ch
Feedback
Skyline media

Skyline media

前往频道在 Telegram

📈 Telegram 频道 Skyline media 的分析概览

频道 Skyline media (@skyline7777) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 26 844 名订阅者,在 新闻与媒体 类别中位列第 8 978,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 245

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 26 844 名订阅者。

根据 28 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -679,过去 24 小时变化为 -25,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 4.16%。内容发布后 24 小时内通常能获得 N/A% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 1 117 次浏览,首日通常累积 0 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 3

📝 描述与内容策略

尚未提供频道描述。

凭借高频更新(最新数据采集于 29 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 新闻与媒体 类别中的关键影响点。

26 844
订阅者
-2524 小时
-1247
-67930
帖子存档
Repost from Natnael Mekonnen
ለፅንፈኛው ቡድን ሊደርስ የነበረ መሣሪያና ተተኳሽ በቁጥጥር ስር ውሏል። ለፅንፈኛው ቡድን ሊደርስ የነበረ መሣሪያና ተተኳሽ በጉባ ክፍለ ጦር ሠራዊት በቁጥጥር ስር ውሏል። ክፍለጦሩ በፅንፈኛው ቡድን
+2
ለፅንፈኛው ቡድን ሊደርስ የነበረ መሣሪያና ተተኳሽ በቁጥጥር ስር ውሏል። ለፅንፈኛው ቡድን ሊደርስ የነበረ መሣሪያና ተተኳሽ በጉባ ክፍለ ጦር ሠራዊት በቁጥጥር ስር ውሏል። ክፍለጦሩ በፅንፈኛው ቡድን ላይ አስፈላጊውን እርምጃም ወስዷል። ከሱዳን ተነሰቶ ወደ አዊ ዞን ጃዊ ወረዳ ልዩ ቦታው በለስ ወንዝ ተሻግሮ ለዘራፊው ፅፈንኛ ቡድን የተለያዬ መሳሪያና ተተኳሾችን ለማድረሰ ባሰበው ቡድን ላይ በቀጠናው የሚገኘው ሠራዊት የማያዳግም እርምጃ መውሰዱን የክፍለጦሩ ሬጅመንት አዛዥ ሻለቃ ገብረ ህይወት ሃይላይ ተናግረዋል። ተላላኪው ቡድን ለፅንፈኛው ሊያደርሰው የነበረ 08 ብሬን ፣ 15 ክላሸ ፣ 8 ሺህ 139 የብሬን ጥይት፣ 15 ሺህ 382 የክላሸ ጥይት እና 05 ሞተር ሳይክል በሠራዊቱ ቁጥጥር ስር መዋሉን እና በርካታ የፅንፈኛው ቡድኑ አባላት መመታታቸውን ሻለቃ አዛዡ ሻለቃ ገብረ ህይወት ሃይላይ መናገራቸዉን ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ ያገኘነዉ መረጃ ያመለክታል።

መረጃ‼️ የቀይ ባሕር አፋሮች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት፣ የዓለም መንግሥታት የኤርትራ መንግሥት ከተመድ የሰብዓዊ መብቶች ተቆጣጣሪ ልዩ ራፖርተር ጋር እንዲተባበርና ልዩ ራፖርተሩ ወደ ኤርትራ እንዲገቡ እንዲፈቅድ ተጽዕኖ እንዲያደርጉ ጠየቀ። ልዩ ራፖርተሩ በኤርትራ ዙሪያ ለተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ሰሞኑን ያቀረቡትን ሪፖርት እንደሚደግፍ የገለጠው ድርጅቱ፣ ምክር ቤቱ የልዩ ራፖርተሩን ተልዕኮ እንዲያጠናክርና የልዩ ራፖርተሩን የጊዜ ቆይታ እንዲያራዝም ጠይቋል። ድርጅቱ፣ አባል አገራት ኤርትራዊያን ስደተኞችን፣ ጋዜጠኞችንና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን ከኤርትራ መንግሥት የድንበር-ዘለል "ማስፈራሪያዎች" እና "ዛቻዎች" እንዲከላከሉ ጭምር ጥሪ አድርጓ3

👹 🤡 Bibi's new best friend: Israel welcomes Somaliland — and a Red Sea foothold Israeli Prime Minister Benjamin Netanyahu hasn't thought twice before welcoming Somaliland President Abdirahman Mohamed Abdullahi at his office in Jerusalem. There was the whole diplomatic theatre during the pomp-filled visit, with Bibi cynically arguing that "freedom and democracy are stronger than extremism, terrorism and chaos." 👉 Earlier this year, Israel appointed its first ambassador to Somaliland — Michael Lotem — following formal recognition of the breakaway African province in December 2025 and a visit by Israel's foreign minister to Hargeisa in January 2026. Somaliland declared independence from Somalia in 1991 — and remarkably, not a single country has recognized it since then. The embrace has deepened quickly. Since formal recognition late last year, Israel has established an intelligence presence in Somaliland, according to several officials including one from the Somaliland government and a senior Somali official who spoke to Drop Site. News reports also suggest that an Israeli military base is under discussion. Other factors behind Israel’s recognition of Somaliland: ♦️ A forward intelligence post to monitor Houthi missiles and drones ♦️ Naval & air deployment options near Yemen ♦️ A secure logistical hub for crisis resupply ♦️ Leverage against Egyptian, Saudi, and Turkish influence in the Red Sea ♦️ A springboard for possible operations against Iran-aligned forces Recognition for real estate — Israel's latest play in the Horn of Africa. 👍 Boost us | Chat | @geopolitics_prime

ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ማብሰር የምፈልገው ለልጆቻችን የሚተርፍ የሚያልፍ ትልቅ መሰረት እዚህ ቦታ እያስቀመጥን ነው።

‎ሰራዊቱ የማይወዛወዝ ምሰሶ በመሆን ሀገር የማሻገር ተልዕኮውን እየተወጣ ነው – ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መከላከያ ሰራዊቱ ‎የማይወዛወዝ ምሰሶ በመሆ
‎ሰራዊቱ የማይወዛወዝ ምሰሶ በመሆን ሀገር የማሻገር ተልዕኮውን እየተወጣ ነው – ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መከላከያ ሰራዊቱ ‎የማይወዛወዝ ምሰሶ በመሆን ሀገር የማሻገር ተልዕኮውን እየተወጣ ነው አሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ፡፡ ‎ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በማዕከላዊ ዕዝ መኮንኖች የግዳጅ አፈፃፀምና ቀጣይ አቅጣጫዎች መድረክ ላይ በበይነመረብ የማጠቃለያ መልዕክት አስተላልፈዋል። የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለመጠበቅ የተዘጋጀና የተሾመ ወታደራዊ አመራር ዓለም… https://www.fanamc.com/archives/316776

Repost from Addis Admass
ግራ ገባን እኮ ጎበዝ !? - ኧረ ፋታ ስጡን?! መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው:: አጀንዳ እየደራረበና እያፋጠነ በመስጠት የሚያወዛግበን !? የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው ወር አላስቆጠረም:: በዚህ
ግራ ገባን እኮ ጎበዝ !? - ኧረ ፋታ ስጡን?! መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው:: አጀንዳ እየደራረበና እያፋጠነ በመስጠት የሚያወዛግበን !? የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው ወር አላስቆጠረም:: በዚህ ምክንያት ጣሪያ የነካው የኑሮ ውድነት ናላውን ያዞረው ዜጋ ግራ በተጋባበት ሰዐት መንጃ ፍቃድ እንደ አዲስ ትፈተናላችሁ አለና ክፍያ ያሳሰበውን ምድረ አሽከርካሪ አንጫጫው:: ከኑሮ ውድነት ጋር በተያያዘ በጭንቀት የተሞላው ውክቢያ ሳይረግብ አስደንጋጭ የአዲስ ታርጋ ዋጋ ክፍያ አጀንዳ ተከተለ:: ምን ጉድ ነው !? ዜጋው በእንዲህ ያለ ውክቢያ ግራ ሲጋባ : መንግስት ለዜጎች አሳቢ መስሎ " የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን እኔ ነኝ የምወስነው" እያለን ነው:: ሀሳቡ ባልከፋ:: ግን እሱ በየጊዜው የሚጨምረው የነዳጅ ዋጋና እሱን ተከትሎ የሚግተለተለው የኑሮ ውድነት ቤት እያከራየ የሚተዳደረውን ዜጋ አይመለከተውም ይሆን ?! እንዲህ ማሰቡ ካልቀር ህዝቡም እንዲተሳሰብ እሱ የሚዘውረውን የጭማሪ ማርሽ ለምሳሌ በቤትና በይዞታ ላይ የሚጨመረውን የግብር ልክና መልክ ለምን አያየውም !? ( ልብ አድርጉ ገና የፕሮፐርቲ ታክስ ሊመጣ መሆኑም አይዘነጋም ):: ሌላው ቀርቶ እስከ ቅርብ ጊዜ የፈለከውን ይህል ጊዜ ቆመህ ለሰፈር ወጣቶች አስር በር ብቻ የምትከፍልበት ፓርኪንግ መንግስት ጣልቃ ሲገባበት በትንሹ 40 ብር ደርሷል:: አንድ ደቂቃ እንኳ ብታሳልፍ ደግሞ ተጨማሪ የምትከፍለው በመነሻው ዋጋ ልክ ነው:: መኪና መጠቀም የማይቻልበት ደረጃ እየተደረሰ መስሏል:: እንዲህ እንዲህ እያልን መካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ያለው ዜጋ የሚብከነከንበትን ብዙ ጉዳይ ማንሳት ይቻላል:: ግራ ገባን እኮ ጎበዝ !? እባካችሁ ፉታ ስጡን?! ( ጋዜጠኛና የህግ ባለሙያ ሳሙኤል ፍቅሬ)

ብልፅግና የድሮን ጥቃት ፈፀመብን - ህወሓት‼️ የብልፅግና መንግሥት በጀት፣ ነዳጅ፣ መድሃኒት፣ ገንዘብ በመዝጋት ተጨማሪ ጭካኔዎችን በመፈጸም ሊያሸንፋቸው ያልቻሉትን በድሮን ለማጥፋት ጥቃት እየፈፀመ
ብልፅግና የድሮን ጥቃት ፈፀመብን - ህወሓት‼️ የብልፅግና መንግሥት በጀት፣ ነዳጅ፣ መድሃኒት፣ ገንዘብ በመዝጋት ተጨማሪ ጭካኔዎችን በመፈጸም ሊያሸንፋቸው ያልቻሉትን በድሮን ለማጥፋት ጥቃት እየፈፀመ ነው ሲል ህወሓት ገለፀ። የፌደራል መንግስቱ በትግራይ ላይ ጦርነት እንደገና መጀመሩ አገዛዙ ያለ ጦርነት ሊተርፍ እንደማይችል በግልጽ ያረጋግጣልም ብሏል። ለትግራይ ህዝብ አድልዎ፣ በጀት መዝጋት፣ የድሮን ጥቃት፣ ወዘተ አይገባውም ነበር ያለ ሲሆን፤ የትግራይ ህዝብ የሰላም እና የትዕግስት ጥያቄ እንደ ፍርሃት ተቆጥሯል ብሏል። የትግራይ ህዝብ በክህደት ሊሸነፍ እንደማይችል መታወቅ አለበት ሲል አክሏል። በሽራሮ ታችኛው አዲያቦ ለሊት ላይ በተፈፀመው የድሮን ጥቃት በትግራይ ሰራዊት አባላት ላይ የሞት እና የአካል ጉዳት ደርሷል እንዲሁም በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን የክልሉ መንግሥት በትግርኛ ካስተላለፈው መግለጫ ተመልክተናል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23

Repost from Natnael Mekonnen
ድምጽ የመስጠት ሒደቱ እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ ተራዘመ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ የመስጠት ሒደት እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ ተ
ድምጽ የመስጠት ሒደቱ እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ ተራዘመ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ የመስጠት ሒደት እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ ተራዝሟል አለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፡፡ ምርጫ ቦርድ ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ÷ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከማለዳ 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሒደት ላይ እንደነበር ጠቅሷል፡፡ ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት ተመልክቶ ውሳኔ ማሳለፉን አመልክቷል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) መሠረት ቦርዱ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ብሎ ካመነ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ሊያራዝም እንደሚችል በግልጽ ይደነግጋል። በዚህ መሰረትም የድምጽ መስጫ ሒደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምጽ የመስጠት ሒደቱ እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ነው ቦርዱ ያስታወቀው፡፡ የተመዘገቡ መራጮች መርጠው የተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሒደቱን እንዲያከናውኑም ቦርዱ አሳስቧል፡፡

አፍሪካ ኅብረት ታዛቢ ቡድን መሪ የሆኑት የኬንያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የምርጫ ዝግጅትን ተዘዋውረው እየጎበኙ ነው
+5
አፍሪካ ኅብረት ታዛቢ ቡድን መሪ የሆኑት የኬንያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የምርጫ ዝግጅትን ተዘዋውረው እየጎበኙ ነው

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ:- 1. 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 871 መራጮች ተመዝግበዋል፣ 2.በአጠቃላይ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች ይወዳደራሉ፤ 3. 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲ እጩዎች እንዲሁም 4. 80 የግ
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ:- 1. 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 871 መራጮች ተመዝግበዋል፣ 2.በአጠቃላይ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች ይወዳደራሉ፤ 3. 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲ እጩዎች እንዲሁም 4. 80 የግል እጩዎች በምርጫው ይወዳደራሉ። 5. ፓርቲዎች በተደለደለላቸው የአየር ሰዓት 19 የክርክር መድረኮችን በአምስት ቋንቋዎች አካሂደዋል፤ 6. ተፎካካሪ ፓርቲዎች ከ250 ሺህ በላይ ተወካዮቻቸውን የምርጫውን ሂደት እንዲከታተሉ ይልካሉ፤ 7. ለታዛቢነት የአፍሪካ ሕብረት እና የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ተወካዮቻቸውን ልከዋል፤ 8. 59 አባላት ያሉት የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን በቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት አሁሩ ኬንያታ እየተመራ ሥራውን ይሰራል፤ 9. ኢጋድ 26 አባላት ያሉት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድንን ያሰማራል፤ 10. በሀገር ውስጥ የተደራጁ 55 ሲቪክ ማኅበራት ፈቃድ ወስደው ወደ ሥራ ገብተዋል፤ 55ቱ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች 1 ሺህ 562 የምርጫ ታዛቢዎችን አሰማርተዋል። 11. የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭትን በተመለከተ በአዲስ አበባ ለ33፣ በአፋር ለ32፣ በአማራ ለ130፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ለ22፣ በማዕካላዊ ኢትዮጵያ ለ35፣ በድሬዳዋ ለ48፣ በጋምቤላ ለ14፣ በሐረሪ ለ3፣ በኦሮሚያ ለ179፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ለ56፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ለ22 ክልሎች የምርጫ ቁሳቁስ ተሰራጭቷል።

አስገዳጁ የቤት ኪራይ ውል አዋጅ ሊያበቃ ነው፦ ምን ትላላችሁ? *የቤት ኪራይ ዋጋ ጉዳይ እንዴት አደረጋችሁ? *ለቤት ኪራይ የምትከፍሉት ተመጣጣኝ ነው ብላችሁ ታስባላችሁ? ቤት አከራዮች ቤት ካከራዩ በኋላ ለሁለት ዓመት የቤት ኪራይ እንዳይጨምሩ እና ያከራዩትንም ቤት እንዳያስለቅቁ ይከለክል የነበረው አዋጅ ተግባራዊነቱ ሊያበቃ ጥቂት ጊዜያት ቀርተውታል ። የአዋጁ ተግባራዊነት መጠናቀቅን ቤት ተከራዮች በስጋት ተውጠው ቤት አከራዮች ደግሞ ጓግተው ነው የሚጠብቁት ። ምን ይከሰት ይኾን? መጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቆ የነበረው የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ሊጠናቀቅ ጥቂት ሳምንታት ብቻ ነው የቀሩት ። አስገዳጁ የሁለት ዓመት የውል ዘመን እና የዋጋ ቁጥጥር ማዕቀፍ በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ እና በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በመኖሪያ ቤት ኪራይ ላይ መጠነኛ መረጋጋትን ፈጥሮ መቆየቱ ይነገርለታል ። የአዋጁ ተግባራዊነት ሊያበቃ ጥቂት ሳምንታት ብቻ ቀርቷል ። ስለ አስገዳጁ የቤት ኪራይ አዋጅ እና ተግባራዊነቱ ሊያከትም ስለመኾኑ ምን አስተያየት አላችሁ?  ተወያዩበት

ነዳጅና ጋዝ ለአለም ገበያ ኢትዮጵያ የነዳጅ እና የጋዝ ምርቶቿን በጅቡቲ በኩል ለአለም ገበያ ለማቅረብ እቅድ አውጥታለች ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጋዝ እና ድፍድፍ ነዳጅን በጅቡቲ በኩል ለአለም ገበያ የመላ
ነዳጅና ጋዝ ለአለም ገበያ ኢትዮጵያ የነዳጅ እና የጋዝ ምርቶቿን በጅቡቲ በኩል ለአለም ገበያ ለማቅረብ እቅድ አውጥታለች ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጋዝ እና ድፍድፍ ነዳጅን በጅቡቲ በኩል ለአለም ገበያ የመላክ እቅዷን ከጅቡቲ ጋር የተጋራች ሲሆን የተጣራ የነዳጅ ምርቶችንም ከጅቡቲ በቧንቧ ታስገባለች። ሃሳቡን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ብሩክ ታዬ ለጅቡቲ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ አቅርበዋል። የጅቡቲ የዜና ወኪል (ADI) እንደዘገበው ፕሬዚዳንቱ እቅዱን ተቀብለዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ያቀረበው ሃሳብ ሁለት ምዕራፎችን ያካተተ ነው። የመጀመሪያው ምዕራፍ 113 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የተጣራ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ሲሆን ከጅቡቲ ወደብ ተነስቶ መጨረሻው በኢትዮጵያ ጅቡቲ ድንበር ላይ በሚገኘው ደወሌ ላይ ነው። ሁለተኛው ምዕራፍ 760 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የጋዝ እና ድፍድፍ ነዳጅ መስመር ዝርጋታ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ውስጥ ካለው የኦጋዴን ክልል ጀምሮ እስከ ጅቡቲ ወደብ ድረስ ይዘልቃል። ለሁለቱም የቧንቧ መስመር ዝርጋታ እና የነዳጅ ማጣሪያዎች አጠቃላይ ወጪ ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ ነው። የፕሮጀክቶቹ ስኬት በኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ እና በዳንጎቴ ኢንቨስትመንት ግሩፕ መካከል ያለውን ትብብር ወደ ላቀ እና ስትራቴጂካዊ ደረጃ እንደሚያሳድገው ይጠበቃል። ከ7 ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የተገኘውን ድፍድፍ ነዳጅ ወደ ውጭ ለመላክ ቱቦ እየተቀበረ መሆኑን መዘገቡ የሚታወስ ነው። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23

የአስመራው ቡድንና የህወሓት አንጃ እኩል ተጠያቂነት ይጠብቃቸዋል። የሻአቢያና ህወሓት በኢትዮጵያ ያለውን ሰላምና ፈጣን ልማት በማደናቀፍ ሀገሪቱን ለመበተን እያደረጉት ላለው አፍራሽ እንቅስቃሴ እኩል ተጠያቂነት እንደሚጠብቃቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። በሚኒስቴሩ የዳያስፖራ አገልግሎት ኃላፊ አምባሳደር ፍጹም አረጋ በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ባደረጉት ውይይት እንደገለጹት ሻአቢያና ህወሓት በጅምር የቀረውን ሃገር የማፍረስ ሴራ ለማስቀጠል ጥምረት ፈጥረዋል። የአስመራውና የህወሃት አንጃ ቡድኖች አላማው በምርጫ ሰበብ ሁከትና ግርግር በመፍጠር የተጀመረውን ፈጣን ልማትና እድገት በማስተጓጎል ወደ ለየለት ጦርነት እንድንገባ ነው ያሉት አምባሳደሩ፣ ለዚህም ጥምረት በመፍጠር ዝግጅት ሲያደርጉ መቆየታቸውን አስረድተዋል ። የቡድኖቹ ትንኮሳና ጠብ አጫሪነት ድርጊቶች ወደ ጦርነት ለመግባት ከበቂ በላይ ምክንያት ቢሆኑም መንግሥት በአርቆ አስተዋይነት ያሉት ልዩነቶች እና አለመግባባቶች በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኙ በማድረግ በልማት ሥራው ላይ ማተኮሩን አስታውቀዋል። ሁለቱም አካላት በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ቡድኖችን በማሰልጠንና በማስታጠቅ ተጠምደው እንደሚገኙ ገልጸው ከድርጊታቸው የማይቆጠቡ ከሆነ እኩል ተጠያቂነት እንደሚጠብቃቸው አስጠንቅቀዋል። _ የዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው የህወሓት አንጃ ስምምነቱን ጥሱ ህጋዊ አስተዳደር ለማፍረስ እያሴረ መሆኑን ጠቁመው በፌዴራል መንግስት በኩል የፕሪቶሪያውን የግጭት የማቆም ስምምነት አክብረው የመቆየት ፍላጎት አስረድተዋል ። የህወሓት አንጃ ቡድን እራሱ ግጭት እየጀመረ ተጠቂ መስሎ የመታየት ልማድ ያለው በመሆኑ በተለይ ዳያስፖራዎች ጉዳዩን በንቃት እንዲከታተሉ አሳስበዋል። የአስመራውም ሆኑ የመቀሌውን እንቅስቃሴ መንግሥት በንቃት እንዲከታተልና አስፈላጊ የሆነውን እርምጃ በጊዜ እንዲወስድ ተሳታፊዎቹ ጠይቀዋል። በአንተነህ አብርሃም

ኢትዮጵያ እና አሜሪካ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ቋሚ የሁለትዮሽ ምክክር ማዕቀፍ ስምምነት ተፈራረሙ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ እና አሜሪካ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ቋሚ የሁለትዮሽ የምክክር ማዕቀፍ ስምምነት በዋሽንግተን ዲሲ ተፈራርመዋል። ስምምነቱን ከኢትዮጵያ ወገን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) እና ከአሜሪካ ወገን በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ አሊሰን ሁከር ፈርመዋል። በስምምነቱ ኢትዮጵያና አሜሪካ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ይበልጥ የሚያጠናክሩ የጋራ ትግበራ የሚሹ የትብብር አድማሶችን በማስፋት በሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት ተስማምተዋል። የተፈረመው የሁለትዮሽ መዋቅራዊ ምክክር በየዓመቱ አንዴ አዲስ አበባ ሌላ ጊዜ ዋሽንግተን የሚካሄድ ሲሆን÷ የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ስብሰባውን በጋራ የሚመሩት ይሆናል። ኢትዮጵያ እና አሜሪካ የሁለትዮሽ መዋቅራዊ ምክክር ሦስት ምሰሶዎችን ያካተተ እንዲሆን ተስማምተዋል። አንደኛው የኢኮኖሚ ብልጽግናን፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ሲሆን÷ በዚህ ክፍል የሁለትዮሽ ኢኮኖሚያዊ እና የንግድ ትስስር የበለጠ ማጠናከር እና ኢንቨስትመንት እና ንግድን ለማስፋት እንደሚሰራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል። ሁለተኛው የመከላከያ እና ጸጥታ ትብብርን እንደሚመለከትና በዚህም የጸጥታ ጉዳይ ትብብርን ማጠናከር እና በጋራ የደኅንነት ጉዳዮች ዙሪያ ተሳትፎን ማጠናከርን እንደሚያካትት ተገልጿል። የመጨረሻውን እና ሦስተኛው ምሰሶ ቀጣናዊ ሰላም እና መረጋጋትን የተመለከተ ሲሆን÷ በዚህ ክፍል የጋራ ጥቅምን እንዲሁም ቀጣናዊ ሰላምንና ደኅንነትን የሚያስጠብቁ አካሄዶችን በመፈተሽ እና በትብብር መሥራትን ያረጋግጣልም ነው የተባለው። ይህ ቋሚ የሁለትዮሽ ምክክር ማዕቀፍ ስምምነት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ዘላቂ በሆነ መንገድ የሚያስቀጥል እና የሚያጠናክር እንደሆነ ሚኒስቴሩ አብራርቷል። በተያያዘ መረጃ የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ከኢትዮጵያ አቻቸው ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል። በውይይታቸውም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የጸጥታ አጋርነት ለማስፋት እና የንግድ ዕድሎችን ለማሳደግ መምከራቸውን አመልክተዋል።

photo content

የፋይዳ ስልክ ለመቀየር‼️👇 በፋይዳ ምዝገባ ወቅት የሰጡት ስልክ ቁጥር ስህተት ነበረው? ወይስ ከምዝገባ በኃላ ስልክ ቁጥር ቀይረዋል? እንዴት ማስተካከል እችላለው ብለው እያሰቡ ነው? 1. ለፋይዳ
የፋይዳ ስልክ ለመቀየር‼️👇 በፋይዳ ምዝገባ ወቅት የሰጡት ስልክ ቁጥር ስህተት ነበረው? ወይስ ከምዝገባ በኃላ ስልክ ቁጥር ቀይረዋል? እንዴት ማስተካከል እችላለው ብለው እያሰቡ ነው? 1. ለፋይዳ ሲመዘገቡ በሌላ ሰው ስልክ ቁጥር ተመዝገበው ከነበረ እና አሁን ወደ ራስዎ ስልክ ቁጥር ለመቀየር ከፈለጉ ድረገፅ https://id.et/update ላይ በመግባት በአካል መሄድ ሳያስፈልግዎ መቀየር ይችላሉ። (ያስተውሉ፡ በዚህ ሂደት ወደ ነባሩ ስልክ የአንድ ጊዜ የይለፍ ቃል ወይም OTP ስለሚላክ ስልኩ በእጅዎ ሊሆን ይገባል) 2.  እንዲሁም በምዝገባ ወቅት የራስዎ ስልክ ቁጥር ሲሞላ የቁጥር ስህተት ካጋጠመ https://id.et/updatecenters ላይ በአቅራቢያ በሚያገኟቸው የመረጃ ማስተካከያ ጣቢያዎች በአካል በመሄድ መቀየር ይችላሉ። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23

😎 ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት በፈረንጆቹ 2026 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ9.2 በመቶ በማደግ ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት ቀዳሚውን ስፍራ እንደሚይዝ ቅድመ ትንበያውን አስቀምጧል። 🤩 የኢትዮጵያ ዕድገት በአፍሪካ ትልቅ ኢኮኖሚ አላቸው ከሚባሉት ኡጋንዳ (7.5 %)፣ ሩዋንዳ (7.2 %)፣ ኬንያ (4.5%)፣ ናይጄሪያ (4.1%) እና ደቡብ አፍሪክ (1.0%) እንደሚበልጥ ተገልጿል። የመንግሥት የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎች ለአዎንታዊ ትንበያው ትልቅ አስተዋፅኦ ማድረጋቸው ተጠቁሟል።

ዳስ ጣል /አንሳዉ/! አዲስ አበባ አዶ ሸገር የሁሉ አይደል ሞላዉ ሀገሩ በፍቅር ጠርተን ከዳር እስከዳር መሐል ገቡና አቆሙን ከዳር ። ባቆዩት ሀገር ጀግኖች በአንድነት እንዴት ይገፋል ኢትዮጵያዊነት
ዳስ ጣል /አንሳዉ/! አዲስ አበባ አዶ ሸገር የሁሉ አይደል ሞላዉ ሀገሩ በፍቅር ጠርተን ከዳር እስከዳር መሐል ገቡና አቆሙን ከዳር ። ባቆዩት ሀገር ጀግኖች በአንድነት እንዴት ይገፋል ኢትዮጵያዊነት ። ለካ እንዲህ ነዉ ማለቅ እህ እያሉ ነዶ ሀገር የሞተበት የት ያለቅሳል ሂዶ ። ባሳደገኝ ቀዬ ባደኩበት መንደር ባይተዋር ሰዉ ሁኜ እንደሌለዉ ሀገር ያቆምኳትን ሀገር ተፈትኜ በእሳት እንዴት አቀርቅሬ ባንዴራዬን ላንሳት ። አባይ ለዘዴዉ ባፍ ይቀድማል አምኖ መከዳት እንዴት ያማል ወርቅ ያበረደ ደርሶት አለት እንዴት ይችላል ዝም ማለት ከነገ ዛሬ ይሻል ባልኩኝ የራሴን እንባ ተነጠኩኝ ። የትኛው ዘፈን ተመቻችሁ? የአማራ ፋኖ የግንባር ወቅታዊ ፈጣንና ትኩስ መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ይወዳጁ 👇 https://t.me/fanoiswinnerlogo21