"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን /አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ። 📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜንለምት @fentanesh21_23 🗯ፈንታነሽ / የእመ ብርሃን ልጅ🤗
Mostrar más📈 Análisis del canal de Telegram "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
El canal "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 (@orthodoxtewahdoc) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 25 358 suscriptores, ocupando la posición 2 926 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 1 321 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 25 358 suscriptores.
Según los últimos datos del 26 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -56, y en las últimas 24 horas de -21, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 3.78%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 2.59% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 959 visualizaciones. En el primer día suele acumular 658 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 15.
📝 Descripción y política de contenido
El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን
/አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc
ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ።
📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜንለምት
@fentanesh21_23
🗯ፈንታነሽ / የእመ ብርሃን ...”
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 27 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.
Carga de datos en curso...
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 27 julio | 0 | |||
| 26 julio | 0 | |||
| 25 julio | +24 | |||
| 24 julio | 0 | |||
| 23 julio | +23 | |||
| 22 julio | +27 | |||
| 21 julio | +14 | |||
| 20 julio | +29 | |||
| 19 julio | +1 | |||
| 18 julio | 0 | |||
| 17 julio | +1 | |||
| 16 julio | +22 | |||
| 15 julio | +24 | |||
| 14 julio | +15 | |||
| 13 julio | +23 | |||
| 12 julio | 0 | |||
| 11 julio | 0 | |||
| 10 julio | 0 | |||
| 09 julio | +13 | |||
| 08 julio | +19 | |||
| 07 julio | +33 | |||
| 06 julio | +36 | |||
| 05 julio | +3 | |||
| 04 julio | 0 | |||
| 03 julio | 0 | |||
| 02 julio | +49 | |||
| 01 julio | +15 |
| 2 | ✝በዚህች ሐምሌ 20 ዕለት የጻድቁ ዓቢየ እግዚእ ታናሽ እኅት ትቀድሰነ ማርያም ልጅ፤ የደብረ ሃሌ ሉያው ኮከብ አቡነ ሳሙኤል (በ1347 ዓ/ም) ዐረፉ✝
✝እናታቸው ትቀድሰነ ማርያም አባታቸው ይስሐለነ እግዚእ ይባላሉ።
✝የመጀመሪያ ስማቸው አቡነ ዓብየ እግዚእ ነአኩቶ ለአብ ብለዋቸዋል።
✝አባ እንጦንስ ኢትዮጵያዊ ደግሞ አቡነ ሳሙኤል ብለዋቸዋል።
✝ደቀ መዝሙራቸው አባ ገብረ መስቀል ይባላሉ።
"በረከታቸው በዝታ ትደርብን!"
✝ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት
🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)
🔗https://t.me/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan | 509 |
| 3 | "አጠንክረኝ" በሉት!
አንዳንዴ እንዲሁ ልባችሁ ትደክማለች፣ የመታፈን የመታወክ ስሜት ይሰማታል፣ የምትሰሩት ጥቂት ነው ድካማችሁ ግን እጅግ ብዙ ነው፣ ትልቅ ብሩህ ተስፋ ይታያችኋል ዛሬ ግን በጨለማ ውስጥ ትመላለሳላችሁ፣ አቅም ጉልበት እንዳላችሁ ታውቃላችሁ ነገር ግን እርሱም አሁን ከድቷችኋል፣ ሰው ሁሉ የሚፈልጋችሁ የሚወዳችሁ ይመስላችኋል ነገር ግን ሰው የሚፈልጋችሁ የምትጠቅሙት ከሆነ ብቻ እንደሆነ እያያችሁት ነው። ከዚህ ምድራዊ እውነት ጋር አትታገሉ። ይሔ ሁኔታ የሰው ልጅ ተፈጥሮ ነውና አትደናገጡ አትጨነቁ እዲሁ አምናችሁ ተቀበሉት። ለዚህ ችግር መፍትሔው ሌላ ልፋት፣ ሌላ ድካም፣ ሌላ ስራ ወይም ሌላ ሰው አይደለም። ለዚህ ሁሉ መፍትሔው የልብ እረፍት ነው። ልባችሁ ታርፍ ዘንድ ፍቀዱ፣ ልባችሁ አባቷን ታገኝ ዘንድ ፍቀዱ፣ አምላኳ ይፈውሳት ዘንድ በሩን ክፍቱላት። ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር ክፍሉ እንዲህ ይላል፦ "ከሀዘን የተነሳ ሰውነቴ አንቀላፋች በቃልህ አጠንክረኝ።" እናንተም እንዲህ በሉ "አጠንክረኝ፣ አበርታኝ፣ ደግፈኝ፣ ፈውሰኝ።" ምድራዊ ሩጫ ከዓለም ድካም አያሳርፋችሁም፣ ስለቁስና ገንዘብ መጨነቅ ሀብትና ንብረት አይጨምርላችሁም፣ ሰውን ለማስደሰት መኳተን የሰው ፍቅር አይሰጣችሁም። ምድር የራሷ ያልተፃፈ ህግ አላትና ህጓን በሙግትና በክርክር ለማስቀየር አትሞክሩ።
አዎ! "አጠንክረኝ" በሉት! ሰው ሆናችሁ አለመድከም፣ ሰው ሆናችሁ አለመዛል አትችሉምና በእያንዳንዱ የህይወት ጉዟችሁ አጠንክረኝ በሉት፣ እኔ ጉልበት የለኝምና አንተ ጉልበት ሁነኝ፣ አንተ አበርታኝ፣ አንተ አሻግረኝ በሉት። ብዙዎቻ በራሳቸው ሃይልና ጉልበት ይመካሉ፣ ብዙዎች በራሳቸው ንብረትና ሀብት፣ በዘመድ አዝማድ ይመካሉ ነገር ግን እነዛ የተመኩባቸው አንዳቸው እንኳን ዋስ ጠበቃ፣ አዳኝ ሆነዋቸው አያውቁም። ብልህና በሳል፣ ጠቢብና አስተዋይ የሆኑ ሰዎች ብቻ የሚያውቁት አንድ የተለየ እውነት አለ። እርሱም በምድርም በሰማይም፣ በየብስም በውሃ ውስጥም ዋስ ጠበቃቸው፣ ጠባቂያቸው እውነተኛ ወዳጃቸው አምላካቸው እንደሆነ ያውቃሉ። ይህንን ማወቅ የተለየ ተሰጥዖ ወይም የተለየ ተነሳሽነት አያስፈልገውም ነገር ግን አንድ ነገር ያስፈልገዋል፦ ፈሪሃ እግዚአብሔር ያስፈልገዋል። በመውደድ አምላክን መፍራት፣ በማፍቀር፣ ስራዎቹን በማድነቅ፣ ማዳኑን በማየት፣ ቸርነት ርህራሔውን በማስተዋል አምላክን መፍራት ያስፈልጋል። አንዳንዶች እርሱ ድከሙ፣ እርሱ ጣሩ፣ እርሱ ተሰቃዩ ያላቸው ይመስል ሌትከቀን ምሬታቸውን ወደርሱ ይልካሉ። ነገር ግን ምሬትን ልኮ ደስታን ማግኘት፣ ችግርን ተንትኖ ሰላምን ማትረፍ አይቻልም። ወደ አምላካችሁ ምን አየላካችሁ እንደሆነ ራሳችሁን ጠይቁ። እርሱ ልብና ኩላሊትን የሚመረምር አምላክ ነውና ለያናዳንዱ ሃሳብና ንግግራቹ ፍፁም ተጠንቀቁ። አንዳች የምሬት ስህተት እንኳን እልፍ ፈተናን፣ እልፍ ድካምን ልታመጣ እንደምትችል አስተውሉ።
አዎ! ጀግናዬ..! ልብህ እንዳትፈተን አትታገል ይልቅ በፈተናም ሆነ በደስታ ውስጥ በአምላኳ ተማምና እንድታርፍ አግዛት። አሁን አሁን ብዙ ሰው ብቻውን የሚሰቃይ፣ ብቻውን ተለይቶ የተጎዳ፣ እንዲሁ ብቻውን ሰላም ያጣ ይመስለዋል። ነገር ግን እውነቱ ሌላ ነው በዚህ ዘመን የሚኖር በየትኛውም የዓለም ክፍል የሚገኝ ሰው ሁሉ እረፍት የለም፣ ውስጡ ሰላም ጎድሎታል፣ መረጋጋት ተስኖታል፣ ድካሙ ፍሬ አጥቶበታል። የሚያውቅ ያውቀዋል ግማሹ በዝናው ውስጥ ሊደበቅ ይሞክራል፣ ግማሹ በሰው ተከቦ ሊያመልጠው ይሻል፣ ሌላው ደግሞ ያለእረፍት በመስራት የሚያመጣው ገንዘብ ነፃነትን እንዲገዛለት ይፈልጋል። ነገር ግን ሀሉም የተሳሳቱት አንድ ነገር አለ። ነፃ ህይወት በዚህ ምድር ላይ የለም፣ በድብብቆሽ የሚመጣ አንዳች ደስታና ሰላም የለም። መረጋጋትን ከፈለክ መሸሹን አቁመህ ስሜትን ፊትለፊት ተጋፈጠው፣ የእውነት ከጭንቀትና ከድብርት መውጣት ከፈለክ በፍፁም አትቸኩል፣ ነፍስህን አታፍናት። ዓለም ከምትሰጥህ በላይ የሰማይ አባትህ የሚሰጥህን በረከት ለመቀበል ዝገጁ ሁን፣ ሺህ ዓመት ብትሮጥ፣ ለዘመናት ጠንክረህ ብትሰራ፣ ለዓመታት ደከመኝ ሳትል ብትለፋ የማትቀድመህ ፈጣሪ እንዳለ አስተውል። በእያንዳንዱ እርምጃህ እርሱን አስቀድም፣ የውስጥ ሰላምና እርፍትን ብቻ ሳይሆን እርሱን በማመን ብቻ የምታገኘውን ዘላለማዊ በረከት አጣጥም። | 1 |
| 4 | ❗ከዋሸህ አትማል አንዱ ኃጢአት ይበቃል📍
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"📖ምሳ 1፥33☦📚
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
📗ስንክሳር ዘወርኃ ሐምሌ 20
https://t.me/Orthodoxtewahdoc
🌹የያዕቆብ ሌሊት ይሁንልን🕊
በጸሎታችሁ ወለተ ሥላሴ እያላችሁ እስቡኝ | 625 |
| 5 | Sin texto... | 608 |
| 6 | ዓመታት እያለፉ ሲሄዱ፣ሁሉም ነገር ይለወጣል! ጸንቶ የሚኖረው ግን ለሌሎች የሰጠነው ፍቅር፣ ያሳየነው ቸርነት፣ የፈጠርነው ውበት፣ የሌሎችን ሸክም ለማቃለል ያደረግነው እገዛ እና የገዛ ዕድላችንን በፅናት የተቀበልንበት ድፍረት ብቻ ነው!
Amari La | 685 |
| 7 | ለማንም ሰው ክፉ ነገር አልመኝም። ነገር ግን፣ የራሳቸውን ባህሪ የሚያስከትለውን ውጤት በትክክል እንዲረዱ፣ ልክ እንደራሳቸው የሆነን ሰው አንዴ ብቻ እንዲያገኙ የምመኛቸው አንዳንድ ሰዎች አሉ። | 790 |
| 8 | ስለ ሊቀ መላእክት ስለ ቅዱስ ገብርኤል ስለ ቅድስት ኢየሉጣ ወ ቅዱስ ቂርቆስ ጠበለ ፃድቅ ቅመሱ🌷🥰 | 805 |
| 9 | ወር በገባ በ20 ፃድቁ አባታችን አቡነ ሃፂር ናቸው ።
ወቶ ከመቅረት ካልታሰበ አደጋ ይሰውሩን።🙏❤ | 697 |
| 10 | ❇#ፃድቁ_አባ_ዮሐንስ_ሐፂር_።
☞•••ወር በገባ በ20 የአቡነ ዮሐንስ ሐፂር ወርሐዊ መታሰቢያቸው ነው አቡነ ዮሐንስ ሐጺር ቁመታቸው አጭር ስለ ነበር ዮሐንስ ሐጺር አጭሩ ዮሐንስ ተብለዋል፡፡ ☞በ18 ዓመታቸው እስቄጠስ ገዳም ገቡ ☞አባታችን አቡነ ዮሐንስ በታዛዥነታቸው በእጅጉ ይታወቃሉ፡፡ ይህንንም ለመፈተን አንድ ቀን አባ ባይሞይ የደረቀ እንጨት አንስተው ለአቡነ ዩሐንስ ሰጧቸውና ይህን ደረቅ እንጨት ትከለውና ውሃ እያጠጣህ አብቅለው ፍሬ እስኪያፈራም ተንከባከበው አሏቸው፡፡
☞አቡነ ዮሐንስም በፍጹም መታዘዝ እሸ ብለው ደረቁን እንጨት ተክለው ሦስት
ዓመት ሙሉ ከሩቅ ቦታ በቀን ሁለት ጊዜ ውኃ እየቀዱ በማምጣት ማጠጣት
ጀመሩ፡፡
☞በ3ኛውም ዓመት ደረቁ እንጨት ጸድቆ ለመለመ ታላቅ ዛፍም ሆኖ አብቦ
አፍርቶ ጣፋጭ ፍሬ አፈራ፡፡ አባ ባይሞይም ፍሬውን ቆርጠው ወስደው የታዛዡን
የትሑቱን ፍሬ እንሆ ቅመሱ እያሉ ሀቅዱሳን ሰጧቸው፡፡ ቅዱሳኑም እግዚአብሔርን
እያመሰገኑ ተመገቡ፡፡
]አባታችን ትልቁ የቅድስና ደረጃ ላይ ሲደርሱ ቀና ቢሉ ሥልሱ ቅዱስን
ይመለከታሉ ዝቅ ቢሉ ደግሞ እንጦሮጦስን ያያሉ፡፡ አቡነ ዮሐንስ ሐጺር በታላቅ
ተጋድሎአቸው ሥሉስ ቅዱስን በገሃድ ለማየት የበቁ ታላቅ አባት ናቸው፡፡
☞ከአባታችን ከአባ ዮሐንስ ሐጺር የህይወት ትምህርቶች መካከል
☞1'1☞የጠላቱን ከተማ ለመቆጣጠር የዘመተ ንጉሥ አስቀድሞ የውኃውን
መንገድ ይዘጋል፤ የእህሉንም መግቢያ ይይዛል፡፡ ያንጊዜ ጠላቶቹ ይራባሉ
ይጠማሉ፡፡ በመጨረሻም እጃቸውን ይሰጣሉ፡፡ የነፍስን ፆር ለማሸነፍም
በተመሳሳይ መንገድ መጠቀም ይገባል፡፡ በጾም በረኃብ ከጸና የነፍሱ ጠላቶች
ይዳከማሉ፡፡
☞1'2☞እኔ በትልቅ ዋርካ ሥር የተቀመጠንና አራዊት ሊጣሉት የመጣን ሰው
እመስላለሁ፡፡ ሊቋቋማቸው እንደማይችል ከተረዳ ሸሽቶ ወደ ዛፋ በመውጣት
ነፍሱን ያድናል፡፡ በእኔም የተፈጸመው ይኸው ነው፡፡
☞በባኣቴ ተቀምጪ ክፋ ሐሳቦች ሊቃወሙኝ ሲመጡ ልቋቋማቸው እንደማልች
ባወቅኩ ጊዜ በጸሎት ወደ፡እግዚአብሔር ሸሽቼ እመሽጋለሁ፡፡ በዚያም ከጠላቶቼ
ፍላፃ እድናለሁ፡፡
☞1'3☞መለወጥ የምትፈለግን ነፍስ በተመለከተ አባ ዮሐንስ እንዲህ አለ
በአንዲት ከተማ ውስጥ ብዙ ወዳጆች የነበሯት አንዲት አመንዝራ ሴት ነበረች፡፡
ከገዥዎቹ አንዱ ቀረባትና መልካም ሴት ለመሆን ቃል ግቢልኝና አገባሻለሁ
አላት፡፡ እርሷም ቃል ገባችለትና ተጋቡ፡፡ ወደ ቤቱም ወሰዳት፡፡
☞የቀድሞ አፍቃሪዎቿ ያቺን ሴት ፈለጓት እርስ በርሳቸውም ያ ልዑል ወደ ቤቱ
ወሰዷታል ወደ ቤቱ ብንሔድ ይቀጣናል፡፡ ነገር ግን ፧ጓሮ በኩል እንሒድ፤
ለርሷም እና ፏጭላት የፋጨቱን ድምጽ ስትሰማ ከደርቡ ወርዳ ወደኛ
ትመጣለች በዚህም ያለ ችግር እናገኛታለን ተባባሉ፡፡ ወደ ቤቷም ጓሮ ተጉዘው
ያፏጩ ጀመር፡፡
☞እርሷ ግን የፋጨቱን ድምፅ ስትሰማ ጆሮዎቿን ደፈነች፡፡ ወደ ውሳጣዊው
እልፍኝም ገባች፡፡ በሩንም ጥርቅም አድርጋ ዘጋች፡፡
☞ይቺ ሴት የኛ ነፍስ ምሳሌ ናት፡፡ ወዳጆቿ የተባለም ፈተናዎቿ ናቸው፡፡ ገዥ
የተባለውም ክርስቶስ ነው፡፡ እልፍኝ የተባለው ዘለዓለማዊ ቤት ነው፡፡ እነዚያ
የሚያፏጩት ክፋዎች አጋንንት ናቸው፡፡ ነገር ግን ነፍስ ሁለጊዜም በክርስቶስ
አምባነት ትሸሸጋለች፡፡
☞(በዲያቆን ዳንኤል ክብረት"በበረሓው ጉያ ውስጥ ከሚለው መጻሐፍ
የተወሰደ፡፡)
☞የጻድቁ አባታችን የአቡነ ዮሐንስ ሐጺር የጸሎታቸው በረከት አይለየን፡፡
☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ
☞ | 575 |
| 11 | Sin texto... | 394 |
| 12 | 🌹#ቅዱስ_በብኑዳ ሰማዕት🌹
❖📌 ወር በገባ በ20 የቅዱስ በብኑዳ መታሰቢያ ነው ይህ ቅዱስ ለብቻው የሚኖር ዕውነተኛ ተጋዳይ ነው የእግዚአብሔር መልአክም ተገልጦለት የመቀደሻ ልብስ ለብሰህ ወርደህ ለመኰንኑ ተገለጥለት አለው።
❖ በዚያን ጊዜ መኰንኑ አርያኖስ ከመርከብ ወርዶ ወደዚያች አገር ወደብ መድረሻው ጊዜ ነበር፤ ይህንንም ባሕታዊ ፈልጎት አላገኘውም ነበር፤ እነሆ ቅዱስ በብኑዳም በፈቃዱ መጥቶ ወደ መኰንኑ ሔዶ በክብር ባለቤት በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ የማምን በግልጥ እኔ ክርስቲያን ነኝ ብሎ በታላቅ ቃል ጮኸ።
❖ መኰንኑም ፈልጎ ያጣው የታወቀ ባሕታዊ መሆኑን በአወቀ ጊዜ እንዲአሠቃዩት በእግር ብረትም አሥረው ከጨለማ ቤት እንዲጥሉት አዘዘ፤ በዚያን ጊዜም ብርሃን ወጣ የእግዚአብሔር መልአክም ከሕማሙ ፈወሰው አበረታው አጽናናውም።
❖ በዚያችም አገር ስሙ ቄርሎስ የሚባል ምእመን ሰው ነበረ ከእርሱ ጋራም ሚስቱና ዐሥራ ሁለት ጐልማሶች ልጆቹ አሉ፤ እነዚህን ሁሉንም የከበረ በብኑዳ አስተማራቸው አጽናንቷቸውም ራሶቻቸውን ቆርጠዋቸው በሰማዕትነት ሙተው አክሊልን ተቀበሉ።
❖ አርያኖስም ተቆጥቶ በቅዱሱ አንገት ከባድ ደንጊያ ሰቅለው ወደ ባሕር ይጥሉት ዘንድ አዘዘ በእግዚአብሔር ኃይልም ከድንጋዩ ጋራ ዋኘ ደግሞ ከሰሌን ዛፍ ላይ ይሰቅሉት ዘንድ አዘዘ ያቺም ሰሌን ዐሥራ ሁለት ዘለላን አፍርታ ለመጪው ትውልድም መታሰቢያ ሆነች፤ ከዚህም በኋላ የከበረች ራሱን ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለ በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን።
አርኬ
✍️ሰላም ዕብል ለበብኑዳ ሰማዕት። እንተ አግሀደ ብርሃነ በቤተ ጽልመት። ወአመ ሰቀልዎ ሎቱ መልዕልተ በቀልት። አውጽአት ፍሬ በይእቲ ሰዓት። እስከ ጉቡአን አንከሩ እምዛቲ ትእምርት።
✍️ሰላም ለክሙ ማኅበረ በብኑዳ በሕቁ። ዐሠርተ ወክልኤቱ እለ ትትኌለቁ። ወሰላም ካዕበ ለዘተለውዋ ለጽድቁ። ቄርሎስ ወብእሲቱ ወዓዲ ደቂቁ። እስከ በደሞሙ ኅቡረ ተጠምቁ።
🌹ምንጭ እህታችን ፍቅርተ ሥላሴ🌹 | 450 |
| 13 | Sin texto... | 438 |
| 14 | ✝††† እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እና ለታላቁ ሰማዕት ማር ቴዎድሮስ ሊቀ ሠራዊት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። †††
††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††
††† ✝በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም✝ †††
††† ለስም አጠራሯ ክብር ይሁንና እመ ብርሃን ድንግል ማርያም በዚህች ቀን ወደ ቤተ መቅደስ ገብታለች:: በዓሉ ከሰላሳ ሦስቱ የእመቤታችን በዓላት እንደ አንዱ አይቆጠርም:: ምክንያቱም ቅዱሳን ሊቃውንት በዓታ ከበዓታ ጋር ይስማማል ብለው የታኅሣሥ ሦስትን በዓል ከሰላሳ ሦስቱ ደምረውታል::
እመቤታችን ወደ ቤተ መቅደስ የገባችው ሁለት ጊዜ ሲሆን:-
1.ዛሬ የምናከብረውና በተወለደች በሰማንያ ቀኗ የገባችበት ነው:: (ከግንቦት 1 ጀምረን እናስላው: 80 ቀን ይመጣል::)
ኦሪት እንዳዘዘው ቅዱሳን ኢያቄምና ሐና ንጽሕት ሕፃን ድንግል ማርያምን ታቅፈው: የርግብ ልጆች (ግልገሎች): ዋኖስም ይዘው ወደ ቤተ መቅደስ ሒደዋል::
ካህናቱ ዘካርያስና ስምዖን ወጥተው በደስታ ተቀብለዋቸዋል:: እመቤታችን ለወላጆቿ ማኅጸን የከፈተች በኩር ናትና በእግዚአብሔር ፊት አቅርበዋታል::
2.ከሦስት ዓመታት በኋላ እንደ ስዕለታቸው ወደ ቤተ መቅደስ ወስደው ለእግዚአብሔር ሰጥተዋት ተመልሰዋል::
እግዚአብሔር ዛሬ ያልቃል: ነገ ይደቃል የማይባለውን የድንግል እናቱን ፍቅር አብዝቶ ያድለን:: በረከቷም በእኛ ላይ ጸንቶ ይኑር::
†††✝ ቅዱስ ቴዎድሮስ ሰማዕት✝ †††
††† በቤተ ክርስቲያን የሰማዕታት አለቅነት ከተሰጣቸው ሰማዕታት አንዱ የሆነው ማር ቴዎድሮስ የተወለደው በምድረ አንጾኪያ (ሶርያ) በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው:: አባቱ ዮሐንስ በትውልድ ግብጻዊ የሆነ ክርስቲያን ነው:: እናቱ ግን አስቸጋሪና ጣዖት አምላኪ ሶርያዊት ነበረች::
ባልና ሚስት አብረው ሲኖሩ ሚስት ባሏ ክርስቲያን መሆኑን አታውቅም ነበር:: ቴዎድሮስ (የእግዚአብሔር ስጦታ ማለት ነው) በተወለደ ጊዜ ግን ጠብ ተነሳ:: እሱ ክርስትና ለማስነሳት: ሚስት ደግሞ ወደ ጣዖት ቤት ለመውሰድ ተጋጩ:: ሚስት ወገኖቿ ባለስልጣኖች ናቸውና ልጁን ቀምታ ባሏን ዮሐንስን ወደ ግብጽ አሳደደችው::
ዮሐንስ በስደት ባለበት ሃገር ስለ ልጁ ፈጽሞ ይጸልይ: ያለቅስም ገባ:: እግዚአብሔር ደግሞ ልመናውን ሰማ:: ማር ቴዎድሮስ ወጣት በሆነ ጊዜ ማንም ሳይጠራው ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔዶ ተማረ: ተጠመቀ:: ዕለት ዕለትም ጾምና ጸሎትን ከምጽዋት ጋር ያበዛ: ድንግልናውን ለመጠበቅ ይተጋ ነበር::
በዛው ልክ ደግሞ ገና በሃያ ዓመቱ በጉልበቱ ኃያል: በውበቱም ደመ ግቡ: በጠባዩም ገራገር ነበርና ተወዳጅ ነበር:: ነገሥታቱም የአንጾኪያ የጦር ሠራዊት አለቃ አድርገው ሾሙት:: እነሆ እስከ ዛሬ "የሠራዊት አለቃ" ተብሎ ይጠራል::
ማር ቴዎድሮስ በተሳተፈባቸው ጦርነቶች ሁሉ ተሸንፎ አያውቅም:: ይልቁኑ የነገሥታቱን (የጠላት) ልጆች በመማረክ ነው የሚታወቀው:: እንዲያውም አንድ ጊዜ ከአሕዛብ ጋር በተደረገ ጦርነት ብቻውን አሸንፏቸዋል::
የፋርስ ሰዎች ሊዋጉ ሲመጡ መልአክ ከሰማይ ወርዶ ሰይፍ ሰጠው:: ፋርሶችን "በከንቱ ከምትጠፉ ወደ ሃገራችሁ ተመለሱ" አላቸው:: እነርሱ ግን ተሳለቁበት:: ከፈረሱ ወርዶ ወደ ምስራቅ ዙሮ ጸልዮ በመስቀል አማተበ:: በመካከላቸው ገብቶም በመልአኩ ሰይፍ ለወሬ ነጋሪ ሳያስቀር አጠፋቸው::
አንድ ቀን ወደ አንድ ከተማ ቢገባ ዘንዶ ሲመለክ አገኘ:: ይባስ ብሎ የአንዲት ክርስቲያን ልጆችን ለመስዋዕትነት ሲያቀርቧቸው ተመለከተ:: በስመ ሥላሴ አማትቦ: በፈረሱ ላይም ተቀምጦ ዘንዶውን በጦር ገደለው:: የዘንዶውም ርዝመት ሃያ አራት ክንድ ነበር::
ከነገር ሁሉ በኋላ ቅዱስ ቴዎድሮስ ስለ አባቱ ወሬ ሰምቶ: ካለበት ሥፍራ አፈላልጎ አግኝቶ ደስ አሰኘው:: እስኪያርፍ አብሮት ቆይቶ: ቀብሮት ወደ አንጾኪያ ሲመለስ ግን የሚያሳዝን ነገር ጠበቀው::
ክርስቶስ ተክዶ:
ጣዖት ቁሞ:
አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለው:
የክርስቲያኖች ደም ፈሶ:
ከተማዋ በግፍ ተሞልታ ተመለከተ:: እርሱም በዚያች ሰዓት መወሰን ነበረበትና አደረገው:: የሁሉ ሠራዊት አለቃ ቢሆንም የክብር ልብሱን አውልቆ: ባጭር ታጥቆ በንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ ፊት ቆመ::
††† ማር ቴዎድሮስ በአደባባይ እንዲህ ተናገረ:- "አንሰ አመልኮ ለክርስቶስ ንጉሠ ስብሐት በኩሉ ልብየ: ወእሠውዕ ሎቱ - እኔስ የክብር ባለቤት ክርስቶስን በፍጹም ልቤ አመልከዋለሁ: ለእርሱም ብቻ እሠዋለሁ::" ንጉሡ በቁጣ መሬት ላይ ጥለው እንዲደበድቡት አዘዘ:: ወታደሮቹ ደሙ እስኪንጠፈጠፍ ገረፉት::
በብዙ መክፈልተ ኩነኔ አሰቃይተው በእሳት አቃጠሉት:: እርሱ ግን በጸሎቱ እሳቱን ውኃ አደረገው:: ወታደሮቹ እርሱን በብዙ አሰቃዩ:: እርሱ ግን በእግዚአብሔር ኃይል ጸና: ታገሠ::
በመጨረሻም ጌታችን በግርማ ወርዶ "ወዳጄ ቴዎድሮስ ስምህን የጠራ: መታሠቢያህን ያደረገ: ገድልህን (ዜናህን) የጻፈ: ያጻፈ: ያነበበ: ገዝቶ በቤቱ ውስጥ ያኖረውን ሁሉ እምርልሃለሁ" አለው::
በስሙም ረድኤት እንደሚደረግ ነግሮት ዐረገ:: ወታደሮቹም በዚህ ቀን አንገቱን ሰይፈው የክብር አክሊልን ተቀብሏል:: እጅግ ብዙ ሺህ ሰዎችም አብረውት ተሰይፈዋል::
††† ቸሩ ፈጣሪ ከሰማዕቱ በረከት ይክፈለን::
††† ሐምሌ 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም (በሰማንያ ዕለት)
2.ቅዱስ ወክቡር ማር ቴዎድሮስ ሰማዕት (የሠራዊት አለቃ)
3.ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዘእስክንድርያ
4.አራት መቶ አራት ሰማዕታት (የቅዱስ ቂርቆስ ማኅበር)
5.ቅድስት አውስያ (የማር ቴዎድሮስ እናት - በልጇ ምክንያት ያመነች እናት ናት)
††† ወርኀዊ በዓላት
1..ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር
2.ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ
3.ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮጵያ)
4.አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና
5.ቅድስት ሳድዥ የዋሒት
††† "እግዚአብሔር ለኛ የሰማዕትነትን ሥራ ይሰጠን ዘንድ ቅዱሳን ስለሚሆኑ ሰማዕታት እንማልዳለን::" †††
(ሥርዓተ ቅዳሴ ቁ. ፸፫)
††† "በጐንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማን ነው? ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኳ መከራን ብትቀበሉ ብጹዓን ናችሁ:: ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ:: አትናወጡም:: ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስን በልባችሁ ቀድሱት:: በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ:: ነገር ግን በየውሃነትና በፍርሃት ይሁን::" †††
(፩ጴጥ. ፫፥፲፫-፲፮)
††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† | 555 |
| 15 | Sin texto... | 621 |
| 16 | ✝ቅዱስ ገብርኤል ሆይ የተሰጠህ ክብር ታላቅ ነው✝
Size:- 29.3MB
Length:-1:24:12
በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
http://t.me/abagebrekidan
http://t.me/abagebrekidan | 858 |
| 17 | *➕ የ3 ዓመት ሕፃን የእናቱ የእምነት ጉድለት* በጸሎት አራቀላት በእጁም ይዟት ወደ ሕይወት መራት እናቱም “ልጄ ሆይ አንተ ከእንግዲህ አባቴ ነህ እኔም ልጅህ ነኝ” “ያች የተወለድክባት ዕለት ቀኗ የተባረከችና የተቀደሰች ናት” አለችው።
➕ ከፍላቱ የተነሣ እንደነጎድጎድ የሚያስፈራ የነበረው እንደ ማለዳ ውርጭ ቀዘቀዘላቸው ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና።
➕ በልደተ ሥጋ ታናሽ በመንፈስ ጐልማሳ፤ እንደ ዕጣን ንጹሕ እንደ ወይንም አስደሳች ለኾነ ለቂርቆስ ሰላምታ ይገባል ( አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም )
➕ እግዚአብሔር አምላካችን የሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ የቅድስት ኢየሉጣን የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል በረከታቸውንና ረድኤታቸውን ያድለን አሜን።
✍️ አምኃ ሥላሴ / መኩሪያ ተስፋዬ | 1 005 |
| 18 | ©ገብርኤል መልአክ
ጥራዝ 3.ቁ 115
ገብርኤል መልአክ ወረደ ኀበ ቂርቆስ ወእሙ ኢየሉጣ/፪/ ቅድስት
ዘአጥፍኦ ለነበልባለ እሳት ዘአድኀኖሙ ለሰማዕት/፪/
ትርጉም፡- ሰማዕታትን ያዳናቸውና የእሳቱን ነበልባል ያጠፋው ገብርኤል ወደ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ ወረደ። | 892 |
| 19 | " ሐምሌ 19 ይህች ቀን ቅዱስ ገብርኤል ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣን ከእሳት ያወጣበት ቀን ነው።በረከታቸው ይደርብን እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ ደስታን አብሳሪው ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል እኛንም እንደ ረመጥ አሳት ከሚያቃጥል ኃጢዓት ያውጣን፡፡🙏 | 1 080 |
| 20 | 🌷መልክአ ቅዱስ ገብርኤል📗
ደስታን አብሳሪው ቅዱስ ገብርኤል ሆይ ሰላም እልሃለሁ/፫/
ቅዱስ ገብርኤል በዕለተ ቀኑ ከክፉ ነገር ሁሉ ይሰውረን ለሀገራችን ፅኑ ሰላምን ያምጣልን አሜን🙏 | 1 021 |
