ru
Feedback
እግዚአብሔርን ማወቅ

እግዚአብሔርን ማወቅ

Открыть в Telegram

ሰላምታ በተለዋወጥን ቁጥር ይመስገን ስለምንለው አምላካችንና አባታችን እግዚአብሔር ያለንን ዕውቀት ለማዳበር የሚያግዝ ቻነል ነው፡፡

Больше
925
Подписчики
-224 часа
-17 дней
+1130 день

Загрузка данных...

Облако тегов
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Входящие и исходящие упоминания
---
---
---
---
---
---
Привлечение подписчиков
июль '26
июль '26
+10
в 0 каналах
июнь '26
+43
в 0 каналах
Get PRO
май '26
+31
в 0 каналах
Get PRO
апрель '26
+45
в 0 каналах
Get PRO
март '26
+33
в 0 каналах
Get PRO
февраль '26
+49
в 0 каналах
Get PRO
январь '26
+45
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '25
+54
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '25
+38
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '25
+37
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '25
+31
в 0 каналах
Get PRO
август '25
+32
в 0 каналах
Get PRO
июль '25
+45
в 0 каналах
Get PRO
июнь '25
+49
в 0 каналах
Get PRO
май '25
+24
в 0 каналах
Get PRO
апрель '25
+19
в 0 каналах
Get PRO
март '25
+18
в 0 каналах
Get PRO
февраль '25
+11
в 0 каналах
Get PRO
январь '25
+9
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '24
+19
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '24
+25
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '24
+27
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '24
+17
в 0 каналах
Get PRO
август '24
+20
в 0 каналах
Get PRO
июль '24
+35
в 0 каналах
Get PRO
июнь '24
+21
в 0 каналах
Get PRO
май '24
+23
в 0 каналах
Get PRO
апрель '24
+12
в 0 каналах
Get PRO
март '24
+31
в 0 каналах
Get PRO
февраль '24
+11
в 0 каналах
Get PRO
январь '24
+15
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '23
+15
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '23
+12
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '23
+13
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '23
+479
в 0 каналах
Дата
Привлечение подписчиков
Упоминания
Каналы
11 июля0
10 июля+1
09 июля+1
08 июля0
07 июля+1
06 июля+1
05 июля+1
04 июля0
03 июля0
02 июля+4
01 июля+1
Посты канала
ጴጥሮስ ወጳውሎስ ( ጴጥሮስና ጳውሎስ ) ::   ቅዱስ ጳውሎስ ፡፡ ሳውል(ጳውሎስ) ግን የጌታን ደቀ መዛሙርት እንዲገድላቸው ገና እየዛተ.. ወንዶችንም ሴቶችንም.. እያሰረ ወደ ኢየሩሳሌም ያመጣቸው ዘንድ በደማስቆ ላሉት ምኵራቦች ደብዳቤ ..ለመነ። ሲሄድም ወደ ደማስቆ በቀረበ ጊዜ ድንገት በእርሱ ዙሪያ ከሰማይ ብርሃን አንጸባረቀ፤በምድርም ላይ ወድቆ ሳለ፡- ሳውል ሳውል፥ ስለ ምን ታሳድደኛለህ? የሚለውን ድምፅ ሰማ።ጌታ ሆይ፥ ማን ነህ? አለው። እሱም፡- አንተ የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ፤ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል አለው።እየተንቀጠቀጠና እየተደነቀ፡- ጌታ ሆይ፥ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ? አለው። ጌታም፡- ተነሥተህ ወደ ከተማ ግባና ታደርገው ዘንድ የሚያስፈልግህን ይነግሩሃል አለው።…ሳውልም ከምድር ተነሣ፥ አይኖቹም በተከፈቱ ጊዜ ምንም አላየም፤ እጁንም ይዘው እየመሩ ወደ ደማስቆ አገቡት። ሳያይም ሦስት ቀን ኖረ፤ አልበላምም አልጠጣምም ፡፡ ..ሐናንያ የሚሉት ..ደቀ መዝሙር ነበረ፥ ጌታም በራእይ፡- ሐናንያ ሆይ፥ ..ሳውል የሚሉትን ..ሰው ፈልግ.. አለው። ሐናንያም መልሶ፡- ጌታ ሆይ፥ ..በቅዱሳንህ ላይ ስንት ክፉ እንዳደረገ ስለዚህ ሰው ..ሰምቼአለሁ፤ ..ስምህን የሚጠሩትን ሁሉ ለማሰር ..ሥልጣን አለው አለ። ጌታም፡- ..ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፤ ..ሐናንያም ሄዶ ወደ ቤቱ ገባ፥ እጁንም ጭኖበት፡- ..ሳውል ሆይ፥ ጌታ፥ በ.. መንገድ የታየህ ኢየሱስ ነው፥ ደግሞ ..ላከኝ አለ። ወዲያውም እንደ ቅርፊት ያለ ከዓይኑ ወደቀ፥ ያን ጊዜም ደግሞ አየ፤ ተነሥቶም ተጠመቀ፥ ወዲያውም ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ..ሰበከ። የሰሙትም ሁሉ ተገረሙና፡- ይህ በኢየሩሳሌም ይህን ስም የሚጠሩትን ያጠፋ አይደለምን? ስለዚህስ ታስረው ወደ ካህናት አለቆች ይወስዳቸው ዘንድ ወደዚህ አልመጣምን? አሉ። ሳውል ግን እየበረታ ሄደ፤ .. አይሁድ ሊገድሉት ተማከሩ፤ ሳውል ግን አሳባቸውን አወቀ። ይገድሉትም ዘንድ በሌሊትና በቀን የከተማይቱን በር ሁሉ ይጠቀብቁ ነበር፤ ደቀ መዛሙርት ግን በሌሊት ወስደው በቅጥር ላይ አሳልፈው በቅርጫት አወረዱት። ሳውልም ወደ ኢየሩሳሌም በደረሰ ጊዜ ከደቀ መዛሙርት ጋር ይተባበር ዘንድ ሞከረ፤ ሁሉም ደቀ መዝሙር እንደ ሆነ ስላላመኑ ፈሩት። በርናባስ ግን ወስዶ ወደ ሐዋርያት አገባውና ጌታን በመንገድ እንዴት እንዳየውና እንደ ተናገረው ..በኢየሱስ ስም ደፍሮ እንዴት እንደ ነገረ ተረከላቸው ( የሐዋ 9፥1-27) ።   ማብራሪያ ቅዱስ ጳውሎስ የቀድሞ ስሙ ሳውል ነበር፡፡ እንደ ጴጥሮስ ከ12ቱ ሐዋርያነት አንዱ አልነበረም፡፡ የጌታ ደቀ መዛሙርትን ማለት ከአይሁድ እምነት ወደ ክርስትና የተመለሱትን ወደ እስር ቤት እንዲገቡ የሚያደርግ ነበር ( የሐዋ 8 ፥ 3 )፡፡ ሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ በድንጋይ ተወግሮ ሲገደል የተስማማ ሰው ነበር (የሐዋ 7 ፥ 58 - 60 ፤ 22 ፥ 20 )፡፡ ይህን ሁሉ የሚያደርገው ክርስትና እንዳይስፋፋና እንዲጠፋ በመፈለግ ነው፡፡ እንደ ለመደው በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ያመኑትን አይሁድ እንዲታሰሩ ወደ ደማስቆ ሲሄድ ያልጠበቀው ክስተት ተከሰተ፡፡ ታላቅ ብርሃን በራ፡፡ ሳውል ( ጳውሎስ ) መሬት ላይ ወደቀ፡፡ እስከ አሁን ሲያሳድድ፡- ስለምን ታሳድደኛለህ? የሚል አላጋጠመውም ነበር ፡፡ አሁን ግን፡- ሳውል ብሎ ስሙን ጠርቶ፡- ስለምን ታሳድደኛለህ? የሚል ጠያቂ ተገኘ፡፡ ስለምን ታሳድደኛለህ? ባዩ ሳውልን ግን መሬት ላይ ጥሎት ነበር፡፡ መሬት ላይ የወደቀው ሳውል ከአቅሙ በላይ የሆነ ኃያል ስለመጣበት ጌታ ብሎ ጠርቶ፡- ጌታ ሆይ አንተ ማን ነህ? አለ፡፡ የማይጋፋው ባላጋራ ሆነበት፡፡ የሚያሳድደው ክርስቲያኖችን ቢሆንም (በዚህ ሰዓት ስማቸው ደቀመዛሙርት ነበር የሚባሉት) እነርሱን ማሳደድ ክርስቶስን ማሳደድ ስለሆነ ፡- ማን ነህ ብሎ ለጠየቀው ጥያቄ፡- የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ፤…ይብስብሀልም አለው፡፡ የተንቀጠቀጠውና የተገረመው ሳውል ሊያሸንፈው ያልቻለውን መሬት ላይ የጣለውን ፡- ጌታ ሆይ በማለት ጠርቶ፡- ምን አደርግ ዘንድ ትወድዳለህ ? ብሎ ጠየቀ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስም ሊያደርግ የሚገባውን ነገር ነገረው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ሐናንያን ፡- ሄደህ ለሳውል ጸልይለት ሲለው በጣም ነበር የፈራው ፡፡ ሳውል በአሳዳጅነቱ ይታወቅ ነበር፡፡ ሳውል አምኖ ተጠመቀ፤ አይኖቹም ተከፈቱ ፡፡ ስለ ክርስቶስ አዳኝነት መስበክ ጀመረ ፡፡ መስበኩን ያዩ ሰዎች ሊያሳስራቸው የመጣ እንጂ እውነት አልመሰላቸውም ነበር፡፡ ያላመኑት አይሁድ ደግሞ ሲሰብክ ሲሰሙ ሊገድሉት ፈለጉ፡፡ ከተማይቱ ዙሪያዋን ቅጥር ነበራትና በበሩ ሲወጣ ሊገድሉት  አስበው በሩ ላይ ይጠብቁት ነበር፡፡ እርሱ ግን በቅጠሩ ላይ በዘዴ ዘሎ በመውረድ አመለጠ፡፡    ቅዱስ ጴጥሮስ ፡፡ ጴጥሮስም ከቤት ውጭ በአጥሩ ግቢ ተቀምጦ ነበር፤ አንዲት ገረድም ወደ እርሱ ቀርባ። አንተ ደግሞ ከገሊላው ከኢየሱስ ጋር ነበርህ አለችው።እርሱ ግን፡- የምትዪውን አላውቀውም ብሎ በሁሉ ፊት ካደ። ወደ በሩም ሲወጣ ሌላይቱ አየችውና በዚያ ላሉት፡- ይህ ደግሞ ከናዝሬቱ ከኢየሱስ ጋር ነበረ አለች። ዳግመኛም ሲምል። ሰውየውን አላውቀውም ብሎ ካደ። ጥቂትም ቈይተው በዚያ ቆመው የነበሩ ቀርበው ጴጥሮስን፡- አነጋገርህ ይገልጥሃልና በእውነት አንተ ደግሞ ከእነርሱ ወገን ነህ አሉት። በዚያን ጊዜ፡- ሰውየውን አላውቀውም ብሎ ሊራገምና ሊምል ጀመረ። ወዲያውም ዶሮ ጮኸ። ጴጥሮስም፡-ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ ያለው የኢየሱስ ቃል ትዝ አለው፤ ወደ ውጭም ወጥቶ መራራ ልቅሶ አለቀሰ ( ማቴ 26 ÷ 69 - 75 ) ፡፡   ማብራሪያ ቅዱስ ጴጥሮስ ችኩል ባሕሪ የነበረው ሲሆን ጌታችን ኢየሱስን፡- አላውቀውም ብሎ ክዶም ነበር፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወቱ ሲበረታ ግን ወንጌልን ደፍሮ የሰበከ ነበር፡፡ የጳውሎስም ሆነ የጴጥሮስ ታሪክ ሰፊ ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጴጥሮስ፡- እንደ ጌታዬ አትስቀሉኝ በማለት ቁልቁል ተሰቅሎ፣ ጳውሎስ ደግሞ በሰይፍ ተቀልቶ እንደ ሞቱ ይነገራል፡፡ የሁለቱም መታሰቢያ በዓል ሐምሌ 5 ቀን ነው፡፡ ከሰማዕታት ጽናትን እንማራለን፡፡ እነርሱ ላመኑት ለክርስቶስ ለነፍሳቸው ሳይቀር አልሳሱም፡፡ መውደቅ መነሣት ያለ ነው፡፡ ለምሳሌ ጴጥሮስ ክዶ ነበር፡፡ ነገር ግን ከውድቀታችን ተምረን የሞተልንን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እስከ ሕይወታችን ፍጻሜ  ድረስ መከተል ይገባናል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግ አምላክ ነው፡፡ የካደውን ጴጥሮስን አሳዳጁን ጳውሎስንም ይቅር ብሎ እንዲያገለግሉት ያደረገ አምላክ ነው፡፡ ደካሞች ናችሁ ብሎ እኛንም አይተወንም፡፡  እንደ ጴጥሮስና ጳውሎስ እግዚአብሔር መጽናትን ያድለን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie

2
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
26
3
የሐዋርያት ሥራ ጥናት ፡፡ ክፍል 38 ፡፡ የጳውሎስ መወገርና የመጀመሪያው ሐዋርያዊው ጉዞ መጠናቀቁ ፡፡   ከክፍል 37 ባጭሩ ፡፡ በልስጥራንም ..አንካሳ የሆነ፥ ..ሰው ነበር። ..ጳውሎስ በታላቅ ድምፅ፡- በእግርህ ቁም አለው። ..ተንሥቶ ይመላለስ ነበር። ሕዝቡም ጳውሎስ ያደረገውን ባዩ ጊዜ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው.. ፡- አማልክት ሰዎችን መስለው ወደ እኛ ወርደዋል አሉ፤ በከተማውም ፊት ቤተ መቅደስ ያለው የድያ ( የጣዓት ) ካህን ኮርማዎችንና የአበባን አክሊሎች ..ሊሠዋላቸው ወደደ። ሐዋርያት በርናባስና ጳውሎስ ግን ..ልብሳቸውን ቀደው ..እንዲህም አሉ። እናንተ ሰዎች፥ ..እኛ ደግሞ እንደ እናንተ የምንሰማ ሰዎች ነን፥ ..ወደ ሕያው እግዚአብሔር ዘወር ትሉ ዘንድ ወንጌልን እንሰብካለን.. ( የሐዋ 14 ÷ 8 - 18 ) ። --------////--------   አይሁድ ግን ከአንጾኪያና ከኢቆንዮን መጡ፤ ሕዝቡንም አባብለው ጳውሎስን ወገሩ የሞተም መስሎአቸው ከከተማ ወደ ውጭ ጐተቱት። ደቀ መዛሙርት ግን ከበውት ሳሉ፥ ተነሥቶ ወደ ከተማ ገባ። በነገውም ከበርናባስ ጋር ወደ ደርቤን ወጣ። በዚያችም ከተማ ወንጌልን ሰብከው እጅግ ደቀ መዛሙርትን ካደረጉ በኋላ፥ የደቀ መዛሙርትን ልብ እያጸኑ በሃይማኖትም ጸንተው እንዲኖሩ እየመከሩና፡- ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናል እያሉ፥ ወደ ልስጥራን ወደ ኢቆንዮንም ወደ አንጾኪያም ተመለሱ። በየቤተ ክርስቲያኑም ሽማግሌዎችን ከሾሙላቸው በኋላ ጦመውም ከጸለዩ በኋላ፥ ላመኑበት ለጌታ አደራ ሰጡአቸው። በጲስድያም አልፈው ወደ ጵንፍልያ መጡ፥ በጴርጌንም ቃሉን ከተናገሩ በኋላ ወደ አጣልያ ወረዱ፥ ከዚያም ስለ ፈጸሙት ሥራ ለእግዚአብሔር ጸጋ አደራ ወደ ተሰጡበት ወደ አንጾኪያ በመርከብ ሄዱ። በደረሱም ጊዜ ቤተ ክርስቲያኑን ሰብስበው እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ያደረገውን ሁሉ ለአሕዛብም የሃይማኖትን ደጅ እንደ ከፈተላቸው ተናገሩ። ከደቀ መዛሙርትም ጋር አያሌ ቀን ተቀመጡ ( የሐዋ 14 ÷ 19 - 28 ) ።   ማብራሪያ በልስጥራን ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ መራመድ የማይችለው ሰው ጳውሎስ በእግርህ ቁም ሲለው ተፈውሶ ቆሞ መራመድ ስለ ቻለ በጣዖት ቤተ መቅደስ የሚያገለግለው ካህንና ሕዝቡ የሚያመልኩአቸው አማልክት መስለዋቸው መሥዋዕት ሊያቀርቡላቸው ወደው ነበር፡፡ እነ ጳውሎስ ወንጌልን ከሰበኩላቸው በኋላ እንዳይሠዉላቸው በጭንቅ አስትተዋቸዋል፡፡ አይሁድ እነጳውሎስ ወንጌል መስበካቸውን እንዳይቀጥሉ በአንጾኪያና በኢቆንዮን ስደት አድርሰውባቸው ነበር፡፡ እነጳውሎስ በልስጥራን እንዳሉ በሰሙ ጊዜ ከአንጾኪያና ከኢቆንዮን ድረስ መጡ፡፡ ጳውሎስን ወገሩት፡፡ የተዉትም የሞተ ስለ መሰላቸው ነበር፡፡ ጳውሎስ መሸሽ በተገባው ሰዓት ከበርናበስ ጋር ሆኖ ከመወገር ሸሽቶ አምልጦአል፡፡ መሸሽ ባልቻለ ሰዓት ግን ተወገረ፡፡ በሰማዕቱ እስጢፋኖስ መወገር የተስማመው ጳውሎስ ( የሐዋ 7 ÷ 54 - 60 )  እንደ እስጢፋኖስ ተወግሮ ባይሞትም ከሞት ግን ተርፎአል፡፡ የወገሩት አይሁድ ዘወር ሲሉለት ብድግ ብሎ ተነሥቶ ከበርናበስ ጋር ወደ ደርቤን ሄደ፡፡ በደርቤንም ብዙ ሰዎች ኢየሱስ ክርስቶሰን በማመን ክርስቲያን እንዲሆኑ አድርገዋል፡፡ ደርቤን በትንሹ እስያ በሊቃኦንያ አገር የነበረች ከተማ ናት ( የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ) ፡፡ ጳውሎስና በርናባስ በአይሁድ በድጋሚ ሊያደርስባቸው የሚችለውን መከራ ሳይፈሩ እንደ ገና ወደ ኋላ ወደ ልስጥራን - ኢቆንዮን - አንጾኪያ - ጴርጌን ተመለሱ፡፡ እነዚህ የገላትያ አብያተ ክርስቲያናት የተመሰረቱት በመጀመሪያው የሐዋርያው ጳውሎስ ጉዞ ነበር፡፡ ገላትያ ዛሬ ቱርክ በምትባለው አገር ያለች ናት፡፡ በየደረሱበትም ክርስቲያኖችን አንዲጸኑ እየመከሩአቸው በየቤተ ክርስቲያኑም ሽማግሌዎችን ሾመውላቸዋል፡፡ ሽማግሌዎች ሲል ቀሳውስትን ለማለት ነው፡፡ ቀሳውስት በግዕዝ ሲሆን ቀሳውስት የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ናቸው፡፡ አገልግሎታቸውንም ፈጽመው ወደ ተነሡባት ወደ ሶርያዋ አንጾኪያ ተመልሰዋል፡፡ ብዙ ሰዎች በተለይ አሕዛብ ክርስትናን እንዲቀበሉ በማድረግ ውጤታማ አገልግሎት አድርገዋል፡፡ የሐዋ ም 13ና ም 14 የሐዋርያው የጳውሎስ የመጀመሪያው ጉዞ ተብሎ ይታወቃል፡፡ በጌታችን በኢየሱስ የሚያምን ሰው ይድናል፡፡ ቅዱሳኑ ጳውሎስና በርናባስ ፡- ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናል በማለት የመከሩንን ምክር ደግሞ ሳንዘነጋ የተለያየ መከራ ቢገጥመንም መዳናችንን እስከ መጨረሻ ድረስ ልናጸና ይገባል፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሚያዝያ 18ና ሐምሌ 14 በሚቀደሰው ቅዳሴ ላይ የሐዋ 14 ÷ 19 – 28 ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌ) ፡፡ ይቀጥላል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
35
4
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
34
5
ከመታወቅ የሚያልፈው የክርስቶስ ፍቅር ፡፡ ስለዚህ ምክንያት በሰማይና በምድር ያለ አባትነት ሁሉ ከሚሰየምበት ከአብ ፊት እንበረከካለሁ፤ በመንፈሱ በውስጥ ሰውነታችሁ በኃይል እንድትጠነክሩ ክርስቶስም በልባችሁ በእምነት እንዲኖር እንደ ክብሩ ባለ ጠግነት መጠን ይስጣችሁ፤ የእናንተ ሥርና መሠረት በፍቅር ይጸና ዘንድ፥ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ስፋቱና ርዝመቱ ከፍታውም ጥልቅነቱም ምን ያህል መሆኑን ለማስተዋል፥ ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር ለማወቅ ትበረቱ ዘንድ፥ እስከ እግዚአብሔርም ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ ( ኤፌ 3 ÷ 14 - 19 )  ።   ማብራሪያ ሐዋርያው ጳውሎስ፡- ሰብኬአለሁና የእኔን ድርሻ ተወጥቻለሁ ፡፡ ቃሉን ሰምቶ ማድረግ የምዕመኑ ጉዳይ ስለ ሆነ የራሳቸው ጉዳይ የማይል መልካም መጋቢ በመሆኑ የሰበካቸውን እንዲያስተውሉ ደግሞ ሲጸልይላቸው ይታያል፡፡ እንበረከካለሁ ያለው ለዚህ ነው ፡፡ በእግዚአብሔር አብ ፊት በእስያ በምትገኘው በኤፌሶን ( ራዕይ 1 ÷ 11 )  ለሚኖሩት ለምእምናን  የጸለየው ጸሎት ፡- 1)  በልባቸው በእምነት ያኖሩት ክርስቶስ ሁልጊዜም እንዲኖር በውስጥ ሰውነታቸው እንዲጠነክሩ እግዚአብሔር ከክብሩ ባለጠግነቱ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ኃይል እንዲሰጣቸው 2)  ሥርና መሠረታቸው በፍቅር የጸና እንዲሆን 3)  የአንድን ነገር ስፋት ፣ ርዝመት ፣  ከፍታና ጥልቀት ምን ያህል እንደ ሆነ ለማወቅ እንደሚፈለግ እነርሱም የክርስቶስን ፍቅር ምን ያህል እንደ ሆነ እንዲያስተውሉ 4)   እስከ እግዚአብሔር ፍጹም ሙላት ደርሰው እንዲሞሉ 5)  ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር እንዲያውቁ ነው ፡፡ የክርስቶስ ፍቅር ከመታወቅ በላይ ነው ፡፡ ክርስቶስ ለኛ ያለውን ፍቅር ጠንቅቆ ለመረዳት ያዳግታል፡፡ ከመታወቅ በላይ ነው ፡፡ ከመታወቅ በላይ ነው ሲባል ጨርሶ ሊታወቅ የማይችል ማለት አይደለም፡፡ አወቅነው ስንል አውቀነው የማንጨርሰው ነው ፡፡ በደረስንበት ልክ እየረቀቀብን የሚሄድ ነው ፡፡ ያወቅነው ነገር ግን ከመታወቅ ደግሞ ያለፈ ነው ፡፡ ለዚህም ነው ሐዋርያው የኤፌሶን ክርስቲያኖች ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር የበለጠ ማወቅ እንዲችሉ የጸለየላቸው ፡፡ የክርስቶስን ፍቅር በቃ ይሄን ያህላል ብለን ልንወስነው አንችልም፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን !   ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
67
6
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
56
7
የሐዋርያት ሥራ ጥናት :: ክፍል 37 :: ጳውሎስና በርናባስ ወንጌል መስበካቸውና እግሩ የተፈወሰው ሰው፡፡   ከክፍል 36 ባጭሩ :: በኢቆንዮንም እንደ ቀድሞ ( ጳውሎስና በርናባስ ) ወደ አይሁድ ምኵራብ ገብተው ከአይሁድና ከግሪክ ሰዎች ብዙ እስኪያምኑ ድረስ ተናገሩ። ..የከተማውም ሕዝብ ተከፍለው እኵሌቶቹ ከአይሁድ እኵሌቶቹም ከሐዋርያት ጋር ሆኑ። አሕዛብና አይሁድ ግን ከአለቆቻቸው ጋር ሊያንገላቱአቸውና ሊወግሩአቸው ባሰቡ ጊዜ፥ አውቀው ልስጥራንና ደርቤን ወደሚባሉት ወደ ሊቃኦንያ ከተማዎች በእነርሱም ዙሪያ ወዳለው አገር ሸሹ፤ በዚያም ወንጌልን ይሰብኩ ነበር ( የሐዋ 14 ÷ 1 - 7 ) ። --------////--------   በልስጥራንም እግሩ የሰለለ፥ ከእናቱም ማኅፀን ጀምሮ አንካሳ የሆነ፥ ከቶም ሄዶ የማያውቅ አንድ ሰው ተቀምጦ ነበር። ይህም ሰው ጳውሎስ ሲናገር ይሰማ ነበር፤ እርሱም ትኵር ብሎ ተመለከተውና ይድን ዘንድ እምነት እንዳለው ባየ ጊዜ፥ በታላቅ ድምፅ፡- ቀጥ ብለህ በእግርህ ቁም አለው። ብድግ ብሎም ተንሥቶ ይመላለስ ነበር። ሕዝቡም ጳውሎስ ያደረገውን ባዩ ጊዜ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው በሊቃኦንያ ቋንቋ፡- አማልክት ሰዎችን መስለው ወደ እኛ ወርደዋል አሉ፤ በርናባስንም ድያ አሉት፤ ጳውሎስንም እርሱ በመናገር ዋና ስለ ነበረ ሄርሜን አሉት። በከተማውም ፊት ቤተ መቅደስ ያለው የድያ ካህን ኮርማዎችንና የአበባን አክሊሎች ወደ ደጃፍ አምጥቶ ከሕዝቡ ጋር ሆኖ ሊሠዋላቸው ወደደ። ሐዋርያት በርናባስና ጳውሎስ ግን ይህን በሰሙ ጊዜ ልብሳቸውን ቀደው ወደ ሕዝቡ መካከል እየጮኹ ሮጡ፥ እንዲህም አሉ። እናንተ ሰዎች፥ ይህን ስለ ምን ታደርጋላችሁ? እኛ ደግሞ እንደ እናንተ የምንሰማ ሰዎች ነን፥ ከዚህም ከንቱ ነገር ሰማይንና ምድርን ባሕርንም በእነርሱም ያለውን ሁሉ ወደ ፈጠረ ወደ ሕያው እግዚአብሔር ዘወር ትሉ ዘንድ ወንጌልን እንሰብካለን። እርሱ ( እግዚአብሔር ) ባለፉት ትውልዶች አሕዛብን ሁሉ በገዛ ራሳቸው ጐዳና ይሄዱ ዘንድ ተዋቸው። ከዚህም ሁሉ ጋር መልካም ሥራ እየሠራ፥ ከሰማይ ዝናብን ፍሬ የሚሆንበትንም ወራት ሲሰጠን፥ ልባችንንም በመብልና በደስታ ሲሞላው ራሱን ያለ ምስክር አልተወም። ይህንም ብለው እንዳይሠዉላቸው ሕዝቡን በጭንቅ አስተዉአቸው ( የሐዋ 14 ÷ 8 - 18 ) ።   ማብራሪያ ጳውሎና በርናባስ ወደ ኢቆንዮን የመጡት በጲስድያ ባለችው አንጾኪያ ወንጌልን ስለ ሰበኩ ብዙ ሕዝብ አመኑ፡፡ ያላመኑት አይሁድ ስደት ስላስነሡባቸው በትንሹ እስያ በገላትያ ጠቅላይ ግዛት ወዳለች ከተማ ወደ ኢቆንዮን መጡ፡፡ በኢቆንዮንም ግማሹን ሕዝብ በወንጌል እንዲያምን አደረጉት፡፡ ያላመኑት ክፍሎች ሊወግሩአቸው ሲሉ ከሸሹባት ከተማ አንድዋ ልስጥራን ናት፡፡ ልስጥራን በትንሹ እስያ  በሊቃኦንያ አገር የነበረች ከተማ ነበረች ( የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ) ፡፡ በልስጥራን ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ መራመድ የማይችለው ሰው ጳውሎስ፡- በእግርህ ቁም ሲለው ተፈውሶ ቆሞ መራመድ ቻለ፡፡ በከተማቸውም የጣዖት ቤተ መቅደስ ነበር፡፡ በዛ ያሉ ሰዎች ጣዖትን የሚያመልኩ ነበሩ፡፡ የተፈወሰውን ሰው ያዩ ሰዎችና በጣዖት ቤተ መቅደስ እንዲያገለግል የተሾመው ካህን ሳይቀር ለነጳውሎስ መሥዋዕትን ሊሠውላቸው ወደዱ፡፡ የሚያመልኩአቸው በስም የጠቀሱአቸው ጣዖታት ( ድያና ሄርሜን ) ሰዎችን መስለው የተገለጡ መስሎአቸው ነበር፡፡ እነ ጳውሎስ ግን ሰው እንደ ሆኑ አስረድተው እንዳይሰዉላቸው አስረዱአቸው፡፡ ከሰማይ ዝናብ እያዘነበ ከምድር የምንበላውን ፍሬ በሚሰጥ በእግዚአብሔር እንዲያምኑ ነገሩአቸው፡፡ ከዛ በፊት ግን እግዚአብሔርን ትተው ሌሎች አማልክትን ሲያመልኩ እግዚአብሔር እንደ ፈቃዳቸው እንዲሄዱ ትቶአቸው እንደ ነበርም ገልጸውላቸዋል ፡፡ ስለ ሰው ልጆች ኃጢአት ሲል ስለ ሞተው ኢየሱስ ክርስቶስ በማስተማር ወንጌልንም ሰብከውላቸዋል፡፡ እንዳይሠዉላቸው ግን ያስተዉአቸው በቀላሉ አልነበረም፡፡ ወንጌል እንደ ተፈወሰው ሰው የሥጋ ፈውስን፣ በዋነኛነት ደግሞ የነፍስ ፈውስን የሚያስገኝ ነው፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በሚያዝያ 23 በሚቀደሰው ቅዳሴ ላይ የሐዋ 14 ÷ 1 – 23 ሲነበብ ከበላይ በጥቂቱ ያብራራሁት የሐዋ 14 ÷ 8 – 18  እንደሚነበብ ለመጠቆም እወዳለሁ  ( መጽሐፈ ግጻዌ) ፡፡ ይቀጥላል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
52
8
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
53
9
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
79
10
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
57
11
የሐዋርያት ሥራ ጥናት ፡፡ ክፍል 36 ፡፡ ጳውሎስና በርናባስ ወንጌልን በመስበካቸው ያጋጣማቸው ስደት፡፡   በኢቆንዮንም እንደ ቀድሞ ወደ አይሁድ ምኵራብ ገብተው ከአይሁድና ከግሪክ ሰዎች ብዙ እስኪያምኑ ድረስ ተናገሩ። ያላመኑት አይሁድ ግን የአሕዛብን ልብ በወንድሞች ላይ አነሣሡ አስከፉም። ምልክትና ድንቅ በእጃቸው ይደረግ ዘንድ እየሰጠ ለጸጋው ቃል ስለ መሰከረው ስለ ጌታ ገልጠው እየተናገሩ ረጅም ወራት ተቀመጡ። የከተማውም ሕዝብ ተከፍለው እኵሌቶቹ ከአይሁድ እኵሌቶቹም ከሐዋርያት ጋር ሆኑ። አሕዛብና አይሁድ ግን ከአለቆቻቸው ጋር ሊያንገላቱአቸውና ሊወግሩአቸው ባሰቡ ጊዜ፥ አውቀው ልስጥራንና ደርቤን ወደሚባሉት ወደ ሊቃኦንያ ከተማዎች በእነርሱም ዙሪያ ወዳለው አገር ሸሹ፤ በዚያም ወንጌልን ይሰብኩ ነበር ( የሐዋ 14 ÷ 1 - 7 ) ።   ማብራሪያ ጳውሎና በርናባስ ወደ ኢቆንዮን የመጡት በጲስድያ ባለችው አንጾኪያ ወንጌልን በመስበካቸውና ብዙ ሕዝብ ስላመኑ አይሁድ ስደት ስላስነሡባቸው ነው፡፡ ኢቆንዮን በትንሹ እስያ በገላትያ ጠቅላይ ግዛት ያለች ከተማ ናት ( የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ) ፡፡ በኢቆንዮንም እንደ ተለመደው ወደ አይሁድ የጸሎት ቤት ምኵራብ በመግባት ብዙ ሰው እስኪያምኑ ድረስ ተናገሩ፡፡ ያመኑት ሰዎች ከአይሁድና ከግሪክ ሰዎች ነበሩ፡፡ ያላመኑት አይሁድ ጥላቻን መፍጠር ጀመሩ፡፡ ይሁን እንጂ ጳውሎና በርናባስ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ገልጠው እየተናገሩ ረጅም ወራት ነበር የተቀመጡት፡፡ ጌታም በነጳውሎስ ተአምራትና ድንቅ ነገሮች ያደርግ ነበር፡፡ ይህን ያደረገው ደግሞ የሚያስተምሩት ( የጸጋው ) ቃል ትክክለኛ መሆኑን ለማረጋገጥ ነበር፡፡ የኢቆንዮን ከተማ ሕዝብ ለሁለት ተከፈሉ፡፡ ግማሾቹ ከአይሁድ ጋር ግማሾቹ ከነጳውሎስ ጋር ተባበሩ፡፡ ያላመኑት አሕዛብ ሆኑ ያላመኑትም አይሁድ ከአለቆቻቸው ጋር ሆነው መከራ ሊያደርሱባቸውና ሊወግሩአቸው ባሰቡ ጊዜ ልስጥራንና ደርቤን ወደሚባሉት የሊቃኦንያ ከተማዎችና በዙሪያቸውም ወዳሉት አገር ሸሹ፡፡ በደረሱበትም አገር የምሥራቹን ቃል ( ወንጌልን ) ይሰብኩ ነበር እንጂ መከራ ይደርስብናል ብለው ወንጌልን ከመስበክ አልተቆጠቡም፡፡ ሸሹ የሚለው ቃል የሚያስተምረን ነገር አለው፡፡ ዝም ብሎ መከራ መቀበልም አይገባም ፡፡ መሸሽ ከተቻለ መሸሽ አለብን እንጂ መሸሽ እየቻልን መከራ በመቀበል አላስፈላጊ ዋጋ መክፈል የለብንም፡፡ ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን መሞቱና መቀበሩ ከሙታንም መነሣቱ ሁሌም መነገርና መሰበክ አለበት፡፡ ስለ ኃጢአታችን ሲል የሞተልንን የክርስቶስን ፍቅር ስናስታውስ በክርስትና ሕይወታችን እንበረታለን፡፡ እርሱ ስለኛ ኃጢአት ባይሞትልን ማን ነበር የሚሞትልን? ለሞተልን ከኃጢአታችንም በደሙ ላጠበን ምስጋና ይሁን ፡፡ አሜን! የሐዋ 14 ÷ 1 – 7 በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሰኔ 24 በሚቀደሰው ቅዳሴ ላይ የሚነበብ ነው ( መጽሐፈ ግጻዌ) ፡፡ ይቀጥላል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
53
12
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
58
13
አምሮ ያየነው ሁሉ መጨረሻው ያማረ አይደለም፡፡ አብራምም በከብት በብርና በወርቅ እጅግ በለጠገ። … ሎጥ ደግሞ የላምና የበግ መንጋ ድንኳንም ነበረው። በአንድነትም ይቀመጡ ዘንድ ምድር አልበቃቸውም  የነበራቸው እጅግ ነበረና በአንድነት ሊቀመጡ አልቻሉም። የአብራምንና የሎጥን መንጎች በሚጠብቁት መካከልም ጠብ ሆነ… አብራምም ሎጥን አለው። እኛ ወንድማማች ነንና በእኔና በአንተ በእረኞቼና በእረኞችህ መካከል ጠብ እንዳይሆን እለምንሃለሁ። ምድር ሁሉ በፊትህ አይደለችምን? ከእኔ ትለይ ዘንድ እለምንሃለሁ፤ አንተ ግራውን ብትወስድ እኔ ወደ ቀኝ እሄዳለሁ፤ አንተም ቀኙን ብትወስድ እኔ ወደ ግራ እሄዳለሁ። ሎጥም ዓይኑን አነሣ፥ በዮርዳኖስ ዙሪያ ያለውንም አገር ሁሉ ውኃ የሞላበት መሆኑን አየ፤ እግዚአብሔር ሰዶምንና   ገሞራን ከማጥፋቱ አስቀድሞ… እንደ እግዚአብሔር ገነት በግብፅ ምድር አምሳል ነበረ። ሎጥም በዮርዳኖስ ዙሪያ ያለውን አገር ሁሉ መረጠ፤ ሎጥም ወደ ምሥራቅ ተጓዘ፤ አንዱም ከሌላው እርስ በርሳቸው ተለያዩ። ዘፍጥ 13 ና 19 ማብራሪያ ወንድሜ ብሎ ቢጠራውም  አብርሃም ለሎጥ አጎት ነው፡፡ በእረኞቻቸው መካከል ጠብ ተፈጥሮ ጠቡ አብርሃምንና ሎጥንም ጭምር ሊያጣላ  ስለሚችል አብርሃም አንድ ዘዴ አመጣ፡፡ ለሎጥ ቅድሚያ ዕድሉን በመስጠት የፈለገውን ስፍራ እንዲመጥ ነገረው፡፡ ሎጥ ሲያየው ያማረ የመሰለውን አብርሃም ሳይወስድበት መረጠ፡፡ በጊዜው እንደ እግዚአብሔር ገነት ነበር፡፡ ስፍራው ሰዶምና ገሞራ ይባላል፡፡ ሎጥ ሰዶምና ገሞራን መረጠና ከአብርሃም ጋር በሰላም ተለያዩ፡፡  ከተወሰነ ዓመት በኋላ የሰዶምና ገሞራ ሰዎች እግዚአብሔርን በመበደላቸው እግዚአብሔር ከሰማይ እሳት አዝንቦ ሰዶምና ገሞራን አጠፋት፡፡ ሎጥ ያማረ ምድር የመረጠ ቢመስለውም ምርጫው ግን ትከክል አልነበረም፡፡ መልካም ምድር የመረጠ ቢመስለውም የሚቃጠል ምድር ማለት ለእሳት አልፎ የተሰጠ ምድር ነበር የመረጠው፡፡ እኛ ስንመርጥ ስናየው ያማረ ከሆነ መጨረሻው ያማረ ይመስለናል፡፡ ምርጫችንን እግዚአብሔር ካልመረጠልን ያማረ የመሰለን ነገር መጨረሻው ያማረ ላይሆን ይችላል፡፡ እኛ የአንድ ነገርን የመጀመሪያን ማማር ልናውቅ እንችላለን፤ መጨረሻው ግን የከፋ ቢሆን እንኳን የማወቅ ችሎታ የለንም፡፡ አንዳንዴ የሚገርመው እግዚአብሔር ለምን ይህን አይሰጠኝም ብለን ሳይሰጠን ሲቀር ከእግዚአብሔር ጋር የተጣላንበት ነገር ሳይቀር የማይጠቅመንን ነው፡፡ እርሱ ደግሞ ለልጆቹ የሚጠቅመውን ስለሚያስብ የማይጠቅመንን አንዴት ይስጠን? እርሱ እኮ ደህና ያልሆነውን ነገር ደህና አስመስሎ አታሎ እንደሚሸጥ ነጋዴ አይደለም፡፡ ምርጫችንን ስለወደድነው ብቻ ሳይሆን መልካም መሆኑንም ለማወቅ የእግዚአብሔርን ፈቃድ መጠየቅ ተገቢ ነው፡፡ አንድ ሰው ቤት ሲገዛ የሚያምር ስለሆነ አይገዛም፡፡ ስላማረው ብቻ ቢገዛ ነገ ያ ቤት በመንገድ መክንያት ፈራሽ ቢሆን ገዢው ተጎጂ  ይሆናል፡፡ ስለዚህ ማንም ሰው ቤቱንና አካባቢውን ለመግዛት ቢወደውም የሚመለከተው የመንግሥት ተቋም ጋር በመሄድ ስለ ቦታው ያጣራል፡፡ እኛም በሕይወታችን ላይ ውሳኔ ካማሳላፋችን በፊት ወደ እግዚአብሔር በመቅረብ ስለ ጉዳዩ መጠየቅ ይኖርብናል፡፡ ለእግዚአብሔር የነገሩት ነገር ምንግዜም መፍትሔ አለው፤ ከመክሰር እንድናለን፡፡ ስናየው ያማረ እንኳን ቢመስለን ለእግዚአብፈሔር ማማከሩ የተሸለ ነው፡፡ አይተነው አምሮን የገዛነውልብስ ወዲያ ቀለሞ ሲለቅ አጋጥሞናል፡፡ በተለይ በትዳር ጉዳይ አብዝተን እግዚአብሔርን ብንጠይቅና የእርሱን ፈቃድ አውቀን ብንገባ ይሻላል፡፡ የገዛነው ልብስ ቀለሙ የሚለቅ ቢሆን ገንዘባችንን ይጭነቀው እንጂ ሌላ ልብስ መግዛት የቻላል፡፡ እንደ ትዳርና ሌሎች ነገሮች በሕይወታችን ላይ ምስቅልቅል ለሚፈጥሩ ጉዳዮች እግዚአብሔርን ማማከር ተገቢ ነው፡፡ ፈጥነን ወስነን ሊጎዳን ከሚችል ውሳኔ በመቆጠብ እግዚአብሔርን አማክረን ዘግይተን ቢሰጠን ይሻላል፡፡ ቀስ ብለው ያሽከርክሩ ማለት ይሄ አይመስላችሁም፡፡ ተቻኩለው የነዱት መኪናና ቸኩለው የወሰኑት ውሳኔ ዋጋ ማስከፈሉ የማይቀር ነው፡፡ ኪሳችሁን ተጠንቀቁ እንደሚባለው ስለ ውሳኔአችንም  “ ጠንቀቅ ይበሉ” የሚል ትልቅ መልዕክት የያዘ ትምህርት ነው የዛሬው፡፡ ሁሌም እንዲመርጥልን ምርጫችንን ለእግዚአብሔር ብንተውለት ይሻላል፡፡ እግዚአብሔር የመረጠልን ብቻ ነው መጨረሻውም ያማረ የሚሆነው፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
72
14
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
57
15
የሐዋርያት ሥራ ጥናት :: ክፍል 35 :: የከተማው ሰው ሁሉ የእግዚአብሔርን ቃል ይሰሙ ዘንድ እንደ ተሰበሰቡ፡፡   ከክፍል 34 ባጭሩ :: ..እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፥ በእርሱ በኩል የኃጢአት ስርየት እንዲነገርላችሁ፥ በሙሴም ሕግ ትጸድቁበት ዘንድ ከማይቻላችሁ ሁሉ ያመነ ሁሉ በእርሱ እንዲጸድቅ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን ( የሐዋ 13 ÷ 24 - 43 ) ። ----////-----   በሁለተኛውም ሰንበት ከጥቂቶቹ በቀር የከተማው ሰው ሁሉ የእግዚአብሔርን ቃል ይሰሙ ዘንድ ተሰበሰቡ። አይሁድም ብዙ ሕዝብ ባዩ ጊዜ ቅንዓት ሞላባቸው፥ እየተሳደቡም ጳውሎስ የተናገረውን ቃል ተቃወሙ። ጳውሎስና በርናባስም ገልጠው፡- የእግዚአብሔር ቃል አስቀድሞ ለእናንተ ይነገር ዘንድ ያስፈልጋል፤ ከገፋችሁትና የዘላለም ሕይወት እንዳይገባችሁ በራሳችሁ ከፈረዳችሁ ግን፥ እነሆ፥ ወደ አሕዛብ ዘወር እንላለን። እንዲሁ ጌታ፡- እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ለማዳን ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ ብርሃን አድርጌሃለሁ ብሎ አዞናልና አሉ። አሕዛብም ሰምተው ደስ አላቸው የእግዚአብሔርንም ቃል አከበሩ፥ ለዘላለም ሕይወትም የተዘጋጁ ሁሉ አመኑ፤ የጌታም ቃል በአገሩ ሁሉ ተስፋፋ። አይሁድ ግን የሚያመልኩትን የከበሩትንም ሴቶችና የከተማውን መኳንንት አወኩ፥ በጳውሎስና በበርናባስም ላይ ስደትን አስነሥተው ከአገራቸው አወጡአቸው። እነርሱ ግን የእግራቸውን ትቢያ አራግፈውባቸው ወደ ኢቆንዮን መጡ። በደቀ መዛሙርትም ደስታና መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው ( የሐዋ 13 ÷ 44 - 52 ) ።   ማብራሪያ ጳውሎስ አስተምሮ ሲጨርስ ሕዝቡ እነ ጳውሎስ በሚመጣው ሳምንት እንዲያስተምሩአቸው ቀጠሮ ይዘው ተለያይተው ነበር፡፡ በሳምንቱ በቀጠሮው ቀን የከተማው ሰው ሁሉ ግልብጥ ብሎ መጣ ፡፡ የቀረ ሰው ቢኖር ጥቂት ሰው ብቻ ነበር፡፡ ብዙ ሕዝብ ስለ ተሰበሰበ አይሁድ ቀንተው ጳውሎስ ስለ ክርስቶስ ገልጦ የሚያስተምረውን ቃል መቃወም ጀመሩ፡፡ አይሁድ እነ ጳውሎስ የሚሰብኩትን ክርስቶስን በማመን የዘላለም ሕይወት ማግኘት ሲገባቸው ስብከታቸውን ስለ ገፉ የዘላላም ሕይወት እንዳይገባቸው በራሳቸው ላይ ፈረዱ፡፡ ለአሕዛብ ብርሃን አድርጌሃለሁ የሚለውን በትንቢት የተነገረውን ( ኢሳ 49 ÷ 6 ) ቃል ጠቅሰው እናንተ አይሁድ የማትሰሙን ከሆነ አሕዛብን እናስተምራለን ሲሉ አሕዛብ ደስ ተሰኙ፡፡ እነ ጳወሎስ ለአሕዛብ የመዳንን ቃል በመስበክ ብርሃን እንደሚሆኑ ከትንቢተ ኢሳይያስ የጠቀሱትን ከአንደበታቸው ሰምተዋልና፡፡ አሕዛብ የሰሙትን የእግዚአብሔር ቃል አክብረው በመቀበላቸውና የዘላለምን ሕይወት እንዲያገኙ ፈልገው ሞቶ በተሰቀለው ከሙታንም በተነሣው በኢየሱስ አመኑ፡፡ አይሁድ ቢቃወሙም ወንጌል ግን የጲስድያ በሆነችው በአንጾኪያ አገር ተስፋፋ፡፡ ተቃወሚዎቹ አይሁድ እነጳውሎስን ላይ ስደት ስላስነሡባቸውና ከአገራቸው እንዲወጡ ስላስደረጉአቸው ወደ ኢቆንዮን ሄዱ፡፡ ባመኑት ደቀ መዛሙርት ላይ ግን ደስታና መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፡፡ የጌታችን የኢየሱስ ወንጌል ደስታ ይሰጣል፡፡ ወንጌሉን በምናምነው ላይ ደስታ ብቻ ሳይሆን መንፈስ ቅዱስም ይሞላብናል ( ያድርብናል) ፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ቅዳሴ ሲቀደስ ከበላይ ከጠቀስኩት ክፍል በሌሎች ቀናትና በሚያዝያ 8 ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌ ) ፡፡ ይቀጥላል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
67
16
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
60
17
የጸሎታችን መልስ ቢዘገይም በትዕግስት ብንጠብቅ እግዚአብሔር እጅግ የሚያስደስት ነገር ይሰጠናል ፡፡   ..ዘካርያስ የሚባል አንድ ካህን ነበረ፤ ሚስቱም ከአሮን ልጆች ነበረች፥ ስምዋም ኤልሳቤጥ ነበረ። ሁለቱም በጌታ ትእዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ። ኤልሳቤጥም መካን ነበረችና ልጅ አልነበራቸውም፤ ሁለቱም በዕድሜያቸው አርጅተው ነበር። ..በእግዚአብሔር ፊት ሲያገለግል፥ .. ሕዝቡ ሁሉ በውጭ ቆመው ይጸልዩ ነበር። የጌታም መልአክ ..ታየው። ዘካርያስም ባየው ጊዜ ደነገጠ፥ ፍርሃትም ወደቀበት። መልአኩም እንዲህ አለው። ዘካርያስ ሆይ፥ ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ። ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል። በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል.. ዘካርያስም መልአኩን፡- እኔ ሽማግሌ ነኝ ምስቴም በዕድሜዋ አርጅታለችና ይህን በምን አውቃለሁ? አለው። መልአኩም መልሶ፡- እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፥ እንድናገርህም ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር፤ እነሆም፥ በጊዜው የሚፈጸመውን ቃሌን ስላላመንህ፥ ይህ ነገር እስከሚሆን ቀን ድረስ ዲዳ ትሆናለህ መናገርም አትችልም አለው። ሕዝቡም ዘካርያስን ይጠብቁት ነበር፤ በቤተ መቅደስም ውስጥ ስለ ዘገየ ይደነቁ ነበር። በወጣም ጊዜ ሊነግራቸው አልቻለም፥ በቤተ መቅደስም ራእይ እንዳየ አስተዋሉ፤ እርሱም ይጠቅሳቸው ነበር፤ ድዳም ሆኖ ኖረ። የማገልገሉም ወራት ሲፈጸም ወደ ቤቱ ሄደ። ከዚህም ወራት በኋላ ሚስቱ ኤልሳቤጥ ፀነሰችና፡- ነቀፌታዬን ከሰው መካከል ያስወግድልኝ ዘንድ ጌታ በተመለከተበት ወራት እንዲህ አድርጎልኛል ስትል ራስዋን አምስት ወር ሰወረች። ..በስድስተኛውም ወር መልአኩ ገብርኤል ..ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ፥ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ። ..መልአኩም እንዲህ አላት፡- ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻልና አትፍሪ። እነሆም፥ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፥ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ። .. እነሆም ዘመድሽ ኤልሳቤጥ፥ እርስዋ ደግሞ በእርጅናዋ ወንድ ልጅ ፀንሳለች፥ ለእርስዋም መካን ትባል ለነበረችው ይህ ስድስተኛ ወር ነው፤ ማርያምም በዚያ ወራት ..ወደ ይሁዳ ከተማ ፈጥና ወጣች፥ ወደ ዘካርያስም ቤት ገብታ ኤልሳቤጥን ተሳለመቻት። ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ፤ በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ ሞላባት፥ በታላቅ ድምፅም ጮኻ እንዲህ አለች። አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፥ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው። የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል? እነሆ፥ የሰላምታሽ ድምጽ በጆሮዬ በመጣ ጊዜ ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሎአልና። ከጌታ፤ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብፅዕት ናት። ..ማርያምም ሦስት ወር የሚያህል በእርስዋ ዘንድ ተቀመጠች ወደ ቤትዋም ተመለሰች። የኤልሳቤጥም የመውለጃዋ ጊዜ ደረሰ፥ ወንድ ልጅም ወለደች። ጎረቤቶችዋም ዘመዶችዋም ጌታ ምሕረቱን እንዳገነነላት ሰምተው ከእርስዋ ጋር ደስ አላቸው። ..በአባቱም ስም ዘካርያስ ሊሉት ወደዱ። እናቱ ግን መልሳ፡- አይሆንም፥ ዮሐንስ ይባል እንጂ አለች። እነርሱም፡- ከወገንሽ ማንም በዚህ ስም የተጠራ የለም አሉአት። አባቱንም ማን ሊባል እንዲወድ ጠቀሱት። ብራናም ለምኖ፡- ስሙ ዮሐንስ ነው ብሎ ጻፈ። ሁሉም አደነቁ። ያንጊዜም አፉ ተከፈተ መላሱም ተፈታ እግዚአብሔርንም እየባረከ ተናገረ። ለጎረቤቶቻቸውም ሁሉ ፍርሃት ሆነ፤ ይህም ሁሉ ነገር በይሁዳ በተራራማው አገር ሁሉ ተወራ፤ የሰሙትም ሁሉ፡- እንኪያ ይህ ሕፃን ምን ይሆን? እያሉ በልባቸው አኖሩት፤ የጌታ እጅ ከእርሱ ጋር ነበረችና ( ሉቃ 1 ÷ 5 - 66) ፡፡   ማብራሪያ ካህኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ባልና ሚስት ሲሆኑ በእግዚአብሔር ሕግ የሚሄዱ ደጋግ ሰዎች ነበሩ፡፡ በዘመናቸው እግዚአብሔር ልጅ እንዲሰጣቸው ቢለምኑም ልጅ አልነበራቸው፡፡ ካህኑ ዘካርያስ በቤተ መቅደስ እያገለገለ እያለ መልአኩ ገብርኤል ተገልጦ ፡- ጸሎትህ ተሰምቶአል ፤ ሚስትህ ኤልሳቤጥ ልጅ ተወልዳለች አለው፡፡ ዘካርያስ እርሱም ሚስቱም አርጅተው ስለ ነበሩ መልአኩ፡- ልጅ ትወልዳለህ ያለውን ምሥራች በመጠራጠሩ ልጁ እስኪወለድ ድረስ ዲዳ እንደሚሆን ነገረው፡፡ ዘካርያስም ዲዳ ሆኖ ወደ ሚስቱ ተመለሰ፡፡ ከስድስት ወር በኋላ መልአኩ ገብርኤል ወደ ድንግል ማርያም ተልኮ ጌታችን ኢየሱስን እንደምትወልድ አበሠራት፡፡ ዘመድዋ ኤልሳቤጥም በእርጅናዋ ልጅ እንደ ፀነሰች ስለ ነገራት ማርያም ወደ ዘመድዋ ኤልሳቤጥ ሄደች፡፡ ቅድስት ማርያም ኤልሳቤጥን ባየቻት ጊዜ ተሳለመቻት፡፡ ድንግል ማርያም ኤልሳቤጥን ሰላም ስትላት ፅንሱ ዮሐንስ በደስታ ዘለለ፡፡ ኤልሳቤጥ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልታ ማርያምን ፡- የጌታዬ እናት በማለት ጠራቻት ፡፡ ለኤልሳቤጥ ድንግል ማርያም ጌታን እንደ ፀነሰች በመንፈስ ቅዱስ ተገለጠላት፡፡ ድንግል ማርያም በዘመድዋ ኤልሳቤጥ ሦስት ወር ከቆየች በኋላ ወደ ቤትዋ ተመለሰች፡፡ ኤልሳቤጥ ልጅዋን ስትወልድ፡- ስሙ ዮሐንስ ይባል ስትል የሚያውቁአት አልተስማሙም ነበር፡፡ ዘካርያስ በምልክት ሲጠየቅ በጽሑፍ፡- ዮሐንስ ብሎ ጻፈ፡፡ ሁሉም ተደነቁ፡፡ ዘካርያስ መላሱ ተፈታና ዲዳ መሆኑ ቀረ፡፡ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ በእግዚአብሔር ሕግ መሰረት የሚጓዙ ቢሆኑም ልጅ እንዲሰጣቸው ለምነው እግዚአብሔር ባይሰጣቸውም እግዚአብሔርን በማመን የጸኑ ነበሩ፡፡ መውለድ በማይችሉበት ዕድሜ ልጅ እንዲያገኙ ደግሞ እግዚአብሔር አድርጎአቸዋል፡፡ ለእነርሱ የዘገየው ጸሎት ስሙ በመልአክ የወጣና ጌታችን ኢየሱስን ያጠመቀ የተባረከ ልጅ እንዲሰጣቸው አስደርጎአል፡፡ እግዚአብሔርን ጠይቀነው የጸሎታችን መልስ ቢዘገይም በትዕግስት እንደነ ዘካርያስ ብንጠብቅ እግዚአብሔር በእርሱ ጊዜ እጅግ የሚያስደስት ነገር ይሰጠናል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን !  ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
79
18
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
66
19
የሐዋርያት ሥራ ጥናት :: ክፍል 34 :: ጳውሎስ በመጀመሪያ ጉዞው ስለ ክርስቶስ ሰፋ ባለመልኩ ያስተማረው ከባለፈው የቀጠለ ትምህርት፡፡   ከክፍል 33 ባጭሩ ፡፡ ..ዳዊትን ..እንዲነግሥ አስነሣው፥ ሲመሰክርለትም፡- እንደ ልቤ የሆነ ሰው ፈቃዴንም ሁሉ የሚያደርግ ..ዳዊትን አገኘሁ አለ። ከዚህም ሰው ዘር እግዚአብሔር እንደ ተስፋው ቃል ለእስራኤል መድኃኒትን እርሱም ኢየሱስን አመጣ ( የሐዋ 13 ÷ 13 - 23 ) ። ----////-----   ከመምጣቱ በፊት ዮሐንስ አስቀድሞ ለእስራኤል ሕዝብ ሁሉ የንስሐን ጥምቀት ሰብኮ ነበር።  ዮሐንስም ሩጫውን ሲፈጽም ሳለ፡- እኔ ማን እንደ ሆንሁ ታስባላችሁ? እኔስ እርሱን አይደለሁም፤ ነገር ግን እነሆ፥ የእግሩን ጫማ እፈታ ዘንድ ከማይገባኝ ከእኔ በኋላ ይመጣል ይል ነበር። እናንተ ወንድሞቻችን፥ የአብርሃም ዘር ልጆች ከእናንተ መካከልም እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሆይ፥ ለእናንተ የዚህ የመዳን ቃል ተላከ። በኢየሩሳሌም የሚኖሩ ሰዎችና አለቆቻቸው እርሱንና በየሰንበቱ የሚነበቡትን  ስላላወቁ በፍርዳቸው ፈጽመዋልና፤ ለሞትም የሚያደርስ ምክንያት አንድ ስንኳ ባያገኙበት፥ ይገድለው ዘንድ ጲላጦስን ለመኑት፤ ስለ እርሱም የተጻፈውን ሁሉ በፈጸሙ ጊዜ ከእንጨት አውርደው በመቃብር አኖሩት። እግዚአብሔር ግን ከሙታን አስነሣው፤ በሕዝብም ዘንድ ምስክሮቹ ለሆኑት ከእርሱ ጋር ከገሊላ ወደ ኢየሩሳሌም ለወጡት ብዙ ቀን ታያቸው። እኛም ለአባቶች የተሰጠውን ተስፋ የምስራቹን ለእናንተ እንሰብካለን፤ ይህን ተስፋ እግዚአብሔር በሁለተኛው መዝሙር ደግሞ፡- አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ ወለድሁህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ኢየሱስን አስነሥቶ ለእኛ ለልጆቻቸው ፈጽሞአልና። እንደገናም ወደ መበስበስ እንዳይመለስ ከሙታን እንደ አስነሣው፥ እንዲህ፡- የታመነውን የዳዊትን ቅዱስ ተስፋ እሰጣችኋለሁ ብሎአል። ደግሞ በሌላ ስፍራ፡- ቅዱስህን መበስበስን ያይ ዘንድ አትሰጠውም ይላልና። ዳዊትም በራሱ ዘመን የእግዚአብሔርን አሳብ ካገለገለ በኋላ አንቀላፋ፥ ከአባቶቹም ጋር ተጨምሮ መበስበስን አየ፤ ይህ እግዚአብሔር ያስነሣው ግን መበስበስን አላየም። እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፥ በእርሱ በኩል የኃጢአት ስርየት እንዲነገርላችሁ፥ በሙሴም ሕግ ትጸድቁበት ዘንድ ከማይቻላችሁ ሁሉ ያመነ ሁሉ በእርሱ እንዲጸድቅ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን። እንግዲህ እናንተ የምትንቁ፥ እዩ ተደነቁም ጥፉም አንድ ስንኳ ቢተርክላችሁ የማታምኑትን ሥራ በዘመናችሁ እኔ እሠራለሁና ተብሎ በነቢያት የተነገረው እንዳይደርስባችሁ ተጠንቀቁ። በወጡም ጊዜ ይህን ነገር በሚመጣው ሰንበት ይነግሩአቸው ዘንድ ለመኑአቸው። ጉባኤውም ከተፈታ በኋላ ከአይሁድና ወደ ይሁዲነት ገብተው ከሚያመልኩ ብዙዎች ጳውሎስንና በርናባስን ተከተሉአቸው፥ እነርሱም ሲነግሩአቸው በእግዚአብሔር ጸጋ ጸንተው እንዲኖሩ አስረዱአቸው ( የሐዋ 13 ÷ 24 - 43 ) ።   ማብራሪያ ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ክርስቶስ በብዙ ምስክርነት ነው ያስተማረው፡፡ ü  መጥምቁ ዮሐንስ ስለ ክርስቶስ፡- የእግሩን ጫማ እፈታ ዘንድ የማይገባኝ ነኝ ብሎ ነበር፡፡ ü  ጳውሎስ፡- ለእናንተ የመዳን ቃል ተላከ ባለው ንግግሩ ኢየሱስ ክርስቶስ የመጣው የሰው ልጆችን ለማዳን እንደ ሆነ አስረዳ፡፡ ü  በነቢያት ትንቢት የተነገረለት ቢሆንም አይሁድ ግን የነቢያትን ድምፅ መስማት ትተው እንደ ሰቀሉት አወሳ፡፡ ስለ እርሱም የተጻፈውን ሁሉ በፈጸሙ ጊዜ ማለቱም በትንቢት ስለ መሞቱም ቀድሞ የተነገረ መሆኑን ነው፡፡ ü  ቢሰቀልም ከሙታን ስለ መነሣቱን መሰከረ፡፡ ምስክሮቹ ላላቸው ለሐዋርያትም እንደታያቸው አስገነዘበ፡፡ ü  ክርስቶስ ለቀደሙት አባቶች ተስፋ የተሰጠ በመሆኑ የምሥራቹን እንሰብካለን በማለት የክርስቶስን የማዳን ሥራን መናገር ምሥራች እንደ ሆነ ተናገረ አበሰረ፡፡ ü  በመዝሙር ም. 2 አንተ ልጄ ነህ ተብሎ የተነገረው ስለ ኢየሱስ መሆኑን አብራራ ( አብ ወልድን ነው አንተ ልጄ ነሀ ያለው ) ፡፡ ü  በመዝሙር ( ም. 15 )፡- ቅዱስን መበስበስበስን ያይ ዘንድ አትሰጠውም የተባለው ክርስቶስ ሞቶ ቢቀበርም ሥጋው መበስበስን እንዳላገኘውና ከሞት እንደ ተነሣ ለማስረዳት ዳዊት ስለ ክርስቶስ የተናገረው እንደ ሆነና ዳዊት ግን ሞቶ ሥጋው የበሰበሰ ስለመሆኑ ጠቆመ፡፡ ü  በሙሴ ሕግ መጽደቅ እንደማይቻልና በክርስቶስ ያመነ ግን የኃጢአት ስርየት ስለሚያገኝ እንደሚጸድቅ አስረዳ፡፡ ጳውሎስ አስተምሮ ሲጨርስ ሕዝቡ እነ ጳውሎስ በሚመጣው ሳምንት እንዲያስተምሩአቸው ቀጠሮ ይዘው ተለያዩ፡፡ ብዙዎችም ትምህርታቸውን ስለ ተቀበሉ ጳውሎስና በርናባስ ሕዝቡን በእግዚአብሔር ጸጋ ጸንተው እንዲኖሩ መከሩአቸው፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በየካቲት 30ና በሰኔ 2 ቅዳሴ ሲቀደስ ከበላይ ከጠቀስኩት ክፍል ከፊሉ ከቁ. 24 - ቁ. 32  ያለው ሲነበብ ከቁ. 30 - ቁ. 43 ያለው ደግሞ በታኅሳስ 23 ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌ ) ፡፡ ይቀጥላል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
66
20
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ሰባኬ ወንጌል ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል  ማግኘት ትችላላችሁ https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w ▶️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/EMaweq ▶️ ፌስቡክ fb.me/yeglie
50