጃዎች ይይዛሉ፡፡
በዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ሠራተኞች እርካታ ኦዳ ቡልቱም፣ ቀብሪደሃር እና ሰላሌ ዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ እርካታ የተመዘገበባቸው ሲሆኑ፤ መቐለ፣ ደብረ ማርቆስ እና መቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ ዝቅተኛ የአስተዳደር ሠራተኞች እርካታ የተጠቀሰባቸው ናቸው፡፡
ሐራማያ፣ ዓዲግራት እና ወልድያ ዩኒቨርሲቲዎች በአካባቢው ማኅበረሰብ ዘንድ በሚሰጡት አገልግሎት ከፍተኛ እርካታ ከተመዘገበባቸው መካከል ሲሆኑ፤ ዲላ፣ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እና ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በአካባቢው ማኅበረሰብ ዝቅተኛ የእርካታ ደረጃ ከተመዘገበባቸው መካከል ቀዳሚዎቹ መሆናቸውን ጥናቱ ጠቅሷል፡፡
ተማሪዎች በማደሪያ እና በመመገቢያ ስፍራዎች ላይ ከፍተኛ ቅሬታ እንዳላቸው የሚገልፀው ጥናቱ፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንም በደሞዝና ጥቅማ ጥቅም ደስተኛ እንዳልሆኑ ጥናቱ አመላክቷል፡፡ #ShegerFM
@tikvahuniversity | 35 636 |
| 12 | Sin texto... | 32 538 |
| 13 | የሴጅ አርቲስተሪ ፕሮጀክት ቀን
እሑድ ጳጉሜ 01/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 02:00 እስከ ምሽቱ 12፡00 ሰዓት
በሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በክረምቱ ለሁለት ወራት በፕሮግራሚንግ እና ኮዲንግ፣ በመሰረታዊ ኮምፒውተር እና ቋንቋ ትምህርቶች ሲሰለጥኑ የቆዩ ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ተማሪ ልጆች የመጨረሻ መመረቂያ ፕሮጀክታቸውን ያቀርባሉ።
የእነዚህን ተመራቂ ተማሪዎቻችንን የምረቃ ስራዎች በፒያሣ ኤልያና ሆቴል በሚገኝው ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ተገኝተው እንዲያዩ እና አስተያየትዎን እንዲያካፍሉን ጋብዘንዎታል።
የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ደራርቱ ህንፃ 5ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com
Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute | 33 851 |
| 14 | 🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ!
► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ
► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው
► የኮሪያ ሆስፒታል እህት ኩባንያ
15ኛ ዙር የህክምና ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን!
🎓 ኮሌጃችን ያስተማራቸውን ተማሪዎች በሙሉ የብቃት ምዘና ፈተና ማሳለፍ ችሏል!
ለማመልከት 👇
https://maps.app.goo.gl/oxRezU99L2DqnngD6
አድራሻ፦
አዲስ አባባ፣ ገርጂ ኮሪያ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ሬጅስትራር ቢሮ
የምዝገባ ጊዜ 👇
እስከ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ድረስ። አሁኑኑ ይመዝገቡ!
☎️ 0116395020
ድረ-ገጽ፦ www.mmc-edu.net
Facebook: https://web.facebook.com/MMCmedcollege/
#MyungsungMedicalCollege | 38 971 |
| 15 | የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግር በመጠናቀቁ አዲስ ፕሬዝዳንት ለመሾም የውድድር ማስታወቂያ በቅርቡ ይወጣል፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግር ጊዜው በማብቃቱ አዲስ ፕሬዝዳንት ለመሾም የሚያስችለውን የውድድር ማስታወቂያ ለማውጣት የመጨረሻ ዝግጅት ላይ እንደሚገኝ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ ለሸገር ኤፍኤም ተናግረዋል፡፡
የውድድር ማስታወቂያው በቅርብ ቀናት እንደሚወጣ ሚኒስትር ዴኤታው ገልፀዋል።
ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ከነሐሴ 24/2015 ዓ.ም ጀምሮ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡
በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ውሳኔ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ የሆነው ሐምሌ 28/ 2015 ዓ.ም እንደነበር አይዘነጋም፡፡
@tikvahuniversity | 53 719 |
| 16 | በሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ለአስር ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ አመራር ለመመደብ የሚያስችል የውድድር ማስታወቂያ ይፋ እንደሚሆን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
የአስሩ ዩኒቨርሲቲዎች አመራር ምደባ ከተጠናቀቀ በኋላ ደግሞ ለ17 ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ አመራር ለመመደብ የውድድር ማስታወቂያ እንደሚወጣ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሽኔ ለሸገር ኤፍኤም ተናግረዋል።
ከዚህ በኋላ የዩኒቨርሲቲ አመራሮች የሚመደቡት በውድድር ብቻ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ውድድሩ ብቃትና ስብዕና ላይ መሰረት ያደረገ ትክክለኛ ውድድር እንደሚሆን ገልፀዋል።
የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ለመሆን ከዚህ በኋላ ግዴታ ሦስተኛ ዲግሪ የማይጠየቅ ሲሆን፣ ኢንዱስትሪዎችን ጨምሮ በየትኛውም ተቋም የሚገኙ ባለሙያዎች ለኃላፊነቱ መወዳደር ይችላሉ ብለዋል።
@tikvahuniversity | 47 340 |
| 17 | ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ምደባን ለማዘመን ከቀጣዩ የትምህርት ዘመን ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዘ አዲስ የአሰራር ስርዓት ሊዘረጋ ነው፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች ጋር ባደረጉት የምክክር መድረክ እንደገለፁት፣ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ስብጥር ብዝሃነትን ባካተተ፣ መቻቻልንና ሀገራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ሊሆን ይገባል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በዩኒቨርሲቲዎች ከተማሪዎች ምደባና ዝውውር ጋር ተያይዘው የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ከቀጣዩ የትምህርት ዘመን ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዘ አዲስ የአሰራር ስርዓት በትምህርት ሚኒስቴር እንደሚዘረጋ ገልፀዋል።
ከበጀት አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ዩኒቨርሲቲዎች የተመደበላቸውን በጀት ለታቀደለት ዓላማ ብቻ በቁጠባና በተጠያቂነት መንፈስ መጠቀም እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክንደያ ገብረህይወት (ፕ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርስቲዎቹ በስምምነት ተማሪዎችን ሲያዘዋውሩ ለትምህርት ሚኒስቴር ማሳወቅ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
@tikvahuniversity | 37 379 |
| 18 | #ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ
የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ላይ ነው❗️
BSc Fields of Study:
→ Doctor of Medicine
→ Doctor of Dental Medicine
→ Bachelor of Dental Science
→ Nursing
TVET Programs:
→ Dental Therapy
→ Nursing
→ Medical Laboratory
→ Pharmacy
→ Radiography
⭐️ የ CPD ማዕከል አገልግሎት!
☎️ 0913398780 / 0911596059
አድራሻ፦
CMC አደባባይ ከፀሐይ ሪል እስቴት ጀርባ ከ ICMC ጠቅላላ ሆስፒታል አጠገብ
📍 Addis Ababa, CMC Square, Behind Tsehay Real Estate, next to ICMC General Hospital
Facebook: https://www.facebook.com/Lorcanmedicalcollege
Tiktok: https://www.tiktok.com/@lorcan.medical.co | 33 840 |
| 19 | #KiburCollege
ክቡር ኮሌጅ የአፍሪካ የቢዝነስ ስኩል ማኅበር አባል ተቋም ሲሆን ክህሎትን መሠረት ያደረገ ተግባራዊ የትምህርት አሰጣጥን የሚከተል ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ነው።
✅ በመጀመሪያ ዲግሪ
✅ ቴክኒክና ሙያ (TVET)
✅ በ Remedial Program
✅ አጫጭር ስልጠናዎች
በዳግም ምዝገባ ፍቃድ ባገኘንባቸው የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን ለመቀበል በምዝገባ ላይ ነን!!
Website: https://kibur.net
አድራሻ፦ ጀሞ ሚካኤል ከአፍሪካ ህንፃ አጠገብ
☎️ 0113854042 / 0904848586
Telegram: https://t.me/kiburcollege
Facebook: https://www.facebook.com/kiburcollege | 38 398 |
| 20 | የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ ያድርጉ!
በ2018 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሐግብር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ እንድታደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ ማድረጊያ ጊዜ 👇
ከነሐሴ 28/2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 05/2018 ዓ.ም
የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ የሚያደርጉበት ሊንክ 👇
https://student.ethernet.edu.et/
የሕክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከስድስት ወር በታች ህጻን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል ተብሏል።
@tikvahuniversity | 58 915 |
