uk
Feedback
እግዚአብሔርን ማወቅ

እግዚአብሔርን ማወቅ

Відкрити в Telegram

ሰላምታ በተለዋወጥን ቁጥር ይመስገን ስለምንለው አምላካችንና አባታችን እግዚአብሔር ያለንን ዕውቀት ለማዳበር የሚያግዝ ቻነል ነው፡፡

Показати більше
936
Підписники
+124 години
+47 днів
+1730 день

Триває завантаження даних...

Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
липень '26
липень '26
+27
в 0 каналах
червень '26
+43
в 0 каналах
Get PRO
травень '26
+31
в 0 каналах
Get PRO
квітень '26
+45
в 0 каналах
Get PRO
березень '26
+33
в 0 каналах
Get PRO
лютий '26
+49
в 0 каналах
Get PRO
січень '26
+45
в 0 каналах
Get PRO
грудень '25
+54
в 0 каналах
Get PRO
листопад '25
+38
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '25
+37
в 0 каналах
Get PRO
вересень '25
+31
в 0 каналах
Get PRO
серпень '25
+32
в 0 каналах
Get PRO
липень '25
+45
в 0 каналах
Get PRO
червень '25
+49
в 0 каналах
Get PRO
травень '25
+24
в 0 каналах
Get PRO
квітень '25
+19
в 0 каналах
Get PRO
березень '25
+18
в 0 каналах
Get PRO
лютий '25
+11
в 0 каналах
Get PRO
січень '25
+9
в 0 каналах
Get PRO
грудень '24
+19
в 0 каналах
Get PRO
листопад '24
+25
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '24
+27
в 0 каналах
Get PRO
вересень '24
+17
в 0 каналах
Get PRO
серпень '24
+20
в 0 каналах
Get PRO
липень '24
+35
в 0 каналах
Get PRO
червень '24
+21
в 0 каналах
Get PRO
травень '24
+23
в 0 каналах
Get PRO
квітень '24
+12
в 0 каналах
Get PRO
березень '24
+31
в 0 каналах
Get PRO
лютий '24
+11
в 0 каналах
Get PRO
січень '24
+15
в 0 каналах
Get PRO
грудень '23
+15
в 0 каналах
Get PRO
листопад '23
+12
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '23
+13
в 0 каналах
Get PRO
вересень '23
+479
в 0 каналах
Дата
Залучення підписників
Згадування
Канали
25 липня+2
24 липня+1
23 липня+1
22 липня+1
21 липня+1
20 липня+1
19 липня0
18 липня+1
17 липня0
16 липня+3
15 липня+1
14 липня+3
13 липня+2
12 липня0
11 липня0
10 липня+1
09 липня+1
08 липня0
07 липня+1
06 липня+1
05 липня+1
04 липня0
03 липня0
02 липня+4
01 липня+1
Дописи каналу
የሐዋርያት ሥራ ጥናት :: ክፍል 53 :: ለጳውሎስ የተሰጠው ሀብተ ፈውስ ፡፡   ክፍል 52 ባጭሩ :: ..ጳውሎስ ..ወደ ኤፌሶን መጣ፥ ..ወደ ምኵራብም ገብቶ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት እየተነጋገረና እያስረዳቸው ..በግልጥ ይናገር ነበር። ..ጢራኖስም በሚሉት በትምህርት ቤት ዕለት ዕለት ይነጋገር ነበር። በእስያም የኖሩት ሁሉ አይሁድም የግሪክ ሰዎችም የጌታን ቃል እስኪሰሙ ድረስ ሁለት ዓመት ያህል እንዲህ ሆነ ( የሐዋ 19 ÷ 1 - 10 )። ------///------   እግዚአብሔርም በጳውሎስ እጅ የሚያስገርም ተአምራት ያደርግ ነበር፤ ስለዚህም ከአካሉ ጨርቅ ወይም ልብስ ወደ ድውዮች ይወስዱ ነበር፥ ደዌያቸውም ይለቃቸው ነበር ክፉዎች መናፍስትም ይወጡ ነበር። አጋንንትንም እያወጡ ይዞሩ ከነበሩት አይሁድ አንዳንዶች፡- ጳውሎስ በሚሰብከው በኢየሱስ እናምላችኋለን እያሉ ክፉዎች መናፍስት ባሉባቸው ላይ የጌታን የኢየሱስን ስም ይጠሩባቸው ዘንድ ሞከሩ። የካህናትም አለቃ ለሆነ አስቄዋ ለሚሉት ለአንድ አይሁዳዊ ይህን ያደረጉ ሰባት ልጆች ነበሩት። ክፉው መንፈስ ግን መልሶ፡- ኢየሱስንስ አውቀዋለሁ ጳውሎስንም አውቀዋለሁ፤ እናንተሳ እነማን ናችሁ? አላቸው። ክፉው መንፈስም ያለበት ሰው ዘለለባቸው ቆስለውም ከዚያ ቤት ዕራቁታቸውን እስኪሸሹ ድረስ በረታባቸው አሸነፋቸውም። ይህም በኤፌሶን በሚኖሩት ሁሉ በአይሁድና በግሪክ ሰዎች ዘንድ የታወቀ ሆነ፥ በሁላቸውም ላይ ፍርሃት ወደቀባቸው፥ የጌታም የኢየሱስ ስም ተከበረ፤ አምነውም ከነበሩት እጅግ ሰዎች ያደረጉትን እየተናዘዙና እየተናገሩ ይመጡ ነበር። አስማተኞችም ብዙዎቹ መጽሐፋቸውን ሰብስበው በሰው ሁሉ ፊት አቃጠሉት፤ ዋጋውም ቢታሰብ አምሳ ሺህ ብር ሆኖ ተገኘ። እንዲህም የጌታ ቃል በኃይል ያድግና ያሸንፍ ነበር ( የሐዋ 19 ÷ 11 - 20 )።   ማብራሪያ ጳውሎስ በኤፌሶን ሁለት ዓመት ያህል ወንጌልን እየሰበከ እንደ ቆየ አይተናል፡፡ ቆይታው በሁለት ዓመት ሳያበቃ ቀጥሎአል፡፡ መፈወስ ከመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች አንዱ ነው፡፡ እግዚአብሔር በጳውሎስ የሚያስገርም ተአምራት ያደርግ ነበር፡፡ የሚስገርመው ተአምራቱ ደግሞ በሽተኞች ጳውሎስ ጋር ሳይመጡ መፈወሳቸው ነበር፡፡ ወደ ጳውሎስ የመጡ ሰዎች ከአካሉ ጨርቅ ወይም ልብስ ወስደው በሽተኞቹን ሲያስነኩ ከበሽታቸው ይፈወሱ ነበር፡፡ ከክፉ መናፍስትም ጭምር ነጻ ይወጡ ነበር፡፡ ፈውስ መደረጉ ሰዎች ወንጌልን እንዲያምኑ ነው፡፡ አንዳንዶች በፈውስ ምክንያት ወደ ክርስትና ሕይወት የሚመለሱ አሉ፡፡ ወደ ክርስትና ለመመለስ ግን የግድ ፈውስ መጠበቅ አያስፈልግም፡፡ ጳውሎስ ርኩሳን መናፍስትን ሲያወጡ ያዩ ያላመኑ አይሁድ ደግሞ ፡- ጳውሎስ በሚሰብከው በኢየሱስ ስም ውጡ እያሉ ክፉዎች መናፍስት ያሉባቸው ሰዎች ላይ የጌታችን የኢየሱስን ስም ጠሩባቸው፡፡  ክፉው መንፈስ ያደረበት ሰው ኢየሱስን እንደሚያውቀው፣ ጳውሎስንም እንደሚያውቀው ነግሮአቸው ፡- እናንተሳ እነማን ናችሁ? አላቸው። በዚህ ብቻ ሳያበቃ አቆሰላቸውም፡፡ ሲበረታባቸው ከነበሩበት ቤት ዕራቁታቸውን ሸሹ፡፡ ይህን ታሪክ የሰሙ ሁሉ ፈሩ፡፡ የጌታችን የኢየሱስ ስምም ተከበረ፡፡ በጌታችን በኢየሱስ ያመኑ ሰዎች ያደረጉትን እየተናዘዙና እየተናገሩ ይመጡ ነበር፡፡ አስማት ከሚሠሩ ብዙዎቹ መጽሐፋቸውን ሰብስበው በመምጣት ሰው እያያቸው አቃጠሉት፡፡ የጌታ ቃል ተብሎ የተጠቀሰው ወንጌል እየተስፋፋ መሄዱን ቀጠለ፡፡ ወንጌል አስማተኞችን ከአስማታቸው ነጻ እንዳወጣቸው በተለያዩ ሱስ ውስጥና በክፉ ዲያብሎስ አሠራር ያሉትን ነጻ የሚያወጣ ነው፡፡ ወንጌል ያሸንፋል እንጂ አይሸነፍም፡፡ እግዚአብሔር ለጳውሎስ ሀብተ መንፈስ ቅዱስን እንዳሳደረበት በኛም የመንፈስ ቅዱስን ሀብታት ያሳድርብን፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን ለምሳሌ ታህሳስ 30 ቅዳሴ ሲቀደስ በሐዋ 19 ÷ 8 – 21 ያለው ሲነበብ ከበላይ የጠቀስኩት ክፍል ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌ) ፡፡ ይቀጥላል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie

2
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
9
3
ገብርኤል እየበረረ መጣ፡፡   በዳርዮስ በመጀመሪያ ዓመት፥ … እኔ ዳንኤል የኢየሩሳሌም መፍረስ የሚፈጸምበትን ሰባውን ዓመት፥ እግዚአብሔር በቃሉ ለነቢዩ ለኤርምያስ የተናገረውን የዓመቱን ቍጥር በመጽሐፍ አስተዋልሁ።ማቅ ለብሼ በአመድም ላይ ሆኜ ስጾም እጸልይና እለምን ዘንድ ፊቴን ወደ ጌታ ወደ አምላክ አቀናሁ።  ወደ አምላኬም ወደ እግዚአብሔር ጸለይሁ፥ ተናዝዤም እንዲህ አልሁ፡- ጌታ ሆይ፥ ከሚወድዱህና ትእዛዝህን ከሚፈጽሙ ጋር ቃል ኪዳንንና ምሕረትን የምትጠብቅ ታላቅና የምታስፈራ አምላክ ሆይ፥ ኃጢአትን ሠርተናል፥ በድለንማል፥ ክፋትንም አድርገናል፥ ዐምፀንማል፥ …አሁንም ሕዝብህን ከግብጽ ምድር በበረታች እጅ ያወጣህ፥ እንደ ዛሬም ቀን ዝና ለአንተ ያገኘህ ጌታ አምላካችን ሆይ፥ ኃጢአትን ሠርተናል፥ ክፋትንም አድርገናል።  ....ቍጣህና መዓትህ ከከተማህ ከኢየሩሳሌም ከቅዱስ ተራራህ እንዲመለስ እለምንሃለሁ። … አምላኬ ሆይ፥ በፊትህ የምንለምን ስለ ብዙ ምሕረትህ ነው እንጂ ስለ ጽድቃችን አይደለምና ጆሮህን አዘንብለህ ስማ፤ ዓይንህን ገልጠህ ጥፋታችንና ስምህ የተጠራባትን ከተማ ተመልከት። አቤቱ፥ ስማ፤ አቤቱ፥ ይቅር በል፤ አቤቱ፥ አድምጥና አድርግ፤ አምላኬ ሆይ፥ ስምህ በከተማህና በሕዝብህ ላይ ተጠርቶአልና ስለ ራስህ አትዘግይ።   እኔም ገና ስናገር ስጸልይ፥ በኃጢአቴና በሕዝቤም በእስራኤል ኃጢአት ስናዘዝ፥ በአምላኬም በእግዚአብሔር ፊት ስለ ተቀደሰው ስለ አምላኬ ተራራ ስለምን፥ ገናም በጸሎት ስናገር አስቀድሜ በራእይ አይቼው የነበረው ሰው ገብርኤል እነሆ እየበረረ መጣ፤ በማታም መሥዋዕት ጊዜ ዳሰሰኝ። አስተማረኝም፥ ተናገረኝም እንዲህም አለ፡- ዳንኤል ሆይ፥ ጥበብንና ማስተዋልን እሰጥህ ዘንድ አሁን መጥቻለሁ። አንተ እጅግ የተወደድህ ነህና በልመናህ መጀመሪያ ላይ ትእዛዝ ወጥቶአል፥ እኔም እነግርህ ዘንድ መጥቻለሁ ( ዳን 9 ) ፡፡    ማብራሪያ አይሁድእግዚአብሔርን ስለበደሉ እግዚአብሔር ወደ እርሱ እንዲመለሱ ብዙ ጊዜ ቢናገራቸውም አልተመለሱም፡፡ ስለዚህ በምርኮ አገር 70 ዓመት እንዲኖሩ አደረጋቸው፡፡ ተማርከው ከሄዱት አንዱ ዳንኤልም ነበር፡፡ እንዲያውም መጀመሪያ ከሄዱት ምርኮኞች ውስጥ ነበር፡፡ ወጣት ሆኖ የሄደው ዳንኤል በምርኮ አገር 70 ዓመት ገዳማ ኖbል፡፡ አሁን ዕድሜው አዛውንት በሚያስብለው ደረጃ ነው፡፡ 70 ዓመት የሚጠናቀቅበትን ጊዜ አሰላውና በጾምና በጸሎት ሆኖ በእግዚአብሔር ፊት ቀረበ፡፡ የሠሩትን ኃጢአት ተናዘዘ፡፡ እግዚአብሔርን እንደ በደሉትና በነቢያቱም ተመለሱ ቢባሉም አለመቀበላቸውንም ተናዘዘ፡፡ በደላቸው እጅግ ታላቅ እንደ ሆነም ገለጠ ፡፡ እግዚአብሔር ስላስማረካቸውም ባደረገው ነገር ጻድቅ እንደሆነ መሰከረ፡፡ የታላቁ የእግዚአብሔር ሕዝብ ሆኖ በጠላት እጅ መማረክ ያሳፍራልና  በመማረካቸው ያተረፉት እፍረትን መከናነብ እንደ ነበርም ጠቀሰ፡፡ የበደሉት ባለውለታቸውን ይኸውም አባቶቻቸውን ከግብጽ ያወጣውን አምላክ ነበር፡፡ እንደዚህ በድሎ ስማን ብሎ መጸለይ እንዴት ይቻላል? ብዙ ዕዳ ኖሮብን እንደገና ያንኑ ሰው ብድር መጠየቅ ያስፈራል፡፡ ዳንኤል ይህ ሁሉ በደል እያለ፡- ምን ብሎ ስማኝ ይበል? ያስፈራል፡፡ ከመጀመሪያውኑ፡- የምታስፈራ አምላክ ሆይ ብሎ ያለውም ለዚህ ነው፡፡ እንዲሰማው የተማጸነበት መንገድ ግን ልብን ይነካል፡፡  እንዲህ አለ፡- አምላኬ ሆይ፥ በፊትህ የምንለምን ስለ ብዙ ምሕረትህ ነው እንጂ ስለ ጽድቃችን አይደለምና ጆሮህን አዘንብለህ ስማ፡፡ ገና ስለ ራሱ ኃጢአትና ስለ ሕዝቡ ኃጢአት ተናዝዞ ( ይቅር በለን ብሎ) እያለ መልአኩ ገብርኤል እየበረረ መጣ፡፡ እየበረረ የሚለው ቃል ለአንድ ጉዳይ በጣም ትኩረት ተሰጥቶ በአስቸኳይ ለሚሆን ነገር ነው፡፡ አይሁድ በድለውና ዳንኤል ራሱን በማዋረድ፡- የምንለምንህ ስለ ብዙ ቸርነትህ ነው ብሎ ቸርነቱን ታምኖ ዳንኤል ሲጸልይ ገብርኤል እየበረረ መጣ፡፡ መልአኩ ገብርኤልም ለዳንኤል ገና መጸለይ ሲጀምር መልስ እንደ ተመለሰና መልሱን ግን ፡- የምንለምንህ ስለ ብዙ ምሕረትህ ነው ካለ በኋላ መሆኑ ነው ይነግረው ዘንድ እንደ መጣ አስታወቀው፡፡ ምንም ጽድቅ በሌለን ሰዓት ፣ በበደላችን ባሰለቸነው ሰዓት እንኳ፡- ይቅር በለን በማለት ፡- የምንለምንህ ስለብዙ ምሕረትህ ነው እንጂ ስለ ጽድቃችን አይደለምና ጆሮህን አዘንብለህ ስማን ብለን ስንጸልይ የሚሰማንና የሚያዝንልን አምላክ ነው ያለን፡፡ እግዚአብሔር ከምንለው በላይ ይቅር ባይ አምላክ ነው፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
69
4
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
61
5
የሐዋርያት ሥራ ጥናት :: ክፍል 52 :: ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ኤፌሶን መምጣቱ ፡፡   አጵሎስም በቆሮንቶስ ሳለ ጳውሎስ በላይኛው አገር አልፎ ወደ ኤፌሶን መጣ፥ አንዳንድ ደቀ መዛሙርትንም አገኘ። ባመናችሁ ጊዜ መንፈስ ቅዱስን ተቀበላችሁን? አላቸው። እነርሱም፡- አልተቀበልንም መንፈስ ቅዱስ እንዳለ ስንኳ አልሰማንም አሉት። እንኪያ በምን ተጠመቃችሁ? አላቸው። እነርሱም፡- በዮሐንስ ጥምቀት አሉት። ጳውሎስም፡- ዮሐንስስ ከእርሱ በኋላ በሚመጣው በኢየሱስ ክርስቶስ ያምኑ ዘንድ ለሕዝብ እየተናገረ በንስሐ ጥምቀት አጠመቀ አላቸው። ይህንም በሰሙ ጊዜ በጌታ በኢየሱስ ስም ተጠመቁ፤ ጳውሎስም እጁን በጫነባቸው ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ወረደባቸው በልሳኖችም ተናገሩ፥ ትንቢትም ተናገሩ። ሰዎቹም ሁሉ አሥራ ሁለት ያህሉ ነበር። ወደ ምኵራብም ገብቶ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት እየተነጋገረና እያስረዳቸው ሦስት ወር ያህል በግልጥ ይናገር ነበር። አንዳንዶች ግን እልከኞች ሆነው በሕዝብ ፊት መንገዱን እየሰደቡ ባላመኑ ጊዜ፥ ከእነርሱ ርቆ ደቀ መዛሙርትን ለየ፥ ጢራኖስም በሚሉት በትምህርት ቤት ዕለት ዕለት ይነጋገር ነበር። በእስያም የኖሩት ሁሉ አይሁድም የግሪክ ሰዎችም የጌታን ቃል እስኪሰሙ ድረስ ሁለት ዓመት ያህል እንዲህ ሆነ ( የሐዋ 19 ÷ 1 - 10 )።   ማብራሪያ ጳውሎስ በኤፌሶን ያገኛቸውን ደቀ መዛሙርት ፡- መንፈስ ቅዱስን ተቀበላችሁን? ሲላቸው አለመቀበላቸውንና መንፈስ ቅዱስ እንዳለም አለመስማታቸውን ነገሩት፡፡ ስለ መንፈስ ቅዱስ ግንዛቤ ላይኖራቸው የቻለው በንስሐ ጥምቀት በዮሐንስ ስለ ተጠመቁ ነበር፡፡ ጳውሎስ ሲነግራቸው ግን በኢየሱስ ስም ተጠመቁ፡፡ በኢየሱስ ስም ተጠመቁ የተባለው በአብ ፣ በወልድ ፣ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችቸው ( ማቴ 28 ÷ 19 ) ብሎ ጌታችን ኢየሱስ ለሐዋርያት የነገራቸውን ጥምቀት ነው፡፡ ጳውሎስ እጁን ጭኑ ሲጸልይላቸው መንፈስ ቅዱስ በግልጽ ወርዶ ሲሠራ ታየቶአል፡፡ ለሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ወርዶ በታየው መልኩ ማለት ነው፡፡ በበዓለ ኀምሳ ሐዋርያት በልሳን ተናግው እንደ ነበረው በልሳን ተናገሩ፡፡ ልሳን የማይታወቅ ቋንቋ አይደለም ፤ ልሳኑ ሰዎች በሚሰሙት ቋንቋ ካልሆነ ጥቅም የለውም፡፡ ተናጋሪው ለራሱ ይናገር ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ በቆሮንቶስ መልእክቱ ተናግሮአል ( 1ቆሮ 14 ÷ 27 ፡ 28 )  ፡፡ ጳውሎስ በአይሁድ የጸሎት ቤት በምኵራብ እየገባ ወንጌልን ይሰብክ ነበር፡፡ አልሰማ ሲሉት ደግሞ በትምህርት ቤት ሳይቀር ይሰብክ ነበር፡፡ በእስያ ሁለት ዓመት ያህል ወንጌልን እየሰበከ ቆይቶአል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ወረደባቸው የሚለው ቃል የሚያስረዳን ሁሌም መንፈስ ቅዱስ ከኛ ሊለይ በማይገባ በኩል ሊያድርብን እንደሚገባ ነው፡፡ ያለ መንፈስ ቅዱስ ክርስትና ከባድ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ ግን ሁሌም አድሮብን ሲኖር በክርስትናችን ውጤታማ እንሆናለን፡፡ መንፈስ ቅዱስ ሁሌም እንዲያድርብንና ከኛም እንዳይለይ እግዚአብሔርን ከለመንነው ይህን ጸሎታችንን እግዚአብሔር ይሰማል፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ  ቅዳሴ በተቀደሰ ቁጥር የሐዋርያት ሥራ ከሚነበቡ መጽሐፍት አንዱ ነው፡፡ ይቀጥላል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
66
6
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
54
7
ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ደም የተዋጀች ናት ፡፡   ጳውሎስ በእስያ እጅግ እንዳይቀመጥ ኤፌሶንን ይተው ዘንድ ቆርጦ ነበርና ..ከሚሊጢንም ወደ ኤፌሶን ልኮ የቤተክርስቲያንን ሽማግሌዎች አስጠራቸው፤ ወደ እርሱም በመጡ ጊዜ እንዲህ አላቸው። ..ወደ እግዚአብሔር ዘንድ ንስሐንና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ማመንን ለአይሁድና ለግሪክ ሰዎች እየመሰከርሁ በጉባኤም በየቤታችሁም አወራሁላችሁና አስተማርኋችሁ እንጂ፥ ከሚጠቅማችሁ ነገር አንዳች ስንኳ አላስቀረሁባችሁም። ..የእግዚአብሔርን ጸጋ ወንጌልን መመስከር እፈጽም ዘንድ ነፍሴን በእኔ ዘንድ እንደማትከብር እንደ ከንቱ ነገር እቆጥራለሁ። አሁንም፥ እነሆ፥ እኔ የእግዚአብሔርን መንግሥት እየሰበክሁ በመካከላችሁ የዞርሁ ሁላችሁ ከእንግዲህ ወዲህ ፊቴን እንዳትዩ አውቃለሁ። ..በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ ( የሐዋ 20 ÷ 16 - 28 ) ።   ማብራሪያ ሐዋርያው ጳውሎስ ኤፌሶንን ለቆ መሄድ ስላሰበ የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎችን አስጠራቸው ፡፡ የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎች የሚለው በግዕዙ ቀሲሳን ይለዋል ፡፡ ቀሲሳን ማለት ቀሳውስት ማለት ነው ፡፡ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን ቀሳውስት ብላ ስትጠራ ግዕዙን ስለምትጠቀም ነው ፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎቹን ብዙ ነገር ብሎአቸዋል ፡፡ ከቁ. 16 - 28 ባለው ንባብ እኔ ትኩረት ልሰጠው የፈለኩትን ብቻ ነው ያሰፈርኩት ፡፡ የጠራቸውን የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎች እንደ ተናገረው አስተሮአቸዋል ፤ በመንፈሳዊው ረገድ በብዙ ጠቅሞአቸዋል ፡፡ ራሱ ወንጌል ሰብኮላቸው አምነውም ሊሆኑ ይችላሉ ፡፡ የሾማቸውም እርሱ ሊሆን ይችላል ፡፡ ምክንያቴ ደግሞ በኤፌሶን ሦስት ዓመት ያህል በመቆየት ወንጌልን ሰብኮ ብዙ ሰዎች እንዲያምኑ አድርጎአል ( የሐዋ 20 ÷ 31 ) ። በሰበከባቸው ቦታዎች የቤተ ክርስቲያንን አገልጋዮች የሚሾምበት ጊዜ ነበር  ( የሐዋ 14 ÷ 23 ) ፡፡ ሐዋርያው ከተናገረው ፡- ü  አይሁድም የግሪክም ሰዎች ንስሐ እንዲገቡና በኢየሱስ ክርስቶስ እንዲያምኑ መመስከሩ ü  የእግዚአብሔርን የጸጋውን ወንጌልን ማስተማሩ ü   የእግዚአብሔርን መንግሥት መስበኩ ተጠቃሾች ናቸው ፡፡ ከበላይ የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎች ያላቸውን ወረድ ስንል ጳጳሳት በማለት ጠርቶአቸዋል ፡፡  ከፈቃደ መንፈስ ቅዱስ ጳጳሳት ሆነው የተሸሙትን ታዲያ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን እንዲጠብቁአት አሳስቦቸዋል ፡፡ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ምእመናንን ከተኩላዎች መጠበቅ አለባቸው ፡፡ ሐዋርያው እንደ ተናገረው ቤተ ክርስቲያን የተዋጀችው በደም ነው ፡፡ ደሙን በቀራንዮ ባፈሰሰው በክርስቶስ ደም ፡፡ በብሉይ ኪዳን የሰውም ሆኑ የእንስሳት በኩር የእግዚአብሔር ነው ፡፡ የሰው በኵር ሲሆን መዋጀት ይችላል ፡፡ አባት የበኩር ልጁን፡- የኔ ነው ማለት አይችልም፡፡ የበኵር ልጅ የእግዚአብሔር ነው ፡፡ አባት ልጁን ማስቀረት ከፈለገ የተተመነውን ገንዘብ መክፈል አለበት ( ዘኁ 18 ÷ 16 )  ፡፡ ገንዘቡን ከፈለ ማለት ልጁን ዋጀ ማለት ነው ፡፡ ስለዚህ በብር ወይም በገንዘብ መዋጀት እንደ ነበር አየን ማለት ነው ፡፡ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን የዋጃት በብር አይደለም ፡፡ በገዛ ደሙ ነው ፡፡ እኛ በክርስቶስ ያመንን ምዕመናን ቤተ ክርስቲያን ተብለን እንጠራለን፡፡ ቤተ ክርስቲያን ማለት በክርስቶስ ያመኑ የምዕመናን ኅብረት ማለት ነውና፡፡ ቤተ ክርስቲያን የተዋጀችው በብር ወይም በገንዘብ አይደለም ፡፡ በብር ወይም በገንዘብ ሊተመን በማይችል በክርስቶስ ደም ነው ፡፡ ቅዳሴ ተቀድሶ፡- አሜን ተብሎ ፡- እትዉ በሰላም ( በሰላም ግቡ ) ከመባሉ በፊት ቄሱ የሚለውን ላስነብባችሁ ፡፡ …በአንድ ልጅህ በጌታችንና በአምላካችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በክቡር ደሙ የዋጀሃት ቤዛም የሆንኻት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንህንም ጠብቃት ( የሐዋርያት ቅዳሴ  ) ፡፡ ቤተ ክርስቲያን በኢየሱስ ክርስቶስ ክቡር ደም እንደ ተዋጀች በቅዳሴም ላይ ይነገራል ፡፡ እኛ ኦርቶዶክሳውያን በክርስቶስ ደም የተዋጀን ነን ፡፡ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በገዛ ደሙ የተዋጀች ናት ፡፡ እርስዋ ራሷም ( የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ) መልሳ ፡- በልጅህ ደም የዋጃሃት ቤተ ክርስቲያንሀን ጠብቃት ብላ የምትጸልይ ናት ፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በመስከረም 25 ቅዳሴ ሲቀደስና ከቁ. 9 - 28 ያለው ሲነበብ ከበላይ የጠቀሱኩት ክፍል ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌ ) ፡፡ ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
82
8
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
68
9
የሐዋርያት ሥራ ጥናት ፡፡ ክፍል 51 ፡፡ የቅዱስ ጳውሎስ ሦስተኛው ሐዋርያዊ ጉዞ ጅማሮ ፡፡   ከክፍል 50 ባጭሩ፡፡ …ወደ ቂሣርያም በደረሰ ጊዜ ወጥቶ ለቤተ ክርስቲያን ሰላምታ ከሰጠ በኋላ ወደ አንጾኪያ ወረደ ( የሐዋ 18 ÷ 12 - 22 )። -------/////--------   ጥቂት ቀንም ቆይቶ ወጣ፥ ደቀ መዛሙርትንም ሁሉ እያጸና በገላትያ አገርና በፍርግያ በተራ አለፈ። በወገኑም የእስክንድርያ ሰው የሆነ ነገር አዋቂ የነበረ አጵሎስ የሚሉት አንድ አይሁዳዊ ሰው ወደ ኤፌሶን ወረደ፤ እርሱም በመጻሕፍት እውቀት የበረታ ነበረ። እርሱ የጌታን መንገድ የተማረ ነበረ፥ የዮሐንስንም ጥምቀት ብቻ አውቆ በመንፈስ ሲቃጠል ስለ ኢየሱስ ይናገርና በትክክል ያስተምር ነበር። እርሱም በምኵራብ ገልጦ ይናገር ጀመር። ጵርስቅላና አቂላም በሰሙት ጊዜ፥ ወስደው የእግዚአብሔርን መንገድ ከፊት ይልቅ በትክክል ገለጡለት። እርሱም ወደ አካይያ ማለፍ በፈቀደ ጊዜ፥ ወንድሞቹ አጸናኑት፥ ይቀበሉትም ዘንድ ወደ ደቀ መዛሙርት ጻፉለት፤ በደረሰም ጊዜ አምነው የነበሩትን በጸጋ እጅግ ይጠቅማቸው ነበር፤ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ እንደ ሆነ ከመጻሕፍት እየገለጠ ለአይሁድ በሁሉ ፊት በጽኑ ያስረዳቸው ነበርና ( የሐዋ 18 ÷ 23 - 28 )።   ማብራሪያ ከሐዋ ም 18 ÷ 23 – ም 21 ÷ 16 ያለው የሐዋርያው የጳውሎስ ሦስተኛው ጉዞ ተብሎ ይጠራል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ገላትያ አገርና ፍርግያ በመሄድ ያመኑትን ክርስቲያኖች አጸና፡፡ ገላትያ ዛሬ ቱርክ በሚባል አገር ውስጥ ይገኛል፡፡ በመጀመሪያው ጉዞው በገላትያ ባሉ ከተሞች ወንጌልን ሰብኮ ነበር፡፡ ጳውሎስ ባልና ሚስቶቹን አቂላንና ጵርስቅላን ትቶአቸው ወደ ነበረበት ወደ ኤፌሶን አጵሎስ የሚባል አይሁዳዊ ወረደ፡፡ ኤፌሶን በእስያ የምትገኝ ከተማ ናት፡፡ አጵሎስን ጨምሮ በግብፅ በምትገኘው በእስክንድርያ ብዙ አይሁድ ይኖሩ ነበር፡፡ አጵሎስ የብሉይ ኪዳን ቅዱሳት መጻሕፍትን በደንብ የተማረ ነበር፡፡ በመንፈስ ቅዱስ እየተቃጠለ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ በትክክል ያስተምር ነበር፡፡ ይሁን እንጂ እርሱ የሚያውቀው የዮሐንስን ጥምቀት ብቻ ነበር፡፡ ዮሐንስ ያጠምቅ የነበረው ከርስቶስ እስኪመጣ ነበር፡፡ አጵሎስ ስለ ጌታችን ኢየሱስ እውቀት አለው፡፡ ሙሉ እውቀት ነበር የሌለው፡፡ በአይሁድ የጸሎት ቤት ምኵራብ በመግባት መጥምቁ ዮሐንስ ፡- ከኔ በኋላ ይመጣል ስላለው ክርስቶስ ሳይፈራ ይናገር ነበር፡፡ እግዚአብሔር አጵሎስን ወደ ኤፌሶን ያመጣው ከአቂላና ጵርስቅላ ጋር ሊያገናቸው ነበርና ስለ ክርስቶስ ከፊት ይልቅ በትክክል ገለጡለት፡፡ አጵሎስ በግሪክ ወደምትገኘው አካይያ ለመሄድ በፈለገ ጊዜ ወንድሞች አበረታቱት፤ በዛም ክርስቲያኖች እንዲቀበሉት ደብዳቤ ጻፉለት፡፡ በደረሰም ጊዜ በክርስቶስ አምነው የነበሩትን በጣም ጠቀማቸው፡፡ በብሉይ መሲሕ ተብሎ ስለ ክርስቶስ ተነግሮ ነበርና፡- ያ መሲሕ መጥቶአል፡፡ እርሱም ኢየሱስ ነው እያለ ከብሉይ መጻሕፍት እየጠቀሰ አይሁዳውያንን ያስረዳቸው ነበር፡፡ እኛ ኦርቶዶክሳውያን በኢየሱስ ክርስቶስ እናምናለን፡፡ አንዳንዶች ያመነውን ክርስቶስ፡- ተቀበሉ ሲሉን ይደመጣሉ፡፡ ለኦርቶዶክስ ምዕመን ጌታን ተቀበል ተብሎ አይሰበክም፡፡ ጌታን ኢየሱስን እናውቀዋለን፡፡ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ያለን እውቀት ግን ከፊት ይልቅ የበለጠ እያደገ መምጣት አለበት፡፡ በቤተ ክርስቲያን ስብከተ ወንልን ማጠናከር አለብን ሲባል መቼም እንሰማለን፡፡ ስብከተ ወንጌል የተባለው እኮ ስለ ክርስቶስ ነው፡፡ የኢ/ኦ/ተቤ/ክ የቅዱስ ጳውሎስ አርአያን በመከተል ወንጌልን በትጋት ለመስበክ ያለምንም መዘናጋት ሁሌም ቁርጠኝነቱ ሊኖራት ይገባል፡፡ ወንጌልን ሲሰበክ ያለነው እንጸናለን፤ የራቁት ወደ ቤቱ ይመጣሉ፤ ኢአማንያን ደግሞ ወደ ማመን ይመጣሉ፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በጳጉሜ 1 ቅዳሴ ሲቀደስ በሐዋ 18 ÷ 23 - 28 ያለው ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌ) ፡፡ ይቀጥላል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
67
10
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
66
11
እግዚአብሔር ባሪያን ገዢ አድርጎ የሚሾም ነው ፡፡ ይሁዳም ወንድሞቹን እንዲህ አላቸው። ወንድማችንን.. ኑ፥ ለእስማኤላውያን እንሽጠው፥ ..ወንድሞቹም የእርሱን  ነገር ሰሙት። የምድያም ነጋዶችም አለፉ፤ ..ለእስማኤላውያንም ዮሴፍን በሀያ ብር ሸጡት፤ እነርሱም ዮሴፍን ወደ ግብፅ ወሰዱት ( ዘፍጥ 37 ÷ 26 - 28 ) ።  ..የፈርዖን ጃንደረባ የዘበኞቹም አለቃ የሚሆን የግብፅ ሰው ጲጥፋራ ወደ ግብፅ ካወረዱት ከእስማኤላውያን እጅ ገዛው። እግዚአብሔር ከዮሴፍ ጋር ነበረ፥ ሥራውም የተከናወነለት  ሰው ሆነ፤ በግብፃዊው ጌታውም ቤት ነበረ   ። ዮሴፍም በጌታው ፊት ሞገስን አገኘ፥ እርሱንም ያገለግለው ነበር፤ በቤቱም ላይ ሾመው.. ..የዮሴፍም ፊቱ መልከ  መልካምና ውብ ነበረ። ከዚህም በኋላ እንዲህ ሆነ፤ የጌታው ሚስት ..ከእኔም ጋር ተኛ አለችው። ..ልብሱን ተጠማጥማ ያዘች፤ እርሱም ልብሱን በእጅዋ ትቶላት ሸሸ.. ጌታው ወደ ቤቱ እስኪገባ ድረስም ልብሱን ከእርስዋ ዘንድ አኖረች። ..እንዲህ ብላ ነገረችው። ..ዕብራዊው ባሪያ ( ዮሴፍን ነው ) ..ወደ እኔ ገባ፤ ..ድምፄን ከፍ አድርጌ ስጮኽ ልብሱን በእጄ ተወና ወደ ውጭ ሸሸ።  ጌታውም፡- ..የሚስቱን ቃል በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ። የዮሴፍም ጌታ ..ወደ ግዞት ቤት አገባው.. ( ዘፍጥ 39 ÷ 1 ፡ 2 ፡ 4 ፡ 7 ፡ 12 ፡ 16 - 20  ) ። ( ከዓመታት በኋላ ) ፈርዖንም ልኮ ዮሴፍን አስጠራ፥ ከግዞት ቤትም አስቸኰሉት፤ ..ወደ ፈርዖንም ገባ። ፈርዖንም ዮሴፍን አለው። ሕልምን አየሁ፥ የሚተረጕመውም አልተገኘም፤ ሕልምን እንደ ሰማህ፥ እንደ ተረጐምህም ስለ አንተ ሰማሁ፡፡ ዮሴፍም ፈርዖንን አለው። የፈርዖን ሕልሙ አንድ ነው፤ እግዚአብሔር ሊያደርገው ያለውን ለፈርዖን ነግሮታል። ..በግብፅ ..ጥጋብ የሚሆንባቸው  ሰባት ዓመታት ይመጣሉ፤ ከዚህ በኋላ የሰባት ዓመት ራብ ይመጣል.. ፈርዖንም ዮሴፍን፡- በግብፅ ምድር ሁሉ ላይ ሾምሁህ አለው።  ፈርዖን ቀለበቱን ከእጁ አወለቀ በዮሴፍ እጅም አደረገው፥ ነጭ የተልባ እግር ልብስንም አለበሰው፥ በአንገቱም  የወርቅ ዝርግፍን አደረገለት፤ የእርሱም በምትሆን በሁለተኛይቱ ሰረገላ አስቀመጠው፥  አዋጅ ነጋሪም፡- ስገዱ እያለ በፊት በፊቱ ይጮኽ ነበር፤  እርሱም በግብፅ ምድር ሁሉ ላይ ተሾመ። ዮሴፍም በግብፅ ንጉሥ በፈርዖን ፊት በቆመ ጊዜ ዕድሜው ሠላሳ ዓመት ነበረ.. ( ዘፍጥ 41 ÷ 14 ፡ 15 ፡ 25 ፡ 29 ፡ 30 ፡ 41 - 43  ) ።   (ዮሴፍ በግብፅ ገዢ ስለ መሆኑ የዮሴፍ ወንድሞች ለአባታቸው የተናገሩት ) እንዲህም ብለው ነገሩት ( ለአባታቸው ) ፡- ዮሴፍ ገና በሕይወቱ ነው፥ እርሱም በግብፅ ምድር ሁሉ ላይ ገዥ ሆኖአል.. ( ዘፍጥ 45 ÷ 26 ) ፡፡ ማብራሪያ የዮሴፍ ወንድሞች በዮሴፍ ስለሚቀኑበት በይሁዳ ወንድማቸው ምክር ተስማምተው ሸጡት ፡፡ ዮሴፍን የገዙት ለግብፅ ንጉሥ ለፈርዖን ሹም ለሆነው ለጲጥፋራ ሸጡት ፡፡ ዮሴፍ በባርነት ሲያገለግል የጌታው ሚስት ከኔ ጋር ዝሙት ፈጽም ስትለው እምቢ በማለቱ በሀሰት ክስ ተወንጅሎ ወደ እስር ቤት ተወረወረ ፡፡ ዮሴፍ በትንሹ ከሁለት ዓመታት በላይ መታሰሩ እሙን ነው ፡፡ ምክንያቱም ከእርሱ በኋላ ወደ እስር ቤት ገብቶ የተፈታው የጠጅ አሳላፊዎች አለቃ ለሁለት ዓመታት መታሰሩን ስለምናገኝ ( ዘፍጥ 41 ÷ 1 ) ዮሴፍ ደግሞ ከዛም በፊት በእስር ቤት ነበረ ፡፡ ፈርዖን ሕልም ባለመ ጊዜ ዮሴፍ ሕልም እንደሚፈታ በመስማቱ ከእስር ቤት እንዲፈታ አስደረገ ፡፡ ዮሴፍ ሕልም እንደሚፈታ ለፈርዖን የነገረው ደግሞ የተፈታው የጠጅ አሳላፊዎች አለቃ ነበር ፡፡ ሕልም አልሞ ዮሴፍ ሕልሙን ተርጕሞለት ነበር ፡፡ ፈርዖን ሕልሙን ለዮሴፍ ነገረው፤ ዮሴፍም ሕልሙን በመተርጎም ሰባት ዓመታት የጥጋብ ፣ ሌሎች ሰባት ዓመታት የረሃብ እንደሚመጡ አስገነዘበው ፡፡ ፈርዖን ዮሴፍን ከእርሱ በታች ገዢ አድርጎ በ30 ዓመቱ ሾመው ፡፡ እግዚአብሔር ዮሴፍን በሸጡት ወንድሞቹም ፊት ገዢ አድርጎ አሳይቶአቸዋል ፡፡ እግዚአብሔር ሰው የማያምነውን ነገር አደረገ ፡፡ የዮሴፍ ወንድሞች ዮሴፍን ሸጠው ሲያበቁ ለአባታቸው ግን፡- ልጅህ ሞቶአል ብለው ነበር የነገሩት ( ዘፍጥ 37 ÷ 29 - 35 )  ፡፡ ሞተ ተብሎ የተVረተበት ዮሴፍ ገዢ ሆኖ ተገኘ ፡፡ እግዚአብሔር በእርሱ የታመነውን ሰው ሊያውም ባሪያ የነበረውን ዮሴፍን ገዢ አድርጎ የሾመ አምላክ ነው ፡፡ ዮሴፍ የመዋረድን ዝቅተኛውን ባርነትን ካየ በኋላ በአምላኩ እስከ መጨረሻ በመታመኑ የሆነውን አይተናል ፡፡ እግዚአብሔር ለወግ ለማዕረግ ያበቃል ፡፡ ዮሴፍን ገና በለጋ ዕድሜው ከሚወደው አባቱ ለይቶ ለብቻው አኖረው ፡፡ ከመከራ ሁሉ እየጠበቀው ያሳደገውና ለወግ ለማዕረግ በማድረስ በግብፅ ገዢ እንዲሆን ያደረገ እኛንም አይተወንም ፡፡ የእግዚአብሔር ሀሳብ ሰው በክርስቶስ አምኖ መንግሥቱን እንዲወርስ ነው ፡፡ በምድር ስንኖርም የሚረዳን ዘመድ አዝማድ ባይኖረን ለወግ ለማዕረግ ያበቃናል፡፡ እንደ ዮሴፍ መታገሥ ግን አስፈላጊ ነው ፡፡ ዮሴፍ ብዙ ዓመታትን በመጠበቅ ታግሦአል ፡፡ ውጣ ውረዱ ቢበዛብንም እንደ ዮሴፍ እግዚአብሔርን እንታመነው ፡፡ ከፊታችን የተሻለ የክብር ጊዜ አለ ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን ! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
90
12
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
72
13
የሐዋርያት ሥራ ጥናት :: ክፍል 50 :: የቅዱስ ጳውሎስ ሁለተኛው ሐዋርያዊ ጉዞ መጠናቀቅ ፡፡   ጋልዮስም በአካይያ አገረ ገዥ በነበረ ጊዜ፥ አይሁድ በአንድ ልብ ሆነው በጳውሎስ ላይ ተነሡ፥ ወደ ፍርድ ወንበርም አምጥተው፡- ይህ ሕግን ተቃውሞ እግዚአብሔርን ያመልኩት ዘንድ ሰዎችን ያባብላል አሉ። ጳውሎስም አፉን ሊከፍት ባሰበ ጊዜ፥ ጋልዮስ አይሁድን፡- አይሁድ ሆይ፥ ዓመፅ ወይም ክፉ በደል በሆነ እንድታገሣችሁ በተገባኝ፤ ስለ ቃልና ስለ ስሞች ስለ ሕጋችሁም የምትከራከሩ ከሆነ ግን፥ ራሳችሁ ተጠንቀቁ እኔ በዚህ ነገር ፈራጅ እሆን ዘንድ አልፈቅድምና አላቸው። ከፍርድ ወንበርም ፊት አስወጣቸው። የግሪክ ሰዎችም ሁሉ የምኩራብ አለቃ ሶስቴንስን ይዘው በወንበሩ ፊት መቱት፤ በእነዚህም ነገሮች ጋልዮስ ግድ የለውም ነበር። ከዚህም በኋላ ጳውሎስ እጅግ ቀን ተቀምጦ ወንድሞቹንም ተሰናብቶ በመርከብ ወደ ሶርያ ሄደ፤ ስለትም ነበረበትና ራሱን በክንክራኦስ ተላጨ፤ ጵርስቅላና አቂላም ከእርሱ ጋር ነበሩ። ወደ ኤፌሶንም በደረሱ ጊዜ እነዚያን ከዚያ ተዋቸው፥ ራሱ ግን ወደ ምኵራብ ገብቶ ከአይሁድ ጋር ይነጋገር ነበር። እነርሱም ብዙ ጊዜ እንዲቀመጥላቸው ሲለምኑት እሺ አላለም፤ ነገር ግን ሲሰናበታቸው፡- የሚመጣውን በዓል በኢየሩሳሌም አደርግ ዘንድ ይገባኛል እግዚአብሔር ቢፈቅድ ግን ወደ እናንተ ደግሞ እመለሳለሁ አላቸው። ከኤፌሶንም በመርከብ ተነሣ። ወደ ቂሣርያም በደረሰ ጊዜ ወጥቶ ለቤተ ክርስቲያን ሰላምታ ከሰጠ በኋላ ወደ አንጾኪያ ወረደ። ( የሐዋ 18 ÷ 12 - 22 )።   ማብራሪያ አካይያ በግሪክ አገር ያለ ነው፡፡ በአካይ ላይ አገረ ገዥ በነበረው በጋልዮስ ፊት አይሁድ ጳውሎስን አቅርበው ከሰሱት፡፡ የአሁኑን ጨምሮ ጳውሎስ ስለ ወንጌል ብዙ መከራ የተቀበለ ሰው ነው፡፡ ስለ ወንጌል በሚቀበለው መከራ፡- ታከተኝ ያላለ የእግዚአብሔር ሰው ነው፡፡ ሕግን ይቃወማል ተብሎ በሐሰት የተከሰሰው ጳውሎስ ስለ ተከሰሰበት ጉዳይ ሊመልስ ሲል አገረ ገዢው አይሁድን ክሳቸው በገዢው ፊት ውኃ የማይቋጥር ከሆነ እንደማይፈርድላቸው ከነገራቸው በኋላ ከፊቱ አስወጣቸው፡፡  የአይሁድ የጸሎት ቤት የምኩራብ አለቃው ሶስቴንስ ሲደበደብ እያየ አገረ ገዢው ግድ አልሰጠውም፡፡ ሊከሱት የፈለጉት ጳውሎስ እያለ የምኩራብ አለቃው ሶስቴንስ ለምን እንደ ተደበደበ በግልጽ አልተጠቀሰም፡፡ ከዚህ ነገር በኋላም ጳውሎስ በቆሮንቶስ ብዙ ቀን ተቀመጠ፡፡ ከዚያም በመርከብ ወደ ሶርያ አቀና፡፡ ጳውሎስ ስለት እንደ ነበረበት መገለጹ ስለቱ ምን እንደ ነበረ ባይጠቀስም ክንክራኦስ በተባለ ስፍራ ጠጉሩን መላጨቱ የስለቱ ጊዜ ሲፈጸም የሚደረግ ሥርዓት እንደ ሆነ በብሉይ ተጠቅሶአል ( ዘኁ   6 18 ፡ 19 ) ፡፡ ጳውሎስ ጉዞውን ወደ ኤፌሶን አቅንቶ ከአይሁድ ጋር የእግዚአብሔርን ቃል ይነገጋገር ነበር፡፡ በኤፌሶን እንዲሰነብትላቸው ቢጠይቁትም አሁን ወደ ኢየሩሳሌም መሄድ እንደሚፈልግና የእግዚአብሔር ፈቃድ ከሆነ ተመልሶ ሊያያቸው እንደሚፈልግ ነግሮአቸው የጉዞውን መዳረሻ አንጾኪያ አድርጎአል፡፡ አንጾኪያ ሀገረ ስብከቱ ናት፡፡ ከሐዋ ም 15 ÷ 36 – ም 18 ÷ 22 ያለው የሐዋርያው የጳውሎስ ሁለተኛው ጉዞ ተብሎ ይጠራል፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ  ቅዳሴ በተቀደሰ ቁጥር የሐዋርያት ሥራ ከሚነበቡ መጽሐፍት አንዱ ነው፡፡ ይቀጥላል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
85
14
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
78
15
ለምኑ ይሰጣችኋል ፡፡   ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፈትላችሁማል። የሚለምነው ሁሉ ይቀበላልና፥ የሚፈልገውም ያገኛል፥ መዝጊያንም ለሚያንኳኳ ይከፈትለታል።ወይስ ከእናንተ፥ ልጁ እንጀራ ቢለምነው፥ ድንጋይን የሚሰጠው ከእናንተ ማን ሰው ነው? ዓሣስ ቢለምነው እባብን ይሰጠዋልን? እንኪያስ እናንተ ክፉዎች ስትሆኑ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠትን ካወቃችሁ፥ በሰማያት ያለው አባታችሁ ለሚለምኑት እንዴት አብልጦ መልካም ነገርን ይሰጣቸው? (ማቴ 7 ፥ 7 - 11 ) ፡፡   ማብራሪያ ለምንድን ነው የማንጸልየው? ኃጢአተኞች ስለሆንን እግዚአብሔር አይሰማንም ብለን ሊሆን ይችላል ፡፡ ሥጋ ለባሽ ነንና ኃጢአት መሥራታችን የማይቀር ነው ፡፡ ኃጢአት ሠርተን፡- ይቅር በለን ሳንል ብንጸልይ አይሰማንም ፡፡ እኛ ደካሞች ነን ፡፡ ኃጢአት አይለየንም ነገር ግን በደላችንን ይቅር በለን እያልን እንድንጸልይ ተነግሮናል፡፡ ስንጸልይ፡- አባታችን ሆይ እንላለን ፡፡ በአባታችን ሆይ ጸሎት ውስጥ፡- በደላችንን ይቅር በለን ስለምንል ይቅር ይለናል፡፡ አባታችን ሆይ በሰማይ የምትኖር እያልን ስንጸልይ፡- አባታችን ሆይ ስንለው አባታችን እያልነው ነው፡፡ እግዚአብሔር አባታችን ነው፡፡ ሰዎች የቱንም ያህል ክፉ ቢሆኑ እንኳን ለልጆቻቸው በእንጀራ ፋንታ ድንጋይ አይሰጡም፡፡ ታዲያ ቸሩ አባት እግዚአብሔርማ ሁልጊዜም በደላችንን ይቅር በለን እያልን የምንጸልየውን ጸሎት እንዴት አይሰማ? ይሰማል እንጂ!!! ስለዚህ አንኳኩ ይከፈትላችኋል ስለተባልን እናንኳኳ፡፡ ስለ ተቸገርኩና በችግሬ ግዜ ስለምነው ይሰማኛል ወይ? ለሚል ጠያቂ፡- ይቅር በለኝ ብለን ከለመንነው አዎ ይሰማናል፡፡ ምናሴ የሚባል ንጉሥ እግዚአብሔርን በጣም የበደለ ክፉ ሰው ሲሆን ቢናገረውም እግዚአብሔርን ፈጽሞ ያልሰማ ንጉሥ ነበር፡፡ ሲጨንቀው ግን እግዚአብሔር ይቅር እንዲለውና ጸሎቱን እንዲሰማው ለመነ፡፡ እግዚአብሔር ይቅር ብሎት ጸሎቱንም ሰምቶታል፡፡ እግዚአብሔርም ምናሴንና ሕዝቡን ተናገራቸው፤ ግን አልሰሙትም። ..በተጨነቀም ጊዜ አምላኩን እግዚአብሔርን ፈለገ፥ በአባቶቹም አምላክ ፊት ሰውነቱን እጅግ አዋረደ ( ይቅር በለኝ አለ )፥  ወደ እርሱም ጸለየ፤ እርሱም ተለመነው ( 2 ዜና 33 ÷ 10-13 ) ፡፡ እግዚአብሔርን የበደለው ምናሴ ጨንቆት ሲለምነው፡- ሲጨንቅህ ነው እንዴ የምትለምነኝ ? ሳይል እግዚአብሔር ተለምኖታል፡፡ እኛም እንለምነው ይለመነናል፡፡ ስለ ጤናችንም እንለምነው፡፡ በተለያየ በሽታ ስንያዝ እንዲያድነን ዘወትር እንለምነው፡፡ ወንጌላዊው ዮሐንስ ጋይዮስ ስለሚባለው ጤና ይጸልይ ነበር፡፡ እንዲህ በማለትም ጽፎለታል፡- ጤና እንዲኖርህ እጸልያለሁ ( 3ተኛ ዮሐ ቁ 2) ። የለመነውን ያንኑ እንድንቀበል እኛም ስለ ራሳችንንና ስለ ታመሙ ሰዎችም እንለምነው፡፡ ለምኑ ይሰጣችኋል ያለን አምላክ ስለ ጤናችንም የለመነውን ልመና ይሰማናል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
90
16
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
83
17
የሐዋርያት ሥራ ጥናት ፡፡ ክፍል 49 ፡፡ የሐዋርያው ጳውሎስ የወንጌል አገልግሎት በቆሮንቶስ ፡፡   ከዚህም በኋላ ጳውሎስ ከአቴና ወጥቶ ወደ ቆሮንቶስ መጣ። በወገኑም የጳንጦስ ሰው የሚሆን አቂላ የሚሉትን አንድ አይሁዳዊ አገኘ፤ እርሱም ከጥቂት ጊዜ በፊት ከሚስቱ ከጵርስቅላ ጋር ከኢጣልያ መጥቶ ነበር፥ አይሁድ ከሮሜ ይወጡ ዘንድ ቀላውዴዎስ አዞ ነበርና፤ ወደ እነርሱ ቀረበ፥ ሥራቸውም አንድ ስለ ነበረ በእነርሱ ዘንድ ተቀምጦ በአንድ ላይ ሠሩ፤ ሥራቸው ድንኳን መስፋት ነበረና። በየሰንበቱም ሁሉ በምኵራብ ይነጋገር ነበር፥ አይሁድንና የግሪክንም ሰዎች ያስረዳ ነበር። ሲላስና ጢሞቴዎስም ከመቄዶንያ በወረዱ ጊዜ፥ ጳውሎስ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ እንደ ሆነ ለአይሁድ እየመሰከረ ለቃሉ ይተጋ ነበር። ነገር ግን በተቃወሙትና በተሳደቡ ጊዜ፥ ልብሱን እያራገፈ፡- ደማችሁ በራሳችሁ ነው፤ እኔ ንጹሕ ነኝ ከእንግዲህ ወዲህ ወደ አሕዛብ እሄዳለሁ አላቸው። ከዚያም ወጥቶ ኢዮስጦስ ወደሚባል እግዚአብሔርን ወደሚያመልክ ሰው ቤት ገባ ቤቱም በምኩራብ አጠገብ ነበረ። የምኵራብ አለቃ ቀርስጶስም ከቤተ ሰዎቹ ሁሉ ጋር በጌታ አመነ፥ ከቆሮንቶስ ሰዎችም ብዙ በሰሙ ጊዜ አምነው ተጠመቁ። ጌታም ሌሊት በራእይ ጳውሎስን፡- እኔ ከአንተ ጋር ነኝ፥ ማንም ክፉ ሊያደርግብህ የሚነሣብህ የለምና አትፍራ፥ ነገር ግን ተናገር ዝምም አትበል፤ በዚህ ከተማ ብዙ ሕዝብ አሉኝና አለው። በመካከላቸውም የእግዚአብሔርን ቃል እያስተማረ ዓመት ከስድስት ወር ተቀመጠ ( የሐዋ 18 ÷ 1 - 11 )።   ማብራሪያ ጳውሎስ ከግሪኳ አቴና ወደ ሌላኛይቱ የግሪክ ከተማ ቆሮንቶስ መጣ፡፡ ባልና ሚስቶቹን አቂላና ጵርስቅላን አገኘ፡፡ እነርሱ ከኢጣልያ ወደ ቆሮንቶስ መጥተው ነበር፡፡ እንደ ጳውሎስ ሥራቸው ድንኳን መስፋት ነበር፡፡ ጳውሎስ ወንጌልን እየሰበከ በግሉ ደግሞ ድንኳን በመስፋት የሚተዳደር ሰው ነበር፡፡ እንደ ተለመደው ወደ አይሁድ ምኵራብ በመግባት ቃሉን ይነግራቸው ጀመር፡፡ ለግሪክ ሰዎችም ሳይቀር ይናገር ነበር፡፡ ሲላስና ጢሞቴዎስ በመቄዶንያ አገር ከምትገኘው ከቤርያ ስለመጡ አብረው ማገልገል ጀመሩ፡፡ ጳውሎስ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ነግሮአቸው ላልተቀበሉት አይሁድ፡- እኔ ከደሙ ንጹሕ ነኝ፤ ወደ አሕዛብ እሄዳለሁ ይላቸው ነበር፡፡ በቆሮንቶስ የምኵራብ አለቃውን ጨምሮ ብዙ ሰዎች በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው ተጠምቀዋል፡፡ ጌታም ለጳውሎስ በሌሊት ተልጦ፡- ከአንተ ጋር ነኝ፤ ክፉ ሊያደርግብህ የሚነሣብህ የለም፤ አትፍራ ፤ ቃሉን ስበክ፤ ዝም አትበል ፤ ገና የሚያምኑ ብዙ ሰዎች አሉኝ እያለ ያበረታታው ነበር፡፡  ቅዱስ ጳውሎስ ወንጌልን እያስተማረ ዓመት ከስድስት ወር ያህል በቆሮንቶስ ተቀምጦአል፡፡ ወንጌል ማለት የምሥራች ማለት ሲሆን ምሥራቹ ደግሞ ክርስቶስ እኛን ለማዳን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ መሞቱና እኛን ስለማጽደቅም ከሞት መነሣቱ ነው፡፡ የሚያምንብኝም ሁሉ ለዘላለም አይሞትም ( ዮሐ 11 ÷ 26 ) ስላለ አምነን የተከተልነው እኛ የዘላለም ሞትን አንሞትም፡፡ ከዘላለም ፍርድም ያድነናል፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ቅዳሴ በተቀደሰ ቁጥር የሐዋርያት ሥራ ከሚነበቡ መጽሐፍት አንዱ ነው፡፡ ይቀጥላል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
88
18
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
89
19
ዛሬያችን ጨለማ መስሎ ቢታየን የታመንነው አምላክ ነጋችንን ብሩህ ያደርገዋል ፡፡   ስሙ ሕልቃና የተባለ ኤፍሬማዊ ሰው ነበረ.. ሁለትም ሚስቶች ነበሩት፤ የአንዲቱ ስም ሐና የሁለተኛይቱም ስም ፍናና ነበረ፤ ለፍናናም ልጆች ነበሩአት፥ ለሐና ግን ልጅ አልነበራትም። ሐናንም ( ሕልቃና ) ይወድድ ነበር.. እግዚአብሔር ግን ማኅፀንዋን ዘግቶ ነበር.. ጣውንትዋ ታስቆጣት ታበሳጫትም ነበር.. ሐናም ታለቅስ ነበር፥ አንዳችም አትቀምስም ነበር። ሐና ተነሣች። ካህኑም ዔሊ በእግዚአብሔር መቅደስ መቃን አጠገብ በመንበሩ ላይ ተቀምጦ ነበር። እርስዋም በልብዋ ትመረር ነበር፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸለየች፥ ጽኑ ልቅሶም አለቀሰች። እርስዋም። አቤቱ፥ የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ የባሪያህን መዋረድ ተመልክተህ ብታስበኝ፥ እኔንም ባትረሳ፥ ለባሪያህም ወንድ ልጅ ብትሰጥ፥ ዕድሜውን ሁሉ ለእግዚአብሔር እሰጠዋለሁ፥ ምላጭም በራሱ ላይ አይደርስም ብላ ስእለት ተሳለች። .. ሴቲቱም መንገድዋን ሄደች በላችም፥ ፊትዋም ከእንግዲህ ወዲያ አዘንተኛ መስሎ አልታየም።  ..ወደ ቤታቸው መጡ። ሕልቃናም ሚስቱን ሐናን አወቃት፤ እግዚአብሔርም አሰባት፤  የመፅነስዋም ወራት ካለፈ በኋላ ሐና ወንድ ልጅ ወለደች፤ እርስዋም። ከእግዚአብሔር ለምኜዋለሁ ስትል ስሙን ሳሙኤል ብላ ጠራችው ( 1ሳሙ 1 ) ።    ብላቴናውም ሳሙኤል በዔሊ ፊት እግዚአብሔርን ያገለግል ነበር፤ በዚያም ዘመን የእግዚአብሔር ቃል ብርቅ ነበረ፤ ራእይም አይገለጥም ነበር። በዚያም ዘመን እንዲህ ሆነ፤ የዔሊ ዓይኖች ማየት እስኪሳናቸው ድረስ መፍዘዝ ጀምረው ነበር። ዔሊም በስፍራው ተኝቶ ሳለ፥ …ሳሙኤልም የእግዚአብሔር ታቦት ባለበት በእግዚአብሔር መቅደስ ተኝቶ ሳለ፥ እግዚአብሔር ሳሙኤልን ጠራው፤ እርሱም፡- እነሆኝ አለ። ወደ ዔሊም ሮጠ፡- እነሆኝ የጠራኸኝ አለው። እርሱም፡- አልጠራሁህም፤ ተመልሰህ ተኛ አለው። ሄዶም ተኛ። እግዚአብሔርም ደግሞ፡- ሳሙኤል ሆይ ብሎ ጠራው። ሳሙኤልም ተነሥቶ ወደ ዔሊ ሄደና። እነሆኝ የጠራኸኝ አለው። እርሱም፡- ልጄ ሆይ፥ አልጠራሁህም፤ ተመልሰህ ተኛ ብሎ መለሰ። ሳሙኤል ግን ገና እግዚአብሔርን አላወቀም ነበር፥ የእግዚአብሔርም ቃል ገና አልተገለጠለትም ነበር። እግዚአብሔርም ሳሙኤልን እንደ ገና ሦስተኛ ጊዜ ጠራው። እርሱም ተነሥቶ ወደ ዔሊ ሄደና እነሆኝ የጠራኸኝ አለ። ዔሊም እግዚአብሔር ብላቴናውን እንደ ጠራው አስተዋለ። ዔሊም ሳሙኤልን፡- ሄደህ ተኛ ቢጠራህም። አቤቱ፥ ባሪያህ ይሰማልና ተናገር በለው አለው። ሳሙኤልም ሄዶ በስፍራው ተኛ። እግዚአብሔርም መጥቶ ቆመ፥ እንደ ቀድሞውም፡- ሳሙኤል ሳሙኤል ብሎ ጠራው። ሳሙኤልም፡- ባሪያህ ይሰማልና ተናገር አለው። እግዚአብሔርም ሳሙኤልን አለው፡- እነሆ፥ የሰማውን ሁሉ ሁለቱ ጆሮቹ ጭው የሚያደርግ አንድ ነገርን በእስራኤል አደርጋለሁ።  በዚያም ቀን በቤቱ ላይ የተናገርሁትን ሁሉ በዔሊ አወርዳለሁ፤ … ልጆቹ የእርግማን ነገር እንዳደረጉ አውቆ አልከለከላቸውምና ስለ ኃጢአቱ በቤቱ ለዘላለም እንድፈርድ አስታውቄዋለሁ… ሳሙኤልም እስኪነጋ ተኛ፥ ማልዶም ተነሥቶ የእግዚአብሔርን ቤት ደጅ ከፈተ። ሳሙኤልም ራእዩን ለዔሊ መንገር ፈራ። ዔሊም ሳሙኤልን ጠርቶ፡- ልጄ ሳሙኤል ሆይ፥ አለ፤ እርሱም። እነሆኝ አለ።  እርሱም፡- እግዚአብሔር የነገረህ ነገር ምንድር ነው? ከእኔ አትሸሽግ፤ … ሳሙኤልም ነገሩን ሁሉ ነገረው፥ አንዳችም አልሸሸገውም። ዔሊም፡- እርሱ እግዚአብሔር ነው፤ ደስ ያሰኘውን ያድርግ አለ ( 1ሳሙ 3 ) ።   ማብራሪያ ሐና ልጅ የሌላት መካን በመሆኗ ትበሳጭ ነበር፡፡ ትመረርም ነበር፡፡ ምንም እንኳን ጣውንትዋ ( የባልዋ ሚስት ) ብታበሳጫትም የባሰ እንድትበሳጭና እንድትመረር የሚያደርጋት የነበረው ልጅ ስለ ሌላት ነበር፡፡ ወደ እግዚአብሔር ቤት ከባልዋ ጋር በወጣች ጊዜ ግን ለየት ያለ ጸሎት አደረገች፡፡ ከጸለየችም በኋላ ፊቷ የሀዘንተኛ ፊት መሆኑ ቀረ፡፡ የጸለየችው ጸሎት ደግሞ እግዚአብሔር ልጅ እንዲሰጣት ነበር፡፡ ያቺ ትመረርና ትበሳጭ የነበረች ሴት ሳሙኤልን ወለደች፡፡ ተጨማሪ ልጆችም ወልዳለች ( 1ሳሙ 2 ÷ 21  ) ፡፡ ሳሙኤል ደግሞ እግዚአብሔር የሚወደውና ምሥጢሩን ያካፈለው ብላቴና ነበር፡፡ በዘመኑም ታላቅ የእግዚአብሔር ሰው ነበር፡፡ ሐና የተወሰኑ ጊዜዎችዋን በመመረር ያጠፋች ሴት ናት፡፡ መጨረሻ ላይ ግን ጉዳይዋን ጸልያ በእግዚአብሔር ላይ ከጣለች በኋላ ማዘንና መመረሩን ትታለች፡፡ ሐና እንደ ሳሙኤል የመሰለ ልጅ እግዚአብሔር የሚሰጣት ሆኖ ሳለ ነው ሕይወትዋ የጨለመ መስሎ ታያት፡፡ ልጅ የማትወልድ መስሎ ይታያትም ነበር ፡፡ ከፊትዋ ግን ሳሙኤልን የመሰለ ልጅ በመውለድ ብሩህ ጊዜ እንደሚኖራት አልገመተችም፡፡ እንግዲህ ወንድሞቼና እህቶቼ በፊታችን መልካም ቀን የሌለን እየመሰለን አንበሳጭ ፤ ተስፋ አንቁረጥ፡፡ እግዚአብሔርን አምላኩ ያደረገ ሰው ሁሌም ብሩህ ጊዜያቶች ከፊቱ አሉ፡፡ የተከላችሁት ወይን ለጊዜው ዘለላ ፍሬ ኖሮት ባታዩበትና ባትቀጥፉት፣ ነገ ግን አፍርቶ ዘለላ ዘለላ የሆንውን ፍሬውን በእጃችሁ ይዛችሁና ከፍሬው እየበላችሁ መደሰታችሁ የማይቀር ነው፡፡ እንደዚሁም እግዚአብሔርን ተስፋ በምናደርግበት ነገር እግዚአብሔርም የልመናችንን መልስ ይሰጠናልና ዛሬ ኪሳችን ባዶ ቢሆን ፣ ራዕያችን ባይሳካ አንመረር ፤ አንዘን፡፡ ማስታወስ የምፈልገው ስለ ምንፈልገው ነገር እግዚአብሔርን መለመናችንን መዘንጋት የለብንም፡፡ ከለመንን በኋላ ማዘን የለብንም ፤ ተስፋ እንደሌለው ሰውም መሆን የለብንም፡፡ የለመንነውን ነገር የሚፈጽምልን አባት አለ፡፡ የለመንነው ነገር ደግሞ እንደ ፈቃዱ መሆን እንዳለበት መርሳት አይኖርብንም፡፡ እግዚአብሔርን የያዝን ሰዎች በለመንነው ነገር ነገ ከእግዚአብሔር የምንቀበል ሰዎች ነንና ነጋችን ( የነገው ሕይወታችን ) ብሩህ ነው፡፡ ጨለማ ነገ የለንም፡፡ ዛሬ የጨለመ መስሎን ቢታየን የነገው ቀን ግን በፍጹም የጨለመ አይደለም፡፡ ዛሬ የጨለመብን መስሎ ስለ ተሰማን በፊታችን ያሉት ጊዜያት በሙሉ ጨለማዎች እንደ ሆኑ እንዳናስብ፡፡ በአንደኛው ሳንቲም ገጽ ያለው ነገር ማንኛውም ነገር ( ስዕል በሉት ሌላም ነገር ) በሌላኛው ገጽ እርሱ ራሱው አይሆንም፡፡ ዛሬ የሕይወት ሳንቲም ገጽታችን ጨለማ መስሎ ከታየን ፣ የነገው የሕይወት ሳንቲም ገጽታችን ብሩህ መሆኑ የማይቀር ነው ፡፡ የምናምነው እግዚአብሔር ለሐና እንዳደረገላት ለኛም ያደርግልናል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
90
20
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
82