3 444
مشترکین
-424 ساعت
-107 روز
-5330 روز
آرشیو پست ها
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥቆማ
የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን የነጻ ትምህርት ዕድል ጥሪ አቅርቧል።
የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ጠንካራ ሀገራዊ የኒውክሊየር መሰረተ ልማት ለመገንባት የሚያስችሉ ከፍተኛ ባለሙያዎችን ለማፍራት ለኢትዮጵያውያን ተማሪዎችና ሰልጣኞች በሩሲያ የነጻ ትምህርት ዕድል ማመቻቸቱን አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ለ2026/27 የትምህርት ዘመን በሩሲያ በሚገኙ ስመጥር የሳይንስና የምህንድስና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ መማር የሚፈልጉ ብቁ አመልካቾች እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል።
የሚሰጡ የትምህርት ዘርፎች በኒውክሊየር ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ላይ ያተኮሩ ሲሆን እነዚህን ዘርፎችንም ያካትታል ፡-
- Nuclear Power Engineering and Heat Physics (BSc & MSc)
- Nuclear Physics and Technology (BSc)
- Nuclear Power Plants Design, Operation and Engineering (BSc)
- Heat Power Engineering (BSc)
- Management in Technological Systems (MA)
የመወዳደሪያ መስፈርቶች ?
• ለመጀመሪያ ዲግሪ (BSc) ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት ያልበለጠ እና የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ አማካኝ ውጤታቸው 500 እና ከዚያ በላይ የሆነ።
• ለሁለተኛ ዲግሪ (MSc/MA) ዕድሜያቸው ከ30 ዓመት ያልበለጠ እና በሳይንስና ምህንድስና ዘርፍ በከፍተኛ ውጤት የተመረቁ።
ሴት አመልካቾች ለዘርፉ እንዲበረታቱ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል።
መስፈርቱን ምታሟሉ አመልካቾች ከዛሬ ጀምሮ ባሉት 5 የሥራ ቀናት ውስጥ የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን እና ደጋፊ ሰነዶቻችሁን በPDF በማዘጋጀት በኮሚሽኑ የኢሜል አድራሻ enecinfo@enec.gov.et መላክ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።
ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
Repost from Mesfin mekuria @ Ambo University (WFSBSS)
+9
Sample mathes formula
Repost from Mesfin mekuria @ Ambo University (WFSBSS)
20 Coordinate Geometry Formulas
A detailed coordinate geometry formula sheet covering distance, section, midpoint, slope, line equations, circle equations, and centroid. It is helpful for quick revision and problem-solving practice.
#CoordinateGeometry #MathsFormulas #GeometryRevision #StudyTips #ExamPreparation
Repost from Mesfin mekuria @ Ambo University (WFSBSS)
20 Circle Geometry Theorems
A complete circle geometry theorem sheet covering angles, chords, tangents, arcs, secants, and sector formulas. The diagram-based layout makes revision easier for solving circle-related problems.
#CircleGeometry #GeometryTheorems #MathsNotes #CircleRules #examrevision
📢 የምዝገባ ጊዜ ተራዝሟል!
ዲጂታል ኢትዮጵያን በሳይበር ደህንነት እና በቴክኖሎጂ እውቀት ለመገንባት ራዕይ ላላቸው ወጣቶች የተዘጋጀው 5ተኛው ዙር የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ ሰመር ካምፕ የዕጩ ሰልጣኞች ምዝገባ ጊዜ ተራዝሟል!
ባለፉት ዙሮች በካምፑ አልፈው ዛሬ ላይ የራሳቸውን የቴክኖሎጂ ስታርት-አፕ የመሰረቱ፣ በድሮን ቴክኖሎጂ፣ በኢምቤድድ ሲስተምስ እና በሳይበር ደህንነት ዘርፍ ሀገራዊ ችግር ፈቺ ስራዎችን እየሰሩ ያሉ የካምፑ ፍሬዎችን ተመልክተናል።
እርስዎስ የዚህ ጉዞ አካል ለመሆን ምን ይጠብቃሉ?
📅 የምዝገባ ማጠቃለያ ቀን፦ እስከ ግንቦት 17 / 2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ!
የቴክኖሎጂ እና የሳይበር ተሰጥኦ ያላቸው፣ መስፈርቱን የሚያሟሉ ወጣቶች የተራዘመውን እድል ተጠቅማችሁ ፈጥናችሁ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን።
🔗 የምዝገባ ሊንክ፦ https://ctc.insa.gov.et/registration
ፈጠራችሁን ወደ ተግባር ቀይራችሁ የሀገራችሁን የሳይበር ሉዓላዊነት የምታስከብሩበት መድረክ ይጠብቃችኋል!
#INSA #CyberTalent2018 #SummerCamp #CyberSecurity #DigitalEthiopia2030 #TechTalent
ተጨማሪ የሳይበር ደህንነት መረጃዎችን ለማግኘት፡-
• ድረ ገጽ፦ https://www.insa.gov.et
• ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/INSA.ETHIOPIA
• ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@insa_et?_t=8qBKkyp092r&_r=1
• ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/@cyberigna1003/featured
• ቴሌግራም፦ https://t.me/insagovet
• ትዊተር (X) ፦ https://twitter.com/INSAEthio
• ሊንክድኢን:- https://www.linkedin.com/.../information-network.../
• የሳይበር ጥቃት ጥቆማ ለመስጠት፡- ነጻ የስልክ መስመር 933
Repost from Arada education office
የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች የሚለማመዱባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆኑ።
(ግንቦት 6/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች የሚለማመዱባቸው አድራሻዎች ይፋ አድርጋል።
የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን በበይነ መረብ (CBT) ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን ሁሉም ተፈታኞች በተደለደሉበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር ትይዩ ባለው ማስፈንጠሪያ በመጠቀም USER Name በሚለው ላይ የፈተና አዳራሽ መግቢያ ካርድ ላይ ያለውን አድሚሽን ቁጥር በማስገባት እና Pass word በሚለው ላይ 1234 በማስገባት በዴስክቶፕ ኮምፕዩተር፣ በላፕቶፕ ኮምፕዩተር፣ በታብሌት፣ በስልክና በመሰል የኤልክትሮኒክስ መሣሪያዎች ማንኛውንም ዓይነት ኢንተርኔት አማራጭ በመጠቀም ከግንቦት 07/2018 ዓ/ም ከጥዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከፈተናው ድረስ መለማመመድ ይችላሉ ተብላል።
ተፈታኞች አዲሚሽን ካርድ ከየትምህርት ቤቶቻቸው ማግኘት የሚችሉ ሲሆን በየጊዜው የተለያዩ የሚለማመዱባቸውን ፈተናዎች በተከታታይ የሚሰጥ መሆኑን ፈተናዎች አገልግሎት ገልፃል።
ስለሆነም መምህራን ፣ የትምህርት ቤት አመራርና ወላጆች ተፈታኞቹ እንዲለማመዱ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንዲያደርጉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ጥሪ አቅርባል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+2
#AddisAbaba
የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ፈተናዎች የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
በአዲስ አበባ የ2018 የትምህርት ዘመን ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና እና የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡
በዚህ መሰረት የ6ኛ ክፍልፈተና ሰኔ 8 ፣ 9 እና 10/2018 ዓ.ም እንዲሁም የ8ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
በ6ኛ ከፍል 84,882 ተማሪዎች በ199 የመፈተኛ ጣቢያዎች እንዲሁም በ8ኛ ከፍል 86,808 ተማሪዎች በ201 የመፈተኛ ጣቢያዎች ፈተናዉን ለመውሰድ ተመዝግበዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመስጠት 667 የፈተና ማዕከላት ተዘጋጁ
NBC Ethiopia
። ። ። ። ። ። ። ።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና በ667 የፈተና ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው አለ።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) እንደገለጹት፥ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናን በ97 ዩኒቨርሲቲዎች እና በ570 የክልል ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ፈተና መደበኛ ተማሪዎችን ጨምሮ በሁሉም ፕሮግራሞች በተፈጥሮ ሳይንስ 306 ሺህ 964 እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ 257 ሺህ 255 በድምሩ 564 ሺህ 219 ተማሪዎች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡
ፈተናውን በሙሉ አቅም በበይነ መረብ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ÷ በተለያዩ ምክንያቶች ቁጥራቸው አነስተኛ የሆኑ በወረቀት የሚፈተኑ ተማሪዎች እንደሚኖሩም ጠቁመዋል።
በየክልሎች እና የፈተና ማዕከላት ያለው አቅም የተለያየ ቢሆንም በርካታ ኮምፒዩተሮች ለፈተና ዝግጁ እየተደረጉ እንደሚገኙ አመልክተዋል።
ከባለፈው አርብ ጀምሮ ለተፈታኞች የበይነ መረብ የሙከራ ፈተና መሰጠት መጀመሩን አንስተዋል።
ፈተናው በ6 ዙር እንደሚሰጥና በማህበራዊ ሳይንስ በሶስት ዙር በተመሳሳይ በተፈጥሮ ሳይንስ ደግሞ በሶስት ዙር በመሆኑ አንድ ኮምፒዩተር ስድስት ተማሪን ያስተናግዳል ነው ሉት።
ተማሪዎች የፈተና ስርዓቱን እንዲለማመዱና ትምህርት ቤቶች እና ወላጆች ለተፈታኝ ተማሪዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉም አስገንዝበዋል።
Repost from Tikvah-University
#ጥቆማ #INSA #CyberTalentChallenge
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) 5ኛ ዙር የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ ሰመር ካምፕ ምዝገባ ማድረግ ጀምሯል፡፡
ፕሮግራሙ ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት እስከ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ድረስ ያሉ ልዩ ተሰጥኦና ፍላጎት ያላቸውን ታዳጊ ወጣቶች እንደሚያካትት አስተዳደሩ አሳውቋል።
🚀 የምዝገባ ጊዜ፦
ከሚያዚያ 29 እስከ ግንቦት 10/2018 ዓ.ም
ለመመዝገብ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) እንደሚያስፈልግ ተገልጿል፡፡
የመወዳደሪያ ዘርፎች፦
🔹 ሳይበር ደህንነት
🔹 ዴቨሎፕመንት
🔹 ኢምቤድድ ሲስተም
🔹 ኤሮስፔስ
🔹 ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ
የሰመር ካምፕ ፕሮግራሙ የሚካሔድባቸው ዩኒቨርሲቲዎች፦
➫ አዲስ አበባ ሳይንሳና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
➫ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
➫ ጅማ ዩኒቨርሲቲ
➫ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ
➫ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
➫ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ
ለመመዝገብ 👇🏼
https://ctc.insa.gov.et/registration
@tikvahuniversity
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 የትምህርት ዘመን ያሉ ፈተናዎች የሚሰጡባቸውን ቀናት እና የመሠረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና (EGRA and EGMA) የሚካሄድበትን ጊዜ ይፋ አደረገ።
አገልግሎቱ በትምህርት ዘርፉ እየተደረገ ያለውን ውጤታማ ሪፎርም ተከትሎ የአጠቃላይና የከፍተኛ ትምህርት ፈተናዎችን እየሠጠ ይገኛል። በመሆኑም ተፈታኞች አስፈላጊውን የይዘትና የስነ-ልቦና ዝግጅት እንዲደርጉ እንዲሁም ወላጆች፣ መምህራንና በየደረጃው ያለው የትምህርት አመራር ተፈታኞቻቸው የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እንዲያደርጉ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ ጊቾሮ (ዶ/ር ) አሳስበዋል።
በተያያዘም የመሠረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና (EGRA and EGMA) ጥናትና ምርምር ሥራ ለትምህርት ልማትና ጥራት መሻሻል ያለውን አይተኬ ሚና በመገንዘብ ትምህርት ቤቶች እና በተዋረድ ያለው የትምህርት አመራር ተገቢውን ትብብር እንዲያደርጉም ዋና ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል።
የፈተና ስርቆትንና ኩረጃን በጋራ እንከላከል!!
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
የጥንቃቄ መልዕክት!
በስምዎ በተመዘገበ ሲም ካርድ የሚፈጸም ህገ-ወጥ ድርጊት ተጠያቂነትን ሊያስከትል ስለሚችል አስፈላጊውን ጥንቃቄ ያድርጉ።
ሲም ካርድዎን በፒን ኮድ ይቆልፉ፣ ለሌሎች አያጋሩ፣ ሲጠፋብዎ ወዲያውኑ ያስዘጉ፣ እየተጠቀሙበት ያለው ሲም ካርድ በስምዎ የተመዘገበ ካልሆነ በእጅዎ እያለ ወደ አገልግሎት ማዕከሎቻችን ቀርበው ያስቀይሩ!
ኢትዮ ቴሌኮም
ለውድ ደንበኛችን፡ የጥንቃቄ መልዕክት አለን።
*
ከሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት ጋር በተያያዘ እርስዎ በአካል ወደ ባንካችን ቅርንጫፎች ሳይመጡ በስልክ ተደውሎ የሚሰጥ ምንም አይነት አገልግሎትም ሆነ የአሠራር ሂደት የሌለን መሆኑን እያሳወቅን፤ የይለፍ ቃልዎን ለሌላ ሶስተኛ ወገን ተጋላጭ ባለማድረግ በጥንቃቄ እንዲገለገሉ እናሳውቃለን፡፡ እንዲሁም “ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ነው” በሚል በስልክ በሚላክ መጠይቅ ምንም አይነት መረጃዎን እንደማንጠይቅዎ በመረዳት እራስዎን ከአጭበርባሪዎች እንዲጠብቁ እናሳስባለን፡፡
በተጨማሪም ፦
⦁ የአፕሊኬሽንም ሆነ USSD ተጠቃሚ ከሆኑ የይለፍ ቃልዎን ከአራት እስከ አስር ዲጂት(ቁጥሮች) ይጠቀሙ፤
⦁ የሞባይል መተግበሪያዎችን (Applications) ወይም ማስፈንጠሪያዎችን (Links) ከማይታወቅና ትክክለኛ ካልሆኑ ምንጮች ስልክዎ ላይ አይጫኑ፤
⦁ ማንኛውንም አይነት መተግበሪያ ከ-Playstore እና ከAppstore ብቻ አውርደው ይጠቀሙ፤
⦁ ጓደኛ ወይም ዘመድ በመምሰል በማንኛውም አይነት የማህራዊ ሚዲያን በመጠቀም የገንዘብ ዝውውር/ብድር ሲጠየቁ ክፍያውን ከመፈፀምዎ በፊት መልዕክቱ ከትክክለኛ ወገን የተላከልዎት መሆኑን ያረጋግጡ፤
⦁ በተለያዩ ስልቶች ከሚፈፀሙ ስርቆቶችና ማጭበርበሮች እራስዎን ይጠብቁ፤
⦁ የአሻራ ደህንነት ማጠናከሪያን ይጠቀሙ፤
⦁ የ*889# ብቻ ተጠቃሚ ከሆኑ እባክዎ ለደህንነትዎ ይበልጥ አስተማማኝና ቀልጣፋ እንዲሁም ተጨማሪ አገልግሎት ወደሚያስገኝልዎ የሞባይል መተግበሪያ ይዛወሩ፡፡
መተግበሪያውን ለማግኘት፦
ለAndroid፦https://play.google.com/store/apps/details?id=com.combanketh.mobilebanking
ለ IOS፦https://apps.apple.com/us/app/cbe-mobile-banking-new/id1534203410
*
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!!
Repost from Addis Ababa Education Bureau
12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅባቸው የትምህርት ዓይነቶችና የክፍል ደረጃዎችን ይፋ ሆኑ።
(መጋቢት 24/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅባቸውን የትምህርት ዓይነቶችና የክፍል ደረጃዎችን ይፋ አድርጓል።
በዚሁ መሠረት ፈተና የሚሰጥባቸው የትምህርት አይነቶች በተፈጥሮ ሳይንስ እንግሊዝኛ ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪና ፊዝክስ መሆናቸውን ገልጿል፡፡
በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ እንግሊዝኛ ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊና ኢኮኖሚክስ ናቸው።
ፈተናው በየትምህርት ዓይነቱ ከ9ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች የሚሸፍን ይሆናል።
የዝግጅት አግባቡም 9ኛ ክፍል ላይ የቀድሞውና የአዲሱ ስርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘት ላይ ያተኩራል።
ከ10ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ያለው በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ላይ የተመሠረተ ይሆናል።
የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት ሆኖ ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን የሚሸፍን መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Repost from Tikvah-University
ተራዝሟል!
በፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሁለተኛው ሲሚስቴር ተጨማሪ ተማሪዎችን ለመቀበል ባወጣው ማስታወቂያ ለመማር ተመዝግባችሁ በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ተማሪዎች ሪፖርት አድርጉ ተብሏል።
ተመዝግባችሁ የመግቢያ ፈተናውን ለመውሰድ ፈቃደኛ የሆናችሁ ተማሪዎች በተመዘገባችሁበት ሊንክ በመግባት በድጋሜ እንድትመዘገቡ ትምህርት ሚኒስቴር ጠይቋል።
በተሰጠው የመመዝገቢያ ጊዜ በርካታ ተማሪዎች ያልተመዘገቡ በመሆናቸው ምዝገባውን መራዘሙን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።
በመሆኑም ያልተመዘገባችሁ ተማሪዎች እስከ አርብ መጋቢት 25/2018 ዓ.ም ድረስ ምዝገባው የተራዘመ በመሆኑ እንድትመዘገቡ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።
@tikvahuniversity
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
