es
Feedback
እግዚአብሔርን ማወቅ

እግዚአብሔርን ማወቅ

Ir al canal en Telegram

ሰላምታ በተለዋወጥን ቁጥር ይመስገን ስለምንለው አምላካችንና አባታችን እግዚአብሔር ያለንን ዕውቀት ለማዳበር የሚያግዝ ቻነል ነው፡፡

Mostrar más
918
Suscriptores
+124 horas
+57 días
-130 días

Carga de datos en curso...

Atraer Suscriptores
junio '26
junio '26
+34
en 0 canales
mayo '26
+31
en 0 canales
Get PRO
abril '26
+45
en 0 canales
Get PRO
marzo '26
+33
en 0 canales
Get PRO
febrero '26
+49
en 0 canales
Get PRO
enero '26
+45
en 0 canales
Get PRO
diciembre '25
+54
en 0 canales
Get PRO
noviembre '25
+38
en 0 canales
Get PRO
octubre '25
+37
en 0 canales
Get PRO
septiembre '25
+31
en 0 canales
Get PRO
agosto '25
+32
en 0 canales
Get PRO
julio '25
+45
en 0 canales
Get PRO
junio '25
+49
en 0 canales
Get PRO
mayo '25
+24
en 0 canales
Get PRO
abril '25
+19
en 0 canales
Get PRO
marzo '25
+18
en 0 canales
Get PRO
febrero '25
+11
en 0 canales
Get PRO
enero '25
+9
en 0 canales
Get PRO
diciembre '24
+19
en 0 canales
Get PRO
noviembre '24
+25
en 0 canales
Get PRO
octubre '24
+27
en 0 canales
Get PRO
septiembre '24
+17
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+20
en 0 canales
Get PRO
julio '24
+35
en 0 canales
Get PRO
junio '24
+21
en 0 canales
Get PRO
mayo '24
+23
en 0 canales
Get PRO
abril '24
+12
en 0 canales
Get PRO
marzo '24
+31
en 0 canales
Get PRO
febrero '24
+11
en 0 canales
Get PRO
enero '24
+15
en 0 canales
Get PRO
diciembre '23
+15
en 0 canales
Get PRO
noviembre '23
+12
en 0 canales
Get PRO
octubre '23
+13
en 0 canales
Get PRO
septiembre '23
+479
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
25 junio0
24 junio+1
23 junio+2
22 junio+4
21 junio+2
20 junio+1
19 junio0
18 junio+1
17 junio+1
16 junio+1
15 junio0
14 junio0
13 junio+1
12 junio+2
11 junio0
10 junio+1
09 junio+1
08 junio+3
07 junio+2
06 junio+2
05 junio+1
04 junio+1
03 junio+1
02 junio+4
01 junio+2
Publicaciones del Canal
የሐዋርያት ሥራ ጥናት :: ክፍል 22 :: የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ታሪክ ::   የጌታም መልአክ ፊልጶስን፡- ተነሥተህ በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ ወደሚያወርደው ምድረ በዳ ወደ ሆነ መንገድ ሂድ አለው። ተነሥቶም ሄደ። እነሆም፥ ህንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት አዛዥና ጃንደረባ የነበረ በገንዘብዋም ሁሉ የሠለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር፤ ሲመለስም በሰረገላ ተቀምጦ የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ያነብ ነበር። መንፈስም ፊልጶስን፡- ወደዚህ ሰረገላ ቅረብና ተገናኝ አለው። ፊልጶስም ሮጦ የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ሲያነብ ሰማና፡- በውኑ የምታነበውን ታስተውለዋለህን? አለው። እርሱም፡- የሚመራኝ ሳይኖር ይህ እንዴት ይቻለኛል? አለው። ወጥቶም ከእርሱ ጋር ይቀመጥ ዘንድ ፊልጶስን ለመነው። ያነበውም የነበረ የመጽሐፉ ክፍል ይህ ነበረ፤ እንደ በግ ወደ መታረድ ተነዳ፥ የበግ ጠቦትም በሸላቹ ፊት ዝም እንደሚል፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም። በውርደቱ ፍርዱ ተወገደ፤ ሕይወቱ ከምድር ተወግዳለችና ትውልዱንስ ማን ይናገራል? ጃንደረባውም ለፊልጶስ መልሶ፡- እባክህ፥ ነቢዩ ይህን ስለ ማን ይናገራል? ስለ ራሱ ነውን ወይስ ስለ ሌላ? አለው። ፊልጶስም አፉን ከፈተ፥ ከዚህም መጽሐፍ ጀምሮ ስለ ኢየሱስ ወንጌልን ሰበከለት። በመንገድም ሲሄዱ ወደ ውኃ ደረሱ፤ ጃንደረባውም፡- እነሆ ውኃ፤ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ምንድር ነው? አለው። ፊልጶስም፡- በፍጹም ልብህ ብታምን፥ ተፈቅዶአል አለው። መልሶም፡- ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ አምናለሁ አለ። ሰረገላውም ይቆም ዘንድ አዘዘ፥ ፊልጶስና ጃንደረባው ሁለቱም ወደ ውኃ ወረዱ፥ አጠመቀውም። ከውኃውም ከወጡ በኋላ የጌታ መንፈስ ፊልጶስን ነጠቀው፤ ጃንደረባውም ሁለተኛ አላየውም፥ ደስ ብሎት መንገዱን ይሄድ ነበርና። ፊልጶስ ግን በአዛጦን ተገኘ፥ ወደ ቂሣርያም እስኪመጣ ድረስ እየዞረ በከተማዎች ሁሉ ወንጌልን ይሰብክ ነበር ( የሐዋ 8 ፥ 26 - 40 ) ።   ማብራሪያ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ እግዚአብሔርን የሚያምን በመሆኑ ካገሩ ድረስ ተነሥቶ የመጣው በኢየሩሳሌም ለእግዚአብሔር ለመስገድ ነው፡፡ ፊልጶስ የጌታ መልአክ ሂድ ወዳለው ወደ ምድረ በዳ ጃንደረባው ወደሚያልፍበት መንገድ አመራ፡፡ ጃንደረባው የልቡን መሻት ፈጽሞ ማለት ለእግዚአብሔር ሰግዶ በሰረገላው እየተመለሰ ነበር፡፡ ሰግዶም ብቻ አልተወም፤ የአምላኩን ቃል ከነቢዩ ኢሳይያስ መጽሐፍ ያነብ ነበር፡፡ የሚያነበው ክፍል ደግሞ ኢሳይያስ ከ700 ዓመት በፊት ክርስቶስ መከራ እንደሚቀበል የተነበየውን ነበር ፡፡ ጃንደረባው ግን ስለ ክርስቶስ መሆኑን አላወቀም፡፡ ጃንደረባው ወደ ፊልጶስ እየቀረበ ሲመጣ መንፈስ ፊልጶስን፡- ወደ ጃንደረባው እንዲቀርብ አዘዘው ፡፡ መንፈስ የተባለው ከሦስቱ አካል አንዱ የሆነውን መንፈስ ቅዱስን ሲሆን መንፈስ ቅዱስ አካል ስላለው ነው ፊልጶስን፡- ወደዚህ ሰረገላ ቅረብና ተገናኝ ያለው። ፊልጶስ  ሲቀርብ ጃንደረባው ከሚያነበው ክፍል፡- የበግ ጦቦት በሸላቹ ፊት ዝም እንደሚል እንዲሁ አፉን አልከፈተም የሚለውን ሲያነብ ስለሰማ ፡- የምታነበውን ታስተውለዋለህ? አለው፡፡ ፊልጶስን ወደ ሰረገላው እንዲወጣ ለመነውና ነቢዩ የሚያወራው ስለ ራሱ ወይስ ስለ ሌላ እንደሆነ እንዲያስረዳው ጠየቀው ፡፡ ፊልጶስ ካነበበው ተነሥቶ ስለ ኢየሱስ ወንጌል ሰበከለት፡፡ ክርስቶስን በማመኑም አጠመቀው፡፡ ጃንደረባውም ሰግዶ ሲመለስ ያላገኘውን ደስታ አሁን አግኝቶ ደስ እያለው ይሄድ ጀመር፡፡ ይህ ሰው እግዚአብሔርን ፈልጎ ካገሩ ድረስ ያን ሁሉ መንገድ ተጉዞ  የመጣው በሰረገላ ነበር፡፡ የሚስተምረው ሰው ለሌለው፤ ዝም ብሎ ለሚያነበው በምድረ በዳ አስተማሪ ላከለት ፡፡ ምድረ በዳ ምንም የማንጠብቅበት ቦታ ነው፡፡ ልፋቱ መና እንዳይቀር እግዚአብሔር በምሕረቱ ምድረ በዳ ላይ ጎበኘው፡፡ ምንም ነገር የለም ብለን ተስፋ በቆረጥነበት ምድረ በዳ ላይ እርሱ ይጎበኘናል፡፡ እግዚአብሔር ስለ አንድ ሰው የሚገደው አምላክ ነው፡፡ ስለ እኛም ስለ አንዳችን ይገደዋል፡፡ ጃንደረባው ክርስትና ተጀምሮ እርሱ ግን በቀድሞ የአይሁድ እምነት እግዚአብሔርን ፍለጋ  ሄደ ፡፡ ሲመለስ ግን እግዚአብሔር በሚበልጠው ወንጌል እንዲያምን አደረገው፡፡ አንዳንዴ እግዚአብሔር በሌለበት የእግዚአብሔር ፈቃድ ያለበት መስሎን  እንወጣለን፡፡ እንደዛም ሆኖ አይተወንም፤ ምሕረቱን አብዝቶ በራሱ መንገድ ይጎበኛናል፡፡ ኢትዮጵያና የክርስትና ሃይማኖት የተዋወቁት በዚህ ጃንደረባ በ34 ዓ.ም ነው፡፡ ለሀገሩ ሕዝብም አስተምሯል ተብሎ ይታመናል (የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ በብፁዕ በአቡነ ጎርጎርዮስ ገጽ 18)፡፡ እንግዲህ እስከዚህ የሐዋርያት ሥራ ም 8 ድረስ መመልከት የቻልነው ወንጌል ይኸውም የምሥራቹ ቃል እየተስፋፋ መምጣቱን ነው፡፡ ዛሬም ሊሰበክ የሚገባው ወንጌል እንደ ሆነ ያስተምረናል፡፡ የክርስቶስ ጉዳይ አስቀድሞ በነቢያትም ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ ነበር፡፡ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባውም በሚያነበው በነቢዩ ኢሳይያስ የትንቢት መጽሐፍ ሰፍሮ አግኝተነዋል፡፡ ነቢያት የተናገሩለትን ክርስቶስን ያመነው ጃንደረባው በልቡ ደስታ  ሞልቶታል፡፡ የሰበከው ፊልጶስም በሌሎች አገሮች ሁሉ ወንጌልን መስበኩን አልተወም፡፡ ለጃንደረባው ቃሉን የገለጠ መንፈስ ቅዱስ በዚህ ዘመን ላለነው ኢትዮጵያውያንም ቃሉን ይግለጥልን ፤ በልቦናችንም ያሳድርልን፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በጥቅምት 14  ቅዳሴ ሲቀደስ የሐዋ 8 ፥ 26 - 40 ያለው ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌ ) ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ይቀጥላል፡፡ ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie

2
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
5
3
እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝበት ጸሎት፡፡   እግዚአብሔርም ..ለሰሎሞን በሌሊት በሕልም ተገለጠለት፤ እግዚአብሔርም፡- ምን እንድሰጥህ ለምን አለ። ሰሎሞንም አለ። ..አቤቱ አምላኬ ሆይ፥ እኔን ባሪያህን በአባቴ በዳዊት ፋንታ አንግሠኸኛል፤ እኔም መውጫንና መግቢያን የማላውቅ ታናሽ ብላቴና ነኝ።  ባሪያህም ያለው አንተ በመረጥኸው ሕዝብህ ስለ ብዛቱም ይቈጠርና ይመጠን ዘንድ በማይቻል በታላቅ ሕዝብ መካከል ነው። ስለዚህም በሕዝብህ ላይ መፍረድ ይችል ዘንድ፥ መልካሙንና ክፉውንም ይለይ ዘንድ ለባሪያህ አስተዋይ ልቡና ስጠው፤ አለዚያማ በዚህ በታላቅ ሕዝብህ ላይ ይፈድ ዘንድ ማን ይችላል?  ሰሎሞንም ይህን ነገር ስለ ለመነ፥ ነገሩ እግዚአብሔርን ደስ አሰኘው። እግዚአብሔርም አለው። ፍርድን ትለይ ዘንድ ለራስህ ማስተዋልን ለመንህ እንጂ ለራስህ ብዙ ዘመናትን ባለጠግነትንም የጠላቶችህንም ነፍስ ሳትለምን ይህን ነገር ለምነሃልና እነሆ፥ እኔ እንደ ቃልህ አድርጌልሃለሁ፤ እነሆ፥  ማንም የሚመስልህ ከአንተ በፊት እንደሌለ ከአንተም በኋላ  እንዳይነሣ አድርጌ ጥበበኛና አስተዋይ ልቡና ሰጥቼሃለሁ።  .. ደግሞም ከነገሥታት የሚመስልህ ማንም እንዳይኖር ያልለመንኸውን ባለጠግነትና ክብር ሰጥቼሃለሁ።  ..ሰሎሞንም ነቃ፥ እነሆም፥ ሕልም ነበረ ( 1ነገ 3 ÷ 5 – 15 ) ፡፡   ማብራሪያ ሰሎሞን ንጉሥ በሆነ ጊዜ ገና ብላቴና ነበር፡፡ ራሱ ብላቴና መሆኑን ለእግዚአብሔር ሲናገር ሰምተነዋል፡፡ ለብላቴናው ለሰሎሞን እግዚአብሔር በሕልም ተገለጠለትና፡- እንድሰጥህ የምትፈልገውን ሁሉ ለምን አለው፡፡ ለምነኝ የተባለው ንጉሥ ሰሎሞን ሺህ ዓመት ልንገሥ አላለም፡፡ ሌላም ነገር እንዲሰጠው አልለመነም፡፡ የለመነው፡-  አስተዋይ ልቡና ስጠኝ ብሎ ነው፡፡ እግዚአብሔርም ሰሎሞን ለራሱ ብዙ ዘመንን ፣ ባለጠግነትን ፣ ጠላቶቹ እንዲጠፉለት ባለመለመኑና፡- አስተዋይ ልቡና ስጠኝ በማለቱ ከእርሱም በፊት ከእርሱም በኋላ እንደ እርሱ የሆነ ጥበበኛ እንዳይነሣ አድርጎ አስተዋይ ልቡና ሰጠው፡፡ ሰሎሞን ነቃ ሕልም ነበረ፡፡ ሕልም እንደ ነበረ ግን አልቀረም፡፡ ሰሎሞን ከነቃ ጀምሮ አጅግ አስተዋይ ሰው መሆን ጀመረ፡፡ ያልለመነውንም ባለጠግነትና ክብር ተሰጠው፡፡ የተሰጠው ባለጠግነትና ክብር ደግሞ ከነገሥታት እርሱን የሚመስል ማንም እንዳይኖር ተደርጎ ነበር፡፡ እግዚአብሔር ያልለመነውንም የሚሰጠን አምላክ ነው፡፡ ወደ እግዚአብሔር ትክክለኛ ጸሎት ስናደርግ ምንም ጥያቄ የሌለው ነገር ምን መሰላችሁ? ያልለመነውንም ነገር እንዲሰጠን ያስደርጋል፡፡ ሰሎሞን እግዚአብሔርን ስጠኝ ያለው አስተዋይ ልቡና በመሆኑ እግዚአብሔር ደስ ተሰኝቶበታል፡፡ ከእግዚአብሔር መለመን ያለብንን ስናውቅ እግዚአብሔርም ደስ ይሰኝብናል፡፡ እግዚአብሔር እንደ ፈቃዱ የሆነውን ነገር ስንለምንው ደስ ይሰኛል፡፡ በተለይ በተለይ ከእርሱ ጋር ስለመኖርና እስከ መጨረሻ በመጽናት መንግሥቱን ስለመውረስ መጸለይ እግዚአብሔርን የበለጠ ደስ ያሰኘዋል ፡፡ እንደ ሰሎሞን አስተዋይ ልቡና ስጠን ማለትንም ሳንዘነጋ ማለቴ ነው፡፡ አስተዋል ልቡና ያለው ሰው ከምንም በላይ ባለ ዘመኑ ሁሉ ከእግዚአብሔር ጋር መኖርን ይለምናል፡፡ ባለ ዘመናችን ከእግዚአብሔር ጋር ከሆንን ሁሉ ያለው እግዚአብሔር የእኛ ነው፡፡ እግዚአብሔር ካለን ሁሉ የኛ ነው፡፡ መለመን ያለብንን ስንለምን ያልለመነውም ጭምር ይሰጠናል፡፡ በተለያዩ ጉዳዮችም ስንጸልይ የሚጠቅመን ምን እንደ ሆነ አናውቅምና፡- አንተ እርዳን እንበለው፡፡ እርዳን ያልነው አምላክ ይረዳናል፡፡ የሚሻለንን እርሱ ያውቅልናል፡፡ በጸሎት መለመን ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውን ልንለመን ይገባል፡፡ ስለ ወደድነው የለመንነው ነገር እግዚአብሔርን ብቻ ሳይሆን ቢሰጠን እኛንም ደስ የማያሰኝ ሊሆን ይችላል፡፡ እግዚአብሔርን ፣ የሚሰጠን እኛንም ደስ የሚያሰኝ ልመና እናቅርብ ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
58
4
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
44
5
የሐዋርያት ሥራ ጥናት ፡፡ ክፍል 21 ፡፡ ሐዋርያት እጃቸውን ሲጭኑ የመንፈስ ቅዱስ መውረድ ፡፡   ከክፍል 20 ባጭሩ ፡፡ በዚያን ቀንም በኢየሩሳሌም ባለች ቤተ ክርስቲያን ላይ ታላቅ ስደት ሆነ፤ ሁሉም  ከሐዋርያትም በቀር ወደ ይሁዳና ወደ ሰማርያ አገሮች ተበተኑ። ..የተበተኑትም ቃሉን እየሰበኩ ዞሩ። ፊልጶስም ወደ ሰማርያ ከተማ ወርዶ ክርስቶስን ሰበከላቸው። ..ሲሞን የሚሉት አንድ ሰው ግን፡- .. እየጠነቈለ የሰማርያንም ወገን እያስገረመ ቀድሞ በከተማ ነበረ። ከታናናሾችም ጀምሮ እስከ ታላላቆቹ ድረስ ..በጥንቈላ ስላስገረማቸው ያደምጡት ነበር። ነገር ግን ስለ እግዚአብሔር መንግሥትና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም እየሰበከላቸው ፊልጶስን ባመኑት ጊዜ፥ ወንዶችም ሴቶችም ተጠመቁ። ሲሞንም ደግሞ ራሱ አመነ፤ ተጠምቆም ከፊልጶስ ጋር ይተባበር ነበር፤ የሚደረገውንም                                       ምልክትና ታላቅ ተአምራት ባየ ጊዜ ተገረመ  ( የሐዋ 8 ÷ 1 - 13 ) ። ------////-------   በኢየሩሳሌምም የነበሩት ሐዋርያት የሰማርያ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንደተቀበሉ ሰምተው ጴጥሮስንና ዮሐንስን ሰደዱላቸው። እነርሱም በወረዱ ጊዜ መንፈስ ቅዱስን ይቀበሉ ዘንድ ጸለዩላቸው፤ በጌታ በኢየሱስ ስም ብቻ ተጠምቀው ነበር እንጂ ከእነርሱ በአንዱ ላይ ስንኳ ገና አልወረደም ነበርና። በዚያን ጊዜ እጃቸውን ጫኑባቸው መንፈስ ቅዱስንም ተቀበሉ። ሲሞንም በሐዋርያት እጅ መጫን መንፈስ ቅዱስ እንዲሰጥ ባየ ጊዜ፥ ገንዘብ አመጣላቸውና:- እጄን የምጭንበት ሁሉ መንፈስ ቅዱስን ይቀበል ዘንድ ለእኔ ደግሞ ይህን ሥልጣን ስጡኝ አለ። ጴጥሮስ ግን እንዲህ አለው። የእግዚአብሔርን ስጦታ በገንዘብ እንድታገኝ አስበሃልና ብርህ ከአንተ ጋር ይጥፋ። ልብህ በእግዚአብሔር ፊት የቀና አይደለምና ከዚህ ነገር ዕድል ወይም ፈንታ የለህም። እንግዲህ ስለዚህ ክፋትህ ንስሐ ግባ፥ ምናልባትም የልብህን አሳብ ይቅር ይልህ እንደ ሆነ ወደ እግዚአብሔር ለምን፤ በመራራ መርዝና በዓመፅ እስራት እንዳለህ አይሃለሁና። ሲሞንም መልሶ፡- ካላችሁት አንዳች እንዳይደርስብኝ እናንተው ወደ ጌታ ለምኑልኝ አላቸው። እነርሱም ከመሰከሩና የጌታን ቃል ከተናገሩ በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፤ በሳምራውያን በብዙ መንደሮችም ወንጌልን ሰበኩ ( የሐዋ 8 ÷ 14 - 25 ) ።   ማብራሪያ ቅዱስ እስጢፋኖስ በመገደሉ በክርስቶስ ያመኑ ደቀ መዛሙርት ( ክርስቲያኖች ) ከተሰደዱበት አገር አንዱ ወደ ሰማርያ ነበር፡፡ በሰማርያ ፊልጶስ ክርስቶስን ስለ ሰበከ ብዙ ሰዎች አምነው ነበር፡፡ ካመኑት አንዱ ደግሞ ጥንቋዩ ሲሞን ነበር፡፡ ሐዋርያት የሰማርያ ሰዎች በክርስቶስ እንዳመኑ ሲሰሙ ጴጥሮስና ዮሐንስ ወደ ሰማርያ ወረዱና ጸለዩላቸው፡፡ ሲጸልዩላቸው መንፈስ ቅዱስ ወረደባቸው፡፡ የጸለዩላቸው እጃቸውን ጭነው ነበር፡፡ አስቀድመው ተጠምቀው ነበር፡፡ የተጠመቁት በጌታ በኢየሱስ ስም ነበር የተባለው በክርስቶስ ሲያምኑ የተጠመቁትን ጥምቀት ለማመልከት ነው፡፡ በአብ ፣ በወልድ ፣ በመንፈስ ቅዱስ ስም የምንጠመቀውን የሚያመለክት ነው፡፡ ሐዋርያት ሥራን የጻፈው ሉቃስ በጌታ በኢየሱስ ስም ተጠመቁ ሲል ጥምቀቱን ከዮሐንስ ጥምቀት ሊለየው የፈለገ ይመስላል፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ንስሐ ግቡ እያለ ያጠምቅ የነበረው ጥምቀት የንስሐ ጥምቀት ነበር፡፡ እንደ ሐዋርያት በእግዚአብሔር ከተሾመ በቀር እጅን በሰው ላይ ጭኖ መጸለይ ተገቢ አይደለም፡፡ የእግዚአብሔር አገልጋዮች እጃቸውን በሰው ላይ በተለያየ ምክንያት ጭነው ሊጸልዩ ይችላሉ፡፡ ሲሞን ልክ እንደ ሐዋርያት እርሱም እጁን ሲጭን መንፈስ ቅዱስ በሰዎች ላይ እንዲወርድ ፈልጎ ገንዘብ ለሐዋርያት ሰጥቶአቸው ሥልጣኑን እንዲሰጡት ጠየቃቸው፡፡ ዛሬ ዛሬ የእግዚአብሔርን ስጦታ በገንዘብ የሚቸረችሩ ብዙ አሉ፡፡ ሲሞን የእግዚአብሔርን ስጦታ በገንዘብ ሊያገኝ መፈለጉ ኃጢአት መሆኑን፣ ንስሐ እንዲገባና ወደ እግዚአብሔር እንዲለምን ሐዋርያት ነገሩት ፡፡ ያመነውን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ከልቡ ፡- ይቅር በለኝ ብሎ ቢለምን ይቅር መባሉ እውነት ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ስለ ሲሞን የሚነገረውን ለጊዜው አልጻፍኩትም፡፡ ሐዋርያት የሆኑት ጴጥሮስና ዮሐንስ ዋና ሥራቸው ወንጌልን መስበክ ነበርና፡- ወንጌል ሰበኩ የሚለን ለዚህ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ በእነርሱ ላይ በወረደ ጊዜ ምስክር እንዲሆኑ ከተነገራቸው አንድዋ ሰማርያ በመሆንዋ ወንጌልን በሰማርያ ሰብከዋል፡፡ ከበላይ ስለ መንፈስ ቅዱስ መውረድ አንስቼ ነበርና የኢትዮጵያ ኦ/ተ/ቤ/ክ አጥምቃ ሜሮን የምትቀባው ሐዋርያት እጃቸውን ጭነው ሲጸልዩ የወረደውን መንፈስ ቅዱስን እንዲቀበሉ ብላ ነው፡፡ እንግዲህ ዘወትር መንፈስ ቅዱስ በእኛ ላይ እንዲያድርብንና ሁሌም ከእኛ እንዳይለይ መጸለይ ተገቢና አስፈላጊ ነው፡፡ በሐዋርያት ሥራ መንፈስ ቅዱስ በግልጽ ሥራውን ሲሰራ እንመለከታለን፡፡  መንፈስ ቅዱስ ከኛ ሳይለየን ሲኖር በብርታት እንመላለሳለን፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወታችንንም ትልቅ ለውጥ ይኖራል፡፡ ይታያልም፡፡ ለቅዱሳን ሐዋርያት የሰጣቸውን መንፈስ ቅዱስ ሁሌም ሳይወሰድብን በእኛም ያሳድርብን፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በመጋቢት 2ና ግንቦት 16 ቅዳሴ ሲቀደስ የሐዋ 8 ÷ 14 – 26 ያለው ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌ) ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ይቀጥላል፡፡ ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
52
6
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
48
7
እግዚአብሔር የሕዝቡን ጭንቀትና መከራ የሚመለከት አምላክ ነው፡፡   በግብፅም ዮሴፍን ያላወቀ አዲስ ንጉሥ ተነሣ።  እርሱም ሕዝቡን፡- እነሆ፥ የእስራኤል ልጆች ሕዝብ ከእኛ ይልቅ በዝተዋል በርትተውማል፤ እንዳይበዙ፥ ሰልፍም በተነሳብን ጊዜ ጠላቶቻችንን አግዘው እንዳይወጉን ከምድሪቱም እንዳይወጡ፥ ኑ እንጠበብባቸው አለ።  በብርቱ ሥራም ያስጨንቁአቸው ዘንድ ግብር አስገባሪዎችን ሾመባቸው፤ ..ነገር ግን እንዳስጨነቁአቸው መጠን እንዲሁ በዙ፥ እጅግም ጸኑ፤ ከእስራኤልም ልጆች የተነሣ ተጸይፈዋቸው ነበር። ግብፃውያንም የእስራኤልን ልጆች በመከራ ገዙአቸው። በጽኑ ሥራ፥ በጭቃ፥ በጡብም በእርሻም ሥራ ሁሉ፥ በመከራም በሚያሠሩአቸው ሥራ ሁሉ፥ ሕይወታቸውን ያስመርሩአቸው ነበር ( ዘጸ 1 ÷ 8 – 14 ) ። ..የእስራኤልም ልጆች ከባርነት የተነሣ አለቀሱ፥ ጮኹም፥ ስለ ባርነታቸውም ጩኸታቸው ወደ እግዚአብሔር ወጣ።  እግዚአብሔርም የለቅሶአቸውን ድምፅ ሰማ፥ እግዚአብሔርም ከአብርሃምና ከይስሐቅ ከያዕቆብም ጋር ያደረገውን  ቃል ኪዳን አሰበ።   እግዚአብሔርም የእስራኤልን ልጆች አየ.. ( ዘጸ 2 ÷ 23 -25 ) ። ሙሴም ..የአማቱን ..በጎች ይጠብቅ ነበር፤ ..ወደ እግዚአብሔርም ተራራ ወደ ኮሬብ መጣ። የእግዚአብሔርም መልአክ በእሳት ነበልባል በእሾህ ቍጥቋጦ መካከል ታየው፤ እነሆም ቍጥቋጦው በእሳት ሲነድድ ቍጥቋጦውም  ሳይቃጠል አየ።  ሙሴም፡-  ልሂድና ቍጥቋጦው ስለ ምን አልተቃጠለም ይህን ታላቅ ራእይ ልይ አለ። እግዚአብሔር እርሱ ይመለከት ዘንድ እንደ መጣ ባየ ጊዜ እግዚአብሔር ከቍጥቋጦው ውስጥ እርሱን ጠርቶ። ሙሴ፥ ሙሴ ሆይ አለ።  እርሱም- እነሆኝ አለ። ወደዚህ አትቅረብ፤ አንተ የቆምህባት ስፍራ የተቀደሰች መሬት ናትና ጫማህን ከእግርህ አውጣ አለው። ደግሞም፡- እኔ የአባትህ አምላክ፥ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ አለው..  እግዚአብሔርም አለ። በግብፅ ያለውን የሕዝቤን መከራ በእውነት አየሁ፥ ከአስገባሪዎቻቸውም የተነሣ ጩኸታቸውን ሰማሁ፤ ሥቃያቸውንም አውቄአለሁ፤ ከግብፃውያንም እጅ አድናቸው ዘንድ፥ ከዚያችም አገር ወተትና ማር ወደምታፈስሰው አገር ወደ ሰፊይቱና ወደ መልካሚቱ አገር ..አወጣቸው ዘንድ ወረድሁ።  አሁንም እነሆ የእስራኤል ልጆች ጩኸት ወደ እኔ ወጣ፤ ግብፃውያንም የሚያደርጉባቸውን ግፍ ደግሞ አየሁ። አሁንም ና፥ ሕዝቤን የእስራኤልን ልጆች ከግብፅ ታወጣ ዘንድ ወደ ፈርዖን እልክሃለሁ ( ዘጸ 3 ÷ 1 – 10 ) ) ። እግዚአብሔር የእስራኤልን ልጆች ከሠራዊታቸው ጋር ከግብፅ ምድር አወጣ ( ዘጸ 12 ÷ 51 ) ።   ማብራሪያ የእስራሌል ልጆች በረሀብ ምክንያት ዮሴፍ ገዢ ሆኖ ወደ ተሾመበት ወደ ግብፅ ከ400 ዓመት ገደማ በፊት ወርደው ነበር፡፡ ዮሴፍ ሲሞት የነገሠው ንጉሥ እስራኤላውያንን እንደ ባሪያ አድርጎ በመግዛት ማስጨነቅ ጀመረ፡፡ ከባድ የጉልበት ሥራም ያሠሩአቸው ስለ ነበር ሕይወታቸውን ያስመርሩአቸው ነበር፡፡ የእስራኤል ልጆች ባርነቱ ሲከብዳቸው ማልቀስ ጀመሩ፡፡ ማልቀስ ምን ያደርጋል አይታገሉም ነበር ? የሚል ሰው ሊኖር ይችላል፡፡ ማልቀሳቸው ጥምቅ ነበረው፡፡ ሲያለቅሱ፣ ሲጮኹ እኮ ነው ጩኸታቸውን እግዚአብሔር የሰማው፡፡ እግዚአብሔር የልቅሶአቸውን ድምፅ ሰማ፡፡ ለአባቶቻቸው ለነ አብርሃም የገባውን ኪዳን አሰበ፡፡ የእስራኤላውያንን ልጆች ተመለከተ፡፡ ሙሴ የአማቱን በጎች እየጠበቀ የእግዚአብሔር መልአክ በቁጥቋጦው መሐል ታየው፡፡ ቁጥቋጦው በእሳት ሲነድድና ቁጥቋጦው ግን ሳይቀጥል ማየቱ ገረመው፡፡ ቁጥቋጦው ለምን አልተቃጠለም? በማለት ጠጋ ብሎ ለማየት ሲቀርብ እግዚአብሔር በስሙ ጠርቶ ፡- ሙሴ ሙሴ አለው፡፡ እነሆኝ አለ፡፡ እግዚአብሔር ለሙሴ የእስራኤላውያንን ጩኸት ፣ መከራ፣ ሥቃያቸውን ፣ የሚፈጸምባቸውን ግፍ እንዳየና ሊያድናቸውም እንደ ወደደ ሙሴንም ከግብፅ እንዲያወጣቸው እንደሚሾመው ነገረው፡፡ ሙሴም እልህ አስጨራሽ ትግል ከግብፅ ንጉሥ ፈርዖን ካደረገ በኋላ እግዚአብሔር የእስራኤልን ልጆች ከግብፅ ምድር አወጣ ፡፡ ሥቃያችን ፣ የሚፈጸምብን ግፍ ሲበዛብን የማያይ ለሚመስለን እግዚአብሔር ያያል፡፡ በቃም ይላል፡፡ እኛ እንደ እስራኤል ልጆች ወደ እርሱ ጩኸታችንን ስናሰማ እግዚአብሔር ጩኸታችንን ይሰማል፡፡ ሥቃያችንንም ይመለከታል፡፡ ከሥቃያችንንና ከመከራችንም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ይገላግለናል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
100
8
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
57
9
የሐዋርያት ሥራ ጥናት ፡፡ ክፍል 20 ፡፡ በቤተ ክርስቲያን ላይ የመጣ ስደት ፡፡   በዚያን ቀንም በኢየሩሳሌም ባለች ቤተ ክርስቲያን ላይ ታላቅ ስደት ሆነ፤ ሁሉም  ከሐዋርያትም በቀር ወደ ይሁዳና ወደ ሰማርያ አገሮች ተበተኑ። በጸሎትም የተጉ  ሰዎች እስጢፋኖስን ቀበሩት ታላቅ ልቅሶም አለቀሱለት። ሳውል ግን ቤተ ክርስቲያንን ያፈርስ ነበር፤ ወደ ሁሉም ቤት እየገባ ወንዶችንም ሴቶችንም እየጐተተ ወደ ወኅኒ አሳልፎ ይሰጥ ነበር። የተበተኑትም ቃሉን እየሰበኩ ዞሩ። ፊልጶስም ወደ ሰማርያ ከተማ ወርዶ ክርስቶስን ሰበከላቸው። ሕዝቡም የፊልጶስን ቃል በሰሙ ጊዜ ያደርጋት የነበረውንም ምልክት ባዩ ጊዜ፥ የተናገረውን በአንድ ልብ አደመጡ። ርኵሳን መናፍስት በታላቅ ድምፅ እየጮኹ ከብዙ ሰዎች ይወጡ ነበርና፤ ብዙም ሽባዎችና አንካሶች ተፈወሱ፤ በዚያችም ከተማ ታላቅ ደስታ ሆነ። ሲሞን የሚሉት አንድ ሰው ግን፡- እኔ ታላቅ ነኝ ብሎ፥ እየጠነቈለ የሰማርያንም ወገን እያስገረመ ቀድሞ በከተማ ነበረ። ከታናናሾችም ጀምሮ እስከ ታላላቆቹ ድረስ ታላቁ የእግዚአብሔር ኃይል ይህ ነው እያሉ ሁሉ ያደምጡት ነበር። ከብዙ ዘመንም ጀምሮ በጥንቈላ ስላስገረማቸው ያደምጡት ነበር። ነገር ግን ስለ እግዚአብሔር መንግሥትና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም እየሰበከላቸው ፊልጶስን ባመኑት ጊዜ፥ ወንዶችም ሴቶችም ተጠመቁ። ሲሞንም ደግሞ ራሱ አመነ፤ ተጠምቆም ከፊልጶስ ጋር ይተባበር ነበር፤ የሚደረገውንም                                                 ምልክትና ታላቅ ተአምራት ባየ ጊዜ ተገረመ  ( የሐዋ 8 ÷ 1 - 13 ) ።   ማብራሪያ ቅዱስ እስጢፋኖስ በመገደሉ ከሐዋርያት በቀር ክርስቲያኖች ወደ ተለያዩ አገሮች  ተሰደዱ፡፡ እስጢፋኖስም ተቀበረ፡፡ አለቀሱለትም፡፡ ሳውል ( ጳውሎስ ) ወደ ክርስትና ገና ስላልተመለሰ ቤተ ክርስቲያንን ያፈርስ ነበር፡፡ ያፈርስ ነበር የሚለው ቃል ቤተ ክርስቲያን ማለት በክርስቶስ ያመኑ የክርስቲያኖች ስብስብ ( ኅብረት ) ስለሆነ ያፈርስ ነበር ሲል በክርስቶስ ያመኑትን ከርስቲያኖች ለማጥፋት መፈለጉን ያሳያል፡፡  ክርስቲያን የሚለው ስም የመጣው ወደ በኋላ ላይ ነበር፡፡ እስጢፋኖስ ሲገደል ተባባሪ የነበረው ጳውሎስ በክርስቶስ ያመኑትን ሰዎች ወደ እስር ቤት እንዲገቡ ያስደርግ ነበር፡፡ ክርስቶስን ያመኑት በስደት ምክንያት ቢበተኑም መከራውን ሳይፈሩ በደረሱበት ቦታ ስለ ክርስቶስ መሞትና መነሣት በስሙም የሚገኘውን ድኅነት ይናገሩ ነበር፡፡ ከሰባቱ ዲያቆናት አንዱ የነበረው ፊልጶስ ወደ ሰማርያ በመሄድ ለሰማርያ ሰዎች ክርስቶሰን ሰበከላቸው፡፡ መንፈስ ቅዱስ ይሠራ ነበርና በፊልጶስም ተአምራት ይፈጸሙ ነበር ፣ ርኵሳን መናፍስት ያለባቸው ሰዎች ነጻ ይወጡ ፣ ብዙ ሽባዎችና አንካሶችም ይፈወሱ ነበር፡፡ በሰማርያ ከተማ ታላቅ ደስታ ሆነ፡፡ በሰማርያ ሲሞን የሚሉት ጥንቋይ ነበር፡፡ ታላቁ የእግዚአብሔር ኃይል እስኪሉት ድረስ በጥንቈላው የሰማርያን ሰዎች ያስገርም ነበር፡፡ ፊልጶስ ክርስቶስን ሰብኮ የሰማርያ ሰዎች አምነው ሲጠመቁ አይቶ ጠንቋዩም ሲሞን አመነ፡፡ ጠንቋዩ ሲሞን ከሚሠራው በላይ ፊልጶስ የሚያደርገውን ምልክትና ተአምራት ባየ ጊዜ ተገረመ፡፡ በእስጢፋኖስ ሞት ምክንያት ከርስቲያኖች ወደ ተለያየ አገሮች መበታተናቸው ወንጌልን በተለያዩ አገሮች እንዲሰብኩ እንዳደረጋቸው ሁሉ በሕይወታችን የሚመጡብን ተግዳሮቶች ደስ ባያሰኙንም በጎ ነገር ይዘው ግን ይመጣሉ፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በሚያዝያ 25 ቅዳሴ ሲቀደስ የሐዋ 8 ÷ 1 – 13 ያለው ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌ) ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ይቀጥላል፡፡ ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
71
10
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
67
11
ለኛ የከበደን ነገር ሁሉ በእግዚአብሔር ዓይን ቀላል ነው፡፡   የሞዓብም ንጉሥ ..ለእስራኤልም ንጉሥ የመቶ ሺህ ጠቦትና የመቶ ሺህ አውራ በጎች ጠጕር ይገብርለት ነበር። አክዓብም ከሞተ በኋላ የሞዓብ ንጉሥ በእስራኤል ንጉሥ ላይ ዐመፀ። ..ንጉሡ ኢዮራም (የእስራኤል ንጉሥ) ..እስራኤልን ሁሉ አሰለፈ። ወደ ይሁዳም ንጉሥ ወደ ኢዮሣፍጥ፡- የሞዓብ ንጉሥ ዐምፆብኛልና ከእኔ ጋር በሞዓብ ላይ ለሰልፍ ትሄዳለህን? ብሎ ላከ። እርሱም፡- እወጣለሁ … አለ፡፡ የእስራኤል ንጉሥና የይሁዳ ንጉሥ የኤዶምያስም ንጉሥ ሄዱ፤ የሰባትም ቀን መንገድ ዞሩ፤ ለሠራዊቱና ለተከተሉአቸውም እንስሶች ውኃ አልተገኘም። የእስራኤልም ንጉሥ፡- ወዮ! እግዚአብሔር በሞዓብ እጅ አሳልፎ ይሰጣቸው ዘንድ እነዚህን ሦስቱን ነገሥታት ጠርቶአልና ወዮ አለ። ኢዮሣፍጥም፡- ..እግዚአብሔርን የምንጠይቅበት የእግዚአብሔር ነቢይ በዚህ አይገኝምን? አለ። ከእስራኤልም ንጉሥ ባሪያዎች አንዱ፡- … ኤልሳዕ እዚህ አለ ብሎ መለሰ። ..የእስራኤል ንጉሥና ኢዮሣፍጥ የኤዶምያስም ንጉሥ ወደ እርሱ ወረዱ።  ኤልሳዕም የእስራኤልን ንጉሥ፡- እኔ ከአንተ ጋር ምን አለኝ? ወደ አባትህና ወደ እናትህ ነቢያት ሂድ አለው። የእስራኤልም ንጉሥ፡- አይደለም፥ በሞዓብ እጅ ይጥላቸው ዘንድ እግዚአብሔር እነዚህን ሦስት ነገሥታት ጠርቶአል አለው። ኤልሳዕም፡- ..ሕያው እግዚአብሔርን! የይሁዳን ንጉሥ ኢዮሣፍጥን ያላፈርሁ ብሆን ኖሮ አንተን ባልተመለከትሁና ባላየሁ ነበር። ..እንዲህም አለ፡- እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡- በዚህ ሸለቆ ሁሉ ጕድጓድ ቆፍሩ። … ነፋስ አታዩም፥ ዝናብም አታዩም፥ ይህ ሸለቆ ግን ውኃ ይሞላል፤ እናንተም ..እንስሶቻችሁም ትጠጣላችሁ። ይህም በእግዚአብሔር ዓይን ቀላል ነገር ነው፤ ደግሞም ሞዓባውያንን በእጃችሁ አሳልፎ ይሰጣል.. በነጋውም ..ውኃ በኤዶምያስ መንገድ መጣ፥ ምድሪቱም ውኃ ሞላች። ሞዓባውያንም ሁሉ ነገሥታት ሊወጉአቸው እንደ መጡ በሰሙ ጊዜ ..ተሰበሰቡ፤ ..ማልደውም ተነሡ፤ ፀሐይም በውኃው ላይ አንጸባረቀ፥ ሞዓባውያንም በፊታቸው ውኃው እንደ ደም ቀልቶ አዩና፡- ይህ ደም ነው፤ ..ነገሥታት እርስ በርሳቸው ተዋጉ፥ እርስ በርሳቸውም ተጋደሉ፤ ሞዓብ ሆይ፥ እንግዲህ ወደ ምርኮህ ሂድ አሉ።  ወደ እስራኤል ሰፈር በመጡ ጊዜ እስራኤላውያን ተነሥተው ሞዓባውያንን መቱ ..ከፊታቸው ሸሹ ( 2 ነገ 3 ÷ 4 - 24 ) ፡፡   ማብራሪያ አክአብ በተባለ የእስራኤል ንጉሥ ጊዜ የሞዓብ ንጉሥ ይገብር ነበር ፡፡  የአክአብ ልጅ ኢዮራም ሲነግሥ ግን በቁጥር የተጠቀሱትን የበጎች ጠጕር አልገብርም በማለት ዐመፀ ፡፡ ኢዮራም የሞዓብን ንጉሥ ብቻውን ለመግጠም የፈራ ይመስላል ፡፡ የይሁዳን ንጉሥና የኤዶምያስን ንጉሥ እንዲያግዙት ርዳታቸውን ጠየቀ  ፡፡ ዛሬም ባለው ፖለቲካ የምናየው እንደዚሁ ነው ፡፡ አንድ አገር ጦርነት ሲገጥም ወዳጅ አገራት አብረው አልፎም ተርፎ ወታደሮቻቸውን እስከ መላክ የሚደርሱበት ጊዜ አለ ፡፡ የእስራኤሉ ንጉሥ ኢዮራም ርዳታቸውን ስለ ጠየቃቸው የይሁዳና የኤዶምያስ ንጉሥ ሠራዊታቸውን አስከትተው አሰላላፋቸውን ከኢዮራም ጋር በማድረግ ለሰልፍ ተነሡ ፡፡  ንጉሡ ኢዮራም ነገሥታቱ አብረውት በመዝመታቸው በደስታ እንደሚፈነጥዝ ቢታወቅም ጥምሩ ጦር ላይ ግን አደጋ ተደቀነ ፡፡ የውኃ እጦት ችግር በመከሰቱ ነበር ፡፡ ከባዕድ አምልኮ ነጻ ያልሆነው ጦርነቱን በሞዓብ ንጉሥ ላይ የሰበቀው ኢዮራም ፡- ወዮ አለ ፡፡ እርሱን ሊበቀለው በእርሱም ጦስ ነገሥታቱን እግዚአብሔር አክለብልቦ አምጥቶ በሞዓብ ንጉሥ አሳልፎ ሊሰጣቸው የጠራቸው መሰለው ፡፡ የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ፡- የእግዚአብሔር ነቢይ እንፈልግ ባለው መሠረት ኤልሳዕ የተባለውን ነቢይ አገኙ፡፡ ኤልሳዕ እግዚአብሔርን ትቶ በባዕድ አምልኮ የተዘፈቀውን ኢዮራምን ሲያይ ፡- የእናቱንና የአባቱን የሀሰት ነቢያትን እንዲጠየቅ ነገረው ፡፡ ኢዮራም ግን፡- በሞዓብ እጅ እንወድቅ ይሆንን? በማለት ነቢዩ ኤልሳዕን መወትወት ቀጠለ ፡፡ ስለ ወተወተው ሳይሆን የይሁዳን ንጉሥ ኢዮሣፍጥን በማክበር እንደ እርሱ ሥራ ግን ሊተባበረው አልፈለገም ነበር ፡፡ በባዐድ አምልኮ ለተዘፈቀውና ደንግጦ ለነበረው ኢዮራም እግዚአብሔር በጠላቶቹ እጅ አሳልፎ እንደማይሰጠው የምሥራች ተነገረው ፡፡ ኢዮራም ጣዖት አምላኪ ቢሆንም እግዚአብሔር ግን አላሳፈረውም፡፡ አንተ አምላካችን ነህ ብለን የሙጥኝ ያልነውን እኛንማ እንዴት አይረዳ ? ኢዮራምና ነገሥታቱ ጕድጓድ ቆፍሩ እንደ ተባሉት ቆፈሩ እንጂ ደመና በሰማይ ሳናይ አንቆፍርም በማለት አልተጠራጠሩም፡፡ ጕድጓዱ በውኃ ተሞላ ፡፡ ከሰማይ በዘነበ ዝናብ ሳይሆን ከምድር በተገኘ ፡፡ ይህ ውኃ ነው እንግዲህ ፀሐይ አንጸባርቆበት ሲያዩ ደም መስሎ ታያቸውና ፡- ሦስቱ ነገሥታት እርስ ተጨራርሰዋል በማለት ሞዓባውያኑ ሞርኮ ለማጋበስ ሰከም ሰከም እያሉ ሲሄዱ የጥምር ጦሩ ሰለባ መሆን ጀመሩ ፡፡ ሦስቱ ነገሥታት ምንም ባለፉበት ጦርነት ነገር ግን በእግዚአብሔር ጥበብ አሸናፊ ሆነው ተገኙ ፡፡ በእግዚአብሔር ዓይን ቀላል ነው እንደ ተባሉት ሁሉም ነገር ቀላል ሆኖ ተገኘ ፡፡ ለኛ የከበደን ነገር ሁሉ በእግዚአብሔር ዓይን ቀላል ነው፡፡ እንዴት ቀላል እንደ ሆነ ደግሞ በምሳሌ ላሳያችሁ ፡፡ ተጥዶ ያለ ወተት ሲፈላ ገንፍሎ ሊፈስ መስሎአችሁ ሮጣችሁ ሄዳችሁ፡- እፍ ስትሉት  መፍሰሱን ያቆማል ፡፡ እንደዛ ያሳቀቃችሁ ፡- ከእፍታ ያላለፈ ነገር ነበር፡፡ በሕይወታችን ከባድ ነው የምንለው ነገር ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ ከእፍታ እንዳላለፈው ወተት እጅግ በጣም ቀላል ነው ፡፡ በእግዚአብሔር ዓይን ሁሉም ነገር ቀላል ነው ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
110
12
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
74
13
የሐዋርያት ሥራ ጥናት ክፍል 19 የሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ መገደል ፡፡ ከክፍል 17ና 18 ባጭሩ ..ጌታም፡- ..ወደ ግብፅ እልክሃለሁ አለው። ..ሙሴን እግዚአብሔር ..ላከው። ይህ ሰው ( ሙሴ ) በግብፅ ምድርና በኤርትራ ባሕር በምድረ በዳም አርባ ዓመት ድንቅና ምልክት እያደረገ አወጣቸው ( የሐዋ 7 ÷ 23 – 36 ) ። ..እንዳየው ምስል አድርጎ ይሠራት ዘንድ ሙሴን ተናግሮ እንዳዘዘው፥ የምስክር ድንኳን ከአባቶቻችን ዘንድ በምድረ በዳ ነበረች፤ አባቶቻችንም ደግሞ በተራ ተቀብለው እግዚአብሔር በፊታቸው ያወጣቸውን የአሕዛብን አገር በያዙት ጊዜ ከኢያሱ ጋር አገቡአት፥ እስከ ዳዊት ዘመንም ድረስ ኖረች። እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ አግኝቶ ለያዕቆብ አምላክ ማደሪያን ያገኝ ዘንድ ለመነ። ነገር ግን ሰሎሞን ቤት ሠራለት። ነገር ግን ነቢዩ፡- ሰማይ ዙፋኔ ነው ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት፤ ለእኔ ምን ዓይነት ቤት ትሠራላችሁ? ይላል ጌታ፥ ወይስ የማርፍበት ስፍራ ምንድር ነው? ይህንስ ሁሉ እጄ የሠራችው አይደለምን? እንዳለ፥ ልዑል የሰው እጅ በሠራችው አይኖርም ( የሐዋ 7 ÷ 37 – 50 ) ። -----////////----------- እናንተ አንገተ ደንዳኖች ልባችሁና ጆሮአችሁም ያልተገረዘ፥ እናንተ ሁልጊዜ መንፈስ ቅዱስን ትቃወማላችሁ፤ አባቶቻችሁ እንደ ተቃወሙት እናንተ ደግሞ። ከነቢያትስ አባቶቻችሁ ያላሳደዱት ማን ነው? የጻድቁንም መምጣት አስቀድሞ የተናገሩትን ገደሉአቸው፤ በመላእክት ሥርዓት ሕግን ተቀብላችሁ ያልጠበቃችሁት እናንተም አሁን እርሱን አሳልፋችሁ ሰጣችሁት ገደላችሁትም። ይህንም በሰሙ ጊዜ በልባቸው በጣም ተቈጡ ጥርሳቸውንም አፋጩበት። መንፈስ ቅዱስንም ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት የእግዚአብሔርን ክብር ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና፡-  እነሆ፥ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ አለ። በታላቅ ድምፅም እየጮኹ ጆሮአቸውን ደፈኑ፥ በአንድ ልብ ሆነውም ወደ እርሱ ሮጡ፥ከከተማም ወደ ውጭ አውጥተው ወገሩት። ምስክሮችም ልብሳቸውን ሳውል በሚሉት በአንድ ጎበዝ እግር አጠገብ አኖሩ። እስጢፋኖስም፡- ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ነፍሴን ተቀበል ብሎ ሲጠራ ይወግሩት ነበር። ተንበርክኮም፡- ጌታ ሆይ፥ ይህን ኃጢአት አትቍጠርባቸው ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህንም ብሎ አንቀላፋ። ሳውልም በእርሱ መገደል ተስማምቶ ነበር ( የሐዋ 7 ÷ 51 - 60 ) ። ማብራሪያ ሙሴ እስራኤልን ከግብፅ ያወጣ ሰው ሲሆን ቤተ መቅደስም ሥራልኝ እግዚአብሔር ብሎት ከድንኳን ሰርቶአል፡፡ ቤተ መቅደስዋ  የምስክር ድንኳን ( ደብተራ ኦሪት ) ትባላለች፡፡ ሙሴ ሲሞት ኢያሱ እስራኤላውያንን ወደ ምድረ ርስት አስገባቸው፡፡ እስከ ሰሎሞን ድረስ በድንኳን የነበረው ቤተ መቅደስ በሰሎሞን የተሻለ ተደርጎ ተሠራ፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ፡- ልዑል የሰው እጅ በሠራችው አይኖርም ብሎ ትንቢት ተናግሮ ነበርና ክርስቶስ ለኛ በመሞቱ እኛን ቤተ መቅደስ አድርጎ አከበረን፡፡ ባለ መቅደሶቹ አይሁድ ክርስቶስን አለማመናቸው ሳያንስ እንዲያውም ሰቅለው ገደሉት፡፡ አንገተ ደንዳኖች መሆናቸውን ያየው ቅዱስ እስጢፋኖስ ገሰጻቸው፤ መንፈስ ቅዱስንም እንደሚቃወሙ ነገራቸው፡፡ የክርስቶስን መምጣት የተነበዩትን ነቢያት አባቶቻችሁ እንደ ገደሉ ሁሉ ልጆቻቸው እናንተ ደግሞ ክርስቶስን ገደላችሁት በማለት ተናገራቸው፡፡ ያላቸውን የሰሙ አይሁድ ተቆጡ፤ ጥርሳቸውንም አፋጩ፡፡ እስጢፋኖስ ግን መንፈስ ቅዱስን ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት ኢየሱስ ክርስቶስን በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየ፡፡ ከአብ ጋር በተካከለ ክብር ኢየሱስን ያየው ቅዱስ እስጢፋኖስ ፡- በተከፈቱ ሰማያት የሰው ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስን በእግዚአብሔር አብ ቀኝ ቆሞ እያየሁት ነው ሲላቸው በታላቅ ድምፅ በመጮኽ ያልተገረዘውን ጆሮአቸውን ደፈኑ፡፡ ሊወግሩት በአንድ ልብ ሆኑና ከከተማው ውጭ አውጥተው ወገሩት፡፡ ሳውል የተባለው ጳውሎስ በእስጢፋኖስ መገደል ተስማምቶ የገዳዮችን ልብስ ይጠብቅ ነበር፡፡ እስጢፋኖስ እየወገሩት፡-  ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ ነፍሴን ተቀበል አለ፡፡ ኃጢአታቸውንም አትቍጠርባቸው በማለትም ጸለየ፡፡ ይህንም ብሎ አረፈ፡፡ ሁሌም ከቅዱሳን የምንማረው ነገር አለ፡፡ በእውነት ለሚወግሩት ማነው ፡- ኃጢአታቸውን አትቍጠርባቸው የሚል? እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ በአንዴ እንዲህ መሆን አይቻልም፡፡ ቢሆንም ክርስቶስን በሕይወቱ እንዳሳየው እስጢፋኖስ እኛም በሂደት ሕይወቱን ልንመስል ይገባል፡፡ የእስጢፋኖስን ሕይወት ባለመምሰላችን ተስፋ መቁረጥ የለብንም፡፡ ጴጥሮስ ጌታችን ኢየሱስን ሊይዙት ከመጡት አንዱን በያዘው ሰይፍ ጆሮውን እንደ ቆረጠው ልብ እንበል፡፡ እንደ እስጢፋኖስ ይቅር በላቸው ማለት አልቻለም፡፡ በወጣኒነት ብዙ ጉድለቶች በሕይወታችን ይታያሉ፡፡  ሰማዕታት ነፍሳቸውን ከሰጡ እኛ ትንሽዋን ነገር ለእግዚአብሔር መተውን ግን መለማመድ ያስፈልጋል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ይቀጥላል፡፡ ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
81
14
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
67
15
የመጨረሻው የእግዚአብሔር የጦር መሣሪያ የተባለው የመንፈስ ሰይፍ ነው፡፡ ሰይፍ የማጥቂያ መሣሪያ ነው፡፡ የመጣውን ጠላት በሰፍይ እንዳይሆን አድርጎ መሸኘት ይቻላል፡፡ እንደ ሰይፍ የተመሰለው ደግሞ የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ ቃሉን ሁልጊዜ መማር ( ማወቅ ) ማለት ዲያብሎስን ድል ለማድረግ እጅግ በጣም ይጠቅመናል፡፡ ቃሉን ለማወቅና ለመማር ብዙ ጊዜአችንን እንስጥ፡፡ ብዙ ጊዜ ድል የምንነሳው ቃሉ ስሌለን ነው፡፡ ለምሳሌ እግዚአብሔርን በየቀኑ እንበድላለን እንበል፡፡ የምንበድለው ግን ፈልገን ሳይሆን ፈተና በዝቶብን ነው፡፡ ያንን ፈተና ደግሞ ያመጣብን ዲያብሎስ ነው፡፡ በየቀኑ ስለ በደልነው ዲያብሎስ እግዚአብሔርን እያሳዘንነው እንደሆነና ከኛ ጋር እንዳልሆነ ይነግረናል፡፡ በዚህ ጊዜ የበለጠ ተስፋ በመቁረጥ ለዲያብሎስ እጅ እንድንሰጥና እንድንማረክ እንሆናለን፡፡ ቃሉን ብናውቅ ግን የበደልነው አምላክ መሐሪ መሆኑን ስለምንረዳ፡- ይቅር በለን እያልን በመለመን፣ ከዚህ ፈተናም እንዲያወጣን እየተማጸንን ሰንታክት ስለምንጸልይ ፣ ዲያብሎስ ምንም ቢለን ጆሮ ስለማንሰጠው ድል እንነሳዋለን፡፡ ስለዚህ የዲያብሎስን የተንኮል ሥራ መቋቋም እንድንችልና ድል እንድንነሳው  እውነትን እንያዝ፣ በጽድቅ እንጓዝ፣ ወንጌልን መመከቻ እንድርግ፣ በእግዚአብሔር ላይ ያለን እምነት ጠንካራ ይሁን፣ መዳናችን እናስተውል፣  የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑረን፡፡ ለሁሉም ነገር መፍትሄው ቃሉን መማር ነውና ቃሉን ተግተን እንማር፡፡ በጸሎትም እግዚአብሔርን እየለመንን ከተጓዝን ማንኛውንም የተንኮል ሥራውን መቋቋም እንችላለን፤ ድልም እንነሳዋለን፡፡ ወአምላከ ሰላም ለይቀጥቅጦ ለሰይጣን በታሕተ እገሪክሙ ፍጡነ፡፡ ጸጋሁ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ የሀሉ ምስለ ኵልክሙ፡፡ አሜን! የሰላምም አምላክ ሰይጣንን ከእግራችሁ በታች ፈጥኖ ይቀጠቅጠዋል። የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን ( ሮሜ 16 ÷ 20 ) ።   ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
88
16
የዲያብሎስን የተንኮል ሥራ ለመቋቋምና ሁልጊዜ ድል እንድንነሳው ማድረግ ያለብን ፡፡   የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ። መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ። ስለዚህ በክፉው ቀን ለመቃወም፥ ሁሉንም ፈጽማችሁ ለመቆም እንድትችሉ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ አንሡ። እንግዲህ ወገባችሁን በእውነት ታጥቃችሁ፥ የጽድቅንም ጥሩር ለብሳችሁ፥ በሰላም ወንጌልም በመዘጋጀት እግሮቻችሁ ተጫምተው ቁሙ፤ በሁሉም ላይ ጨምራችሁ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ አንሡ፤ የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው። በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ ( ኤፌ 6 ÷ 10- 18 ) ፡፡   ማብራሪያ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዲያብሎስን ሥራ ለማፍረስ የእኛን ሥጋ በመልበስ የተገለጠ ሲሆን በመስቀልም ላይ ስለኛ ኃጢአት በመሞቱ ዲያብሎስን ድል ነስቶልናል፡፡ እኛም ዘወትር ድል ልንነሳው ይገባል፡፡ ዲያብሎስ ተንኮለኛ ነው፡፡ በተንኮሉ ሔዋንን እንዳሳሳታት እኛንም ለማሳሳት ሁሌ ይፈልጋል፡፡ ጳውሎስ የኤፌሶንን መልዕክት የጻፈው በሮም ታስሮ በነበረበት ወቅት ነው፡፡ ሮማዊ ወታደር በጦርነት ወቅት ሊለብሳቸው የሚገባቸውን የጦር መሣሪያዎችን በመዘርዘር ልክ እንደዚሁ ከኛም የሚጠበቅብንን ነገር ሊያስገነዝበን ይወዳል፡፡ አንድ ወታደር ወደ ውጊያ ሲሄድ የጦር መሣሪያ መያዝ እንዳለበት፣ ክርስቲያን የዲያብሎስን የተንኮል ሥራ ለመቋቋምና ራሱንም ድል ለመንሳት የሚያስፈልገው ነገር የእግዚአብሔርን የጦር ዕቃ ( መሣሪያ) መልበስ ነው፡፡ ከዲያቢሎስ ጋር በምናደርገው መጋደል፣ ውጊያው መንፈሳዊ ነው እንጂ ሥጋዊ አይደለም፡፡ ሰዎች በክፋት ቢነሳሱብን ሰዎቹን ያነሳሳብን ዲያብሎስ እንደ ሆነ ማወቅ አለብን፡፡ ስለዚህም ከሥጋና ከደም ( ከሰው ) ጋር እንደምንጋደል ማሰብ የለብንም፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወታችን በዲያብሎስ እንዳንሸነፍ የምናደርገው ትግል መንፈሳዊ ውጊያ ይባላል፡፡ መንፈሳዊ ውጊያ ( ጦርነቱ) ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር  ከተባሉት ጋር ነው፡፡ ባጭሩ መንፈሳዊ ውጊያ የምናደርገው ከርኩሳን መናፍስት ጋር ነው፡፡ ተቋቁመን ዲያብሎስን ድል መንሳት እንድንችል መልበስ ያለብንን የእግዚአብሔርን የጦር ዕቃዎች አንድ በአንድ እንመልከት፡፡ ወገባችንን በእውነት መታጠቅ ፡፡ ሮማውያን ወታደሮች በወገባቸው ላይ ዝናር ይታጠቁ ነበር፡፡ የሀሰት አባት ዲያብሎስን ለማሸነፍ ከሚያስፈልገን አንዱ እውነትን ይዞ መገኘት ነው፡፡ በየትኛውም ነገራችን በእውነት መመላሰስ አለበን፡፡ እውነትን የያዘ ሰው ወገቡን ዝናር እንደ ታጠቀ ሰው ነው፡፡ ጽድቅን እንደ ጥሩር መልበስ ፡፡ ጥሩር ከአንገት እስከ ጉልበት የሚደርስ የጦር መሣሪያ መከላከያ ነው፡፡ ወደ ደረት የተላከን የጦር መሣሪያ የሚከላከልልን ጥሩር ነው፡፡ ለክርስቲያን በጽድቅ መጓዝ አማራጭ የሌለው ነገር ከመሆኑ ባሻገር ኃጢአትን እንድንሠራ በጠላት ለሚላክብን ሽንገላና ማባበያ ብርቱ መከላከያም ነው፡፡ ዲያብሎስ ኃጢአትን ብንሠራ እንደሚጠቅመን አድርጎ በተለያየ ዘዴ ሊያሳምነን (ሊሸነግለን) ይፈልጋል፡፡ ሁሌም ጽድቅን ማድረግ ዓላማችን ሲሆን ሀሳቡን አንቀበለውም፡፡ እንድንሠራ የሚያስጎመጀንን ኃጢአት በመናቅ በጽድቅ መሄድ ጠቀሜታው ታላቅ ነው፡፡ እንኳን በጽድቅ ሳንጓዝ አግኝቶን ይቅርና በጽድቅ እየተጓዝንም የጠላት ክስ ከባድና መቋቋም የሚያቅተን ጊዜ አለ፡፡ ወንጌልን እንደ ጫማ መጫማት ፡፡ ጫማ ለእግራችን አስፈላጊ እንደሆነ ሁሉ ወንጌል በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ወንጌል ማለት የምሥራች ማለት ነው፡፡ የምሥራቹ ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለኛ ኃጢአት መሞቱና እኛን ማዳኑ ነው፡፡ ወንጌሉም የሰላም ወንጌል ነው፡፡ እግራችን ጫማ እንደማይለየው ሁልጊዜ ይህ የምሥራች ማለት ክርስቶስ እኛን ማዳኑን ከልባችን ሊጠፋ አይገባም፡፡ ይህ የምሥራች ሁልጊዜ በልባችን ሲኖር ዲያብሎስን ድል እንነሳዋለን፡፡ የእምነት ጋሻ ፡፡ ጋሻ በእጅ የሚያዝ የጦር መሣሪያ መከላከያ ነው፡፡ ተዋጊ ሰው ከጠላት የሚወረወሩት የጦር መሣሪያዎች ወደ ሰውነቱ እንዳይደርሱና እንዳይጎዱት ቀድሞ የሚከላከለውና የሚያመክነው በጋሻው በመመከት ነው፡፡ ዲያብሎስ ወደኛ የሚልካቸው ፍላጻዎች የሚንበለበሉ ናቸው፡፡ የሚንበለበሉ የሚለው ቃል እንደሚነግረን እጅግ አደገኛና ጎጂ መሆናቸውን ነው፡፡ ሰይጣን ሊጎዱን የሚችሉትን ማናቸውንም ሀሳቦች ወደ አዕምሮአችን ይልካል፡፡ እነዚህን እንደ ፍላጻ ያሉ ሀሳቦች መመከት የምንችለው በእግዚአብሔር ላይ በእምነት በመደገፍ ነው፡፡ እኛ ታናሽ ምንም ማድርግ የማንችል ብንሆንም ያመነው አምላክ ግን ታላቅ መሆኑን ሁልጊዜም እንመን፡፡ በእግዚአብሔር ላይ ያለንን እምነት ማጠንከር አለብን፡፡ እምነት ልክ እንደ ጋሻ ነው፡፡  የመዳን ራስ ቁር ፡፡ ራስ ቁር በራስ ላይ የሚደፋ የጦር መሣሪያ መከላከያ ነው፡፡ ወደ ራስ ለተላከ ቀስት የራሱ ቁሩ መከላከያ ነው፡፡ ወንጌል ክርስቶስ ሊያድነን እንደ ሞተልን ይነግረናል፡፡ እኛ መሰቀል ሲገባን ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ተሰቅሎአል፡፡ መዳናችን በክርስቶስ ተፈጽሞአል፡፡ ስለ መዳናችን የምንፈጽመው ነገር የለም፡፡ ከኛ የሚጠበቀው አምነነው መከተል ብቻ ነው፡፡ አምነነው ከተከተልነው መንግሥቱን ያወርሰናል፡፡ አምነነው ተከትለነው መንግሥቱን እንደማያወርሰን የምናምን ከሆነ ክርስቲያን በመሆን ለምን እንደክማለን? የማንጸድቅ ከሆነ ለምንስ ስለ ክርስትና ልክ መሆን ከሌሎች ጋር በመከራከር ጊዜአችንን እናጠፋለን? ክርስቲያን መሆናችን ዋናው ዓላማው እኮ መንግሥቱን ለመውረስ ነው፡፡ ክርስቶስ ሞቶልን የማንጸድቅ ከሆነ ወደ ምድር መምጣቱ ከንቱ ነው ማለት ነው፡፡ ክርስቶስ የመጣው እኛን ለማዳን መሆኑን መዘንጋት የለብንም፡፡ ተሰቅሎ አድኖናል፡፡ አምነነው ከተከተልነው መዳን ይሆንልናል፡፡ ይህ የመዳን ተስፋ በልባችን አለ ማለት ልክ እንደ ራሱ ቁሩ ነው፡፡ አምነን እስከ ተከተልነው ያለ ጥርጥር መዳን ሆኖልናል፡፡ ስለ መዳናችን ደግሞ እከሌ ሊመሰክርልን አይገባም፡፡ ልጆቹ በመሆናችን በእኛ ያደረው የእግዚአብሔር መንፈስ ብቻ ነው ሊመሰክርልን የሚገባው፡፡ ልጆቹ እንደ ሆንን ተሰማን ማለት መዳናችንን ( መንግሥቱን መውረሳችንን) እርግጠኞች ነን ማለት ነው፡፡ ይህ እምነት ሲኖረን በእርግጠኝነት ዲያብሎስን ድል እንነሳዋለን፡፡  ከበላይ የተጠቀሱት የእግዚአብሔር የጦር መሣሪያዎች በሙሉ በጣም ስለሚያስፈልጉን ሊኖሩን ይገባል፡፡ ሁሉም ለመከላከያ የሚያገለግሉ ናቸው፡፡ ለራሳችን የራሱ ቁር ፣ ለደረታችን ጥሩር፣ ለወገባችን ዝናር ፣ ለእግራችን ጫማ፣ ወደኛ ለሚላኩ የጦር መሣሪያዎች ቀድመው ወደ ሰውነታችን ሳይደርሱ መመከቻ ጋሻ ፡፡ ጋሻውን አልፎ ወደ ራስ ለተላከ ቀስት የራሱ ቁሩ ሲከላከል ፣ ለደረት የተሰደደውን ደግሞ ጥሩር ይከላከለዋል፡፡
72
17
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
65
18
የሐዋርያት ሥራ ጥናት ፡፡ ክፍል 18 ፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ ስለ ደብተራ ኦሪትና ስለ ሰሎሞን ቤተ መቅደስ የሰጠው መቋጫ ንግግር ፡፡   ከክፍል 17 ባጭሩ ፡፡ ..ጌታም፡- ..ወደ ግብፅ እልክሃለሁ አለው። ..ሙሴን እግዚአብሔር ..ላከው። ይህ ሰው ( ሙሴ ) በግብፅ ምድርና በኤርትራ ባሕር በምድረ በዳም አርባ ዓመት ድንቅና ምልክት እያደረገ አወጣቸው ( የሐዋ 7 ÷ 23 – 36 ) ። -----////////-----------   ይህ ሰው ለእስራኤል ልጆች፡- እግዚአብሔር ከወንድሞቻችሁ እንደ እኔ ያለ ነቢይ ያስነሣላችኋል፤ እርሱን ስሙት ያላቸው ሙሴ ነው። ይህ ሰው በሲና ተራራ ከተናገረው መልአክና ከአባቶቻችን ጋር በምድረ በዳ በማኅበሩ ውስጥ የነበረው ነው፤ ይሰጠንም ዘንድ ሕይወት ያላቸውን ቃላት ተቀበለ፤ ለእርሱም አባቶቻችን ሊታዘዙት አልወደዱም፤ ነገር ግን ገፉት በልባቸውም ወደ ግብፅ ተመለሱ፤ አሮንንም፡- በፊታችን የሚሄዱ አማልክት ሥራልን፤ ይህ ከግብፅ ምድር ያወጣን ሙሴ ምን እንደ ሆነ አናውቅምና አሉት። በዚያም ወራት ጥጃ አደረጉ ለጣዖቱም መሥዋዕት አቀረቡ፥ በእጃቸውም ሥራ ደስ አላቸው። እግዚአብሔር ግን ዘወር አለ የሰማይንም ጭፍራ ያመልኩ ዘንድ አሳልፎ ሰጣቸው፥ በነቢያትም መጽሐፍ፡- እናንተ የእስራኤል ቤት፥ አርባ ዓመት በምድረ በዳ የታረደውን ከብትና መሥዋዕትን አቀረባችሁልኝን? ትሰግዱላቸውም ዘንድ የሠራችኋቸውን ምስሎች እነርሱንም የሞሎክን ድንኳንና ሬምፉም የሚሉትን የአምላካችሁን ኮከብ አነሣችሁ፤ እኔም ከባቢሎን ወዲያ እሰዳችኋለሁ ተብሎ እንዲህ ተጽፎአል። እንዳየው ምስል አድርጎ ይሠራት ዘንድ ሙሴን ተናግሮ እንዳዘዘው፥ የምስክር ድንኳን ከአባቶቻችን ዘንድ በምድረ በዳ ነበረች፤ አባቶቻችንም ደግሞ በተራ ተቀብለው እግዚአብሔር በፊታቸው ያወጣቸውን የአሕዛብን አገር በያዙት ጊዜ ከኢያሱ ጋር አገቡአት፥ እስከ ዳዊት ዘመንም ድረስ ኖረች። እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ አግኝቶ ለያዕቆብ አምላክ ማደሪያን ያገኝ ዘንድ ለመነ። ነገር ግን ሰሎሞን ቤት ሠራለት። ነገር ግን ነቢዩ፡- ሰማይ ዙፋኔ ነው ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት፤ ለእኔ ምን ዓይነት ቤት ትሠራላችሁ? ይላል ጌታ፥ ወይስ የማርፍበት ስፍራ ምንድር ነው? ይህንስ ሁሉ እጄ የሠራችው አይደለምን? እንዳለ፥ ልዑል የሰው እጅ በሠራችው አይኖርም ( የሐዋ 7 ÷ 37 – 50 ) ።   ማብራሪያ ሙሴ እስራኤላውያንን እየመራ ከግብፅ ያወጣቸው ነው፡፡ በምድረ በዳም አሥርቱን ትእዛዛት ከእግዚአብሔር ተቀብሎአል፡፡ እንደ እኔ ያለ ነቢይ እግዚአብሔር ያስነሣላችኋል ብሎ ሲናገር፡- ነቢይ ያለው ለጊዜው ከእርሱ በኋላ የሚነሣውን ኢያሱን ሲሆን ፍጻሜ ግን ክርስቶስን ነበር፡፡ ሙሴ በሲና ተራራ ከእግዚአብሔር ጋር ሲነጋገር ሕዝቡ ፡- ከግብፅ ካወጣቸው ከእግዚአሔር በቀር ሌላ አምላክ እንዳያመልኩ ተነግሮአቸው እነርሱ ግን የጥጃ ጣዖት ሠርተው ያመለኩ ነበሩ፡፡ በኢያሱ መሪነት አገራቸውም ገብተው ሲያበቁ ጣዖት የማምለክ አባዜአቸው አለቅ ብሎአቸው ጣዖት ማምላካቸውን ስለ ቀጠሉና እጅግ ደግሞ ሲያበዙት በባቢሎናውያን እንዲማረኩ እግዚአብሔር አድርጎአቸው ነበር ፡፡ ሙሴ ከድንኳን ቤተ መቅደስ እንዲሠራ በእግዚአብሔር ስለ ተነገረው የምስክር ድንኳን ( ደብተራ ኦሪትን ) ሠርቶ ነበር፡፡ ሙሴ ሞቶ ኢያሱ ሕዝበ እስራኤላውያንን ወደ አገራቸው አስገባቸው፡፡ እስከ ዳዊት ድረስ እግዚአብሔር የሚመለከው በደብተራ ኦሪት ( ከድንኳን በተሠራ መቅደስ ) ነበር፡፡ ዳዊት በተሻለ መልኩ ለእግዚአብሔር ቤት ሊሠራ ፈልጎ አልተፈቀደለትም፡፡ ልጁ ሰሎሞን  ለእግዚአብሔር ቤት ( ቤተ መቅደስ ) ሠራለት ፡፡ ከሰሎሞን ከብዙ ዘመን በኋላ የተነሣው ነቢዩ ኢሳይያስ ፡- ለእኔ ምን ዓይነት ቤት ትሠሩልኛለችሁ? ልዑል የሆንኩት እግዚአብሔር የሰው እጅ በሠራችው አይኖርም በማለት እግዚአብሔር የተናገረውን ነገር ለሕዝበ እስራኤል ነግሮአቸው ነበር፡፡ በሐዋርያት ሥራ በምዕራፍ 7 የቅዱስ እስጢፋኖስ ንግግር መቋጫ እግዚአብሔር ሰው በሠራው ቤተ መቅደስ አይኖርም ነው፡፡ የመጀመሪያይቱ ቤተ መቅደስ ሙሴ ከድንኳን የሠራት ቤተ መቅደስ ናት፡፡ በመቀጠል ሰሎሞን ደግሞ በተሻለ መልኩ ቤተ መቅደስ ሠራ፡፡ ራሱ ሰሎሞን ፡- ሰማይ ከሰማይም በላይ ያለው ሰማይ የማይዝህ አምላክ ሆይ እኔ የሠራሁት ቤት ላንተ እንዴት ያንስ ? ( 1ነገ 8 ÷ 27 ) በማለት ቤተ መቅደሱ ለእግዚአብሔር እንደማይመጥን ተናግሮ ነበር፡፡ ሰሎሞን የሠራው ቤተ መቅደስ በባቢሎናውያን ፈርሶም ነበር፡፡ አይሁድም ተማርከው ተወስደው ነበር፡፡ ከምርኮ ሲመለሱ ቤተ መቅደሱን ሠርተውት ነበር፡፡ በነእስጢፋኖስ ዘመን ባለ መቅደሶቹ አይሁድ በቤተ መቅደሳቸው ቢኩራሩም እስጢፋኖስ ግን፡- ልዑል እግዚአብሔር የሰው እጅ በሠራው አይኖርም በማለት የቤተ መቅደሱ አገልግሎት እንዳከተመ አስረዳቸው፡፡ እውነተኛ ቤተ መቅደስ በክርስቶስ ያመንን ሰዎች ነን፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ብሎአል፡- የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ ( 1ቆሮ 3 ÷ 17  ) ። በክርስቶስ የምናምን ክርስቲያኖች እግዚአብሔር እኛን ክርስቲያኖቹን ቤተ መቅደሱ በማድረግ አክብሮናል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ይቀጥላል፡፡ ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
59
19
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
49
20
የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል ፡፡   የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም  ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል ( ዮሐ 1 ÷ 7)  ፡፡   ማብራሪያ የየኔታ የጥንት ማሪዎች አቡጊዳን ሲጨርሱና መልእክተ ዮሐንስ ሲያነቡ ይህን ቃል በዛ በሕፃንነታቸው ጊዜ በሕፃን አንደበት ፡- ያነጽሐነ እምኩሉ ኃጣውኢነ ( ከኃጢአታችን ሁሉ ያነጻናል ) በማለት ለንባብ ችሎታ ያነቡት ነበር፡፡ መልእክተ ዮሐንስ ማለት ከመጀመሪያይቱ የዮሐንስ መልእክት ከምዕራፍ አንድ የተወሰደ ነው፡፡ ልጅ የተባለው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ወልድ የአብ ልጅ ነው፡፡ ስለኛ ኃጢአት ደሙ በቀራንዮ ፈሷል፡፡ ያ የፈሰሰው ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል፡፡ ምንም ዓይነት ኃጢአት ሠርተን እግዚአብሔርን፡- ይቅር በለን ስንል ከየትኛውም ኃጢአት በዚህ ደም እንነጻለን፡፡ ደግሞም የነጻን በእግዚአብሔር ፊት መቅረብ የምንችል ክርስቲያኖች ነን፡፡ የፈሰሰው ደሙ እንዲሁ የፈሰሰ አይደለም፡፡ ከአቤል ጀምሮ  እስከ ዘካርያስ (ኢየሱስ ክርስቶስ እስከ መጣበት ዘመን) ድረስ ብዙ ሰዎች ደማቸው በከንቱ ፈሷል፡፡ የኢየሱስም ደም በዚሁ መልኩ እንዲሁ የፈሰሰ አይደለም፡፡ ከፈሰሰ እንደማይታፈስም ውኃ የክርስቶስ ደም እንዲሁ ፈስሶ የቀረ አይደለም፡፡ ደሙ ለኛ ለሰው ልጆች የፈሰሰ ነው፡፡ ከኃጢአታችን ሊያነጻን የፈሰሰ ነው፡፡ በዲያብሎስ ክስ ምክንያት በእግዚአብሔር ፊት እንዳይቆሙ ለሚደርጋቸው ሰዎች ሁሌም በፊቱ እንዲቆሙ የሚያደርግ ደም ነው፡፡ በራሱ መቆም ያልቻለ ተከሳሽ በጠበቃው አማካኝነት ፍርድ ቤት ለመቆም እንደሚችል እኛም እግዚአብሔር ፊት መቆም የማንችል ሲሆን የፈሰሰው ደም ግን ለኛ በመሆኑ እግዚአብሔርን ፡- አባታችን ብለን ያለ ፍርሀት በመጥራት እንድንለምነው  የሚያቆመን ደም ነው፡፡ ኃጢአተኞች ናችሁ እያለ ከምንናፍቀው አባታችን ፊት ዘወትር እንዳንቀርብ ዲያብሎስ ሲከሰን በዚህ ደም የነጻንና ከኃጢአታችንም የተሸፈንን መሆናችንን ልብ ማለት ከቻልን ድል እንነሳዋለን፡፡ ከኃጢአት ሁሉ የሚያነጻ መሆኑንም አንዘንጋ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
62