ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
کانال ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ) (@zikirekdusn) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 52 102 مشترک است و جایگاه 1 017 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 638 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 52 102 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 03 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 403 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 13 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 7.63% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 5.23% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 3 975 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 2 724 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 04 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 05 سپتامبر | +17 | |||
| 04 سپتامبر | +25 | |||
| 03 سپتامبر | +22 | |||
| 02 سپتامبر | +26 | |||
| 01 سپتامبر | +10 |
| 2 | https://youtu.be/QhguAezTUzg?si=uCgU6l68uTWOfa7k | 187 |
| 3 | بدون متن... | 1 689 |
| 4 | ✝እንኳን አደረሳችሁ !
☞ተፈጸመ ወርኀ ነሐሴ ቡሩክ፤ በሰላመ እግዚአብሔር ስቡሕ ወውዱስ፤ አሜን።
ወአመ ፴፦
✝ተዝካረ በዓሉ ለቅዱስ ማርቆስ ዘአንበሳ፥ ወንጌላዊ ወሐዋርያ ወሰማዕት
✝ወተዝካረ በዓሎሙ ለቅዱሳን፦ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት፥ ወአባ ሣሉሲ ክቡር፥ ወማር ጎርጎርዮስ ነባቤ መለኮት፥ ኦርኒ ንጽሕት፥ ወጤቀላ ድንግል፥ አንስት ንጹሐት ጲስጢስ፡ አላጲስ፡ ወአጋጲስ፥ ወቅድስት ሶፍያ እሞን፥ ወጻድቃን ዘዴጎ
❖ ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወንጹሕ ወድንግል፥ ወነቢየ እግዚአብሔር ልዑል፥ ማር ሚልክያስ ቡሩክ፥ ገሣጼ አብዳን፥ ዘተናገረ ትንቢተ ለሕዝበ ጼዋ፥ እምድኅረ ተሐንጸት ኢየሩሳሌም (፩ዱ እም፲ወ፪ቱ ደቂቀ ነቢያት ጻድቃን)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወንጹሕ ወድንግል፥ ገባሬ ተአምር ወመንክር፥ ማር እንድርያስ ወልደ ዮና፥ ሐዋርያሁ ወሰማዕቱ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ዘሎቱ ስብሐት ወአኮቴት፥ ቀዳሚሆሙ ለአርድእት፥ ወ፩ዱ እም፲ወ፪ቱ ሐዋርያት አበዊነ (ዘገብረ መንክረ በዛቲ ዕለት)
✝ክቡራን ወዐቢያን፥ ጻድቃን ንጹሐን፥ ወሐዋርያት መስተጋድላን፥ እለእስክንድሮስ ወሮፎስ ሰማዕታት፥ አርድእተ ቅዱስ እንድርያስ (ዘአስተርአዮሙ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ዘሎቱ ስብሐት)
✝ቅድስት ወቡርክት፥ ስብሕት ወክብርት፥ ዜና ማርያም እምነ ዘደሪጻ፥ መናኒተ ዓለም፥ ገዳማዊት ወተሐራሚት፥ ፈዋሲተ ዱያን ወገባሪተ ኃይል (ኢትዮጵያዊት)
°ቅድስት መካና ገዳመ ደሪጻ፥ ወቅዱሳን ውሉዳ መነኮሳት
✝ቅድስት ወቡርክት፥ ስብሕት ወክብርት፥ ማርያም ክብራ ተጋዳሊት፥ መናኒተ ዓለም፥ ወመዋዒተ ፍትወት፥ ወገባሪተ ተአምር ወመንክር (ዘደብረ ሊባኖስ)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወንጹሕ ወድንግል፥ ኃያል ወመስተጋድል፥ ወኤጲስ ቆጶስ ቡሩክ፥ ማር አባ ሙሴ ዘሀገረ ፈርማ፥ ብእሴ ሞገስ ወግርማ
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወንጹሕ ወድንግል፥ ጽሙድ ወመስተጋድል ኢትዮጵያዊ፥ ወብእሴ እግዚአብሔር፥ ማር አባ ዮስጢኖስ ገዳማዊ፥ መምህረ ሐፄ ዘርዓ ያዕቆብ ጻድቅ (ዘፈጸመ ገድሎ በምድረ ኤርትራ)
°ቅድስት ገዳሙ፥ ወቅዱሳን ውሉዱ መነኮሳት ጻድቃን
❖ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡
https://t.me/zikirekdusn | 1 620 |
| 5 | بدون متن... | 1 461 |
| 6 | ሴቶችን አትናቁ.m4a | 4 077 |
| 7 | بدون متن... | 4 018 |
| 8 | https://t.me/zikirekdusn | 2 786 |
| 9 | እንኳን አደረሰን !
ቅድስት ማርያም ክብራ ዘደብረ ሊባኖስ ዛሬ በዓለ ዕረፍቷ ነው።
የታላቁ ገዳም (በሴቶች ገዳም) የመጀመሪያዋ ሴት እመምኔት የነበረችው ቅድስት 70 (፸) ዘመን በተጋድሎ ኑራለች።
ከበረከቷ ያሳትፈነ!
https://t.me/zikirekdusn
https://www.youtube.com/@ZikereKedusan | 2 497 |
| 10 | بدون متن... | 1 796 |
| 11 | Deacon Yordanos Abebe:
፨፨፨በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን በዚችም ዕለት የእናታችን የቅድስት ዜና ማርያም አመታዊ የዕረፍት በዓሏ መታሰቢያ ነው፨፨፨
✝✞✝ ቅድስት ዜና ማርያም ✝✞✝
፨ በ11መቶ ክፍለ ዘመን በቅዱስ ላሊበላ ዘመነ መንግሥት ግንቦት 30 ቀን በጎጃም ክፍለ ሀገር ተወለደች። የአባቷ ስም ገብረ ክርስቶስ የእናቷ ስም አመተ ማርያም ይባላሉ። እጅግ እግዚአብሔርን የሚፈሩ፡ ቅዲስ ጋብቻቸውን በንጽሕና የሚጠብቁ፡ ለሰው የሚራሩ ደጋግ ሰዎች ነበሩ። እንዲህ ባለ መልካም ግብር ከኖሩ በኀላ በፈቃደ እግዚአብሔር 3 ወንዶች ልጆች እናት አንዲት ሴት ልጅ ወለዱ። ይህችም ሴት ልጅ ተወዳጇ እናታችን ቅድስት ዜና ማርያም ናት።
፨ ቅድስት ዜና ማርያም እናት እና አባቷን እያገለገለች፡ ፈርሐ እግዚአብሔን፡ በጎ ምግባርን ከወለጆቿ እየተማረች አደገች። ለአቅመ ሔዋንም በደረሰች ጊዜ ወላጆቿ ለአንድ ወጣት አጯት። ታላቅ ግብዣ ተደረጎ በተክሊል ተዳረች። በዚያው ወራት ግን የዜና ማርያም እናት አመተ ማርያም አምስተኛ ልጅ ወልዳ ተኝታ ሳለች በአካባቢው ሕማመ ብድብድ (ተላላፊ በሽታ) በመነሳቱ የዜና ማርያም እናት ታማ ነበር፡ በመጨረሻም ከዚህ ኃላፊ ዓለም አረፈች።
፨ ከዚህ በኋላ የታመመውን ወንድሟንና ሌሎቹንም በመያዝ ከተላላፊው በሽታ ለመትረፍ ሲሉ አካባቢውን ለቀው ወደ በረሃ ወጡ። በዚያም ሌሊት የዱር አራዊት መጥተው ከበቧቸው ሁሉንም ሊበሏቸው ሞከሩ እናታችን ቅድስት ዜና ማርያም ስመ እግዚአብሔርን ስትጠራ አራዊቱ ወደኋላ በመሸሽ ከአካባቢው ራቁ። እርሷም ከክፉ ሁሉ የጠበቃቸውን፡ ከአራዊት መበላት የሰወራቸውን እግዚአብሔርን አመሰገነች። በነጋም ጊዜ የታመመውን ወንድሟን እና ሌሎችን በመያዝ መንገድን ቀጠሉ አንዲት ባዶ ቤት አግኝተው ከእርሷ ተጠጉ። በፀሐዩ ንዳድና ታናሽ ወንድሟን በማዘል እጅግ ስለደከመች ከባድ እንቅልፍ ጣላት። ጠዋት ስትነሳ ግን የታመመው ወንድሟ ከአጠገቧ አላገኘችውም ሌሊት የዱር አራዊት በልተውታልና። አጅም አዘነች የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው ብላ አራሷን አፅናናች የወንድሟን ተረፈ ሥጋ አጠራቅሟ ቀበረች። በመቀጠልም በአካባቢው ካለ ገዳም ሔዳ ምንኩስናን ተቀበለች።
፨ ከዚህ በኋላ ባሏ አባቷን ሚስቴን አምጣ እያለ ስለጨቀጨቀው ከብዙ ልፋት እና ድካም ፈልጎ አገኛት ወደ ሀገሯም ወሰዳት። በዚያም ወደ ጉባኤ ቀርባ ለምን ወደ ገዳመ እንደሄደች እና ባሏን አንደከዳች ተጠየቀች። እርሷም እግዚአብሔር ከብዙ መከራ አድኖኛል እና እራሴን ለእግዚአብሔር ሰጥቻለሁ አለች። የጉባኤው ተሰብሳቢ በሏ ሀብቷን ወርሶ እንዲያሰናብታት ፈረዱ። እርሷም በዚህ ነገር በመስማማት የነበራትን ላም እና በሮች አስረከበች።
፨ ከዚህ በኋላ በአባቷ ቤት ለአንድ ዓመት ያህል በመቀመጥ የእናቷን ተዝካር አውጥታ ወደ ገዳሙ ተመለሰች በዛም ለጥቂት አመታት የተለያዩ ገድላትን ስትፈጽም ከቆየች በኋሏ ከነፍስ አባቷ ባሕታዊ አባ ገብረ መስቀል ጋር ወደ ጎንደር ሀገረ ስብከት ልዩ ስሙ እንፍራንዝ (ጣራ ገዳም) አካባቢ ዋሻ እንድርያስ በተባለው ለ25 ዓመት በብሕትውና ኖረች። አሁንም ድረስ በዚያ ዋሻ እናታችን ዜና ማርያም በፀሎት ጊዜዋ እንቅልፍ እንዳይጥላት ስትጠቀምበት የነበረ ዘንግ ፣ የምተቆምበት ዙሪያውን በገመድ የታሰረ የተቦረቦረ ግንድ አሁንም ድረስ ተአምር እየሰሩ ይገኛሉ። ከዚህም በመቀጠል ዛሬ ዜና ማርያም ተብሎ ወደ ሚጠራው ዋሻ ሔደች በዚያም በጾምና በጸሎት በልዩ ልዩ ተጋድሎ እስከ እለተ እረፍቷ ድረስ በዚያ ኖራለች።
+++ የገድል ዓይነቶች +++
፨ በየሰዓቱ ከ 100-300 ትሰግድ ነበር
፨ ሁለት ቀን እየፆመች በሶስተኛ ቀን ጥቂት ጥሬ ቀምሳ ሳምንቱን ታሳልፈው ነበር
፨ 150ን መዝሙረ ዳዊት እና ወንጌል በየቀኑ ትጸልይ ነበር
፨ በብሕትውና ወራት ማር፣ ቅቤን፣ ወተትን ፈጽሞ አትቀምስም ነበር
፨ የጌታችን መከራ መስቀል እና ስትየ ሐሞት በማሰብ በየሳምንቱ ዓርብ ዓርብ ኮሶ የሚባል ቅጠል እየበጠበጠች ከቅል ውስጥ ከሚገኘው መራራ ፍሬ ጋር በማዋሐድ ትጠጣ ነበር
፨ ከጸሎት እና ከስግደት በምታርፍበት ጊዜ አትክልት በመትከል እና በመኮትኮት ጊዜዋን ታሳልፍ ነበር
፨ የጌታችንን ግርፋቱን በማሰብ 100 ጊዜ ጀርባዋን ስለምትገረፍ እና ደም ስለሚፈሳት ጀርባዋ ይቆስል እና ይተላ ነበር።
+++ተአምራት+++
፨ ዓይናቸውን በተለያየ በሽታ የታመሙ ሰውዎች ሁሉ ከህመማቸው ተፈውሰዋል
፨ የራስ በሽታ ( የራስ ፍልጠት፣ ጭንቀት፣ ማዞር) የታመሙ ጸበሉን በመቀባት ድነዋል፡፡
፨ ጸበሉን በመጠመቅ፤ የጻድቋን ተአምር በማዘል፤ ስዕለት በመሳል መካኖች ወላድ ሆነዋል። ሌሎች በየቀኑ ብዙ ተአምራትን እናታችን ቅድስት ዜና ማርያም ታደርጋለች።
+++ቃል ኪዳን+++
ቅድስት ዜና ማርያም ከዚህ ዓለም የምታርፍበት ጊዜ እንደደረሰ በመንፈስ ቅዱስ በአወቀች ጊዜ ከታላቅ ዛፍ ወጥታ ስትፀልይ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከቅድስት ድንግል ማርያምና ከእልፍ አእላፋት ቅዱሳን መላእክት ጋር፣ ከነቢያት፣ ከሐዋርያት፣ ከሰማዕታት፣ ከጻድቃን፣ ከደናግል መነኮሳት ጋር በመሆን ተገልጾ ከአረጋጋት በኋላ ቃል ኪዳንን ሰጧታል።
፨ በፀሎትሽ ያመነውን ኃጢአቱን ይቅር እለዋለሁ
፨ በስምሽ የተራበውን ያበላ በመንግስተ ሰማያት ኅብስተ ሕይወት አበላዋለሁ፤ የተጠማውን ያጠጣ ጽዋዓ ሕይወትን አጠጣዋለሁ
፨ መጽሐፈ ገድልሽን የጻፈውን፡ ያጻፈውን፡ የሰማውን፡ ያሰማውን ስሙን በዓምደ ወርቅ እጽፈዋለሁ
፨ ከሕፃንነትሽ እስከ አሁን ድረስ ስለ እኔ ብለሽ ብዙ መከራ ተቀብለሻል፦ ደጅሽን የረገጠ የሦስት ጭነት ጤፍ ያህል ነፍሳትን እንደሚምርላት፡ እንዲሁም ከሲዖል ነፍሳትን እንደሚያወጣላት ጌታችን በማይታበል ቃሉ ቃልኪዳን ገብቶላታል። እንዲሁም ከሲዖል ነፍሳትን እንደሚያወጣላት፡፡
+++ ገዳሟ እና መገኛው+++
፨ የቅድስት ዜና ማርያም መካነ መቃብሯ ( ጸበሏ) በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ከም ከም ወረዳ ይገኛል ቦታውም አዲስ ዘመን ከተማ 20 ኪ.ሜ ርቆ የሚገኝ ሲሆን ከከተማው በስተሰሜን በኩል "ደሪጣ" ቀበሌ ገበሬ ማህበር ውስጥ ይገኛል።
"ደሪጣ"
ሸክላ ማርያም ተብላ ትጠራ የነበረችው ቦታ ስያሜው ተቀይሮ ደሪጣ ዜና ማርያም ዋሻ (ገዳም) ተብሎ እስከ አሁን ድረስ እየተጠራ ይገኛል፡፡ ይህን ስያሜ ያገኘውም በቅድስት ዜና ማርያም ገድል ውስጥ " ወትሰቲ ሲካር (ኮሶ) ደሪፃ" የሚል ቃል ይገኛል። ይህም ማለት ኮሶ የተባለውን እንጨት (ቅጠል) ቀጥቅጣ (አልማ) ከቅል ውስጥ ከሚገኘው ፍሬ ጋር በማደባለቅ ትጠጣለች ማለት ነው። ስለዚህ ቦታው "ደሪፃ" ተብሎ ተሰየመ በማለት በአካባቢው የሚገኙ አባቶች ይናገራሉ። በመጨረሻም ተጋድሎዋን በመፈጸም በዚሁ በተቀደሰ ስፍራ ነሐሴ 30 ቀን ከዚህ አለም ድካም ዐርፋለች። የእናታችን የቅድስት ዜና ማርያም በረከቷ ቸርነቷ ይደርብን። አሜንን!!
+++ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎታ፡፡ ወበረከታ ለቅድስት ዜና ማርያም የሀሉ ምስሌነ ለዓለመ ዓለም አሜን!!! +++
(በዲ/ያዕቆብ ሙሉጌታ / ዝክረ ቅዱሳን)
https://t.me/zikirekdusn
https://www.youtube.com/@ZikereKedusan | 1 782 |
| 12 | ✞And regarding this Abba Heryakos says, “[You are] the unsoiled hall of Malachi” (Anaphora of St. Mary No.36).✞The Prophet St. Malachi passed away after serving his Creator and guiding the people. Malachi means “angel, also one that’s sent.” And he was from the Tribe of Issachar.
✞✞✞ May the God of the Saints give us the thirteenth month sanctified and for repentance, as he has blessed the past twelve months. And may He grant us from the blessings of the Saints.
✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 30th of Nehasse
1. St. Andrew the Apostle
2. St. Malachi the Prophet
3. Abba Moses of the City of Farma
✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. Mark, the Apostle
2. Abba Shalusi the Honorable
3. St. Gregory the Theologian
4. St. Sophia Martyr
5. St. John the Baptist
✞✞✞ “Therefore take heed to your spirit, and let none deal treacherously against the wife of his youth. For the Lord, the God of Israel, saith that he hateth putting away” ✞✞✞
Mal. 2:15-16
✞✞✞ “Will a man rob God? Yet ye have robbed me. But ye say, Wherein have we robbed thee? In tithes and offerings. Ye are cursed with a curse: for ye have robbed me, even this whole nation.” ✞✞✞
Mal. 3:8-9
✞✞✞ Salutation to God ✞✞✞
(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe) | 1 731 |
| 13 | Memhir Esuendale:
Feasts of Nehasse 30
✞✞✞On this day we commemorate the Apostle St. Andrew and the Prophet Malachi✞✞✞
✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞
✞✞✞Our merciful God has enabled us to complete the Month of Nehasse in peace by the protection of His Fatherly grace; and without Him judging us saying, “Your sins have amassed and your bodies are defiled”. We forget that in these past thirty days, millions have died, millions have fallen ill and many have renounced their faith.
✞And we did not encounter all these, not because we are/were good, rather it was because His mercy was many folds upon us. Now, we have to pray to reach to the New Year in peace.
✞On this day, we commemorate the following saints.
✞✞✞St. Andrew the Apostle✞✞✞
✞✞✞The Holy Apostle was born and grew up around Bethsaida and was the younger brother of the Arch-apostle St. Peter. And his father was Jona. The Saint learned fishing from his older brother from his childhood. And when he was older, after learning the Old Testament, he became the disciple of St. John the Baptist.
✞After the Lord returned from His fast (in the Desert of Judea), St. Andrew followed Him inspired by the Holy Spirit. There, hearing St. John the Baptist’s testimony, “Behold the Lamb of God, which taketh away the sin of the world” (John 1:29), St. Andrew followed the Lord.
✞And for this, he was able to be called the first disciple of Christ. (John 1:47) And the scholar Mar Gelawdios in his praise to St. Mary (Hymns of the Icon) confirms it saying, “Mary you are the faith of the First Apostle Andrew.”
✞The Gospel tells us that the Holy Apostle was a haste servant (John 6:9/12:22). He preached in many parts of the world though his See was Lydda (Lod); after learning under the Lord for three years and three months, and receiving the Holy Spirit at the day of Pentecost.
✞Today is the day, on which the Apostle spoke with the Lord in a ship and saved St. Matthias from the hands of men who were cannibals (ate people).
✞Because all the seamen said that they would not allow St. Andrew and his disciples, who went to a dock to sail, to board their boats for a journey that would take thirty days, our Lord Jesus Christ, to Whom belongs glory, came as a young captain and took the Apostle and his disciples. Thus, He enabled them to complete the voyage in hours, which would have taken them thirty days.
✞St. Andrew thought that the captain was just a man and preached about the Lord to the Lord and wished Him well. However, when he knew that the captain was our Lord, he was shocked and wept.
✞As it says in the hymn,
“When he discerned You, and identified Your semblance;
He said ‘All that I told Thee in arrogance,
Redeem which I transgressed and have forgiveness’”
✞And he then said, “Forgive me?” and the Lord replied, “Be strong! I am with you.” The Holy Apostle departed while hastening for the Gospel on Tahisas 4 (December 13).
✞✞✞St. Malachi the Prophet✞✞✞
✞✞✞Malachi is one of the twelve Minor Prophets and is called the “Last Prophet.” There are two reasons for this.
1. There is no book of prophecy written after him.
2. And because the Era after his departure was the “Era of Priest”; even though prophets were extant in those times, only about a handful were spoken of.
✞The saint was born around six hundred years before the birth of Christ. And he has rebuked the people of Israel after their return from exile [from Babylon]. This was because the people did not stop committing sin, even after they returned from seventy years of bondage.
✞Especially, he rebuked those who dealt treacherously their wives of youth (Mal. 2:14), and he enunciated about tithes and offerings (first born and the like) (Mal. 3:8). He also spoke about our Lady the Virgin Mary by symbolizing her with a hall, which is pure (Mal. 3:1). | 1 847 |
| 14 | بدون متن... | 1 654 |
| 15 | ††† እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ እንድርያስ እና ለቅዱስ ሚልክያስ ነቢይ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††
††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††
††† መሐሪ እግዚአብሔር ኃጢአታችሁ በዛ: ሰውነታችሁ ከፋ ሳይል በአባታዊ ርሕራሔው ጠብቆ ይሔው ወርኀ ነሐሴን በሰላም አስፈጸመን:: አይመስለንም እንጂ በእነዚህ ሰላሳ ቀናት ሚሊየኖች አንቀላፍተዋል: ሚሊየኖች በደዌ ዳኝነት ተይዘዋል: በርካቶቹም ከሃይማኖታቸው ወጥተዋል::
እኛ ይህ ሁሉ ያልደረሰብን በጐ ስለሆንን አይደለም:: ይልቁኑ ቸርነቱ በእኛ ላይ ስለበዛ ብቻ ነው እንጂ:: አሁንም በሰላም ከአዲሱ ዘመን እንዲያደርሰን ልንማጸነው ይገባል::
በዚህች ዕለት ደግሞ እነዚህን ቅዱሳን እናከብራለን::
††† ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ †††
††† ቅዱሱ ሐዋርያ ተወልዶ ያደገው በቤተ ሳይዳ አካባቢ ሲሆን የሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ ትንሽ ወንድም ነው:: አባቱም ዮና ይባላል:: ገና ከልጅነቱ ጀምሮ ዓሣ ማጥመድን ከትልቅ ወንድሙ ተምሯል:: እድሜው ከፍ ባለ ጊዜ ኦሪትን ተምሮ የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሆኗል::
ከእርሱም እያገለገለ ለስድስት ወራት ተምሯል:: በወቅቱ ከወንጌላዊው (ወልደ ዘብዴዎስ) ዮሐንስ ጋር ቅርብ ባልንጀራም ነበር:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተጠመቀ ጊዜ ያን ድንቅ ምሥጢረ ሥላሴ ከተመለከቱትም አንዱ ነው::
ጌታ ከጾም (ከገዳመ ቆረንቶስ) በተመለሰ ጊዜ እንድርያስ መንፈስ ቅዱስ አነሳስቶት ተከትሎታል:: መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ "ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር ዘያዐትት ኃጢአተ ዓለም - የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ እነሆ::" ማለቱን ሰምቶ ቅዱስ እንድርያስ ጌታን ተከተለ::
በዚህም የመጀመሪያው የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ለመባል በቃ:: (ዮሐ. 1:47) ሊቁ ማር ገላውዴዎስም እመቤታችንን ሲያመሰግናት
"ለሐዋርያ እንድርያስ ቀዳማዊ ማርያም ሃይማኖቱ ( ለመጀመሪያው ሐዋርያ ለእንድርያስ ሃይማኖቱ ማርያም አንቺ ነሽ::)" ብሏል::
(መልክዐ ስዕል)
ቅዱሱ ሐዋርያ ስሉጥ (ፈጣን) አገልጋይ እንደ ነበርም ወንጌል ይነግረናል:: (ዮሐ. 6:9, 12:22) ለሦስት ዓመታት ከሦስት ወር ከጌታ እግር ሥር ተምሮ: በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስን ተቀበሎ: ምን ሃገረ ስብከቱ ልዳ ብትሆን ብዙ አሕጉረ ዓለምን ሰብኳል::
ይህች ቀን ሐዋርያው ከጌታ ጋር በመርከብ ውስጥ የተነጋገረባትና ቅዱስ ማትያስን ሰውን ከሚበሉ ሰዎች እጅ ያዳነባት ናት::
ቅዱስ እንድርያስ ሰላሳ ቀናት የሚፈጅ የባሕር ላይ ጉዞ ለማድረግ ከአርድእቱ ጋር ወደ ወደብ ቢሔድም መርከበኞች ሁሉ አናሳፍርም በማለታቸው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወጣት መርከበኛ መስሎ ሐዋርያውንና አርድእቱን የሰላሳውን ቀን መንገድ በሰዓታት ልዩነት እንዲጨርሱ አድርጓል::
ቅዱስ እንድርያስም ፍጡር (እንዲሁ ሰው) መስሎት ለጌታችን ስለ ጌታችን ሰብኮለታል: መርቆታልም:: መርከበኛው ጌታችን መሆኑን ሲያውቅም ደንግጦ አልቅሷል::
"ሶበ አእመረ ኪያሁ ወጠየቀ አምሳሎ:
ዘተናገርኩ በድፍረት ምስሌከ ኩሎ:
ሥረይ ሊተ ጌጋይየ ወኅድግ ይቤሎ::" እንዲል "ማረኝ?" ብሎታል:: ጌታችንም "አይዞህ እኔ ከአንተ ጋር ነኝ::" ብሎታል:: ቅዱሱ ሐዋርያ ለወንጌል አገልግሎት ተግቶ ያረፈው ታኅሣሥ 4 ቀን ነው::
††† ቅዱስ ሚልክያስ ነቢይ †††
††† ሚልክያስ ከአሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ ሲሆን "የመጨረሻው ነቢይ" እየተባለ ይጠራል:: ለዚህ ምክንያቶቹ ሁለት ናቸው::
1ኛ. ከእርሱ በኋላ የተጻፈ ጥሬ የትንቢት መጽሐፍ የለም::
2ኛ.እርሱ ካረፈ በኋላ ያለው ዘመን "ዘመነ ካህናት" በመሆኑ ምንም ነቢያት በየጊዜው ባይጠፉ ጐልተው የተነገረላቸው ጥቂቶቹ ናቸው::
ቅዱሱ የተወለደው ቅ/ል/ክርስቶስ ስድስት መቶ ዓመት አካባቢ ሲሆን ከሚጠት (ከባቢሎን ምርኮ መልስ) ሕዝቡን ገስጿል:: ሕዝቡ ከሰባ ዓመት መከራ እንኳን ተመልሶ ኃጢአትን መሥራትን ቸል አላለም ነበር::
በተለይ የልጅነት ሚስታቸውን የሚያታልሉትን ገስጿል:: (ሚል. 2:14) ስለ አሥራትና በኩራትም ተናግሯል:: (ሚል. 3:8) እመቤታችን ድንግል ማርያምንም በንጽሕት አዳራሽ መስሎ ተናግሯል::
"ጽርሕ ንጽሕት ዘሚልክያስ" እንዳሉ አባ ሕርያቆስ::
(ቅዳሴ ማርያም)
ነቢዩ ቅዱስ ሚልክያስ ፈጣሪውን አገልግሎ: ሕዝቡን መክሮ ዐርፏል:: ሚልክያስ ማለት "መልአክ: አንድም የተላከ" ማለት ነው:: ነገዱ ከነገደ ይሳኮር ነው::
††† አምላከ ቅዱሳን አሥራ ሁለቱን ወራት እንደ ባረከልን አሥራ ሦስተኛዋንም ለንስሐ ቀድሶ ይስጠን:: ከቅዱሳኑም በረከትን ያካፍለን::
††† ነሐሴ 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ
2.ቅዱስ ሚልክያስ ነቢይ
3.አባ ሙሴ ዘሃገረ ፈርማ
††† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ማርቆስ ዘአንበሳ (ሐዋርያ)
2.አባ ሣሉሲ ክቡር
3.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
4.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
5.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
††† "ስለዚህ መንፈሳችሁን ጠብቁ:: ማንም የልጅነት ሚስቱን አያታልል:: 'መፋታትን እጠላለሁ' ይላል የእሥራኤል አምላክ: የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር::" †††
(ሚል. ፪፥፲፭)
††† "ሰው እግዚአብሔርን ይሰርቃልን? እናንተ ግን እኔን ሰርቃቹሃል:: እናንተም 'የሰረቅንህ በምንድን ነው?' ብላቹሃል:: በአሥራትና በበኩራት ነው:: እናንተ: ይህ ሕዝብ ሁሉ እኔን ሰርቃቹሃልና በእርግማን ርጉሞች ናችሁ::" †††
(ሚል. ፫፥፰)
††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† | 2 615 |
| 16 | بدون متن... | 3 908 |
| 17 | https://youtu.be/NV2QBmcSw7E?si=rVB2i7Ch4X984oGg | 1 |
| 18 | https://youtu.be/NV2QBmcSw7E?si=6UIthXD9YXAy5CTJ | 4 341 |
| 19 | https://youtu.be/So17bkirMnY?si=s-cGpD-FY4iRSPaB | 4 486 |
| 20 | بدون متن... | 4 471 |
