Hawassa University
📈 تحلیل کانال تلگرام Hawassa University
کانال Hawassa University (@hucommunicationsoffice) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 34 034 مشترک است و جایگاه 5 608 را در دسته آموزش و رتبه 988 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 34 034 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 13 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 320 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 18 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 13.32% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 8.77% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 4 535 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 2 987 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“One of the top ranking first generation Universities in Ethiopia.”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 14 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 14 ژوئن | 0 | |||
| 13 ژوئن | +20 | |||
| 12 ژوئن | +47 | |||
| 11 ژوئن | +209 | |||
| 10 ژوئن | +125 | |||
| 09 ژوئن | +201 | |||
| 08 ژوئن | +7 | |||
| 07 ژوئن | +12 | |||
| 06 ژوئن | 0 | |||
| 05 ژوئن | 0 | |||
| 04 ژوئن | +7 | |||
| 03 ژوئن | +21 | |||
| 02 ژوئن | 0 | |||
| 01 ژوئن | 0 |
| 2 | ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ወጪ የተሰሩ ፕሮጀክቶችን አስመረቀ::
*//*
ሰኔ 6/2018 ዓ/ም
የሲዳማ ብ/ክ/መ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ እና የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ማስፋፊያ በ2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ወጪ የተሰሩ 6 ፕሮጀክቶችን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል::
ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉት ፕሮጀክቶች ልዩ የቀዶ ሕክምናና የወሊድ ፅኑ ህሙማን ክፍል፣ የክሊኒካል ሙከራ ማዕከል (Clinical Trial Unit)፣ የሕፃናት ቀዶ ሕክምና የልህቀት ማዕከል፣ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የጡት ወተት ባንክ፣ የኦክሲጅን ማምረቻና የሕክምና ጋዝ ሥርዓት፣ እና የሕክምና ቆሻሻ ማቃጠያ (Incinerator) ናቸው::
ርዕሰ መስተዳድሩ በምረቃው ወቅት እንዳሉት፥ በጤናው ዘርፍ እየተመዘገበ ያለው አበረታችና ወጪ ቆጣቢ ውጤት የተቋሙን ትልቅ አቅም የሚያሳይ ነው፡፡ ፕሮጀክቶቹ የጤና አገልግሎትን ለማስፋፋት፣ የሕብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅና ጥራት ያለው ሕክምና ለማቅረብ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸውም ገልጸው የክልሉ መንግስት አስፈላጊ በሆኑ ዘርፎች ለበለጠ ስኬታማ ሥራ ድጋፍ እንደሚያደርግ ቃል ገብተዋል።
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው መንግሥት በመላ ሀገሪቱ ጥራት ያለውና ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ለሕዝቡ ለማድረስ እየሰራ መሆኑን አመልክተው የጤና ሥርዓቱ ከሕክምና አገልግሎት ባሻገር በሽታን በመከላከል፣ በምርምር፣ በእናቶችና ሕጻናት ጤና እንዲሁም በአካባቢ ጤና ጥበቃ ዘርፎች ላይ ትኩረት በመስጠት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። | 1 882 |
| 3 | ይሄም ዛሬ ይመረቃል!
*//*
ሰኔ 6/2018 ዓ/ም
ፕሮጀክት 6፡ ለአካባቢ ጥበቃ እና ለሕዝብ ጤና አዲስ ስኬት!
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል (HUCSH) ዘመናዊ የቆሻሻ ማቃጠያ ተገነባ!
የሕክምና ቆሻሻን በአግባቡ አለማስወገድ ለጤናና ለአካባቢ ከፍተኛ አደጋ ያስከትላል። ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት፣ ተቋማችን እጅግ ዘመናዊና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የቆሻሻ ማቃጠያ (Incinerator) ገጥሞ ወደ ሥራ አስገብቷል።
ይህ ቴክኖሎጂ ምን ልዩ ያደርገዋል?
ከፍተኛ የቃጠሎ አቅም፦ ከ850°C እስከ 1300°C በሚደርስ ሙቀት ቆሻሻን በማቃጠል፣ መጠኑን ወደ 3-5% አመድ ብቻ ይቀንሳል። በሰዓት እስከ 400 ኪሎ ግራም ቆሻሻ የማስወገድ አቅም አለው።
ሁሉን አቀፍ የቆሻሻ አያያዝ፦ ስለታም መሣሪያዎችን (መርፌዎች)፣ ፓቶሎጂካዊ ቆሻሻዎችን (ሕብረ ሕዋሳት/ፈሳሾች) እና ጊዜ ያለፈባቸው መድኃኒቶችን/ኬሚካሎችን በአንድ ላይ ያቃጥላል።
አካባቢን የማይበክል :- የጢስ ማውጫ ጋዝ ወደ አየር ከመውጣቱ በፊት የሚያጸዳ የሚያጣራ መሳሪያ የተገጠመለት በመሆኑ፣ ጎጂ ጋዞች እንዳይወጡ ያደርጋል። የአውሮፓውያኑን የጽዳት ስታንዳርድ ሰርቲፊኬት አግኝቷል።
የሙቀት ኃይል አጠቃቀም ፦ ከቃጠሎው የሚወጣውን ሙቀት በመጠቀም ሆስፒታሉ በሰዓት 5,000 ሊትር ሙቅ ውሃ እንዲያገኝ ያስችላል፤ ይህም የተቋሙን ወጪ በእጅጉ ይቀንሳል።
ዘላቂነት፦ ተቋራጩ ለአምስት ዓመታት የጥገናና የክትትል አገልግሎት ይሰጣል።
ይህ ማዕከል ሆስፒታላችንን ለሕሙማን፣ ለሠራተኞችና ለማህበረሰቡ ደህንነቱ የተጠበቀ ለማድረግ የምናደርገውን ጥረት አንድ ትልቅ እርምጃ ወደፊት ያራምደዋል።
ንፁህ አካባቢ – ጤናማ ማህበረሰብ!
እንኳን ደስ አለን!
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት! | 3 115 |
| 4 | ደግሞ ሌላ የምስራች!
*//*
ፕሮጀክት 5፡ የሕይወት እስትንፋስ ዋስትና!
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል (HUCSH) እጅግ ዘመናዊ የሕክምና ጋዝ ሥርዓት ተገነባ!
የሕክምና ጋዝ አቅርቦት የአንድ ዘመናዊ ሆስፒታል የጀርባ አጥንት ነው። የተቋማችንን የሕሙማን ደህንነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ (NFPA 99) ደረጃውን የጠበቀ ዘመናዊ የሕክምና ጋዝ ሥርዓት (MGS) አስገጥመናል። ይሄም ነገ ይመረቃል!
የሥርዓቱ ልዩ መገለጫዎች፦
ግዙፍ የኦክሲጅን ማምረቻ ማዕከል፦ በሃይል ቆጣቢነቱ በሚታወቀው የVSA ቴክኖሎጂ የሚሠራ ሲሆን፣ በሰዓት 30 ሜትር ኪዩብ ኦክሲጅን ማምረት የሚችሉ 9 ግዙፍ ጄነሬተሮች ስላሉት የሆስፒታሉን ፍላጎት ከመሸፈን ባለፈ ለሌሎች ተቋማት የሚተርፍ አቅም አለው።
ሁሉን አቀፍ ጋዞች፦ ከኦክሲጅን በተጨማሪ የሕክምና አየር (Medical Air)፣ ቫኩም እና ናይትረስ ኦክሳይድ በዘመናዊ የመዳብ አውታረ መረብ አማካኝነት ለክፍሎች ያሰራጫል።
ዘመናዊ መሠረተ ልማት፦
575 ሄድዎሎች (Head Walls)፦ በሕሙማን አልጋዎች አጠገብ የተገጠሙ ሲሆን፣ 27ቱ ለቀዶ ሕክምናና ለፅኑ ሕክምና ማዕከል (ICU) የሚሆኑ ተንጠልጣይ (Pendant) ሄድዎሎች ናቸው።
15 ድርብ ቡም መብራቶች፦ ለቀዶ ሕክምና ክፍሎች የተገጠሙ ከፍተኛ ቴክኖሎጂዎች።
9 VIP ክፍሎች፦ ልዩ ፓነሎችና ዘመናዊ አልጋዎች የተሟሉላቸው።
የጋዝ ሙሌት ጣቢያ፦ ሆስፒታሉ ለራሱ ተጠባባቂ እንዲኖረው ከማድረግ ባለፈ፣ ለአካባቢው ክሊኒኮችና ሆስፒታሎች ሲሊንደር የመሙላት አገልግሎት ይሰጣል። 1,100 ሲሊንደሮች ለዚሁ አገልግሎት ዝግጁ ናቸው።
የጥገና ዋስትና፦ ፕሮጀክቱ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የጥገናና የክትትል አገልግሎት ጥቅልን ያካትታል።
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት! | 3 408 |
| 5 | አሁንም ሌላ ታላቅ የምስራች አለን!
ፕሮጀክት 4: ታሪካዊ ስኬት ለኢትዮጵያ!
በሀገራችን የመጀመሪያው የሰው ጡት ወተት ባንክ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል (HUCSH) ተመሰረተ!
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል በጀርመኑ FMBI ፋውንዴሽን በElse-Kröner Foundation እና በጀርመን የኢኮኖሚ ትብብርና ልማት ሚኒስቴር (BMZ) የገንዘብ ድጋፍ እና በGIZ የሆስፒታሎች አጋርነት በሀገራችን ኢትዮጵያ በጨቅላ ሕጻናት እንክብካቤ ረገድ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ የሆነ የመጀመሪያው የሰው ጡት ወተት ባንክ በማቋቋም በይፋ ሥራ አስጀምሯል።
የጡት ወተት ባንክ በዓለም ላይ የ100 ዓመት ታሪክ ቢኖረውም፣ በአፍሪካ እስካሁን ይህ አገልግሎት የሚገኘው በ8 ሀገራት ብቻ ነበር። ዛሬ ኢትዮጵያ ይህንን አገልግሎት በማስተዋወቅ 9ኛዋ አፍሪካዊት ሀገር ሆናለች።
አስፈላጊነቱ (ክሊኒካዊ ጠቀሜታው)፦
ያለ ዕድሜያቸው ለተወለዱና ክብደታቸው አነስተኛ ለሆኑ ሕጻናት የእናት ወተት መድኃኒት ነው። ይህ ባንክ፦
ሕጻናትን ከአስከፊ የሆድ ውስጥ ሕመም (NEC) እና ከደም መመረዝ (Sepsis) ይከላከላል።
እናቶች በሕመም ወይም በሌላ ምክንያት ጡት ማጥባት በማይችሉበት ጊዜ አስተማማኝ አማራጭ ይሆናል።
በፋብሪካ ወተቶች ውስጥ የማይገኙ በሽታ የመከላከል አቅም ያላቸውን ፀረ-አካላት (Antibodies) ለሕጻናት ይሰጣል።
ደህንነቱ የተጠበቀ አሠራር
ምርመራ፦ ለጋሽ እናቶች ጥብቅ የጤና እና የደም ምርመራ ይደረግላቸዋል።
ማምከን፦ «PiAstra» በተሰኘ ዘመናዊ ማሽን በሙቀት የማምከን (Pasteurization) ሂደት ውስጥ ያልፋል፤ ይህም ተህዋስያንን በማጥፋት ንጥረ ነገሮችን ይጠብቃል።
ማከማቸት፦ በሕክምና ደረጃ በሚዘጋጁ ማቀዝቀዣዎች ውስጥ ተከማችቶ ለሚፈልጉ ሕጻናት ይሰራጫል።
እንኳን ደስ አለን!
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት! | 3 439 |
| 6 | ተጨማሪ የምስራች ዜና!
ሰኔ 5/2018 ዓ/ም
ፕሮጀክት 2፡ የኢትዮጵያ የጤና ምርምር ሉዓላዊነት አዲስ ምዕራፍ፡ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የክሊኒካል ሙከራ ማዕከል (Clinical Trial Unit) ነገ ይመረቃል!
ለጤና ውሳኔዎችና ፖሊሲ ቀረፃ በውጭ ሀገር መረጃዎች ላይ ጥገኛ መሆን የሕዝባችንን ጄኔቲክስ፣ የአኗኗር ዘይቤ ወይም ነባራዊ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ ላይገልጽ ይችላል። ይህንን ታሪካዊ ክፍተት ለመሙላት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በሐምሌ 2016 (July 2024) CTUን ያቋቋመ ሲሆን፣ ሚያዝያ 20 ቀን 2018 ዓ.ም (April 28, 2026) የዩኒቨርሲቲው ሴኔት በተሰጠው ይፋዊ ፈቃድ ከአርማወር ሃንሰን ምርምር ኢንስቲቱት (AHRI) እና ከPREGART ፕሮጀክት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ክሊኒካል ሙከራ ማዕከል (CTU) ከነሙሉ ግብዓቶች በማስገንባት በይፋ ወደ ሥራ ገብቷል፡ ፡
የማዕከሉ ዋና ዋና ስኬቶች እና ጥቅሞች፦
ዓለም አቀፍ እውቅና፦ ማዕከሉ በአፍሪካ ክሊኒካዊ ምርምር አውታረ መረብ (ACRN) ጋር ተመዝግቧል፤
ይህም ተቋሙን ለአህጉራዊ የምርምር ትብብር ዝግጁ ያደርገዋል።
የምርምር ሉዓላዊነት፦ መድኃኒቶች፣ የሕክምና መሣሪያዎችና የሕክምና ዘዴዎች በራሳችን ማህበረሰብ ተጨባጭ ሁኔታ ላይ ተመስርተው እንዲፈተሹ በማድረግ በውጭ የመረጃ ምንጮች ላይ ያለብንን ጥገኝነት ይቀንሳል።
የሰው ኃይል ልማት፦ ለተማሪዎች፣ ለመምህራን እና ለጤና ባለሙያዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያላቸውን የምርምር ክህሎቶች ለማስረጽ ዕድል ይፈጥራል።
ተወዳዳሪነት፦ እንደ WHO፣ NIH እና Wellcome Trust ካሉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር የጋራ ምርምር ለመስራትና ዓለምአቀፍ ድጎማ (International Grants) ለማግኘት ተቋሙን ብቁ ያደርገዋል።
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት! | 3 967 |
| 7 | Congratulations to Hawassa University Community!
*//*
June 12, 2026
Hawassa University has been granted another patent for waste water treatment technology.
Thank you our researchers for your dedication to innovative solutions!
Office of Vice President for Research and Collaboration
Hawassa University
Ever to Excel! | 4 554 |
| 8 | ታላቅ የምስራች ዜና!
*//*
ሰኔ 5/2018 ዓ/ም
ለሲዳማ እና አጎራባች ክልሎች ሕዝቦች ትልቅ የምስራች አለን!
በሀዋሳ ዩንቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለጤና አገልግሎት ጥራት አዲስ ምዕራፍ ተከፍቷል!
ኮሌጁ ነገ ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ/ም የተለያዩ የማስፋፊያ ፕሮጀክቶቹን ባለድርሻ አካላት ባሉበት በድምቀት ያስመርቃል!
ፕሮጀክት 1፡ ለጤና አገልግሎት ጥራት አዲስ ምዕራፍ የሆነው ልዩ የቀዶ ሕክምና እና የወሊድ ጽኑ ሕሙማን እንክብካቤ ክፍል (ICU) ይመረቃል!
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሰዎችን ሕይወት ለመታደግና ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የሚያደርገውን ጉዞ በታላቅ ስኬት ቀጥሏል።
እስካሁን ድረስ ተቋማችን ሁሉንም የጽኑ ሕሙማን አይነቶች በአንድ አጠቃላይ ጽኑ ሕሙማን ክፍል (ICU) ውስጥ ሲያስተናግድ በመቆየቱ አብዘኛው ሕሙማን በአልጋ እጥረት እና በቦታ ጥበት ምክኒያት አስፈላጊ የሆኑ የቀዶ ሕክምና ሂደቶች መዘግየት እንዲሁም ተገቢውን ክሊኒካዊ እንክብካቤ ሳያገኙ እንድቆዩ ዳርጓቸዋል፡፡
አዲሱ የቀዶ ሕክምና ክፍል ሕንፃ 8 አልጋ ያለው የቀዶ ሕክምና እና የወሊድ ICU ያለው ሲሆን የቀዶ ሕክምና እና የወሊድ ድንገተኛ አደጋ ያጋጠማቸው እናቶች ልዩና ፈጣን ሕይወት አድን ሕክምና እንዲያገኙ ዕድል ይፈጥራል።
ይህ ሕንፃ በውስጡ 11 እጅግ ዘመናዊ የቀዶ ሕክምና ክፍሎች (Operating Theatres)፤ ሙሉ የሕክምና ማገገሚያ እና የማምከኛ ተቋማትና ከፍተኛ እና ልዩ የቀዶ ሕክምና አገልግሎት መስጫዎችን ያካትታል::
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት! | 4 624 |
| 9 | ድጋፎችን በማግኘት ተጽዕኖ መፍጠርና ለመጪው ትውልድ ምሳሌ መሆን እንደሚገባቸው አብራርተዋል። የቀድሞ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምሩቅና የሥራ ኃላፊ ዶ/ር በዛወርቅ አሁን ላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ካላቸው የአመራርነት ተሞክሮ ባሻገር የኢትዮጵያ ባዮሎጂካል ሶሳይቲን በፕሬዝዳንትነት እየመሩ ያሉ ሳይንቲስት እና ተመራማሪ ናቸው::
ሴት ምሁራን ማህበረሰቡንና ሀገርን የሚቀይሩ ትርጉም ያላቸውና ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆኑ ምርምሮች ላይ በስፋት መሰማራት እንደሚገባቸው የጠቆሙት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ኮሌጅ የምርምርና ትብብር ተባባሪ ዲንና ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር ሄዋን ደምሴ የወቅቱ የአካዳሚክ ተቋማት አሠራሮች ሴቶች በምርምርና በስትራቴጂካዊ ውሳኔ ሰጪነት ቦታዎች ላይ በግንባር ቀደምትነት እንዲሳተፉ የሚያበረታቱ መሆን ይገባቸዋል ብለዋል። ዶ/ር ሔዋንም በሰፊ የምርምር ስራቸው እና ዓለምአቀፍ ተሳትፏቸው ተምሳሌታዊ ተሞክሮ ያላቸው ከመሆኑም በላይ በኢትዮጵያ ሴቶች በሳይንስ ማህበር ውስጥ ም/ፕሬዝዳንት እንደሆኑ ተገልፅዋል::
ሁለቱ የሳይንስ መምህራንና አንጋፋ ተመራማሪ እንስቶች የሕይወት ልምዳቸውን እና ስለ መሪነት ያላቸውን እውቀትና ግንዛቤ ለተሳታፊዎች ካቀረቡ በኃላ በመድረኩ ማጠቃለያ ተሳታፊዎች በአካዳሚክ ዘርፍ ሴቶች የሚያጋጥሟቸውን ማህበራዊና ተቋማዊ ጫናዎች እንዴት ማሸነፍ እንደሚችሉ እና እርስ በእርስ የሚደጋገፉበትን የሙያ መረብ (Network) መፍጠር በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል።
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት! | 4 454 |
| 10 | የተፈጥሮኖና ቀመር ሳይንስ ኮሌጁ ሴት ምሁራንን ለላቀ የምርምርና አመራር ብቃት የሚነቃቃ የምክክር ወርክሾፕ አዘጋጀ።
*
ሰኔ 4/2018 ዓ/ም
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ "Beyond the Tenure Track: Inspiring Women Academicians for Impactful Research and Executive Leadership" በሚል መሪ ቃል ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የአመራርነት አቅም ግንባታ ስልጠናና የተሞክሮ ልውውጥ የምክክር ወርክሾፕ ከ60 በላይ ለሚሆኑ የዩኒቨርሲቲው ሴት መምህራንና የሥራ ኃላፊዎች ተሰጥቷል።
የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ዙፋን በደዊ በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር በሀገራችን በሴቶች ላይ የሚደርሰውን አሉታዊ ሁሉን አቀፍ ጫና በመቋቋም በራሳቸው ጉዳይ ላይ የመወሰን አቅማቸውን በየጊዜው በማሳደግና ራሳቸውን ለመሪነት በማብቃት ረገድ መልካም ስራዎች የተሰሩ ቢሆንም ይህንን አጠናክረው ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል። ዶ/ር ዙፋን አክለውም እያንዳንዱ ሰው የውስጥ ጥንካሬውንና የግል ብቃቱን በመገንባት ለራሱ "እኔ እችላለሁ፤ አደርገዋለሁ" የሚል ጽኑ እምነት ሊኖረው እንደሚገባ በመግለጽ፤ ሴቶችም በትምህርት፣ በምርምርና አመራር ዘርፎች ውሳኔ ሰጪነታቸውንና ተሳትፏቸውን በማጠናከር የሀገራቸውን ዕድገት ማስቀጠልና በህብረተሰቡ ውስጥ በጎ ተፅዕኖ መፍጠር እንደሚገባቸው አመልክተዋል።
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጋብዘው በመድረኩ ላይ ስልጠናና የተሞክሮ ገለጻ ያደረጉት መምህርትና ተመራማሪ ዶ/ር በዛወርቅ አፈወርቅ በበኩላቸው ሴት ምሁራን መደበኛውን የአካዳሚክ የዕድገት ደረጃ (Tenure Track) ማሟላት ላይ ብቻ ትኩረት ከማድረግ በመውጣት ወደ ከፍተኛ የአመራር እርከን ለመምጣት ያላቸውን እምቅ አቅም በመጠቀም እንዲሁም ተቋማዊ | 4 976 |
| 11 | بدون متن... | 4 637 |
| 12 | IoT_Exit Sene 05_2018 EC_Session 3_260611_113717.pdf | 6 948 |
| 13 | IoT_Exit Sene 05_2018 EC_Session 2_260611_113506.pdf | 6 968 |
| 14 | IoT_Exit Sene 05_2018 EC_Session 1_260611_113054.pdf | 6 973 |
| 15 | Main Campus_Sene_05_Session 3.pdf | 7 333 |
| 16 | Main Campus_Sene_05_Session_2.pdf | 7 397 |
| 17 | Main Campus_Sene_05_Session 1.pdf | 7 366 |
| 18 | Sene 05 Exiit Exam Placement.pdf | 7 568 |
| 19 | Main_Sene_04_2018_Round 3.pdf | 7 771 |
| 20 | Main_Sene_04_2018_Round 2.pdf | 7 705 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
