uk
Feedback
እግዚአብሔርን ማወቅ

እግዚአብሔርን ማወቅ

Відкрити в Telegram

ሰላምታ በተለዋወጥን ቁጥር ይመስገን ስለምንለው አምላካችንና አባታችን እግዚአብሔር ያለንን ዕውቀት ለማዳበር የሚያግዝ ቻነል ነው፡፡

Показати більше
925
Підписники
+224 години
+127 днів
+1130 день

Триває завантаження даних...

Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
червень '26
червень '26
+41
в 0 каналах
травень '26
+31
в 0 каналах
Get PRO
квітень '26
+45
в 0 каналах
Get PRO
березень '26
+33
в 0 каналах
Get PRO
лютий '26
+49
в 0 каналах
Get PRO
січень '26
+45
в 0 каналах
Get PRO
грудень '25
+54
в 0 каналах
Get PRO
листопад '25
+38
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '25
+37
в 0 каналах
Get PRO
вересень '25
+31
в 0 каналах
Get PRO
серпень '25
+32
в 0 каналах
Get PRO
липень '25
+45
в 0 каналах
Get PRO
червень '25
+49
в 0 каналах
Get PRO
травень '25
+24
в 0 каналах
Get PRO
квітень '25
+19
в 0 каналах
Get PRO
березень '25
+18
в 0 каналах
Get PRO
лютий '25
+11
в 0 каналах
Get PRO
січень '25
+9
в 0 каналах
Get PRO
грудень '24
+19
в 0 каналах
Get PRO
листопад '24
+25
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '24
+27
в 0 каналах
Get PRO
вересень '24
+17
в 0 каналах
Get PRO
серпень '24
+20
в 0 каналах
Get PRO
липень '24
+35
в 0 каналах
Get PRO
червень '24
+21
в 0 каналах
Get PRO
травень '24
+23
в 0 каналах
Get PRO
квітень '24
+12
в 0 каналах
Get PRO
березень '24
+31
в 0 каналах
Get PRO
лютий '24
+11
в 0 каналах
Get PRO
січень '24
+15
в 0 каналах
Get PRO
грудень '23
+15
в 0 каналах
Get PRO
листопад '23
+12
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '23
+13
в 0 каналах
Get PRO
вересень '23
+479
в 0 каналах
Дата
Залучення підписників
Згадування
Канали
28 червня0
27 червня+2
26 червня+3
25 червня+2
24 червня+1
23 червня+2
22 червня+4
21 червня+2
20 червня+1
19 червня0
18 червня+1
17 червня+1
16 червня+1
15 червня0
14 червня0
13 червня+1
12 червня+2
11 червня0
10 червня+1
09 червня+1
08 червня+3
07 червня+2
06 червня+2
05 червня+1
04 червня+1
03 червня+1
02 червня+4
01 червня+2
Дописи каналу
የሐዋርያት ሥራ ጥናት ፡፡ ክፍል 25 ፡፡ ፈውስ ፡፡   ጴጥሮስም በየስፍራው ሁሉ ሲዞር በልዳ ወደሚኖሩ ቅዱሳን ደግሞ ወረደ። በዚያም ከስምንት ዓመት ጀምሮ በአልጋ ላይ ተኝቶ የነበረውን ኤንያ የሚሉትን አንድ ሰው አገኘ፤ እርሱም ሽባ ነበረ። ጴጥሮስም፡- ኤንያ ሆይ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ይፈውስሃል፤ ተነሣ ለራስህም አንጥፍ አለው። ወዲያውም ተነሣ። በልዳና በሰሮናም የሚኖሩ ሁሉ እርሱን አይተው ወደ ጌታ ዘወር አሉ። በኢዮጴም ጣቢታ የሚሉአት አንዲት ደቀ መዝሙር ነበረች፥ ትርጓሜውም ዶርቃ ማለት ነው፤ እርስዋም መልካም ነገር የሞላባት ምጽዋትም የምታደርግ ነበረች። በዚያም ወራት ታመመችና ሞተች፤ አጥበውም በሰገነት አኖሩአት። ልዳም ለኢዮጴ ቅርብ ናትና ደቀ መዛሙርት ጴጥሮስ በዚያ እንዳለ ሰምተው፥ ወደ እነርሱ ከመምጣት እንዳይዘገይ እየለመኑ ሁለት ሰዎች ወደ እርሱ ላኩ። ጴጥሮስም ተነሥቶ ከእነርሱ ጋር መጣ፤ በደረሰም ጊዜ በሰገነት አወጡት መበለቶችም ሁሉ እያለቀሱ ዶርቃ ከእነርሱ ጋር ሳለች ያደረገቻቸውን ቀሚሶችንና ልብሶችን ሁሉ እያሳዩት በፊቱ ቆሙ። ጴጥሮስም ሁሉን ወደ ውጭ አስወጥቶ ተንበርክኮም ጸለየ፥ ወደ ሬሳውም ዘወር ብሎ። ጣቢታ ሆይ፥ ተነሺ አላት። እርስዋም ዓይኖችዋን ከፈተች ጴጥሮስንም ባየች ጊዜ ተቀመጠች። እጁንም ለእርስዋ ሰጥቶ አስነሣት፤ ቅዱሳንንና መበለቶችንም ጠራ ሕያውም ሆና በፊታቸው አቆማት። ይህም በኢዮጴ ሁሉ የታወቀ ሆነ፥ ብዙ ሰዎችም በጌታ አመኑ። በኢዮጴም ስምዖን ከሚሉት ከአንድ ቍርበት ፋቂ ጋር አያሌ ቀን ኖረ ( የሐዋ 9 ÷ 32 - 43 ) ።   ማብራሪያ በችኩልነቱ እንዲሁም ፡- አላውቅህም ብሎ ክርስቶስን የካደው ጴጥሮስ ከስምንት ዓመት ጀምሮ ሽባ ሆኖ የኖረውን ሰው ፡- ኢየሱስ ክርስቶስ ይፈውስሃል በማለት ፈወሰው፡፡ ፈውስ የሚደረገው በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ነው፡፡ የፈውሱ ዓላማ ደግሞ ሰዎች በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እንዲያምኑ ነው፡፡ ሌላው በጴጥሮስ የተፈጸመው ተአምር ደግሞ ከሞት የተነሣችው ጣቢታ የምትባል ሴት ናት፡፡ ጣቢታ ምጽዋት የምታደርግ ሴት ነበረች፡፡ ምጽዋት ለሌሎች ካለን ላይ ማካፈልን ያመለክታል፡፡ ምጽዋት በእግዚአብሔር ዘንድ ደስ የሚያሰኝ ሥራ ነው፡፡ ይህች ሴት ደቀ መዝሙር ነበረች ስለሚል በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ያመነች ነበረች፡፡ ታማ ብትሞትም ቅዱስ ጴጥሮስ ሲጸልይላት ከሞት ተነሥታለች፡፡ በእርስዋም በተሠራው ተአምር ብዙዎች በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምነዋል፡፡ በቅዱሳን ሐዋርያት ስብከትና በሚያደርጉትም ተአምራት ወንጌል እየተስፋፋ መምጣቱን እናያለን፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በጥር 30ና በሐምሌ 1 ቅዳሴ ሲቀደስ ከበላይ ከጠቀስኩት ከፊሉ ከቁ . 36 - ቁ.43 ያለው ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌ ) ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ይቀጥላል፡፡ ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie

2
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
10
3
የአፌ ቃልና የልቤ አሳብ በፊትህ ያማረ ይሁን።    አቤቱ፥ ረድኤቴ መድኃኒቴም፥ የአፌ ቃልና የልቤ አሳብ በፊትህ ያማረ ይሁን ( መዝ 18(19) ÷ 14 ) ።    ማብራሪያ አፍ ( አንደበት ) የሚናገረው በልብ ውስጥ የሞላውን ነው፡፡ ልቡ በክፋት የተሞላ ሰው አንደበቱ የሚያወጣው ቃል መልካምና የሚያንጽ ሊሆን አይችልም፡፡ ልቡ በመልካም ነገር የተሞላ ሰው ግን ከአንደበቱ መልካም የሆነ ነገርን ያወጣል፡፡ በፍቅር የተሞላ ልብ ሁሌም የአፉ ቃል ያማሩ ናቸው፡፡ ልብንና አንደበትን እንደ መጠበቅ ከባድ ነገር የለም፡፡ ከልባችን ሞልቶ አንደበታችን የሚያወጣው ክፉ ቃል ከሆነ ሰዎችንና እግዚአብሔርን እናሳዝናለን፡፡ ክፉ ቃል መናገር የማንፈልግ አንኳን ሆነን ተናጋሪ ሰው የሚያናግረን ጊዜ አለ፡፡ ተናግሮ አናጋሪን ያዝልን የምንለው የተናጋሪው የአንደበት ቃል ያማረ ካልሆነ ለተናገረን ክፉ ቃል አጸፋውን ስንሰጥ እኛም ክፉ ቃል ከአፋችን እንዳይወጣ የማንፈልገው ሳንቀር በአናጋሪው ተገደን ያማረ ቃል ላናወጣ ስለምንችል ነው፡፡ በቃል ( በንግግር ) የማይሳሳት ደግሞ ማንም የለም፡፡ የአንደበት ቃል መልካም ካልሆነ ምን ያህል እንደሚጎዳ ሁላችን እናውቃለን፡፡ ሰዎች ተናግረውን ተጎድተን የምናውቅ ብዙ አለን፡፡ ታዲያ እኛም እንዳንጎዳ መጠንቀቅ አለብን፡፡ ያማረ የሚለው ቃል ግልጽ በመሆኑ ቃሉን ለመፍታት ምንም አስፈላጊ አይደለም፡፡ ይልቅስ ያማረ ብለን የምንጠራው ነገር ምን አለ? ለእያንዳንዳችን የተለያየ ነገር ያማረ ሆኖ ይታየናል፡፡ ልክ ያማረ ነው ብለን እንዳሰብነው ነገር፡- የአፌ ቃልና የልቤ አሳብ በፊትህ ያማረ ይሁን ብሎ ከመጸለይ ውጪ ያማረ ነገር የለም፡፡ ማንኛውም የልባችን ሀሳብና የአፋችን ቃል ያማረ እንዲሆን አምላካችንን በዚህ ቃል እንደ መዝሙረኛው ብንለምነው ይሰማናል፡፡ እንደዚህ ያለውን ጸሎትማ አምላካችን ይወደዋል፡፡ ሰላም የሚሰጠውን ቃልህን የምታስተምረን አምላካችን ሆይ እናመሰግንሃለን፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
66
4
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
51
5
የሐዋርያት ሥራ ጥናት ፡፡ ክፍል 24 ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ጌታችን ኢየሱስ ስም ደፍሮ መናገሩ ፡፡   ከክፍል 23 በጥቂቱ ፡፡ ሳውል ( ጳውሎስ ) ግን የጌታን ደቀ መዛሙርት እንዲገድላቸው ገና እየዛተ ..ሄደ፥ ..ሲሄድም ወደ ደማስቆ በቀረበ ጊዜ ድንገት በእርሱ ዙሪያ ከሰማይ ብርሃን አንጸባረቀ፤ በምድርም ላይ ወድቆ ሳለ፡- ሳውል ሳውል፥ ስለ ምን ታሳድደኛለህ? የሚለውን ድምፅ ሰማ። ጌታ ሆይ፥ ማን ነህ? አለው። እርሱም፡- አንተ የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ፤ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል አለው። እየተንቀጠቀጠና እየተደነቀ፡- ጌታ ሆይ፥ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ? አለው። ጌታም፡- ተነሥተህ ወደ ከተማ ግባና ታደርገው ዘንድ የሚያስፈልግህን ይነግሩሃል አለው። ..ሐናንያም ..እጁንም ጭኖበት፡-፣ ወንድሜ ሳውል ሆይ፥ ጌታ፥ እርሱም በመጣህበት መንገድ የታየህ ኢየሱስ ነው፥ ደግሞ ታይ ዘንድና መንፈስ ቅዱስ ይሞላብህ ዘንድ ላከኝ አለ። ..ተነሥቶም ተጠመቀ፥ ..ወዲያውም ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በምኵራቦቹ ሰበከ.. ( የሐዋ 9 ÷1 - 25 ) ። -------------///////----------   ሳውልም ወደ ኢየሩሳሌም በደረሰ ጊዜ ከደቀ መዛሙርት ጋር ይተባበር ዘንድ ሞከረ፤ ሁሉም ደቀ መዝሙር እንደ ሆነ ስላላመኑ ፈሩት። በርናባስ ግን ወስዶ ወደ ሐዋርያት አገባውና ጌታን በመንገድ እንዴት እንዳየውና እንደ ተናገረው በደማስቆም በኢየሱስ ስም ደፍሮ እንዴት እንደ ነገረ ተረከላቸው። በጌታም በኢየሱስ ስም ደፍሮ እየተናገረ በኢየሩሳሌም ሲወጣና ሲገባ ከእነርሱ ጋር ነበረ፤ ከግሪክ አገርም መጥተው ከነበሩት አይሁድ ጋር ይነጋገርና ይከራከር ነበር፤ እነርሱ ግን ሊገድሉት ፈለጉ።  ወንድሞችም ይህን ባወቁ ጊዜ ወደ ቂሣርያ ወሰዱት ወደ ጠርሴስም ሰደዱት። በይሁዳም ሁሉና በገሊላ በሰማርያም የነበሩት አብያተ ክርስቲያናት በሰላም ኖሩ ታነጹም፤ በእግዚአብሔርም ፍርሃትና በመንፈስ ቅዱስ መጽናናት እየሄዱ ይበዙ ነበር ( የሐዋ 9 ÷ 26 - 31 )    ። ማብራሪያ ቅዱስ ጳውሎስ የመጀመሪያው ስሙ ሳውል እንደ ነበር አይተናል፡፡ በሰማዕቱ እስጢፋኖስ መገደል የተስማማው ሳውል ሌሎችም በጌታችን በኢየሱስ ያመኑ ሰዎች እንዲታሰሩ ያደርግ ነበር፡፡ ወደ ደማስቆ ሲሄድ ግን፡-  የምታሳድደኝ እኔ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ ያለው ክርስቶስ የሚያሳድደውን ሳውልን ለራሱ ምርጥ ዕቃ አደረገው፡፡ ሳውልም ያሳድድው ስለ ነበረው ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን መሰከረ፡፡ ሳውል የድንግል ማርያም ልጅ ስለ መሆኑ ያልመሰከረው ጠፍቶት አይደለም፡፡ ከማርያም መወለዱን አይሁድ ያምኑ ነበር፡፡ የአብ ልጅ መሆኑን ግን አላመኑበትም ስለዚህም ነው የእግዚአብሔር ልጅ ነው ብሎ የመሰከረው፡፡ የገዛ ወገኖቹ አይሁድ ሊገድሉት ስላሰቡ ከደማስቆ ወደ ኢየሩሳሌም ሸሽቶ አመለጠ፡፡ ወደ ኢየሩሳሌም በመጣ ጊዜ በክርስቶስ ካመኑት ደቀ መዛሙርት ጋር ሊተባበር ሲሞክር ሁሉም ፈሩት፡፡ ቀድሞ ያሳድዳቸው ስለ ነበር አሁን ለዛ ዓላማ የመጣ ነበር የመሰላቸው፡፡ በርናባስ ግን ወደ ሐዋርያት ወስዶት ጌታችን በደማስቆ እንደ ተገለጠለትና በኢየሱስ ስምም ደፍሮ እየተናገረ መሆኑን አስታወቃቸው፡፡ ሳውል በኢየሱስ ስም ደፍሮ መናገሩን በኢየሩሳሌምም ሳለ  አልተወም ነበር፡፡ አይሁድ በመግደል ያምኑ ነበርና ሊገድሉት ሲሉ ወደ ተወለደባት ጠርሴስ ሄደ ፡፡ ወደ ፊት የሳውልን ታሪክ ስናይ ታሪኩ የሚጀምረው ከጠርሴስ ነው፡   በቁ31 አብያተ ክርስቲያናት የሚላቸው በክርስቶስ ያመኑትን የምዕመናንን ስብስብ ( ሕብረት ) ነው፡፡ መከራና ስደት ቢበዛባቸውም እንዳይበዙ ግን ሊያግዳቸው አልቻለም፡፡ እግዚአብሔርን በመፍራት ይመላለሱ ነበር፡፡ መንፈስ ቅዱስም ያጽናናቸው ነበር፡፡ በሐዋርያት ሥራ ልናየው የተፈለገው የጌታችን ወንጌል እንዴት እንደ ተሰበከ ነው፡፡  ወንጌል ማለት ምሥራች ማለቱ ሲሆን እኛን ሊያድነን የመጣው ከቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደው ኢየሱስ እንደ ሆነ ነው፡፡ የነቢያት ትንቢታቸው ተፈጽሞ ሐዋርያት ስብከታቸው አድርገውታል፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በየካቲት 20ና 23 ቅዳሴ በሚቀደስበት ጊዜ የሐዋ 9 ÷ 23 - 32 ያለው ሲነበብ ከበላይ የጠቀስኩት ክፍል ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌ ) ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ይቀጥላል፡፡ ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
58
6
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
50
7
በእርሱ ( በክርስቶስ ) ድህነት ባለ ጠጎች ሆንን ፡፡   የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቸር ስጦታ አውቃችኋልና፤ ሀብታም ሲሆን፥ እናንተ በእርሱ ድህነት ባለ ጠጎች ትሆኑ ዘንድ ስለ እናንተ ድሀ ሆነ ( 2ቆሮ 8 ÷ 9 ) ።   ማብራሪያ ሐዋርያው ጳውሎስ ከበላይ ስለ ክርስቶስ ያለውን ሀሳብ ያነሳበት ምክንያት አለው ፡፡ ከክርስቶስ ምን ልንማር እንደምንችል በምፈልግበት ጊዜ ወደፊት የማነሳው ይሆናል፡፡ ለዛሬ ግን ትኩረት መስጠት የፈለግኩት የክርስቶስን ቸር ስጦታ ነው ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቸር ነው ፡፡ ቸር ነው የምንለውም እጅግ ለጋስ በመሆኑ ነው ፡፡ ቸር መሆኑን ደግሞ በመስማት ሳይሆን ተደርጎልንም አይተናል፡፡ ለምነነው እንዲሁ የሰጠን በቍጥር ገልጠን የማንጨርሰው ብዙ ነገር አለ ፡፡ ሐዋርያው የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስ ቸር ስጦታ የገለጠበት መንገድ እጅግ ደስ በሚያሰኝ መልኩ ነው ፡፡  ሀብታም ሲሆን ድሀ ሆነ ይለናል ፡፡ ሀብታም ሲከስር ድሀ ሊሆን ይችላል ፡፡ ይሄ የሚያከራክር ነገር አይደለም ፡፡ ክርስቶስ ግን ድሀ የሆነው ስለ እናንተ ነው ይለናል ፡፡ ክርስቶስ ከክበሩ ራሱን ዝቅ አድርጎ የኛን ሥጋ ለብሶ ሀብታም ሲሆን ምንም እንደ ሌለው ድሀ ሆኖ ተገለጠ ፡፡ እርሱ ድሀ የሆነው በእርሱ ድህነት እኛ ባለ ጠጎች እንድንሆን ነው ፡፡ ራሱን ድሀ አድርጎ ሌላውን ባለ ጠጋ ማን ያደርጋል? ያልኩት ይቅርና ቢሰጥ ያን ያህል ላይጎድልበት መለገስ የማይወድ ስንት ባለ ጠጋ አለ ? ክርስቶስ ለኛ ያልሆነው ምን አለ ? ሀብታም ሲሆን ራሱን ደሀ አደረገ ፡፡ ቍስ የሆነ ነገር ምንም ባይኖረን በእግዚአብሔር ነገር ባለ ጠጋ ተደርገናል ፡፡ ድሀ ሆነን ባለጠጋ ካደረገን እንዲህ የሆነልህ ክርስቶስ በምድራዊ ነገራችንስ እንዴት አይገደውም? ፡፡ እንዴትስ አያስብልንም ? ለሚቀድመው መንፈሳዊ ነገር እንዲህ ካደረገልን ለምድራዊ ነገራችን ደግሞ አያስብልንም ልንል አንችልም ፡፡ መንፈሳዊ ባለጠግነትን ስናነሳ ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት ድሀ ሊያውም የተራቆትን ነበርን ፡፡ ባለ ጠጋ እንድንሆን ስለ እኛ በመስቀል ላይ ተሰቀለ ፡፡ ታዲያ ድሀ ሆነን ሲያየን ባለ ጠጋ ያደረገንን ጌታ እንዴት አንወደው? እንዴትስ እስከ ሕይወታችን ፍጻሜ አንከተለው ? ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በድህነታችን የወደደን የድሀ ወዳጅ ነው ፡፡ ምንም የሌለውን ድሀን ማን ይወዳል ? ሊያውም ባለ ጠጋ ሆኖ ነው የወደደን ፡፡ ክርሰቶስ ድሀን የሚወድ ባለጠጋ ነው ፡፡ በአንድ ጊዜ ሰዎችን ባለ ጠጋ ስለሚያደርገው ሎተሪ ላንሳ ፡፡ ከፍተኛውን ብር የሚያስገኘው ዕጣ የወጣለት ሰው በአንዴ ባለጠጋ መሆን ይችላል እንጂ የቆረጡት በሚሊየን የሚቆጠሩት ሁሉ ግን ባለ ጠጋ መሆን አይችሉም ፡፡ ዕጣው የመጀመሪያን ዕድለኛ ሰውና እንደየደረጃቸው ጥቂቶችን ብቻ ባለ ጠጋ ያደርጋል ፡፡ በክርስቶስ ግን ባለጠጋ የተደረግነው ያመንነው ሁሉ ነን ፡፡ በኢትዮጵያ ብቻ ያለነው አይደለም ፡፡ በዓለም ሁሉ ላሉት ትክክለኛ የክርስትና አስተምህሮ ላላቸው ክርስቲያኖች ይሠራል ፡፡ እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ ቸር ማን አለ ? ያመኑትን ሁሉ ባለ ጠጋ እንዳደረገ እንደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያለስ ማን አለ ? በራሱም ፣ በአባቱም ፣ በመንፈስ ቅዱስም ፊት ራቁቱን በመሆኑ ኃፍረት እንደሚሰማው ሰው በመሆን ሳይሆን በወርቅ መጎናጸፊያ እንደ ተጎናጸፈ እንደ ባለ ጠጋ ሆነን እንድንቀርብ አድርጎናል ፡፡       እንግዲህ ተራቁተን የነበርን በክርስቶስ በማመናችን ባለጠጋ ተደርገናል ፡፡ እርሱ ስለ እኛ ተዋርዶ እኛን አክብሮናል ፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በሌሎች ጊዜያትም እንዲሁም በሕዳር 6 ቅዳሴ ሲቀደስና ከቁ 1 – 16 ያለው በሚነበብ ሰዓት ከበላይ የጠቀስኩት ክፍል ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌን ይመልከቱ ) ፡፡ ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
79
8
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
60
9
የሐዋርያት ሥራ ጥናት ፡፡ ክፍል 23 ፡፡ የቅዱስ ጳውሎስ መጠራት ፡፡   ሳውል ( ጳውሎስ ) ግን የጌታን ደቀ መዛሙርት እንዲገድላቸው ገና እየዛተ ወደ ሊቀ ካህናት ሄደ፥ በዚህ መንገድ ያሉትንም ሰዎች ወንዶችንም ሴቶችንም ቢያገኝ፥ እያሰረ ወደ ኢየሩሳሌም ያመጣቸው ዘንድ በደማስቆ ላሉት ምኵራቦች ደብዳቤ ከእርሱ ለመነ። ሲሄድም ወደ ደማስቆ በቀረበ ጊዜ ድንገት በእርሱ ዙሪያ ከሰማይ ብርሃን አንጸባረቀ፤ በምድርም ላይ ወድቆ ሳለ፡- ሳውል ሳውል፥ ስለ ምን ታሳድደኛለህ? የሚለውን ድምፅ ሰማ። ጌታ ሆይ፥ ማን ነህ? አለው። እርሱም፡- አንተ የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ፤ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል አለው። እየተንቀጠቀጠና እየተደነቀ፡- ጌታ ሆይ፥ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ? አለው። ጌታም፡- ተነሥተህ ወደ ከተማ ግባና ታደርገው ዘንድ የሚያስፈልግህን ይነግሩሃል አለው። ከእርሱም ጋር በመንገድ የሄዱ ሰዎች ድምፁን እየሰሙ ማንን ግን ሳያዩ እንደ ዲዳዎች ቁሙ። ሳውልም ከምድር ተነሣ፥ አይኖቹም በተከፈቱ ጊዜ ምንም አላየም፤ እጁንም ይዘው እየመሩ ወደ ደማስቆ አገቡት። ሳያይም ሦስት ቀን ኖረ፤ አልበላምም አልጠጣምም። በደማስቆም ሐናንያ የሚሉት አንድ ደቀ መዝሙር ነበረ፥ ጌታም በራእይ፡- ሐናንያ ሆይ፥ አለው፡፡ እርሱም፡- ጌታ ሆይ፥ እነሆኝ አለ። ጌታም፡- ተነሥተህ ቅን ወደ ሚባለው መንገድ ሂድ፥ በይሁዳ ቤትም ሳውል የሚሉትን አንድ የጠርሴስ ሰው ፈልግ፤ እነሆ፥ እርሱ ይጸልያልና፤ ሐናንያ የሚሉትም ሰው ገብቶ ደግሞ እንዲያይ እጁን ሲጭንበት አይቶአል አለው። ሐናንያም መልሶ፡- ጌታ ሆይ፥ በኢየሩሳሌም በቅዱሳንህ ላይ ስንት ክፉ እንዳደረገ ስለዚህ ሰው ከብዙዎች ሰምቼአለሁ፤ በዚህም ስምህን የሚጠሩትን ሁሉ ለማሰር ከካህናት አለቆች ሥልጣን አለው አለ። ጌታም፡- ይህ በአሕዛብም በነገሥታትም በእስራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፤ ስለ ስሜ ስንት መከራ ሊቀበል እንዲያስፈልገው እኔ አመለክተዋለሁና አለው፡፡ ሐናንያም ሄዶ ወደ ቤቱ ገባ፥ እጁንም ጭኖበት፡-፣ ወንድሜ ሳውል ሆይ፥ ጌታ፥ እርሱም በመጣህበት መንገድ የታየህ ኢየሱስ ነው፥ ደግሞ ታይ ዘንድና መንፈስ ቅዱስ ይሞላብህ ዘንድ ላከኝ አለ። ወዲያውም እንደ ቅርፊት ያለ ከዓይኑ ወደቀ፥ ያን ጊዜም ደግሞ አየ፤ ተነሥቶም ተጠመቀ፥ መብልም በልቶ በረታ። በደማስቆም ካሉት ደቀ መዛሙርት ጋር ጥቂት ቀን ኖረ። ወዲያውም ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በምኵራቦቹ ሰበከ። የሰሙትም ሁሉ ተገረሙና። ይህ በኢየሩሳሌም ይህን ስም የሚጠሩትን ያጠፋ አይደለምን? ስለዚህስ ታስረው ወደ ካህናት አለቆች ይወስዳቸው ዘንድ ወደዚህ አልመጣምን? አሉ ፡፡ ሳውል ጳውሎስ) ግን እየበረታ ሄደ፥ በደማስቆም ለተቀመጡት አይሁድ ይህ ክርስቶስ እንደ ሆነ አስረድቶ መልስ ያሳጣቸው ነበር። ብዙ ቀንም ሲሞላ አይሁድ ሊገድሉት ተማከሩ፤ ሳውል ግን አሳባቸውን አወቀ። ይገድሉትም ዘንድ በሌሊትና በቀን የከተማይቱን በር ሁሉ ይጠብቁ ነበር፤ ደቀ መዛሙርት ግን በሌሊት ወስደው በቅጥር ላይ አሳልፈው በቅርጫት አወረዱት ( የሐዋ 9 ÷ 1 - 25 ) ።   ማብራሪያ ቅዱስ ጳውሎስ የመጀመሪያው ስሙ ሳውል ነበር፡፡ ሳውል በሰማዕቱ እስጢፋኖስ መገደል የተስማማ ነበር ፡፡ በክርስቶስ ያመኑ ሌሎችም ደቀ መዛሙርት ፈጽመው እንዲጠፉ የሚጥር ነበር፡፡ ከኢየሩሳሌም በመውጣት ወደ ደማስቆ በመሄድ በክርስቶስ ያመኑትን ምዕመናን አስሮ ሊያመጣ ሲጓዝ በታላቅ ብርሃን ጌታችን ኢየሱስ ተገለጠለት፡፡ ሐናንያ ለሚባል ሰው ጌታችን ተገልጦ ሳውል ወደሚባለው ሰው ሂድ ሲባል ፈራ ፡፡ ሳውል በጌታ በኢየሱስ ያመኑትን እንደሚያሳድድ ስለሚያውቅ ነበር፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሳውልን ለራሱ  የተመረጠ ዕቃ እንዳደረገው ሲነገረው ሐናንያ በመሄድ እጁን ጭኖ ጸለየለት፡፡ ሳውልም ተጠመቀ፡፡ አይኖቹም ታውረው ነበርና ተከፍተው ማየት ቻሉ፡፡ ሐናንያ ሲጸልይለት መንፈስ ቅዱስ በሳውል ላይ ስላደረበት በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እየታገዘ ያሳድደው ስለ ነበረው ክርስቶስ አዳኝነቱን ይመሰክርለት ጀመር፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር አብ ልጅ መሆኑን ላላመኑት አይሁድ በምኵራቦች መናገር ጀመረ፡፡ ስለ ክርስቶስ አዳኝነት ሲመሰክር የሰሙ ደቀ መዛሙርት ተገረሙ፡፡ ሊያስራቸውም የመጣ መስሎአቸውም ነበር፡፡ ያላመኑትን አይሁድ ስለ ክርስቶስ በመመስከር መልስ ያሳጣቸው ነበር፡፡ አይሁድ ሊገድሉት ስላሰቡ በከተማይቱ በር ቆመው ይጠብቁት ነበር፡፡ አንዳንድ ከተሞች ዙሪያቸውን ቅጥር አላቸው፡፡ ነገር ግን ሳውል በበር ሲጠብቁት በክርስቶስ ያመኑት ደቀ መዛሙርት በሌሊት በቅጥር ላይ በቅርጫት አድርገው አወረዱትና ከሞት እንዲተርፍ አደረጉት፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በየካቲት 25 ቅዳሴ ሲቀደስ ከበላይ ከጠቀስኩት ከቁ 1 - 25 ካለው ከፊሉ ከቁ. 1 - 10 ያለው ይነበባል ፡፡ ከቁ . 11 - ቁ . 25 ካለው ከፊል ከፊሉ በተለያዩ ቀናት ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌ ) ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ይቀጥላል፡፡ ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
69
10
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
60
11
ይቅርታ ማድረግ እየፈለግን ቢያቅተን ምን እናድርግ?   ስለዚህ መንግሥተ ሰማያት ባሮቹን ሊቈጣጠር የወደደን ንጉሥ ትመስላለች። መቈጣጠርም በጀመረ ጊዜ፥ እልፍ መክሊት ዕዳ ያለበትን አንድ ሰው ወደ እርሱ አመጡ። የሚከፍለውም ቢያጣ፥ እርሱና ሚስቱ ልጆቹም ያለውም ሁሉ እንዲሸጥና ዕዳው እንዲከፈል ጌታው አዘዘ። ስለዚህ ባሪያው ወድቆ ሰገደለትና፡- ጌታ ሆይ፥ ታገሠኝ፥ ሁሉንም እከፍልሃለሁ አለው። የዚያም ባሪያ ጌታ አዘነለትና ለቀቀው፥ ዕዳውንም ተወለት። ነገር ግን ያ ባሪያ ወጥቶ ከባልንጀሮቹ ከባሮቹ መቶ ዲናር ዕዳ ያለበትን አንዱን አገኘና፡- ዕዳህን ክፈለኝ ብሎ ያዘና አነቀው። ነስለዚህ ባልንጀራው ባሪያ ወድቆ፡- ታገሠኝ፥ ሁሉንም እከፍልሃለሁ ብሎ ለመነው። እርሱም አልወደደም፥ ግን ሄዶ ዕዳውን እስኪከፍል ድረስ በወኅኒ አኖረው። ባልንጀሮቹ የሆኑ ባሮችም ያደረገውን አይተው እጅግ አዘኑ፥ መጥተውም የሆነውን ሁሉ ለጌታቸው ገለጡ። ከዚያ ወዲያ ጌታው ጠርቶ፡- አንተ ክፉ ባሪያ፥ ስለ ለመንኸኝ ያን ዕዳ ሁሉ ተውሁልህ፤ እኔ እንደ ማርሁህ ባልንጀራህ የሆነውን ያን ባሪያ ልትምረው ለአንተስ አይገባህምን? አለው። ጌታውም ተቈጣና ዕዳውን ሁሉ እስኪከፍለው ድረስ ለሚሣቅዩት አሳልፎ ሰጠው። ከእናንተ እያንዳንዱ ወንድሙን ከልቡ ይቅር ካላለ፥ እንዲሁ ደግሞ የሰማዩ አባቴ ያደርግባችኋል (ማቴ 18 ÷ 23 – 35) ፡፡   ማብራሪያ ከበላይ ያለው ምሳሌ በእግዚአብሔር መንግሥት ይቅር መባባል እንደሚገባ የሚያስተምር ነው ፡፡ ይቅር አለማለት ደግሞ እንደሚጎዳ ያሳያል፡፡ ንጉሡ በባሮቹ ዘንድ ያለውን ሂሳብ መተሳሰብ ጀመረ፡፡ አንድ አገልጋዩ ላይ እልፍ መክሊት ( ዐሥር ሺህ) ብር ዕዳ አገኘበት፡፡ ብሩ ብዙ በመሆኑ መክፈል አልቻለም፡፡ ጌታው ፡- ራሱ አጋልጋዩ ፣ ሚስቱ ፣ ልጆቹና ያለው ሁሉ ተሽጦ እንዲከፈለው አዘዘ፡፡ መክፈል የማይችለው ብዙ ዕዳ ያለበት አገልጋይ ግን እግሩ ላይ ወድቆ ፡- ታገሠኝ፤ እከፍልሃለሁ በማለት ለመነው፡፡ ንጉሡ ግን አዘነለት፡፡ ማረውም፡፡ እከፍልሃለሁ ቢለውም እንደማይከፍለው ስለ ስለ ተገነዘበ ዕዳውን ተወለት፡፡ ዕዳው የተተወለት ባሪያ በጣም ትንሽ ብር አበድሮት ወዳልመለሰት ሰው በመሄድ ፡- ዕዳህን ክፈለኝ ብሎ አነቀው፡፡ መቶ ዲናር ማለት 50 ብር መክፈል ያልቻለውም ሰው ወድቆ ለመነው፡፡ ንጉሡ የተወለትን ብዙ ብር በማሰብ በጣም ትንሿን ሊተውለት አሊያም እስከሚከፍል ሊታገሰው አልቻለም፡፡ ይባስ ብሎ አሳሰረው፡፡ ንጉሡ ያ ባሪያ ያደረገውን ነገር በሰማ ጊዜ እንደዚያ ወድቆ ሲለምነው ክፉ የማይመስለው ሰው ክፉ መሆኑን ነገረው፡፡ ደግሞም  ፡- እኔ እንደ ማርሁህ ልትምረው ይገባህ ነበር በማለት ይቅርታ አድራጊ አለመሆኑን አስረዳው፡፡ ወደ እስር ቤትም ወረወረው፡፡ ታዲያ ይህ ሰው ምን ተጠቀመ? ይቅር አለማለት ጉዳት እንዳለው ታሪኩ በግልጽ ያስተምረናል፡፡ ይቅርታ አለማድረግ ማለት የሚጎዳን ነገር ማድረግ ማለት ነው፡፡ የሚጎዳንን ነገር ደግሞ ማድረግ ማን ይፈልጋል? እንግዲህ ይቅርታ ካለማለት የሚተረፍ ነገር ምንም የለም፡፡ አንዳንድ ሰዎች የበደላቸውን ሰው ፡- ይቅር አልለውም ሲሉ ይደመጣሉ፡፡ እሺ ግን ይቅር ባለማለታቸው ሰውዬውም ካልተጎዳ አለማለታቸው ምን የሚጠቅማቸው ነገር አለ? ይቅር የማይሉት ሰው ከእነርሱ የሚጠቀመው ነገር ካለ ይቅር አለማለታቸው ምናልባት ሰውየውን ለመጉዳት ነው  ማለት ነው፡፡ የፈለገ ቢሆን:- ይቅር በለኝ ተብለን ግን ይቅር አለማለት አይከብድም? ምንም አይከብድም? እዚህ ምድር ላይ ስንኖር ሳንበድል ወይም ሳንበደል መኖር  አይቻልም፡፡ ባንፈልግም፣  የቱንም ያህል ብንጠነቀቅም አንዴ የኛ ብር ወደ ሰው፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ የሰው ብር ወደኛ የሚመጣበት ጊዜ እንዳለ ሁሉ እንዴ መበደል ሌላ ጊዜ ደግሞ መበደል ይኖራል፡፡ ይቅርታ በመባባል ግን ቅራኔን  መልክ ማስያዝ ይቻላል፡፡ በሆነ አጋጣሚ ብር ስንቀባበል ፡- ባለፈው ብር ስትሰጠኝ ጨምረህ ነው የሰጠኸኝ፤ በል ያንን ብር ቀንሰህ ስጠኝ እንደምንባባል ተበዳዮች ብቻ ሆነን መኖር ስለማንችል ተበድለን ይቅር ማለታችን በበደልን ሰዓት ይቅር አልልም ለሚለን ምክንያት እናሳጣዋለን፡፡ ይቅር አልልም ቢል እንኳን ይቅር ያልነውን በፍቅር ከነገርነው ማስተዋሉ የማይቀር ነው፡፡ ብዙ ጊዜ ይቅር ማለት ለምን ይከብደናል? አንዳንድ ሰው ተበድሎ ካልተበቀለው በቀር የተበደለውን መርሳት አይችልም፡፡ እንደርሱ አባባል፡- እሠራለታለሁ ያለውን ካልሠራለት ማለቴ ነው፡፡  ይቅር ስንልም ተግዳሮቶች አሉብን፡፡ ከሚያስቡልን ሰዎች የምንባለው ነገር አለ፡፡ እንደዛ አድርጎሽ (አድርጎህ ) እንዴት ይቅር ትዪዋለሽ ( ትላታለህ )? ይቅርታ ከተባልኩ ምን ማድረግ እችላለሁ? ከይቅርታ በላይ ምን አለ? ብለው ላረጉት ይቅረታ ወደ ኋላ የማይሉ እንዳሉ ሁሉ በቃራኒው ይቅር ያሉትን ሰው እንደ ገና በማኩረፍ መሪአቸውን አዙረው ይቅርታቸውን የሚያስመልሱ አሉ፡፡ ይቅርታ ማድረግ እንድንችል ማድረግ ያለብን ፡፡ ለሰዎች ይቅርታ ማድረግ እንድንችል እግዚአብሔርን የምንበድለውን በደል ደግሞም ይቅር በለን ስንለው የሚያደርግልንን ይቅርታ እንመልከት፡፡ እግዚአብሔርን የበደልነውን ያህል ማንም እኛን በድሎን አያውቅም ፡፡ እግዚአብሔር እንደዛ በድለነው ይቅርታ የሚያደርግልንን ስናስብ ትንሽ ለበደልን ሰው ይቅርታ ማድረጉ አይከብድም፡፡ በእውነት ይህን ካስተዋልን የይቅርታ ( ይቅር የምንል ) ሰዎች እንሆናለን ፡፡ ይቅር የሚል ሰው ደግሞ ትልቅ ሰው ነው፡፡ መንፈሰ እግዚአብሔር ያደረበት ነው፡፡ የይቅርታ ሰው መሆን ውጤታማ ያደርገናል፡፡ ተበድሎ ፡- ይቅር በለኝ ሳይባል ደግሞ ይቅር የሚል ሰው ደግሞ ይኖር ይሆን ? የሚገርማችሁ የእግዚአብሔር ይቅርታው የበለጠ እየገባችሁ ሲመጣ ፡- ይቅርታ ባትባሉም ይቅር ማለት ትጀምራላችሁ፡፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
87
12
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
78
13
የሐዋርያት ሥራ ጥናት :: ክፍል 22 :: የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ታሪክ ::   የጌታም መልአክ ፊልጶስን፡- ተነሥተህ በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ ወደሚያወርደው ምድረ በዳ ወደ ሆነ መንገድ ሂድ አለው። ተነሥቶም ሄደ። እነሆም፥ ህንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት አዛዥና ጃንደረባ የነበረ በገንዘብዋም ሁሉ የሠለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር፤ ሲመለስም በሰረገላ ተቀምጦ የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ያነብ ነበር። መንፈስም ፊልጶስን፡- ወደዚህ ሰረገላ ቅረብና ተገናኝ አለው። ፊልጶስም ሮጦ የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ሲያነብ ሰማና፡- በውኑ የምታነበውን ታስተውለዋለህን? አለው። እርሱም፡- የሚመራኝ ሳይኖር ይህ እንዴት ይቻለኛል? አለው። ወጥቶም ከእርሱ ጋር ይቀመጥ ዘንድ ፊልጶስን ለመነው። ያነበውም የነበረ የመጽሐፉ ክፍል ይህ ነበረ፤ እንደ በግ ወደ መታረድ ተነዳ፥ የበግ ጠቦትም በሸላቹ ፊት ዝም እንደሚል፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም። በውርደቱ ፍርዱ ተወገደ፤ ሕይወቱ ከምድር ተወግዳለችና ትውልዱንስ ማን ይናገራል? ጃንደረባውም ለፊልጶስ መልሶ፡- እባክህ፥ ነቢዩ ይህን ስለ ማን ይናገራል? ስለ ራሱ ነውን ወይስ ስለ ሌላ? አለው። ፊልጶስም አፉን ከፈተ፥ ከዚህም መጽሐፍ ጀምሮ ስለ ኢየሱስ ወንጌልን ሰበከለት። በመንገድም ሲሄዱ ወደ ውኃ ደረሱ፤ ጃንደረባውም፡- እነሆ ውኃ፤ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ምንድር ነው? አለው። ፊልጶስም፡- በፍጹም ልብህ ብታምን፥ ተፈቅዶአል አለው። መልሶም፡- ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ አምናለሁ አለ። ሰረገላውም ይቆም ዘንድ አዘዘ፥ ፊልጶስና ጃንደረባው ሁለቱም ወደ ውኃ ወረዱ፥ አጠመቀውም። ከውኃውም ከወጡ በኋላ የጌታ መንፈስ ፊልጶስን ነጠቀው፤ ጃንደረባውም ሁለተኛ አላየውም፥ ደስ ብሎት መንገዱን ይሄድ ነበርና። ፊልጶስ ግን በአዛጦን ተገኘ፥ ወደ ቂሣርያም እስኪመጣ ድረስ እየዞረ በከተማዎች ሁሉ ወንጌልን ይሰብክ ነበር ( የሐዋ 8 ፥ 26 - 40 ) ።   ማብራሪያ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ እግዚአብሔርን የሚያምን በመሆኑ ካገሩ ድረስ ተነሥቶ የመጣው በኢየሩሳሌም ለእግዚአብሔር ለመስገድ ነው፡፡ ፊልጶስ የጌታ መልአክ ሂድ ወዳለው ወደ ምድረ በዳ ጃንደረባው ወደሚያልፍበት መንገድ አመራ፡፡ ጃንደረባው የልቡን መሻት ፈጽሞ ማለት ለእግዚአብሔር ሰግዶ በሰረገላው እየተመለሰ ነበር፡፡ ሰግዶም ብቻ አልተወም፤ የአምላኩን ቃል ከነቢዩ ኢሳይያስ መጽሐፍ ያነብ ነበር፡፡ የሚያነበው ክፍል ደግሞ ኢሳይያስ ከ700 ዓመት በፊት ክርስቶስ መከራ እንደሚቀበል የተነበየውን ነበር ፡፡ ጃንደረባው ግን ስለ ክርስቶስ መሆኑን አላወቀም፡፡ ጃንደረባው ወደ ፊልጶስ እየቀረበ ሲመጣ መንፈስ ፊልጶስን፡- ወደ ጃንደረባው እንዲቀርብ አዘዘው ፡፡ መንፈስ የተባለው ከሦስቱ አካል አንዱ የሆነውን መንፈስ ቅዱስን ሲሆን መንፈስ ቅዱስ አካል ስላለው ነው ፊልጶስን፡- ወደዚህ ሰረገላ ቅረብና ተገናኝ ያለው። ፊልጶስ  ሲቀርብ ጃንደረባው ከሚያነበው ክፍል፡- የበግ ጦቦት በሸላቹ ፊት ዝም እንደሚል እንዲሁ አፉን አልከፈተም የሚለውን ሲያነብ ስለሰማ ፡- የምታነበውን ታስተውለዋለህ? አለው፡፡ ፊልጶስን ወደ ሰረገላው እንዲወጣ ለመነውና ነቢዩ የሚያወራው ስለ ራሱ ወይስ ስለ ሌላ እንደሆነ እንዲያስረዳው ጠየቀው ፡፡ ፊልጶስ ካነበበው ተነሥቶ ስለ ኢየሱስ ወንጌል ሰበከለት፡፡ ክርስቶስን በማመኑም አጠመቀው፡፡ ጃንደረባውም ሰግዶ ሲመለስ ያላገኘውን ደስታ አሁን አግኝቶ ደስ እያለው ይሄድ ጀመር፡፡ ይህ ሰው እግዚአብሔርን ፈልጎ ካገሩ ድረስ ያን ሁሉ መንገድ ተጉዞ  የመጣው በሰረገላ ነበር፡፡ የሚስተምረው ሰው ለሌለው፤ ዝም ብሎ ለሚያነበው በምድረ በዳ አስተማሪ ላከለት ፡፡ ምድረ በዳ ምንም የማንጠብቅበት ቦታ ነው፡፡ ልፋቱ መና እንዳይቀር እግዚአብሔር በምሕረቱ ምድረ በዳ ላይ ጎበኘው፡፡ ምንም ነገር የለም ብለን ተስፋ በቆረጥነበት ምድረ በዳ ላይ እርሱ ይጎበኘናል፡፡ እግዚአብሔር ስለ አንድ ሰው የሚገደው አምላክ ነው፡፡ ስለ እኛም ስለ አንዳችን ይገደዋል፡፡ ጃንደረባው ክርስትና ተጀምሮ እርሱ ግን በቀድሞ የአይሁድ እምነት እግዚአብሔርን ፍለጋ  ሄደ ፡፡ ሲመለስ ግን እግዚአብሔር በሚበልጠው ወንጌል እንዲያምን አደረገው፡፡ አንዳንዴ እግዚአብሔር በሌለበት የእግዚአብሔር ፈቃድ ያለበት መስሎን  እንወጣለን፡፡ እንደዛም ሆኖ አይተወንም፤ ምሕረቱን አብዝቶ በራሱ መንገድ ይጎበኛናል፡፡ ኢትዮጵያና የክርስትና ሃይማኖት የተዋወቁት በዚህ ጃንደረባ በ34 ዓ.ም ነው፡፡ ለሀገሩ ሕዝብም አስተምሯል ተብሎ ይታመናል (የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ በብፁዕ በአቡነ ጎርጎርዮስ ገጽ 18)፡፡ እንግዲህ እስከዚህ የሐዋርያት ሥራ ም 8 ድረስ መመልከት የቻልነው ወንጌል ይኸውም የምሥራቹ ቃል እየተስፋፋ መምጣቱን ነው፡፡ ዛሬም ሊሰበክ የሚገባው ወንጌል እንደ ሆነ ያስተምረናል፡፡ የክርስቶስ ጉዳይ አስቀድሞ በነቢያትም ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ ነበር፡፡ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባውም በሚያነበው በነቢዩ ኢሳይያስ የትንቢት መጽሐፍ ሰፍሮ አግኝተነዋል፡፡ ነቢያት የተናገሩለትን ክርስቶስን ያመነው ጃንደረባው በልቡ ደስታ  ሞልቶታል፡፡ የሰበከው ፊልጶስም በሌሎች አገሮች ሁሉ ወንጌልን መስበኩን አልተወም፡፡ ለጃንደረባው ቃሉን የገለጠ መንፈስ ቅዱስ በዚህ ዘመን ላለነው ኢትዮጵያውያንም ቃሉን ይግለጥልን ፤ በልቦናችንም ያሳድርልን፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በጥቅምት 14  ቅዳሴ ሲቀደስ የሐዋ 8 ፥ 26 - 40 ያለው ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌ ) ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ይቀጥላል፡፡ ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
91
14
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
76
15
እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝበት ጸሎት፡፡   እግዚአብሔርም ..ለሰሎሞን በሌሊት በሕልም ተገለጠለት፤ እግዚአብሔርም፡- ምን እንድሰጥህ ለምን አለ። ሰሎሞንም አለ። ..አቤቱ አምላኬ ሆይ፥ እኔን ባሪያህን በአባቴ በዳዊት ፋንታ አንግሠኸኛል፤ እኔም መውጫንና መግቢያን የማላውቅ ታናሽ ብላቴና ነኝ።  ባሪያህም ያለው አንተ በመረጥኸው ሕዝብህ ስለ ብዛቱም ይቈጠርና ይመጠን ዘንድ በማይቻል በታላቅ ሕዝብ መካከል ነው። ስለዚህም በሕዝብህ ላይ መፍረድ ይችል ዘንድ፥ መልካሙንና ክፉውንም ይለይ ዘንድ ለባሪያህ አስተዋይ ልቡና ስጠው፤ አለዚያማ በዚህ በታላቅ ሕዝብህ ላይ ይፈድ ዘንድ ማን ይችላል?  ሰሎሞንም ይህን ነገር ስለ ለመነ፥ ነገሩ እግዚአብሔርን ደስ አሰኘው። እግዚአብሔርም አለው። ፍርድን ትለይ ዘንድ ለራስህ ማስተዋልን ለመንህ እንጂ ለራስህ ብዙ ዘመናትን ባለጠግነትንም የጠላቶችህንም ነፍስ ሳትለምን ይህን ነገር ለምነሃልና እነሆ፥ እኔ እንደ ቃልህ አድርጌልሃለሁ፤ እነሆ፥  ማንም የሚመስልህ ከአንተ በፊት እንደሌለ ከአንተም በኋላ  እንዳይነሣ አድርጌ ጥበበኛና አስተዋይ ልቡና ሰጥቼሃለሁ።  .. ደግሞም ከነገሥታት የሚመስልህ ማንም እንዳይኖር ያልለመንኸውን ባለጠግነትና ክብር ሰጥቼሃለሁ።  ..ሰሎሞንም ነቃ፥ እነሆም፥ ሕልም ነበረ ( 1ነገ 3 ÷ 5 – 15 ) ፡፡   ማብራሪያ ሰሎሞን ንጉሥ በሆነ ጊዜ ገና ብላቴና ነበር፡፡ ራሱ ብላቴና መሆኑን ለእግዚአብሔር ሲናገር ሰምተነዋል፡፡ ለብላቴናው ለሰሎሞን እግዚአብሔር በሕልም ተገለጠለትና፡- እንድሰጥህ የምትፈልገውን ሁሉ ለምን አለው፡፡ ለምነኝ የተባለው ንጉሥ ሰሎሞን ሺህ ዓመት ልንገሥ አላለም፡፡ ሌላም ነገር እንዲሰጠው አልለመነም፡፡ የለመነው፡-  አስተዋይ ልቡና ስጠኝ ብሎ ነው፡፡ እግዚአብሔርም ሰሎሞን ለራሱ ብዙ ዘመንን ፣ ባለጠግነትን ፣ ጠላቶቹ እንዲጠፉለት ባለመለመኑና፡- አስተዋይ ልቡና ስጠኝ በማለቱ ከእርሱም በፊት ከእርሱም በኋላ እንደ እርሱ የሆነ ጥበበኛ እንዳይነሣ አድርጎ አስተዋይ ልቡና ሰጠው፡፡ ሰሎሞን ነቃ ሕልም ነበረ፡፡ ሕልም እንደ ነበረ ግን አልቀረም፡፡ ሰሎሞን ከነቃ ጀምሮ አጅግ አስተዋይ ሰው መሆን ጀመረ፡፡ ያልለመነውንም ባለጠግነትና ክብር ተሰጠው፡፡ የተሰጠው ባለጠግነትና ክብር ደግሞ ከነገሥታት እርሱን የሚመስል ማንም እንዳይኖር ተደርጎ ነበር፡፡ እግዚአብሔር ያልለመነውንም የሚሰጠን አምላክ ነው፡፡ ወደ እግዚአብሔር ትክክለኛ ጸሎት ስናደርግ ምንም ጥያቄ የሌለው ነገር ምን መሰላችሁ? ያልለመነውንም ነገር እንዲሰጠን ያስደርጋል፡፡ ሰሎሞን እግዚአብሔርን ስጠኝ ያለው አስተዋይ ልቡና በመሆኑ እግዚአብሔር ደስ ተሰኝቶበታል፡፡ ከእግዚአብሔር መለመን ያለብንን ስናውቅ እግዚአብሔርም ደስ ይሰኝብናል፡፡ እግዚአብሔር እንደ ፈቃዱ የሆነውን ነገር ስንለምንው ደስ ይሰኛል፡፡ በተለይ በተለይ ከእርሱ ጋር ስለመኖርና እስከ መጨረሻ በመጽናት መንግሥቱን ስለመውረስ መጸለይ እግዚአብሔርን የበለጠ ደስ ያሰኘዋል ፡፡ እንደ ሰሎሞን አስተዋይ ልቡና ስጠን ማለትንም ሳንዘነጋ ማለቴ ነው፡፡ አስተዋል ልቡና ያለው ሰው ከምንም በላይ ባለ ዘመኑ ሁሉ ከእግዚአብሔር ጋር መኖርን ይለምናል፡፡ ባለ ዘመናችን ከእግዚአብሔር ጋር ከሆንን ሁሉ ያለው እግዚአብሔር የእኛ ነው፡፡ እግዚአብሔር ካለን ሁሉ የኛ ነው፡፡ መለመን ያለብንን ስንለምን ያልለመነውም ጭምር ይሰጠናል፡፡ በተለያዩ ጉዳዮችም ስንጸልይ የሚጠቅመን ምን እንደ ሆነ አናውቅምና፡- አንተ እርዳን እንበለው፡፡ እርዳን ያልነው አምላክ ይረዳናል፡፡ የሚሻለንን እርሱ ያውቅልናል፡፡ በጸሎት መለመን ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውን ልንለመን ይገባል፡፡ ስለ ወደድነው የለመንነው ነገር እግዚአብሔርን ብቻ ሳይሆን ቢሰጠን እኛንም ደስ የማያሰኝ ሊሆን ይችላል፡፡ እግዚአብሔርን ፣ የሚሰጠን እኛንም ደስ የሚያሰኝ ልመና እናቅርብ ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
92
16
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
74
17
የሐዋርያት ሥራ ጥናት ፡፡ ክፍል 21 ፡፡ ሐዋርያት እጃቸውን ሲጭኑ የመንፈስ ቅዱስ መውረድ ፡፡   ከክፍል 20 ባጭሩ ፡፡ በዚያን ቀንም በኢየሩሳሌም ባለች ቤተ ክርስቲያን ላይ ታላቅ ስደት ሆነ፤ ሁሉም  ከሐዋርያትም በቀር ወደ ይሁዳና ወደ ሰማርያ አገሮች ተበተኑ። ..የተበተኑትም ቃሉን እየሰበኩ ዞሩ። ፊልጶስም ወደ ሰማርያ ከተማ ወርዶ ክርስቶስን ሰበከላቸው። ..ሲሞን የሚሉት አንድ ሰው ግን፡- .. እየጠነቈለ የሰማርያንም ወገን እያስገረመ ቀድሞ በከተማ ነበረ። ከታናናሾችም ጀምሮ እስከ ታላላቆቹ ድረስ ..በጥንቈላ ስላስገረማቸው ያደምጡት ነበር። ነገር ግን ስለ እግዚአብሔር መንግሥትና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም እየሰበከላቸው ፊልጶስን ባመኑት ጊዜ፥ ወንዶችም ሴቶችም ተጠመቁ። ሲሞንም ደግሞ ራሱ አመነ፤ ተጠምቆም ከፊልጶስ ጋር ይተባበር ነበር፤ የሚደረገውንም                                       ምልክትና ታላቅ ተአምራት ባየ ጊዜ ተገረመ  ( የሐዋ 8 ÷ 1 - 13 ) ። ------////-------   በኢየሩሳሌምም የነበሩት ሐዋርያት የሰማርያ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንደተቀበሉ ሰምተው ጴጥሮስንና ዮሐንስን ሰደዱላቸው። እነርሱም በወረዱ ጊዜ መንፈስ ቅዱስን ይቀበሉ ዘንድ ጸለዩላቸው፤ በጌታ በኢየሱስ ስም ብቻ ተጠምቀው ነበር እንጂ ከእነርሱ በአንዱ ላይ ስንኳ ገና አልወረደም ነበርና። በዚያን ጊዜ እጃቸውን ጫኑባቸው መንፈስ ቅዱስንም ተቀበሉ። ሲሞንም በሐዋርያት እጅ መጫን መንፈስ ቅዱስ እንዲሰጥ ባየ ጊዜ፥ ገንዘብ አመጣላቸውና:- እጄን የምጭንበት ሁሉ መንፈስ ቅዱስን ይቀበል ዘንድ ለእኔ ደግሞ ይህን ሥልጣን ስጡኝ አለ። ጴጥሮስ ግን እንዲህ አለው። የእግዚአብሔርን ስጦታ በገንዘብ እንድታገኝ አስበሃልና ብርህ ከአንተ ጋር ይጥፋ። ልብህ በእግዚአብሔር ፊት የቀና አይደለምና ከዚህ ነገር ዕድል ወይም ፈንታ የለህም። እንግዲህ ስለዚህ ክፋትህ ንስሐ ግባ፥ ምናልባትም የልብህን አሳብ ይቅር ይልህ እንደ ሆነ ወደ እግዚአብሔር ለምን፤ በመራራ መርዝና በዓመፅ እስራት እንዳለህ አይሃለሁና። ሲሞንም መልሶ፡- ካላችሁት አንዳች እንዳይደርስብኝ እናንተው ወደ ጌታ ለምኑልኝ አላቸው። እነርሱም ከመሰከሩና የጌታን ቃል ከተናገሩ በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፤ በሳምራውያን በብዙ መንደሮችም ወንጌልን ሰበኩ ( የሐዋ 8 ÷ 14 - 25 ) ።   ማብራሪያ ቅዱስ እስጢፋኖስ በመገደሉ በክርስቶስ ያመኑ ደቀ መዛሙርት ( ክርስቲያኖች ) ከተሰደዱበት አገር አንዱ ወደ ሰማርያ ነበር፡፡ በሰማርያ ፊልጶስ ክርስቶስን ስለ ሰበከ ብዙ ሰዎች አምነው ነበር፡፡ ካመኑት አንዱ ደግሞ ጥንቋዩ ሲሞን ነበር፡፡ ሐዋርያት የሰማርያ ሰዎች በክርስቶስ እንዳመኑ ሲሰሙ ጴጥሮስና ዮሐንስ ወደ ሰማርያ ወረዱና ጸለዩላቸው፡፡ ሲጸልዩላቸው መንፈስ ቅዱስ ወረደባቸው፡፡ የጸለዩላቸው እጃቸውን ጭነው ነበር፡፡ አስቀድመው ተጠምቀው ነበር፡፡ የተጠመቁት በጌታ በኢየሱስ ስም ነበር የተባለው በክርስቶስ ሲያምኑ የተጠመቁትን ጥምቀት ለማመልከት ነው፡፡ በአብ ፣ በወልድ ፣ በመንፈስ ቅዱስ ስም የምንጠመቀውን የሚያመለክት ነው፡፡ ሐዋርያት ሥራን የጻፈው ሉቃስ በጌታ በኢየሱስ ስም ተጠመቁ ሲል ጥምቀቱን ከዮሐንስ ጥምቀት ሊለየው የፈለገ ይመስላል፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ንስሐ ግቡ እያለ ያጠምቅ የነበረው ጥምቀት የንስሐ ጥምቀት ነበር፡፡ እንደ ሐዋርያት በእግዚአብሔር ከተሾመ በቀር እጅን በሰው ላይ ጭኖ መጸለይ ተገቢ አይደለም፡፡ የእግዚአብሔር አገልጋዮች እጃቸውን በሰው ላይ በተለያየ ምክንያት ጭነው ሊጸልዩ ይችላሉ፡፡ ሲሞን ልክ እንደ ሐዋርያት እርሱም እጁን ሲጭን መንፈስ ቅዱስ በሰዎች ላይ እንዲወርድ ፈልጎ ገንዘብ ለሐዋርያት ሰጥቶአቸው ሥልጣኑን እንዲሰጡት ጠየቃቸው፡፡ ዛሬ ዛሬ የእግዚአብሔርን ስጦታ በገንዘብ የሚቸረችሩ ብዙ አሉ፡፡ ሲሞን የእግዚአብሔርን ስጦታ በገንዘብ ሊያገኝ መፈለጉ ኃጢአት መሆኑን፣ ንስሐ እንዲገባና ወደ እግዚአብሔር እንዲለምን ሐዋርያት ነገሩት ፡፡ ያመነውን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ከልቡ ፡- ይቅር በለኝ ብሎ ቢለምን ይቅር መባሉ እውነት ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ስለ ሲሞን የሚነገረውን ለጊዜው አልጻፍኩትም፡፡ ሐዋርያት የሆኑት ጴጥሮስና ዮሐንስ ዋና ሥራቸው ወንጌልን መስበክ ነበርና፡- ወንጌል ሰበኩ የሚለን ለዚህ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ በእነርሱ ላይ በወረደ ጊዜ ምስክር እንዲሆኑ ከተነገራቸው አንድዋ ሰማርያ በመሆንዋ ወንጌልን በሰማርያ ሰብከዋል፡፡ ከበላይ ስለ መንፈስ ቅዱስ መውረድ አንስቼ ነበርና የኢትዮጵያ ኦ/ተ/ቤ/ክ አጥምቃ ሜሮን የምትቀባው ሐዋርያት እጃቸውን ጭነው ሲጸልዩ የወረደውን መንፈስ ቅዱስን እንዲቀበሉ ብላ ነው፡፡ እንግዲህ ዘወትር መንፈስ ቅዱስ በእኛ ላይ እንዲያድርብንና ሁሌም ከእኛ እንዳይለይ መጸለይ ተገቢና አስፈላጊ ነው፡፡ በሐዋርያት ሥራ መንፈስ ቅዱስ በግልጽ ሥራውን ሲሰራ እንመለከታለን፡፡  መንፈስ ቅዱስ ከኛ ሳይለየን ሲኖር በብርታት እንመላለሳለን፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወታችንንም ትልቅ ለውጥ ይኖራል፡፡ ይታያልም፡፡ ለቅዱሳን ሐዋርያት የሰጣቸውን መንፈስ ቅዱስ ሁሌም ሳይወሰድብን በእኛም ያሳድርብን፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በመጋቢት 2ና ግንቦት 16 ቅዳሴ ሲቀደስ የሐዋ 8 ÷ 14 – 26 ያለው ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌ) ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ይቀጥላል፡፡ ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
89
18
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
88
19
እግዚአብሔር የሕዝቡን ጭንቀትና መከራ የሚመለከት አምላክ ነው፡፡   በግብፅም ዮሴፍን ያላወቀ አዲስ ንጉሥ ተነሣ።  እርሱም ሕዝቡን፡- እነሆ፥ የእስራኤል ልጆች ሕዝብ ከእኛ ይልቅ በዝተዋል በርትተውማል፤ እንዳይበዙ፥ ሰልፍም በተነሳብን ጊዜ ጠላቶቻችንን አግዘው እንዳይወጉን ከምድሪቱም እንዳይወጡ፥ ኑ እንጠበብባቸው አለ።  በብርቱ ሥራም ያስጨንቁአቸው ዘንድ ግብር አስገባሪዎችን ሾመባቸው፤ ..ነገር ግን እንዳስጨነቁአቸው መጠን እንዲሁ በዙ፥ እጅግም ጸኑ፤ ከእስራኤልም ልጆች የተነሣ ተጸይፈዋቸው ነበር። ግብፃውያንም የእስራኤልን ልጆች በመከራ ገዙአቸው። በጽኑ ሥራ፥ በጭቃ፥ በጡብም በእርሻም ሥራ ሁሉ፥ በመከራም በሚያሠሩአቸው ሥራ ሁሉ፥ ሕይወታቸውን ያስመርሩአቸው ነበር ( ዘጸ 1 ÷ 8 – 14 ) ። ..የእስራኤልም ልጆች ከባርነት የተነሣ አለቀሱ፥ ጮኹም፥ ስለ ባርነታቸውም ጩኸታቸው ወደ እግዚአብሔር ወጣ።  እግዚአብሔርም የለቅሶአቸውን ድምፅ ሰማ፥ እግዚአብሔርም ከአብርሃምና ከይስሐቅ ከያዕቆብም ጋር ያደረገውን  ቃል ኪዳን አሰበ።   እግዚአብሔርም የእስራኤልን ልጆች አየ.. ( ዘጸ 2 ÷ 23 -25 ) ። ሙሴም ..የአማቱን ..በጎች ይጠብቅ ነበር፤ ..ወደ እግዚአብሔርም ተራራ ወደ ኮሬብ መጣ። የእግዚአብሔርም መልአክ በእሳት ነበልባል በእሾህ ቍጥቋጦ መካከል ታየው፤ እነሆም ቍጥቋጦው በእሳት ሲነድድ ቍጥቋጦውም  ሳይቃጠል አየ።  ሙሴም፡-  ልሂድና ቍጥቋጦው ስለ ምን አልተቃጠለም ይህን ታላቅ ራእይ ልይ አለ። እግዚአብሔር እርሱ ይመለከት ዘንድ እንደ መጣ ባየ ጊዜ እግዚአብሔር ከቍጥቋጦው ውስጥ እርሱን ጠርቶ። ሙሴ፥ ሙሴ ሆይ አለ።  እርሱም- እነሆኝ አለ። ወደዚህ አትቅረብ፤ አንተ የቆምህባት ስፍራ የተቀደሰች መሬት ናትና ጫማህን ከእግርህ አውጣ አለው። ደግሞም፡- እኔ የአባትህ አምላክ፥ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ አለው..  እግዚአብሔርም አለ። በግብፅ ያለውን የሕዝቤን መከራ በእውነት አየሁ፥ ከአስገባሪዎቻቸውም የተነሣ ጩኸታቸውን ሰማሁ፤ ሥቃያቸውንም አውቄአለሁ፤ ከግብፃውያንም እጅ አድናቸው ዘንድ፥ ከዚያችም አገር ወተትና ማር ወደምታፈስሰው አገር ወደ ሰፊይቱና ወደ መልካሚቱ አገር ..አወጣቸው ዘንድ ወረድሁ።  አሁንም እነሆ የእስራኤል ልጆች ጩኸት ወደ እኔ ወጣ፤ ግብፃውያንም የሚያደርጉባቸውን ግፍ ደግሞ አየሁ። አሁንም ና፥ ሕዝቤን የእስራኤልን ልጆች ከግብፅ ታወጣ ዘንድ ወደ ፈርዖን እልክሃለሁ ( ዘጸ 3 ÷ 1 – 10 ) ) ። እግዚአብሔር የእስራኤልን ልጆች ከሠራዊታቸው ጋር ከግብፅ ምድር አወጣ ( ዘጸ 12 ÷ 51 ) ።   ማብራሪያ የእስራሌል ልጆች በረሀብ ምክንያት ዮሴፍ ገዢ ሆኖ ወደ ተሾመበት ወደ ግብፅ ከ400 ዓመት ገደማ በፊት ወርደው ነበር፡፡ ዮሴፍ ሲሞት የነገሠው ንጉሥ እስራኤላውያንን እንደ ባሪያ አድርጎ በመግዛት ማስጨነቅ ጀመረ፡፡ ከባድ የጉልበት ሥራም ያሠሩአቸው ስለ ነበር ሕይወታቸውን ያስመርሩአቸው ነበር፡፡ የእስራኤል ልጆች ባርነቱ ሲከብዳቸው ማልቀስ ጀመሩ፡፡ ማልቀስ ምን ያደርጋል አይታገሉም ነበር ? የሚል ሰው ሊኖር ይችላል፡፡ ማልቀሳቸው ጥምቅ ነበረው፡፡ ሲያለቅሱ፣ ሲጮኹ እኮ ነው ጩኸታቸውን እግዚአብሔር የሰማው፡፡ እግዚአብሔር የልቅሶአቸውን ድምፅ ሰማ፡፡ ለአባቶቻቸው ለነ አብርሃም የገባውን ኪዳን አሰበ፡፡ የእስራኤላውያንን ልጆች ተመለከተ፡፡ ሙሴ የአማቱን በጎች እየጠበቀ የእግዚአብሔር መልአክ በቁጥቋጦው መሐል ታየው፡፡ ቁጥቋጦው በእሳት ሲነድድና ቁጥቋጦው ግን ሳይቀጥል ማየቱ ገረመው፡፡ ቁጥቋጦው ለምን አልተቃጠለም? በማለት ጠጋ ብሎ ለማየት ሲቀርብ እግዚአብሔር በስሙ ጠርቶ ፡- ሙሴ ሙሴ አለው፡፡ እነሆኝ አለ፡፡ እግዚአብሔር ለሙሴ የእስራኤላውያንን ጩኸት ፣ መከራ፣ ሥቃያቸውን ፣ የሚፈጸምባቸውን ግፍ እንዳየና ሊያድናቸውም እንደ ወደደ ሙሴንም ከግብፅ እንዲያወጣቸው እንደሚሾመው ነገረው፡፡ ሙሴም እልህ አስጨራሽ ትግል ከግብፅ ንጉሥ ፈርዖን ካደረገ በኋላ እግዚአብሔር የእስራኤልን ልጆች ከግብፅ ምድር አወጣ ፡፡ ሥቃያችን ፣ የሚፈጸምብን ግፍ ሲበዛብን የማያይ ለሚመስለን እግዚአብሔር ያያል፡፡ በቃም ይላል፡፡ እኛ እንደ እስራኤል ልጆች ወደ እርሱ ጩኸታችንን ስናሰማ እግዚአብሔር ጩኸታችንን ይሰማል፡፡ ሥቃያችንንም ይመለከታል፡፡ ከሥቃያችንንና ከመከራችንም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ይገላግለናል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
128
20
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
83