"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን /አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ። 📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜንለምት @fentanesh21_23 🗯ፈንታነሽ / የእመ ብርሃን ልጅ🤗
Mostrar más📈 Análisis del canal de Telegram "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
El canal "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 (@orthodoxtewahdoc) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 25 425 suscriptores, ocupando la posición 2 905 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 1 316 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 25 425 suscriptores.
Según los últimos datos del 28 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 1, y en las últimas 24 horas de 8, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 3.70%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 2.61% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 940 visualizaciones. En el primer día suele acumular 663 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 13.
📝 Descripción y política de contenido
El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን
/አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc
ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ።
📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜንለምት
@fentanesh21_23
🗯ፈንታነሽ / የእመ ብርሃን ...”
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 29 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.
Carga de datos en curso...
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 29 julio | +40 | |||
| 28 julio | +28 | |||
| 27 julio | +28 | |||
| 26 julio | 0 | |||
| 25 julio | +24 | |||
| 24 julio | 0 | |||
| 23 julio | +23 | |||
| 22 julio | +27 | |||
| 21 julio | +14 | |||
| 20 julio | +29 | |||
| 19 julio | +1 | |||
| 18 julio | 0 | |||
| 17 julio | +1 | |||
| 16 julio | +22 | |||
| 15 julio | +24 | |||
| 14 julio | +15 | |||
| 13 julio | +23 | |||
| 12 julio | 0 | |||
| 11 julio | 0 | |||
| 10 julio | 0 | |||
| 09 julio | +13 | |||
| 08 julio | +19 | |||
| 07 julio | +33 | |||
| 06 julio | +36 | |||
| 05 julio | +3 | |||
| 04 julio | 0 | |||
| 03 julio | 0 | |||
| 02 julio | +49 | |||
| 01 julio | +15 |
| 2 | "አጠንክረኝ" በሉት!
⩩⩩⩩⩩_⨳⨳⨳⨳⨳_⋕⋕⋕⋕
አንዳንዴ እንዲሁ ልባችሁ ትደክማለች፣ የመታፈን የመታወክ ስሜት ይሰማታል፣ የምትሰሩት ጥቂት ነው ድካማችሁ ግን እጅግ ብዙ ነው፣ ትልቅ ብሩህ ተስፋ ይታያችኋል ዛሬ ግን በጨለማ ውስጥ ትመላለሳላችሁ፣ አቅም ጉልበት እንዳላችሁ ታውቃላችሁ ነገር ግን እርሱም አሁን ከድቷችኋል፣ ሰው ሁሉ የሚፈልጋችሁ የሚወዳችሁ ይመስላችኋል ነገር ግን ሰው የሚፈልጋችሁ የምትጠቅሙት ከሆነ ብቻ እንደሆነ እያያችሁት ነው። ከዚህ ምድራዊ እውነት ጋር አትታገሉ። ይሔ ሁኔታ የሰው ልጅ ተፈጥሮ ነውና አትደናገጡ አትጨነቁ እዲሁ አምናችሁ ተቀበሉት። ለዚህ ችግር መፍትሔው ሌላ ልፋት፣ ሌላ ድካም፣ ሌላ ስራ ወይም ሌላ ሰው አይደለም። ለዚህ ሁሉ መፍትሔው የልብ እረፍት ነው። ልባችሁ ታርፍ ዘንድ ፍቀዱ፣ ልባችሁ አባቷን ታገኝ ዘንድ ፍቀዱ፣ አምላኳ ይፈውሳት ዘንድ በሩን ክፍቱላት። ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር ክፍሉ እንዲህ ይላል፦ "ከሀዘን የተነሳ ሰውነቴ አንቀላፋች በቃልህ አጠንክረኝ።" እናንተም እንዲህ በሉ "አጠንክረኝ፣ አበርታኝ፣ ደግፈኝ፣ ፈውሰኝ።" ምድራዊ ሩጫ ከዓለም ድካም አያሳርፋችሁም፣ ስለቁስና ገንዘብ መጨነቅ ሀብትና ንብረት አይጨምርላችሁም፣ ሰውን ለማስደሰት መኳተን የሰው ፍቅር አይሰጣችሁም። ምድር የራሷ ያልተፃፈ ህግ አላትና ህጓን በሙግትና በክርክር ለማስቀየር አትሞክሩ።
አዎ! "አጠንክረኝ" በሉት! ሰው ሆናችሁ አለመድከም፣ ሰው ሆናችሁ አለመዛል አትችሉምና በእያንዳንዱ የህይወት ጉዟችሁ አጠንክረኝ በሉት፣ እኔ ጉልበት የለኝምና አንተ ጉልበት ሁነኝ፣ አንተ አበርታኝ፣ አንተ አሻግረኝ በሉት። ብዙዎች በራሳቸው ሃይልና ጉልበት ይመካሉ፣ ብዙዎች በራሳቸው ንብረትና ሀብት፣ በዘመድ አዝማድ ይመካሉ ነገር ግን እነዛ የተመኩባቸው አንዳቸው እንኳን ዋስ ጠበቃ፣ አዳኝ ሆነዋቸው አያውቁም። ብልህና በሳል፣ ጠቢብና አስተዋይ የሆኑ ሰዎች ብቻ የሚያውቁት አንድ የተለየ እውነት አለ። እርሱም በምድርም በሰማይም፣ በየብስም በውሃ ውስጥም ዋስ ጠበቃቸው፣ ጠባቂያቸው እውነተኛ ወዳጃቸው አምላካቸው እንደሆነ ያውቃሉ። ይህንን ማወቅ የተለየ ተሰጥዖ ወይም የተለየ ተነሳሽነት አያስፈልገውም ነገር ግን አንድ ነገር ያስፈልገዋል፦ ፈሪሃ እግዚአብሔር ያስፈልገዋል። በመውደድ አምላክን መፍራት፣ በማፍቀር፣ ስራዎቹን በማድነቅ፣ ማዳኑን በማየት፣ ቸርነት ርህራሔውን በማስተዋል አምላክን መፍራት ያስፈልጋል። አንዳንዶች እርሱ ድከሙ፣ እርሱ ጣሩ፣ እርሱ ተሰቃዩ ያላቸው ይመስል ሌትከቀን ምሬታቸውን ወደርሱ ይልካሉ። ነገር ግን ምሬትን ልኮ ደስታን ማግኘት፣ ችግርን ተንትኖ ሰላምን ማትረፍ አይቻልም። ወደ አምላካችሁ ምን አየላካችሁ እንደሆነ ራሳችሁን ጠይቁ። እርሱ ልብና ኩላሊትን የሚመረምር አምላክ ነውና ለያንዳንዱ ሃሳብና ንግግራቹ ፍፁም ተጠንቀቁ። አንዳች የምሬት ስህተት እንኳን እልፍ ፈተናን፣ እልፍ ድካምን ልታመጣ እንደምትችል አስተውሉ።
አዎ! ጀግናዬ..! ልብህ እንዳትፈተን አትታገል ይልቅ በፈተናም ሆነ በደስታ ውስጥ በአምላኳ ተማምና እንድታርፍ አግዛት። አሁን አሁን ብዙ ሰው ብቻውን የሚሰቃይ፣ ብቻውን ተለይቶ የተጎዳ፣ እንዲሁ ብቻውን ሰላም ያጣ ይመስለዋል። ነገር ግን እውነቱ ሌላ ነው በዚህ ዘመን የሚኖር በየትኛውም የዓለም ክፍል የሚገኝ ሰው ሁሉ እረፍት የለም፣ ውስጡ ሰላም ጎድሎታል፣ መረጋጋት ተስኖታል፣ ድካሙ ፍሬ አጥቶበታል። የሚያውቅ ያውቀዋል ግማሹ በዝናው ውስጥ ሊደበቅ ይሞክራል፣ ግማሹ በሰው ተከቦ ሊያመልጠው ይሻል፣ ሌላው ደግሞ ያለእረፍት በመስራት የሚያመጣው ገንዘብ ነፃነትን እንዲገዛለት ይፈልጋል። ነገር ግን ሁሉም የተሳሳቱት አንድ ነገር አለ። ነፃ ህይወት በዚህ ምድር ላይ የለም፣ በድብብቆሽ የሚመጣ አንዳች ደስታና ሰላም የለም። መረጋጋትን ከፈለክ መሸሹን አቁመህ ስሜትን ፊትለፊት ተጋፈጠው፣ የእውነት ከጭንቀትና ከድብርት መውጣት ከፈለክ በፍፁም አትቸኩል፣ ነፍስህን አታፍናት። ዓለም ከምትሰጥህ በላይ የሰማይ አባትህ የሚሰጥህን በረከት ለመቀበል ዝገጁ ሁን፣ ሺህ ዓመት ብትሮጥ፣ ለዘመናት ጠንክረህ ብትሰራ፣ ለዓመታት ደከመኝ ሳትል ብትለፋ የማትቀድመው ፈጣሪ እንዳለ አስተውል። በእያንዳንዱ እርምጃህ እርሱን አስቀድም፣ የውስጥ ሰላምና እረፍትን ብቻ ሳይሆን እርሱን በማመን ብቻ የምታገኘውን ዘላለማዊ በረከት አጣጥም።
Amari La | 446 |
| 3 | ብዙዎች "ወላጆች ያልተሳኩ ህልሞቻቸውን በልጆቻቸው በኩል ለመኖር ይሞክራሉ"። ብዙ ወላጆች እውን ማድረግ ያልቻሏቸው ህልሞች፣ መጀመር ያልቻሏቸው የሙያ መስኮች ወይም ሙሉ በሙሉ ያልተጠቀሙባቸው ተሰጥኦዎች አሏቸው። ብዙውን ጊዜ እነዚህ ያልተሳኩ ምኞቶች በዝምታ ወደ ልጆቻቸው ያስተላልፉታል፤ ይህም እንደ ምክር ሳይሆን እንደ ግዴታ ወይም የሚጠበቅ ነገር ሆኖ ነው። ልጁ፣ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ፣ የእሱ ወይም የእሷ ሚና ወላጆቹ ራሳቸው መኖር ያልቻሉትን ህይወት መኖር እንደሆነ እንዲያምን ይደረጋል። ይህ ጫና ፍቅርን ከባለቤትነት ስሜት ጋር ያምታታል። የልጁን ልዩ ማንነት ከማጎልበት ይልቅ፣ ልጁን የሌላ ሰው ያልተጠናቀቀ ታሪክ መፈጸሚያ ያደርገዋል። ካሊል ጂብራን በ"(The Prophet) በተሰኘው መጽሐፉ ላይ እንደጻፈው፡- "ልጆቻችሁ የእናንተ ልጆች አይደሉም። እነሱ የራሳችሁ የህይወት ምኞት ውጤቶች ናቸው። በእናንተ በኩል ወደዚህ ዓለም ይመጣሉ እንጂ ከእናንተ አይመነጩም፤ ከእናንተ ጋር ቢሆኑም የእናንተ ንብረት አይደሉም።" ወላጆች ልጃቸው ራሳቸው የተዉትን መንገድ (ለምሳሌ ዶክተር፣ አርቲስት ወይም ስራ ፈጣሪ መሆንን) እንዲከተል ሲገፋፉ፣ ልጁ ማንነቱ በተከፋፈለ ወይም ግልጽ ባልሆነ ሁኔታ ያድጋል። የራሱ ፍላጎቶች እና የማወቅ ጉጉቶች ብዙውን ጊዜ በኃላፊነት ጫና ስር ይጨፈለቃሉ። ውጤቱም እርካታ ሳይሆን መራራነት፣ እንዲሁም አንዳንድ ጊዜ ጥልቅ የሆነ የህልውና ቀውስ ነው። ካርል ጁንግ እንዲህ ብሏል፡- "ለአንድ ልጅ ትልቁ ሸክም የወላጆቹ ያልተሟላ ህይወት ነው።" ጤናማ ፍቅር ቀጣይነትን አይጠይቅም፤ ይልቁንም ነገሮችን የማግኘት እና የመለየት (discovery) ሂደትን ያበረታታል። ይህ ማለት ልጆች እኛ እንድንሆን የፈለግነው ሳይሆን፣ እነሱ ራሳቸው የሆኑትን ሰው እንዲሆኑ መምራት ማለት ነው። ወላጆች ማነሳሳት፣ ማስተማር እና መደገፍ ይችላሉ፤ ነገር ግን የመጨረሻው ምርጫ የልጁ መሆን አለበት። በግዴታ የተጫነ ህልም እንደ እስራት ሰንሰለት ሲሆን፣ በራስ ጥረት የተገኘ ህልም ግን ወደ እውነተኛ እርካታ የሚወስድ መንገድ ነው።
እንደ ወላጅ፣ ልጆች እናንተ አስባችሁት የነበረውን መንገድ ብቻ ሳይሆን የራሱን መንገድ እንዲከተል ለማድረግ ምን ታደርጋላችሁ? እንዲሁም እንደ ልጅ፣ የወላጆችህን ያልተሳኩ ህልሞች ጫና ተሰምቷችሁ ያውቃል? ያንን ጫና እንዴት አስወገዳችሁት?
Amari L | 527 |
| 4 | ☞ ሐምሌ 23 የጌታችንን ጎን በጦር የወጋው በኃላምበጌታችን አምኖ ወንጌልን ሰብኮ በሰማዕትነት ያረፈው፡፡ የሰማዕቱ ለንጊኖስ ሰማዕትነት የተቀበለበት ዓመታዊመታሰቢያው ነው፡፡ | 510 |
| 5 | "ቅዱስ ጊዮርጊስ ማለት ኮከብ"ብርህ ሐረገወይን ፀሐይ "ማለት ነው ሊቀ ሰማእቱ ቅዱስ ጊዮርግስ በጥር 20ቀን በ 277ዓ/ም ተወለደ። ሃገሩ ፍልስጤም ሲሆን ልዩ ስሟ ልዳ ይበላል አባቱ ዞሮንቶስ አንስጣስዮስ ይባላል።ከልዳ መኳንንት ተሽሞ ይኖር ነበር፥እናቱ ቴዎብስታ (አቅሌስያ ትባላለሽ።ማርታና እስያ እህቶች ነበሩት።
🌿❤️ 10አመት ሲሞላው አባቱ ስለ ሞተ ሌላ ደግ ክርስትያናዊ መስፍን ከቤቱ አሳደገው።በጦር ሃይልም አሰለጠነው።20ዓመት ሲሞላን 15 ዓመት ልጅ ሊያጋቡት ሲሉ እግዚአብሔር የመስፍኑን ነፍስ ወሰደ ቅዱስ ጊዮርግስ ወደ ቤሩት ሄደ።
በቤሩት አደራጎን ያመልኩና ሴት ልጃቸውን ይገብሩለት ነበርና በኃይለ መስቀል ድል ነስቶት ህዝቡን ወደ አምልኮት እግዚአብሔር አስገብቷቸዋል።
🌿❤️ ወደፍርስ ቢመለ ዲድያኖስ ሰባ ነገስታት ሰብስቦ ጣኦታት ሰብስቦ ሲሰግድ ቢያገኛቸው ለሃይማኖት ቀናዒ ነውና ከቤተ መንግስቱ ገብቶ እኔ ክርስትያን ነኝ በእየሱስ ክርስቶስ አምናለሁ አለው።እርሱንም መንነቱ ከተረዳ በኃላ አንተ እማ የእኛ ነህ በ10አህጉር ላይ እሾምሃለሁ የእኔን አምላክ አጵሎንን አምልክ አለው።ቅዱስ ጊዮርግስም ሽሞት ሽልማትክ ለአንተ ይሁን እኔ አምላኬ እየሱስ ክርስቶስ አልክድም አለ"።በዚ ግዜ እጅግ ተናዶ መከራን አጸናበት እርሱግን"ይህን ከሀዲ እስካስፈራው ድረስ ነፍሴን አትውሰድ"በማለት እግዚአብሔር ለመነና እንደ ጸሎቱ ተደረገለት በእምነቱ ጽናት ለሰው ሊሸከም የማይቻለው መከራ የተቀበለ ቅዱስ አባት ነው።
ወስብሓት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክብር አሜን
🌹💚❤️🌿 🌹💚❤️🌿 | 458 |
| 6 | Sin texto... | 367 |
| 7 | ቅዱስ ዳዊት ታላቅና ገናና የከበረ ንጉሥ ከመሆኑ የተነሣ መንግሥቱ የመሢሕ መንግሥት ምሳሌ ሆኗል፤ መሢሑም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዳዊት ስም ብዙ ጊዜ በመጽሐፍ ቅዱስ ተጠቅሶ ይገኛል። (ኢሳ 9፡7፣ ኤር 23፡5-6፣ ኤር 33፡14-17፣ ሕዝ 34፡23፣ ሆሴዕ 3፡5) በሐዲስ ኪዳንም ወንጌላዊያኑ ጌታችንን ‹‹የዳዊት ልጅ›› በማለት ነው መጀመሪያ ነገረ ልደቱን ማውሳት የጀመሩት፡፡ ማቴ 1፡1፡፡ ራሱ ጌታችንም ‹‹እኔ የእሴይ ሥርና የዳዊት ዘር ነኝ›› ብሏል፡፡ ራእ 22፡16፡፡
ቅዱስ ዳዊት 7 ሀብታት የተሰጡት ጻድቅ አባት ነው፡፡ እነዚህም የተሰጡት ሀብታት፡- ሀብተ ክህነት፣ ሀብተ መንግሥት፣ ሀብተ መዊዕ (የማሸነፍ ሀብት)፣ ሀብተ ትንቢት፣ ሀብተ ኃይል፣ ሀብተ በገና (ዝማሬ) እና ሀብተ ፈውስ ናቸው። ቅዱስ ዳዊት 24 ሰዓት ሙሉ የእግዚአብሔር ምስጋና እንዳይቋረጥ መዘምራንን መድቦ እንዲያገለግሉ ያደርግ ነበር፡፡ ራሱም 10 አውታር ባለው በገና ሌት ተቀን በፍጹም ተመስጦ ያመሰግን ነበር፡፡ በመዝሙሩም አጋንንትን ያቃጥል ነበር፡፡ መዝሙረ ዳዊት በውስጡ የያዘው ሚሥጢር እጅግ ጥልቅ ነው፡፡ አባቶቻችን ዛሬም በዱር በጫካ ሆነው መዝሙረ ዳዊትን አብዝተው ይደግማሉ፡፡ እንኳንስ የሰው ልጅ ይቅርና ‹‹መዝሙረ ዳዊትን›› ሰማያውያን ቅዱሳን መላእክትም እግዚአብሔርን ለማመስገኛነት ተጠቅመውበታል፡፡ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እድሜ ዘመኑን እግዚአብሔርን በማገልገልና በመፍራት ኖሮ በታኅሣሥ 23 ቀን በሰላም ዐርፎ በኢየሩሳሌም ተቀብሯል፡፡ የቅዱስ ዳዊት ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
https://t.me/Orthodoxtewahdoc ቤተሰብ ይሁ | 327 |
| 8 | እግዚአብሔርም ለነቢዩ ናታን ተገለጸለት። ናታን ከል ለብሶ ከል ጠምጥሞ ጦር ይዞ ሄደ። ዳዊት “ነቢየ እግዚአብሔር አመጣጥህ በደኅና ነውን?” አለው። “የምነግርህ አለኝ” አለው። “መቶ በጎች ያሉት ሰው ነበር። ከአንዲት በግ ሌላ ምንም ምን የሌለው ጎረቤት ነበረው። መንገድ ሲሄድ አደራ ሰጥቶት ሄደ፡፡ ያ ሰው እንግዳ ቢመጣበት መቶ በጎቹን አስቀምጦ የእርሱን አንዲት በግ አርዶ እንግዳውን ሸኘበት። እርሱንም ለሰው እንዳይነግርብኝ ብሎ ገደለው። በዚህ እግዚአብሔር አዝኗል” አለው። ዳዊትም ይህን ጊዜ “ይህን የሚያደርግ በከተማዬ ካለ ሞት ይገባዋል” አለ። ነቢዩም ወዲያው “ንጉሥ ሆይ! ይህን ሁሉ ያደረግህ አንተ ነህ፣ በራስህ ፈረድህ ባለጸጋ የተባልህ አንተ ደኃ የተባለ ኦርዮን ነው። መቶ በጎች የተባሉ አሥሩ ዕቁባቶችህ ናቸው። አንዲት በግ የተባለች ቤርሳቤህ ናት። እንግዳ የተባለ ፈቃደ ሥጋ ነው። ፈቃደ ሥጋህ ቢነሳብህ 10ሩ ዕቁባቶችህን አስቀምጠህ ከቤርሳቤህ ደረስህ። ኦርዮንንም አስገደልከው። በዚህ እግዚአብሔር አዝኗል” አለው። ይህንንም ሲሰማ ዳዊት ልዋል ልደር ሳይል ዕለቱን ጉድጓድ አስምሶ ማቅ ለብሶ ሱባኤ ይዞ ሌት ተቀን ተንስቅስቆ አለቀሰ፡፡ እግዚአብሔርም ጥንቱን መርጦታልና ጸሎቱን ሰማው። ነቢዩ ናታን ዳግመኛ መጥቶ “በነፍስህ ምሬሀለሁ ብሎሀል። በሥጋህ ግን ኃጢአት ያለፍዳ አይነጻምና ለሦስት ወር ልጅህ መንግሥትህን ይነጥቅሀል፤ ዕቁባቶችን ይቀማሀል” አለው። ዳዊትም “ይህ እንዲሆን በምን ዐውቃለሁ?” አለ። “የሚወለደው ሕፃን ይሞታል፣ እርሷን ግን አግባት ወንድ ልጅ ትወልድልሀለች ስሙን ሰሎሞን ትለዋለህ” አለው። ቀን ከሌት አብዝቶ ያለቅስ ነበርና ከዕንባው ብዛት የተነሣ መሬቱ እርሶ ሠርዶ አብቅሎ ሰውነቱን ተብትቦ ይዞት ነበር። ብላቴኖቹ ቆርጠው አወጡት።
ከዚህም በኋላ ሕፃኑ ተወልዶ ታመመ። “እኔን በነፍሴ እንደማረኝ ሕፃኑንም በሥጋው ይማረው” ብሎ ማቅ ለብሶ አመድ ነስንሶ ያለቅስ ጀመር። ሕፃኑ ሞተ፤ ከወደቀበት ተነስቶ ተጣጥቦ ልብሰ መንግሥቱን ለብሶ ማዕድ ቀረበ። ከምሳ መልስ “ታመመ ስንልህ ማዘንህ ሞተ ስንልህ እንዲህ ማድረግህ ስለምንድር ነው?” አሉት። “ውኃ ከፈሰሰ ይታፈሳልን? እንዲሁ ወደርሱ እንሄዳለን እንጂ እርሱ ወደኛ አይመጣም” ብሏቸዋል። ጌታ የተናገረው አይቀርምና ቅዱስ ዳዊት ፍዳን ሊቀበል ሰይጣን የበኵር ልጁ አምኖንን በእኅቱ በትዕማር ፍቅር እንዲያድርበት አደረገ። ኢዮናዳብ የሚባል የአጎቱ ልጅ ሰውነቱ ከስቶ ፊቱ ገርጥቶ ቢያየው “አንተ የንጉሥ ልጅ ሆነህ ምን ያከሳሀል?” አለው። “ፈርቼ እንጂ እኅቴ ትዕማርን ወድጃታለሁ” አለው። “ታመምሁ ብለህ ተኛና አባትህ ሊጠይቅህ መጥቶ ልጄ ብላ ሲልህ በትዕማር እጅ ቢሆን ኖሮ ሁለት ሦስት እንጎቻ በበላሁ ነበር በለው ያዝልሀል” አለው። እርሱም እንደመከረው አደረገ፡፡ ዳዊትም ትዕማርን አስጠርቶ እንድታሰናዳለት አዘዛት። “እኅቴ አንቺን ብዬ እንጂ እህል የሚያቀርብልኝማ መቼ አጣሁ” ብሎ ያዛት። እርሷም “ወንድሜ ይህን አታድርገው እኔን የተናቀች የተጠላች ታደርገኛለህ፣ አንተም ከሰነፎች እንደ አንዱ ትቆጠራለህ” አለቸው። አምኖን ግን በግድ አስነወራት። ወዲያውም ፊት ከወደዳት መውደድ ይልቅ ኋላ የጠላት መጥላት በለጠና ‹‹ውጪልኝ›› አላት። “ከቀደመው የአሁኑ ክፋትህ ይከፋል ተወኝ” አለችው። ብላቴናውን ጠርቶ አስወጥቶ እንዲዘጋባት አደረገ። እርሷም የለበሰችውን ባለህብር ልብስ ቀዳ አመድ ነስንሳ እያለቀሰች ስትሄድ ወንድሟ አቤሴሎም አገኛት። ያስነወራት አምኖን መሆኑን ዐውቆ “ወንድምሽ ነውና አትግለጪበት” ብሎ አጽናንቶ ዳዊት በከተማ ያሠራው ቤት ነበርና ከዚያ አስቀመጣት።
ከሁለት ዓመት በኋላ አቤሴሎም ድግስ ደግሶ ዳዊትን ጠራው። “አስቀድመህ ብትነግረኝ መልካም ነበረ አሁን ግን እኔ ስመጣ መኳንንቱ፣ መሳፍንቱ ወይዛዝርቱ ስለሚከተሉኝ ይበዛብሃል አይሆንም” አለው። “ያም ባይሆን ታላቅ ወንድሜ አምኖን ይገኝልኝ” አለ። እርሱም ‹‹ይሂድልህ›› አለው። ከዚህ በኋላ አምኖን በልቶ ሲጠግብ፤ ጠጥቶ ሲሰክር አቤሴሎም ብላቴኖቹን አዝዞ አስገደለውና እርሱ ወደናቱ ሀገር ጌድሶር ሸሸ። ዳዊት ለልጁ ለአምኖን አለቀሰለት። ከሁለት ዓመት በኋላ አምኖንን እየረሳ አቤሴሎምን እያስታወሰ ሄደ። ቢትወደዱ ኢዮአብ ይህን ዐውቆ አንዲት ቴቁሄያዊት ልኮ አስታረቀው። አቤሴሎም ከአባቱ ጋር ከታረቀ በኋላ በሠረገላ ሆኖ እስራኤልን “ምን ዳኛ አለና ይፈርድላችኋል? እኔማ ይህችን መንግሥት ጥቂት ጊዜ ባገኛት ቀን በፀሐይ ሌሊት በመብራት ፈርጄ ኢየሩሳሌምን አቀናት ነበር” ሲል ሰንብቶ ዳዊትን ለምኖ ሥርዓተ መንግሥት አስወጥቶ ሁለት መቶ መኳንንት ይዞ ‹‹አቤሴሎም በኬብሮን ነገሠ›› እያለ ነጋሪት አስጎሠመ። ዳዊት ይህን ሰምቶ “ኑ ከኢየሩሳሌም እንሽሽ” አለ። ኢዮአብና አቢሳ ግን ‹‹እንዋጋለን›› አሉት። ቅዱስ ዳዊትም ‹‹ጌታ ልጅህ መንግሥትህን ይነጥቅሀል፣ እዋጋለሁ አትበል ብሎኛል አይሆንም›› ብሎ ተራ ልብስ ለብሶ ተራ ጫማ ተጫምቶ ከከተማው ወጥቶ ሦስት ወራት በጫካ ሲያዝን ኖሯል። ከሦስት ወር በኋላ አቤሴሎም ሲዋጋ ሞተ። ዳዊት ወደ ቤተ መንግሥቱ ቢመለስ ዓሥሩ ዕቁባቶቹን ልጁ አርክሷቸው ተገኘ። እርሱም እስከ ፍጻሜ ዘመኑ ሳይደርስባቸው ቀርቷል።
ከዚህም በኋላ ቅዱስ ዳዊት ብዙ ጊዜ ቆይቶ “የባሕርይህን ፍሬ በዙፋንህ ላይ አኖራለሁ›› ያለው ቃል ተፈጽሞለት ልጁ ሰሎሞንን በዙፋኑ አስቀምጦ በነገሠ በ40 ዘመኑ በሰላም ዐርፏል። 1ኛ ነገ 2፡12-14፡፡
ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ነሐሴ 13 ቀን ተጸነሰ፣ በሚያዝያ 6 ቀን በይሁዳ በቤተልሔም ሀገር ተወልደ። 1ኛ ሳሙ 16፡10-11፡፡ እረኛና ብላቴና የነበረ ቢሆንም የፍልስጤማውያኑን ኃያል ሰው ጎልያድን በ12 ዓመቱ 5 ጠጠርን ከወንዝ ለቅሞ በወንጭፍ ወርውሮ ገድሏል፡፡ 1ኛ ሳሙ 12፡45-51፡፡ ንጉሥ ሳዖል በጌልቦአ ተራራ በራሱ እጅ ከሞተ በኋላ አስቀድሞ በይሁዳ 7 ዓመት በመላው እስራኤል 33 ዓመት ነግሡዋል፡፡ 2ኛ ሳሙ 2፡4፤ 5፡1-5፡፡ ‹‹እግዚአብሔር እንደ ልቡ የሆነ ሰው መርጦአል” (1ኛ ሳሙ 13፡14) ተብሎ በእግዚአብሔር የተመረጠና ነገረ ሥጋዌን፣ ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን፣ ዳግም ምጽዓትን፣ ነገረ ማርያምን፣ ክብረ ቅዱሳንን፣ በስፋትና በጥልቀት የተናገረ የብሉይ ኪዳን ‹‹ወንጌላዊ›› የተባለ ቅዱስ ነቢይ ነው። “ብዙ ውሾች ከብበውኛልና የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ እጆቼንና እግሮቼን ቸነከሩኝ። አጥንቶቼ ሁሉ ተቈጠሩ እነርሱም አዩኝ ተመለከቱኝም። ልብሶቼን ለራሳቸው ተከፋፈሉ፥ በቀሚሴም ላይ ዕጣ ተጣጣሉ…” እያለ የጌታችንን መከራ መስቀል በትንቢት ተናግሯል፡፡ መዝ 21 (22)፡ 16-18፡፡
“አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።”፣ “ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል። አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊት ይቃጠላል፥ በዙሪያውም ብዙ ዐውሎ አለ…” እያለ የጌታችንን ዕርገቱንና ዳግመኛ ለፍርድ የሚመጣ መሆኑን በግልጽ ተናግሯል፡፡ መዝ 46(47)፡4-5፣ መዝ 49(50)፡ 1-5፡፡ “የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች” እያለ የእመቤታችንን ክብር አይቶ በትንቢት ተናግሯል፡፡ መዝ 44(45)፡9፡፡ | 236 |
| 9 | 🌹#ነብዮ_ቅዱስ ዳዊት🌹
📌•••ወር በገባ በ23 የልብ አምላክ የነብዮ ንጉሠ እስራኤል ቅዱስ ዳዊት፡- ወርኃዊ መታሰብያው ነው #ዳዊት ማለት ‹‹ኅሩይ›› ማለት ነው። አንድም ‹‹ልበ አምላክ›› ማለት ነው። ሐዋ 13፡22፡፡ ትውልዱ ከነገደ ይሁዳ ነው። አባቱ እሴይ እናቱ ሁብሊ ይባላሉ። ሁብሊ መልከ መልካም ሴት ነበረች። ከጎረቤታቸው ያለ ጎልማሳ መልኳን እያየ በሐጸ ዝሙት ተነደፈ። እሴይ የእሷም ፈቃድ እንደሆነ አውቆ መንገድ እሄዳለሁ ብሎ ስንቁን ይዞ ወጣ። የሄደ መስሎ ከዚያው ውሎ ሲመሽ በልብሱ ተሸፋፍኖ ድምጹን ለውጦ ያንን ሰው መስሎ ገብቶ ከእርሷ ጋር አድሮ ጎህ ሳይቀድ ወጥቶ ሄደ። ዳዊት በዚህ ዕለት ተጸንሷል። “እነሆ፥ በዓመፃ ተፀነስሁ፥ እናቴም በኃጢአት ወለደችኝ” (መዝ 50፡5) ማለቱ ስለዚህ ነው። ቅዱሱም ተወልዶ ጉልበቱ ከጸና በኋላ የአባቱን በጎች ሲጠብቅ አድጓል።
ንጉሥ ሳኦል ከጌታ ፈቃድ በወጣ ጊዜ እግዚአብሔር ሳሙኤልን ቅብዐ መንግስሥት እንዲቀባው አደረገ። 1ኛ ሳሙ 16፡1-13፡፡ ከዚህ በኋላ በረድኤተ እግዚአብሔር ጎልያድን በአንድ ጠጠር ገደለ። ግዳይ ጥሎ ሲመለስ ሴቶች “ሳኦል ሺህ ገደለ ዳዊት እልፍ ገደለ” እያሉ እየዘፈኑ ተቀበሉት። ቅንዐት አድሮበት ነገር ግን አስቀድሞ ምሎለት ነበርና የመቶ ፍልስጤማውያንን ሸለፈት ተቀብሎ ልጁ ሜልኮልን ዳረለት። አንድ ቀን ሊገድሉት ሲማከሩ ሜልኮል ሰምታ ሽሽ አለችው። ሳዖልም ሶስት ሺህ ሠራዊት ይዞ ተከተለው፡፡ ከሠራዊቱ ተለይቶ ሰውነቱን ለመፈተሽ ዳዊት ካለበት ዋሻ ውስጥ ገባ። ጨለማ ነበርና ሰው መኖሩን አላወቀም። አቢሳ ዳዊትን ጠላትህን አሳልፎ ሰጥቶሀልና ልውደቅበት አለ። ተው ኦሪት ‹‹በእግዚአብሔር መሢሕ ላይ እጅህን አታንሳ›› ትላለችና አይሆንም አለው። እርሱ የልብሱን ዘርፍ በሰይፉ ቀዶ ያዘ። ሲወጣ ተከትሎ ወጥቶ “ንጉሥ ሆይ ዳዊት ቢያገኝህ አይምርህም የሚሉህን ለምን ትሰማለህ እነሆ ዛሬ አሳልፎ ሰጥቶኝ ነበር። ነገር ግን የልብስህን ዘርፍ ከመቅደዴ በቀር ምንም ምን እንዳላደረግሁህ አንተ ታውቃለህ” ብሎ ቅዳጁን አሳየው። ሳኦልም ድምጹን ከፍ አድርጎ በማልቀስ ‹‹ልጄ ዳዊት ሆይ! እኔ ክፉ በመለስሁልህ ፋንታ በጎ መልሰህልኛልና አንተ ከእኔ ይልቅ ጻድቅ ነህ። እግዚአብሔርም በእጅህ አሳልፎ ሰጥቶኝ ሳለ አልገደልኸኝምና ለእኔ መልካም እንዳደረግህልኝ አንተ ዛሬ አሳየኸኝ። ጠላቱን አግኝቶ በመልካም መንገድ ሸኝቶ የሚሰድድ ማን ነው? ስለዚህ ለእኔ ስላደረግኸው ቸርነት እግዚአብሔር ይመልስልህ። አሁንም እነሆ! አንተ በእርግጥ ንጉሥ እንድትሆን የእስራኤልም መንግሥት በእጅህ እንድትጸና እኔ ዐአውቃለሁ›› አለው፡፡ 1ኛ ሳሙ ም 24፡፡ ከዚህም በኋላ ዳዊት በነገሠ ጊዜ ለልጆቹ እንዲራራላቸው ሳኦል ቃል አስገብቶት ወደ ቤተ መንግሥቱ መለሰው። ዳዊት ግን በረሀ በረሀውን ሲዞር ቆይቷል።
በሐቅለ-ፋራን ሳለ ናባል የሚባል ባለጸጋ ድግስ ደግሶ በጎቹን አሸልቶ ሲያበላ ሲያጠጣ ብላቶኖቹ “ምሳ ላክልኝ ብለህ ላክበት” አሉት። “ተው አይሆንም ያለ እንደሆነ እጣላዋለሁ” አለችው። “ይህን ያህል ጊዜ አንዲት ጠቦት እንኳ ሳትነካ ከብቶቹን ጠብቀህለት እምቢ ይላልን ላክበት ግድ የለህም አሉት።” እንኪያስ ሔዳችሁ ንገሩት አለ። ሄደው ቢነግሩት “የማነው ዳዊት” ብሎ አልሰጥም አለ። ዳዊት ይህን ሲሰማ ተቆጥቶ ሊጣላው ተነሳ። ሚስቱ አቤግያ ይህን ሰምታ 5 በግ አሳርዳ አሠርታ፣ 5ቱን አሰናድታ የበለስ የወይን ጥፍጥፍ 500 እንጀራ፣ 12 ጭነት ዱቄት አሲዛ ሄደች። ዳዊት ከመንገድ አገኛትና “ባልሽን ልታድኚው መጣሽን?” ብሎ ያመጣችውን ተቀብሏት ተመለሰ። ናባል ማታ ሰክሮ ነበርና አቤግያ ሳትነግረው አደረች። ሲነጋ ትናንት ዳዊት ሊጣላህ መጥቶ ነበር አለችው። ዳዊት ብሎ ደነገጠ። ልቡን አጥቶ ሰንብቶ በ10ኛው ቀን መልአኩ ቀስፎታል። እመቤታችንና ጌታችን ከአብራኳ አሉና እሷን ግን ኀዘኗን ከጨረሰች በኋላ ዳዊት ሚስት አድርጓታል። 1ኛ ሳሙ ም25፡፡
ከዚህ በኋላ ሳኦል ፍልስጤማውያን በጠላትነት ተነሱበትና ገጠማቸው። ከጠላቶቹ አንዱ ቀስቱን መርዝ ቀብቶ ጎኑን መታውና እንደ እሳት አቃጠለው። ሎሌውን ጠርቶ ገደልነው እንዳይሉ አንተ ጨርሰኝ” አለው። “ጌታዬ ንጉሥ ሆይ ባሪያህ ካንተ ጋር እሞታለሁ እንጂ እገድልሃለውን?” ብሎ እምቢ አለው። የገዛ ሠይፉን ከምድር ተክሎ ወደቀበት። ሌሎቹም እርሱን አይተው በገዛ ሠይፋቸው እየተወጉ ሞቱ። ዳዊት የርሱንና የልጁ የዮናታንን ሞት ሲሰማ አዘነ። ግጥም እየገጠመ አለቀሰላቸው። ከሳዖል ሞት በኋላ ዳዊት መንግሥቱን አጽንቶ ጽዮንን አቅንቶ ተቀመጠ። ታቦተ ጽዮንንም በዕልልታ በሆታ ወደከተማው አስገባ። የሳኦል ልጅ ሜልኮል ዳዊትን በታቦተ ጽዮን ፊት ሲዘምር አይታ በልቧ ናቀችው። ሲገባ ልትቀበለው ወጥታ “የእስራኤል ንጉሥ በባሪያዎቹ ቆነጃጅት ፊት ዕርቃኑን በመግለጹ ምን ይከብር?” ብላ በአሽሙር ዘለፈችው። በዚህ ቢያዝንባት መካን ሆና ሞታለች። “ሜልኮል እስከምትሞት ድረስ ልጅ አልወለደችም ነበር” እንዲል። 2ኛ ሳሙ ም6፡፡
በዘመኑ የነበረው ነቢይ ቅዱስ ናታን ነው። እርሱም ሊጠይቀው መጥቶ ሳለ አዝኖ አየው። “ምን ሆነህ ታዝናለህ?” አለው። ቅዱስ ዳዊትም “እኔ በጽድ በዝግባ በተሠራ ቤት ተቀምጬ ታቦተ ጽዮን በድንኳን ስትኖር ምነው አላዝን?” አለ። “ጠላት ጠፍቶልሀል፤ መንግሥትህም ጸንቶልሀል አታንጽምን?” አለው። “ያስ ቢሆን ያለፈቃደ እግዚአብሔር ይሆናልን?” አለ። ከዚህም በኋላ ሁለቱም ቀኖና ገቡ። የቤተ መቅደስ ነገር ለናታን ተገልጾለት “አንተ አይደለህም የምትሠራልኝ ከአብራክህ የተከፈለ ልጅህ ይሠራልኛል” ብሎታል። 2ኛ ሳሙ 7፡1-17፡፡ ለቅዱስ ዳዊት ግን የበለጠ የሥጋዌ ነገር ተገልጾለት “እነሆ በኤፍራታ ሰማነው” ብሏል። መዝ 131፡6፡፡
ኢዮአብና አቢሳ ጠላት ለመመለስ ታቦተ ጽዮንን አሲዘው ሠራዊት አስከትለው ወደ አራቦት ዘመቱ። ቅዱስ ዳዊት ግን ከከተማ ቀርቶ ነበር። በሰገነቱ ሲመላለስ ቤርሳቤህን በአፀደ ወይን ውስጥ ስትተጣጠብ አይቷት ፍቅረ ዝሙት አደረበት። “የማን ሚስት ናት?” አለ። “የኦርዮን” አሉት። ኦርዮን ዘምቶ ነበር። “የባልንጀራህን ሚስት አትመኝ” (ዘጸ 20፡14-17) ያለውን ተላልፎ አስጠርቶ ደረሰባትና ጸነሰች። ጽንስ ያሳስትልኛል ብሎ እቦ ኦርዮንን አስጠርቶ ስለጦሩ ሁኔታ ከጠየቀው በኋላ “ወደቤትህ ሂድ” አለው። ኦርዮን ግን ድንኳን አስተክሎ ከዘበኞቹ ጋር አደረ። “አልመጣም” ብሎ ላከችበት። ዳግመኛም የሚያሰክር መጠጥ አጠጥቶ “ወደቤትህ ግባ” አለው። “ጌታዬ ንጉሥ ሆይ ታቦተ ጽዮን ተማርካ እስራኤላውያንም ዋዕየ ፀሐዩን ቁረ ሌሊቱን ታግሠው በሜዳ ሲሆኑ እኔ ቤቴ ገብቼ ተድላ ደስታ አደርግ ዘንድ ይገባልን?” ብሎ እምቢ አለ። በማግሥቱ “ኦርዮንን ፊት መሪ አድርጉት ጦሩ ሲበረታ ትታችሁት ሽሹ እሱ በዚያ ይሙት” የሚል ጽፎ አትሞ “ለኢዮአብ ስጠው” ብሎ ሰጠው። የዋህ ነውና የሞቱን ደብዳቤ ይዞ ሄዶ ሰጠው። ኢዮአብ እንደታዘዘው ኦርዮን ከፊት አሳልፈው ጦሩ ሲበረታ ተጠቃቅሰው ወደኋላ ሸሹ። እርሱ መለስ ብሎ “ምን ሆናችሁ?” ቢላቸው ጠላቶቹ ደርሰው ልብ ራሱን ብለው ገድለውታል። | 248 |
| 10 | Sin texto... | 261 |
| 11 | ††† እንኳን ለእናታችን ቅድስት መሪና ሰማዕት እና ቅዱስ ለንጊኖስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። †††
††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††
††† ታላቋ ቅድስት መሪና ሰማዕት (SAINT MARINA THE GREAT) †††
††† እናታችን ቅድስት መሪና ስም አጠራራቸው ከከበረ : ተጋድሏቸው ካማረ ታላላቅ ሴት ሰማዕታት አንዷ ናት:: ተወልዳ ያደገችው ከዋናው ዘመነ ሰማዕታት በፊት በ2ኛው መቶ ክ/ዘመን ሶርያ አካባቢ ነው:: አባቷ ዳኬዎስ የሚባል ጣዖት አምላኪ ቢሆንም እናቷ ግን ክርስቲያን ነበረች::
ነገር ግን እናቷ ገና በ5 ዓመቷ ሞተችባትና ለሞግዚት ተሰጠች:: የእግዚአብሔር ጥበብ ሆኖ ሞግዚቷ ደግ ክርስቲያን ነበረችና ለ10 ዓመታት ሃይማኖተ ክርስቶስን እና ምግባረ ጽድቅን አስተማረቻት:: ዕድሜዋ 15 ዓመት ሲሆን አባቷ ዳኬዎስ አረፈ::
በዘመኑ ዳኬዎስ የሚሉት (ቅዱስ መርቆሬዎስን የገደለው) ክፉ ንጉሥ ነበርና ክርስቲያኖችን አሳደዳቸው:: ይህን ዜና ቅድስት መሪና ስትሰማ ደስ አላት:: እጅግ ባማረ ንጽሕና እንደ ኖረች ሁሉ በክርስቶስ ስም ደሟን ለማፍሰስ አስባ ወደ ንጉሡ መኮንን ሔደች::
††† አበው እንዳስተማሩን ከሴቶች ሰማዕታት በውበትና ደም ግባት እንደ ቅዱሳት:-
*መሪና
*አርሴማ እና
*ጣጡስ የሚያክል የለም:: ዐይንን ማፍዘዝ የሚችል ውበት ነበራቸው::
መኮንኑ መልኩዋን ዐይቶ ሰውነቱ ተናወጠ:: "ጣዖት አምልኪና የእኔ ሚስት ሁኚ" አላት:: እርሷ ግን መኮንኑን ከነ ጣዖቱ አቃለለችው:: "እኔ የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ" አለችው::
መኮንኑ ካነጋገሯ የተነሳ ተቆጥቶ ይገርፏት ዘንድ አዘዘ:: መሬት ላይ ጥለው በብረት ዘንግ ቢመቷት አካሏ እየተቆረጠ ብዙ ደም ፈሰሰ:: ወስደውም ጨለማ ውስጥ ጣሏት:: ቅዱስ ሚካኤል ከሰማይ ወርዶ አድኗት: አጽንቷትም ዐረገ::
በማግስቱ በመጋዝ አካሏን ቆራርጠው ጣሉ:: ዳግመኛ ሊቀ መላእክት አዳናት:: ወደ ጨለማ ክፍል ወስደው ሲጥሏት ትልቅ ዘንዶ መጣባት:: እጆቿ ተዘርግተው እጸለየች ዋጣት:: እርሷ ግን ጸሎቷን ቀጠለች:: ከደቂቃዎች በሁዋላ ግን ዘንዶው ለ2 ተሰነጠቀና እጆቿ እንደተዘረጉ ወጣች::
በሌላ ቀን ግን ሰይጣን ፊት ለፊት መጥቶ ታገላት:: ከሰማይ ነጭ ርግብና መስቀል ወርዶላታልና አልቻላትም:: ከእግሯ በታች ጥላ ደጋግማ ረገጠችው:: ሰይጣንም በሐፍረት እየጮኸ ሔደ::
"ለሰይጣን ኬደቶ ከመ አሣዕን በእግር" እንዲል:: (እንዲህ ነበሩ የቀደመው ዘመን እናቶቻችን)
መኮንኑ ከክርስትና ያስወጣት ዘንድ በትልቅ ጋን ውሃ አስፈልቶ "በዚያ ላይ ቀቅሏት" አለ:: ድንገት ግን ከሰማይ ነጭ ርግብ ወርዳ: ውሃውን አቀዝቅዛ: 3 ጊዜ በውሃው አጠመቀቻት:: (እስከዚህ ሰዓት ድረስ አልጠመቀችም ነበርና)
ርግቧ የብርሃን ልብስ አልብሳ: አክሊለ ክብር ደፋችላት:: መኮንኑ ተስፋ ስለ ቆረጠ "አንገቷን በሰይፍ ምቱ" አለ:: በዚያች ሰዓት የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወርዶ "ብጽዕት መሪና ብጽዐን ይገባሻል" አላት::
"ስምሽ በሚጠራበት: መታሰቢያሽ በሚደረግበት ሁሉ በዚያ ረድኤት: በረከት ይበዛል:: አንቺን ያከበረውን አከብረዋለሁ:: ከርስትሺም አስገባዋለሁ" ብሏት ጌታችን ዐረገ::
ወታደሮቹ አንገቷን በሰየፉ ጊዜ ታላቅ መነዋወጽ ሆነ:: ድውያን ተፈወሱ: ዕውሮች አዩ: አንካሶች ረቱ: የማይሰሙትም ሰሙ:: ቅዱሳን መላእክትም ከሰማያት ወርደው የቅድስት መሪናን ነፍስ በዝማሬ አሳረጉ::
††† ቅዱስ ለንጊኖስ ሰማዕት †††
††† ለንጊኖስ ማለት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስብከት ዘመን የዺላጦስ ወታደር የነበረ ሰው ነው:: ስለ ጌታችን ተአምራት በየጊዜው ይሰማ ነበር:: ሔዶ እንዳያገኘው ግን አይሁድን ይፈራ ነበር:: እነርሱ "በክርስቶስ ያመነ ሁሉ ከምኩራብ ይባረር" ብለው ነበርና:: (ዮሐ. 9:22)
ጌታችን በተሰቀለባት ዕለተ ዐርብ ግን ጭንቅ ሆነበት:: ጌታን እንዲሰቅሉ ከታዘዙ ወታደሮች እንደ አንዱ ተመርጦ ነበርና በዘዴ "አሞኛል" ብሎ እስከ 9 ሰዓት ድረስ ቆየ::
በሁዋላ ግን አይሁድ "በክርስቶስ ሞት ያልተባበረ ሁሉ ወንጀለኛ ነው" የሚል አዋጅ በማስነገራቸው እየፈራ ቀራንዮ ሲደርስ "ጐኑን ውጋው" ብለው ረዥምና ጥቁር ጦር ሰጡት:: ለንጊኖስ ወደ ጌታችን ዐይን ተመለከተ:: እያየው እንዳልሆነ ገመተ::
ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው በባሕርይ ሥልጣኑ ለይቷልና ጦሩን ጨብጦ ወደ ጌታ ጐን ልኮ ወጋው:: ከጌታ ቀኝ ጐንም በ"ለ" አምሳል ትኩስ ደምና ውሃ ፈሰሰ:: አንዷ ፍንጣቂ ሔዳ የታወረች ዐይኑ ላይ ዐርፋ ዐይኑን አበራች::
ለለንጊኖስ ታላቅ ደስታ ሆነ:: ለእኛ ግን ማየ ገቦና ደመ ገቦ ፈለቀልን:: የጌታችን ትእግስቱና ቸርነቱ ግን ይደንቃል::
"ከመ ኢየሐስብ ቦቱ ዘኩናተ እዱ ርግዘቶ::
በኃጣውኢሁ ለዘኢፈቀደ ሞቶ::
ምሕረቶ እሴብሕ ወዐዲ ትዕግስቶ::" እንዳሉ ሊቃውንት::
ጌታችን ከተነሳ በሁዋላ ለንጊኖስ ወደ ቅዱስ ዼጥሮስ ዘንድ ሒዶ ስለ እውነት : ስለ ሃይማኖትም ተማረ:: ተጠምቆ: ምድራዊ ወታደርነቱን ትቶ እየሰበከ ከኢየሩሳሌም ወደ ቀዸዶቅያ ወረደ:: ለዘመናትም ጌታችን ክርስቶስን በሥርዓተ ወንጌል አገለገለ::
በመጨረሻም በጢባርዮስ ቄሣር ዘመን አይሁድ አሳደዱት: አንገላቱት:: የነርሱ ወገን ስለነበረም መከራ አጸኑበት:: የጽድቅ አርበኛና የክርስቶስ ሐዋርያ ቅዱስ ለንጊኖስ ግን ጸና:: በዚህች ዕለትም አይሁድ አንገቱን ቆርጠውት ለሰማዕትነት በቃ:: ቅዱሱ በሕይወቱም በዕረፍቱም ተአምራትን ሠርቷል::
††† እግዚአብሔር በቸር ጥሪው ሁላችንም ወደ ቀናው የጽድቅ ጐዳና ይጥራን:: ከሰማዕታቱም ረድኤት በረከት ይክፈለን::
††† ሐምሌ 23 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅድስት መሪና እናታችን (ታላቋ ሰማዕት)
2.ቅዱስ ለንጊኖስ ሐራ (ሐዋርያና ሰማዕት)
3.ቅዱስ አብጥልማዎስ
††† ወርኀዊ በዓላት
1.ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት
2.ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት
3.ነቢየ ጽድቅ ቅዱስ ሰሎሞን (ንጉሠ እሥራኤል)
4.አባ ጢሞቴዎስ ገዳማዊ
5.ቅዱስ ዳንኤል ነቢይ
6.አባ ሳሙኤል
7.አባ ስምዖን
8.አባ ገብርኤል
††† "ወደ ጌታ ኢየሱስ በመጡ ጊዜ ግን እርሱ ፈጽሞ እንደ ሞተ አይተው ጭኑን አልሰበሩም:: ነገር ግን ከጭፍሮች አንዱ ጐኑን በጦር ወጋው:: ወዲያውም ደምና ውሃ ወጣ:: ያየውም መስክሯል : ምስክሩም እውነት ነው:: እናንተም ደግሞ ታምኑ ዘንድ : እርሱ እውነት እንዲናገር ያውቃል:: ይህ የሆነ:-
"ከእርሱ አጥንት አይሰበርም" የሚል የመጽሐፍ ቃል እንዲፈጸም ነው:: ደግሞም ሌላው መጽሐፍ:-
"የወጉትን ያዩታል" ይላል::" †††
(ዮሐ. 19:33)
††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
https://t.me/zikirekdusn | 323 |
| 12 | Sin texto... | 363 |
| 13 | +1 "" አትፍሪ ! "" (ዘፍ. ፳፩፥፲፯)
°ገድለ ቅዱስ ቂርቆስ፥ ወእሙ ኢየሉጣ
(ሐምሌ 19 - 2018) | 549 |
| 14 | አንዲት እንቁራሪት ቀስ ብላ ውኃ በተሞላ ድስት ውስጥ ትገባለች። የድስቱ ውኃ ቀስ በቀስ በምድጃ ላይ መንደድ ይጀምራል። ውኃው እየሞቀ ሲሄድ እንቁራሪቷ ምንም ዓይነት ምቾት ማጣት አላሳየችም፤ ይልቁንስ ከአካሏ የሙቀት መጠን ጋር ውኃውን ለማስማማት ሰውነቷን ታስተካክላለች።
....
ውኃው እየተከተከተ እና እየፈላ ሲሄድ፣ እንቁራሪቷ አሁንም ከአዲሱ የሙቀት መጠን ጋር ለመላመድ ጥረት ታደርጋለች። በመጨረሻም ውኃው እጅግ ከመፍላቱ የተነሳ እንቁራሪቷ ከድስቱ ዘልላ ለመውጣት ትሞክራለች። ነገር ግን ሰውነቷን ከሙቀቱ ጋር ለማስማማት አቅሟን በሙሉ ጨርሳ ስለነበር፣ ዘልላ የመውጣት ጉልበት በማጣቷ በፈላው ውኃ ውስጥ ተቀቅላ ትሞታለች።
...
እንቁራሪቷን የገደላት ማን ነው?
...
እንቁራሪቷን የገደላት መውጣት በነበረባት ሰዓት ውኃው ጋር ለመላመድ ስትታገል አቅሟን መጨረሷ ነው። በሕይወታችን ውስጥ ጎጂ ከሆኑ ሁኔታዎች፣ መጥፎ ልምዶች ወይም መርዛማ ግንኙነቶች ጋር “እየተላመድን” አቅማችንን እንጨርሳለን። መቀየር ወይም መውጣት ያለብንን ነገር በጊዜ መወሰን አለብን። | 713 |
| 15 | ሐምሌ 22 (፳፪) እንኳን ለቅዱስ ዑራኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችኹ አደረሰን።
"ዑራኤል የተባለ መልአክ ሊረዳኝ መጣ" ዕዝ ሱቱ ፪÷፩
✥ ቅዱስ ዑራኤል ከ7ቱ ሊቀ መላእክት አንዱ ነው። መላእክት በስማቸው ቅጥያ ኤል የሚል ቃል አለ ይኸውም እግዚአብሔር ማለት ነው። "ዑር" ማለት ብርሃን፤ "ኤል" ማለትም እግዚአብሔር ማለት ነው።ዑራኤል ማለት የብርሀን ጌታ፣ የብርሀን አምላክ ማለት ነው።
✥ የሰማይን ሚስጥር ለሄኖክ እውቀትን የገለጸለት መልአክ ነው። የፀሐይን የጨረቃን የከዋክብትንና የሰማይ ሰራዊትን ብርሃንን የሚመራ እርሱ መሆኑን ለሄኖክ ነግሮታል። መ.ሄኖክ 28፥13
✔️በብርሃናት ሁሉ ሊቀ ብርሃናት ሆኖ የተሾመው ቅዱስ ዑራኤል ነው።
✔️ቅዱስ ዑራኤል በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ ስለሆነ እርሱም መባርቅትን ለጥጋብና ለበረከት እንዲሁም ነጎድጓድን ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል። መ.ሄኖክ ፮፥፪
➕ ምስጢረ ሰማይና እውቀትንም ሁሉ ለሄኖክ የገለጸለት የፀሐይን የጨረቃን የከዋክብትንና የሰማይ ሰራዊትን ብርሃንን የሚመራ እርሱ መሆኑን ለሄኖክ ነግሮታል።
✥ ቅዱስ ዑራኤል ልቡናን የሚያበራ እውቀትን የሚገልጽ ርሑሩህ መልአክ ነው። ቅዱስ ዑራኤል ለነብዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋአ ልቡናን አጠጥቶት ሰማያዊ ሚስጥራትን ገልፆለታል። ነብዩ እጅግ ብዙ ቁጥር ያላቸውን መጻሕፍት ደርሷል። በሰዓታቱም "ንዒ ኀቤየ ኦ ድንግል ምስለ ኤልያስ ወኤልሳዕ ነቢያተ እስራኤል ወምስለ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋዓ ልቡና ዘአስተዮ ዑርኤል፡፡"/// "ነይ ወደ እኛ ድንግል ሆይ ከእስራኤል ነብያት ከኤልያስና ከኤልሳ እንዲሁም ዑራኤል ጽዋ ልቡናን ካጠጣው ከእዝራ ሱቱኤል ጋር።"
✥ ሌላኛው ቅዱስ ዑራኤል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእጸ መስቀል ላይ በቀራንዮ በአምስቱ ቅንዋት( ሳዶር፣አላዶር፣ዳናት፣አዴራ፣ሮዳስ) ሲቸነከር ይህ ብርሃናዊ መልአክ ነው ከጎኑ የክርስቶስን ደም በጽዋ ቀድቶ በዓለም ሁሉ የረጨው።
✥እመቤታችን ወደ ግብፅ በተሰደደች ጊዜ በዚህ የጭንቅ ጊዜ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን እየተራዳ መንገድን እየመራት በብርሃን ወደ ሀገረ ግብፅ ቀጥሎም ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም አስራት ወደ ሆነቻት ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ እየመራት መጥቷል። ማቴ 2÷13-15
✥ " ሰላም ለአእጋሪከ ወለሰኰናከ እለ ሖራ። ፍና ተራድኦ ግሙራ። ዑራኤል ለድንግል ፍኖተ ምድረ ግብፅ አመራ። ሠለስተ ዓመተ በስደት እንዘ ታስቅቁ ነቢራ። ከመ በፍስሓ ትትመየጥ ለበዊእ ሀገራ።"///" ዑራኤል ሆይ ለእርዳታ ፈጽመው ለሚፈጥኑት እግሮችህና ሰኰናህ ሰላም እላለሁ። ዑራኤል ሆይ በስደት ወራት ለድንግል የምድረ ግብፅን መንገድ ያመለከትካት አንተ ነህ። ሦስት ዓመት እያለቀሰችና እያዘነች በስደት ከቆየች በኋላ ተመልሳ ወደ ሀገሯ እንድትገባ የደስታ የምስራች ያበሰርካት አንተ ነህና።" መልክአ ዑራኤል
✥ ሌላው የእውቀትን ብርሃን የገለጸላቸው የእውቀትን ጽዋ ያጠጣቸው ለሊቁ አባታችን አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ነው። እኚም አባታችን በመልአኩ ተራዳኢነት ብዙ ድርሰቶችን ደርሰዋል። እመቤታችንም በምልጃዋ ቅዱስ ዑራኤል የእውቀትን ጽዋ ያጠጣቸው ዘንድ አድርጋለች። አባ ጊዮርጊስ እመቤታችንን ይወዷት ስለነበረ አርጋኖን ሌሎችንም ደርሰዋል።
የሊቀ ብርሃናት ቅዱስ ዑራኤል በረከት ተራዳኢነት ኣይለየን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር | 1 149 |
| 16 | ❗ከዋሸህ አትማል አንዱ ኃጢአት ይበቃል📍
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"📖ምሳ 1፥33☦📚
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
📗ስንክሳር ዘወርኃ ሐምሌ ፳፪/22
https://t.me/Orthodoxtewahdoc
🌹የያዕቆብ ሌሊት ይሁንልን🕊
በጸሎታችሁ ወለተ ሥላሴ እያላችሁ እስቡኝ | 775 |
| 17 | Sin texto... | 760 |
| 18 | የሆነ ቀን የሙጥኝ ያልኩባቸው ነገሮች ደርሰው ከእጄ እንደገቡ ሲሰማኝ... ሰው ነኝና ሰውነቴ መስመር ስቶ እንዳልንቃቸው ዋጋ እንደሌላቸው እንዲሰማቸው ፣ የውሀ ሽታ የሆነ ደስታም ተስፋም እንዳልሰጣቸው እሰጋለሁ!
ሰው ነኝና ሰውነቴን የሳትኩ ቀን ራስ ወዳድ የሆንኩ እለት ያቃኑኝን እንዳልሰብር የኖሩልኝን እንዳልገ-ድል አጥብቄ እፈራለሁ ...ለዚህ ደግሞ መሸሽ ደጉ መሄድ ደጉ ሰውነቴን ለመቀበል ከሰው መራቅ በጀኝ...ብቸኝነቴ ምቾቴ ነው 🔥
መልካም አዳር🥰🦋✝ | 822 |
| 19 | ፈተናህ ባልተጠበቀ ሁኔታ ሊመጣ እንደሚችል ሁሉ፣ እፎይታህም እንዲሁ በድንገት ሊመጣ ይችላል። በጭራሽ ተስፋ አትቁረጥ። ወደፊት የሚጠብቅህን ነገር አሁን ላይ ባለህበት ሁኔታ አትለካው። ማዕበሎች ለዘላለም አይቆዩም፤ አስቸጋሪ ጊዜያትም እንዲሁ። ዛሬ እያለፍህበት ያለው ፈታኝ ምዕራፍ፣ ነገ ተስፋ አለመቁረጥህ ምን ያህል ትክክል እንደነበር የሚያስታውስህ ታሪክ ሊሆን ይችላል።
ሰናይ ምሽት🦋🤲🥰 | 906 |
| 20 | ትክክለኛው ችግር ሰዎች አንተን ለማስቀመጥ በሚፈልጉት ቦታ ላይ ሳይሆን፣ አንተ ራስህ ለመሆን በምትመርጠው ቦታ ላይ ነው። በሌሎች እይታ ውስጥ ያለህ ቦታ የእነሱ አስተያየት ውጤት ነው፤ ነገር ግን ራስህን በዚያ ቦታ ውስጥ ከገደብክ፣ ያ የአንተ ድክመት ነው። እውነተኛ ዋጋህ የሚወሰነው በሌሎች ውሳኔዎች ሳይሆን፣ ከእነሱ አስተያየቶች በላይ ከፍ ብለህ ለመውጣት በምታደርገው ድፍረት ነው።
Amari La
ደህና አምሹ🥰🦋 | 932 |
