እግዚአብሔርን ማወቅ
前往频道在 Telegram
ሰላምታ በተለዋወጥን ቁጥር ይመስገን ስለምንለው አምላካችንና አባታችን እግዚአብሔር ያለንን ዕውቀት ለማዳበር የሚያግዝ ቻነል ነው፡፡
显示更多962
订阅者
无数据24 小时
+27 天
+2430 天
数据加载中...
吸引订阅者
九月 '26
九月 '26
+1
在0个频道中
八月 '26
+42
在0个频道中
Get PRO
七月 '26
+33
在0个频道中
Get PRO
六月 '26
+43
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+31
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+45
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+33
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+49
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+45
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+54
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+38
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+37
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+31
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+32
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+45
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+49
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+24
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+19
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+18
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+11
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+9
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+19
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+25
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+27
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+17
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+20
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+35
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+21
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+23
在0个频道中
Get PRO
四月 '24
+12
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+31
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+11
在0个频道中
Get PRO
一月 '24
+15
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+15
在0个频道中
Get PRO
十一月 '23
+12
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+13
在0个频道中
Get PRO
九月 '23
+479
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 03 九月 | 0 | |||
| 02 九月 | +1 | |||
| 01 九月 | 0 |
频道帖子
አማኑኤል ተስፋ በታጣ ሰዓት ከጎናችን የሚቆም ነው፡፡
እግዚአብሔርም ደግሞ ተናገረኝ እንዲህም አለኝ።
ይህ ሕዝብ በቀስታ የሚሄደውን የሰሊሆምን ውኃ ጠልቶአልና፥ ረአሶንንና የሮሜልዩንም ልጅ ወዶአልና ስለዚህ፥
እነሆ፥ እግዚአብሔር ብርቱና ብዙ የሆነውን የወንዝ ውኃ፥ የአሦርን ንጉሥና ክብሩን ሁሉ፥ ያመጣባቸዋል፤ መስኖውንም ሁሉ ሞልቶ ይወጣል፥ በዳሩም ሁሉ ላይ ይፈስሳል፤
እየጐረፈም ወደ ይሁዳ ይገባል፤ እያጥለቀለቀም ያልፋል፥ እስከ አንገትም ይደርሳል፤ አማኑኤል ሆይ፥ የክንፉ መዘርጋት የአገርህን ስፋት ትሞላለች ( ኢሳ 8 ÷ 5 - 8 ) ።
ማብራሪያ
እግዚአብሔር ተናገረኝ እንዲህም አለኝ የሚለው ነቢዩ ኢሳይያስ ነው፡፡ ረአሶን የሶርያ ንጉሥ ነው፡፡ የሮሜልዩ ልጅ የተባለው ደግሞ የእስራኤል ንጉሥ ነው፡፡ በዚህ ሰዓት እስራኤል ለሁለት የተከፈለችበት ጊዜ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ለሁለት ከቅርብ ዓመታት በፊት ኢትዮጵያና ኤርትራ ተብላ እንደተከፈለች እስራኤልም እንዲሁ እስራኤልና ይሁዳ ተብላ ለሁለት ተከፍላ ነበር፡፡
እስራኤል ሰሜናዊው ክፍል ሲሆን ይሁዳ ደቡባዊው ክፍል ነው፡፡ ለሁለትም ከተከፈሉ በኋላ ብዙ ጊዜ ውጊያ አድርገዋል፡፡ ኢትዮጵያና ኤርትራ ከተከፈሉ በኋላ እንደ ተዋጉት፡፡
የይሁዳ ንጉሥና ሕዝቡ በምንጭ ውኃ ( በሰሊሆም ምንጭ ውኃ ) የተመሰለውን እግዚአብሔርን ትተው በእስራኤልና በሶርያ ንጉሥ ተስፋ አድርገው ነበር፡፡
በእስራኤልና በሶርይ ንጉሥ ቢታመኑም ሁለቱም ነገሥታት ሊቋቋሙት የማይችሉትን ሌላ የአሦርን ንጉሠ ነገሥት እንደሚያመጣባቸው እግዚአብሔር ተናገረ፡፡ አመጣጡ ደግሞ ወንዝ ሞልቶ ዳርቻን ሁሉ በሚያጥለቀልቅና እየጎረፈ ሲመጣ ያገኘውን በመጠራረግ ሁሉን ነገር ከመሸፈን አልፎ ሙላቱ እስከ አንገት በሚደርስ መልኩ ነው፡፡
ንጉሠ ነገሥቱ አደጋ ለመጣል በዚህ መልኩ ቢመጣም እግዚአብሔር ግን ለይሁዳ ሕዝብ መልሶ እንደሚራራ ሲነግረን ኢሳይያስ እንዲህ ይላል፡፡
አማኑኤል ሆይ፥ የክንፉ መዘርጋት የአገርህን ስፋት ትሞላለች።
አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከኛ ጋር ማለት ነው፡፡
ኢሳይያስ የይሁዳ ሕዝብ እንዲጠፉ እግዚአብሔር ዝም እንደማይልና በጭንቃቸውም ሰዓት ተመልሶ ተስፋ እንደሚሆናቸው ይገልጻል፡፡ እነርሱ እግዚአብሔርን ተስፋ ማድረግ ትተው ሳሉ እርሱ ግን ዶሮ ጫጩቶቿን በክንፎቿ ሰውራ እንደምትጠብቅ ምድሪቱንም በተዘረጉት ክንፎቹ ከዳር እስከ ዳር እንደሚሸፍን ያስታውቃቸዋል፡፡
አማኑኤል አምላካችን የጭንቅ ቀን ደራሻችን ነው፡፡ ዙሪያው ጨለማ ሲሆንብን ፡- አለሁ የሚለን አጽናኛችን ነው፡፡ ድቅድቅ ጨለማ ሆኖ ምንም ብርሃን የሚባል በሌለበት ሰዓት ብርሃን ሆኖ ለሕይወታችን ተስፋ የሚፈነጥቅልን ነው፡፡
አንድ ሰው በውኃ ውስጥ ቢገባና ውኃው እስከ አንገቱ ደርሶ ስናይ እንደሚያስጨንቅ በሕይወታችን ነገሮች ልክ እንደዚህ ሆነው ቢታዩንም አማኑኤል አለልን፡፡ እስከ አንገታችን ይሸፍኑን እንጂ አያሰምጡንም፡፡
ነገሮቻችን የቱንም ያህል ጣራ ቢነኩ በአማኑኤል አምላካችን ጣቶች ሲዳሰሱ ይሟሽሻሉ፤ ይከስማሉም፡፡
እየበረረ በማምለጡ ማንም ስለማይደርስበትና እንኳን ሊያዝ ያየቱ ሁሉ ነፍሳቸውን ለማዳን መንገድ ስለሚለቁለት ሽምጥ በመጋለቡ በሬው የእነርሱ ስለ መሆኑ ተስፋቸውን እንጠፍጥፈው እርማቸውን ሰዎች ቢያወጡም ለአማኑኤል ግን ልክ እንደዚህ ተስፋችንን ያንጠፈጠፍንበት ነገር ሁሉ ቀላል ነው፡፡ ነገሩንም የሚገለበጥ አምላክ ነው፡፡
ክፉ ይመጣል ብንባል አንፍራ፡፡ ያመንነው አማኑኤል አምላካችን ክንፎቹን ዘርግቶ የሚሰውረን አምላክ ነው፡፡ ልክ በራስ እንደሚጠለቅ የራስ ቁር (ሄልሜት) ክንፎቹን የሚያስጠልቀን ነው፡፡
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አማኑኤል ሆኖ የመጣው የሰው ዘር በምድር ላይ ኃጢአቱ በዝቶ የሚያድነው አጥቶ ተስፋ በቆረጠበት ሰዓት ነው፡፡
ምንም በሌለበት ምድረ በዳ የጥም ቃጠሎ በበዛበት አማኑኤል ተስፋ የሚሆን አምላክ ነው፡፡ ምድረ በዳውን፡- ለምለም ሁን ቢለው የሚሆን ፣ ባዶ ሸለቆውን በውኃ ጢም እንዲል የሚያደርግ ነው፡፡ ምድረ በዳችንን ገነት በማድረግ ሸለቆአችንንም በውኃ የሚሞላ ነው፡፡ ምንም ለሌላት ምስኪን ድሀ ባልቴት ( አሮጊት) አማኑኤል ሙላቷ ነው፡፡ እርሱ የድሆችም መመኪያ ነው፡፡
አማኑኤል ሁሉ ነገራችን ነው፡፡ የአገራችንን ዳርቻዎች ሁሉ በክንፎቹ የሚጋርድ አምላክ ነው፡፡
ስብሐት ለከ አማኑኤል አምላኪየ ኵሎ ጊዜ፡፡
ፈጣሪዬ አማኑኤል ሆይ ላንተ ሁልጊዜ ምስጋና ይገባል፡፡
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie
| 2 | ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 53 |
| 3 | በመገረፉ ቁስል ተፈወስን፡፡
ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ። በዚያም ሰቀሉት፥ ከእርሱም ጋር ሌሎች ሁለት፥ አንዱን በዚህ አንዱን በዚያ ኢየሱስንም በመካከላቸው ሰቀሉ። .. ኢየሱስም ..ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ። .. ነገር ግን ከጭፍሮች አንዱ ጎኑን በጦር ወጋው፤ ወዲያውም ደምና ውኃ ወጣ ( ዮሐ 19 ÷ 17 - 34 )።
ክርስቶስ ..ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና። .. ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ ( 1ጴጥ 2 ÷ 21 – 25 )፡፡
ማብራሪያ
አይሁድ ክርስቶስን ከያዙት በኋላ በጲላጦስ ፊት አቀረቡት፡፡ ሲወለድ ሄሮድስ በይሁዳ ላይ ገዢ እንደ ነበረ ሁሉ ክርስቶስ ሲሰቀል ጲላጦስ በይሁዳ ላይ ገዢ ነበር፡፡ ጲላጦስም የሕዝቡን ፈቃድ ሊያደርግ ወዶ በርባንን ፈታላቸው፥ ኢየሱስንም ገርፎ እንዲሰቀል አሳልፎ ሰጠ ( ማር 15 ÷ 15 ) ፡፡
ጲላጦስ ኢየሱስን እንዲገረፍ በማድረጉ ጌታችን ሰውነቱን ለገራፊዎች አሳልፎ ሰጠ፡፡ ተገረፈ፡፡ በመገረፉ ደግሞ ቆሰለ፡፡
ኢሳይያስ የቆሰለው ስለኛ በደል ( መተላለፍ ) መሆኑን ሲናገር፡-
እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ (ኢሳ 53 ÷ 5 ) በማለት ነበር፡፡ በመገረፉ ቁስል ደግሞ እኛ ተፈወስን፡፡
ሰው ተጣልቶ በድንጋይ ግንባሩን በመመታቱ ግንባሩ ቆስሎ አይተን እናውቃለን፡፡ ክርስቶስ ስለኛ ቆሰለ፡፡ በመገረፉ ምክንያት በሰውነቱ ላይ ያለው ቁስል ስለኛ ነው፡፡ በመቸንከሩ ምክንያት በእጆቹና በእግሮቹ የቆሰለው ስለኛ ነው፡፡ በጦር ጉኑን ተወግቶ የቆሰለውም ስለኛ ነው፡፡
በድንጋይ ተፈንክቶ የቆሰለን ሰው ደሙ እየፈሰሰ ስንይ ምን ይሰማናል? ክርስቶስም ስለኛ ቆሰለ፤ ደሙም ፈሰሰ፡፡ እኛን ለማዳን ስለኛ ቆሰለ፡፡ አንዲህ መከራ ተቀብሎና ቆስሎ እንዳልዳንን ብናስብ ቁስሉ ምስክር ነው፡፡ በእጁና በእግሩ ያለው የችንካሩ ምልክት ስለኛ ነው፡፡
ሐዋርያት ጌታ ከሙታን እንደ ተነሣ ለቶማስ ሲነግሩት እንዲህ አለ፡-
የችንካሩን ምልክት በእጆቹ ካላየሁ ጣቴንም በችንካሩ ምልክት ካላገባሁ እጄንም በጎኑ ካላገባሁ አላምንም አላቸው።
በእጆቹ ላይ ችንካር ያለው ስለኛ የቆሰለውን ነው፡፡ ጣቴን በችንካሩ ምልክት ካላገባሁ ያለው ስለኛ የቆሰለው ነው፡፡ ደግሞሞ በእግሮቹም ጭምር ችንካር በመኖሩ የእግሩም ችንካር ስለኛ የቆሰለው ነው፡፡ እጄንም በጎኑ ካላገባሁ ያለው ስለኛ በመቁሰሉ ነው፡፡
ከሳምንት በኋላ ጌታ እንደ ገና ለደቀ መዛሙርቱ ቶማስ ባለበት ተገለጠ፡፡ ቶማስን እንዲህ አለው፡-
ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ፤ እጅህንም አምጣና በጎኔ አግባው፡ ቶማስም፡- ጌታዬ አምላኬም ብሎ መለሰለት (ዮሐ 20 ÷ 25 -27 ) ፡፡
ጌታችን ኢየሱሰ ክርስቶስ ስለ እርሱ ( ስለ ቶማስ) ና ስለኛ በመቁሰሉ በእጆቹና በጎኑ ያለውን ቁስል እንዲያይ ለቶማስ ሲያሳየው፡- ጌታዬ አምላኬም ብሎ መለሰለት፡፡
ገንዘብ ሊለምናችሁ ፈልጎ ገንዘብ እንድትሰጡት ሰውነቱን በመግለጥ ቀዶ ጥገና ስለ ተደረገ ( ኦፕራስዮን በመደረጉ ምክንያት ) የቆሰለውን ሲያሳያችሁ ምን ይሰማችኋል? የተወደዳችሁ ክርስቲያኖች ዛሬም ጌታ ስለኛ የቆሰለውን የእጁን ችንካር ያሳየናል፡፡ ደግሞም በጦር በመወጋቱ የቆሰለውን የጎኑን ቁስል ጭምር ያሳየናል፡፡ ስለኛ በመቸንከሩ በእጆቹና በእግሮቹ የቆሰለውን ቁስል እንመልከት ፤ የተወጋውን ጎኑን እንይ፡፡ ስለኛ መሆኑን እያሰብን ስንመለከት ምን ተሰማን?
እንዲህ የቆሰለው እኛ እንድንድን ነው፡፡ እስከ መጨረሻም በመጽናት መንግሥቱን እንድንወርስ ነው፡፡ ጌታችን ስለኛ የሆነው እስከ መቁሰል በመድረስ ነው፡፡ የእጆቹንና የእግሮቹን ችንካር ልብ እንበል፡፡ የተወጋው ጎኑንም አንርሳ፡፡ ያዳነን እንዲህ ቆስሎልን ነው፡፡
ወስብሐት ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ፡፡ አሜን!
ምስጋና ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ይሁን፡፡ አሜን!
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 85 |
| 4 | ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 77 |
| 5 | ልጁ ልባል የማይገባኝን ልጁ አደረገኝ፡፡
አንድ ሰው ሁለት ልጆች ነበሩት። ከእነርሱም ታናሹ አባቱን- አባቴ ሆይ፥ ከገንዘብህ የሚደርሰኝን ክፍል ስጠኝ አለው። ገንዘቡንም አካፈላቸው።ከጥቂት ቀንም በኋላ ታናሹ ልጅ ገንዘቡን ሁሉ ሰብስቦ ወደ ሩቅ አገር ሄደ፥ ከዚያም እያባከነ ገዘቡን በተነ።ሁሉንም ከከሰረ በኋላ በዚያች አገር ጽኑ ራብ ሆነ፥ እርሱም ይጨነቅ ጀመር።ሄዶም ከዚያች አገር ሰዎች ከአንዱ ጋር ተዳበለ፥ እርሱም እሪያ(ዐሣማ) ሊያሰማራ ወደ ሜዳ ሰደደው።
እሪያዎችም ከሚበሉት አሰር ሊጠግብ ይመኝ ነበር፥ የሚሰጠውም አልነበረም።ወደ ልቡም ተመልሶ እንዲህ አለ- እንጀራ የሚተርፋቸው የአባቴ ሞያተኞች ስንት ናቸው? እኔ ግን ከዚህ በራብ እጠፋለሁ።ተነሥቼም ወደ አባቴ እሄዳለሁና። አባቴ ሆይ፥ በሰማይና በፊትህ በደልሁ፥ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም፤ ከሞያተኞችህ እንደ አንዱ አድርገኝ እለዋለሁ።ተነሥቶም ወደ አባቱ መጣ። እርሱም ገና ሩቅ ሳለ አባቱ አየውና አዘነለት፥ ሮጦም አንገቱን አቀፈውና ሳመው።
ልጁም፡- አባቴ ሆይ፥ በሰማይና በፊትህ በደልሁ፥ ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም አለው።አባቱ ግን ባሪያዎቹን አለ፡- ፈጥናችሁ ከሁሉ የተሻለ ልብስ አምጡና አልብሱት፥ ለእጁ ቀለበት ለእግሩም ጫማ ስጡ፤የሰባውን ፊሪዳ አምጥታችሁ እረዱት፥ እንብላም ደስም ይበለን፤ይህ ልጄ ሞቶ ነበርና ደግሞም ሕያው ሆኖአል፤ ጠፍቶም ነበር ተገኝቶአልም። ደስም ይላቸው ጀመር።
ታላቁ ልጁ በእርሻ ነበረ፤ መጥቶም ወደ ቤት በቀረበ ጊዜ የመሰንቆና የዘፈን ድምፅ ሰማ፤ ከብላቴናዎችም አንዱን ጠርቶ። ይህ ምንድር ነው? ብሎ ጠየቀ። እርሱም:- ወንድምህ መጥቶአልና በደኅና ስላገኘው አባትህ የሰባውን ፊሪዳ አረደለት አለው።
ተቈጣም ሊገባም አልወደደም፤ አባቱም ወጥቶ ለመነው። እርሱ ግን መልሶ አባቱን:- እነሆ፥ ይህን ያህል ዓመት እንደ ባሪያ ተገዝቼልሃለሁ ከትእዛዝህም ከቶ አልተላለፍሁም፤ ለእኔም ከወዳጆቼ ጋር ደስ እንዲለኝ አንድ ጥቦት ስንኳ አልሰጠኸኝም፤
ነገር ግን ገንዘብህን ከጋለሞቶች ጋር በልቶ ይህ ልጅህ በመጣ ጊዜ፥ የሰባውን ፊሪዳ አረድህለት አለው። እርሱ ግን። ልጄ ሆይ፥ አንተ ሁልጊዜ ከእኔ ጋር ነህ፥ ለእኔም የሆነ ሁሉ የአንተ ነው፤
ዳሩ ግን ይህ ወንድምህ ሞቶ ነበረ ሕያው ስለ ሆነ ጠፍቶም ነበር ስለ ተገኘ ደስ እንዲለን ፍሥሐም እንድናደርግ ይገባናል አለው ( ሉቃ 15 ÷ 11 - 32 ) ።
ማብራሪያ
ከበላይ ያለው ታሪክ ምሳሌ ነው፡፡ በዳዩ ልጅ ወደ አባቱ ሲመጣ አባቱ፡- መሄጃ ስታጣ መጣህ አይደል? መከራውን በደንብ ቀመስካት፤ ሰው የሚነግርህን አልሰማ ብለህ ( አሁንማ አየሃት፤ ልክ ገባህ፤ መከራዋን ቀመስካት ወ.ዘ.ተ) አላለውም፡፡ በድሎም ቢሆን ግን ጥፋቱን አውቆ የመጣውን ልጅ የበለጠ አንገት በሚያስቀረቅር ንግግር አልተናገረውም፡፡ ይልቅስ አዘነለት፤አንገቱን አቅፎ ሳመው፡፡ ለበደለው ልጅ ከሁሉ የተሸለ ልብስ እንዲለብስ፣ ለእጁ ቀለበት፣ ለእግሩም ጫማ እንዲሰጠው አዘዘ ፡፡ የሰባውን ፍሪዳ አረደለት፡፡ ታላቅ ልጅ በሆነው ነገር ደስተኛ አልነበረም፡፡ አዎ የወንድምና የአባት ፍቅር በጣም ይለያያል ፡፡ አባት ምንም ቢሆን አባት ነው፡፡
ድርሻውን የወሰደው ልጅ ወደ አባቱ የተመለሰው ባሪያ ሆኖ ለመኖር ነው፡፡ ደግሞም አባቱን፡- ልጅህ ልባል አይገባኝም ብሎታል፡፡ አባት ግን፡- ይህ ልጄ ሞቶ ነበርና በሚለው ንግግሩ ውስጥ ልጁ እንደሆነ ተናገረ ( ቁ. 24 ) ፡፡
እግዚአብሔርም ሰው በድሎት ወደ እርሱ ሲመጣ ወደ እርሱ የሚመጣውን አትምጣ አይልም፤
ምንም አጥፊዎች ብንሆን ወደ እርሱ ስንመጣ ግን ይራራልናል፡፡ ልጄ ብሎ ይጠራናል፡፡ አባት ልጁን ይወዳል ፡፡ ይህ አባት ድርሻውን የወሰደውን ልጁን አቅፎ ከተቀበለው መሐሪ የሆነው አባታችን እግዚአብሔር እኛን ልጆቹን እንዴት ይጠላናል? ስንጸልይስ እንዴት አይሰማንም? ከቤቱ ወጥተን በድለነው እንኳን ወደ እርሱ ስንመለስ ይቀበለናል፡፡
ኦ ወልድ ዋሕድ እግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ስብሐት ለዓለመ ዓለም ፡፡ አሜን ፡፡
ወልድ ዋሕድ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ምስጋና ላንተ ይሁን ለዘላለሙ፡፡ አሜን፡፡
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 90 |
| 6 | ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 85 |
| 7 | ገና ከመጀመሪያም ስለ ሰው የነበረ የእግዚአብሔር መልካም አሳብ፡፡
በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ።
.. እግዚአብሔርም፡- ምድር ..ቡቃያን በምድርም ላይ እንደ ወገኑ ዘሩ ያለበትን ፍሬን የሚያፈራ ዛፍን ታብቅል አለ፤ እንዲሁም ሆነ። ምድርም ..ቡቃያን እንደ ወገኑ ዘሩም ያለበትን ፍሬን የሚያፈራ ዛፍን እንደ ወገኑ አበቀለች። እግዚአብሔርም ያ መልካም እንደ ሆነ አየ።
..እግዚአብሔርም ሁለት ታላላቆች ብርሃናትን አደረገ፤ ትልቁ ብርሃን በቀን እንዲሠለጥን፥ ትንሹም ብርሃን በሌሊት እንዲሰለጥን፤ ከዋክብትንም ደግሞ አደረገ።
..እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው። እግዚአብሔርም ባረካቸው፥ እንዲህም አላቸው። ብዙ፥ ተባዙ፥ ምድርንም ሙሉአት፥ ግዙአትም፤ የባሕርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ግዙአቸው።
እግዚአብሔርም አለ። እነሆ መብል ይሆናችሁ ዘንድ በምድር ፊት ሁሉ ላይ ዘሩ በእርሱ ያለውን ሐመልማል ሁሉ፥ የዛፍን ፍሬ የሚያፈራውንና ዘር ያለውንም ዛፍ ሁሉ ሰጠኋችሁ፤
ለምድርም አራዊት ሁሉ፥ ለሰማይም ወፎች ሁሉ፥ ሕያው ነፍስ ላላቸው ለምድር ተንቀሳቃሾችም ሁሉ የሚበቅለው ሐመልማል ሁሉ መብል ይሁንላቸው፤ እንዲሁም ሆነ (ዘፍጥ 1 ÷ 1 ፡ 11 ፡ 16 ፡ 27 – 30 ) ።
እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው፤ በአፍንጫውም የሕይወት እስትንፋስን እፍ አለበት፤ ሰውም ሕያው ነፍስ ያለው ሆነ።
እግዚአብሔር አምላክም አለ። ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ የሚመቸውን ረዳት እንፍጠርለት።
እግዚአብሔር አምላክም በአዳም ከባድ እንቅልፍን ጣለበት፥ አንቀላፋም፤ ከጎኑም አንዲት አጥንትን ወስዶ ስፍራውን በሥጋ ዘጋው።
እግዚአብሔር አምላክም ከአዳም የወሰዳትን አጥንት ሴት አድርጎ ሠራት፤ ወደ አዳምም አመጣት። አዳምም አለ። ይህች አጥንት ከአጥንቴ ናት፥ ሥጋም ከሥጋዬ ናት፤ እርስዋ ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል (ዘፍጥ 2 ÷ 7 : 18 : 21 - 23 ) ።
ማብራሪያ
እግዚአብሔር በመጀመሪያ ሰማይንና ምድርን ፈጠረ፡፡ ምድር የሰው ልጅ የሚኖርባት ስትሆን ለሰው ልጅ መብል የሚሆኑትንም በሙሉ እንድታበቅልም ነበር፡፡
የመጀመሪያው ሰው አዳም ሲፈጠር ብቻውን ነበር፡፡ መልካሙን የሚያስብልን አምላክ :- መልካም አይደለም አለ፡፡ መልካም አይደለም ያለውን አንብባችሁት የለ? :- ለሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ ፡፡ ሰው ብቻውን እንዳይሆን አሰበለት፡፡ ረዳት የምትሆንን ሴትን ፈጠረለት፡፡
እግዚአብሔር ለሰው ልጆች መልካም መልካሙን ያስብልናል፡፡ ሴት ማለት ወንድ ብቻውን እንዳይሆን የተፈጠለች አስፈላጊያችን ናት፡፡ ከማግባታችን በፊት ለእህትነት የምታስፈልገን ፣ አግብታናት ለረዳትነት የምታስፈልገን ውድ የእግዚአብሔር ስጦታ ናት፡፡
ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም ነው የተባለው፡፡ ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም ለተባለው ሰው ረዳት ሴት ደግሞ ሰጠው፡፡ ያቺ ረዳት ታዲያ ከሩቅ አልመጣችም ካጠገቡ ከጎኑ ተፈጠረችለት ፡፡ ረዳቱን ከራሱ ጉኑ ላይ ፈጥሮ ሰጠው፡፡
አዳም ጎን ኖሮት ከጎኑ ግን ረዳት ማስገኘት አልቻለም፡፡ የጠቢባን ጠቢቡ እግዚአብሔር ግን ከራሱ ጎን ለጎኑ የምትሆን ከጎኑ የማትለየውን ረዳት ፈጠረለት፡፡ ስለ ረዳትነትዋ ብቻ ከጌዜ አካያ ስለ ጻፍኩ እንጂ ሌለም ነገር ማንሳት ይቻል ነበር፡፡
ወንድና ሴት ሆኑና ዓለም ተጀመረ፡፡ ወንድና ሴት በአዲሲቱ ምድር ኑሮአቸውን ተያያዙት፡፡ ያልዘሩትን እህል እግዚአብሔር አብቅሎላቸው መመገብ ጀመሩ፡፡ የሰው ልጅ አምላኩ ባወጣለት ጸሐይ ብርሃን በቀን እያገኘ ለሌሊቱ ደግሞ ጨረቃና ከዋክብትን ብርሃናቸውን እየሰጡት መኖሩን ተያያዘው፡፡ ብዙና ብዙ እንዲሆኑ ደግሞ ባረካቸው፡፡ እንዲህ ዛሬ የበዛነው ስለ ተባረክን ነው፡፡ ታዲያ ሰንበዛ ትግሬ ፣ ጉራጌ ፣ አማራ ፣ ኦሮሞ፣ ወላይታ ወዘተ ተባብለን ልንልያይ አልነበረም፡፡
ያኔ ድሮ በመጀመሪያ ትግሬ ፣ አማራ ፣ጉራጌ ፣ ኦሮሞ ፣ ወላይታ ወዘተ ወዘተ የሚባል ነገር የለው፡፡ ሰው ተብሎ ሲጠራ ነው ያነበብው፡፡
እግዚአብሔር ሰውን ሲፈጥረው የሚበላው ከባሕር ለምሳሌ እንደ ዓሦች የመሳሉትን ከምድርም እጅግ ብዙ መብልን አዘጋጅቶለት እንጂ ምግብ በሌለበት ምድር አላመጣውም፡፡ እጅግ ለኑሮ የምትመች ምድር ነበር የሰጠው፡፡
የፈጠረን ከማኅፀን እኛንም ያወጣን ፈጣሪ ዛሬም ልክ እንደ አዳም ያስብልናል፡፡ ለአዳም ለቀኑ ብርሃን እንድትሆን የሰጠውን ጸሐይ ዛሬም አልወሰደብንም፡፡ ሲመሽ በእጃችን የእጅን ባትሪ ይዘን እንደምናበራው ጸሐይ በሰው እጅና በተቋም ሥር ብትሆን በየቀኑ የምትወጣዋን ጸሐይ ማን ይይዝልን ነበር ? ያዢው ሲለው ሲይዝልን ፣ መያዙ ሲደክመው ደግሞ በቀን በጨለማ እንድንውል እንደረግ ነበር፡፡ ደጉ የሰማይ አምላክ የፈጠረን ጌታ በሰማይ ሰቀላትና ብንበድለውም ብናስደስተውም የሰጠንን ጸሐይ ሳይነጥቀን ይኸው ሁልጊዜ ያበራልናል፡፡
መኖርና መንቀሳቀስ የቻልን እስትንፋሱን ስለ ሰጠን ነው ፡፡ እስትንፋሳችን ራሱ የእርሱ ነው፡፡ እስትንፋሱን ሲወስድብን መኖር እናቆማለን፡፡ እስትንፋሱን የሰጠን ለኑሮ የሚያስፈልገንን ሌላውን ነገር እንዴት አይሰጠንም?
ረዳት የሚሆኑን ሴቶች እነርሱም ተባርከው በዝተው እዚህ ደርሰናል፡፡ አዳም ከጎኑ የወጣችውን ሔዋን ሲያያት ምን እንዳላት ሴቶች አንብባችኋል፡፡
ውድ እህቴ አንቺ የአጥንቴ አጥንት የሥጋዬ ሥጋ ነሽ፡፡ ከኔ ከወንዱ ተገኝተሻልና፡፡ ነገ ተነገ ወዲያ ደግሞ እናቴንና አባቴን የምተውብሽ ፣ የምጣበቅብሽ፣ መልሼም ከአንቺ ጋር አንድ ሥጋ የምሆንብሽ ነሽ፡፡ ወንድና ሴት ሁለት ሆነው ልዩነትን ሳይሆን የሚሰብኩት አንድነትን የሚሰብኩ ናቸው፡፡ የወጣችበትን ጎናችንን ስንዳብስ አጥንቱ ጎድሎ ብናይም ያቺ አጥንታችን በፊታችን ሴት ሆና የራስዋ ቁመና ያላት ሆና የምናያት ድንቅ የእግዚአብሔር ፍጥረት ናት፡፡
እናንተ ሴቶች ከእኛ የተገኛችሁ ናችሁ፡፡ እኛም አንኮ+ም፡፡ ከእግዚአብሔር የተገኘን እንጂ ራሳችንን ያስገኘን ብርቱዎች አይደለም ፡፡ እናንተ ለኛ ተፈጥራችኋል፡፡ እናንተ ከሌላችሁን ረዳት የሌለን ብቸኞች እንሆን ነበር፡፡ እኛ ብቻችንን ብንሆን መልካም አይሆንለንም ነበር፡፡ እናንተን እግዚአብሔር ስለ ሰጠን መልካም ሆነልን፡፡ ረዳታችን ለአንድ ቀን ከኛ ባትኖር ረዳት የሌለን ብቸኞች መሆናችን ያን ጊዜ ይገባናል፡፡
ዛሬም እንደ መጀመሪያ ጊዜ እግዚአብሔር ለኛ ለሰዎች ያስብልናል፡፡ ለእያንዳንዳችን ከበጎ ፈቃዱ የተነሳ ያዘጋጀልን መልካም መልካም ነገርም አለው፡፡ ለፈጠራችሁ ለእግዚአብሔር ልባችሁ የቀና ብዙ ሰዎች አላችሁ፡፡ እግዚአብሔርም ለናንተ ቅንና መልካም አምላክ ነው፡፡ እንደምትወዱት ይወዳችኋል፡፡ እርሱን ሁሌም እንደምትሹት እርሱም ለእናንተ መልካም አምላክ ነው፡፡
ወደ ተነሣሁበት ሀሳብ ስመለስ የሰው ልጅ የታሪኩን ጅማሬ ያስቃኘኋችሁን አትረሱትም፡፡ እግዚአብሔር የፈጠራቸው የወንድና የሴት ታሪክ ያልኩአችሁን ይመስል ነበር፡፡ ከመጀመሪያም እግዚአብሔር ለሰው ያለውን መልካሙን ሀሳቡንም አትዘነጉትም፡፡ በሉ እንግዲህ ሰላማችሁ ይብዛ ፤ ወንድ የተባላችሁ ወንድሞቼ ፣ ሴት የተባላችሁ እህቶቼ ዘመናችሁ በስኬት የተሞላ ያድርገው፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን! | 88 |
| 8 | ▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 1 |
| 9 | ገና ከመጀመሪያም ስለ ሰው የነበረ የእግዚአብሔር መልካም አሳብ፡፡
በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ።
.. እግዚአብሔርም፡- ምድር ..ቡቃያን በምድርም ላይ እንደ ወገኑ ዘሩ ያለበትን ፍሬን የሚያፈራ ዛፍን ታብቅል አለ፤ እንዲሁም ሆነ። ምድርም ..ቡቃያን እንደ ወገኑ ዘሩም ያለበትን ፍሬን የሚያፈራ ዛፍን እንደ ወገኑ አበቀለች። እግዚአብሔርም ያ መልካም እንደ ሆነ አየ።
..እግዚአብሔርም ሁለት ታላላቆች ብርሃናትን አደረገ፤ ትልቁ ብርሃን በቀን እንዲሠለጥን፥ ትንሹም ብርሃን በሌሊት እንዲሰለጥን፤ ከዋክብትንም ደግሞ አደረገ።
..እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው። እግዚአብሔርም ባረካቸው፥ እንዲህም አላቸው። ብዙ፥ ተባዙ፥ ምድርንም ሙሉአት፥ ግዙአትም፤ የባሕርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ግዙአቸው።
እግዚአብሔርም አለ። እነሆ መብል ይሆናችሁ ዘንድ በምድር ፊት ሁሉ ላይ ዘሩ በእርሱ ያለውን ሐመልማል ሁሉ፥ የዛፍን ፍሬ የሚያፈራውንና ዘር ያለውንም ዛፍ ሁሉ ሰጠኋችሁ፤
ለምድርም አራዊት ሁሉ፥ ለሰማይም ወፎች ሁሉ፥ ሕያው ነፍስ ላላቸው ለምድር ተንቀሳቃሾችም ሁሉ የሚበቅለው ሐመልማል ሁሉ መብል ይሁንላቸው፤ እንዲሁም ሆነ (ዘፍጥ 1 ÷ 1 ፡ 11 ፡ 16 ፡ 27 – 30 ) ።
እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው፤ በአፍንጫውም የሕይወት እስትንፋስን እፍ አለበት፤ ሰውም ሕያው ነፍስ ያለው ሆነ።
እግዚአብሔር አምላክም አለ። ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ የሚመቸውን ረዳት እንፍጠርለት።
እግዚአብሔር አምላክም በአዳም ከባድ እንቅልፍን ጣለበት፥ አንቀላፋም፤ ከጎኑም አንዲት አጥንትን ወስዶ ስፍራውን በሥጋ ዘጋው።
እግዚአብሔር አምላክም ከአዳም የወሰዳትን አጥንት ሴት አድርጎ ሠራት፤ ወደ አዳምም አመጣት። አዳምም አለ። ይህች አጥንት ከአጥንቴ ናት፥ ሥጋም ከሥጋዬ ናት፤ እርስዋ ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል (ዘፍጥ 2 ÷ 7 : 18 : 21 - 23 ) ።
ማብራሪያ
እግዚአብሔር በመጀመሪያ ሰማይንና ምድርን ፈጠረ፡፡ ምድር የሰው ልጅ የሚኖርባት ስትሆን ለሰው ልጅ መብል የሚሆኑትንም በሙሉ እንድታበቅልም ነበር፡፡
የመጀመሪያው ሰው አዳም ሲፈጠር ብቻውን ነበር፡፡ መልካሙን የሚያስብልን አምላክ :- መልካም አይደለም አለ፡፡ መልካም አይደለም ያለውን አንብባችሁት የለ? :- ለሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ ፡፡ ሰው ብቻውን እንዳይሆን አሰበለት፡፡ ረዳት የምትሆንን ሴትን ፈጠረለት፡፡
እግዚአብሔር ለሰው ልጆች መልካም መልካሙን ያስብልናል፡፡ ሴት ማለት ወንድ ብቻውን እንዳይሆን የተፈጠለች አስፈላጊያችን ናት፡፡ ከማግባታችን በፊት ለእህትነት የምታስፈልገን ፣ አግብታናት ለረዳትነት የምታስፈልገን ውድ የእግዚአብሔር ስጦታ ናት፡፡
ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም ነው የተባለው፡፡ ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም ለተባለው ሰው ረዳት ሴት ደግሞ ሰጠው፡፡ ያቺ ረዳት ታዲያ ከሩቅ አልመጣችም ካጠገቡ ከጎኑ ተፈጠረችለት ፡፡ ረዳቱን ከራሱ ጉኑ ላይ ፈጥሮ ሰጠው፡፡
አዳም ጎን ኖሮት ከጎኑ ግን ረዳት ማስገኘት አልቻለም፡፡ የጠቢባን ጠቢቡ እግዚአብሔር ግን ከራሱ ጎን ለጎኑ የምትሆን ከጎኑ የማትለየውን ረዳት ፈጠረለት፡፡ ስለ ረዳትነትዋ ብቻ ከጌዜ አካያ ስለ ጻፍኩ እንጂ ሌለም ነገር ማንሳት ይቻል ነበር፡፡
ወንድና ሴት ሆኑና ዓለም ተጀመረ፡፡ ወንድና ሴት በአዲሲቱ ምድር ኑሮአቸውን ተያያዙት፡፡ ያልዘሩትን እህል እግዚአብሔር አብቅሎላቸው መመገብ ጀመሩ፡፡ የሰው ልጅ አምላኩ ባወጣለት ጸሐይ ብርሃን በቀን እያገኘ ለሌሊቱ ደግሞ ጨረቃና ከዋክብትን ብርሃናቸውን እየሰጡት መኖሩን ተያያዘው፡፡ ብዙና ብዙ እንዲሆኑ ደግሞ ባረካቸው፡፡ እንዲህ ዛሬ የበዛነው ስለ ተባረክን ነው፡፡ ታዲያ ሰንበዛ ትግሬ ፣ ጉራጌ ፣ አማራ ፣ ኦሮሞ፣ ወላይታ ወዘተ ተባብለን ልንልያይ አልነበረም፡፡
ያኔ ድሮ በመጀመሪያ ትግሬ ፣ አማራ ፣ጉራጌ ፣ ኦሮሞ ፣ ወላይታ ወዘተ ወዘተ የሚባል ነገር የለው፡፡ ሰው ተብሎ ሲጠራ ነው ያነበብው፡፡
እግዚአብሔር ሰውን ሲፈጥረው የሚበላው ከባሕር ለምሳሌ እንደ ዓሦች የመሳሉትን ከምድርም እጅግ ብዙ መብልን አዘጋጅቶለት እንጂ ምግብ በሌለበት ምድር አላመጣውም፡፡ እጅግ ለኑሮ የምትመች ምድር ነበር የሰጠው፡፡
የፈጠረን ከማኅፀን እኛንም ያወጣን ፈጣሪ ዛሬም ልክ እንደ አዳም ያስብልናል፡፡ ለአዳም ለቀኑ ብርሃን እንድትሆን የሰጠውን ጸሐይ ዛሬም አልወሰደብንም፡፡ ሲመሽ በእጃችን የእጅን ባትሪ ይዘን እንደምናበራው ጸሐይ በሰው እጅና በተቋም ሥር ብትሆን በየቀኑ የምትወጣዋን ጸሐይ ማን ይይዝልን ነበር ? ያዢው ሲለው ሲይዝልን ፣ መያዙ ሲደክመው ደግሞ በቀን በጨለማ እንድንውል እንደረግ ነበር፡፡ ደጉ የሰማይ አምላክ የፈጠረን ጌታ በሰማይ ሰቀላትና ብንበድለውም ብናስደስተውም የሰጠንን ጸሐይ ሳይነጥቀን ይኸው ሁልጊዜ ያበራልናል፡፡
መኖርና መንቀሳቀስ የቻልን እስትንፋሱን ስለ ሰጠን ነው ፡፡ እስትንፋሳችን ራሱ የእርሱ ነው፡፡ እስትንፋሱን ሲወስድብን መኖር እናቆማለን፡፡ እስትንፋሱን የሰጠን ለኑሮ የሚያስፈልገንን ሌላውን ነገር እንዴት አይሰጠንም?
ረዳት የሚሆኑን ሴቶች እነርሱም ተባርከው በዝተው እዚህ ደርሰናል፡፡ አዳም ከጎኑ የወጣችውን ሔዋን ሲያያት ምን እንዳላት ሴቶች አንብባችኋል፡፡
ውድ እህቴ አንቺ የአጥንቴ አጥንት የሥጋዬ ሥጋ ነሽ፡፡ ከኔ ከወንዱ ተገኝተሻልና፡፡ ነገ ተነገ ወዲያ ደግሞ እናቴንና አባቴን የምተውብሽ ፣ የምጣበቅብሽ፣ መልሼም ከአንቺ ጋር አንድ ሥጋ የምሆንብሽ ነሽ፡፡ ወንድና ሴት ሁለት ሆነው ልዩነትን ሳይሆን የሚሰብኩት አንድነትን የሚሰብኩ ናቸው፡፡ የወጣችበትን ጎናችንን ስንዳብስ አጥንቱ ጎድሎ ብናይም ያቺ አጥንታችን በፊታችን ሴት ሆና የራስዋ ቁመና ያላት ሆና የምናያት ድንቅ የእግዚአብሔር ፍጥረት ናት፡፡
እናንተ ሴቶች ከእኛ የተገኛችሁ ናችሁ፡፡ እኛም አንኮ+ም፡፡ ከእግዚአብሔር የተገኘን እንጂ ራሳችንን ያስገኘን ብርቱዎች አይደለም ፡፡ እናንተ ለኛ ተፈጥራችኋል፡፡ እናንተ ከሌላችሁን ረዳት የሌለን ብቸኞች እንሆን ነበር፡፡ እኛ ብቻችንን ብንሆን መልካም አይሆንለንም ነበር፡፡ እናንተን እግዚአብሔር ስለ ሰጠን መልካም ሆነልን፡፡ ረዳታችን ለአንድ ቀን ከኛ ባትኖር ረዳት የሌለን ብቸኞች መሆናችን ያን ጊዜ ይገባናል፡፡
ዛሬም እንደ መጀመሪያ ጊዜ እግዚአብሔር ለኛ ለሰዎች ያስብልናል፡፡ ለእያንዳንዳችን ከበጎ ፈቃዱ የተነሳ ያዘጋጀልን መልካም መልካም ነገርም አለው፡፡ ለፈጠራችሁ ለእግዚአብሔር ልባችሁ የቀና ብዙ ሰዎች አላችሁ፡፡ እግዚአብሔርም ለናንተ ቅንና መልካም አምላክ ነው፡፡ እንደምትወዱት ይወዳችኋል፡፡ እርሱን ሁሌም እንደምትሹት እርሱም ለእናንተ መልካም አምላክ ነው፡፡
ወደ ተነሣሁበት ሀሳብ ስመለስ የሰው ልጅ የታሪኩን ጅማሬ ያስቃኘኋችሁን አትረሱትም፡፡ እግዚአብሔር የፈጠራቸው የወንድና የሴት ታሪክ ያልኩአችሁን ይመስል ነበር፡፡ ከመጀመሪያም እግዚአብሔር ለሰው ያለውን መልካሙን ሀሳቡንም አትዘነጉትም፡፡ በሉ እንግዲህ ሰላማችሁ ይብዛ ፤ ወንድ የተባላችሁ ወንድሞቼ ፣ ሴት የተባላችሁ እህቶቼ ዘመናችሁ በስኬት የተሞላ ያድርገው፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን!
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ | 1 |
| 10 | ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 74 |
| 11 | ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 94 |
| 12 | የበደልነው አምላክ ከበደልነው በኋላ እንኳን የሚያሳየን ርኅራኄ ፡፡
የእስራኤልም ልጆች በእግዚአብሔር ፊት እንደ ገና ክፉ ሥራ ሠሩ በኣሊምንና አስታሮትን የሶርያንም አማልክት፥ የሲዶናንም አማልክት፥ የሞዓብንም አማልክት፥ የአሞንንም ልጆች አማልክት፥ የፍልስጥኤማውያንንም አማልክት አመለኩ፤ እግዚአብሔርንም ተዉ፥ አላመለኩትምም።
የእግዚአብሔርም ቍጣ በእስራኤል ላይ ነደደ፥ በፍልስጥኤማውያንና በአሞን ልጆች እጅ አሳልፎ ሰጣቸው። በዚያም ዓመት የእስራኤልን ልጆች ሥቃይ አበዙባቸው፤ ..የእስራኤልን ልጆች ሁሉ አሥራ ስምንት ዓመት ተጋፉአቸው። ..እስራኤልም እጅግ ተጨነቁ።
የእስራኤልም ልጆች፡- አምላካችንን ትተን በኣሊምን አምልከናልና አንተን በድለናል ብለው ወደ እግዚአብሔር ጮኹ። እግዚአብሔርም የእስራኤልን ልጆች አላቸው። ግብፃውያን፥ አሞራውያንም፥ የአሞንም ልጆች፥ ፍልስጥኤማውያንም፥ ሲዶናውያንም፥ አማሌቃውያንም፥ ማዖናውያንም አላስጨነቋችሁምን? ወደ እኔም ጮኻችሁ፥ እኔም ከእጃቸው አዳንኋችሁ። እናንተ ግን ተዋችሁኝ ሌሎችንም አማልክት አመለካችሁ፤ ስለዚህም ደግሞ አላድናችሁም። ሄዳችሁም የመረጣችኋቸውን አማልክት ጥሩ፤ እነርሱም በመከራችሁ ጊዜ ያድኑአችሁ።
የእስራኤልም ልጆች እግዚአብሔርን፡- እኛ ኃጢአትን ሠርተናል፤ አንተ ደስ የሚያሰኝህን አድርግብን ዛሬ ግን፥ እባክህ፥ አድነን አሉት። ሌሎችንም አማልክት ከመካከላቸው አስወገዱ፥ እግዚአብሔርንም አመለኩ፤ ነፍሱም ስለ እስራኤል ጕስቍልና አዘነች ( መሳ 10 ÷ 6 - 16 )።
ማብራሪያ
በአሥርቱ ትእዛዛት ውስጥ የተካተተውን፡- ከኔ በቀር ሌላ አማልክት አታምልኩ የሚለውን ትእዛዛት የተነገራቸው እስራኤላውያን አምላካቸውን እግዚአብሔርን ትተው በአሊምን ፣ አስታሮትን አንዴ የሶርያን ሌላ ግዜ የሲዶንን አማልክት ሲላቸው የአሞን ልጆችን አማልክት ብቻ ምኑ ቅጡ ልበላችሁ በዓይነት በዓይነት የተለያዩ አማልክትን ( ጦዖታትን ) አመለኩ፡፡ እግዚአብሔርን ማምለክ እርግፍ አድርገው ተዉ፡፡ ምስጋናውንና ውዳሴውን ትተው ለሌሎች አማልክት ማጠኑን ተያያዙት፡፡
እግዚአብሔርን ስለተዉት ተቆጣና እግዚአብሔር በፍልስጥኤማውያንና በአሞን ልጆች አሳልፎ ሰጣቸው፡፡ እስራኤልንም ሥቃይ አበዙባቸው፡፡ ለአሥራ ስምንት ዓመት አደቀቁአቸው ( በጽኑ አገዛዝ ገዙአቸው )፡፡ የእስራኤል ልጆች እጅግ ተጨነቁ፡፡ እጅግ ተጨንቀው ሳለ ያመለኩአቸው አማልክት አንዳቸውም ግን ሊረዱአቸው አልቻሉም፡፡
ይህ ሁሉ ሥቃይ ለምን እንደ ደረሰባቸው ያስተዋሉት እስራኤላውያን፡- አምላካችንን ትተን በኣሊምን (ጣዖትን ) አምልከናልና አንተን በድለናል በማለት ወደ እግዚአብሔር ጮኹ። እግዚአብሔር ደግሞ መለሰ፤ ፡- እኔን ትታችሁ ሌሎች አማልክትን ስላመለካችሁ አላድናችሁም፤ ያመለካችኋቸው አማልክትን ለምኑ ( ጥሩ ) ፤ በዚህ በመከራ ጊዜ ያድኑአቸሁ አላቸው፡፡
እግዚአብሔር ከዚህ በፊት እስራኤልንን ግብፃውያንና ሌሎችም አስጨንቀዋቸው በነበሩ ሰዓት ወደ እርሱ ሲጮኹ ረድቶአቸው ነበር ፡፡ ታዲያ ያዳናቸውን አምላክ ውለታውን ረስተው ስለ ተዉት ነበር አሁን፡- አላድናችሁም በማለት የመለሰላቸው፡፡
የእስራኤልም ልጆች በሚያሳዝን ሁኔታ እግዚአብሔርን፡- እኛ ኃጢአትን ሠርተናል፤ አንተ ደስ የሚያሰኝህን አድርግብን ዛሬ ግን፥ እባክህ፥ አድነን አሉት። ሌሎች አማልክትን መማለክን ተዉና እርሱን አምላክ አደረጉ፡፡ የበደሉት እግዚአብሔር የእስራኤላውያንን ጕስቍልና አይቶ ራራላቸው እንጂ አልጨከነባቸውም፡፡
እግዚአብሔር ከበደሉት በኋላ ለእስራኤላውያን ያሳየው ርኅራኄ የሚያስደንቅ ነበር፡፡ እግዚአብሔርን ትቶ ሌላ አምላክ በማምለክ እግዚአብሔርን መበደልና እግዚአብሔርን አምላክ አድርጎ እግዚአብሔርን መበደል በጣም ይለያያል፡፡ ሌላ አምላክን ማምለክ የከፋ ኃጢአት ነው፡፡ እንደዛም በድለውት መልሶ ራርቶላቸዋል፡፡
ሰው ሆኖ የማይበድል የለምና እግዚአብሔርን እንበድላለን ፤ ይቅር በለን ፤ እርዳን በምንለው ሰዓት ግን የሚረዳን አምላክ እንጂ ቸል እንዳሉት እስራኤላውያን ቸል የሚል አምላክ አይደለም፡፡ ይልቁን ደግሞ ከበደልነው በኋላ የሚያሳየን ርኅራኄ ከእርሱ ጋር በደስታ እንድንቀጥል የሚያደርግና ኃይል የሚሰጥ ነው፡፡
እግዚአብሔር ስለ ፍቅሩ ፣ ርኅራኄው ፣ ምሕረቱ ብዙ አልተሰበከለትም፤ ብዙም አልተነገረለትም፡፡ ብዙ ብንሰብክለት ብዙ ብንናገርለት እንኳን ከምንሰብክለትና ከምንናገርለት በላይ ርኅሩኅ ነው፡፡ ከበደልነው በኋላ የሚያሳየንን ፍቅሩንና ርኅራኄን ስናስተውል ከዚህ አምላክ ጋር ሁሌም እንድንኖርና እንዳንርቀው የሚያደርግ እንደ ምድር ስበት የሆነ የፍቅሩና የርኅራኌ ስበት ሁሌ እየሳበን ከእርሱ ጋር እንድንኖር ያደርገናል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን!
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 88 |
| 13 | የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፡፡
በንጉሡ በአርጤክስስ በሀያኛው ዓመት ..የወይን ጠጅ በፊቱ በነበረ ጊዜ ጠጁን አንሥቼ ለንጉሡ ሰጠሁት። ቀድሞ ግን በፊቱ ያለ ኃዘን እኖር ነበር። ንጉሡም፡- ሳትታመም ፊትህ ለምን አዘነ? ይህ የልብ ኅዘን ነው እንጂ ሌላ ነገር አይደለም አለኝ። እጅግም ብዙ አድርጌ ፈራሁ።
ንጉሡንም፡- ንጉሡ ሺህ ዓመት ይንገሥ፤ የአባቶቼ መቃብር ያለባት ከተማ ተፈትታለችና፥ በሮችዋም በእሳት ተቃጥለዋልና ፊቴ ስለ ምን አይዘን? አልሁት። ንጉሡም፡- ምን ትለምነኛለህ? አለኝ። እኔም ወደ ሰማይ አምላክ ጸለይሁ። ንጉሡንም፡- ንጉሡን ደስ ቢያሰኝህ፥ ባሪያህም በፊትህ ሞገስ ቢያገኝ፥ እሠራው ዘንድ ወደ ይሁዳ ወደ አባቶቼ መቃብር ከተማ ስደደኝ አልሁት።
ንግሥቲቱም በአጠገቡ ተቀምጣ ሳለች ንጉሡ፡- መንገድህ እስከ መቼ ድረስ ይሆናል? መቼስ ትመለሳለህ? አለኝ። ንጉሡም ይሰድደኝ ዘንድ ደስ አለው፤ እኔም ዘመኑን ቀጠርሁለት። ንጉሡንም፡- ንጉሡ ደስ ቢለው፥ እስከ ይሁዳ አገር እንዲያደርሱኝ በወንዝ ማዶ ላሉት ገዦች ደብዳቤ ይሰጠኝ፤ ..ንጉሡም በእኔ ላይ መልካም እንደ ሆነችው እንደ አምላኬ እጅ ሰጠኝ።
በወንዙም ማዶ ወዳሉት አለቆች መጥቼ የንጉሡን ደብዳቤ ሰጠኋቸው ንጉሡም ከእኔ ጋር የሠራዊቱን አለቆችና ፈረሰኞች ሰደደ። ሰንባላጥና ጦብያ ለእስራኤል ልጆች መልካምን ነገር የሚሻ ሰው እንደ መጣ በሰሙ ጊዜ እጅግ ተበሳጩ። ወደ ኢየሩሳሌምም ደረስሁ፥ ..የፈረሰውንም የኢየሩሳሌምን ቅጥር፥ በእሳትም የተቃጠሉትን በሮችዋን ተመለከትሁ።
..ለአይሁድና ለካህናቱ፥ ለታላላቆችና ለሹማምቱም፥ ሥራም ይሠሩ ለነበሩት ለሌሎች ..እኔም፡- እኛ ያለንበትን ጕስቍልና ኢየሩሳሌም እንደ ፈረሰች፥ በሮችዋም በእሳት እንደ ተቃጠሉ ታያላችሁ፤ አሁንም ከእንግዲህ ወዲህ መሳለቂያ እንዳንሆን ኑና የኢየሩሳሌምን ቅጥር እንሥራ አልኋቸው። የአምላኬም እጅ በእኔ ላይ መልካም እንደሆነች፥ ንጉሡም የነገረኝን ቃል ነገርኋቸው። እነርሱም። እንነሣና እንሥራ አሉ። እጃቸውንም ለበጎ ሥራ አበረቱ።
ሰንባላጥ፥ ጦብያ፥ ዓረባዊውም ጌሳም በሰሙ ጊዜ በንቀት ሳቁብን፥ ቀላል አድርገውንም። ይህ የምታደርጉት ነገር ምንድር ነው? በውኑ በንጉሡ ላይ ትሸፍቱ ዘንድ ትወድዳላችሁን? አሉ። እኔም መልሼ፡- የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፥ እኛም ባሪያዎቹ ተነሥተን እንሠራለን ..አልኋቸው ( ነህ 2 ) ።
ማብራሪያ
አይሁድ ተማርከው ወደ ባቢሎን ተወስደው ነበር፡፡ ከ70 ዓመት በኋላ የተመለሱት ተመልሰው የቀሩት ደግሞ በባዕድ አገር ይኖሩ ነበር፡፡ ነህምያ በባዕድ አገር የሚኖር ሲሆን ንጉሡ የሚጠጣውን የወይን ጠጅ የሚያቀርብ ሰው ነበር፡፡ ከምርኮ የተመለሱት አይሁድ አገራቸውን በከፊል መሥራት ቢጀምሩም ጠላቶቻቸው የሠሩትን እንዳፈረሱባቸውና በእሳት እንዳቃጠሉባችው ሲሰማ ነህምያ እጅግ አዘነ፡፡
ነህምያ የወይን ጠጁን ሊያቀርብ ወደ ንጉሡ ሲገባ ንጉሡ የነህምያን በታላቅ ሀዘን ውስጥ መሆኑን ተረድቶ ሲጠይቀው ጉዳዩን አስረዳው፡፡ ወገኖቹ አይሁድ የፈረሰችውን አገራቸውን መልሰው ቢሠሩም ልማቱን ያልወደዱ ሰዎች እያቃጠሉባቸውና እያፈረሱባቸው መሆኑን ነገረው፡፡
ንጉሡ፡- ምን ላድርግልህ ? ሲለው ነህምያ አስቀድሞ ወደ እግዚአብሔር የጸለየውን ጸሎት ይኸውም ንጉሡ የዓመት ፍቃድ እንዲሰጠውና ወደ አገሩ ሄዶ አገሩን አልምቶ እንዲመጣ መጸለዩን ነገረው፡፡ ንጉሡ እንዲሄድ ለነህምያ ፍቃድ ሰጠው፡፡ ነህምያ በንጉሡ ስር ባለችው አገሩ ሄዶ አገሩን እንዲያለማ የሚያስችለውን የመሥሪያ ፈቃድ ደብዳቤም ይዞ ነበር፡፡
የነህምያን መምጣትና የጀመረውን ከተማዋን መልሶ የመሥራት ጅማሬ የሰሙ ጠላቶቹ ተበሳጩ ፤ የፈረሰው መልሶ ሊሠራ ስለሆነ ተቆጡ ፤ ተስፋ የሚያስቆርጥ ንግግርም ተናገሩአቸው፡፡ ነሀምያ ግን፡- የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል እኛም ተነሥተን እንሠራለን በማለት ራሱን ሕዝቡንም ሁሉ አበረታ፡፡ ነህምያ ፡- የሰማዩ አምላክ ያከናውንልናል ብሎ እግዚአብሔርን ተማመነ እንጂ የወይን ጠጅ የሚያቀርብለትን ንጉሥ አለተማመነም፡፡
ነህምያ ቀድሞ መጸለዩ ወደ ንጉሡ ገብቶ ፈቃድ ሲጠይቀው መከናወን እንዲሆንለት ወደ አገሩም ሄዶ ለሚሠራው ሥራ አሁንም እንዲከናወነለት አምላኩ ረድቶታል፡፡
እግዚአብሔርን እያመለክን ስንኖር እርሱ ደግሞ የኛን ነገር የሚያከናውንልን ፣ ነገራችንን የሚሠራልን አምላክ ነው፡፡ መሥራት ያቃታችሁን ነገር ወዳጃችሁ ግን የሚችለውን ጉዳይ ወደ ወዳጃችሁ ሄዳችሁ፡- ሥራልኝ እንደምትሉት በጸሎት የነገርነውን ነገር እግዚአብሔርም የሚሠራልን አምላክ ነው፡፡
መከናወን እንዳይኖረን ሰዎች የቱንም ያህል ቢደክሙ የፈጠረን በደሙ የዋጀን አምላክ ነገራችንን ያከናውንልናል፡፡ እኛ ማከናወን ያቃተንን ነገር የሰማይ አምላክ ያከናውነዋል፡፡ ይከናወናል ብለን የማንጠብቀውን ነገር ሁሉ የሚያከናውንልን አምላክ አለን፡፡ ክርስቲያን በሚያከናውንለት አምላክ ሁሌም ተስፋ ያለው ነው፡፡
ክርስቲያን ያለ ተስፋ በምድር ላይ አይጓዝም፡፡ በሰማይም ቤት ያለው ተስፈኛ ነው፡፡ ተስፋውን ደግሞ የጣለው በሚያከናውንለት አምላክ ነው፡፡ ሰው ከሌለህ ምንም ነገር አይከናወንልህ የሚባልበት ዘመን ላይ ነው ያለነው፡፡ የሚያከናውንለትን አምላክ የያዘ እርሱ ከሰው በላይ የሆነ አምላክ አለው ፡፡ እንግዲህ ሰው የለኝም ማን ይረዳኛል? ለሚል ሰው የሰማይ አምላኩ በራሱ መንገድ ያከናውንለታል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን !
ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን (ሰባኬ ወንጌል )
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 120 |
| 14 | ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 97 |
| 15 | ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ በሦስተኛው ቀን ተነሣ ::
እኔ ደግሞ የተቀበልሁትን ከሁሉ በፊት አሳልፌ ሰጠኋችሁ እንዲህ ብዬ፡- መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ፥
ለኬፋም ታየ በኋላም ለአሥራ ሁለቱ፤
ከዚያም በኋላ ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች በአንድ ጊዜ ታየ፤ ከእነርሱም የሚበዙቱ እስከ አሁን አሉ አንዳንዶች ግን አንቀላፍተዋል፤
ከዚያም በኋላ ለያዕቆብ ኋላም ለሐዋርያት ሁሉ ታየ፤
ከሁሉም በኋላ እንደ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ደግሞ ታየኝ። እኔ ከሐዋርያት ሁሉ የማንስ ነኝና፥ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ስላሳደድሁ ሐዋርያ ተብዬ ልጠራ የማይገባኝ፤ ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ የሆንሁ እኔ ነኝ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋው ከንቱ አልነበረም ከሁላቸው ይልቅ ግን ደከምሁ፥ ዳሩ ግን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው እንጂ እኔ አይደለሁም።
እንግዲህስ እኔ ብሆን እነርሱም ቢሆኑ እንዲሁ እንሰብካለን እንዲሁም አመናችሁ ( 1ቆሮ 15 ÷ 3 - 11 ) ።
ማብራሪያ
ሐዋርያው ጳውሎስ ክርስቶስ ከሙታን መነሣቱንና ለዘረዘራቸው ሰዎች መታየቱን ይገልጣል ፡፡
1) ለኬፋ
ኬፋ የሐዋርያው የጴጥሮስ ሌላኛው ስሙ ነው ( ዮሐ 1 ÷ 43 ) ፡፡ ክርስቶስ፡- አላውቅህም ብሎ ለካደው ለጴጥሮስ ተገልጦ ታይቶአል ፡፡ ጴጥሮስ የቀድሞ ስሙ ስምዖን ነበር ( ሉቃ 24 ÷ 34 ) ።
2) ለአሥራ ሁለቱ
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ሲገለጥላቸው ይሁዳ ስለሌለ አሥራ አንድ ነበሩ ፡፡ በመጀመሪያው ሲገለጥላቸው ቶማስም ስላልነበረ አሥር ነበሩ ( ዮሐ 20 ÷ 19 - 29 ) ፡፡ በሁለተኛው ለአሥራ አንዱ ሲገለጥ ቶማስ ነበረ ፡፡ ይሁዳም ጎድሎ ስማቸው አሥራ ሁለቱ ተብለው ይጠቀሳሉ ፡፡ በይሁዳ ፋንታ ማትያስ 12ተኛ ሆኖ የተቆጠረው ጌታችን ካረገ በኋላ ነው ( የሐዋ 1 ÷ 15 - 26 ) ፡፡
3) ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች
አንዳንዶች ያላቸው በሕይወተ ሥጋ የሌሉ ቢሆኑም 1ኛ ቆሮንቶስን እስከ ጻፈበት ጊዜ ድረስ የሚበዙት ግን በሕይወተ ሥጋ ስለ ነበሩ ፡፡
4) ለያዕቆብ
ያዕቆብን ለብቻው ያመጣዋል ፡፡ የጌታ ወንድም ተብሎ የሚጠራው ነው የሚሆነው ፡፡ ራሱን ግን የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ብሎ ነው የሚጠራው ( ያዕ 1 ÷ 1 ) ፡፡ ከትንሣኤ በፊት አላመነም ነበር ( ማቴ 13 ÷ 55 ፡ 56 ፣ ዮሐ 7 ÷ 5 ) ፡፡ በመጀመሪያው የሐዋርያት ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረገም ነበር ( የሐዋ 15 ÷ 13 - 21 ) ፡፡
5) ለሐዋርያት ሁሉ
12ቱ ደቀ መዛሙርት ሐዋርያት ተብለው ይጠራሉ ፡፡ ከበላይ እንደ ተገለጠላቸው ጠቅሶ ነበር ፡፡ መልሶ አምጥቶአቸዋል ፡፡ ሲያርግም ከማረጉ በፊትም አርባ ቀን ይታያቸው ነበር ( የሐዋ 1 ÷ 1 - 3 )
6) ለራሱ ለጳውሎስም
ጳውሎስ የቀድሞ ስሙ ሳውል ነበር ፡፡ በክርስቶስ ያመኑትን ያሳድድ ነበር ፡፡ የሚሳድዳቸውን የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ብሎ ጠርቶአቸዋል ፡፡ ያመኑትን በሚያሳድድ ሰዓት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጦለት አምኖአል ( የሐዋ 9 ÷ 1 - 9 ) ፡፡
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቢገለጥለትም ራሱን፡- ጭንጋፍ በማለት ይጠራል ፡፡ ከሐዋርያት የሚያንስና ሐዋርያም ተብሎ ሊጠራ የማይገባው መሆኑን ጠቅሶ የሆነለት በሥራው ሳይሆን በእግዚአብሔር ጸጋ መሆኑን ተናግሮአል ፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ ያልጠቀሳቸው ጌታ የተገለጠላቸው ሌሎችንም ከወንጌል መጥቀስ ይቻል ነበር ፡፡ ሐዋርያው ስለ ክርስቶስ መነሣት ምስክሮች የሚሆኑትን ከበላይ ያሉትን ሰዎች ያቀረበው ከቆሮንቶስ ሰዎች አንዳንዶች ስለ ትንሣኤ ሙታን የተጠራጠሩ ስለ ነበሩ ነው ( 1ቆሮ 15 ÷ 12 - 19 ) ፡፡
ሐዋርያት ፡- ተነሥቶአል ብለው እንዳስተማሩ እርሱም፡- ተነሥቶአል ብሎ ማስተማሩንና ያመኑትን ደግሞ ፡- እናንተም እንዲህ አመናችሁ ብሎአቸዋል ፡፡
ሞተ ፣ ተቀበረ ፤ ተነሣ የሚሉት ቁልፍ ቃላት ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ናቸው ፡፡ ክርስትና ስለ ክርስቶስ የምንሰብከውና የምናስተምረው ሃይማኖት ነው ፡፡ ክርስቶስ የሞተው ስለ ኃጢአታችን ነው ፡፡ ሁሌም ልንዘነጋው የማይገባ ቃል ነው ፡፡
ስለ ኃጢአታችን ሞተ ፤ ተቀበረ ፤ ሞቶ አልቀረም በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶአል ፡፡
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በሌላ ጊዜ እንዲሁም በግንቦት 30 ቅዳሴ ሲቀደስና ከቁ.1 - 12 ያለው በሚነበብ ሰዓት ከበላይ የጠቀስኩት ክፍል ይነበባል ( መጽሐፈ ግጻዌን ይመልከቱ ) ፡፡
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 141 |
| 16 | ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 101 |
| 17 | እግዚአብሔር መፈጸሙ ላይቀር ፣ አይሳካም ብለን የኛ መደምደም ፡፡
እግዚአብሔርም ሳሙኤልን፡- በእስራኤል ላይ እንዳይነግሥ ለናቅሁት ለሳኦል የምታለቅስለት እስከ መቼ ነው? ..በልጆቹ መካከል ንጉሥ አዘጋጅቻለሁና ወደ እሴይ ..እልክሃለሁ አለው።
ሳሙኤልም.. እሴይንና ልጆቹንም.. ጠራቸው። እሴይም ከልጆቹ ሰባቱን በሳሙኤል ፊት አሳለፋቸው። ሳሙኤልም እሴይን፡- እግዚአብሔር እነዚህን አልመረጠም አለው።
ሳሙኤልም እሴይን፡- የቀረ ሌላ ልጅ አለህን? አለው። እርሱም፡- ታናሹ ገና ቀርቶአል፤ እነሆም፥ በጎችን ይጠብቃል አለ። ሳሙኤልም እሴይን፡- ..ልከህ አስመጣው አለው።
ልኮም አስመጣው፤ ..እግዚአብሔርም፡- ይህ ነውና ተነሥተህ ቅባው አለ። ሳሙኤልም የዘይቱን ቀንድ ወስዶ ..ቀባው.. ( 1ሳሙ 16 ÷ 1 - 13 ) ።
እንዲህም ሆነ፤ ዳዊት ፍልስጥኤማዊውን ( ጎልያድን ) ገድሎ በተመለሰ ጊዜ፥ ..ንጉሡን ሳኦልን ሊቀበሉ ሴቶች ..ወጡ። ሴቶችም፡- ሳኦል ሺህ፥ ዳዊትም እልፍ ገደለ እያሉ ..ይዘፍኑ ነበር።
ሳኦልም ..ይህም ነገር አስከፋው፤ ..በነጋውም ..ዳዊትም ..በገና ይመታ ነበር። ሳኦልም፡ ዳዊትን ከግንቡ ጋር አጣብቄ እመታዋለሁ ብሎ ጦሩን ወረወረ። ዳዊትም ..ከፊቱ ዘወር አለ ( 1ሳሙ 18 ÷ 6 - 10 ) ።
ሳኦልም ለልጁ ለዮናታንና ለባሪያዎቹ ሁሉ ዳዊትን ይገድሉ ዘንድ ነገራቸው። ..ዮናታን ግን ዳዊትን እጅግ ይወድድ ነበር ( 1ሳሙ 19 ÷ 1 - 10 ) ።
ዳዊትም .ወደ ዮናታንም መጥቶ፡- በእኔና በሞት መካከል አንድ እርምጃ ያህል ቀርቶአል ብሎ ማለ ( 1ሳሙ 20 ÷ 1 - 3 ) ።
( የሳኦል መሞት )
ፍልስጥኤማውያንም ከእስራኤል ጋር ተዋጉ፤ በዚያም ቀን ሳኦል ሦስቱም ልጆቹ.. ሞቱ ( 1ሳሙ 31 ÷ 1 ፡ 6 )።
የእስራኤልም ሽማግሌዎች.. ንጉሥ ይሆን ዘንድ ዳዊትን ቀቡት። ..መንገሥ በጀመረ ጊዜ የሠላሳ ዓመት ልጅ ነበረ፥ አርባ ዓመትም ነገሠ ( 2ሳሙ 5 ÷ 3 ፡ 4 ) ።
ማብራሪያ
እግዚአብሔር ሳኦልን ንጉሥ አድርጎ በእስራኤል ላይ ቢሾመውም እግዚአብሔርን ስላላከበረ ናቀው ( 1ሳሙ 15 ÷ 1 - 30 ) ፡፡ ለሳኦል ለሚያለቅሰው ለነቢዩ ሳሙኤል ወደ እሴይ እንዲሄድ ነገረው ፡፡ እግዚአብሔር ከእሴይ ልጆች ሊያነግሠው የፈለገው ሰው ነበር፡፡
ሳሙኤል እሴይን አስጠራ፡፡ እሴይም ሰባት ልጆቹን ይዞ ቢመጣም ለንጉሥነት አልተሾሙም ፡፡ የተወውን ዳዊትን ሲያስመጣ እግዚአብሔር ዳዊት ንጉሥ ሆኖ እንዲቀባ ስለ ተናገረ ተቀባ፡፡
ንጉሥ እንድትሆኑ የተቀባችሁት እናንተ ብትሆኑ እንዴት ባለ ዓይነት ተስፋ እንደምትሞሉ አስቡት? በአእምሮአችሁ ምን ዓይነት ቤተ መንግሥት እንደምትገነቡና ሌላም ብዙ ጥሩ ነገር እንደሚመላለስ?
ወደ ዳዊት ልመልሳችሁ ፡፡ በአንድ ወቅት ዳዊት ጎልያድን ገድሎ ሲመለስ ሴቶች ዳዊትን ከንጉሡ ሳኦል በላይ ጀግና ገዳይ አድርገው ስለ ዘፈኑለት ሳኦል ተከፋ ፡፡ በነጋታው ሊገድለው ጦሩን ቢወረውርበትም ዳዊት አመለጠ ፡፡
ሳኦል ዳዊትን ለሚወደው ለልጁ ዮናታንና ለባሪያዎቹ ዳዊትን እንዲገድሉት ትእዛዝ ሰጠ ፡፡ በሳኦል ሞት ስለ ተዛተበት ዳዊትም ፡- በእኔና በሞት መካከል አንድ እርምጃ ያህል ቀርቶአል በማለት የሚሞት መስሎ ተሰማው ፡፡ ትነግሣለህ የተባለውን ተስፋ ዘነጋው፡፡
ወደ እናንተ ልመለስ ፡፡ ከአዲስ አባባ ተስታችሁ ራቅ ወዳለ ቦታ ለመሄድ ፈልጋችሁ መኪናችሁን እያስከረከራችሁ በታላቅ ወኔ ጉዞ ጀመራችሁ ልበል፡፡ ብዙ ኪሎ ሜትር ከተጓዛችሁ በኋላ እደርስበታለሁ ያላችሁበት ቦታ ስለ መድረሳችሁ ያላችሁ ተስፋ እየተሸረሸረ መጥቶ መኪናችሁን ማሽከርከር አቆማችሁ ፡፡
መኪናችሁን በተመለከተ ምንም ዓይነት ችግር አላጋጠማትም ፡፡ ነዳጅ አላት ፡፡ የቴክኒክ ችግርም አላጋጠማችሁም ፡፡ እናንተ ሞተርዋን ጥፍጥፍት ሳላደረጋችሁኋት ቆመች ፡፡ ችግሩ ማን ጋር ነው? መኪናዋ ጋር ወይስ እናንተ ጋር ? ችግሩ እናንተ ጋር ነው፡፡ መኪናዋን አስነሥታችሁ ማሽከርከር ብትጀምሩ ወደፊት መጓዝ ትችላላችሁ ፡፡
ንጉሥ እንድትሆኑ እንደ ዳዊት የተቀባችሁት እናንተ ብትሆኑ ስላችሁ እንዴት ባለ ታላቅ ተስፋ እንደ ተሞላችሁ አታስታውሱም ? ታዲያ አሁን ለምን ዛላችሁ? መጀመሪያም ተስፋ ያደረጋችሁት እግዚአብሔርን ነው ፡፡ አሁንም ተስፋችሁን በእርሱ አድርጉ፡፡ እርሱ ያደርገዋል ፡፡
እንደሚነግሠው እንደ ዳዊት እንደምትነግሡ አስቡና በተስፋ ተሞሉ ፡፡ አሁንስ ያቆማችኋትን መኪና ማሽከርከር አትጀምሩም ? ልባችሁን በብርታት የሚሞላውን የዳዊትን መጨረሻ ላሳያችሁ ፡፡
ዳዊትን ካልገደልኩ ይል የነበረው ሳኦል ከጠላቶቹ ጋር ውጊያ አድርጎ ሳይቀናው ቀረና ሞተ ፡፡ እሞታለሁ ይል የነበረው ዳዊት ደግሞ እግዚአብሔር የተናገረውን ሳያስቀርበት አነገሠው ፡፡ ወደ ዳዊት አንድ እርምጃ የቀረው ሞት ባለበት ሲቆም ዳዊት ግን እንኳን ሊሞት ሊያውም አርባ ዓመት ነገሠ፡፡ ከመንገሡ በፊት ያጋጠመው መከራ ትንሽ፣ የንግሥናው ዘመን አበዛዙ !
ከእግዚአብሔር እንደምንቀበል ተስፋ ያደረግነው ነገር እኛ ከመዛላችን የተነሳ ሊሳካ አይችልም ብንልም እግዚአብሔር ግን የገባልንን ተስፋ ይፈጽማል ፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ አሜን !
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 121 |
| 18 | ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 103 |
| 19 | የጸሎት ኃይል ::
… ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።
ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥ ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች ( ያዕ 5 ÷ 16 -18 ) ።
ማብራሪያ
አንዳችን ለሌሎቻችን መጸለይ አለብን፡፡ ብርቱ ያልነው ሰው ሀዘን ( ለቅሶ ወይም መከራ ) ቢያጋጥመው እንደ ሌላው ጊዜ ተግቶ ሊጸልይ አይችልም፡፡ በዚህ ጊዜ የሌሎቻችን የጸሎት ድጋፍ ያስፈልገዋል፡፡ ከሀዘኑ በቶሎ እንዲወጣ ብንጸልይ አገዝነው ማለት ነው፡፡ አንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ የሚለውን ቃል ተግባራዊ አደረግን ማለት ነው፡፡
የጻድቅ ሰው ጸሎት ኃይል አለው፤ ታላቅ ነገርም ያደርጋል፡፡
ኤልያስ ምን እንዳደረገ እናውቃለን፡፡ ዝናብ እንዳይዘንብ ጸለየ፤ 3 ዓመት ከ 6 ወር ያህል ዝናብ አልዘነበም፤ መልሶ ሲጸልይ ዝናብ ዘነበ፡፡ ኤልያስ ያደረገው ነገር ትልቅ ነገር ነው፡ ( 1ነገ 17 ÷ 1 - 7 ፤ 18 ÷ 41 - 46 ) ፡፡
ኤልያስ ዝናብ እንዳይዘንብ ቢያደርግም መልሶ ሲጸልይ ዝናብ እንዲዘንብ ቢያደርግም እንደኛ ሰው ( ሥጋ ለባሽ ) መሆኑን እንዳነዘነጋ ተነግሮናል፡፡
እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ የሚለው ቃል እኛም ተበረታተን እንደ ኤልያስ እንድንጸልይ ነው እንጂ፡- ጻድቁ ኤልያስ ካልጸለየላችሁ በስተቀር እግዚአብሔር አይሰማችሁም አልተባልንም፡፡ ስንጸልይ እግዚአብሔር ከኛ ከሚፈልገው ነገር አንዱ፡- ይሰማናል ብለን በእምነት እንድንጸልይ ነው፡፡
የንስሐ ጸሎት ( በቤቱ መመላለስ ላቃታችሁ ) ፡፡
ክርስቶስ ሆይ ስለ በደሌ ሞትክልኝ፤ እኔ ግን ዓለምን ትቼ አንተን መከተል አቃተኝ፡፡
ሕይወቴን ቀይረው፡፡ እንደ ቸርነትህ መጠን እኔ ኃጢአተኛውን ዛሬ ይቅር በለኝ ፡፡ ያጎበጠኝ ኃጢአቴ ከላዬ ይነሣና ይቅለለኝ፡፡
ሰው ከለመነህ በኋላ አንድ ቀን እግዚአብሔር ልመናዬን ይሰጠኛል ይላል፡፡ በደሌን ግን አንድ ቀን ይቅር ትለኛለህ የምለው አይደለም፡፡ ያጎበጠኝ ኃጢአቴ ዛሬ ከላዬ ይነሳና ይቅለለኝ፡፡
ቃልህ፡- ለምኑ ይሰጣችኋል ይላል፡፡ እኔ ግን በዓለም የተጠላለፍኩ አንተን የምበድል ነኝና ለምኑ ይሰጣችኋል ብትልም፡- አቤቱ ስማኝ ለማለት በቃልህ መሄድ ያልቻልኩ ደካማ ነኝ ፡፡
ድሀ ሰው ሲለምን ፡- ደጃችን ላይ እንድትቆምና እንጀራ እንድትለምን ማን ፈቀደልህ? እንደማይባል በፊትህ ቆሜ ይቅር እንድትለኝ እለምንሃለሁ፡፡ ድሀው ለማኝ ለምኖ ባይሰጡት፡- ስጡኝ እንጂ? የማለት መብት የለውም፡፡ እኔም እንደዚህ ድሀ ሰው ሳይገባኝ ፊትህ ቆሜአለሁ፡፡ ከቸርነትህ የተነሳ ማረኝ፡፡ ነፍሴን አሳርፋት፤ ይቅር ስትለኝ ነፍሴ እረፍት ታገኛለች፡፡
እግዚአብሔር ሆይ ካንተ ጋራ መኖር እፈልጋለሁ፡፡ እንግዲህ በመንፈሳዊ ሕይወቴ የበረታሁ እንድሆን አግዘኝ ፡፡ እንደ ኤልያስ በእምነትም መጸለይ እንድችል ጸጋህን አብዛልኝ፡፡ በሚያስፈልገኝ ሁሉ አስበኝ፡፡ ጸሎቴን ሰምተህ የምትሰጠኝ ደግሞ ስለ ጽድቄ ሳይሆን ስለ ብዙ ቸርነትህ ስትል ነው፡፡
ከበላይ ያለውን ጸሎት በሚመስል መልኩ ጠዋት ከቤታችን ከመውጣታችን በፊት ማታም ከመተኛታችን በፊት እንዲሁም በሚያስፈልገን ነገር ሁሉ እንጸልይ፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ አሜን!!
✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 140 |
| 20 | ✍ ዘማሪ ዲያቆን ንጉሤ ጥላሁን ( ወንጌል ሰባኪ ) በተጨማሪም የንድፍና የኮምፒዩተር ባለሙያ
▶️ ስብከቶቼንና መዝሙሮቼን በዩቱቤ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ
https://youtube.com/channel/UC5CXetEDzzsnMHbPAT-b_0w
▶️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMaweq
▶️ ፌስቡክ
fb.me/yeglie | 104 |
