fa
Feedback
Skyline media

Skyline media

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام Skyline media

کانال Skyline media (@skyline7777) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 26 404 مشترک است و جایگاه 9 209 را در دسته اخبار و رسانه‌ها و رتبه 1 265 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 26 404 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 22 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -551 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -38 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 4.41% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 1.97% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 1 164 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 520 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 3 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 23 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانه‌ها تبدیل کرده‌اند.

26 404
مشترکین
-3824 ساعت
-1387 روز
-55130 روز
آرشیو پست ها
እነዚህ የአፋብን ፋኖ ሃይል የረገፈበት የጦር ሜዳ ውሎ ፎቶዎች ናቸው። ክረምት ይህች ክረምት ያሉት ለዚህ ነበር ያሳዝናል።

photo content
+9

photo content
+9

በአዲስ አበባ ለጨረታ ለቀረቡ ቦታዎች በካሬ ሜትር 265 ሺሕ ብር መሰጠቱ ታወቀ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬትና ልማት አስተዳደር ቢሮ ለጨረታ ካቀረባቸው 427 ቦታዎች ውስጥ፣ የቀረበው ከፍ
በአዲስ አበባ ለጨረታ ለቀረቡ ቦታዎች በካሬ ሜትር 265 ሺሕ ብር መሰጠቱ ታወቀ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬትና ልማት አስተዳደር ቢሮ ለጨረታ ካቀረባቸው 427 ቦታዎች ውስጥ፣ የቀረበው ከፍተኛ ዋጋ በካሬ ሜትር 265 ሺሕ ብር መሆኑና ቦታውም ካዛንቺ እንደሆነ ታወቀ፡፡፡ የመሬትና ልማት አስተዳደር ቢሮ የመሬት ዝግጅት ባንክና ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ተስፋዬ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በአምስተኛ ዙር እየተካሄደ በሚገኘው የመሬት ሊዝ ጨረታ 18 ሔክታር መሬት ቀርቧል፡፡ በሊዝ ለማጫረት ከቀረቡ ቦታዎች ውስጥ ካዛንቺስ የሚገኝ አንድ ቦታን በካሬ ሜትር 265 ሺሕ ብር ለመግዛት ከተጫራች ዋጋ መቅረቡን፣ እስካሁን በአምስት ክፍላተ ከተሞች በተደረገው የጨረታ ሒደት 76 ተጫራቾች በጊዜያዊነት ጨረታውን ማሸነፍ መቻላቸውን አክለው ገልጸዋል፡፡ ለጨረታው የቀረቡ ቦታዎች የሚገኙት በዘጠኝ ክፍላተ ከተሞች እንደሆኑ የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ በአጠቃላይ የጨረታ ሰነዱን ገዝተው የተጫረቱት ብዛት 6,885 ተጫራቾች  እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡ ዝቅተኛ... ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/140095/

photo content

ደርባባዋ ወ/ሮ ትልቅ ሰው ገዳሙ ስትታወስ በትልቅነቷ ነው። አዲስ አበባ ካዛንቺስ አካባቢ ሚጢጢ አረቄ መሸጫ ከፍታ ምሽቱን ታደምቅ ነበር። ከትልቁም ከትንሹም ጋር ተግባቢ ሳቂታና ተጫዋች ናት ትልቅ ሰው። ታላቋ ይሏታል ሲያቀማጥሏት። ባለስልጣንና ባለሃብት እንዲሁም ባለዝና ትወዳለች። የጦር ሜዳ ጀግና ባለማእረግ ካገኘች ትልቅ ሰው ህልሟ እንደተሳካ ትቆጥረዋለች። ስመጥር ሰዎችን ወዳጅ ማድረግ የግሏ ነው። አሁን ላለችበት የሃብት ማማ ሰዎችን መረማመጃ በማድረግ ተገልግላባቸዋለች።  የሁሉ  ወዳጅ መሆን ትችልበታለች የምትባለው ወ/ሮ ትልቅ ሰው በአንድ ጊዜ የብልጽግናም የፋኖም ወዳጅ መሆን የምትችል ምትሃተኛ ነች ይሏታል። ወዳጅ መሆን ብቻም አይደለም መሃል ገብታ ማመሱንም ማማሰሉንም ትችልበታለች። በሁለት ተዋጊ ሃይሎች መካከል በግራም በቀኝም ያሉትን ምን ጎደለ ምን ልሙላላችሁ ማለቱን ታውቅበታለች። እሳት ነክሰው እሳት ጎርሰው ጣታቸውን በጠመንጃ ምላጭ ላይ የቀሰሩ ወንድማማቾች የሁለቱም የልብ ወዳጅ መሆን ለሁሉም የጎደለን መሙላት በወ/ሮ ትልቅ ሰው ካልሆነ በቀር በሌሎች አይታሰብም። አማጺውንም መንግስትንም የማስታጠቅ ልዩ ተስጥኦና  ጥበብ ያለው በእሷ እጅ ነው።  ብዙዎች ጠብመንጃ አንጋች ነጋዴ መሳይ ፖለቲከኛ ነች ይሏታል። ምክንያቱም በምትነዳው መኪና የጋቢና ወንበር ላይ እኔ ነኝ ያለ፣ የተወለወለ ፣ ውሃ ያልነካው ክልሽ አጋድማ በመሃል አዲሳባ የምትንቀሳቀስ ብቸኛ እንስት ብትኖት እሷ ነች።  ባለስልጣናት ከሃብቷ ጀርባ ቢኖሩም ደፍረው አይናገሯትም። ተገልግላባቸዋለችና የአገልግሎት ክፍያዋን እንዴት እንደምታወራርድ በደንብ ታውቅበታለች።  በጎጃም "ዝናብ" ማስዘነብ ታውቅበታለች ተብላ ትሞካሻለች። "ዝናብ" የሚለው ይሰመርበት። በዛም ምክንያት የዘውድ አክሊል የደፋች ናት ይባልላታል። ዘውዱ ደግሞ ከወርቅና አልማዝ የተዘጋጅ እጅግ ውድ ነው።  ባልጠጋ ናትና ከምርጦች መርጣ መጋባት ከልካይ የላትም።  ምንም እድሜ ቢገፋም መንታ ልጆችን ጽንሳ ከመውለድም አላገዳትም። እነሆ በአሜሪካ ቬርጂኒያ ሪችመንድ ከተማ ስትታረስ ቆይታ የፊታችን እሁድ ወደ አዲስ አበባ ትመለሳለች። በጎልማሳነት እድሜ መንታ ወላድ ናትና ለክብሯ ሪችትና መድፍ ሊተኮስ ፣ አበባ ተነስንሶ ቀይ ምንጣፍ ሊነጠፍ ኮሚቴ ተቋቁሞ ሽር ጉድ ማለት ከጀመረ ቀናት አልፈዋል። የሚገርመው ነገር በአንድ ጊዜ ሁለት ኮሚቴዎች መቋቋማቸው ነው። አንደኛው የአዲስ አበባው እንግዳ ተቀባይ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ በታላቁ የሃረሩ ቁልቢ ገብርኤል የሚዘጋጀው በሽብሸባና በቤተክርስቲያን ዝማሬ የሚታጀበው በሃገሪቷ ታሪክ ታይቶም ሆነ ተሰምቶ የማይታወቀው ደማቁ የህጻናት ክርስትናን ማስነሳት ስነስርዓት ነው። ይሄ ስነስርዓት የሚካሄደው ሐምሌ 19 ቀን በቁልቢ ገብርኤል እለት የሚካሄደው ሌሎች የቤተክርስቲያን የጸሎት ስርዓቶች ጎን ለጎን ነው ወይስ ሌሎች ፕሮግራሞች ታጥፈው የሚለው የምናየው ይሆናል።  የሆነው ሆኖ ሁለቱም ኮሚቴዎች በከባድ ውጥረት በስራ ላይ ናቸው የሃምሌው ዝናብ ሂደቱን የተሳካ እንዲሆን ይፈቅዳል ወይስ አይፈቅድም የሚለውን አብረን እናያለን። 

የአርጀንቲና እግር ኳስ ማኅበር FBI የማጭበርበር ወንጀል ምርመራ እየተደረገበት ነው የአርጀንቲና እግር ኳስ ማኅበር (AFA) እና የማኅበሩ ፕሬዚዳንት ክላውዲዮ ታፒያ በዩናይትድ ስቴትስ የፍትሕ ሚኒስቴር እና በኤፍ.ቢ.አይ (FBI) የመጀመሪያ ደረጃ የፋይናንስ ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል። ባለሥልጣናቱ ምርመራውን የጀመሩት በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ካለው የዓለም ዋንጫ ጋር በተያያዘ በአሜሪካ ባንኮች በኩል የተዘዋወረው በመቶዎች የሚቆጠር ሚሊዮን ዶላር ከሕገ-ወጥ ገንዘብ ማሸሽ ወይም ከባንክ ማጭበርበር ጋር የተያያዘ ሊሆን ይችላል በሚል ጥርጣሬ ነው። በዋናነት የአሜሪካ ፌደራል አቃቤ ህጎች ጉዳዩን እንደ ወንጀል እንዲመለከቱት ያደረጋቸው ሁለት ዋና ዋና አጠራጣሪ ነገሮች (ቀይ መብራቶች) በመገኘታቸው ነው፡- የጠፋው 57 ሚሊዮን ዶላር፦ መርማሪዎች ከጠቅላላው የገቢ ክምችት ውስጥ በግምት ከ42 ሚሊዮን እስከ 57 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ ገንዘብ ተቀንሶ በቀጥታ በፎሎሪዳ ወደሚገኙ የካርቶን (shell) ኩባንያዎች መተላለፉን ደርሰውበታል። እነዚህ ኩባንያዎች ምንም አይነት ሰራተኛ፣ የቢሮ ቦታ ወይም ህጋዊ የንግድ እንቅስቃሴ የሌላቸው ናቸው። ይህ የተዘወረው ገንዘብ ከፍተኛ መጠን ያለው ክፍል በአርጀንቲና ውስጥ ከመንግስት ማህበራዊ እገዛ (ዌልፌር) በሚያገኙ ሰዎች ስም ወደተከፈቱ የባንክ አካውንቶች መግባቱ ተደርሶበታል። በሚሊዮን የሚቆጠር የአለም አቀፍ እግር ኳስ ገቢ በማህበራዊ ረድኤት ተጠቃሚዎች የግል አካውንት ውስጥ የሚቀመጥበት ምንም አይነት ምክንያታዊ አመክንዮ የለም። እርስዎ ያነሱት ንፅፅር ዋናውን ችግር ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። ብሄራዊ ቡድኖች ለ50 ሚሊዮን ዶላሩ የአለም ዋንጫ ታላቅ ሽልማት በሚወዳደሩበት ወቅት፣ ከጀርባ የሚፈሰው ከፍተኛ የንግድ ጥሬ ገንዘብ ለምዝበራ በእጅጉ የተጋለጠ ነው። በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ በአሜሪካ ባንኮች በኩል እያሳለፉ፣ ከፍተኛ መጠን ያለውን ድርሻ ደግሞ ወደሌሉ የይስሙላ ኩባንያዎች ማስተላለፍ በትክክል የፌደራል ማጭበርበር (wire fraud) እና የገንዘብ ማጠብ (money laundering) ምርመራውን ያስነሳው ዋናው ምክንያት ነው። ይህ ምርመራ ማኅበሩ ዓለም አቀፍ የንግድ ስምምነቶቹን እንዴት እንዳዋቀረ ትኩረት ያደረገ ሲሆን፣ በተለይም የማኅበሩን የውጭ አገር ውሎች ያስተዳድር በነበረው ቱርፕሮድኤንተር (TourProdEnter LLC) በተባለው ኩባንያ እንቅስቃሴ ላይ ያተኩራል። መርማሪዎች በአሁኑ ወቅት በሲቲ ባንክ፣ ባንክ ኦፍ አሜሪካ እና ጄፒ ሞርጋን ባሉ ትልልቅ የፋይናንስ ተቋማት በኩል የተንቀሳቀሰውንና ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚገመተውን የገንዘብ ፍሰት በጥብቅ እየተከታተሉ ይገኛሉ። በሜዳ ላይ አርጀንቲና በዓለም ዋንጫው የ16ቱ ክበብ ማጣሪያ ግብፅን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት ባሸነፈችበት ወቅት፣ ከሜዳ ውጪ ያለው የሕግ ምርመራ በቪዲዮ ኮንፈረንስ አማካኝነት ከባለሀብቱ ጊልየremote ቶፎኒ ጋር ለሦስት ሰዓታት የቆየ የምስክርነት ቃል ፍለጋ ስብሰባ በማድረግ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ለተፈጠረው ሁኔታ ምላሽ የሰጡት በሰሜን አሜሪካ የአርጀንቲና እግር ኳስ ማኅበር ተወካይ ቶማስ ሬጋላዶ እና የወንጀል ጠበቃው ማሪያኖ ሊዛርዶ በሕግ ምርመራው ወቅት የንጽሕና ግምት መብት እንዲከበር ጠይቀዋል። ሬጋላዶ የምርመራ እርምጃዎች ብቻቸውን ጥፋተኝነትን እንደማያረጋግጡ የገለጹ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በዩናይትድ ስቴትስ በኩል በይፋ የተመሠረተ የወንጀል ክስ የለም። አርጀንቲና በዓለም ዋንጫው ሩብ ፍጻሜ ከስዊዘርላንድ ጋር ለምታደርገው ጨዋታ እየተዘጋጀች ባለችበት ወቅት ይህ ከሜዳ ውጪ ያለ ጉዳይ ለቡድኑ ትልቅ መነጋጋሪያ ሆኗል።

Repost from Natnael Mekonnen
ለፅንፈኛው ቡድን ሊደርስ የነበረ መሣሪያና ተተኳሽ በቁጥጥር ስር ውሏል። ለፅንፈኛው ቡድን ሊደርስ የነበረ መሣሪያና ተተኳሽ በጉባ ክፍለ ጦር ሠራዊት በቁጥጥር ስር ውሏል። ክፍለጦሩ በፅንፈኛው ቡድን
+2
ለፅንፈኛው ቡድን ሊደርስ የነበረ መሣሪያና ተተኳሽ በቁጥጥር ስር ውሏል። ለፅንፈኛው ቡድን ሊደርስ የነበረ መሣሪያና ተተኳሽ በጉባ ክፍለ ጦር ሠራዊት በቁጥጥር ስር ውሏል። ክፍለጦሩ በፅንፈኛው ቡድን ላይ አስፈላጊውን እርምጃም ወስዷል። ከሱዳን ተነሰቶ ወደ አዊ ዞን ጃዊ ወረዳ ልዩ ቦታው በለስ ወንዝ ተሻግሮ ለዘራፊው ፅፈንኛ ቡድን የተለያዬ መሳሪያና ተተኳሾችን ለማድረሰ ባሰበው ቡድን ላይ በቀጠናው የሚገኘው ሠራዊት የማያዳግም እርምጃ መውሰዱን የክፍለጦሩ ሬጅመንት አዛዥ ሻለቃ ገብረ ህይወት ሃይላይ ተናግረዋል። ተላላኪው ቡድን ለፅንፈኛው ሊያደርሰው የነበረ 08 ብሬን ፣ 15 ክላሸ ፣ 8 ሺህ 139 የብሬን ጥይት፣ 15 ሺህ 382 የክላሸ ጥይት እና 05 ሞተር ሳይክል በሠራዊቱ ቁጥጥር ስር መዋሉን እና በርካታ የፅንፈኛው ቡድኑ አባላት መመታታቸውን ሻለቃ አዛዡ ሻለቃ ገብረ ህይወት ሃይላይ መናገራቸዉን ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ ያገኘነዉ መረጃ ያመለክታል።

መረጃ‼️ የቀይ ባሕር አፋሮች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት፣ የዓለም መንግሥታት የኤርትራ መንግሥት ከተመድ የሰብዓዊ መብቶች ተቆጣጣሪ ልዩ ራፖርተር ጋር እንዲተባበርና ልዩ ራፖርተሩ ወደ ኤርትራ እንዲገቡ እንዲፈቅድ ተጽዕኖ እንዲያደርጉ ጠየቀ። ልዩ ራፖርተሩ በኤርትራ ዙሪያ ለተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ሰሞኑን ያቀረቡትን ሪፖርት እንደሚደግፍ የገለጠው ድርጅቱ፣ ምክር ቤቱ የልዩ ራፖርተሩን ተልዕኮ እንዲያጠናክርና የልዩ ራፖርተሩን የጊዜ ቆይታ እንዲያራዝም ጠይቋል። ድርጅቱ፣ አባል አገራት ኤርትራዊያን ስደተኞችን፣ ጋዜጠኞችንና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን ከኤርትራ መንግሥት የድንበር-ዘለል "ማስፈራሪያዎች" እና "ዛቻዎች" እንዲከላከሉ ጭምር ጥሪ አድርጓ3

👹 🤡 Bibi's new best friend: Israel welcomes Somaliland — and a Red Sea foothold Israeli Prime Minister Benjamin Netanyahu hasn't thought twice before welcoming Somaliland President Abdirahman Mohamed Abdullahi at his office in Jerusalem. There was the whole diplomatic theatre during the pomp-filled visit, with Bibi cynically arguing that "freedom and democracy are stronger than extremism, terrorism and chaos." 👉 Earlier this year, Israel appointed its first ambassador to Somaliland — Michael Lotem — following formal recognition of the breakaway African province in December 2025 and a visit by Israel's foreign minister to Hargeisa in January 2026. Somaliland declared independence from Somalia in 1991 — and remarkably, not a single country has recognized it since then. The embrace has deepened quickly. Since formal recognition late last year, Israel has established an intelligence presence in Somaliland, according to several officials including one from the Somaliland government and a senior Somali official who spoke to Drop Site. News reports also suggest that an Israeli military base is under discussion. Other factors behind Israel’s recognition of Somaliland: ♦️ A forward intelligence post to monitor Houthi missiles and drones ♦️ Naval & air deployment options near Yemen ♦️ A secure logistical hub for crisis resupply ♦️ Leverage against Egyptian, Saudi, and Turkish influence in the Red Sea ♦️ A springboard for possible operations against Iran-aligned forces Recognition for real estate — Israel's latest play in the Horn of Africa. 👍 Boost us | Chat | @geopolitics_prime

ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ማብሰር የምፈልገው ለልጆቻችን የሚተርፍ የሚያልፍ ትልቅ መሰረት እዚህ ቦታ እያስቀመጥን ነው።

‎ሰራዊቱ የማይወዛወዝ ምሰሶ በመሆን ሀገር የማሻገር ተልዕኮውን እየተወጣ ነው – ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መከላከያ ሰራዊቱ ‎የማይወዛወዝ ምሰሶ በመሆ
‎ሰራዊቱ የማይወዛወዝ ምሰሶ በመሆን ሀገር የማሻገር ተልዕኮውን እየተወጣ ነው – ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መከላከያ ሰራዊቱ ‎የማይወዛወዝ ምሰሶ በመሆን ሀገር የማሻገር ተልዕኮውን እየተወጣ ነው አሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ፡፡ ‎ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በማዕከላዊ ዕዝ መኮንኖች የግዳጅ አፈፃፀምና ቀጣይ አቅጣጫዎች መድረክ ላይ በበይነመረብ የማጠቃለያ መልዕክት አስተላልፈዋል። የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለመጠበቅ የተዘጋጀና የተሾመ ወታደራዊ አመራር ዓለም… https://www.fanamc.com/archives/316776

Repost from Addis Admass
ግራ ገባን እኮ ጎበዝ !? - ኧረ ፋታ ስጡን?! መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው:: አጀንዳ እየደራረበና እያፋጠነ በመስጠት የሚያወዛግበን !? የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው ወር አላስቆጠረም:: በዚህ
ግራ ገባን እኮ ጎበዝ !? - ኧረ ፋታ ስጡን?! መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው:: አጀንዳ እየደራረበና እያፋጠነ በመስጠት የሚያወዛግበን !? የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው ወር አላስቆጠረም:: በዚህ ምክንያት ጣሪያ የነካው የኑሮ ውድነት ናላውን ያዞረው ዜጋ ግራ በተጋባበት ሰዐት መንጃ ፍቃድ እንደ አዲስ ትፈተናላችሁ አለና ክፍያ ያሳሰበውን ምድረ አሽከርካሪ አንጫጫው:: ከኑሮ ውድነት ጋር በተያያዘ በጭንቀት የተሞላው ውክቢያ ሳይረግብ አስደንጋጭ የአዲስ ታርጋ ዋጋ ክፍያ አጀንዳ ተከተለ:: ምን ጉድ ነው !? ዜጋው በእንዲህ ያለ ውክቢያ ግራ ሲጋባ : መንግስት ለዜጎች አሳቢ መስሎ " የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን እኔ ነኝ የምወስነው" እያለን ነው:: ሀሳቡ ባልከፋ:: ግን እሱ በየጊዜው የሚጨምረው የነዳጅ ዋጋና እሱን ተከትሎ የሚግተለተለው የኑሮ ውድነት ቤት እያከራየ የሚተዳደረውን ዜጋ አይመለከተውም ይሆን ?! እንዲህ ማሰቡ ካልቀር ህዝቡም እንዲተሳሰብ እሱ የሚዘውረውን የጭማሪ ማርሽ ለምሳሌ በቤትና በይዞታ ላይ የሚጨመረውን የግብር ልክና መልክ ለምን አያየውም !? ( ልብ አድርጉ ገና የፕሮፐርቲ ታክስ ሊመጣ መሆኑም አይዘነጋም ):: ሌላው ቀርቶ እስከ ቅርብ ጊዜ የፈለከውን ይህል ጊዜ ቆመህ ለሰፈር ወጣቶች አስር በር ብቻ የምትከፍልበት ፓርኪንግ መንግስት ጣልቃ ሲገባበት በትንሹ 40 ብር ደርሷል:: አንድ ደቂቃ እንኳ ብታሳልፍ ደግሞ ተጨማሪ የምትከፍለው በመነሻው ዋጋ ልክ ነው:: መኪና መጠቀም የማይቻልበት ደረጃ እየተደረሰ መስሏል:: እንዲህ እንዲህ እያልን መካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ያለው ዜጋ የሚብከነከንበትን ብዙ ጉዳይ ማንሳት ይቻላል:: ግራ ገባን እኮ ጎበዝ !? እባካችሁ ፉታ ስጡን?! ( ጋዜጠኛና የህግ ባለሙያ ሳሙኤል ፍቅሬ)

ብልፅግና የድሮን ጥቃት ፈፀመብን - ህወሓት‼️ የብልፅግና መንግሥት በጀት፣ ነዳጅ፣ መድሃኒት፣ ገንዘብ በመዝጋት ተጨማሪ ጭካኔዎችን በመፈጸም ሊያሸንፋቸው ያልቻሉትን በድሮን ለማጥፋት ጥቃት እየፈፀመ
ብልፅግና የድሮን ጥቃት ፈፀመብን - ህወሓት‼️ የብልፅግና መንግሥት በጀት፣ ነዳጅ፣ መድሃኒት፣ ገንዘብ በመዝጋት ተጨማሪ ጭካኔዎችን በመፈጸም ሊያሸንፋቸው ያልቻሉትን በድሮን ለማጥፋት ጥቃት እየፈፀመ ነው ሲል ህወሓት ገለፀ። የፌደራል መንግስቱ በትግራይ ላይ ጦርነት እንደገና መጀመሩ አገዛዙ ያለ ጦርነት ሊተርፍ እንደማይችል በግልጽ ያረጋግጣልም ብሏል። ለትግራይ ህዝብ አድልዎ፣ በጀት መዝጋት፣ የድሮን ጥቃት፣ ወዘተ አይገባውም ነበር ያለ ሲሆን፤ የትግራይ ህዝብ የሰላም እና የትዕግስት ጥያቄ እንደ ፍርሃት ተቆጥሯል ብሏል። የትግራይ ህዝብ በክህደት ሊሸነፍ እንደማይችል መታወቅ አለበት ሲል አክሏል። በሽራሮ ታችኛው አዲያቦ ለሊት ላይ በተፈፀመው የድሮን ጥቃት በትግራይ ሰራዊት አባላት ላይ የሞት እና የአካል ጉዳት ደርሷል እንዲሁም በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን የክልሉ መንግሥት በትግርኛ ካስተላለፈው መግለጫ ተመልክተናል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23

Repost from Natnael Mekonnen
ድምጽ የመስጠት ሒደቱ እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ ተራዘመ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ የመስጠት ሒደት እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ ተ
ድምጽ የመስጠት ሒደቱ እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ ተራዘመ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ የመስጠት ሒደት እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ ተራዝሟል አለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፡፡ ምርጫ ቦርድ ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ÷ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከማለዳ 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሒደት ላይ እንደነበር ጠቅሷል፡፡ ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት ተመልክቶ ውሳኔ ማሳለፉን አመልክቷል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) መሠረት ቦርዱ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ብሎ ካመነ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ሊያራዝም እንደሚችል በግልጽ ይደነግጋል። በዚህ መሰረትም የድምጽ መስጫ ሒደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምጽ የመስጠት ሒደቱ እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ነው ቦርዱ ያስታወቀው፡፡ የተመዘገቡ መራጮች መርጠው የተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሒደቱን እንዲያከናውኑም ቦርዱ አሳስቧል፡፡

አፍሪካ ኅብረት ታዛቢ ቡድን መሪ የሆኑት የኬንያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የምርጫ ዝግጅትን ተዘዋውረው እየጎበኙ ነው
+5
አፍሪካ ኅብረት ታዛቢ ቡድን መሪ የሆኑት የኬንያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የምርጫ ዝግጅትን ተዘዋውረው እየጎበኙ ነው

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ:- 1. 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 871 መራጮች ተመዝግበዋል፣ 2.በአጠቃላይ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች ይወዳደራሉ፤ 3. 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲ እጩዎች እንዲሁም 4. 80 የግ
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ:- 1. 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 871 መራጮች ተመዝግበዋል፣ 2.በአጠቃላይ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች ይወዳደራሉ፤ 3. 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲ እጩዎች እንዲሁም 4. 80 የግል እጩዎች በምርጫው ይወዳደራሉ። 5. ፓርቲዎች በተደለደለላቸው የአየር ሰዓት 19 የክርክር መድረኮችን በአምስት ቋንቋዎች አካሂደዋል፤ 6. ተፎካካሪ ፓርቲዎች ከ250 ሺህ በላይ ተወካዮቻቸውን የምርጫውን ሂደት እንዲከታተሉ ይልካሉ፤ 7. ለታዛቢነት የአፍሪካ ሕብረት እና የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ተወካዮቻቸውን ልከዋል፤ 8. 59 አባላት ያሉት የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን በቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት አሁሩ ኬንያታ እየተመራ ሥራውን ይሰራል፤ 9. ኢጋድ 26 አባላት ያሉት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድንን ያሰማራል፤ 10. በሀገር ውስጥ የተደራጁ 55 ሲቪክ ማኅበራት ፈቃድ ወስደው ወደ ሥራ ገብተዋል፤ 55ቱ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች 1 ሺህ 562 የምርጫ ታዛቢዎችን አሰማርተዋል። 11. የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭትን በተመለከተ በአዲስ አበባ ለ33፣ በአፋር ለ32፣ በአማራ ለ130፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ለ22፣ በማዕካላዊ ኢትዮጵያ ለ35፣ በድሬዳዋ ለ48፣ በጋምቤላ ለ14፣ በሐረሪ ለ3፣ በኦሮሚያ ለ179፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ለ56፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ለ22 ክልሎች የምርጫ ቁሳቁስ ተሰራጭቷል።

አስገዳጁ የቤት ኪራይ ውል አዋጅ ሊያበቃ ነው፦ ምን ትላላችሁ? *የቤት ኪራይ ዋጋ ጉዳይ እንዴት አደረጋችሁ? *ለቤት ኪራይ የምትከፍሉት ተመጣጣኝ ነው ብላችሁ ታስባላችሁ? ቤት አከራዮች ቤት ካከራዩ በኋላ ለሁለት ዓመት የቤት ኪራይ እንዳይጨምሩ እና ያከራዩትንም ቤት እንዳያስለቅቁ ይከለክል የነበረው አዋጅ ተግባራዊነቱ ሊያበቃ ጥቂት ጊዜያት ቀርተውታል ። የአዋጁ ተግባራዊነት መጠናቀቅን ቤት ተከራዮች በስጋት ተውጠው ቤት አከራዮች ደግሞ ጓግተው ነው የሚጠብቁት ። ምን ይከሰት ይኾን? መጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቆ የነበረው የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ሊጠናቀቅ ጥቂት ሳምንታት ብቻ ነው የቀሩት ። አስገዳጁ የሁለት ዓመት የውል ዘመን እና የዋጋ ቁጥጥር ማዕቀፍ በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ እና በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በመኖሪያ ቤት ኪራይ ላይ መጠነኛ መረጋጋትን ፈጥሮ መቆየቱ ይነገርለታል ። የአዋጁ ተግባራዊነት ሊያበቃ ጥቂት ሳምንታት ብቻ ቀርቷል ። ስለ አስገዳጁ የቤት ኪራይ አዋጅ እና ተግባራዊነቱ ሊያከትም ስለመኾኑ ምን አስተያየት አላችሁ?  ተወያዩበት

ነዳጅና ጋዝ ለአለም ገበያ ኢትዮጵያ የነዳጅ እና የጋዝ ምርቶቿን በጅቡቲ በኩል ለአለም ገበያ ለማቅረብ እቅድ አውጥታለች ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጋዝ እና ድፍድፍ ነዳጅን በጅቡቲ በኩል ለአለም ገበያ የመላ
ነዳጅና ጋዝ ለአለም ገበያ ኢትዮጵያ የነዳጅ እና የጋዝ ምርቶቿን በጅቡቲ በኩል ለአለም ገበያ ለማቅረብ እቅድ አውጥታለች ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጋዝ እና ድፍድፍ ነዳጅን በጅቡቲ በኩል ለአለም ገበያ የመላክ እቅዷን ከጅቡቲ ጋር የተጋራች ሲሆን የተጣራ የነዳጅ ምርቶችንም ከጅቡቲ በቧንቧ ታስገባለች። ሃሳቡን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ብሩክ ታዬ ለጅቡቲ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ አቅርበዋል። የጅቡቲ የዜና ወኪል (ADI) እንደዘገበው ፕሬዚዳንቱ እቅዱን ተቀብለዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ያቀረበው ሃሳብ ሁለት ምዕራፎችን ያካተተ ነው። የመጀመሪያው ምዕራፍ 113 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የተጣራ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ሲሆን ከጅቡቲ ወደብ ተነስቶ መጨረሻው በኢትዮጵያ ጅቡቲ ድንበር ላይ በሚገኘው ደወሌ ላይ ነው። ሁለተኛው ምዕራፍ 760 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የጋዝ እና ድፍድፍ ነዳጅ መስመር ዝርጋታ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ውስጥ ካለው የኦጋዴን ክልል ጀምሮ እስከ ጅቡቲ ወደብ ድረስ ይዘልቃል። ለሁለቱም የቧንቧ መስመር ዝርጋታ እና የነዳጅ ማጣሪያዎች አጠቃላይ ወጪ ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ ነው። የፕሮጀክቶቹ ስኬት በኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ እና በዳንጎቴ ኢንቨስትመንት ግሩፕ መካከል ያለውን ትብብር ወደ ላቀ እና ስትራቴጂካዊ ደረጃ እንደሚያሳድገው ይጠበቃል። ከ7 ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የተገኘውን ድፍድፍ ነዳጅ ወደ ውጭ ለመላክ ቱቦ እየተቀበረ መሆኑን መዘገቡ የሚታወስ ነው። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23