3 721
Подписчики
+424 часа
+237 дней
+12130 день
Архив постов
Repost from AAU-Official
ከ2019 ዓ.ም ቅድመ ምረቃ ትምህርት ማመልከቻ ጋር በተያያዝ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ የሚከተሉትን ሊንኮች ይጫኑ
1. ለ አጠቃላይ የቅድመ ምረቃ ማመልከቻ
2. ለቅድመ ምረቃ ለቀን መደበኛ መርሃ ግብር ትምህርት አመልካቾች:
3. ለቅድመ ምረቃ ለማታ ተከታታይ መርሃ ግብር ትምህርት አመልካቾች፡
4. ለ ልዩ ፕሬዝዴንሻል የስኮላርሺፕ የትምህርት እድል፤
5. ለ ልዩ የስኮላርሺፕ እድል ለመምህራን ትምህርት፡
ለተጨማሪ መረጃ የዩኒቨርሲቲውን ድረ ገጽ እና ቴሌግራም ቻናሎች እንድትጠቀሙ እናሳውቃለን፡፡
· ድረ-ገጽ፡ https://www.aau.edu.et/
· ቴሌግራም ቻናሎች፡ https://t.me/aau_official ወይም https://t.me/aauGAT
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
Repost from AAU-Official
ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ2019 የትምህርት ዘመን የቅድመ ምረቃ ትምህርት አመልካቾች የምዝገባ ማስታወቂያ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 የትምህርት ዘመን በቅድመ ምረቃ መደበኛ (በመንግስት ስኮላርሺፕ እና በግል ክፍያ) እንዲሁም በማታና ተከታታይ መርሃ-ግብር አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ዝግጅቱን አጠናቋል።
በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ከዚህ በታች በተጠቀሱት ቀናት እና መስፈርቶች መሠረት ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
አስፈላጊ መስፈርቶች እና ቀናት
* የምዝገባ ቀን፡ ከነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ።
* መሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች፡
* በ2015፣ 2016፣ 2017 እና 2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ወስደው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ያመጡ ወይም ደረጃ 4 አጠናቀው (COC) ያለፉ
* የመግቢያ ፈተና (UAT) የሚሰጥበት ቀናት ከጳጉሜን 02 እስከ ጳጉሜን 4 ቀን 2018 ዓ.ም
* ለመመዝገብ የሚከተለውን ሊንክ ይጫኑ:- https://admission.aau.edu.et
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+1
የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ውጤታቸውን ዛሬ ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምረው ማየት ይችላሉ - የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት
የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸውን ማስፈንጠሪያዎች የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጓል፡፡
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን በመጠቀም ውጤታቸውን ማየት የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ አስታውቋል፡፡
በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ
https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ማቅረብና ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡
ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡- በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et፣ ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram፣ አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡
https://result.eaes.et/sms መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መረጃ ያመላክታል፡፡
Repost from Qelem Meda Technologies | QMT
ማስታወቂያ!
(ነሀሴ 11/2018 ዓ.ም) በምስራቅ ጎህ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሳይንስ ልህቀት ማዕከል ለመማር ለተመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፦
ለፈተና የሚቀርባችሁን ክፍለ ከተማ ፣ የተማራችሁበትን የትምህርት ቤት አይነት (የመንግስት ወይም የግል) መሆኑን bs.ministry.et የሚለው ሊንክ ላይ በመግባት ስማችሁን ወይንም የተመዘገባችሁበትን ስልክ ቁጥር በማስገባት እንድትሞሉ እያሳስብን በአጭር ጊዜ ውስጥ የተመደባችሁበትን የመግቢያ ፈተና መውሰጃ ጣቢያ ፣ የፈተና ቀን እና የፈተና ሰዓት የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ
Beeksisa!
Barattoota Mana Barumsaa Sadarkaa 2ffaa Misraaq Goh: Giddugala Saayinsitti Barachuuf Galmooftan Hundaaf:-
Kutaa Magaalaa Qormaataa Itti Fudhatan Kan Isnitti Dhiyaatuufi Mana Barumsaa Itti Barattan (Mootummaa Ykn Dhuunfa) Ta'uu Isaa, Liinkii bs.ministry.et Jedhu Irratti Seenuun Maqaa Keessan Ykn Lakkoofsa Bilbilaa Ittiin Galmooftan Galchuun Akka Odeeffanoo Gaafatamtan Galchitan Cimsinee Isin Hubachiisaa, Buufata Qormaata Seensaa Itti Fudhan Yeroo Gabaabaa Keessatti Guyyaa Qormaataafi Sa’atii Qormaataa Kan Isin Beeksifnu Ta’a.
Biiroo Barnootaa Bulchiinsa Magaalaa Finfinnee
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.
Repost from Tikvah-University
+1
#AREB
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በ2019 የትምህርት ዘመን በክልሉ በሚገኙ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ለሚገቡ ተማሪዎች የምዝገባ ጥሪ አድርጓል፡፡
የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ አዳሪ ትምህርት ቤት - ደሴ፣ የክቡር ዶ/ር ሐዲስ አለማየሁ - ደብረማርቆስ፣ እንዲሁም አዲስ የተገነቡ የደብረ ታቦር እና የሰቆጣ አዳሪ ትምህርት ቤቶች አዲስ ተማሪዎችን ተቀብለው ለማስተማር ዝግጅት በማድረግ ላይ ይገኛሉ።
በመሆኑም በ2018 ዓ.ም በክልሉ ከሚገኙ የመንግሥት እንዲሁም የግል ትምህርት ቤቶች ተምራችሁ፣ ክልላዊ ፈተና የወሰዳችሁና የተቀመጡ መስፈርቶችን የምታሟሉ ተማሪዎች በትምህርት ቤቶቹ ምዝገባ እንድታደርጉ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ጥሪ አስተላልፏል፡፡
መሰፈርቶች
● የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና አማካይ ውጤት ለሴቶች 80% እና ለወንዶች 82%
● የ7ኛ እና የ8ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት አማካይ ውጤት ለሴቶች 83% እና ለወንዶች 85%
የምዝገባ ጊዜ 👇
ከነሐሴ 06-15/2018 ዓ.ም
የምዝገባ ቦታ 👇
በአማራ ክልል በሚገኙ በሁሉም የወረዳ/ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤቶች
የመግቢያ ፈተና በዞን ዋና ከተሞች ነሐሴ 25/ 2018 ዓ.ም ይሰጣል ተብሏል፡፡ (ተጨማሪ መረጃ ከላይ ከተያያዘው ምስል ይመልከቱ፡፡)
@tikvahuniversity
Repost from Testing Center-AAU
How do candidates register for the GAT?
Candidates are required to register for the GAT at the Addis Ababa University GAT portal. To register for the test, candidates are advised to use the following information.
1 https://Portal.aau.edu.et [Open]
2 Apply for exam [click]
3 Test Taker Registration form [fill it]
4 Upload passport size photo [test taker’s photo]
5 Submit [Click]
6 Copy the generated number
7 Use CBE short code 242424 to pay the GAT testing fee of 600 birr/six hundred birr in candidate’s full name (Given name, father’s name, and grandfather’s name) with correct spelling. Foreign applicants are required to pay an equivalent of USD 50 testing fee in Ethiopian Birr. Please check for the up to date exchange rate at the bank.
8 Upload your recent photograph
9 Once paid, download and print your Admission Ticket. Admission Ticket is required to get admission to your exam hall.
10 Candidates are advised to check their test date on regular basis following their registration. Please follow further announcements on the Telegram: Testing Center_IER_AAU(https://t.me/aauGAT) or AAU grand website
Repost from Addis Ababa Education Bureau
ትምህርት ሚኒስቴር በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የ9ኛና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል።
በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉ ተማሪዎች በዚህ ሊንክ https://sbs.moe.gov.et/apply
መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ሚኒስቴር መስራቤቱ አሳውቋል።
(ነሀሴ 5/2018 ዓ.ም)
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Repost from Aviation University Info Center
📢 የኢትዮጵያ አየር መንገድ የይፋዊ የሥልጠና እና የሥራ እድል ማስታወቂያ
(ከነሐሴ 4 እስከ ነሐሴ 8፣ 2018 ዓ.ም. / August 10 – August 14, 2026)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ብቁ ለሆናችሁ አመልካቾች በአየር መንገዱ ሙሉ ስፖንሰርሺፕ (ET Sponsored) የሚሰጡ የሥልጠና እና የሥራ እድሎችን ይፋ አድርጓል። እናንተ ልታሟሏቸው የሚገቡ መስፈርቶች፣ የምዝገባ ቦታዎች እና የሚያስፈልጉ ሰነዶች ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቦላችኋል።
🔹 1. የበረራ አስተናጋጅ (ET Sponsored Trainee Cabin Crew)
የትምህርት ደረጃችሁ: የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና (EUEEC) ወስዳችሁ ቢያንስ 200 ውጤት ያመጣችሁ።
የዕድሜ ገደባችሁ: ከ 21 እስከ 30 ዓመት (ሁለቱም ይካተታሉ)።
የቁመት መስፈርታችሁ:
ሴቶች: ቢያንስ 1.58 ሜትር (የእጅ መድረሻችሁ / Arm Reach ቢያንስ 212 ሴ.ሜ)
ወንዶች: ቢያንስ 1.70 ሜትር
ክብደታችሁ: ከቁመታችሁ ጋር የተመጣጠነ (Proportional)።
የእንግሊዝኛ ቋንቋ ችሎታችሁ: Level III እና ተጨማሪ የውጭ ቋንቋ መናገር መቻል ልዩ አጋጣሚ ይሰጣችኋል።
🔹 2. የአውሮፕላን ቴክኒሽያን እና ሜካኒክ (Trainee Aircraft Mechanic & Technicians)
(የሥራ መደቦች፡ Avionics, Airframe, Maintenance, Powerplant, Structure, Cabin Maintenance & General Mechanic)
የዕድሜ ገደባችሁ: ከ 18 እስከ 25 ዓመት (ሁለቱም ይካተታሉ)።
የቁመት መስፈርታችሁ: ቢያንስ 1.60 ሜትር እና ከዚያ በላይ (ለወንዶችም ለሴቶችም)።
የትምህርት ደረጃችሁ:
የ12ኛ ክፍል ማትሪክ አጠናቃችሁ በ ሒሳብ (Mathematics)፣ ፊዚክስ (Physics) እና እንግሊዝኛ (English) ለእያንዳንዳቸው ቢያንስ 50% እና ከዚያ በላይ ያመጣችሁ፤ ወይም
በ 10+3 / ኮሌጅ ዲፕሎማ / TVET Level III/IV በኤሌክትሮኒክስ፣ አውቶሞቲቭ፣ ሜካኒክስ፣ ኤሮኖቲካል፣ ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ፣ ወይም በተዛማጅ የቴክኒክ ዘርፎች የተመረቃችሁ።
⚠️ ልዩ ማሳሰቢያ ለሜካኒክ (Aircraft Mechanic): የመጀመሪያ ዲግሪ (BA/BSc) ያላችሁ አመልካቾች ከስራ መደቡ በላይ (Overqualified) ስለሆናችሁ ማመልከት አትችሉም።
📄 እናንተ በአካልም ሆነ በኦንላይን ስታመልክቱ ልታያይዟቸው/ልታዘጋጇቸው የሚገቡ ሰነዶች
የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ካርድ እና ከከተማ አስተዳደር የተሰጠ የልደት ሰርተፊኬት
የ10ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት
የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት / የኮሌጅ ዲፕሎማ / Level III/IV (እንደየመደቡ)
የታደሰ የከበሌ መታወቂያ (ፊቱንም ጀርባውንም በግልጽ የሚያሳይ)
አግባብነት ያላቸው ሁሉም የትምህርት ማስረጃዎች ዋናው (Original) እና ፎቶ ኮፒ
📍 እናንተ ማመልከት የምትችሉባቸው የምዝገባ ቦታዎች
አዲስ አበባ ላላችሁ: በኦንላይን ማመልከቻ ፖርታል ብቻ (የማመልከቻው ሊንክ በምዝገባ ወቅት ይከፈታል)።
በክልል ከተሞች ላላችሁ (በአካል በመገኘት):
አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (አዳማ)
አምቦ ዩኒቨርሲቲ (አምቦ)
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ (አርባ ምንጭ)
አሶሳ ዩኒቨርሲቲ (አሶሳ)
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ (ጎንደር)
ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ (ባህር ዳር)
ወሎ ዩኒቨርሲቲ (ደሴ)
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ (ድሬዳዋ)
ቦረና ዩኒቨርሲቲ (ያቤሎ)
ወለጋ ዩኒቨርሲቲ (ነቀምቴ)
ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ - ሐረር ካምፓስ (ሐረር)
ሐዋሳ ኤርፖርት (ሐዋሳ)
ጂጂጋ ዩኒቨርሲቲ (ጂጂጋ)
ጅማ ዩኒቨርሲቲ (ጅማ)
ማዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ - ሮቤ ካምፓስ (ሮቤ)
ሰመራ ዩኒቨርሲቲ (ሰመራ)
ንገሌ ቦረና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ (ነገሌ)
ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ (ወልቂጤ)
⚠️ አስፈላጊ ማሳሰቢያዎች
አንድ መደብ ብቻ: ማንኛውም አመልካች ማመልከት የሚችለው በአንድ የሥራ/የሥልጠና መደብ ላይ ብቻ ነው።
የመረጃ ትክክለኛነት: የሃሰት መረጃ አያይዛችሁ ከተገኛችሁ በሂደቱ ወቅትም ሆነ ከተቀጠራችሁ በኋላ ወዲያውኑ ከስራ እና ከስልጠና የምትሰረዙ ይሆናል።
የምዝገባ ጊዜ: ከነሐሴ 4 እስከ ነሐሴ 8፣ 2018 ዓ.ም. (August 10 – August 14, 2026) ብቻ ስለሆነ በጊዜ እንድታመለክቱ ይመከራል።
Repost from Addis Ababa Education Bureau
ማስታወቂያ!
(ነሀሴ1/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በከተማ አስተዳደሩ የሚሰጠዉን ትምህርት ጥራት ለማላቅ ሞዴል አለም አቀፍ የሳይንስ ልህቀት ማዕከል በመፍጠር በትኩረት በመስራት ላይ የሚገኝ ሲሆን በ2019 የትምህርት ዘመን በምስራቅ ጎህ የሳይንስ ልህቀት ማዕከል ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ከ9ኛ እስክ 12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር የቅድመ ዝግጅት ስራዉን ያጠናቀቀ በመሆኑ በትምህርት ቤቱ ለመማር የምትፈልጉ ተማሪዎች በትምህርት ቢሮ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ላይ በተገለጸው የመወዳደሪያ መስፈርት መሰረት በተጠቀሰው የመመዝገቢያ ሊንክ እስከ 8/12/2018 ዓ.ም ድረስ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
መመዝገቢያ ሊንክ፡- https://bs.ministry.et
Repost from Qelem Meda Technologies | QMT
ሰበር ዜና ከቀለም ሜዳ ቴክኖሎጂስ!
ሐምሌ 28/2018 ዓ.ም.
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም. የ8ኛ ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ !
በቀለም ሜዳ ቴክኖሎጂስ የበለጸገው ዘርፈ ብዙ የፈተና እርማት እና ማስተዳደሪያ ሲስተም (EMaCS Ministry) በመጠቀም ከተማሪዎች ምዝገባ እስከ ውጤት መግለጫ ሰርቲፊኬት ዝግጅት ድረስ ያለው ሂደት በዚሁ ዘመናዊ የዲጂታል አገልግሎት እየተከናወነ ይገኛል።
ስለሆነም ተፈታኝ ተማሪዎች በኮምፒውተር ወይም በስልካቸው የድር መፈለጊያ (Web browser) በመጠቀም፡-
👉 ለ 8ኛ ክፍል https://se.ministry.et/#/result የሚለውን አድራሻ በመክፈት፣
👉 ፊት ለፊት በሚታየው ቅጽ (form) ላይ የተማሪውን መለያ ቁጥር (Registration Number) እና የመጀመሪያ ስማችሁን በማስገባት በማስገባት “ውጤት ይመልከቱ (Check Your Result)” የሚለውን ቁልፍ በመጫን ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ።
በቴሌግራም ቦት አማካኝነት በቀላሉ ለማየት የሚከተሉትን ሂደቶችን ይከተሉ፦
👉ወደ @MinistryResultQMTBOT በመሄድ ቦቱን ያስጀምሩ።
👉ቦቱን ከከፈቱ በኋላ /start የሚለውን ቁልፍ ይጫኑ።
👉ክልላችሁን ምረጡ
👉ክፍላችሁን ምረጡ፡ የሚሰጡትን አማራጮች በመጠቀም “Grade 8” የሚለውን ምረጡ።
👉የሰባት ዲጂት (7-digit) የምዝገባ ቁጥርዎን በመጻፍ ውጤታሁን ማየት ትችላላችሁ።
🎯 ማስታወሻ፡ በቅድሚያ ቪፒኤን (VPN) ማጥፋት ይኖርባችኋል።
Telegram: https://t.me/qelemmedatechnologies
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/78350212/admin/notifications/all/
YouTube:
http://youtube.com/@qelemmedatechnologies
Repost from AAU-Official
ማስታወቂያ
ልጆቻችሁን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሞዴል ማህበረሰብ ት/ቤት (ከ 1-7 ኛ) ክፍል ለማስተማር ያስመዘገባችሁ የዩኒቨርሲቲው ሰራተኛ ያልሆናችሁ ማህበረሰብ በሙሉ፡
* የተማሪዎች የመግቢያ መለያ ፈተና ረቡዕ ሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በ 4:00 ሰዓት ይሰጣል።
* በመሆኑም ልጆቻችሁን በመያዝ ምዝገባ በተካሄደበት ቦታ (አምስት ኪሎ) 3:30 ሰዓት እንድትገኙ እናሳውቃለን።
*ይህንን የመግቢያ ፈተና ያልወሰደን ተማሪ የማንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን ።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሞዴል ማህበረሰብ ት/ቤት
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
#Amhara
የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።
በአማራ ክልል የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።
ከሰኔ 3-5/2018 ዓ.ም የተሰጠውን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና 173,699 ተማሪዎች ውስደው ነበር።
ፈተናውን ከወሰዱት ተማሪዎች መካከልም 135,003 (77.72%) ተማሪዎች 50% እና በላይ ውጤት አስመዝግበዋል።
ተማሪዎችም ውጤታቸውን https://amhara.ministry.et/#/result የሚለውን አድራሻ በመፃፍ ፤ በሚመጣው ቅጽ ላይ የተማሪ መለያ ቁጥር (Registration Number) እና ስም በአማርኛ በማስገባት ፤ ዉጤት ይመልከቱ (Check your result) የሚለውን ቁልፍ በመጫን ማየት ይችላሉ፡፡
በተጨማሪም @emacs_ministry_result_qmt_bot ላይ መመልከት ይችላሉ።
ተማሪዎች ማንኛውም ከውጤት ጋር የተያያዘ ቅሬታ ካላቸው https://amhara.ministry.et/#/complaint ላይ በመግባት ቅሬታቸው ማቅረብ እንደሚችሉ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይደረጋል ተብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሃምሌ 26 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
Repost from Qelem Meda Technologies | QMT
ሰበር ዜና ከቀለም ሜዳ ቴክኖሎጂስ!
ሐምሌ 24/2018 ዓ.ም.
የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም. የ6ኛ ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ !
በቀለም ሜዳ ቴክኖሎጂስ የበለጸገው ዘርፈ ብዙ የፈተና እርማት እና ማስተዳደሪያ ሲስተም (EMaCS Ministry) በመጠቀም ከተማሪዎች ምዝገባ እስከ ውጤት መግለጫ ሰርቲፊኬት ዝግጅት ድረስ ያለው ሂደት በዚሁ ዘመናዊ የዲጂታል አገልግሎት እየተከናወነ ይገኛል።
ስለሆነም ተፈታኝ ተማሪዎች በኮምፒውተር ወይም በስልካቸው የድር መፈለጊያ (Web browser) በመጠቀም፡-
👉 ለ6ኛ ክፍል https://oromia6.ministry.et/#/result የሚለውን አድራሻ በመክፈት፣
👉 ፊት ለፊት በሚታየው ቅጽ (form) ላይ የተማሪውን መለያ ቁጥር (Registration Number) እና የመጀመሪያ ስም በማስገባት
“ውጤት ይመልከቱ (Check Your Result)” የሚለውን ቁልፍ በመጫን ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ።
በቴሌግራም ቦት አማካኝነት በቀላሉ ለማየት የሚከተሉትን ሂደቶችን ይከተሉ፦
👉ወደ @MinistryResultQMTBOT በመሄድ ቦቱን ያስጀምሩ።
👉ቦቱን ከከፈቱ በኋላ /start የሚለውን ቁልፍ ይጫኑ።
👉ክፍልዎን ይምረጡ፡ የሚሰጡትን አማራጮች በመጠቀም “Grade 6” የሚለውን ይምረጡ።
👉የሰባት ዲጂት (7-digit) የምዝገባ ቁጥርዎን ያስገቡ።
👉የመጀመሪያ ስምን (First Name) በትክክል በመጻፍ ውጤታሁን ማየት ትችላላችሁ።
🎯 ማስታወሻ፡ በቅድሚያ ቪፒኤን (VPN) ማጥፋት ይኖርባችኋል።
Telegram: https://t.me/qelemmedatechnologies
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/78350212/admin/notifications/all/
Repost from Qelem Meda Technologies | QMT
ሰበር ዜና ከቀለም ሜዳ ቴክኖሎጂስ!
ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም.
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም. የ6ኛ ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ !
በቀለም ሜዳ ቴክኖሎጂስ የበለጸገው ዘርፈ ብዙ የፈተና እርማት እና ማስተዳደሪያ ሲስተም (EMaCS Ministry) በመጠቀም ከተማሪዎች ምዝገባ እስከ ውጤት መግለጫ ሰርቲፊኬት ዝግጅት ድረስ ያለው ሂደት በዚሁ ዘመናዊ የዲጂታል አገልግሎት እየተከናወነ ይገኛል።
ስለሆነም ተፈታኝ ተማሪዎች በኮምፒውተር ወይም በስልካቸው የድር መፈለጊያ (Web browser) በመጠቀም፡-
👉 ለ6ኛ ክፍል https://ce6.ministry.et/#/result የሚለውን አድራሻ በመክፈት፣
👉 ፊት ለፊት በሚታየው ቅጽ (form) ላይ የተማሪውን መለያ ቁጥር (Registration Number) እና የመጀመሪያ ስም በማስገባት
“ውጤት ይመልከቱ (Check Your Result)” የሚለውን ቁልፍ በመጫን ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ።
በቴሌግራም ቦት አማካኝነት በቀላሉ ለማየት የሚከተሉትን ሂደቶችን ይከተሉ፦
👉ወደ @MinistryResultQMTBOT በመሄድ ቦቱን ያስጀምሩ።
👉ቦቱን ከከፈቱ በኋላ /start የሚለውን ቁልፍ ይጫኑ።
👉ክፍልዎን ይምረጡ፡ የሚሰጡትን አማራጮች በመጠቀም “Grade 8” የሚለውን ይምረጡ።
👉የሰባት ዲጂት (7-digit) የምዝገባ ቁጥርዎን ያስገቡ።
👉የመጀመሪያ ስምን (First Name) በትክክል በመጻፍ ውጤታሁን ማየት ትችላላችሁ።
🎯 ማስታወሻ፡ በቅድሚያ ቪፒኤን (VPN) ማጥፋት ይኖርባችኋል።
Telegram: https://t.me/qelemmedatechnologies
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/78350212/admin/notifications/all/
Repost from Addis Ababa Education Bureau
Beeksisa!
Biiroon Barnootaa Bulchiinsa Magaalaa Finfinnee bara barnootaa 2019tti Mana Barnootaa Bultii addaa Sadarkaa Giddu-galeessaa fi Sadarkaa 2ffaa Shamarranii Itegee Manan, Mana Barnootaa Bultii addaa Dhiiraa Galaan fi Kaampaasii Saayinsii Sheerdiitti barattoota kutaa 7ffaa fi 9ffaa simatee barsiisuuf beeksisa baase irratti hundaa'uun, barattoonni “online” irratti galmee kan raawwattan hundi maqaa keessanii fi buufata qormaata seensa ‘online’ kutaa Magaalaa keessaan buufata qormaataa itti ramadamtan deemuun maaqaa keessan ialaaluun kan dandeessan ta'uu isin beeksisna.
ü kutaa 9ffaaf qormaatni seensaa “online” Roobii, gaafa Guyyaa 22/11/2018 A.L.I. ganama sa'aatii 3:00 irraa eegalee ni kennama.
ü kutaa 7ffaaf , qormaatni seensaa “online” Kamisa, Guyyaa 23/11/2018 A.L.I. ganama sa'aatii 3:00 irraa eegalee ni kennama.
Hubachiisa!
ü
Barattoonni yeroo qormaataf dhuftan waraqaa eenyummaa mana barnoota keessanii fi lakkoofsa galmee ittiin galmooftan qabatanii dhufuun kan isinirra eegamu yoo ta'u, bilbilaa fi meeshaalee elektirooniksii biroo qabatanii dhufuun dhowwaa (dhorkaa) ta'uu isin beeksisna.
Biiroo Barnootaa Bulchiinsa Magaalaa Finfinnee.
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Repost from Addis Ababa Education Bureau
ማስታወቂያ!
(ሀምሌ 20/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2019 የትምህርት ዘመን በእቴጌ መነን የልጅ አገረዶች እና በገላን የወንዶች መካከለኛና ሁለተኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በሚኒሊክ ሳይንስ ሼርድ ካንፓስ የ7ኛ እና የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት በኦን ላይን/online/ ምዝገባ ያከናወናችሁ ተማሪዎች በሙሉ ስም ዝርዝራችሁንና የተመደባችሁበትን የመግቢያ ኦን ላይን/online/ ፈተና መስጫ ጣቢያን በተመዘገባችሁበት በክፍለ ከተማ መመልከት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን
ü ለ9ኛ ክፍል ያመለከታችሁ የመግቢያ ኦን ላይን/online/ ፈተና የሚሰጠው እሮብ በ22/11/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ
ü ለ7ኛ ክፍል ያመለከታችሁ የመግቢያ ኦን ላይን/online/ ፈተና የሚሰጠው ሀሙስ በ23/11/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ
በመሆኑ ተፈታኝ ተማሪዎች ስማችሁ በሚገኝበት የመግቢያ ኦን ላይን/online/ ፈተና መስጫ ጣቢያ ላይ ፈተናው መሰጠት ከሚጀምርበት ሰዓት አንድ ሰዓት ቀድማችሁ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ!
ü ተማሪዎች ለፈተና ስትመጡ የትምህርት ቤታችሁን መታወቂያ እና የ6 እና የ8ኛ ክፍል ሬጅስትሬሽን/ምዝገባ/ ቁጥር ይዛችሁ መምጣት የሚጠበቅባችሁ ሲሆን ስልክና መሰል የኤሌከትሮኒክስ ግብዓቶችን ይዞ መምጣት የተከለከለ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ
