ru
Feedback
የጥበብ ማዕድ

የጥበብ ማዕድ

Открыть в Telegram

ዝም ብለህ ተቀላቀል! @Alazartewodros1 የጥበብ

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала የጥበብ ማዕድ

Канал የጥበብ ማዕድ (@alazartewodros1) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 158 подписчиков, занимая 5 556 место в категории Религия и духовность и 2 247 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 158 подписчиков.

Согласно последним данным от 18 сентября, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -385, а за последние 24 часа — -6, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 5.31%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 1.79% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 805 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 272 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 9.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
ዝም ብለህ ተቀላቀል! @Alazartewodros1 የጥበብ

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 19 сентября, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 158
Подписчики
-624 часа
-647 дней
-38530 дней
Архив постов
አትጨነቂ ይሄን ቃል ብዙ ሰዎች ደጋግመውባችሁ አያውቅም?😔 አንቺ ምን አለብሽ?ምን ቸግሮሽ?ምን ጎሎብሽ ነው አይንሽ እስኪያብጥ ምታለቅሽው? ለምንድነው እንዲህ ምቶኝው ፊትሽን በጭንቀት ነጠብጣቦች ስ
አትጨነቂ
ይሄን ቃል ብዙ ሰዎች ደጋግመውባችሁ አያውቅም?😔 አንቺ ምን አለብሽ?ምን ቸግሮሽ?ምን ጎሎብሽ ነው አይንሽ እስኪያብጥ ምታለቅሽው? ለምንድነው እንዲህ ምቶኝው ፊትሽን በጭንቀት ነጠብጣቦች ስለምን ታበላሻለሽ አታርፊም ብለውሽ አያቁም🥺 ወቅሰውሽ ሰድበውሽ ጥጋብ ነው እንዲህ ሚያደርግሽ ተብለሽ አታቂም??? አፍቅረሽ ነው? ብለውሽስ አያውቁም? ጭንቀትሽ ጨጓራሽን ልጦት ምግብ ሲዘጋሽ ፤በመከራ የበላሽውም ቃርቃር ሲልሽ አርግዘሽ እንዳይሆን ብለው አልተሳለቁብሽም??🥺  ወላጆሽ ላንቺ ብለው ስንት መከራ አይተው እነሱን አለመካስሽ ሆድ አስብሶሽ አያውቅም?? ደግመሽ ደጋግመሽ suicide ሞክረሽ አልሳካ ብሎሽ አያቅም??🥺 በቃ ይሄን ስሜት ካለወቅሽ አትጨነቂ አትበይኝ ተይይ 😢

ሰው ያላሸነፈው ድክመቱ ይጥለዋል። ሊጥለኝ ነው መሰል ተፈታተነኝ…

ያየሁባቸውን ሆኜ አየሁት

ነገሮች የሚያልፉበት ቅጽበት እየኖርን መሆኑን ያጠራጥራል። ያሳለፍናቸው ቀናት እና ሁነቶች የምር እንደሆኑ ማረጋገጥ  እስኪከብድ ድራስ ይፈጥናል፡ ።ሁሉም ነገር የኣይን ብልጭታ ያልህ ኣልፏል።ከመልካሙ ይልቅ ግን የክፉው ተጽእኖ ውስጥ ውስጡን ይበላል ኣልፎ ኣያልፍም ተረስቶ ኣይረሳም ። ሁል ግዜ ወደኋላ ሚጎትት ቅሬታ ኣለ። ይቅር ያላልነው ድክመት ሆኖ የቀረ ርዝራዥ.....    ተበደልን ላልነው ነገር ካሳ እየተጠባበቅን ነው? ትላንት ለምን ሁል ግዜ ክፉውን ብቻ ምናስታውስበት ሆነ ። መልካሙን መልካም ያላልንበት ምክንያት ምንድነው ? .

በደስታቸው ቀን ከረሱህ መቼም አያስታውሱህም!

መንፈሳዊነት ከሚታይበት ይልቅ አለማዊው መንፈሳዊውንም አያይዞ ይኖራል።

አዲስ አበበባ ዩንቨርስቲ ሌክቸረር አድርጎ አስቀርቶኝ እኔን ግን በጣም ሲያሳስበኝ የነበረው ከሔሉ ጋር በየቀኑ ልንገናኝ መሆናችን ነበር። እሷም በተገናኘን ቁጥር ታቱውን እንዳይላት የማታደርገው ጥረት የለም። ሴክስ ላይ የኔ ተሳትፎ እሷ እስክትጨርስ ድረስ ቀጥረው እንደቀሩበት ሰው መስኮት መስኮት ማዬት ሆነ። ቢጨንቀኝ አብሮኝ ሰቅሎ ሌክቸረር የሆነ ጓደኛዬን አማከርኩት። ከነገርኩት ሁሉ መያዝ የቻለው ግን ሔለን የኔን ፊት መነቀሷን ብቻ ነው። ይሕ ስህተቴ የህይወቴን ትልቁን ዋጋ አስከፈለኝ። የግቢው ሰው በአንዴ እሷ ላይ ተነሳባት። "Beauty And The Beast!" እያሉ ሲያሾፉብኝ የኖሩ ሰዎች እኔን ንጉስ እሷን ገረድ አድርገው ለመተረክ አላመነቱም። የሳቁብኝን ያህል ተሳለቁባት። የተዘባበቱብኝን ያህል ተዘባበቱባት። መግቢያ መውጫ አሳጧት። በምላሳቸው ብቻ...ፍቅሬን አሳበዱብኝ። በሔደችበት ሁሉ ነገር ስለማያጣት ግቢው ውስጥ የሚወራው ነገር ሁሉ ስለሷ ይመስላት ጀመር።  በሚሆነው እና በሚመስላት መሀል ያለው መስመር ተቀላቀለባት። ሴቶች ከቢሮዬ ገብተው ሲወጡ ተደብቃ ታያለች። ስዞር ያላዬኋት እየመስላት በፍጥነት ትሸሻለች።  ይዤ «ምን ሁነሽ ነው?» ስላት... «ታዋቂ አደረኩህ አሁንማ ካደኝ!» ትላለች። «ከመታወቅ ጋር ምን አገናኘው ይሔ? እነዚህ ሴቶች ማለት'ኮ ማርክ ይሰጠናል ብለው ያሰቡት መምህር ጋ ሁሉ የሚሔዱ አገር አድርሶች ናቸው!» «ምንም ብትል አትሸውደኝም!» በቃ በማያስጨንቀው ሁሉ ተጨንቃ ታስጨንቀኛለች። ክላስ ራሱ አትገባም። ተደብቃ እኔን ስትከትል ነው የምትውለው። አይኔ እያዬ እያመለጠችኝ ላድናት አልቻልኩም። የሆነ ቀን ጉዳዩን ፈፅመን እንደጨረስን «ሰሞኑን መድሀኒት ስትወስጂ አላይሽም! ሌክቸረር ሆነ ብለሽ ልታረግዥብኝ ነውዴ?» አልኳት። አልሳቀችም። ከሷ መውለድ ለኔ የህይወቴ ትልቁ ግቤ እንደሆነ እያወቀች ለዚህ ቀልዴ አልሳቀችልኝም። ዝም ብላ ነገር ስትበላ ሳይ ርቃ እንደሔደች ገባኝና የምር አሳዘነችኝ። እንዲህ የሁለታችንም ህይወት ከሚያቃውሰው ምናለ ይሔ ታቱ ቀርቶ በነበረ አስባለችኝ። ሽንት ቤት ገብቼ ተከዝኩ። ስወጣ የለችም። የለችም ከሩሙ ሳይሆን ከግቢው፣ ከሀገሩም የለችም። እልም ብላ ጠፋች። ልፈልጋት ሞከርኩ። ጓደኞቿም፣ ቤተሰቦቿም ፊት ነሱኝ። ማንም ሊተባበረኝ ፍቃደኛ አልነበረም። ግቢው አስጠላኝ። ሰላም አጣሁ። እየጠጣህ ትገባለህ በሚል በስድስት ወሩ አባረሩኝ። የግል ኮሌጆች ጋር ፓርት ታይም ማስተማር ጀመርኩ። እነሱ በህይወት እስካለሁ ድረስ ምንም ግድ ስሌላቸው ለሱሴ ተመቹኝ። ተማሪዎቹ ናቸው የሚያሳዝኑኝ። ወይ በሰዓት አልገባ። ወይ የጠቀመ ሀሳብ ይዤላቸው አልሔድ። ሙሉ ትኩረቴ የሔለን መሔድ ላይ ብቻ ነበር። ልረሳት አልቻልኩም። አሳይቶ የሚነሳኝ ነገር ሁሉ ሔለንን ያስታውሰኛል። ጎበዝ ተማሪ ሲሰንፍ ሳይ "ሔለን ሆነ" እለዋለሁ። ደመና ሁኖ አልዘንብ ሲል "ሔለን ነች የዛሬዋ ሰማይ" እላለሁ። ሲጋራ መተርኮሻ ፊትለፊታችን አስቀምጦ "ማጨስ ክልክል ነው" የሚል ማስታወቂያ የለጠፈብንን ቤት "ሔለን ሆቴል" እለዋለሁ። አምላክን ራሱ ሔለን ነው የምለው።  እያሳዩ መንሳት! 'ርሳኝ እያሉ ማስታወስ! አለም ላይ ያለ ነገር ሁሉ ሔለን ነው። ልረሳት አልችልም። በሰከርኩ ቁጥር ሒደው ከነገሯት ብዬ ላገኘሁት ሁሉ ነው እየዞርኩ ስለሷ የማወራው። አሁን አሁን ሁሉም ሰልችቻቸው ገና ስጠጋቸው ሒሳብ ከፍለው ይወጣሉ። እኔም ስገባ ሁሉም እንዲዳረስ በቻልኩት መጠን የማያውቀኝ ሰው ፈልጌ እቀመጣለሁ። ቅርንጫፎቹ ሁሉ በሀረግ ተሸፍነውበት ዛፍ ይሁን ጉቶ የማያስታውቅ ብቻውን የቆመ ነገር ካያችሁ...ያ ዛፍ እኔ ነኝ። ፍቅሯን ብቻዬን እንድሸከም ፈርዳብኝ ሒዳ ሰው መሆኔ የማያስታውቅ ባተሌ! ..... ዛሬም ባር ውስጥ እንደገባሁ እንደልማዴ የማያውቀኝ ሰው ፈልጌ ተቀመጥኩ። ገብቼ ከመቀመጤ የታምራት ደስታን «መቼቼቼ ሰለቸኝ አልኩ?» የሚለውን ለቅሶ ከፍቱብኝ። አብሬው ማልቀስ ጀመርኩ። «መጥፎ ትዝታ ቀሰቀሰ?» አለኝ ፊትለፊቴ ያለው ወጣት። «እእእእእ!» አልኩ ቀድሞ ማውራት ስለጀመረ ደስ እያለኝ። «አይዞን እንግዲህ ያለ ነው። ትኩስ ፍቅር ነው መሰል...በቅርብ ነው'ዴ የተለያያችሁት?» «ትኩስ መሆኑን ትኩስ ነው! ግን አምስት አመት ሆኖታል።» አልኩት። ግራ በመጋባት አዬኝ። «ይገርምሀል! ለኔ ሁሉ ነገር ቀርቶብኝ የእግር ጥፍሯን መቁረጥ በቂዬ ነበር። ፍቅረኛዬን ብቻ አይደለም...በልኬ የተሰራችልኝን አምላኬንም ጭምር ነው ያጣሁት።» ይበረግጋል ብዬ ያሰብከትን ያህል አልበረገገም። የምለው ገብቶታል። «ጥሩ ጊዜ አሳለፋችሁ አንድ ላይ?» አለኝ! «በጣም። በጣም እንጂ። በህይወቴ ማንንም ወድጄ አላውቅም። ቤተሰብ...ሀገር...ጓደኛ..እናት...አባት....ማንንም!! ብቸኛዋ ፍጥረት ነች እሷ። ፍቅር የሚባለውን ነገር አሳይታ ነሳችኝ።» «አውቃለሁ የሚመክርህ ሳይሆን የሚያዳምጥህ  ፈልገህ እንደምታወራኝ። ግን አንዳንድ ነገሮች የምናስበውን ያህል መጥፎ አይደሉም።» አለ ፈራ ተባ እያለ። «አቤት?» «እየውልህ ወንድሜ! ታምራት ደስታ ደስ ይላላ?» ራሴን በአወንታ ነቀነቀኩ። «እና ታምራት በመሞቱ ማዘን ይሻላል ወይስ በመፈጠሩ መደሰት?» አለኝ። ለማነፃፀር ዝም አልኩ። የማሰቢያ ጊዜ ሳይሰጠኝ ቀጠለ። «ዙሮ ተዟዙሮ ሁሉም ሰው የሆነ ቦታ ላይ ይለያያል። እድለኛ ብቻ ነው ትዝታ የሚኖረው። እየቆዘምክ በሁለት ቢራ ቋ የምታደረገው ትዝታ ካለህ ህይወት መጥፎ አይደለችም።» «እሱማ ሲመክሩት ቀላል ነው!» «ልክ ነህ። ከባድ ነው። ግን የማይቻልም አይደለም። እኔም የማፈቅራትን ሴት አጥቻለሁ። ሌላ አግብቼ እየኖርኩም አስባታለሁ። ግን ለምን እሷን አላገባሁም? ብዬ ከዩንቨርስ አሰራር ጋር ግጭት ውስጥ አልገባም። አንተም ሰላም ብታወርድ ይሻልሀል።» «አትደስኩረኝ ባክህ!» አልኩ የምመልስለት አጥቼ። «የምሬን ነው። This is life! የኔዋ ከመሔዷ በፊት ያለችኝ አንድ ነገር ነበር። 'ወደድንም ጠላንም በህይወታችን የገባን ሰው ሁሉ መለያዬት የሚባል አዘቅት ይሰለቅጠዋል። ቅርፁ ወደ ትዝታ ተቀይሮ አብሮን ይኖራል። ያ ሰው 'አለ'ም 'የለም'ም ማለት አንችልም።'  እስካሁን ድረስ ይሔንን ንግግሯን ምንም ሀሰት አላገኘሁበትም። አለች ብለህ ላታቅፋት ትችላለህ። የለችም ብለህ ለማልቀስ የሚያበቃ ድምዳሜ ላይ ግን መድረስ አትችልም። ሌላው ቢቀር አንተ ውስጥ የቀረው ትዝታ አለ። ይልቅ ቆፍጠን በልና በህይወትህ ገብታ ማወቋን ሰለብሬት አድርግ ወዳጄ። ትዝታን የሚያህል አንጡራ ሀብት ተሸክመህ እንዲሁ አታባክነው።» ዝም አልኩ እያፈጠጥኩበት። ሁኔታዬን ሲያይ እንዳሸነፈ ተሰምቶት ብርጭቆውን እያነሳ «ቺርስ ለትዝታችን!» አለ። ቤት ገብቼ ለመኝታ እየተዘጋጀሁም የልጁ ንግግር ተከትሎኝ መጥቷል። ያወራኝ ነገር ሁሉ ደግሜ ባሰብኩት ቁጥር የበለጠ ያሳምናል። ከዩንቨርስ/ከአምላክ አሰራር ጋር ሰላም ማውረድ እንዴት ያለ ነገር ነው? አላውቅም...በትዝታ ሀይል የኖርነውን ደግሜ ለመኖር ስል ግን ልሞክረው ፍቃደኛ ነኝ። ሔሉ ከሔደች ቡኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነገ መንቃት ፈለግኩ። ክላስ እንዳይረፍድብኝ አላርም ሞልቼ ተኛሁ። ፨፨፨፨   ✍️ ማይክል አዝመራው

"የባህር በር ማግኘት ጉዳይ በሰላም ካልሆነ በጉልበትም ቢሆን አይቀርም" ፕሮፌሰር ብረሃኑ ነጋ"‼️ ተማሪዎች ካሁኑ አስቡበት ሊያዘምታቹ ነው መሰል😁

በጠፋ መብራት መሐል ስልክህ ባትሪ ሙሉ ሲሆን እንደሚያስደስትህ… ትንሽ ገንዘብም ማግኘት በዛ ልክ ነው ታሰክረሃለች።

የዛሬን አያሳድረኝ ፤ አይኔን ግንባር ያርገው በዓል አርብ ሲሆን ደስ አይልም! ሲኖትራክ ጎማ ይውጣብኝ ስላቹ…

እንኳን አደረሳችሁ ፤ አደረሰን!
እንኳን አደረሳችሁ ፤ አደረሰን!

ሕመምህን የሚያብሰው ምን እንደሆነ ታውቃለህ? ቁስሉ የፈጠረብህን የህመም ስሜት ለማቆም ምትታገለው ነገር ነው።

በበግ ቤት በግ ገባ የተባለው ለካ እኛን ነው…ሰዉ ረክሶ በጉ ሲወደድ።        ምስኪን በጎች እምበኧ…

የሞባይል ካርድ ከሱቅ ገዝቶ በቴሌብር ከሚከፍል ሰው ጋር እንዴት ነው ስለቢዝነስ ምታወራው?

በጊዜ ያልታረመ መጥፎ ባህሪ ሲቆይ አመለኛ ያደርጋል።

የጠፋን ነገር ለማግኘት ስትፈጋ እሱ ደግሞ ላለመገኘት በዛው ልክ ይለፋል።

እንደሚያንጠባጥብ የውሃ ቅንጣት በረጅም ጊዜ ውስጥ ሸርሽረው የጎዱን ሰዎች ናቸው እኮ እንደቀላል ይቅርታ ብለው ሊያቅፉን የከጀሉት።

. ለብቻ ደጋግፈህ ያቆየኸውን ወዳጅነት የለቀከው እለት እንደቁራ መልእክተኛ ከሄደ አይመለስም ። ጨክኖ በመተውና እያባበሉ በማክረም መሃከል የተወተፈ ነፍስ ምርጫ... .

፡ በደከመ ገላ         በቆሰለ ልቤ እጅግ በተገፋ                ሳልውል አልቀረውም          ሳላስብሽ አንቺን                     በይሆናል ተስፋ ! የ'ውነት ወድጄሽ ነው         እመኚ ተግባሬን                       አንደበቴን ትተሽ እሳት መሞቅ 'ሚያምር              ብለው ሲቆሙ ነው                            ከመሐሉ ገሸሽ…         አቡ(አላዛር ቴዎድሮስ)

፡ እሄድባት የነበረች ‎         የማህሏ ቀጭን መስመር ‎ለእኔ ሰፍታ እንደልቤ ‎                   ታስደስተኝ እንዳልነበር ‎ ‎ወይ ስጠራት አልሰማችኝ ‎                     ስታነሳኝ አልሰማሁም ‎ከእኔ እርቃ ወይ ጠፍታለች ‎                 ወይም ደግሞ እኔ የለሁም ✍ Mekdi @amen1995