cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

This is official Telegram Channel of Ministry of Revenues Medium Taxpayers Branch No 2. Join the channel.

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
3 806
مشترکین
+824 ساعت
+687 روز
+31030 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ከተጨማሪ_እሴት_ታክስ_ነጻ_የሚሆኑ_እቃዎችን_ለመወሰን_የወጣ_መመሪያ_ቁጥር_1006፟_2016_1.pdf2.76 KB
نمایش همه...
የትርፍ ሰዓት ክፍያ ላይ ግብር እንዴት ይሰላል ?

ይህ ቻናል በገቢዎች ሚኒስቴር የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁ.2 ቅ/ጽ/ቤት የከፈተው ኦፊሴላዊ የዩቲዩብ ቻናል ሲሆን በዚህ ቻናል ስለታክስ እና ግብር ነክ የሆኑ ቪዲዮችን የምንጭን ይሆናል፡፡ ሰብስክራይብ በማድረግ የኛ ቤተሰብ ይሁኑ!! This is the ministry of revenue medium tax payers’ number 2 branch office the official YouTube channel. In this channel we upload tax and revenue related videos. Subscribe and be our family!

👍 8
3
የሥራ ሥነ-ምግባር (Work Ethics) ላይ ስልጠና ተሰጠ ************* (ሰኔ 14/2016ዓ.ም አዲስ አበባ) በገቢዎች ሚኒስቴር የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል ለቅርጫፍ ጽ/ቤቱ የማኔጅመንት አባላት የስራ ላይ ሥነ-ምግባር (Work Ethics) በተመለከተ ስልጠና ሰጠ፡፡ ስልጠናው በቅርጫፍ ጽ/ቤቱ ተቋማዊ ስራ አመራር ዘርፍ የተዘጋጀ ነው፡፡ ወ/ሮ አስቴር አዱኛ በቅርጫፍ ጽ/ቤቱ የተቋማዊ አቅም ግንባታ ዘርፍ ም/ስራ አስኪያጅ ገቢዎች አገልግሎት ሰጪ ተቋም እንደመሆኑ መጠን ሥነ-ምግባር ወሳኝ መሳሪያ መሆኑን ገልፀው የሥነ-ምግባር ግድፈት ከትንሹ ጀምሮ እያደገ የሚሄድ በመሆኑ ከጅምሩ መቅጨት ያስፈልጋል የሚል መልዕክታቸውን አስተላልፈው በስልጠናው ያገኘነውን ወደ ተግባር መለወጥ እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል፡፡ በቀጣይም ስልጠናው ለሁሉም የቅርጫፍ ጽ/ቤቱ ሰራተኞች ለመስጠት ዕቅድ እንደተያዘ አክለው ተናግረዋል፡፡ ስልጠናውን የሰጡት በዋናው መስሪያ ቤት የተቋማዊ ስጋት ስራ አመራርና ሥነ-ምግባር ዳይሬክቶሬት የሥነ-ምግባር ትምህርት እና ሀብት ምዝገባ መሪ ባለሙያ የሆኑት አቶ አበራ አምሳሉ ነው፡፡ በስልጠናው የሥነ-ምግባር ፅንስ ሀሳብ፣ የስራ ላይ ሥነ-ምግባር ምንነት፣ የሥነ-ምግባር ጉድለቶች እና መገለጫዎች እንዲሁም የሚያስከትሉት ተፅዕኖ፣ በስራ ቦታ መልካም ሥነ-ምግባርን ለመገንባት መደረግ የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎች በተመለከተ ሰፊ ገለፃ እና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ የስልጠናው ተሳታፊዎችም ስልጠናው ጠቃሚና ስራቸውን ሥነ-ምግባር ተላብሶ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያግዛቸው ጠቁመዋል፡፡ ተቋሙ መልካም ሥነ-ምግባር ያላቸውን ሰራተኞች እውቅና እና ማበረታቻ ቢሰጥ ለሌላውም መነሳሳትን ይፈጥራል የሚል ሀሳባቸውን አጋርተዋል፡፡ ወ/ሮ ሮዛ ጀማል በቅርጫፍ ጽ/ቤቱ የዋና ስራ አስኪያጅ ተወካይ እና የታክስ ስርዓት ዘርፍ ም/ስራ አስኪያጅ በስልጠናው መክፈቻ ንግግራቸው የተቋሙን ራዕይ፣ ተልዕኮ እና እሴት ሥነ-ምግባርን ተላብሶ አገልግሎት መስጠት ወሳኝ በመሆኑ የዛሬው ስልጠና መዘጋጀቱን አስታውቀዋል፡፡ የስልጠናው ተሳታፊዎች ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል ወደ ዕራሳችን በመውሰድ ተቋሙ የሚፈልገውን ሥነ-ምግባር በመላበስ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ግብር÷ ለሀገር ክብር! ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2 ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/mto2infoo ኢሜል፡- [email protected] ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2 በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
نمایش همه...
Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

This is official Telegram Channel of Ministry of Revenues Medium Taxpayers Branch No 2. Join the channel.

👍 3
ለስምንተኛ ዙር ሰልጣኞች ፈተና ተሰጠ ***************** በገቢዎች ሚኒስቴር የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የክፍል ሶስት የሞጁለር ስልጠናን ላጠናቀቁ የስምንተኛ ዙር ሰልጣኞች ፈተና ሰጠ፡፡ የታክስ ከፋይ ምዝገባ፣ ስረዛ እና ክሊራንስ አሰጣጥ፣ ስለ ደረሰኝ እና የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ፣ የታክስ ማስታወቂያዎችና ቅጾች፣ የታክስ ስሌቶችና ሌሎች ክፍያዎችን ስለመክፈል፣ የታክስ አስተዳደራዊ እና የወንጀል ቅጣቶች እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የተለያዩ አዋጆች፣ መመሪያዎችና ደንቦች ላይ ስልጠና በመውሰድ ያጠናቀቁ ናቸው፡፡ ግብር÷ ለሀገር ክብር! ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2 ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/mto2infoo ኢሜል፡- [email protected] ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2 በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
نمایش همه...
👍 2
የግንቦት ወር የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ ******** (ሰኔ 14/2016 ዓ.ም አዲስ አባባ)፡- በገቢዎች ሚኒስቴር የመካከለኛ ግብር ከፋዮች  ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የማኔጅመት አባላት የግንቦት ወር የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል  አካሄዱ፡፡ በግምገማው የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የበላይ ኃላፊዎች፣ የሁሉም የስራ ክፍል የቡድን አስተባባሪዎችና የስራሂደቶች ተገኝተዋል፡፡   ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በግንቦት ወር እቅድ ብር1,559,989,523.75፣ ክንዉኑ ደግሞ ብር1,005,281,511.90 መቻሉ እና ከግንቦት ወር የሁሉም የሥራ ከፍልች የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቧል፡፡ ገቢን በተሻለ ሁኔታ ለመሰብሰብ ልዩ ልዩ ኮሚቴዎችን በማቋቋም የዘመቻ ስራ መስራት መቻሉ፣ ለፌደራል ኦዲት ግኝት ትኩረት በመስጠት ከዉስጥ ኦዲት ጋር በመነጋገር እና በመናበብ ማሰተካከያ መዉሰዱ መቻሉ፣የተሰጠንን እቅድ ለመሳካት የኦዲት ስራዎች የትርፍ ሰዓት ስራ ጭምር በመስራት የመደበኛ እቅድን በፋይል ማሳካት መቻሉ በዕቅድ አፈፃፀሙ ከታዩ ጠንካራ ጎኖች መካከል ሲገኙበት የግብር የውሰኔ ማስታወቅያ ድርሷቸው ክፍያ ያልፈፀሙ ድርጅቶችን የማስጠንቀቂያና የእግድ ድብዳቤ ሙሉ በሙሉ ማዳረስ አለመቻል፤ የተጠራቀመ የገቢ ጉድለት መኖሩ ደግሞ ከታዩ ክፍተቶች መካከል ይገኙበታል፡፡  የማኔጅመንትና መላዉ ሰራተኞች በመተባበር የልዩ ልዩ ኮሚቴዎችን የዘመቻ ስራ አጠናክሮ በማስቀጠል የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ ጥረት ማድረግ፣ ስራዎችን በጥብቅ ዲሲፒሊን መምራት፣በተነሳሽነት መስራት፣መገምገም፣የስራ አፈፃፀም አቅጣጫ ማስቀመጥ፣ ስራ ቆጥሮ መስጥትና መቀበል የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ውስጥ ይገኙበታል፡፡ የዕቅድ አፈፃፀሙ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የዕቅድና በጀት አፈፃፀም ቡድን አስተባባሪ ኮማንደር ሞላ ተሾመ የቀረበ ሲሆን ውይይቱ በወ/ሮ ሮዛ ጀማል የዋና ስራ አስኪያጅ ተወካይ እና የታክስ ስርዓት ዘርፍ ም/ስራ አስኪያጅተ ተመርቷል፡፡ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የተቋቋሙ ኮሚቴዎች ዋና ዋና የጥናቶቹ ግኝቶች ቀርበዋል፡፡   የውይይቱን የማጠቃለያ ሀሳብ የሰጠቱት ወ/ሮ ሮዛ ጀማል በሰጡት አስተያየት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ያሉትን ግብር ከፋዮች በጥናት ላይ በመሞርከዝ ማወቅ መቻሉን ገልፀው በጥናቱ ለተሳተፉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ በቀጣይ ባለው ጊዜ ውስጥ ሁሉም በቡድን ስሜት በመስራት ገቢውን ከፍ ማድድረግ እንደሚገባ ባፅኖት ከሰጡዋቸው የማጠቃለያ አቅጣጫዎች መካከል ይገኙበታል፡፡  
نمایش همه...
👍 4
👍 3
THE EXCISE STAMP MANAGEMENT DIRECTIVE_1004_2024.pdf3.77 KB
👍 2
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.