fa
Feedback
እግዚአብሔርን ማወቅ

እግዚአብሔርን ማወቅ

رفتن به کانال در Telegram

ሰላምታ በተለዋወጥን ቁጥር ይመስገን ስለምንለው አምላካችንና አባታችን እግዚአብሔር ያለንን ዕውቀት ለማዳበር የሚያግዝ ቻነል ነው፡፡

نمایش بیشتر
961
مشترکین
+124 ساعت
+27 روز
+2130 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
اوت '26
اوت '26
+38
در 0 کانال‌ها
ژوئیه '26
+33
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '26
+43
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+31
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+45
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+33
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+49
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+45
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+54
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+38
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '25
+37
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+31
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+32
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+45
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+49
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+24
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+19
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+18
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+11
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+9
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+19
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+25
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+27
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+17
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+20
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+35
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+21
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+23
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+12
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+31
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+11
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+15
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+15
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '23
+12
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+13
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+479
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
28 اوت0
27 اوت+1
26 اوت0
25 اوت0
24 اوت+1
23 اوت+2
22 اوت+2
21 اوت+1
20 اوت+1
19 اوت+1
18 اوت+7
17 اوت+2
16 اوت+1
15 اوت+3
14 اوت+3
13 اوت+1
12 اوت0
11 اوت+1
10 اوت0
09 اوت+3
08 اوت+1
07 اوت+1
06 اوت+1
05 اوت+1
04 اوت+2
03 اوت0
02 اوت+1
01 اوت+1
پست‌های کانال
ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ በሦስተኛው ቀን ተነሣ ::   እኔ ደግሞ የተቀበልሁትን ከሁሉ በፊት አሳልፌ ሰጠኋችሁ እንዲህ ብዬ፡- መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ፥ ለኬፋም ታየ በኋላም ለአሥራ ሁለቱ፤ ከዚያም በኋላ ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች በአንድ ጊዜ ታየ፤ ከእነርሱም የሚበዙቱ እስከ አሁን አሉ አንዳንዶች ግን አንቀላፍተዋል፤ ከዚያም በኋላ ለያዕቆብ ኋላም ለሐዋርያት ሁሉ ታየ፤ ከሁሉም በኋላ እንደ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ደግሞ ታየኝ። እኔ ከሐዋርያት ሁሉ የማንስ ነኝና፥ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ስላሳደድሁ ሐዋርያ ተብዬ ልጠራ የማይገባኝ፤ ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ የሆንሁ እኔ ነኝ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋው ከንቱ አልነበረም ከሁላቸው ይልቅ ግን ደከምሁ፥ ዳሩ ግን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው እንጂ እኔ አይደለሁም። እንግዲህስ እኔ ብሆን እነርሱም ቢሆኑ እንዲሁ እንሰብካለን እንዲሁም አመናችሁ ( 1ቆሮ 15 ÷ 3 - 11 ) ።   ማብራሪያ ሐዋርያው ጳውሎስ ክርስቶስ ከሙታን መነሣቱንና ለዘረዘራቸው ሰዎች መታየቱን ይገልጣል ፡፡ 1)   ለኬፋ ኬፋ የሐዋርያው የጴጥሮስ ሌላኛው ስሙ ነው ( ዮሐ 1 ÷ 43 ) ፡፡ ክርስቶስ፡- አላውቅህም ብሎ ለካደው ለጴጥሮስ ተገልጦ ታይቶአል ፡፡ ጴጥሮስ የቀድሞ ስሙ ስምዖን ነበር ( ሉቃ 24 ÷ 34 ) ። 2)  ለአሥራ ሁለቱ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ሲገለጥላቸው ይሁዳ ስለሌለ አሥራ አንድ ነበሩ ፡፡ በመጀመሪያው ሲገለጥላቸው ቶማስም ስላልነበረ አሥር ነበሩ ( ዮሐ 20 ÷ 19 - 29 ) ፡፡ በሁለተኛው ለአሥራ አንዱ ሲገለጥ ቶማስ ነበረ ፡፡ ይሁዳም ጎድሎ ስማቸው አሥራ ሁለቱ ተብለው ይጠቀሳሉ ፡፡ በይሁዳ ፋንታ ማትያስ 12ተኛ ሆኖ የተቆጠረው ጌታችን ካረገ በኋላ ነው ( የሐዋ 1 ÷ 15 - 26  )  ፡፡ 3)  ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች አንዳንዶች ያላቸው በሕይወተ ሥጋ የሌሉ ቢሆኑም 1ኛ ቆሮንቶስን እስከ ጻፈበት ጊዜ ድረስ የሚበዙት ግን በሕይወተ ሥጋ ስለ ነበሩ ፡፡ 4)  ለያዕቆብ ያዕቆብን ለብቻው ያመጣዋል ፡፡ የጌታ ወንድም ተብሎ የሚጠራው ነው የሚሆነው ፡፡ ራሱን ግን የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ብሎ ነው የሚጠራው ( ያዕ 1 ÷ 1 ) ፡፡ ከትንሣኤ በፊት አላመነም ነበር ( ማቴ 13 ÷ 55 ፡ 56 ፣ ዮሐ 7 ÷ 5 ) ፡፡ በመጀመሪያው የሐዋርያት ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረገም ነበር ( የሐዋ 15 ÷ 13 - 21 ) ፡፡ 5)  ለሐዋርያት ሁሉ 12ቱ ደቀ መዛሙርት ሐዋርያት ተብለው ይጠራሉ ፡፡ ከበላይ እንደ ተገለጠላቸው ጠቅሶ ነበር ፡፡ መልሶ አምጥቶአቸዋል ፡፡ ሲያርግም ከማረጉ በፊትም አርባ ቀን ይታያቸው ነበር ( የሐዋ 1 ÷ 1 - 3 ) 6)  ለራሱ ለጳውሎስም ጳውሎስ የቀድሞ ስሙ ሳውል ነበር ፡፡ በክርስቶስ ያመኑትን ያሳድድ ነበር ፡፡ የሚሳድዳቸውን የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ብሎ ጠርቶአቸዋል ፡፡ ያመኑትን በሚያሳድድ ሰዓት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጦለት አምኖአል ( የሐዋ 9 ÷ 1 - 9 ) ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቢገለጥለትም ራሱን፡- ጭንጋፍ በማለት ይጠራል ፡፡ ከሐዋርያት የሚያንስና ሐዋርያም ተብሎ ሊጠራ የማይገባው መሆኑን ጠቅሶ የሆነለት በሥራው ሳይሆን በእግዚአብሔር ጸጋ መሆኑን ተናግሮአል ፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ ያልጠቀሳቸው ጌታ የተገለጠላቸው ሌሎችንም ከወንጌል መጥቀስ ይቻል ነበር ፡፡ ሐዋርያው ስለ ክርስቶስ መነሣት ምስክሮች የሚሆኑትን ከበላይ ያሉትን ሰዎች ያቀረበው ከቆሮንቶስ ሰዎች አንዳንዶች ስለ ትንሣኤ ሙታን የተጠራጠሩ ስለ ነበሩ ነው ( 1ቆሮ  15 ÷ 12 - 19 ) ፡፡ ሐዋርያት ፡- ተነሥቶአል ብለው እንዳስተማሩ እርሱም፡- ተነሥቶአል ብሎ ማስተማሩንና ያመኑትን ደግሞ ፡- እናንተም እንዲህ አመናችሁ ብሎአቸዋል ፡፡ ሞተ ፣ ተቀበረ ፤ ተነሣ የሚሉት ቁልፍ ቃላት ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ናቸው ፡፡ ክርስትና ስለ ክርስቶስ የምንሰብከውና የምናስተምረው ሃይማኖት ነው ፡፡ ክርስቶስ የሞተው ስለ ኃጢአታችን ነው ፡፡ ሁሌም ልንዘነጋው የማይገባ ቃል ነው ፡፡ ስለ ኃጢአታችን ሞተ ፤ ተቀበረ ፤ ሞቶ አልቀረም በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶአል ፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በሌላ ጊዜ እንዲሁም በግንቦት 30 ቅዳሴ ሲቀደስና ከቁ.1 - 12 ያለው በሚነበብ ሰዓት ከበላይ የጠቀስኩት ክፍል ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌን ይመልከቱ ) ፡፡ ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie

2
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
53
3
እግዚአብሔር መፈጸሙ ላይቀር ፣ አይሳካም ብለን የኛ መደምደም ፡፡   እግዚአብሔርም ሳሙኤልን፡- በእስራኤል ላይ እንዳይነግሥ ለናቅሁት ለሳኦል የምታለቅስለት እስከ መቼ ነው? ..በልጆቹ መካከል ንጉሥ አዘጋጅቻለሁና ወደ እሴይ ..እልክሃለሁ አለው። ሳሙኤልም.. እሴይንና ልጆቹንም.. ጠራቸው። እሴይም ከልጆቹ ሰባቱን በሳሙኤል ፊት አሳለፋቸው። ሳሙኤልም እሴይን፡- እግዚአብሔር እነዚህን አልመረጠም አለው። ሳሙኤልም እሴይን፡- የቀረ ሌላ ልጅ አለህን? አለው። እርሱም፡- ታናሹ ገና ቀርቶአል፤ እነሆም፥ በጎችን ይጠብቃል አለ። ሳሙኤልም እሴይን፡- ..ልከህ አስመጣው አለው።  ልኮም አስመጣው፤ ..እግዚአብሔርም፡- ይህ ነውና ተነሥተህ ቅባው አለ። ሳሙኤልም የዘይቱን ቀንድ ወስዶ ..ቀባው.. ( 1ሳሙ 16 ÷ 1 - 13 ) ። እንዲህም ሆነ፤ ዳዊት ፍልስጥኤማዊውን ( ጎልያድን ) ገድሎ በተመለሰ ጊዜ፥ ..ንጉሡን ሳኦልን ሊቀበሉ ሴቶች ..ወጡ። ሴቶችም፡- ሳኦል ሺህ፥ ዳዊትም እልፍ ገደለ እያሉ ..ይዘፍኑ ነበር። ሳኦልም ..ይህም ነገር አስከፋው፤ ..በነጋውም ..ዳዊትም ..በገና ይመታ ነበር። ሳኦልም፡ ዳዊትን ከግንቡ ጋር አጣብቄ እመታዋለሁ ብሎ ጦሩን ወረወረ። ዳዊትም ..ከፊቱ ዘወር አለ ( 1ሳሙ 18 ÷ 6 - 10 ) ። ሳኦልም ለልጁ ለዮናታንና ለባሪያዎቹ ሁሉ ዳዊትን ይገድሉ ዘንድ ነገራቸው። ..ዮናታን ግን ዳዊትን እጅግ ይወድድ ነበር ( 1ሳሙ 19 ÷ 1 - 10 ) ። ዳዊትም .ወደ ዮናታንም መጥቶ፡- በእኔና በሞት መካከል አንድ እርምጃ ያህል ቀርቶአል ብሎ ማለ ( 1ሳሙ 20 ÷ 1 - 3 ) ።   ( የሳኦል መሞት ) ፍልስጥኤማውያንም ከእስራኤል ጋር ተዋጉ፤ በዚያም ቀን ሳኦል ሦስቱም ልጆቹ.. ሞቱ       ( 1ሳሙ 31 ÷ 1 ፡ 6 )። የእስራኤልም ሽማግሌዎች.. ንጉሥ ይሆን ዘንድ ዳዊትን ቀቡት። ..መንገሥ በጀመረ ጊዜ የሠላሳ ዓመት ልጅ ነበረ፥ አርባ ዓመትም ነገሠ ( 2ሳሙ 5 ÷ 3 ፡ 4 ) ።   ማብራሪያ እግዚአብሔር ሳኦልን ንጉሥ አድርጎ በእስራኤል ላይ ቢሾመውም እግዚአብሔርን ስላላከበረ ናቀው ( 1ሳሙ 15 ÷ 1 - 30 ) ፡፡ ለሳኦል ለሚያለቅሰው ለነቢዩ ሳሙኤል ወደ እሴይ እንዲሄድ ነገረው ፡፡ እግዚአብሔር ከእሴይ ልጆች ሊያነግሠው የፈለገው ሰው ነበር፡፡ ሳሙኤል እሴይን አስጠራ፡፡ እሴይም ሰባት ልጆቹን ይዞ ቢመጣም ለንጉሥነት አልተሾሙም ፡፡ የተወውን ዳዊትን ሲያስመጣ እግዚአብሔር ዳዊት ንጉሥ ሆኖ እንዲቀባ ስለ ተናገረ ተቀባ፡፡ ንጉሥ እንድትሆኑ የተቀባችሁት እናንተ ብትሆኑ እንዴት ባለ ዓይነት ተስፋ እንደምትሞሉ አስቡት? በአእምሮአችሁ ምን ዓይነት ቤተ መንግሥት እንደምትገነቡና ሌላም ብዙ ጥሩ ነገር  እንደሚመላለስ? ወደ ዳዊት ልመልሳችሁ ፡፡ በአንድ ወቅት ዳዊት ጎልያድን ገድሎ ሲመለስ ሴቶች ዳዊትን ከንጉሡ ሳኦል በላይ ጀግና ገዳይ አድርገው ስለ ዘፈኑለት ሳኦል ተከፋ ፡፡ በነጋታው ሊገድለው ጦሩን ቢወረውርበትም ዳዊት አመለጠ ፡፡ ሳኦል ዳዊትን ለሚወደው ለልጁ ዮናታንና ለባሪያዎቹ ዳዊትን እንዲገድሉት ትእዛዝ ሰጠ ፡፡ በሳኦል ሞት ስለ ተዛተበት ዳዊትም ፡- በእኔና በሞት መካከል አንድ እርምጃ ያህል ቀርቶአል በማለት የሚሞት መስሎ ተሰማው ፡፡ ትነግሣለህ የተባለውን ተስፋ ዘነጋው፡፡ ወደ እናንተ ልመለስ ፡፡ ከአዲስ አባባ ተስታችሁ ራቅ ወዳለ ቦታ ለመሄድ ፈልጋችሁ መኪናችሁን እያስከረከራችሁ በታላቅ ወኔ ጉዞ ጀመራችሁ ልበል፡፡ ብዙ ኪሎ ሜትር ከተጓዛችሁ በኋላ እደርስበታለሁ ያላችሁበት ቦታ ስለ መድረሳችሁ ያላችሁ ተስፋ እየተሸረሸረ መጥቶ መኪናችሁን ማሽከርከር አቆማችሁ ፡፡ መኪናችሁን በተመለከተ ምንም ዓይነት ችግር አላጋጠማትም ፡፡ ነዳጅ አላት ፡፡ የቴክኒክ ችግርም አላጋጠማችሁም ፡፡ እናንተ ሞተርዋን ጥፍጥፍት ሳላደረጋችሁኋት ቆመች ፡፡ ችግሩ ማን ጋር ነው? መኪናዋ ጋር ወይስ እናንተ ጋር ? ችግሩ እናንተ ጋር ነው፡፡ መኪናዋን አስነሥታችሁ ማሽከርከር ብትጀምሩ ወደፊት መጓዝ ትችላላችሁ ፡፡ ንጉሥ እንድትሆኑ እንደ ዳዊት የተቀባችሁት እናንተ ብትሆኑ ስላችሁ እንዴት ባለ ታላቅ ተስፋ እንደ ተሞላችሁ አታስታውሱም ? ታዲያ አሁን ለምን ዛላችሁ? መጀመሪያም ተስፋ ያደረጋችሁት እግዚአብሔርን ነው ፡፡ አሁንም ተስፋችሁን በእርሱ አድርጉ፡፡ እርሱ ያደርገዋል ፡፡ እንደሚነግሠው እንደ ዳዊት እንደምትነግሡ አስቡና በተስፋ ተሞሉ ፡፡ አሁንስ ያቆማችኋትን መኪና ማሽከርከር አትጀምሩም ? ልባችሁን በብርታት የሚሞላውን የዳዊትን መጨረሻ ላሳያችሁ ፡፡ ዳዊትን ካልገደልኩ ይል የነበረው ሳኦል ከጠላቶቹ ጋር ውጊያ አድርጎ ሳይቀናው ቀረና ሞተ ፡፡ እሞታለሁ ይል የነበረው ዳዊት ደግሞ እግዚአብሔር የተናገረውን ሳያስቀርበት አነገሠው ፡፡ ወደ ዳዊት አንድ እርምጃ የቀረው ሞት ባለበት ሲቆም ዳዊት ግን እንኳን ሊሞት ሊያውም አርባ ዓመት ነገሠ፡፡ ከመንገሡ በፊት ያጋጠመው መከራ ትንሽ፣ የንግሥናው ዘመን አበዛዙ ! ከእግዚአብሔር እንደምንቀበል ተስፋ ያደረግነው ነገር እኛ ከመዛላችን የተነሳ ሊሳካ አይችልም ብንልም እግዚአብሔር ግን የገባልንን ተስፋ ይፈጽማል ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን ! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
83
4
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
74
5
የጸሎት ኃይል ::   … ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች። ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥ ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች ( ያዕ 5 ÷ 16 -18 ) ።   ማብራሪያ አንዳችን ለሌሎቻችን መጸለይ አለብን፡፡ ብርቱ ያልነው ሰው ሀዘን ( ለቅሶ ወይም መከራ ) ቢያጋጥመው እንደ ሌላው ጊዜ ተግቶ ሊጸልይ አይችልም፡፡ በዚህ ጊዜ የሌሎቻችን የጸሎት ድጋፍ ያስፈልገዋል፡፡ ከሀዘኑ በቶሎ እንዲወጣ ብንጸልይ አገዝነው ማለት ነው፡፡ አንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ የሚለውን ቃል ተግባራዊ አደረግን ማለት ነው፡፡ የጻድቅ ሰው ጸሎት ኃይል አለው፤ ታላቅ ነገርም ያደርጋል፡፡ ኤልያስ ምን እንዳደረገ እናውቃለን፡፡ ዝናብ እንዳይዘንብ ጸለየ፤ 3 ዓመት ከ 6 ወር ያህል ዝናብ አልዘነበም፤ መልሶ ሲጸልይ ዝናብ ዘነበ፡፡ ኤልያስ ያደረገው ነገር ትልቅ ነገር ነው፡ ( 1ነገ 17 ÷ 1 - 7 ፤ 18 ÷ 41 - 46 ) ፡፡ ኤልያስ ዝናብ እንዳይዘንብ ቢያደርግም መልሶ ሲጸልይ ዝናብ እንዲዘንብ ቢያደርግም  እንደኛ ሰው ( ሥጋ ለባሽ ) መሆኑን እንዳነዘነጋ ተነግሮናል፡፡ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ  የሚለው ቃል እኛም ተበረታተን እንደ ኤልያስ እንድንጸልይ ነው እንጂ፡- ጻድቁ ኤልያስ ካልጸለየላችሁ በስተቀር እግዚአብሔር አይሰማችሁም አልተባልንም፡፡  ስንጸልይ እግዚአብሔር ከኛ ከሚፈልገው ነገር አንዱ፡-  ይሰማናል ብለን በእምነት እንድንጸልይ ነው፡፡   የንስሐ ጸሎት ( በቤቱ መመላለስ ላቃታችሁ ) ፡፡ ክርስቶስ ሆይ ስለ በደሌ ሞትክልኝ፤ እኔ ግን ዓለምን ትቼ አንተን መከተል አቃተኝ፡፡ ሕይወቴን ቀይረው፡፡ እንደ ቸርነትህ መጠን እኔ ኃጢአተኛውን ዛሬ ይቅር በለኝ ፡፡ ያጎበጠኝ ኃጢአቴ ከላዬ ይነሣና ይቅለለኝ፡፡ ሰው ከለመነህ በኋላ  አንድ ቀን እግዚአብሔር ልመናዬን ይሰጠኛል ይላል፡፡ በደሌን ግን አንድ ቀን ይቅር ትለኛለህ የምለው አይደለም፡፡ ያጎበጠኝ ኃጢአቴ ዛሬ ከላዬ ይነሳና ይቅለለኝ፡፡ ቃልህ፡- ለምኑ ይሰጣችኋል  ይላል፡፡ እኔ ግን በዓለም የተጠላለፍኩ አንተን የምበድል ነኝና ለምኑ ይሰጣችኋል  ብትልም፡- አቤቱ ስማኝ ለማለት በቃልህ መሄድ ያልቻልኩ ደካማ ነኝ ፡፡ ድሀ ሰው ሲለምን ፡- ደጃችን ላይ እንድትቆምና እንጀራ እንድትለምን ማን ፈቀደልህ?  እንደማይባል በፊትህ ቆሜ ይቅር እንድትለኝ እለምንሃለሁ፡፡ ድሀው ለማኝ ለምኖ ባይሰጡት፡- ስጡኝ እንጂ? የማለት መብት የለውም፡፡ እኔም እንደዚህ ድሀ ሰው ሳይገባኝ ፊትህ ቆሜአለሁ፡፡ ከቸርነትህ የተነሳ ማረኝ፡፡  ነፍሴን አሳርፋት፤ ይቅር ስትለኝ ነፍሴ እረፍት ታገኛለች፡፡ እግዚአብሔር ሆይ ካንተ ጋራ መኖር እፈልጋለሁ፡፡ እንግዲህ በመንፈሳዊ ሕይወቴ የበረታሁ እንድሆን አግዘኝ ፡፡  እንደ ኤልያስ በእምነትም መጸለይ እንድችል ጸጋህን አብዛልኝ፡፡ በሚያስፈልገኝ ሁሉ አስበኝ፡፡ ጸሎቴን ሰምተህ  የምትሰጠኝ ደግሞ ስለ ጽድቄ ሳይሆን ስለ ብዙ ቸርነትህ ስትል ነው፡፡ ከበላይ ያለውን ጸሎት በሚመስል መልኩ ጠዋት ከቤታችን ከመውጣታችን በፊት ማታም ከመተኛታችን በፊት እንዲሁም በሚያስፈልገን ነገር ሁሉ እንጸልይ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ አሜን!! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
102
6
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
80
7
Don't be afraid; you are worth more than many sparrows.   Are not two sparrows sold for a penny ? Yet not one of them will fall to the ground apart from the will of your Father. And even the very hairs of your head are all numbered. So don't be afraid; you are worth more than many sparrows ( Mat  10 ÷ 29 - 31 (NIV) ).   Explanation A sparrow is a small bird with a unique appearance. When our Lord Jesus Christ was teaching, he told them the price of two sparrows (birds). Not one of these sparrows will perish without His permission. Our God cares even for these sparrows.  God, who said that two sparrows are sold for five cents, shows us how much he knows our closets in depth.   What did we feel when we read that our hair is counted? There is nothing that God does not know. He knows all things of ours. He even knows a number of hair of our head.   A person knows his assets in his organization.  He counts it and keeps it.  Let alone the more important matters of ours, God knows the number of hairs of our head.   We have been told not to be afraid.   Don't be afraid means don't worry.  Let me tell you how we don't have to worry anymore. Have you ever bothered to know the number of your hair? It never botheres us.  Why are we not worried about knowing the number of our hair? Of course, about knowing the number of our hair does not wory. There is no need to worry about the number of our hairs.  we have been told not to worry about anything .  What does it mean: There is no need to worry about the number of our hair. We have been told that there is no need to worry about anything else ( Mat 6 ÷ 25-32).   The fact that even a hair of our own is counted in God's eyes shows how much attention is given to any of our issues in God's eyes.   Not even a sparrow falls without the permission of our Father.  Nothing of ours happens without God's knowledge.   As he himself said, you are better than many sparrows.  This means that if he takes care of the sparrows, he will take care of us more than the sparrows.  We must not forget what we were told not to be afraid. To live with God is to live without anxiety.  Even if it worries us, by giving the issue to God, we are free from worry.   Thanks be to God.  Amen! Singer Deacon Negussie Tilahun ( Gospel Preacher  ) Also a drafts man and computer expert For those who want to listen to my sermons and songs, you can find them on my YouTube channel https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w Telegram channel https://t.me/EMaweq Facebook channel fb.me/yeglie
86
8
Singer Deacon Negussie Tilahun ( Gospel Preacher ) Also a drafts man and computer expert For those who want to listen to my s
Singer Deacon Negussie Tilahun ( Gospel Preacher  ) Also a drafts man and computer expert For those who want to listen to my sermons and songs, you can find them on my YouTube channel https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w Telegram channel https://t.me/EMaweq Facebook channel fb.me/yeglie
71
9
አትፍሩ ፡፡ከብዙ ድንቢጦች እናንተ ትበልጣላችሁ። ሁለት ድንቢጦች በአምስት ሳንቲም ይሸጡ የለምን? ከእነርሱም አንዲቱ ያለ አባታችሁ ፈቃድ በምድር ላይ አትወድቅም። የእናንተስ የራሳችሁ ጠጕር ሁሉ እንኳ ተቈጥሮአል። እንግዲህ አትፍሩ ከብዙ ድንቢጦች እናንተ ትበልጣላችሁ ( ማቴ 10 ÷ 29 - 31 ) ።   ማብራሪያ ድንቢጥ ልዩ ልዩ መልክ ያለው አነስተኛ ወፍ ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲያስተምር የሁለት ድንቢጦች ( ወፎች ) ዋጋ ስንት እንደሆነ ነገራቸው፡፡ ከእነዚህ ድንቢጦች ያለ እርሱ ፈቃድ አንዲቱም ብትሆን አትጠፋም፡፡ አምላካችን ለእነዚህ ድንቢጦች እንኳ የሚጠነቀቅ ነው፡፡ ሁለት ድንቢጦች በአምስት ሳንቲም መሸጣቸውን ያወሳ አምላክ የኛንም ጓዳ ጎድጓዳ ምን ያህል እንደሚያውቅ ያሳየናል፡፡ ጠጕራችን መቆጠሩን ስናነብ ምን ተሰማን? እግዚአብሔር የማያውቀው ነገር የለም፡፡ ሁሉ ነገራችንን ያውቃል፡፡ የራስ ጠጕራችንን ቁጥር ሳይቀር ያውቃል፡፡ አንድ ሰው በድርጅቱ ውስጥ ያሉትን ንብረቶቹን ያውቃቸዋል፡፡ ቆጥሮም ያስቀምጣል፡፡ ዋና ዋና ስለምንለው ነገራችን ይቅርና የራስ ጠጉራችንን ቁጥር ሳይቀር እግዚአብሔር የሚያውቅ አምላክ ነው፡፡ አትፍሩም ተብለናል፡፡ አትፍሩ ማለቱ አትጨነቁ ለማለት ነው፡፡ መጨነቅ ደግሞ የሌለብን እንዴት እንደሆነ ልንገራችሁ፡፡ የጠጕራችንን ቁጥር ለማወቅ አስጨንቆን ያውቃል? አስጨንቆን አያውቅም፡፡ የጠጕራችንን ቁጥር ማወቅ ለምን አላስጨነቀንም? በርግጥ የጠጕራችንን ቁጥር ማወቅ አያስጨንቅም፡፡ ስለ ጠጕራችን ቍጥር መጨነቅ የሚያስፈልግ ነገር አይደለም፡፡ የሚገርመው ግን ስለ ምንም ነገር እንዳንጨነቅ ተነግሮናል፡፡ ስለ ጠጕራችን ቁጥር መጨነቅ የሚያስፈልግ ነገር እንዳልሆነ ሁሉ ስለ ሌላውም ( ስለምንጨነቅለት ነገር ) መጨነቅ እንደማያስፈልግ ተነግሮናል ( ማቴ 6÷ 25 - 32 ) ፡፡ በእግዚአብሔር ዘንድ የራሳችን ጠጕር ሁሉ እንኳ መቆጠሩ የኛ ማንኛውም ጉዳይ በእርሱ ዘንድ እንዴት ትኵረት እንደሚሰጠው ያሳያል፡፡ አንዲቱም ድንቢጥ ያለ አባታችን ፈቃድ አትወድቅም፡፡ የኛም ማንኛውም ነገር እግዚአብሔር ሳያውቀው የሚሆን ነገር የለም፡፡ ራሱም እንዳለው ከብዙ ድንቢጦች እናንተ ትበልጣላችሁ። ይህ ማለት ለድንቢጦቹ ከተጠነቀቀ ከድንቢጦች ለምንበልጠው ለኛ አብዝቶ ይጠነቀቅልናል ማለት ነው፡፡ አትፍሩ የተባልነውንም መርሳት የለብንም፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር መኖር ማለት ያለ ጭንቀት መኖር ማለት ነው፡፡ ቢያስጨንቀን እንኳ ጉዳዩን ለእግዚእብሔር በመስጠት ከጭንቀት ነጻ ሆነን የምንኖርበት ኑሮ ነው፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
102
10
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
86
11
እግዚአብሔር መከራችንን ያስረሳናል፡፡   እስራኤልም ( ያዕቆብ ) ዮሴፍን፡-  ወንድሞችህ በሴኬም በጎችን  የሚጠብቁ አይደሉምን? ወደ እነርሱ እልክህ ዘንድ ና አለው። .. ዮሴፍም ወንድሞቹን ..አገኛቸው። እነርሱም በሩቅ ሳለ አዩት፥ ወደ እነርሱም ገና  ሳይቀርብ ይገድሉት ዘንድ በእርሱ ላይ ተማከሩ። አንዱም ለአንዱ እንዲህ አለው። ያ ባለ ሕልም ይኸው መጣ። አሁንም ኑ፥ እንግደለውና በአንድ ጕድጓድ ውስጥ እንጣለው። ..ከሕልሞቹም የሚሆነውን እናያለን። ሮቤል፡-  ደም አታፍስሱ፤ በዚህች ምድረ በዳ ባለችው  ጕድጓድ ጣሉት.. አላቸው። ..ወስደውም ወደ ጕድጓድ ጣሉት፤ ..ዮሴፍን ..ከጕድጓድ አወጡት፤ ለእስማኤላውያንም ዮሴፍን በሀያ ብር ሸጡት፤ እነርሱም ዮሴፍን ወደ ግብፅ ወሰዱት ( ዘፍጥ 37 )  ።  ዮሴፍ ግን ወደ ግብፅ ወረደ፤ ..የግብፅ ሰው ጲጥፋራ ወደ ግብፅ ካወረዱት ከእስማኤላውያን እጅ ገዛው። ..ከዚህም በኋላ እንዲህ ሆነ፤ የጌታው ሚስት በዮሴፍ ላይ ዓይንዋን ጣለች። ከእኔም ጋር ተኛ አለችው። እርሱም እንቢ አለ፥ ..እንዲህም ሆነ፤ በዚያን ጊዜ ሥራውን እንዲሠራ፤ ወደ ቤቱ ገባ፤ በቤትም ውስጥ ከቤት ሰዎች ማንም አልነበረም። ከእኔ ጋር ተኛ ስትል ልብሱን ተጠማጥማ ያዘች፤ እርሱም ልብሱን በእጅዋ ትቶላት ሸሸ ወደ ውጭም ወጣ። እንዲህም ሆነ፤ ልብሱን ትቶ ወደ ውጭ እንደ ሸሸ ባየች ጊዜ፥  ..ጌታው ወደ ቤቱ እስኪገባ ድረስም ልብሱን ከእርስዋ ዘንድ አኖረች። ይህንም ነገር እንዲህ ብላ ነገረችው። ያገባህልን ዕብራዊው ባሪያ ሊሣለቅብኝ ወደ እኔ ገባ፤ እኔም ድምፄን ከፍ አድርጌ ስጮኽ ልብሱን በእጄ ተወና ወደ ውጭ ሸሸ።  ጌታውም፡- ባሪያህ እንዲህ አደረገኝ ብላ የነገረችውን የሚስቱን ቃል በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ። የዮሴፍም ጌታ ..ወደ ግዞት ቤት አገባው .. ( ዘፍጥ 39 ) ። ..ፈርዖንም ልኮ ዮሴፍን አስጠራ፥ ከግዞት ቤትም አስቸኰሉት.. ወደ ፈርዖንም ገባ። ፈርዖንም ዮሴፍን አለው። ሕልምን አየሁ፥ የሚተረጕመውም አልተገኘም፤ ሕልምን እንደ ሰማህ፥ እንደ ተረጐምህም ስለ አንተ ሰማሁ። ዮሴፍም ለፈርዖን እንዲህ ብሎ መለሰ። ይህ በእኔ አይደለም፤ እግዚአብሔር ግን ለፈርዖን በደኅንነት ይመልስለታል። ..ዮሴፍም ፈርዖንን አለው። ..እግዚአብሔር ሊያደርገው ያለውን ለፈርዖን ነግሮታል። .. ፈርዖንም ዮሴፍን፡- በግብፅ ምድር ሁሉ ላይ ሾምሁህ አለው.. ( ዘፍጥ 41 ÷ 1 - 41 )። ዮሴፍም የበኵር ልጁን ስም ምናሴ ብሎ ጠራው፥ እንዲህ  ሲል፡- እግዚአብሔር መከራዬን ሁሉ የአባቴንም ቤት አስረሳኝ፤  የሁለተኛውንም ስም ኤፍሬም ብሎ ጠራው.. ( ዘፍጥ 41 ÷ 51 ፡ 52 ) ።    ማብራሪያ ዮሴፍ እንዲሞት ተፈልጎ በገዛ ወንድሞቹ ሞቱ የተደገሰለት ሰው ነበር፡፡ ከሕልሞቹም በመነሣት እንዳይነግስባቸው ጨምሮም በግብፅ አገር ላይ ጭምር ገዢ እንዳይሆን የሚያደርገውን ጉዞ ለማጨንገፍ በክብር ሳይቀበር በሜዳ ገድለው ሕልሞቹ እንዳይሳካ ለማድረግ ሞክረው ነበር፡፡ ግድያው ባይሳካላቸውም ሸጡት፡፡ የተሸጠው ዮሴፍ በግብፅ በባርነት ማገልገል ጀመረ፡፡ በሚያገለግልበት ቤት የጌታው ሚስት ፡- ከኔ ጋር ካልተኛህ ስትለው፡- እምቢ በማለቱ ሊደፍራት እንደ ነበር በሐሰት ስለ ከሰሰችው ወደ ወህኒ ተወረወረ፡፡ ዮሴፍ በወህኒ እያለ የሕልም መፍታትን ጥበብ በመማሩ የተጨነቀው የግብፅ ንጉሥ ፈርዖን ሕልም በማለሙና ሕልም ፈቺ በማጣቱ ፈርዖን እንዲያስጠራው አደረገ፡፡  የፈርዖንን ሕልም እንዲፈታ እግዚአብሔር ጥበብን ስለ ሰጠው ፈርዖን በግብፅ ምድር ሁሉ ላይ ሾመው፡፡ ዮሴፍን ከመከራው ሁሉ እግዚአብሔር ስላሳለፈው የመጀመሪያውን ልጁን ሲወልድ፡- መከራዬን ሁሉ አስረሳኝ ሲል ልጁን፡- ምናሴ ብሎ ጠራው፡፡ ዮሴፍን ከመከራው ያስረሳ እግዚአብሔር የእኛም ተስፋ ነው፡፡ አስደናቂ ጥበቡን ያየንባቸውን ሰማይንና ምድርን የሠራ እግዚአብሔር በመከራችን ጊዜም ረዳታችን ነው፡፡ የማናልፈው ነገር የለም ፤ ልናልፍ የምንችለው ደግሞ አሻጋሪአችን ማንም ሳይሆን እግዚአብሔር በመሆኑ ነው፡፡ ክረምት አልፎ እንደሚሄድ መከራ ያልነው ሁሉ ያልፋል፡፡ በጋ ሲመጣ ክረምትን እንደምንረሳ መከራችንም አልፎ እንደ ሄደው ክረምት የተረሳ ይሆናል፡፡ በመከራችን ደስ የሚላቸው እንዳሉ ሁሉ መከራችንን የሚያስረሳ ወደጅ የሆነን እግዚአብሔርም አለን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
112
12
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
82
13
  ለሚጠጡት ለምድር አራዊት ምንጮችን የሚያፈልቅ አምላክ ለኛም የሚያስብልን ነው፡፡   ዘይፌኑ አንቅዕት ውስተ rላት ፡፡ ማእከለ አድባር የኀልፉ ማያት … ምንጮችን ወደ ቈላዎች ይልካል፤ በተራሮች መካከል ውኆች ያልፋሉ፤ የዱር አራዊትን ሁሉ ያጠጣሉ፥ የበረሃ አህያዎችም ጥማታቸውን ይረካሉ።  የሰማይም ወፎች በእነርሱ ዘንድ ያድራሉ፥ በድንጋዩ ስንጥቅ መካከልም ይጮኻሉ ( መዝ 103 ( 104 ) ÷ 10 - 12 ) ።     ማብራሪያ ለቤት እንስሳት ውኃ ሲያስፈልጋቸው እኛ እናቀርብላቸዋለን፤ የዱር አራዊቶች ውኃ ይጠጡ አይጠጡ ማን ዞር ብሎ ያያቸዋል፡፡ ስለ ዱር እንስሳት ተመጋቾች ይማገቱ እንጂ የሚያስፈልጋቸውን ውኃ ማቅረብ አይችሉም፡፡ እግዚአብሔር ምንጮች በሸለቆዎች ውስጥ  እንዲፈሱ በተራሮች መካከል እንዲወርዱ የሚያደርገው ለዱር አራዊቶች መጠጥ እንዲሆን ነው፡፡ አራዊቱም ጥማታቸውን ያረካሉ፡፡ አንበሳ ውኃ ጠጣ ብሎ ማን ጨንቆት ያውቃል? ነብርም እንደዚሁ፡፡ በውኃዎች ዳር ባለው የዛፎች ቅርንጫፎች ላይ ደግሞ  ወፎች ጎጆአቸውን በመሥራት ከውኃው ይጠጣሉ፡፡ ለእግዚአብሔርም ያዜማሉ፡፡ መዝሙረኛ ይህን በማሰብ ስለ እግዚአብሔር ተቀኘ፡፡ ጥበቡን ያደናንቃል፡፡ በጥበቡ ያደረገውን ተመልክቶ ያመሰግነዋል፡፡ እግዚአብሔር በሥራው ድንቅ ነው፡፡ እግዚአብሔር በእውነት ድንቅ አምላክ ነው፡፡ እንኳን ለኛ በአርአያውና በአምሳሉ ለተፈጠርነው ለሰው ልጆች ይቅርና ለዱር አራዊቶች ሳይቀር የሚያስብ ነው፡፡ ለፍጥረትም ሁሉ የሚያስብ አምላክ ነው፡፡ የፍጥረት ሁሉ መጋቢ ነው፡፡ ለሚጠጡት ምንጮችን ለምድር አራዊት የሚያፈልቅ አምላክ ለኛም የሚያስብልን አምላክ ነው፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
109
14
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
92
15
ማርያምም በልብዋ እያሰበች ትጠብቀው ነበር ( በልብ መጠበቅ  )  ፡፡   እረኞቹ ..ፈጥነውም መጡ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ። አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ። የሰሙትን ሁሉ እረኞቹ በነገሩአቸው ነገር አደነቁ፤ ማርያም ግን ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ እያሰበች ትጠብቀው ነበር (ሉቃ 2 ÷ 15 – 19 ) ።   እናቱም፡- ልጄ ሆይ፥ ለምን እንዲህ አደረግህብን? እነሆ፥ አባትህና እኔ እየተጨነቅን ስንፈልግህ ነበርን አለችው። እርሱም፡- ስለ ምን ፈለጋችሁኝ? በአባቴ ቤት እሆን ዘንድ እንዲገባኝ አላወቃችሁምን? አላቸው። እነርሱም የተናገራቸውን ነገር አላስተዋሉም። ከእነርሱም ጋር ወርዶ ወደ ናዝሬት መጣ፥ ይታዘዝላቸውም ነበር። እናቱም ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ ትጠብቀው ነበር (ሉቃ 2 ÷ 48 - 51) ።   ማብራሪያ መንጋቸውን በሌሊት እየጠበቁ ላደሩት እረኞች መልአኩ ታላቁን የምሥራች ከነገራቸው በኋላ መድኃኒት በመሆን የተወለደ ጌታ ክርስቶስ ተጠቅልሎ በግርግም ተኝቶ እንደሚገኝ ስላሳወቃቸው እረኞቹ ማርያምና ዮሴፍ ወደ ነበሩበት ግርግም መጡ፡፡ የተነገረለትን ሕጻን እንደተባሉት በግርግም ተኝቶ አገኙት፡፡ ወደ ማርያምና ዮሴፍ የመጡት ጠያቂ እረኞች ያልታሰቡ ነበር፡፡ ይመጣሉ ብለው ያልጠበቁአቸው ጠያቂዎች ነበሩ፡፡ እረኞቹ ፡- የጌታ መልአክ ወደ እነርሱ ቀርቦ የጌታ ክብርም በዙሪያቸው እንዳበራ በታላቅ ፍርሃትም በተዋጡ ሰዓት መልአኩ ፡- እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና ያላቸውን ለማርያምና ለዮሴፍ አስረዱ፡፡ በመቀጠልም ወዳሉበት የመጡት፡- ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ ተብለው እንደሆነ ተናገሩ፡፡ ማርያምና ዮሴፍ ከእረኞቹ በሰሙት ነገር ተደንቀው ነበር፡፡ እረኞቹ ደግሞ ሊነግሩአቸው የሚችሉት ከበላይ ባወራሁት መልኩ ስለሆነ ነው፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያም ግን በልብዋ ትጠብቀው ነበር፡፡   ወደ ሁለተኛውም ታሪክ ላምራ፡፡ ኢየሱስ የ12 ዓመት ሕጻን ሳለ ከማርያምና ከዮሴፍ ጋር ወደ ኢየሩሳሌም የአይሁድን በዓል ለማክበር ሄዶ ነበር፡፡ ሲመለሱ ግን አብሮአቸው መስሎአቸው ነበር ፡፡ ብላቴናው ኢየሱስ ግን በኢየሩሳሌም ቀርቶ ነበር፡፡ ማርያምና ዮሴፍ ወደ ኢየሩሳሌም በመምጣት ፈልገው አገኙት ፡፡ እናቱም ፡- ልጄ ሆይ .. የሚሉትን ቃላት እንመልከታቸው፡፡ ሉቃስ ሲጽፍ እናቱ በማለት ተናግሮአል፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያም ኢየሱሰን በሥጋ በመውለድዋ እናቱ ተብላለች፡፡ እናቱም ትባላለች፡፡ ስለ ወለደችው ራስዋ ደግሞ፡- ልጄ ብላዋለች፡፡ ጸንሳ የወለደችው ስለሆነ፤- ልጄ ብላዋለች፡፡ በሥጋ ወልዳዋለች፡፡ በመለኮት አልወለደችውም፡፡ የድንግል ማርያምን እናትነት ለመካድ የሚፈልጉ ሰዎች አሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በብዙ ቦታ ፡- እናቱ በማለት እናትነትዋን አረጋግጦአል፡፡ ሉቃስ ምዕራፍ ሁለትን ሊዘጋ ሲልም እናቱም ይህን ነገር.. በሚለው ንግግሩ፡- እናቱ በማለት እናትነትዋን ተናግሮአል፡፡ አንዳንዶች ፡- ከማርያም ሥጋ አልነሳም ለማለት የሚደፍሩ አሉ፡፡ እናት የተባለቸው በሥጋ ከእርስዋ ስለ ተወለደ ነው፡፡ ዮሴፍና ማርያም ስለ ፈለጉት ብላቴናው ኢየሱስ ፡- በአባቴ ቤት በሚለው ንግግሩ ፡- አባቴ  ያለው አብን ሲሆን ንግግሩ ግን አልገባቸውም፡፡ ኢየሱስ የአብ ልጅ ነው፡፡ የአብ ልጅ ከድንግል ማርያም በሥጋ ተወለደ፡፡ እናቱ ማርያም ፡- ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ ትጠብቀው ነበር በማለት ለሁለተኛ ጊዜ ሉቃስ ድንግል ማርያም በልብዋ የምትጠብቅ ልባም ሴት መሆንዋን ደገመልን፡፡ እንደ ድንግል ማርያም በልባችን ልንጠብቅ የሚገባን ነገር አለ፡፡ እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ለኛ የሆነ ነገር ሊናገረን ይችላል፡፡ ሁሉን ግን ለሰው የምንነግረው አይደለም፡፡ እንደ ቅድስት ድንግል ማርያም ነገሩን እያሰብነው በልባችን ልንጠብቅ የሚገባን ነገር ይኖራል፡፡ ጸጋ የሞላበት ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው ፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ ፣ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻል የተባለች፣ ጌታችን ኢየሱስን ጸንሳ የወለደች ሆና ሳለ በልብዋ መጠበቅ ያለባትን በልብዋ ትጠብቅ የነበረች መሆንዋን ስናይ ከእርስዋ በልባችን የመጠበቅ ትልቅ ትምህርት እንድንወስድ ያደርገናል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
134
16
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
105
17
የሐዋርያት ሥራ ጥናት ፡፡ ክፍል 78 ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በሮም እስር ቤት ፡፡   ከክፍል 77 ባጭሩ ፡፡ ..ወደ ሮሜም በገባን ጊዜ ጳውሎስ ከሚጠብቀው ወታደር ጋር ለብቻው ይቀመጥ ዘንድ ተፈቀደለት ( የሐዋ 28 ÷ 11 – 16 ) ። ---//---   ከሦስት ቀንም በኋላ ጳውሎስ የአይሁድን ታላላቆች ወደ እርሱ ጠራ፤ በተሰበሰቡም ጊዜ እንዲህ አላቸው። ወንድሞች ሆይ፥ እኔ ሕዝቡን ወይም የአባቶችን ሥርዓት የሚቃወም አንዳች ሳላደርግ፥ ከኢየሩሳሌም እንደ ታሰርሁ በሮማውያን እጅ አሳልፈው ሰጡኝ። እነርሱም መርምረው ለሞት የሚገባ ምክንያት ስላልነበረብኝ ሊፈቱኝ አሰቡ፤ አይሁድ ግን በተቃወሙ ጊዜ፥ ወደ ቄሣር ይግባኝ እንድል ግድ ሆነብኝ እንጂ ሕዝቤን የምከስበት ነገር ኖሮኝ አይደለም። ስለዚህም ምክንያት አያችሁና እነግራችሁ ዘንድ ጠራኋችሁ፤ ስለ እስራኤል ተስፋ ይህን ሰንሰለት ለብሻለሁና። እነርሱም፡- እኛ ከይሁዳ ስለ አንተ ደብዳቤ አልተቀበልንም፥ ከወንድሞችም አንድ ስንኳ መጥቶ ስለ አንተ ክፉ ነገር አላወራልንም ወይም አልተናገረብህም። ነገር ግን ስለዚህ ወገን በየስፍራው ሁሉ እንዲቃወሙ በእኛ ዘንድ ታውቆአልና የምታስበውን ከአንተ እንሰማ ዘንድ እንፈቅዳለን አሉት። ቀንም ቀጥረውለት ብዙ ሆነው ወደ መኖሪያው ወደ እርሱ መጡ፤ ስለ እግዚአብሔር መንግሥትም እየመሰከረ ስለ ኢየሱስም ከሙሴ ሕግና ከነቢያት ጠቅሶ እያስረዳቸው፥ ከጥዋት ጀምሮ እስከ ማታ ድረስ ይገልጥላቸው ነበር። እኵሌቶቹም የተናገረውን አመኑ፥ እኵሌቶቹ ግን አላመኑም፤ እርስ በርሳቸውም ባልተስማሙ ጊዜ፥ ጳውሎስ አንዲት ቃል ከተናገረ በኋላ ሄዱ፤ እንዲህም አለ። መንፈስ ቅዱስ በነቢዩ በኢሳይያስ ለአባቶቻችን፡- ወደዚህ ሕዝብ ሂድና። መስማትን ትሰማላችሁና አታስተውሉም፥ ማየትንም ታያላችሁና አትመለከቱም፤ በዓይናቸው እንዳያዩ በጆሮአቸው እንዳይሰሙ በልባቸውም እንዳያስተውሉ ተመልሰውም እንዳልፈውሳቸው፥ የዚህ ሕዝብ ልብ ደንድኖአል ጆሮአቸውም ደንቁሮአል ዓይናቸውንም ጨፍነዋል በላቸው ሲል መልካም ተናገረ። እንግዲህ ይህ የእግዚአብሔር ደኅንነት ለአሕዛብ እንደ ተላከ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን፤ እነርሱ ደግሞ ይሰሙታል። ይህንም በተናገረ ጊዜ አይሁድ እርስ በርሳቸው እጅግ እየተከራከሩ ሄዱ። ጳውሎስም በተከራየው ቤት ሁለት ዓመት ሙሉ ተቀመጠ፥ ወደ እርሱም የሚመጡትን ሁሉ ይቀበል ነበር፤ ማንም ሳይከለክለው የእግዚአብሔርን መንግሥት እየሰበከ ስለ ጌታ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እጅግ ገልጦ ያስተምር ነበር ( የሐዋ 28 ÷ 17 – 31 ) ።   ማብራሪያ ቅዱስ ጳውሎስ በሮም አገር በተከራየው ቤት ተብሎ በተጠቀሰው አንድ ክፍል ውስጥ ብቻውን  የታሰረ ሲሆን መታሰሩም ስለ ወንጌል ሲል እንጂ የሚያሳስረው ነገር ተገኝቶበት አይደለም፡፡ ለጠራቸው ለአይሁድ ታላላቆች የአባቶችን ሥርዓት በመቃወም እንዳልታሰረ አስረዳቸው፡፡ እነርሱም ስለ እርሱ ምንም ክፉ እንዳልሰሙ ነገሩት፡፡ ስለሚያስተምረው ትምህርት ግን የሚቃወሙ ሰዎች እንዳሉና የሚያስተምረውንም ለመስማት ፈልገው በቀጠሮ ተለያዩ፡፡ በቀጠሮአቸው ቀን ስለ ጌታችን ኢየሱስ ከሙሴ ሕግና ከነቢያት ጠቅሶ አስረዳቸው፡፡ ግማሾቹ ሲቃወሙት ግማሾቹ ተቀበሉት፡፡ ላልተቀበሉት ደግሞ በነቢዩ ኢሳይያስ ፡- ትሰማላችሁ ግን አታስተውሉም ተብሎ የተነገረው ትንቢት እንደ ተፈጸመባቸው አስረዳ፡፡ ትምህርቱን የተቀበሉትና ያልተቀበሉት አይሁድ እየተከራከሩ ሄዱ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በእስር ቤትም ሆኖ ስለ ክርስቶስ መስበኩን አልተወም፡፡ በሮም እስር ቤት ሁለት ዓመት ፣ ወደ ሮም ከመምጣቱ በፊት 2 ዓመት መታሰሩ ይታወቃል፡፡ በድምሩ ሳይፈታ አራት ዓመት በእስር ላይ መሆኑ ነው፡፡ መከራ ሲገጥመን ከአዲስ ኪዳን የቅዱስ ጳውሎስን ታሪክ ስናስብ እኛ እየደረሰብን ያለው በጣም ትንሽ መሆኑን ስለምንረዳ እንድንበረታ ያደርገናል፡፡ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ያሉትን የሌሎችንም የቅዱሳንን ሕይወት ማወቅ ለክርስትና ሕይወታችን በእጅጉ ይረዳናል፡፡  በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን በጥር 3 ቅዳሴ ሲቀደስ ከበላይ የጠቀስኩት ክፍል ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌን ይመልከቱ ) ፡፡ የሐዋርያት ሥራን እንድናጠና አነሳስቶ ላስጀመረኝ፣ አስጀምሮም ላስጨረሰኝ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፡፡ ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
107
18
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
91
19
ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው ማለት ምን ለማለት ነው?   እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን ይከሳቸዋል? የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው፥ የሚኰንንስ ማን ነው? የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው ( ሮሜ 8 ÷ 33 ፡ 34 ) ።   ማብራሪያ ከበላይ ያለው ሀሳብ እንዲህ ለማለት ነው ፡፡ እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን ይከሳቸዋል? ለሚለው መጠይቅ መልሱ ፡- ማንም ሊከሳቸው አይችልም:: ያጸደቃቸው እግዚአብሔር ነውና ፡፡ የሚኰንንስ ማነው ? ለሚለው መጠይቅ ደግሞ ፡- የሞተልን ከሙታንም ተነሥቶ በእግዚአብሔር ቀኝ በክብር ያለው ስለኛ የሚማልደው ኢየሱስ ክርስቶስማ አይፈርድብንም ፡፡ ስለ እኛ የሚማልደው የሚለውን ገና አላብራራሁትም ፡፡ ስለ እኛ የሚማልደው የሚለው ቃል በግሪኩም በግዕዙም አለ፡፡ በግሪኩ ፡- ኢንቱካኔይ ይለዋል ፡፡ በግዕዙ ፡- ወትዋቀሥ በእንቲአነ ( ስለኛ የሚከራከረው ) ይለዋል ፡፡ ስለኛ የሚማልደው ሲል በሰማይ ሆኖ ስለኛ ይለምናል ማለት ግን አይደለም ፡፡ በሰማይ ሆኖ አይለምንም ፡፡ በዚያም ቀን በስሜ ትለምናላችሁ ፡ እኔም ስለ እናንተ አብን እንድለምን የምላችሁ አይደለሁም ( ዮሐ 16 ÷ 26 ) ፡፡ ስለዚህ የምንለምነው እኛ ነን እንጂ እርሱ በአብ ቀኝ ሆኖ እንደማይለምን አስቀድሞ በምድር እያለ ተናግሮአል ፡፡ በምድር እያለ ግን ወደ አባቱ ይለምን ነበር ፡፡ ሁላችንም የምናውቀውን እንኳን ብጠቅስ ሰቅለውት እያሉ ፡-  አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁትምና ይቅር በላቸው ( ሉቃ 23 ÷ 24 )  ) ብሎአል ፡፡ ታዲያ ፡- በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ምን ለማለት ነው? ክርስቶስ በአብ ቀኝ ቢቀመጥም አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦልን ነው ፡፡ እርሱ ግን ( ክርስቶስ ) ስለ ኃጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ተቀመጠ ( ዕብ 10 ÷ 12  ) ፡፡ በብሉይ ኪዳን ሰዎች ስለ ኃጢአታቸው መሥዋዕት ያቀርቡ ነበር ፡፡ መልሰው ሲበድሉ ሌላ መሥዋዕት ያቀርቡ ነበር ፡፡ ክርስቶስ ግን ስለኛ ራሱን መሥዋዕት አድርጎ ያቀረበልን ለዘላለም ነው ፡፡ እግዚአብሔርን ስንበድል መጥቶ እንደ ገና እንዳይሞትልን አንድን መሥዋዕት ለዘላለም ነው ያቀረበልን ፡፡ ስለኛ የሚማልደው የሚለው ራሱን መሥዋዕት አድርጎ ለዘላለም ስላቀረበልን ነው ፡፡ የክርስቶስ የማዳን ሥራ ቀራንዮ ላይ የቆመ ሳይሆን እስከ ዓለም ፍጻሜ ነው፡፡ መሥዋዕት አድርጎ በቀራንዮ ራሱን አሳልፎ በመስጠቱ ከአባቱ ጋር አስታርቆናል ፡፡ ጠላቶች ሳለን ከእግዚአብሔር ጋር በልጁ ሞት ከታረቅን ( ሮሜ 5 ÷ 10  ) ስለሚል ከአባቱ ጋር በእርሱ ሞት መታረቅን አግኝተናል፡፡ በልጁ ሞት ስላለ ልጁ የተባለው ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ፡፡ በጥንትዋ ኦርቶዶክሳዊት አስተምህሮም የክርስቶስ አስታራቂነት ይታመናል ፡፡ ዳግመኛ ክርስቶስ ሰው ከመሆኑ የተነሣ ምንም ምን ሕፀፅ እንደሌለበት እናምናለን፤ በእውነት ሰው የሆነ እግዚአብሔር ቃል ነው እንጂ ፤ ወደ አብ አስታራቂያችን የሚሆን እርሱ ሰውን ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀ ( የቤተ ክርስቲያን ጸሎት ገጽ 47 ) ፡፡ ሰው ከሆነ በኋላም … መሲህ ፣  ኢየሱስ ፣ … አስታራቂ …ተባለ ( ዘቄርሎስ ም 81 ቁ 8 ) ፡፡ ከጊዜ አካያ እንጂ ሌሎች ብዙ ማስረጃዎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ የክርስቶስ አስታራቂነት አሁንም ይታመናል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ሊቅ ብላ ከምትጠራቸው አባቶች መካከል አንዱ ከሆኑት እኔም ተምሬአለሁ ፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር ስለታረቅን እኮ ነው ቀጥታ፡- አባታችን ሆይ በሰማይ የምትኖር… ብለን መጸለይ የቻልነው ፡፡ ክርስቶስ  እንድን መሥዋዕት ለዘላለም ስላቀረበልን አንዳችን ለሌላችን የምንጸልየውን ጸሎት አያስቀርም፡፡ እያንዳንዱ ሰለ ሌላው ይጸልይ ( ያዕ 3 ÷ 16  )  ተብሎአል ፡፡ አንዳችን ለሌላችን የምንጸልየው ጸሎት ምልጃ ይባላል፡፡ እኔ እዚህ እንድደርስ በእግዚአብሔር ቸርነት የአባቶቼ ምልጃ አግዞኛል፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወታችን እየበረታን ስንመጣ እኛ ራሳችን  ስለ ራሳችን መጸለይ እንጀምራለን ፡፡ ስለ ሥጋችን ድካም ላንሳ  ፡፡ ሁሌ እየበረቱ መኖር ከባድ ነው ፡፡ አንዳንዴ በእግዚአብሔር ቤት አለን እንዳይባል የለንም፡፡ የለንም እንዳይባል አለን ፡፡ በዚህ ጊዜ ደግሞ በሌሎች ሰዎች ስለ እኛ የሚደረገው ምልጃ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት አለው፡፡ ወደባሰው ደረጃ ልውረድ በዚህ ዘመን ያለን ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት ትተን በራሳችን ፈቃድ ተመላለስን እንበል፡፡ እግዚአብሔር ፈጽሞ አይተወንም፡፡ ለቤተ ክርስቲያን የሞተላት ክርስቶስ ከኛ በፊት ያሉት ደጋግ አባቶች የጸለዩትን ልመና ያስባል ፡፡ ከኛ በፊት ያሉት ደጋግ አባቶቻቸን እኛን ልጆቸውን ለእግዚአብሔር አደራ ብለው ያለፉ ናቸውና ፡፡ እግዚአብሔር ምልጃቸውን አስቦ ወደ ልባችንም እንደ ገና ይመልሰናል ፡፡ ክርስትና ከምድር ላይ ፈጽሞ እንዲጠፋ አይፈልግምና ፡፡ ለምሳሌ አንድ እናት በሞት አፋፋ ናት እንበል ፡፡ ይህቺ እናት ሕጻን ስለ ሆነው ልጅዋ በእግዚአብሔር ፊት በዘመኑ ሁሉ ጠብቀው ብላ በእምነት ጸልያለት ብትሞት እግዚአብሔር አስቀድማ በአካለ ሥጋ በነበረችበት ዘመን ስለ ልጅዋ የጸለየችውን ጸሎት ሰምቶ ልጅዋን ከክፉ ይጠብቀዋል ፡፡ እግዚአብሔር አብርሃም ሞቶ ለልጁ ለይስሐቅ ፡- ስለ ባርያዬ ስለ አብርሃም  ዘርህን አበዛለሁ ( ዘፍጥ 26 ÷ 23፡24 ) ፡፡ ዳዊት ሞቶ ሳለ፡- ስለ ባሪያዬ ስለ ዳዊት ይህችን ከተማ እጋርዳታለሁ   ( 2ነገ 19 ÷ 34   )  በማለት ባለማሎቹ ከሞቱ በኋላ እንኳን ስለ እነርሱ ሲል የሚያደርገውን መጽሐፍ ቅዱስ ያስነበብናል ፡፡ መጀመሪያ የተነሣሁበትን ሐሳብ ጠቅለል ሳደርገው ክርስቶስ በአብ ቀኝ ሆኖ አይለምንም ፡፡ እንዲያውም እርሱ ራሱ የሚለመን አምላክ ነው ፡፡ ሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሲወገር ፡- …ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና ..ጌታ ኢየሱስ ሆይ ነፍሴን ተቀበል ብሎ ለምኖታል ( የሐዋ 7 ÷ 59  ) ፡፡ ቃሉ እንደሚነግረን በእግዚአብሔር ቀኝ ሆኖ ያየውን  ጌታችን ኢየሱስን ነው የለመነው ፡፡ ስለዚህ ስለኛ የሚማልደው የሚለው ከአባቱ ጋር የታረቅንበትን አንድን መሥዋዕት ለዘላለም ስላቀረበልን ነው ፡፡ በሞቱ ከአባቱ ጋር አስታርቆናል ፡፡ ከአባቱ ጋርም ስላስታረቀን ከአባቱ አያንስም ፡፡ ክርስቶስ ደግሞ ይቅር እንዳላችሁ ( ቆላ 3 ÷ 13  ) ሲለሚል ራሱም ክርስቶስ ይቅር ብሎናል ፡፡ በሌላ ጊዜም ግልጽና በቀላሉ ሊገባን በሚችል መልኩ ሀሳቡን እንደ ገና ማንሳቴ አይቀርም ፡፡  በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን በሌሎች ጊዜያትም እንዲሁም በሐምሌ 13 ቅዳሴ ሲቀደስና ከ18 - 35 ያለው በሚነበብ ሰዓት ከበላይ የጠቀስኩት ክፍል ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌን ይመልከቱ ) ፡፡ ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
153
20
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
106