"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን /አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ። 📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜንለምት @fentanesh21_23 🗯ፈንታነሽ / የእመ ብርሃን ልጅ🤗
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
کانال "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 (@orthodoxtewahdoc) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 25 397 مشترک است و جایگاه 2 992 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 1 324 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 25 397 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 18 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -77 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 33 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 3.78% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 2.61% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 961 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 662 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 14 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን
/አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc
ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ።
📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜንለምት
@fentanesh21_23
🗯ፈንታነሽ / የእመ ብርሃን ...”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 19 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 20 ژوئن | 0 | |||
| 19 ژوئن | +1 | |||
| 18 ژوئن | +39 | |||
| 17 ژوئن | +35 | |||
| 16 ژوئن | +28 | |||
| 15 ژوئن | +31 | |||
| 14 ژوئن | +2 | |||
| 13 ژوئن | 0 | |||
| 12 ژوئن | 0 | |||
| 11 ژوئن | +7 | |||
| 10 ژوئن | +26 | |||
| 09 ژوئن | +41 | |||
| 08 ژوئن | 0 | |||
| 07 ژوئن | 0 | |||
| 06 ژوئن | 0 | |||
| 05 ژوئن | 0 | |||
| 04 ژوئن | 0 | |||
| 03 ژوئن | +2 | |||
| 02 ژوئن | +15 | |||
| 01 ژوئن | +62 |
| 2 | ☦መልክዓ ቅዱስ ሩፋኤል📗
"ቅዱስ ሩፋኤል በእለተ ቀኑ ልጅ አተው በየፀበሉ የሚንከራተቱትን ልጅ ያስታቅፍልን በልጅ ይባርክልን አሜን።🙏
https://t.me/Orthodoxtewahdoc | 124 |
| 3 | ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"📖ምሳ 1፥33☦📚
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
📗ስንክሳር ዘወርኃ ሰኔ ፲፫።13/
https://t.me/Orthodoxtewahdoc
🌹የያዕቆብ ሌሊት ይሁንልን🕊 | 178 |
| 4 | بدون متن... | 78 |
| 5 | ❝"የኔ ሴት ..ችግርን በፈገግታ መጋፈጥ ህመምን በውስጥ መደበቅ ያለ ማንም እርዳታ መበርታት ከቻልሽ እመንኝ ኣንች ማንም ልገምታት የማይችል ጠንካራዋ ሴት ነሽ።🤌🏿💦 | 215 |
| 6 | ❝"የኔ ሴት ..ችግርን በፈገግታ መጋፈጥ ህመምን በውስጥ መደበቅ ያለ ማንም እርዳታ መበርታት ከቻልሽ እመንኝ ኣንች ማንም ልገምታት የማይችል ጠንካራዋ ሴት ነሽ።🤌🏿💦 | 1 |
| 7 | ስለ መልአከ ምክሩ ቅዱስ ሚካኤል ፀበለ ፃድቅ ቅመሱ በቃልኪዳኑ የከርሞ ሰው ይበለን ከቁጥር አያጉድለን።🙏❤ | 243 |
| 8 | ጊዜ ሊመለስ የማይችል ሀብት ነው። በህይወት ውስጥ እጅግ ውድ ሀብት ነው፣ ግን በሚያሳዝን ሁኔታ ብዙ ጊዜ በቀላል ነገሮች እና በከንቱ ነገሮች እናባክነዋለን።
አስታውሱ! የጠፋ ገንዘብ መልሶ ማግኘት ይቻላል፣ የጠፉ ነገሮች ሊመለሱ ይችላሉ፣ ነገር ግን ያለፈ ጊዜ ተመልሶ አይመጣም።
ስለዚህ እያንዳንዱን ቀን በዓላማ አሳልፉት። በደምብ የታሰበበት ውሳኔዎችን ያድርጉ፣ ሕይወትህን የሚያሻሽሉ፣ ህልሞችህን ወደ እውነታ የሚያቀርቡ እና ለሌሎችም ጠቃሚ በሆኑ ነገሮች ላይ ጉልበትህን አፍስሰው።
ጊዜን በመጠቀም ላይ ያለህ ሀሳብ፣ ፍላጎት እና ስትራቴጂ የስኬት ቁልፎች መንገድ ከፋች ናቸው።
ጊዜን በዓላማ ይጠቀሙበት፣ ምክንያቱም ይህ የህይወትን እውነተኛ ዋጋ የሚያስተምር ስጦታ ነው።
Amari La | 213 |
| 9 | ነገ ¹³ፈታሄ ማህጸን ቅዱስ ሩፋኤል ወቶ ከመቅረት ከድገተኛ አደጋ ከዲያብሎስ ፈተና ከመከራ ስጋ ወነፍስ ይጠብቀን አሜን!!!🙏♥ | 146 |
| 10 | ❤ቅዱስ ሩፋኤል🌹
✳ትርጉሙ እንዲህ ነው ፣ በልሳነ ዕብራይስጥ ሩፋ ማለት ጤና ፣ ፈውስ ፣ መድሃኒት ሲሆን ኤል ማለት ደሞ አምላክ ፣ እግዚአብሔር ማለትነው።
♨አምጻኤ ዓለማት እግዚአ መላዕክት እግዚአብሔር በነገደ መላዕክት አለቆች ይኾኑ ሰብዓቱን ሹሟል ። ቅዱስ ሩፋኤልን ከሊቃነ ነገደ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል በመቀጠል በማዕርግ ሶስተኛ ኾኖ የተሾመው ሊቀመላዕክት ነው ፣ ዮሃንስ ወንጌላዊ ቀደም ብሎ ተናግረዋል እንዲህ ይላል ርኢኩ ሰብዓተ መላዕክተ እለ ይቀውሙ ቅድመ እግዚአብሔር ራእ 8:21 ቅዱስ ሩፋኤል የሴቶችን ማህጸን ይፈታ ዘንድ ሥልጣን ተሰጥቶታል ። መላኩ ሩፋኤል በ 23 ነገደ መላዕክት መናብርት ተብለው የሚጠሩት የተሾመው ብርሃናዊ መላክ ነው ። የነገድ ስማቸውን እንዲህ ነው ፣ አጋእዝት ፣ ሓይላት ፣ ሥልጣናት ፣ ሊቃናትና መናብርት ፣ መኳንንትና አርባብና ፣ ኪሩቤልና ሱራፌል አዕላፍም ፣ ድርገታትም ተብለው ይታወቃሉ ። አለቆቻቸውም ዓስር ናቸው ። እሊኽም ፣ ቅዱስ ሚካኤል ፣ ቅዱስ ገብርኤል ፣ ቅዱስ ሩፋኤል ፣ ቅዱስ ፋኑኤል ፣ ቅዱስ ራጉኤል ፣ ቅዱስ ኡራኤል ፣ ቅዱስ ሱርያል ፣ ቅዱስ ሰዳክያል ፣ ቅዱስ ሰላትያል ፣ ቅዱስ አናንኤል ናቸው ። እሊኽ ነገደ መላዕክትም ለዘለዓለም በሰማያት ሕያዋን ኹነው ይኖሩ ዘንድ እግዚአብሔር ወሰናቸው ። ነገር ግን እግዚአብሔር ግን በጠራቸው ግዜ ፈቃዱን ለመፈጸም እሊኽ መላዕክት እስከ ጽርሃ አርያም ይወጣሉ ። በላካችውም ግዜ የፍጥረተ ሁሉ ወሰን እስከኾነችው ጨላማይቱ የባርባሮስ ሥፍራ ድረስ ይወርዳሉ ። ተመልሰውም ብቻውን የነበረው ያለና የሚኖር በአገዛዝ ላይም ሁሉ ሥልጣን ያለው እርሱን ከማመስገን በቀር በሽታም ሞትም ቢሆን ሓዘንም ቢሆን ወደሌለባቸው ቦታቸው ይገባሉ ። እግዚአብሔር ከሊቃነ መላዕክት ሩፋኤል ሠራዊት መርጦ በመንበሩ ዙርያ አቆማቸው ፣ ከእሳት ወርቅ የተሰራ ጽናዎችምና የሚያንጸባርቅ የብርሃን አክሊል አንጓቸው ብርሃን የሆነ ዘንግንም ሰጣቸው ። መልኩ መብረቅ የሆነ የክህነት ልብስን አለበሳቸው ። ከማዕጠንታቸውም ምስጋና የተሞላ መዓዛውም ደስ የሚያሰኝ ዕጣን ይወጣል ፣ እግዚአብሔርም በማዕጠንታችሁ የቅዱሳን ሁሉ ጸሎት ወደኔ ይቀርብ ዘንድ ይደረግላችሁ አላቸው ። አዎ ወደ ፈጣሪያቸውን እግዚአብሔርም ሳያቋርጡ ዘወትር ስለሰው ልጆች ይለምናሉ ፣ በሰማያት የሚኖር የአብም ገጽ ዘወትር ያያሉ ፣ ንስሐ ስለሚገባው አንድ ሓጥእም በእግዚአብሔር መላዕክት ታላቅ ደስታ ይደረጋል ፣ እግዚአብሔር ቅዱሳን መላዕክት ሁሉ ስለዚህ ነገር ፈጥራችኋል ። አዎ ከእግዚአብሔር በስተቀር የመላዕክትን ተፈጥሮ የሚያውቅ ማንም ማንም የለም ። ኩፋሌ 2:7
ቅዱስ ሩፋኤል ቅዱሳን ጻድቃን በገድላቸውም የሚረዳቸው ፣ የምያጽናናቸው ፣ የሚደግፋቸው እርሱ ነው ፣ ፈታሄ ማህጸን ፣ ዐቃቤ ሆህት ፣ ሰዳዴ አጋንንት ፣ ከሣቴ ዕውራን ፣ ፈዋሴ ዱያን ተብሎ በመሆኑ ይታወቃል ።
ሄኖክ 6:3 ዘፍ 3:24
🌹❤️የቅዱስ ሩፋኤል በረከት ፣ የዕልፊ አዕላፍ ነገደ መላዕክት ረድኤት ፣ አማላጅነት ፣ የእግዚአብሄር በጎ ቸርነትና ምህረት ዛሬም ዘወትርም ከኛ ጋር ይሁን 🙏አሜን አሜን አሜን🙏🙏🙏
ወስብሃት ለእግዚአብሄር ።
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክብር አሜን
💓💖❤️💙💜💚💖❤️💙
https://t.me/Orthodoxtewahdoc | 174 |
| 11 | بدون متن... | 108 |
| 12 | 📕#ተአምር_ዘአቡነ_ዘርዓ_ብሩክ🌹
📘☞•••ወር በገባ በ13 ታስበው የሚውሉ አባታችን ዘርዐ ቡሩክ ያደረገው ታአምር ይህ ነው ስሟ ፋሲካዊት በምትባል ሴትዮ ቤት እግዚአብሔር ዳግመኛ ታላላቅ ተአምራት አደረገ፡፡ ያቺም መልካም ሴት ሁል ጊዜ የዘርዐ ብሩክ መታሰቢያውን ታደረግ ነበር አሱንም ከመውደዷ የተነሳ ተገዛችለት ለቃሉም ታዙችለት፡፡
☞በአንድ ወር ለመታሰቢያው የሚሆን የማኀበሯ ተራ በደረሰ ጊዜ ትደክም ጀመር ብዙ ቀን ሰትጥር ስትግር ሰይጣን ቀንቶባት የመታሰቢያውን የወይን ጠጅ አጠፋባት፡፡
☞ይህ ሁሉ የደረሰብኝ ሰለ ኃጢአቴና ሰለ በደሌ ነው ብላ ብዙ ምሾ እያወጣቸ
ፈጽማ አለቀሰች፡፡
☞እግዚአብሔርም የለቅሶዋን ጽናትና ኅዘኗን አይቶ በሰይጣን ቅናት የጠፋባትን ያን ወይን ጠጅ የቃናን ውሃ ለውጦ የጣመ እንዳደረገው ያን ቦዶ እንስራ ወደ ወይን ለወጠው ፈጽሞም ጣፈጠ፡፡
☞በዚያ በጻድቁ አባቷ ዘርዐ ብሩክ ጸሎት ያ የወይን ጠጅ ተለውጦ እንዳ ጣፈጠ ያቺ ሴት አይታ እግዚአብሔርን አመሰገነች፡፡ እናቱ ድንግል ማርያምንም
አመሰገነች በጸሎቱና በአማላጅነቱ ተአምራትን መንክራትን ያየረገላት ቅዱስና
ብፁዕ የሚሆን አባታችን ዘርዐ ቡሩክ እጅግ ወደደችው፡፡
☞የጣፈጠው ያ የወይን ጠጅም በክቡር የሚካኤል በዓል ቀን ዳግመኛ
አለቀባት የነበሩ ብዙ ማኀበርተኞችም እጅግ አዘኑ የወይን ጠጅ ትበደራቸው
ዘንድ በየሀገሩ ዞረች የምትሰጣቸው የወይን ጠጅ ባጣች ጊዜ ከዚያ
ከሚጣፍጠው የወይን ጠጅ የቀረ(የተረፈ)አንድ ማድጋ ቅራሪ አመጣችላቸው
በቀዱት ጊዜ አተላ ሆነ፡፡
☞ያዚ ሴትም እጅግ አዘነች ማኀበርተኞችም ሁሉ እንደ አርሷ አዘኑ ዳግመኛ ቀዱት ንጹህና ጣፈጭ ሆነው አገኙት እጅግ ተደነቀች ማኀበርተኞችም እንደ እርሷ አደነቁ፡፡ ☞ይህ ሁሉ ተአምር የተደረገ በጻዱቁ አባታችን ዘርዐ ብሩክ ጸሎትና ልመና ነው፡፡
☞መታሰቢያውን ለምናደርግ ስሙን ለምንጠራ እንደ እርሷ ተአምራትን
ያድርግልን ለዘለአለሙ አሜን፡፡
☞(ገድለ ዘርዐ ቡሩክ)
☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ
☞https://t.me/Orthodoxtewahdoc | 100 |
| 13 | بدون متن... | 54 |
| 14 | #አቡነ ዮሐንስ ዘደብረ ቢዘን ማለት⁉
♨☞ወር በገባ በ13 የአቡነ ዮሐንስ (ዘደብረ ቢዘን)ወርሐዊ መታሰቢያ በዓል ነው እኚህ ጻድቅ ኢትዮጵያዊ ሲሆኑ በጥቅምት 14 ቀን ተወለዱ ሀገራቸው ትግራይ አድዋ አውራጃ አህሳአ ልዩ ቀበሌ እንዳ መንደር ይባላል።
☞አቡነ ዮሐንስ የአቡነ ፊልጶስ ዘደብረ ቢዘን ደቀመዝሙር ሲሆኑ፣አቡነ ፊልጶስ
ሲያርፉ በሳቸው ተተክው ደብረ ቢዘን ገዳምን በአበምኔትነት አስተዳድረዋል።
☞እንደ ነቢየ እግዚአብሔር ደመናን ዝናም እንዳይሰጥ የለጎሙ የከለከሉ
ስለሆኑ "ለጓሜ ደመና" በመባል ይታወቃሉ።
ነቢዩ ኤልሳዕ በመንፈስ ቅዱስ ሁሉን እንደሚያውቅ ሁሉ አቡነ ዮሐንስም
ሰው በልቡ የሚያስበውን ያውቁ ነበር።
☞አቡነ ዮሐንስ በተወለዱበት ሀገር ትግራይ በአህሳአ በስማቸው የተገደመ
''እንዳ አቡነ ዮሐንስ ገዳም" ፣ዛሬ ደብር ነው።
አቡነ ዮሐንስ በመነኮሱበትና ባገለገሉበት በደብረ ቢዘን ገዳም በኅዳር 13
ቀን አርፈው ተቀብረዋል።
☞""አቡነ ዮሐንስ ዘአስገዶም"" በመባልም ይጠራሉ።
☞በስማቸው የተሰሩ 5 አብያ ተክርስቲያናት አሉ
አምላካችን እግዚአብሔር ስለ ጻድቁ ስለ አቡነ
ዮሐንስ ዘደብረ ቢዘን
ብሎ ከዘመኑ መቅሰፍትና ጥፋት ይሠውረን፡፡
☞(ገድለ አበው ቅዱሳን ዘደብረ ቢዘን)
https://t.me/Orthodoxtewahdoc | 46 |
| 15 | بدون متن... | 44 |
| 16 | ልቤ ለመዳን ይሻልና ለዘለአለሚዊነትህ ከከንቱ ሞት ኀጢአት ያድነኝ ዘንድ እማፀንህ አለውለመንግሥትህ ፍፃሜ የሌለው ቃልህና አካልህ በመልክዕና በቁመት እጅግ የከበረ የምትደነቅ የብርሃናት መገኛ እግዚአብሔር አብ ሆይ ከአቅም በላይ በኾነና ለመይወሰን አካለ አቅም ህና ዳግመኛም ግርማ *ራእዩ ለሚያስደንቅ መልክዕህ ሰላምታ ይገባል* አንተ እውነተኛ አምላክ ሥትሆን ኹሉን በፈቃድህ የፈፀምህ የኹሉ ፈጣሪ እግዚአብሔር አብ ሆይ ኹሉን ማድረግ የሚቻልህ ሁሉን ለአንተ የቀረበ በአንተም ዘንድ አለና በእውነተኛይቱ መንገድ መርተህ ህግን *አስተምረኝ። እግዚአብሔር አብ ሆይ በለሊትና ቀኑን ሙሉ* *ምስጋና ይገባሀል።*
እግዚአብሔር ዓብ ሆይ በክረምት እና በበጋ አውራኀ ልክ ምስጋና ይገባል ።
እግዚአብሔር አብ ሆይ በማይታየውም ኹሉ ዘንድ ምስጋና ይገባል አለም ሳይፈጠር አስቀድሞ የነበረና የአለ የሚኖርም ምስጋናህን እነሆ
ሰማይ ይናገራል አቤቱ እግዚአብሔር አብ ሆይ ከሥጋና ነፍስ መከራ እኔ
_ን ጠብቀኝ ብርሀንህንም አብራልኝ ለዘላለሙ አሜን ።
*አባታችን ሆይ* https://t.me/Orthodoxtewahdoc | 48 |
| 17 | 🌹ወር በገባ በ13 እግዚአብሔር አብ ነው እንኳን አደረሰን🎋
♨#መልክዐ እግዚአብሔር አብ 🌹
📗•••ፀጋን የምታድል የመከራና የችግር ጊዜያትንም የምታሶግድ ፍፁም አለማዊ አምላክ እግዚአብሔር አብ ሆይ ልመናውን የማታቋርጥ ነፍሴ አስቀድሞ ነብያትህ ኄኖክንና ዕዝራን ማስተዋልን እንደመላኋቸው ንጉስን ከወታደሮች ጋራ የሚያጸና ይቅርታህ ይርዳኝ ትልሀለች ።
ወዳጅህ እስራኤልን አፍህን ክፈት እኔም አመላዋለሁ ያልኽው እግዚአብሄር አብ ሆይ አንተ ርኽረኽ እና ፍፁም አምላክ ነህ ምስጋናህን አቀርብ ዘንድ አንደበቴን አዘጋጃለሁ።
በደሴተ ፍጥሞለ ለነበረ ቅዱስ ዮሐንስ ራዕይን የገለፅህ እግዚአብሔር አብሆይ ጉድለት ችልታ በሌለበት አዲስ አንደበት የመፀሐፍት ሚሥጥራትን አንብቢና ተርጉሜ ህግህን ለማስተማር የጀመርሁትን አዲስ ግብር እፈፅም ዘንድ አቤቱ ፀጋህን አድለኝ ።
ከዘመናት አስቀድሞ የነበርኽ የዘመናት ባለቤት ዘመናትንም አሳልፍኽ የምትኖር በባሕርይህ ጉድለት የሌለብህ በፈጡራን ሁሉ አንደበት የምትመሰገን እግዚአብሔር አብ ሆይ ዘመናትን በፀጥታ የምታፈራርቅ አንተ ነኽና ፈጽሞ *ለተመሰገነ ዝክረ ስምህ ሰላምታ ይገባል*
ከእግዚአብሔር ወልድ እና ከእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስጋርራ ዕሩይ የሆንኽ የብርሃኑ ክበብ ለሚያስደንቅ የራስ ፀጉርህና ምሳሌ የሌለው ምስጋና የሚገባህ *እግዚአብሔር አብ*
ሆይ የሦስትነት የአንድነተመቸሀለ ፀሐይ ለአለም ሁሉ ጌጥ ኾኖ ከምዕራብ። እስከ ምሥራቅ ከምድር እስከ ሰማይ ያበርራል የኹላችን መለያ ክብርህ ሰማያትን የመላ ጌትነትህም ፈጽሞ የተመሰገነ *እግዚአብሔር አብ ሆይ*
ከኹለቱ እግዚአብሔር ወልድና እግዚአብሔር።መንፈስ ቅዱስ ጋራ ብርሀን በማስገኘቱ ፈፅሞ ለተመሰገነ ገፅህ ሰላምታ ይገባል ።የብርሀናት ፈጣሬ የሆነ ጨለማ ለማይስማማቸው ብሩሀት አይኖችህና ቅንድቦችህ ሰላምታ ይገባል።ኃይልና ምስጋናም ለአንተ ይገባልና አይኖቼ በምተ ኃጢት እንዳያንቀላፋ በብርሀን እረዴኤትህ ንቁሐን። አድርጋቸው
የምስጋና ምስዋዕት የምትቀበል እግዚአብሔር አብ ሆይ ሁልጊዜ ፀሎትን ለሚያዳምጡና። የሚያንፀባርቅ እሳትን ለተጎናፀፉ ጉነጮችህ ሰላምታ ይገባል ። አቤቱ ዘወትር እንደ አሽኮኮ የምጨነቅየት የጭንቅ ጨኽቴን ታሰወግድልኝ ዘንድ ኤሎሔ ኤሎሔ እያልሁኝ የምለምንህ ፀሎቴን ተቀበልኝ። በኹሉም ሁሉ ሥፈራ የነበርህና ያለህ የምትኖር ሳን ታው በተባሉ የምትመሰገን በባሕርይኅ ኀል ፈት ሸረት የሌለበረህ እግዚአብሔር አብ ሆይ የሚያስደስት መአዛን። ለተመሉ አፈንጫህዎችና ዳግመኛም የተወለደደ ።.
ቃል በሚስባቸው ከንፈሮችህ ሰላምታ ይገባል።
አለም ሳይፈጠር አስቀድሞ የነበርህ አዲሱ አለም ከተገለጠ ቡኋላም ለዘላለም የምትኖር ጌታየ ነህ በፍፁም ምስጋና የተሞላህ የዘላለማዊ አምላክ እግዚአብሔር አብ ሆይ በተወደደ አንደበትህና መለኮታውያን ለኾኑ ጥርሶችህ ሰላምታ ይገባል ።
በእጅ ምሀል አለምን የያዝህ እግዚአብሔር አብ ሆይ ወዶ ፈቅዶ ለሚናገር አንደበትህና እንደ ነጎድጓድ። ለሚያስተጋባ ድምፀ ቃናህ *ሰላምታ ይገባል ።*በአንተ ዘንድ ህልው የኾነ ኹሉን የማገልጥ መንፈስ ቅዱስ የእየነገዱን ቋንቋ ኹሉ ይግለጥልኝ።
ፅድቅንና ይዎሄን.የትህትናም ግብር ሁሉ የምትወድ ጠላት ሳጥናኤልን የጣለውን ትዕቢትን የምትጠላ ገናንነትህን እጅግ የሚያስደንቅ እግዚአብሔር አብ ሆይ የህውሐት እና የጤና እስትንፋስ በኾነ እስትንፋስህ የፀጥታ ደጃፍ ፤
*የሀይልመግለጫ ለሆነ ጉሮሮህ ሰላምታ ይገባል*።
እግዚአብሔር አብ ሆይ እርዝመቱ በሚያስደንቅ ዙሪያውም ክብ ለሆነ መጠኑ ለማይታወቅ *ጽህምህ ሰላምታ ይገባል*።በዝናበ እረዴኤትህ ጠልና ከፍታው እጅግ በበዛ የይቅርታህ ደመና የሕይወቴን ጽድቅ እንደ ካህኑ አሮን ፂም አርዝምልኝ።
ከመገለጥ ይልቅ የተሰወረን የበልጥ የምትሠውረ እግዚአብሔር አብ ሆይ ዕበየ።ግርማህ ለከበበው አንገትህና ዳግመኛም በአንድነት ለጸኑ *ትከሻዎችህ ሰላምታ ይገባል*።የባህርየ ልጅህ ክርስቶስ እንክርዳዱን ከስንዴኤው ለይቶ በእሳት ሲያቃጥል ብጽላሎተ ረድኤቱ ይሠውረኝ።
ጥልቅ ባህር ጥበባት እግዚአብሔር አብ ሆይ ኪሩብ ሊሸከመው ለማይችለው ጀርባህና ዳግመኛም አርባብ የተሰኙ የዋሃን ነገደ መላዕት ላይ *ከብሮ ገንኖ ለሚኖረ ቅዱስ ደረትህ ሰለምታ ይገባል* ።ኪነ ጥበቡ እጅግ የሚያስደንቅ ኃይልህ እኔ ጠቢብ ልጅህን ከስንፍና ይልቅ ጥበብን ያድለኝ።
የክብርህን ነገር ለመናገር የሚያስደንቅ በማስተዋል ለመንግሥትም ፍፃሜ የሌለህ እግዚአብሔር አብ ሆይ የፀጋ ብርሀናትን ለሚያፈልቅ ሕፅንህና ዳግመኛም ለመመገብ *ለተዘረጉ የምህረት እጆችህ ሰላምታ ይገባል*።
ድዊይ የምትፈውስ እግዚአብሔር አብ ሆይ ለአሸናፊ ድል ለሚያንጎናፅፍ ክንዶችህ እና ከአካልህ ጋር ለተስማሙ ክርኖችህ ሰላምታ ይገባል።የሀጥያቴን ደዌ አውሬ ዲያብለስን በወጋህበት በጦር ወግተህ በአዳኝ ሀይል አድነኝ .።
ከእግዚአብሔር አብ ወልድና ከእግዚአብሔር መንፍ ቅዱስ ጋራ በእሳታዊጨ ዙፋንህ ከብረህ ገንነህ የምትኖ አለም ሳይፈጠ አስቀድም በሥልጣነ የባህሪህ የሆቸ እግዚአብሔር አብ ሆይ ለሚያስፈራ አምላካዊ ክንድህ ይህን ። ይህነ ስፊ አለም ለያዘ መሐል *ሰላምታ ይገባል*
የፍቅርና የቸርነት መገኛ ሰማያት በምድር በየብስና በባህር ያሉትን ፍጥረታትን ኹሉ የምትመግብ። እግዚአብሔር አብ ሆይ ይህን አለም ለፈጠሩ ጣቶችህና ድንቅ ሥራዎችህን *ለሚያፈጥኑ ጠረፍሮችህ ሰላምታ ይገባል*
ከንፎቻቸው ስድስት የኾኑ ኪሩቤልና ሱራፌል አንተን የዘወትር ከባህርይ። ልጅህ እግዚአብሔር ወልድና ከባህርይ ሕይወትህ ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ጋራ የሚያመሰግኑህ እግዚአብሔር አብ ሆይ ልብሱ መብረቀ ስብሐት ለኾነ ጎንህና የመኖሪያ ሥፍራ *ለማይወስነው ሆድህ ሰላምታ ይገባል*።
ይቅርታህን ርኀራኄህ ብዙ ነውና በፍጡራን አንደበት ኹሉ የምትመሰገን እግዚአብሔር አብ ሆይ ቅንና የዋህ ልብህና የዘመናትን ፍፃሜ አስቀድሞ ለሚያውቅ ሕሊናህ ሰላምታ ይገባል ክንድህም ለይቅርታ ዘወትር የተዘረጋ ነው ።
።በለይም በታችም ለዘመለአለም ነግሠህ የነበርህና ያለህ የምትኖር ንጉሥ ነገሥት እግዚአብሔር አብ ሀሰይ መልኩ ለሚያስደንቅ ኀንብርትህና ዳግመኛም *ለትጥቁ ደግ ለሚያምር ሀቊህ ሰላምታ ይገባል* አቤቱ ለይልህ አሸናፊ ነው እናአዐፄም አውሬ ዳቢሎስን አሸንፍ ዘንድ የትዕግስትን ትጠረቅ አልብሰኝ
የእግዚአብሔር ወልድ የባህርየ አባት እግዚአብሔር አብ ሆይ ክቡድና መለኮታዊ ለኾኑ ጭኖችህ ዳግመኛም *ለጉልበቶችህ ሰላምታ ይገባል*
ጠላት ዳቢሎስ ከሰጠህው ስልጣነ ከተባረረ ቡሀላ ትጉሀን
ሰማይ ከሆነ ነገደ መላእክት በአንድነት አመሰገኑህ
አለምሠ ሳይፈጠር አስቀድሞ የነበርህ ምድርንም የዘረጋህ ሥራህንም በድንቅ በማስተዋል ከመሥራትህ አሰቀድሞ የምትኖር እግዚአብሔር አብ ሆይ ምድር ለሚያንቀጠቅጡ እግሮችህና ከእግርህ *መረገጨም ጋራ ለተረከዝህ ሰላምት ይገባል*።
የአባታችን አዳም የህይወቱ መሰረት እግዚአብሔር አብ ሆይ *ጋራ ባይለዩ ለሚኖር አስሩ ጥፍሮችህና ጣቶችህም ሰላምታ ይገባል* | 50 |
| 18 | بدون متن... | 52 |
| 19 | ††† እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል እና ለጻድቁ አባ ዮሐንስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። †††
††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††
††† ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት †††
††† ቅዱስ ገብርኤል :-
¤በራማ ከሚኖሩ ሊቃናት አንዱ::
¤አርባብ በሚባሉ አሥር ነገዶች ላይ አለቅነትን የተሾመ::
¤የስሙ ትርጓሜ "እግዚእ ወገብር" (ጌታና አገልጋይ) አንድም "አምላክ ወሰብእ" (የአምላክ ሰው መሆን) ማለት የሆነ::
¤በመጀመሪያዋ የፍጥረት ቀን ዘጠና ዘጠኙን ነገደ መላእክት ያረጋጋ::
¤ብርሃናውያን መላእክትን የሚመራ::
¤በብሉይም ሆነ በሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት አብሣሪነቱ በስፋት የተነገረለት::
¤በተለይ ደግሞ የወልደ እግዚአብሔርን ሰው የመሆን ዜና ይሸከም ዘንድ ያደለው::
¤ከድንግል ማርያም ጎን በፍጹም የማይርቅ::
¤በፈጣን ተራዳኢነቱ ብዙ ቅዱሳንን ያገለገለ ታላቅ ቀናዒ መልአክ ነው::
በዚሕች ዕለት እግዚአብሔር ቅዱስ ገብርኤልን ወደ ባቢሎን ልኮታል:: ሊቀ መላእክት ነቢዩ ዳንኤልን ከአናብስቱ ጥርስ እንዳዳነው መጽሐፍ ነግሮናል::
ይልቁኑ ታላቁ ነቢይ ዳንኤል የተማረኩ ወገኖቹን መመለስ እያሰበ በሃዘን ሲጸልይ በዚሕ ቀን ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ ዳስሶታል:: ባርኮታል:: አጽናንቶታል:: ለዳንኤል በዋነኛነትም ሦስት ምሥጢራትን ገልጾለታል:-
1.የቤተ እሥራኤልን ከሰባ ዘመን በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም መመለስ::
2.የክርስቶስን ሰው መሆንና መሞት::
3.የሐሳዌ መሲሕን በመጨረሻ ዘመን መምጣት ነግሮታል:: ስለዚህም እኛ ቅዱስ ገብርኤልን እንድናከብረው : በጸሎትም እንድንጠራው አባቶቻችን አዝዘውናል::
††† አባ ዮሐንስ ዘኢየሩሳሌም †††
††† ጻድቁ ሃገራቸው መካከለኛው ምሥራቅ አካባቢ ሲሆን የታላቁ ሊቅ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ባልንጀራ ናቸው:: ከሕፃንነታቸው ጀምሮ በክርስትና አድገው : ቅዱሳት መጻሕፍትን ተምረው ወደ ገዳም መንነዋል::
ከታላቁ ኮከበ ገዳም አባ ኢላርዮን ሥርዓተ መነኮሳትን አጥንተው አባ ኤስድሮስን በረድዕነት አገልግለዋል::
ከብዙ ዓመታት ትሕርምትና ገዳማዊ ሕይወት በኋላ የቅድስት ሃገር ኢየሩሳሌም ጳጳስ ሆነው ተሹመዋል:: በጵጵስናቸው ዘመን አንድ ከባድ ስሕተት ሠርተው ነበር::
እርሱም ለቤተ ክርስቲያንና ለነዳያን ከምእመናን የተሠበሠበውን ገንዘብ ለግል ጉዳያቸው አውለው ልብሳቸውና ቤታቸው ወርቅ በወርቅ ሆኖ ነበር:: ፈጣሪ ግን ይሕንን ብክነት ከእርሳቸው ያርቅ ዘንድ ቅዱስ ኤጲፋንዮስን ላከው::
እርሱም በምክንያት ከቆጵሮስ ኢየሩሳሌም ገባ:: ጓደኛ ናቸውና አሳምኖ የወርቅ ንብረቶቹን ሁሉ ወሰደ:: ለነዳያንም ሰጣቸው:: አባ ዮሐንስ ሊቁን "እቃየን ካልመለስክ" ብለው ቢይዙት ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ጸልዮ ዐይናቸው እንዲታወር አደረገ:: አንዳንዴ የታወረ ልብ የሚገለጠው እንዲሕ ነውና::
በደቂቃዎች ልዩነት ዐይነ ስውር የሆኑት አባ ዮሐንስ አለቀሱ:: ሊቁንም "ራራልኝ : አማልደኝ?" አሉት:: እርሱም ጸልዮ አንድ ዐይናቸውን ብቻ አበራላቸው:: "ለምን?" አሉት:: "ተግሳጽ ነው" አላቸው::
ከዚያች ቀን በኋላ አባ ዮሐንስ ወደ ልቡናቸው ተመለሱ:: ቤታቸውን ገዳም አደረጉት:: በሚደነቅ ቅድስና : ፍቅርና ሐዋርያዊ አገልግሎት ምዕመናንን አገልግለው በዚሕች ቀን በመልካም ሽምግልና ዐርፈዋል::
††† የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ረድኤት : የአባ ዮሐንስ በረከት አይለየን::
††† ሰኔ 13 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት (ወደ ዳንኤል የወረደበት)
2.አባ ዮሐንስ ዘኢየሩሳሌም
3.አባታችን ቃይናን (ከአዳም አራተኛ ትውልድ)
4.አባ ማትያን ጻድቅ
††† ወርኀዊ በዓላት
1.እግዚአብሔር አብ
2.ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት
3.ዘጠና ዘጠኙ ነገደ መላእክት
4.ቅዱስ አስከናፍር
5.አሥራ ሦስቱ ግኁሳን አባቶች
6.ቅዱስ አርሳንዮስ ጠቢብ ገዳማዊ
7.አቡነ ዘርዐ ቡሩክ
††† " . . . በአምላኬም በእግዚአብሔር ፊት ስለ ተቀደሰው ስለ አምላኬ ተራራ ስለምን: ገናም በጸሎት ስናገር አስቀድሜ በራእይ አይቼው የነበረው ሰው ገብርኤል እነሆ እየበረረ መጣ:: በማታም መሥዋዕት ጊዜ ዳሰሰኝ:: አስተማረኝም: ተናገረኝም:: እንዲህም አለ:- "ዳንኤል ሆይ! ጥበብንና ማስተዋልን እሰጥህ ዘንድ አሁን መጥቻለሁ::" †††
(ዳን. ፱፥፳-፳፪)
††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
https://t.me/zikirekdusn | 100 |
| 20 | بدون متن... | 128 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
