fa
Feedback
የጥበብ ማዕድ

የጥበብ ማዕድ

کانال بسته

ዝም ብለህ ተቀላቀል! https://t.me/+EpyhX7mXLpE5MDc8 የጥበብ

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام የጥበብ ማዕድ

کانال የጥበብ ማዕድ در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 425 مشترک است و جایگاه 5 446 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 200 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 425 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 27 اوت, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -477 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -18 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 5.35% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 1.71% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 826 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 264 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 10 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
ዝም ብለህ ተቀላቀል! https://t.me/+EpyhX7mXLpE5MDc8 የጥበብ

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 28 اوت, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 425
مشترکین
-1824 ساعت
-1147 روز
-47730 روز
آرشیو پست ها
ከውሸት በላይ ጎጂ እውነት የለም።

እንዴት ነው!?
እንዴት ነው!?

ፍርሐት የገደለህ ቀን ብልጥ ሰዎች ይቀብሩሃል።

🙂
🙂

እየሠሩ መጠየቅ ና እየጠየቁ መስራት አንድ አይደሉም።

At the end of the day እንዳይሆኑብን የፈራናቸው መጥፎ ነገሮች እንዳሰብነው መጥፎ አደሉም፤ እንዲሆኑልንም የጓጓንላቸው ጥሩ ነገሮች አደሉም። በፈራነው አልጠፋንም ፤ በጓጓነውም አላረፍንም�
At the end of the day እንዳይሆኑብን የፈራናቸው መጥፎ ነገሮች እንዳሰብነው መጥፎ አደሉም፤ እንዲሆኑልንም የጓጓንላቸው ጥሩ ነገሮች አደሉም። በፈራነው አልጠፋንም ፤ በጓጓነውም አላረፍንም🙂

አንዳንዴ ማትጣላው ሰው ያስቀይምሃል። ...

‎በራሴ ላይ የጨከንኩ ይመስለኛል። ‎ይህን ሐሳብ ዛሬ በድንገት አላሰብኩትም። ለረጅም ጊዜ በውስጤ እየተጓዘ ነበር፤ እኔ ግን ስሙን አልጠራሁትም። ራሴን ስወቅስ፣ ስገስጽ፣ ስጠይቅ እና ከራሴ በጣም ብዙ ነገር ስጠብቅ እንደ ጥንካሬ ነበር የምቆጥረው። ‎ ‎በአንዱ ምሽት ግን ብቻዬን ተቀምጬ ነበር። ቤቱ ጸጥ ብሏል። ስልኬ ከጎኔ ተዘግቷል። ማንም የሚያየኝ የለም። ማንም የምናገረውን የሚሰማ የለም። በዚያ ጸጥታ ውስጥ ግን አንድ ድምፅ በጣም ግልጽ ሆኖ ተሰማኝ። ‎ ‎የራሴ ድምፅ። ‎ ‎“እንዴት እንዲህ አደረግሽ?” ‎ ‎“ይህን እንዴት አላየሽም?” ‎ ‎“ከዚህ በላይ ማሰብ አትችዪም ነበር?” ‎ ‎እነዚህን ጥያቄዎች ብዙ ጊዜ ሰምቻቸዋለሁ። ከሌሎች ሰዎች ሳይሆን ከራሴ። ‎ ‎ሌላ ሰው ሲሳሳት ግን ታሪኩን ለመስማት እሞክራለሁ። ምን እንዳደረገ ብቻ አልመለከትም፤ ምን እንዳስገደደው፣ ምን እንዳስፈራው፣ ምን እንደጎዳው እጠይቃለሁ። ‎ ‎እኔ ስሳሳት ግን ታሪኬን እረሳለሁ። ‎ ‎ስህተቱን ብቻ አያለሁ። ‎ ‎ምናልባት ይህ ነው በራሴ ላይ የጨከንኩበት ቦታ። ‎ ‎ከራሴ የጠበቅኩት ነገር በጣም ብዙ ነበር። ሁልጊዜ ጠንካራ እንድሆን ፈለግሁ። ሁልጊዜ ትክክል እንድሆን ፈለግሁ። ሰዎች ሲሄዱ እንዳልሰበር፣ ነገሮች ሲያልቁ እንዳልወድቅ፣ ሕይወት ሲከብድ እንዳልደክም ከራሴ ጠበኩ። ‎ ‎ ማልቀስ እንኳን እንደ ድክመት የቆጠርኩበት ጊዜ አለ። ‎ ‎“በርቺ።” ‎ ‎ይህን ቃል ለራሴ ብዙ ጊዜ ተናግሬያለሁ። ‎ ‎ግን አንዳንድ ጊዜ ሰው መበርታት አያስፈልገውም። አንዳንድ ጊዜ መደገፍ ይፈልጋል። አንዳንድ ጊዜ “ትችያለሽ” የሚል ሰው ሳይሆን፣ “እንኳንም አልቻልሽ፤ እረፊ” የሚል ድምፅ ያስፈልገዋል። ‎ ‎ያን ምሽት ራሴን ለረጅም ጊዜ አሰብኳት። ‎ ‎ስንት ጊዜ ተሰብራ እንደተነሳች አሰብኩ። ‎ ‎ስንት ጊዜ ማንም ሳያውቅ እንዳለቀሰች አሰብኩ። ‎ ‎ስንት ጊዜ “ደህና ነኝ” ብላ ውስጧ ግን ምንም ደህና እንዳልነበረ አሰብኩ። ‎ ‎ለምንድ ነው እኔ በራሴ ላይ የምጨክ ነው? ለሌሎች የማሳየውን ርህራሄ እንኳን ለምን አልሰጣትም? ‎ ‎ለምን ሌሎችን ይቅር ማለት ቀላል ሆኖ ለራሴ ግን ይቅርታ መስጠት እንደ ክህደት ይሰማኛል? ‎ ‎ምናልባት ራሴን ይቅር ማለት ስህተቴን ማጽደቅ መስሎኝ ነበር?። ‎ ‎አላውቅም። ‎ ‎አሁን ግን ይህን አላምንም። ‎ ‎ራስን ይቅር ማለት የተሳሳተውን ትክክል ማድረግ አይደለም። የተሳሳተውን ተቀብሎ ከዚያ በኋላ መኖርን መማር ነው። ‎ ‎ያለፈውን መቀየር አልችልም። ያኔ የተናገርኩትን መልሼ ልውሰድ አልችልም። የተሳሳተውን ውሳኔ እንዳልወሰንኩ ማድረግ አልችልም። የጠፋውን ጊዜም መመለስ አልችልም። ‎ ‎ግን አንድ ነገር እችላለሁ። ‎ ‎ያንን የቀድሞ ራሴን መጥላቴን ግን ማቆም እችላለሁ። ‎ ‎ዛሬ በጣም የምተቻት ያቺ ልጅ ያኔ የምታውቀውን ብቻ ነበር የምታውቀው። የነበራትን ጥቂት ጥበብ፣ ጥቂት ተስፋ፣ ጥቂት ድፍረት ይዛ ቀኗን ትገፋ ነበር። ‎ ‎ስለዚህ ዛሬ በእሷ ላይ ለመፍረድ ከመቆም ይልቅ ከጎኗ ለመቆም እፈልጋለሁ። ‎ ‎“አዎ፣ ተሳስተሻል።” እላታለሁ። ‎“አዎ፣ አንዳንድ ሰዎችን በተሳሳተ መንገድ አምነሻል።” ‎“አዎ፣ አንዳንድ ውሳኔዎችሽ ሊለወጡ ቢችሉ ደስ ይለኝ ነበር።” ‎ ‎“ግን እኔ አሁንም እወድሻለሁ።” ‎ ‎ምናልባት ይህ ለራሴ ለመጀመሪያ ጊዜ የምናገረው እውነተኛ የርህራሄ ቃል ነው። ‎ ‎ከዚህ በኋላ እሻሻላለሁ። እማራለሁ። እለወጣለሁ። ግን ራሴን እየጠላሁ አይደለም። ‎ ‎እንደሚያስፈልገኝ ልገስጻት እችላለሁ፤ እንደሚገባት ግን ልያዛት እችላለሁ። ‎ ‎ስትወድቅ እጇን ልይዛት። ‎ስትደክም ላሳርፋት። ‎ስታለቅስ ልተዋት። ስትሳሳት ልምራት። ‎ስትፈራ ከጎኗ ልቆም። ‎ ‎ምክንያቱም ዓለም ለእኔ ሁልጊዜ ርህሩህ አትሆንም። ሰዎችም ሁልጊዜ አይረዱኝም። ሕይወትም ሁልጊዜ አትቀልልልኝም። ‎ ‎እንግዲያስ እኔ ለራሴ ለምን ሌላ ዓለም እሆናለሁ? ‎ ‎ምናልባት ሕይወቴ ውስጥ ከሁሉ በላይ ይቅርታ የሚገባት ሰው እኔ ራሴ ነኝ። ‎ ‎እና ምናልባት ከዛሬ ጀምሮ በራሴ ላይ መጨከን ሳይሆን፣ ራሴን መያዝ መማር አለብኝ። ‎ ‎ምክንያቱም እስከዛሬ ራሴን እየገፋሁ ነው የኖርኩት፤ ‎አሁን ግን ከራሴ ጋር ... ‎ ©️ ሶሪት ‎

የቅርብህ ሰው ላንተ የተገደበ አዘኔታ አለው መጠኑን ካስጨረስው ግን ጉዳትህን እንደ ዜና ያዳምጠዋል።

ምን እያሰብኩ እንደሆነ ሃሳቤ እንኳን ለሌላ ሰው ለኔም  አይገባኝም። እኔ ሃሳብ ውስጥ ስገባ ደመና የሆንኩ ይመስለኛል ሰውነቴ እንደ ቁልል አፈር ተሸርሽሮ ብንን ብሎ ወደ ሰማይ ይጎናል። እኔን ለእኔና ለሃሳቤ ትቶ እሱ አየር ላይ ይንፈላሰሳል። ማሰቤን አልተውኩም አስባለሁ ከራሴ ጋር አወራለሁ..... «እኔ የ25 አመት ወጣት ነኝ ካሳለፍኩት መከራና ስቃይ ጋር ሲተያይ ሃያ አምስት አመት ሳይሆን አንድ ምዕተ ዓመት ያሳለፍኩ ነው ሚመስለኝ። እንደ አያቴ አረጅ ይሆን? የልጅ ልጅ አይ ይሆን? በዚህች እድሜዬ ብዙ ነገር አይቻለሁ ካየሁትም ነገር አንድ ጥሩ ነገር የለም። ምናለ ባልወለድ በእናቴ ማህፀን ደም ሳለሁ እዛው በፈሰስኩ እላለሁ። ሃገር አለኝ ብየ አፌን ሞልቸ አወራለሁ ግን በሃገሬ እንደፈለኩ መንቀሳቀስ አልችልም 10km መሄድ እፈራለሁ። እና አረጅ ይሆን....... ሰዎች በወሬ መኃል « እዚች ዓለም ላይ አምሳ አመት ኑሪያለሁ» ሲሉ በነሱ አምሳ አመት ኑሮ መቅናት ጀምሬያለሁ። ሰው ሰውነቱን ያጣበት ህሊናውን ከቦታው ነቅሎ ባዶ ስጋውን ተሸክሞ በሚዋልልበት በዚ ዘመን እንዴት አረጃለሁ። ለመሆኑ ከአሁን በኋላ የራሴ ቤት ይኖረኝ ይሆን? ኤጭ!! ደሞ የምን ቤት ነው.... ስራ አገኝ ይሆን? ኡፍፍፍፍ!!...... ደሞ የምን ስራ ነው ሃገሩ ሰላም ይሆን ይሆን?........ ሁሉም ነፃነቴን አስጠብቃለሁ በሚል አጉል ዲስኩርና እብሪተኝነት ጫካ ገብቶ እንደኔ አይነቱን የሕይወት ጥፍጥናን ማጣጣም ሚጀምረውን የእጣ ፈንታ ፅዋውን ይደፉበታል። የራሱን ጥቅም ለማስጠበቅ ብሎ በብሔሩና በጎሳው ጥላ ስር ይጠለላል። ድሮ « እለወጣለሁ፣ አገባለሁ፣ ልጅ እወልዳለሁ» የሚል ተስፋ ከፊት ለፊቴ ይብለጨለጭ ነበረ አሁን ግን ያ ብልጭልጩ ተስፋዬ ጠይሟል ። አባት የገዛ፤ የአብራኩ ክፋይ የሆነችውን ልጁን ይደፍራል!! ፣ ይጦረኛል፣ ይንከባከበኛል ፣ ብለው ዋጋ ከፍለው ከሰውነት ተራ ጎድለው ያሳደጉት ልጅ የወላጆቹን ነፍስ ይነጥቃል። ምነው ባልተወለድኩ ማለቴን አልተውም። ድሮ ጎረቤት ለጎረቤት ቡና ይጠጣሉ፣ ታመው ይጠያየቃሉ፣ ዘይትና ሽንኩርት ይዋዋሳሉ፣ ትኩስ እንጀራ በድቁስ ይበላሉ፣ .... ይሄንን የጓረቤት ፍቅር ለአሁኑ ህፃናቶች ባወራ ሚስቁብኝ ይመስለኛል። ምክኒያቱም የአሁን ጉርብትና ፍቅር እንደሌለው አጥሩን ብቻ ማሳየት በቂ ነው ። እና ይሄን ሁሉ ሚያሳየኝ መወለዴ አይደል? ባልወለድ ...።                        ✍️ Henok

የጠገብክለት ሳይሆን የደከምክለት ነው ጥሩ እንቅልፍ የሚገኝ።

የምታውቀውን ርዕስ ላለማውራት ውስጥን ማስቻል ራስን የመግዛት ጥበብ ነው።

ምን ያህል ባይገባን ነው ፍቅራችንን እንደ ሃጥያት የደበቅነው? . ..

ፀፀትን የመሰለ ደስታም በረከትም የለም።             ልብ ላለው ሰው!

በቃ!! ይሀው ነው ጥቁር እውነት 💔
በቃ!! ይሀው ነው ጥቁር እውነት 💔

ለሽንት በወጣበት ሻጩ ከውጪ ገዢው ከውስጥ ሆነው ቢገኙ ሌባ ብሎ ከመጮኽ ይልቅ ንግድ ፍቃዱንም እንዲወስድለት ነጋዴው ይማፀን ጀመር።

፡ እየተወደዱ      መውደድን ከገፉ ይቅር ማለት በዝቶ           ደጋግመው ካጠፉ መሔድን ከጅለው            መንገድ ከሰነቁ                 በምክንያት ጥርግ'ዮሽ ሲሳይ ነው ጓዛቸው       ለተገፊው ካሳ            የእግዜር አበባየ'ሆሽ!!!         አቡ(አላዛር ቴዎድሮስ)      #አበባየሆሽ፦ብስራት!

በቅርቡ በስራ ምክኒያት የተዘዋወርኩበት አዲሱ ሰፈር ገብርኤል ሰፈር ይባላል ፣ ከስራ ወጥቸ ተጣጥቤ፣ ልብሴን ቀይሬ ከጓደኞቼ ጋ እዚያው ሰፈር ላይ የምቀመጥበት መጠጥ ቤት አለ።መጠጥ ቤቱ ምሸት ምሸት ቤት ውስጥ ሰው ስለሚበዛ እኛ በረንዳ ላይ ቁጭ እንላለን ፤ በረንዳው ምቹ በመሆኑ ሰው በሌለበት ሰዓትም በረንዳው ላይ ቁጭ ብለን አላፊ አግዳሚ እናያለን። ከመጠጥ ቤቱ ትንሽ ዝቅ ብሎ የሰይድ ሱቅ አለ ከሱ ወረድ ብሎ ደግሞ "ሰላም ምግብ ቤት" አለ ። በእውነቱ አዲስ ሰፈር ላይ አዲስ ሰው መተዋወቅ ይከብዳል ብየ አስቤ ነበረ እኔ ግን በአንዴ አራት ጓደኞችን አፈራሁ፣ በፍጥነት <ጓደኛ> የሚል ማዕረግ የሰጠኋቸው ለመጠጥ ሰዓት የጨዋታ ማሞቅያነት ብየ አይደለም በቃ..... አለ አይደል ... ሁሉ ነገራቸው እኔን ነው ሚመስል ፤ የኔን ልጣጭ ነው ያገኘሁት። የወደፊት ህልማቸው፣ ፀባያቸው፣ አነጋገራቸው፣ ከነዚህ ሁሉ በተለየ ደግሞ እንድወዳቸው ካረጉኝ ነገሮች መካከል አንዱ አንባቢ መሆናቸው ነው። ቁጭ ብለን የምናወራው chit chat  ሳይሆን ስለ መፅሐፍ ዳሰሳ፣ ስለ ትላልቅ ደራሲያን የህይወት ልምዳቸውንና ዉጣውረዳቸውን ካነበብነው መፅሐፍ እያጣቀስን እንጨዋወታለን፤ ይሄ የዕለት ተዕለት ተግባራችን ሁኖ ቀጥሏል። እንደተለመደው ከዕለታት በአንዱ ቀን ቁጭ ብለን ሳለን ገብርኤል ሰፈር ከረገጥኩና እዚ መጠጥ ቤት ቁጭ ማለት ከጀመርኩ ወዲህ አንዲት ልጅ አለች ሁልቀን! ከሰይድ ሱቅ የሆነ ነገር ገዝታ ትሄዳለች። እኔም ስለ ልጂቷ ምንነትና ማንነት ጠይቄያቸው አላውቅም ነበረ ...ዛሬ ግን በአይኔ ብቻም ሳይሆን በልቤም አየኋት ጥቁር ጃፖኒ በጥቁር ፒጃማ ሱሪ ለብሳለች  .... "እቺን ልጅ ሚያውቃት አለ?"ብየ ጠየኳቸው ሰይድ ሱቅ የገባቺውን ልጅ እያየሁ " አው እኔ አውቃታለሁ" አለ ቢኒ ቀልጠፍ ብሎ "እና እሷ አንተን ታውቅሃለች?" "አዎ ተውቀኛለች ....ግን.." "ግን ምን" "አረ ሱራ ልጂቷ ሰው ምታናግር አይደለችም፤ ኩራቷና ጢባሯ አይጣል ነው" "እና ልጅቷን ካወካት ስለ ባህሪዋ ብትነግረኝ እና በድክመቷ ቀስ ብየ ብገባ" "እንቅጩን ልንገርህ ሱራፌል!! ብዙዎች ሞክረው ደክሟቸው ተመልሰዋል ..... እና የዝናሽን መጠጥ ቤት ምታሞቀውን አንተን "እሺ" ምትል ይመስልሃል?" "ይሀውልህ ቢኒ ብዙዎች አጡ ማለት እኔም አጣለሁ ማለት አይደለም ደግሞም ሞክረናል ያሉ ሰዎች ውሸታቸው ነግረውህ ቢሆንስ? እኔ አንድን ነገር ለመጀመር ካሰብኩ እና ጭንቅላቴን ካሳመንኩ ወደኋላ አልልም። prison break series movie ላይ አላየህም Michael Scofield ሞት የተፈረደበት ወንድሙን ሊያስወጣ ያንን ከባድ እና ጥብቅ ቁጥጥር ያለበትን እስር ቤት (Fox river)  የማምለጥን ወሬ ለወዳጁ ሲያወራ ፤ ወዳጁ ወሬውን ሰምቶ "ተው ይሄን ነገር እስከ ዛሬ ማንም አድርጎት አያውቅም ስለዚህ ይቅርብህ" ብሎ ሲመክረው Scofield ግን አንዴ ጭንቅላቱን ስላሳመነ ምን ብሎ እንደመለሰ ታውቃለህ? " ሌሎች ያላመለጡት ለመውጣት ስላልሞከሩ ነው እኔ ግን ለማምለጥ ወደ ኋላ አልልም "ነበር ያለው ... እኔም ቁጭ ብየ ከምብሰለሰል አንድ ቀን በድፍረት ማውራት አለብኝ" "ግን'ኮ በድፍረት የሚደረግ ነገር ፀፀት አዝሎ እንደሚመጣ አውቀኃል?" "በድፍረት ያልኩህ ወኔ እንጂ በጭፍን የሚገባው ነገር አይደለም በጭፍን ሲደረግ ነው ፀፀትን የሚያመጣው። ደግሞም በየቀኑ በመተያየት ብዛት ወድጃት ለመጀመሪያ ጊዜ ማውራቱን እንዳልፈራ ያንን ፍራት የማስወግድበትን ድፍረት ነዉ ለማለት ያሰብኩት። እኔ ምልህ ቢኒ......" " አቤት.... ምነው?" "ስሟን ንገረኛ......" " እእእእህ!    ስሟ ያብስራ ነው " "ዋው!! ምን አይነት ስም ነው በናት!!! የፈጣሪን ስራ ቅልብጭ አድርጎ ሚመሰክር ስም የአብስራ" አልኩኝ ድምፄን አለስልሼ "እናንተ እስካሁን አላቹ እንዴ!" አሉን ሚኪና ያሬድ ከውስጥ ወጥተው ። እኔና ቢኒ ከእኛ ተለይተው ውስጥ መግባታቸውን ልብ አላልንም ነበረ ለነገሩ የኔን ልብ ያቡዬ ወስዳው እንዴት ልብ ብየ አያለሁ። "አው አለን ግን በምን ሰዓት ወደ ውስጥ ገብታቹ ነው?" አለ ቢኒ ሽቅብ እያየ "ቆይተናል አንድ የስራ ጓደኛችን ውስጥ ነበረ እሱጋ ሁነን ነው" አለ ያሬዶ "ኦው ! እናንተ እህቴ እየደወለች ነው እራት እኛ ቤት ናቹ ተነሱ እንሂድ ፤ ሂሳብም ተዘግቷል" አለን ሚኪ መቼ ይሆን እኔም "ያቡዬ ደወለች እራት እኛ ቤት ናቹ ብየ ወንፈል ምመልሰው?" " ሱራ! አንተ ሱራፌል " ብሎ ጠርቶኝ ከኃሳቤ አናጠበኝ ። እኔን ያልገባኝ ነገር ፍቅር እውር ነው እንዴ? እኔን የያዘኝ የእውር ጨንገር የያዘ ፍቅር ሳይሆን ጅል ፍቅር ነው የያዘኝ። እንዴ!!! አጃጃለኝ'ኮ                  ✍️ Henok

የሚለውጠንን ሳይሆን ሰው የሚወድልንን መስራታችን ከማደግ እንደሚያስቀረን መረዳት ነበረብን።