"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን /አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ። 📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜንለምት @fentanesh21_23 🗯ፈንታነሽ / የእመ ብርሃን ልጅ🤗
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
کانال "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 (@orthodoxtewahdoc) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 25 503 مشترک است و جایگاه 2 874 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 1 362 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 25 503 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 13 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 20 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -20 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 3.75% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 2.86% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 956 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 729 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 12 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን
/አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc
ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ።
📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜንለምት
@fentanesh21_23
🗯ፈንታነሽ / የእመ ብርሃን ...”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 14 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 14 سپتامبر | +10 | |||
| 13 سپتامبر | 0 | |||
| 12 سپتامبر | 0 | |||
| 11 سپتامبر | +2 | |||
| 10 سپتامبر | +33 | |||
| 09 سپتامبر | +41 | |||
| 08 سپتامبر | +31 | |||
| 07 سپتامبر | +33 | |||
| 06 سپتامبر | 0 | |||
| 05 سپتامبر | 0 | |||
| 04 سپتامبر | 0 | |||
| 03 سپتامبر | +23 | |||
| 02 سپتامبر | +55 | |||
| 01 سپتامبر | +16 |
| 2 | •••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"📖ምሳ 1፥33☦📚
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
📗ስንክሳር ዘወርኃ መስከረም ፭/5
ወለተ ሥላሴ ብላችሁ በጸሎታችሁ አስቡኝ
https://t.me/Orthodoxtewahdoc
🌹የያዕቆብ ሌሊት ይሁንልን🕊 | 212 |
| 3 | بدون متن... | 207 |
| 4 | ገብረ መንፈስ ቅዱስ አባታችን
በረከትህ ይግባ ቤታችን🤲♥️🙏 | 355 |
| 5 | በስሜት ብሰሉ!
አንድ በስሜቱ ያልበሰለ ሰው ሁሌም አንድን ከባድ ስራ ለስራት የሚያነቃቃውን ነገር ይፈልጋል፣ አንድ በስሜቱ የበሰለ ሰው ደግሞ ከባዱን ስራ ሺህ ጊዜ ለመስራት ዲሲፕሊን ይፈልጋል። ልዩነታቸው ግልፅ ነው መነቃቃት አንድን ከባድ ስራ ሊያስጨርስ ይችላል ነገር ግን በፍፁም እንደ ዲሲፕሊን ሺህ ከባባድ ስራዎችን ሊያስጨርሰን አይችልም። በስሜት የበሰለ ሰው የስሜቱ ገዢ እንጂ የስሜቱ ተገዢ አይደለም፣ ማድረግ ያለበትን የሚወስኑለት ሁኔታዎች ሳይሆኑ እራሱ ነው፣ እያንዳንዱ ውሳኔው ከስሜት በላይ ወጥነት ባላቸው የማይቋረጡ እንቅስቃሴዎች ስለመቃኘታቸው እርግጠኛ ይሆናል። መነቃቃት አስፈላጊ ነው፣ ሁሌም ከባድ ነገር በመጣ ቁጥር ግን አነቃቂ ነገር መፈለገ ሚዛናዊ እምነት አይደለም። ከውጭ ከሚመጣው ማነቃቂያ በላይ ከውስጥ የሚገፋን የተለየ ስሜት ያስፈልገናል። አስተውሉ፣ ሁሉም ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰው ተፅዕኖውን መፍጠር የቻለው በየቀኑ የሚያነቃቃው ነገር ስላለውና ስሜቱ ስለማይረበሽ ይመስላችኋል? እያንዳንዱ ስኬት ላይ የደረሰ ሰው ስኬታማ የሆነው ስሜቱን እየተከተለ ሲደክመው እያረፈ፣ ሲደብረው ስራውን እየዘለለና እራሱን በጊዜያዊ ምቾት እያታለለ ይመስላችኋል? በፍፁም አይደለም።
አዎ! በምንም ነገር ላይ ጣሪያ ለመንካት በቅድሚያ በስሜት ብሰሉ፤ የትኛውንም የህይወት ከፍታ ለመቆናጠጥ አስቀድማችሁ እንዴት የስሜታችሁ ገዢ እንደምትሆኑ እወቁ። ለመጣው ሰው ሁሉ እየታዘዛችሁ የምትገነቡት ዲሲፕሊን የለም፣ ላያችሁትና ለሰማችሁት ሁሉ ምላሽ በመስጠት የምታመጡት ለውጥ የለም። ብልህ ሰው የትኛውንም ተግባር ከማከናወኑ በፊት ከአላማው ጋር ስለመሄዱ ይመረምራል፣ በሳል ሰው ለተጠየቀው ጥያቄ የእሺታ መልስ ከመስጠቱ በፊት ጥያቄውን ባይቀበል ስለሚያጣው ነገር በጥልቀት ያጠናል። እናንተ በጭፍኑ መነዳት ስታቆሙ የሚነዳችሁ ሰው አይኖርም፣ እራሳችሁን መግዛት ስትችሉ የሚገዛችሁ ውጫዊም ሆነ ውስጣዊ ስሜት አይኖርም። ህይወታችሁን በሒደት የሚቀይረውን፣ የተሻለ ሰው የሚያደርጋችሁን፣ በራስመተማመናችሁን የሚገነባውን ከባዱን ነገር ሺህ ጊዜ ለማድረግ የሚያስፈልጋችሁ መነቃቃት ሳይሆን እራስን መግዛት ወይም ዲሲፕሊን ነው።
አዎ! ጀግናዬ..! በስሜት እንደበሰልክ ለማረጋገጥ ይሔን አንድ ጥያቄ ብቻ መልስ። ጠቃሚ እንደሆነ እያወክ፣ ህይወትህን እንደሚቀይረው እያመንክ ከባድ ስለመሰለህ ብቻ ሳታደርገው የቀረሀው ተግባር ምንድነው? በእርግጥም በስሜት የበሰልክ ከሆንክ ትኩረትህ የተግባሩ ክብደት ወይም ቅለት ሳይሆን የሚያመጣው ለውጥ ይሆናል፣ ስራውን ለመጀመር የምትወስነው ከሚሰማህ ጊዜያዊ ስሜት በመነሳት ሳይሆን በስተመጨረሻ ከምታገኘው ውጤት አንፃር ይሆናል። ቆመህ ህይወት እስክትሰራህ አትጠብቅ፣ ለዓመታት ቀላል ተግባራትን እየደጋገምክ ዋጋቢስ የወረደ ህይወት አትኑር። ደፋርና ስሜቱን የሚገዛ ብርቱ ሰው ካልሆንክ እንዲሁ እያሳበብክና እያለቀስክ ታረጃለህ እንጂ ምንም የምታመጣው ለውጥ አይኖርም። ቆፍጠን ብለህ ተንቀሳቀስ፣ ጥርስህን ነክሰህ ለከባዱ የህይወት ፈተና ተዘጋጅ፣ በጊዜያዊ ብልጭልጭ ነገር አትሸወድ። ራዕይህን እውን የሚደርግልህንና ያመንክበትን አላማ ከዳር የሚያደርስልህን የማይናወጥ ዲሲፕሊን መገንባት ላይ አተኩር። | 552 |
| 6 | እግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው 🙏
ለእኔ ያደረገው ብዙ ነው
እግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው
ለእኔ ያረገልኝ ብዙ ነው ❤️
እረዳት እርሱ ነው ከሰማያት
እግዚአብሔር ጠባቂ የኔን ሕይወት ☦
ብርሃኑን በፊቴ የሚያበራ✨
አምላኬ ድንቅ ነው የእርሱ ስራ🙏
በመንገዴ ሁሉ የሚመራኝ
ስነሳ ስወድቅም የሚያስበኝ🫀
ማንም አልመጣልኝ ከወገኔ
ከሁሉም ይበልጣል እርሱ ለኔ 😍
የእዳዬን ደብዳቤ ውድቅ አድርጎ
ሕይወቴን መራልኝ ወደ በጎ ✨
ኧረ እንደ እግዚአብሔር ማን ይሆናል
እሱን ለሚፈሩት ይታመናል 💞
አንድ ቀን አስቤ ተጨንቄ
ለመኖር አልቻልኩም ተጠንቅቄ❤️🩹
ሁሉን ነገር ለእርሱ ትቸዋለሁ
በምሕረቱ ጥላ እኖራለሁ 🙏
ዘማሪ ቀሲስ እንዳልካቸው ዳኘው 😍 | 553 |
| 7 | አቡነ አሮን መንክራዊ ነገ መስከረም 5 እረፍታቸው ነው በረከታቸው ይደርብን
https://t.me/Orthodoxtewahdoc | 522 |
| 8 | ✝ጻድቅ ንጉሥ አፄ ልብነ-ድንግል✝
✿በመካከለኛው ዘመን የነገሡ መሪዎቻችንን ስዕል ማግኘቱ ከባድ ቢሆንም ይህ የልብነ ድንግል ምስል በመላው ዓለም ታዋቂ ነው፡፡ (በእርግጥ ንብረትነቱ የእኛ አይደለም)
✿ልብነ ድንግል ከ1500-1533 በቆየ ዘመነ ንግሥናቸው፡-
✝ለድንግል እመቤታችን በነበራቸው ፍቅር
✝አድባራትን እና ገዳማትን በማነጽ
✝በደራሲነት (መልክዐ ኤዶምን ፡ ተፈስሒ ማርያምን ፡ ለአዳም ፋሲካሁን ፡ ለኖኅ ሐመሩን ፡ ስብሐተ ፍቁርን . . .)
✝በፍጹም ንስሃቸው (ባጠፉት ጥፋት ጌታ ግራኝን አስነስቶ ሲቀጣቸው በመጸጸታቸው)
✝ለነዳያን በመራራታቸው
✝ለሕገ ቤተ ክርስቲያን ቀናዒ
✝ለጋብቻቸውም ፍጹም ታማኝ በመሆናቸው . . . ይታወቁ ነበር፡፡
✿በ1533 መስከረም 5 ቀን በደብረ ዳሞ (ትግራይ) ከማረፋቸው በፊት እመቤታችንን እያለቀሱ ለመኑ፡፡
"በእንተ ፍቅረ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኬንያ፡፡
እስእለኪ ማርያም በሃሌ ሉያ፡፡
ሐዘና ስምዒ ወብካያ፡፡
ለሃገሪትነ ኢትዮጵያ፡፡" (ስብሐተ ፍቁር)
✿እመቤታችንም "ልመናህን ተቀብየዋለሁ፡፡ ግን በምድር ደስታ የለህምና ለልጅህ ማር ገላውዴዎስ ኃይልን እሰጠዋለሁ፡፡ እርሱም የሃገሪቱን ክብር ይመልሳል" አለቻቸው፡፡
✿ከዚህ አያይዛም በኢትዮጵያ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ የሚሆነውን ሁሉ ነግራ ነፍሳቸውን ከሥጋቸው ለይታለች፡፡
✝የእመቤታችን ጣዕመ ፍቅሯ ፡ የጻድቁ ንጉሥም በረከት በዝቶ ይደርብን፡፡✝
✝ ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር✝
💠"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"💠
/ማቴ፫:፫/
" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል:: አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://t.me/zikirekdusn | 413 |
| 9 | ️🌹📘#የአባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ታሪክ ባጭሩ 🌹
📌 አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሐገራቸው ንሂሳ ግብጽ ነው፡፡ አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ልጅ አጥተው 30 ዘመን ሲያዝኑ ኖረዋል፡፡ አንድ ቀን አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥዕለ ሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን ክብሩ ከሰማይ ከፍታ የሚበጥ ልጅ እንኪ ተቀበይ የሚል ድምጽ ሰማች፡፡
♨ በዚህ መሠረት ቅዱስ አባታችን ጻድቁ አቡዬ ገብረ መንፈስ ቅዱስ መጋቢት 29 ተፀንሰው ታኀሣስ 29 ተወለዱ፡፡
♨አባታችን ዓይን በገለጹ ጊዜ ከሚታይ ነገር ላይ እንዲያርፍ እርሳቸውም በተወለዱ ጊዜ አፈፍ ተነስተው «ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ዘዓውፃእከኒ እምጽልመት ውስተ ብረሃን» ብለው አመስግነዋል።
♨በኋላም ምድራዊ መብል መጠጥ ሳይመገቡ ሳይጠጡ ለምስጋና ተግተው በመኖራቸው መላዕክትን ይመስላሉ፡፡
አባታችን ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
በኢትዮጵያ 262 ኖረው በ562 ዓመታቸው በተስፋቸው ያመነውን በኪዳናቸው የተማጸነ ጌታ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ሊምርላቸው ተስፋቸውን ተቀብለው በዕለተ እሁድ ዐርፈዋል፡፡
♨መላእክት በአክናፈ እሳት ኢየሩሳሌም ወስደው በየማነ ምስዋዕ ቀብረዋቸዋል፡፡
♨ለፅንሰትከ ፤ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሆይ በብሥራተ መልአክ ለተፀነስነከው መፀነስና በወርኃ ታኀሣሥ ለተወለድከው ልደትህ ሰላም እላለሁ።
🙏ክቡሩ አባት ሆይ ስለ ዓለሙ መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ጌትነቱ ልደት ተርሴስ ግብር እንደገበረ፤እኔም ፍጹም ልባዊ የእጅ መንሻ ወርቅ አቀርብልሃለሁ።
💙ለተኃፅኖትከ፥ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሆይ የቤተ ክርስቲያን መብራት የምትሆን የተመረጠች የክብርት እናትህን ጡት ባለመጥባት በመንፈስ ቅዱስ እንክብካቤ ስለ አደግኸው አስተዳደግህ ሰላም እላለሁ።
የአባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት በረከትታቸው አይለየን አሜን
ወስብሓት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክብር አሜን
ቴሌግራም ነው ተቀላቀሉ
https://t.me/Orthodoxtewahdoc | 281 |
| 10 | بدون متن... | 205 |
| 11 | ✳ጴጥሮስ ወ ጳውሎስ📍
"ወር በገባ በ5 የሐዋርያው ቅድስ ጴጥሮስ☞ለሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ወርሐዊ መታሰቢያቸው ነው፡፡☞ቅዱስ ጴጥሮስ የተወለደው በገሊላ ባሕር ዳር በምትገኘው በቤተ ሳይዳ
ነው፡፡ የአባቱ ስም ዮና ይባላል፡፡
☞ጌታን ከመከተሉ በፊት ከአምስት ዓመት ጀምሮ ያደገው በቅፍርናሆም ከተማ
ሲሆን በጎልማሳነቱ ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር በገሊላ ባሕር ዓሣ አጥማጅ
ነበረ፡፡ ማር16-18
☞ለደቀ መዝሙርነት ሲመረጥ ዕድሜው55 ዓመት እንደነበረ ይነገራል፡፡
☞የመጀመሪያ ስሙ ሰምዖን ሲሆን ጌታችን ጴጥሮስ ብሎታል፡፡ በላቲን ቋንቋ
ዐለት ማለት ነው፡፡
☞የመንግሥተ ሰማያት ቁልፍ ተሰጥቶታል፡፡
☞ቅዱስ ጴጥሮስ በማንኛውም ነገር ፈጣንና ቀልጣፋ እንደነበር ይነገራል፡፡
☞ቅዱስ ጴጥሮስ በፍልስጤም፤ በልዳ፤ በኢዮጴ፤ በቂሳሪያ፤ በገላትያ፤ በሮሜና
በተለያዩ ሀገሮች እየተዘዋወረ አሰተምሮ አሳምኗል፡፡
☞ከአሕዛብ ወገን የነበረ ቆርሌዎስን ከነቤተሰቡ አጥምቋል፡፡(የሐዋ' ሥራ
10፥38)
☞በጥብርያዶስ የጥርጥር ባሕር ጌታ እንዳዳነው(ማቴ14፤22)
☞ማልኮስ ጆሮውን እንደቆረጠው(ዮሐ18፤10
ጌታ በአይሁድ እጅ ተይዞ ሳለ የገባው ቃል አጥፎ ሦስት ጊዜ ጌታን አላውቀውም
ብሎ እንደካደ የማቴዎስ 26-፡ ተጠቅሶል
☞በኀላም ግን በንስሐ በመመለሱ ጌታ ግልገሎቼን አሰማረ፤ ጠቦቶቼን ጠብቅ፣
በጎቼን አሰማረ በማለት አደራ እንደሰጠው በወንጌል ተገልጿል (ዮሐ 21፥15)
☞ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ንጉሥ ነገሥት ኔሮን ቄሣር ዘመነ መንግሥት
በክርስቲያኖች ላይ ስደትና መከራ በመስቀል ተስቅሎ ግን እን እንደክርስቶስ
ተስቅሎ ሞት የማይገባኝ ስለሆነ ዘቅዝቃችሁ ስቀሉኝ ብሎ በሐምሌ 5
በሰማዕትነት አርፏል፡፡
☞1'2☞ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ
☞ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የተወለደው ጠርሴስ ከተማ ሲሆን ትውልዱ
ከዕብራውያን ከብንያም ነገድ ነው፡፡
☞ጠርሴስ በንግድ ዓለም የታወቀች የኪልቅያ ዋና ከተማ ነበረች፡፡
☞ሮማውያንም በሥራቸው ለሚተዳደሩ ሕዝቦች የሮማ ዜግነት ይሰጡ ሰለነበረ
የቅዱስ ጳውሎስ አባት በዜግነት ሮማዊ ነበር፡፡
☞ቅዱስ ጳውሎስ በ15 ዓመቱ ወደ ኢየሩሳሌም በመመለስ ከገማልያ
የአይሁድን ሕግና ሥርዓት ጠንቅቆ ተምሯል፡፡
☞በ30 ዓመቱም የአይሁድ ሸንጎ አካል ሆኖ ተቆጥሯል፡፡
☞በአይሁድ ሸንጎ አባልነት ለሁለት ዓመታት በሠራበት ወቅት ለኦሪት እምነቱ
ቀናተኛ ፈሪሳዊ በመሆኑ ክርስቲያኖችን በማንኛውም አጋጣሚ ይቃወምና ያሳድድ
ነበር፡፡
☞ቅዱስ እስጢፋኖስ ክርስትናን በማስተማሩ በአይሁድ ሸንጎ ተከሶ ሲቀርብ
የተከራከረውን ቅዱስ ጳውሎስ ነበረ፡፡
☞ኀላም በድንጋይ እስጢፋኖስ ሲወገር የወጋሪዎችን ልብስ ይጠብቅ የነበረው
እርሱ ነው፡፡
☞ቅዱስ ጳውሎስ ክርስቲያኖችን ሊሳድድ ሲሔድ ድንገት ታላቅ ብርሃን መጥቶ
ሳወል ሳወል ለምን ታሳድደኛለህ የሚል ድምፅ ከሰማይ መጣ፡፡
☞ሐዋርያውም ጳውሎስም ጌታ ሆይ አንተ ማነህ ብሎ በጠየቀ ጌዜ
የምታሳድደኝ እኔ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ አለው፡፡
☞ቅዱስ ጳውሎስ ከዛ በኃላ በሐናንያ ከተጠመቀና ከተማረ በኃላ አይሁድ ለኦሪት
ሕግ ሲቆረቆር የነበረው አሁን ደግሞ ስለ ወንጌል ሲሰብክ በማየታቸው አይሁድ
ሊገሉት ፈለጉ እሱ ግን ገላትያ፤ ጢሮአዳ፤ ኤፌሶን፤ ቆሮንቶስ፤ልስጥራ እና
ሌሎች ከተማ ወንጌልን በማስተማር ቆየ፡፡
☞በመጨረሻም በክርስቲያኖች ላይ ሞት ታወጆ ስለነበረ ሐዋርያው ቅዱስ
ጳውሎስ ከተማ ተይዞ 2 አመትከ7 ወር በጨለማ ቤት በእስር ከቆየ በኀላ በሮም
ከተማ በኦስትያ መንገድ አንገቱ ተሰይፎ በሐምሌ 5ቀን በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡
☞የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እና የቅዱስ ጴጥሮስ የጸሎታቸው በረከት
ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡
☞(ከቤተ ክርስቲያን ታሪክ መጽሐፍ የተወሰደ)
☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ | 240 |
| 12 | بدون متن... | 231 |
| 13 | 📘⛪#ተአምረ አቡነ ፊልጶስ🌹💖
📕•••ወር በገባ በ 5 ታሰበው የሚውሉ የአባታችን የአቡነ ፊልጶስ (ዘ ደብረ ቢዘን) በየወሩ የሚነበብ ገድላቸው ይህ ነው፡፡ወደ ሰማዕቱ አቡነ ፊልጶስ ምስክርነትና ተጋድሎ ወደ ነገሩ ትሩፋት እንመለስ፡፡
☞ሰለ አንደበቴ ድካምና ስለ ልቡናየ ጉድለት እየተንቀጠቀጥኩና እየፈራለሁ
የምነግራችሁ ትንሸ ስሙኝ፡፡
☞ነገር ግን ደስታን የተመላ መንፈሳዊ ቃልን ትሰሙ ዘንድ ገድሉን እናገራለን
መንፈስ ቅዱሳን እንደገለጠልኝ እናገራለሁ፡፡
☞መልካም ሥራን ለመስራት ይፈጥናል በንግግሩ ፀጥ ያለ ነው በሐሳቡም
ዝም ያለ ነው፡፡
☞በነፍሱም ንጽሕ ነው በሥጋውም የፀና ነው ከሰው ሁሉ ጋር ሰላማዊ ነው፡፡
በሥራውም እውነተኛ ነው፡፡ እንግዳ ምጽዋትን ወዳጅ ነው፡
☞ኑሮውም በጾምና በጸሎት ነው፡፡በጸሎትም ጊዜ እንደ ምሰሶ ይቆማል እንደ
መንኮራኩር ይሰግዳል፡፡
☞እንደ በደለኛ ሥጋውን እየገረፈ እንደ ምንጭ ውኃ ዕንባውን ያፈሳል፡፡
☞እንደ ልብስ ማቅን ይለብስ ነበር እንደ መታጠቂያም የብረት እሾህ
ይታጠቃል፡፡ ጥጋቡ ረኃብ ነው፡፡ መተጡም መጠማት ነው፡፡ ደስታውም ጾምና
ጸሎት ነው፡፡
☞መራቆት ነው፡፡ ሙቀቱም ውርጭ ነው የጉኑ ምኝታም እሾህ አሜካላ ነው፡፡ ስለ
ደስታ ምኝታም ከመሬትና ከአመድ ላይ ይተኛል፡፡
☞ዕረፍቱ ሥጋውን የሚያቀዘቅዙ ምንጣፎች ናቸው፡፡ ዕረፍቱም ሰውነቱን
ከሚቆርጥ ከተሳለ ድንጋይ ላይ መተኛት ነው፡፡ ጫማዎቹ የወንጌል ቃላት ናቸው፡፡
☞መመላለሱ ወደ ሃይማኖት ጎዳና ነው፡፡ የእጁ ምርኩዝ ድንቁርናን ጠላትን
የሚያሽንፍ መስቀል ነው፡፡ ዜማው በለሆሳስ ነው፡፡ ትሕትናው ራስን ማዋረድ
ነው፡፡
☞ኑሮው ፀጥታ ነው፡፡ ሰለ አቡነ ፊልጶስ ሁለተኛ በዋልድባ ገዳም የሚ
ገዳማውያን አባቶች ተናገሩ፡፡ ከፀሐይ ይልቅ የሚያበራ ሰውን አየን እንደ
መብረቅም ያበራል በሰማይ ላይም ይበራል በላዩ ላይም የሚያበራ ድባብ አለ
ብለው መስክረው ተናግረዋል፡፡
☞(ገድለ አበው ቅዱሳን ዘደብረ ቢዘን)
☞የጻድቁ አባታችን የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነሐሴ 5ቀን እድሜ እና ጤና ሰቶየዛ ሰው ይበሉን፡፡
☞የጻድቁ አባታችን የአቡነ ፊልጶስ የጸሎታቸው በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡
☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ
https://t.me/Orthodoxtewahdoc
በዚህ ጆይን እያላችሁ አንብቡ እናንብብ ከቅዱሳን በረከት ይክፈለን | 243 |
| 14 | بدون متن... | 177 |
| 15 | ✝✝✝ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፤፤ ✝✝✝
✝ መስከረም 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
+" ቅድስት ሐጊያ ሶፍያ "+
✝ዘመነ ሰማዕታት በሚል በሚታወቀው 3ኛው መቶ ክ/ዘመን ብዙ ቅዱሳት እናቶቻችን ስለ ፍቅረ ክርስቶስ አንገታቸውን ሰጥተዋል:: አንዳንዶቹ ደግሞ ሕይወታቸው እጅግ የሚያምር ነበር:: ከእነዚህ ቅዱሳት እናቶቻችን አንዷ ዛሬ የምናከብራት ሐጊያ ሶፊያ ናት::
+በዚህ ስም ከሚጠሩት አንዷ ስትሆን በቀደመ ሕይወቷ ክርስቶስን አታውቅም ነበር:: ጣዖትን የሚያመልኩ ወላጆቿ አሳድገው አጋቧት:: ከትዳሯም 2 ቡሩካት ሴቶች ልጆች ወልዳለች:: ስማቸውም አክሶስናና በርናባ ይባላል:: ልጆቿ ልብ እያገኙ በሔዱ ጊዜ ቅድስት ሶፍያ ስለ እውነተኛው አምላክ ትመራመር ገባች::
+በወቅቱ የነበሩ ብዙ ሃይማኖቶችን መዘነች:: ከክርስትና በቀር ግን ሌሎቹ ሚዛን እንደማይመቱም አስተዋለች:: "እውነኘተኛው አምላክ ሆይ! ምራኝ: እርዳኝም" ስትል ጸለየች:: መድኃኔ ዓለም ለጠሩት አያሳፍርምና ፈጥኖ በጐውን ጐዳና አሳያት::
+ድኅነት ለልጆቿም ይሆን ዘንድ ሁለቱንም ጠርታ ስለ ክርስትና አማከረቻቸው:: ደስ ብሏቸው ተቀበሏት:: እርሷም ጊዜ ሳታጠፋ ወደ ዻዻስ ሒዳ ማሕተመ ክርስትና: ሃብተ ውልድናን ትቀበል ዘንድ ከልጆቿ ጋር ተጠመቀች:: በቅድስናና ደስ በሚያሰኝ አኗኗርም እስከ መከራ ቀን ቆየች::
+የመከራ ጊዜ ሲደርስም ልጆቿን ጠርታ "ስለ ክርስቶስ ፍቅር እንሙት" አለቻቸው:: ቡሩካቱ አክሶስናና በርናባም ደስ እያላቸው "እሺ" አሏት:: ወዲያውም በመኮንኑ ፊት ቀርበው ክርስቶስን ከመካድና ከስቃይ ሞት የትኛውን እንደሚመርጡ ቢጠየቁ እነርሱ መሞትን መረጡ:: ወደ እሥር ቤትም ከተቷቸው::
+ቅድስት ሶፍያ 2 ልጆቿ ይጸኑላት ዘንድ አዘውትራ ገድለ ሰማዕታትን እና ክብራቸውን ትተርክላቸው ነበር:: በተለይ የታላቁዋን አንጌቤናይት (እመቤት) ሶፍያንና የ3 ልጆቿን (ዺስጢስ: አላዺስና አጋዺስ) ተጋድሎ እየነገረች ታጸናቸው ነበር::
+ከእሥር በኋላ ግርፋት ታዞባቸው እናት ራቁቷን ስትገረፍ መልአክ ወርዶ ሲጋርዳት ልጆች በማየታቸው ደስ አላቸው:: ቅድስት ሐጊያ ሶፍያና 2 ልጆቿ እጅግ የበዛ ስቃይን ስለ ቀናች እምነት ተቀበሉ:: ምላስ እስከ መቆረጥም ደረሱ:: በመጨረሻ ግን በዚህች ቀን ተገድለው አክሊለ ሰማዕታትን ገንዘብ አደረጉ::
+የመከራ ዘመን ካለፈ በኋላ ታላቁ ንጉሥ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ የሁሉን ቅዱሳን ቤት ሠርቶ የእርሷን በመዘንጋቱ ለራሱ ባሰራው ቤተ መንግስት ላይ ተአምር ታይቷል:: ለ3 ያህል ጊዜ ስሙን ሲያስቀርጽ መልአክ እየወረደ ይፍቀው: የሶፍያንም ስም ይጽፈው ነበር::
+በመጨረሻም ንጉሡ ልጁን እስከ መገበር ደርሶ ቤተ መንግስቱ የቅድስት ሶፍያና የ2 ልጆቿ ቤተ ክርስቲያን ለመሆን በቅቷል:: ምንም ለ3 ጊዜያት ያህል ሙሉ እድሳት ቢደረግለትም ዛሬ አሕዛብ የያዙትን ይህንን ቅርስ ንጉሡ የሠራው ከ1700 ዓመታት በፊት ነው::
+" ቅዱስ ማማስ ሰማዕት "+
✝የሰማዕቱ ወላጆች ቴዎዶስዮስና ታውፍና ሲባሉ ማማስ የሚለው የስሙ ትርጉም 'ዕጉዋለ ማውታ - እናት አባቱ የሞቱበት' ማለት ነው:: ለምን እንደዚህ ተባለ ቢሉ:- በዘመነ ሰማዕታት ስደት በሆነ ጊዜ ወላጆቹ ይዘውት ተሰደው ነበር:: ማምለጥ ባይችሉ ይዘው አሠሯቸው::
+በእሥር ቤትም ከስቃዩ ብዛት 2ቱም ልጃቸውን ማማስን እንዳቀፉት ሕይወታቸው አለፈች:: ሕጻኑ ሲያለቅስ የተመለከተች አንዲት ሴትም ራርታ እነርሱን አስቀብራ: እርሱን አሳድጋዋለች:: ስሙንም 'ማማስ' ብላዋለች::
+ቅዱሱ ባደገ ጊዜ የወላጆቹን ጐዳና በመከተሉ ተይዞ ለፍርድ ቀረበ:: ክርስቶስን አልክድም በማለቱም ብዙ ስቃይን አሳልፎ በዚህች ቀን ሰማዕት ሆኗል:: ቅዱስ ማማስ ከዐበይት ሰማዕታት አንዱ ሲሆን በአንበሳ ጀርባ ላይም ይቀመጥ ነበር::
+" አቡነ አሮን መንክራዊ "+
✝ኢትዮዽያዊው ጻድቅ አቡነ አሮን በ14ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበሩ ኢትዮዽያዊ ሲሆኑ በገዳማዊ ሕይወታቸው: በሐዋርያዊ አገልግሎታቸውና ነገሥታቱን ሳይፈሩ በመገሰጻቸው ይታወቃሉ:: በተለይም ሕይወታቸው በተአምር የተሞላ ስለነበር 'አሮን መንክራዊ' (ድንቅ አባት) ተብለው ይጠራሉ::
+አንዳንድ ጊዜም 'አሮን ዘመቄት /ዘደብረ ዳሬት/' በሚልም ይጠራሉ:: የአቡነ አሮን ወላጆች ገብረ መስቀልና ዓመተ ማርያም የሚባሉ ሲሆን ከልጅነታቸው ጀምረው በቅዱስ ቃሉ የታነጹ ነበሩ:: ምናኔን በደብረ ጐል: ከአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ጀምረው ብዙ ገዳማትን መሥርተዋል:: በርካታ ደቀ መዛሙርትንም አፍርተዋል::
+ለወንጌል አገልግሎት በወጡበት ጸሐይን አቁመው: ሕዝቡን ድንቅ አሰኝተዋል:: እንኳን ሰዉ ይቅርና አጋንንትም ያደንቁዋቸው ነበር:: ነገሥታቱንም ስለ ኃጢአታቸው በገሰጹ ጊዜ ራቁትነት: እሥራት: ግርፋትና ስደት ደርሶባቸዋል::
+ጻድቁ ከብዙ ተጋድሎ በኋላ በዚህች ቀን ወሎ መቄት ውስጥ በሚገኘው ገዳማቸው ዐርፈው ተቀብረዋል:: ገዳሙ እስካሁን ያለ ሲሆን ድንቅ ጥበበ እግዚአብሔር የሚታይበት ነው:: ጣራው ክፍት ሲሆን ዝናብ አያስገባም::
+" አፄ ልብነ ድንግል "+
✝እኒህ ንጉሥ ኢትዮዽያን ለዓመታት (ከ1500 እስከ 1532 ዓ/ም) ቢያስተዳድሩም 15ቱ ዓመት ያለቀው በስደት ነው:: ከደጋጉ አፄ ናዖድና ንግሥት ወለተ ማርያም ተወልደው: በሥርዓቱ አድገው ቢነግሡም: በክፉ መካሪዎች ጠንቅዋይ ወደ ቤታቸው ገብቶ ሃገሪቱን ለመከራ ዳርጉዋታል::
+ዛሬም ድረስ ጠባሳው ያለቀቀው የግራኝ ወረራ ለ15 ዓመታት ሃገሪቱን ያለ ካህንና ቤተ ክርስቲያን አስቀርቷት ነበር:: ብዙ ክርስቲያኖችም ሰልመው ቀርተዋል:: አፄ ልብነ ድንግል ግን ደብረ ዳሞ ገዳም ውስጥ ገብተው ንስሃ ጀመሩ: አለቀሱ: ተማለሉ::
+እመቤታችን ተገልጣም "ይቅርታን በነፍስህ እንጂ በሥጋህ አታገኝም" አለቻቸው:: እርሳቸውም ሱባኤውን ቀጥለው: 'ስብሐተ ፍቁርን': 'መልክአ ኤዶምን' የመሰሉ መጻሕፍትን ደርሰው በዚህች ቀን በ ዓ/ም ዐርፈዋል:: እኛ ክርስቲያኖችም እናከብራቸዋለን::
+የቅዱሳኑ አምላክ የወዳጆቹን ፈተና አስቦ ሃገራችንን ከጥፋት: ሕዝቡንም ከስደት ይሰውርልን:: ከበረከታቸውም አይለየን::
+መስከረም 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
2.ቅዱሳት አክሶስናና በርናባ
3.ቅዱስ ማማስ ሰማዕት
4.ቅዱሳን ቴዎዶስዮስና ታውፍና
5.አቡነ አሮን መንክራዊ
6.አፄ ልብነ ድንግል
++"+ ሞቱን በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን: ትንሳኤውን በሚመስል ትንሳኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን:: ከእንግዲህስ ወዲያ ለኃጢአት እንዳንገዛ የኃጢአት ሥጋ ይሻር ዘንድ አሮጌው ሰዋችን ከእርሱ ጋር እንደ ተሰቀለ እናውቃለን:: +"+ (ሮሜ. 6:5)
‹‹‹‹ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ›››› | 347 |
| 16 | بدون متن... | 414 |
| 17 | 🌼እንኳን አደረሳችሁ !
"" ከመካከላቸው ውጡ ! "" (፪ ቆሮ. ፮፥፲፯)
🍀ዐውደ ዓመት
(መስከረም 1 - 2019) | 548 |
| 18 | #ድንግል ሆይ የሚወዱሽ የተወደዱ ናቸው
#ንግስት ሆይ የሚያከብሩሽ የተከበሩ ናቸው
#ንፅሕት_ሆይ -የሚቀድሱሽ የተቀደሱ ናቸው
ፍስሕት_ሆይ -የሚመርቁሽ የተመረቁ ናቸው
#ልዕልት_ሆይ -የሚያደንቁሽ የተደነቁ ናቸው
#ውድስት_ሆይ ---ለንግሥትነትሽ የሚገዙ ሁሉ የተባረኩ ናቸው✝️❤️🤲
🌹✝️━━━━━━ ⊙ ━━━━━━✝️🌹
ድንግል_ሆይ ! ንፅህናን እንደ መላዕክት የለበሽ ፣ እንደ ነብያት መንፈስ ቅዱስን የተመላሽ ፣ ሁሉንም አሸናፊ በሚሆን በልዑል እግዚአብሔር እጅ የታነፅሽ የመለኮት ማደሪያ ነሽ ። ስለዚህ ክብርት ነሽ አርጋኖን ዘሠሉስ
ድንግል ሆይ _ባንቺ ያመን ነን አማላጅነትሽ አይለየን✝️❤️🙏 | 750 |
| 19 | አንዳንዴ ከልብ ሰው መሸሽን ልመዱ ይጠቅማችኋል ፤
ከሰዎች ጋር ያላችሁን ርቀት ሰፋ አድርጉት
የእውነት የሚወዳችሁ የሚያስብላችሁ የሚጨነቅላችሁ ሰው ከሆነ ? በመካከላችሁ ያለው ርቀት ይሰማዋል እናም ወደ እናንተ ቀረብ ይልና ያቺን ርቀት አጥብቦ ወዳጅነቱን ይቀጥላል
ቀድሞውኑ ደሞ በልቡ አንዲት ቅንጣቲት ታህል ቦታ የሌለው ሰው ይበልጥ ርቀታችሁን ያሰፋዋል ይጠፋል ነገር ግን በመጥፋቱ እናንተ ምንም አትጎዱም ትጠቀማላችሁ እንጂ !
ለማንኛውም ዙሪያችሁን በሚያስቡላችሁ ሰዎች ለመክበብ ሞክሩ ።
መልካም ቀን🥰✝🦋 | 785 |
| 20 | ✝መልክአ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ📗
🌷እግዚአብሔር አምላክ ከቅዱስ ወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ በረከት ረድኤት ይክፈለን🤲
https://t.me/Orthodoxtewahdoc ቤተሰብ ይኹኑ
ምልጃና ጸሎት ከሁላች ጋር ይሁን አሜን !!!🙏🙏🙏 | 690 |
