en
Feedback
የጥበብ ማዕድ

የጥበብ ማዕድ

Closed channel

ዝም ብለህ ተቀላቀል! https://t.me/+EpyhX7mXLpE5MDc8 የጥበብ

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel የጥበብ ማዕድ

Channel የጥበብ ማዕድ in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 318 subscribers, ranking 5 524 in the Religion & Spirituality category and 2 224 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 318 subscribers.

According to the latest data from 03 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -469 over the last 30 days and by -15 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 6.03%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 1.93% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 924 views. Within the first day, a publication typically gains 296 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 11.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ዝም ብለህ ተቀላቀል! https://t.me/+EpyhX7mXLpE5MDc8 የጥበብ

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 04 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 318
Subscribers
-1524 hours
-1017 days
-46930 days
Posts Archive
ከ48.1 ሚሊዮን ብር በላይ በሚሆን የካፒታል በጀት የተገነባው ድልድይ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነ። በደቡብ ወሎ ዞን አልብኮ ወረዳ ለዘመናት የነበረውን የትራንስፖርት እንግልት የሚቀርፍና በርካታ ቀበሌዎ
+3
ከ48.1 ሚሊዮን ብር በላይ በሚሆን የካፒታል በጀት የተገነባው ድልድይ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነ። በደቡብ ወሎ ዞን አልብኮ ወረዳ ለዘመናት የነበረውን የትራንስፖርት እንግልት የሚቀርፍና በርካታ ቀበሌዎችን እርስ በእርስ የሚያስተሳስር የ48 ሜትር ርዝመት ያለው የሳልሜኔ ወንዝ የኮንክሬት ድልድይ ግንባታ በሙሉ ጥራትና በፍጥነት መጠናቀቁ ተበሰረ። ላም የሆነች ሀገር አላቢዎቿ ብዙ!

እንደ በቀሉ ሳይሆን እንደ ቃሉ መኖር የችሎታህን ጥግ ያሳያል።

​«ልጅን በስርዓት ማሳደግ» ወይስ «የሰውን አፍ መፍራት»? ​በማህበረሰባችን ልጅ ማሳደግ ሲባል መቆጣት፣ መግረፍ ወይም ጥሩ ትምህርት ቤት ማስገባት እንደ ዋና መስፈርት ይወሰዳል። ነገር ግን ቆም ብለን ብናስበው፡ አብዛኛው ወላጅ የሚያደርጋቸው ነገሮች ለልጁ አስቦ ነው ወይስ «ሰው ምን ይለኛል?» በሚል ፍርሃት? ​ብዙ ጊዜ «ለልጅህ ብዬ ነው» የሚባሉት ውሳኔዎች የልጁን ፍላጎትና የወደፊት ጥቅም ያገናዘቡ ሳይሆኑ፣ የወላጆችን ፍላጎትና የሰውን አፍ ለመሸፈን የሚደረጉ ናቸው። የልጁን እውነተኛ ፍላጎትና ጥቅም ሳይሆን የራሳቸውን ፍላጎትና የማህበረሰቡን መስፈርት ለማሟላት የሚደረግ ጉዞ... ልጅን በአግባቡ ማሳደግ ሊባል ይችላል?

ቡና አፍልታ ፣ ዕራት አቀራርባ ረከቦቶ ፊት ለፊት ትንሺዬ ኩርሲ ወንበር ላይ ቁጭ ብላ ያለወትሮው ስራ ቦታ ያመሸውን ባሏን ትጠብቀዋለች...... መጠበቁ ስልችት ሲላት ስልኳን አንስታ ትደውላለች....... «ሄሎ    ...... ሄሎ  ሄሎ» «ይሰማኛል ,,,   ,,, የት ሁነህ ነው ቆየህ'ኮ» «ምንድነው ምትይኝ አይሰማኝም ናቴ » «የት ሁነህ ነው? ካልተሰማህ speaker ላይ አርገው» ስፒከር on እንዳረገ የባሏ ድምፅ ተውጦ አጠገቡ ላይ የሚለፈልፉት ሰዎች ስልኩን ከጁ የቀሙ ይመስል ድምፃቸው በጉልህ ይሰማት ጀመር........  «ተነገ ወዲያ ወደ ጎጃም ልሄድ ነበር መንገዱ ክፍት ነው?» ይላል አንዱ ድምፀ ቀጭን «አባቱ የሰጠሀኝ መልስ ልክ አይደለም ሃያ ብር ይጎለዋል» «ሽንኩርትና ድንች እንደ ዳይኖሰር ጠፉ እንዴ? ጉሊቶችም ቲማቲምና ቃሪያ ብቻ ነው የሚሸጡት» «ነገ አርሴ ካላሸነፈ ቁርስና ምሳዬ አልበላም»። የባሏን ድምፅ ውጦ ይሄን እንደ እስስት ብዙ መልክ ያለውን የታክሲ ወሬ መስማት ሲሰለቻት ስልኩን Hang up አረገችና በሃሳብ ባህር ሰጠመች ያሉበትን ሁኔታ አምኖ አለመቀበል ፣ ሁል ጊዜ ማማረር ፣ በትንሹ መጨነቅ ፣ ነገ ለሚስተካከለው ነገር ዛሬን ራስን ጥሎ በድባቴ ማሳለፍ መቼ ይሆን የምናቆመው? በእጃችን ላይ ያለውን ዘንግተን፤ በእጃችን ላይ የሌለውን ነገር እያሰብን ማማረር መቼ ይሆን ሚበቃን?፣ ጎዶሎውና ጨለማው ላይ ማፍጠጡን መቼ ይሆን ምናቆመው? ቢኖረንም ባይኖረንም መቼ ይሆን #ተመስገን የምንለው? ይህንን እያሰበች ባሏ በሩን አንኳኳ.. ሩጣ ከፈተች ብቻውን አልነበረም ጓደኛው አብሮት አለ ሰላም ተባባሉና ለዕራት ቁጭ አሉ። «ብሩኬ ዕድለኛ ነህ ቡና በማፍላቴ መጣህ» «ይሄ ዕድል ነው ብለሽ ነው» «እናሳ! አንተ ሁሌ እኛ ቤት ስትመጣ ምንም ነገር ሳይዘጋጅ በባዶ ነበረ ምትወጣው፤ ዛሬ ግን ሁሉ ሙሉ ሁኖ ጠበቀህ፤ ዕድል ማለት ያልተለመደ ነገር ሲገጥምህ ዕድል ይባላል» « አይ ቤዚ! ዕድል'ኮ ይከተለኛል እኔ ነኝ እንጂ ምቀየስበት ደሞም ዕድልን ለማግኘት ምተከፍይው ዋጋ አለ ያ ዋጋ ከተከፈለ ነው ዕድልም የሚመጣው» «እንዴ! ዛሬ ምን ዓይነት ወሬ ነው ምታወሩት? ሲበላ አይወራም ዝም በሉ» አለ ባሏ።                     ✍️ Henok

እንደ ሀገር ስትቀነጭር ግለሰብ አምጥተህ አወዳድረህ ፖለቲካዊ ዘፈን ትከፍታለህ።

አንዳድን ነገር ይለመዳል እንጂ አይቀየርም።

ገንዘብ ለቸገረው አካውንት ቀይርለት ብር ያገኘ እንዲመስለው አሉ።😁

ሳትፈለግ ስትቀር ስትደክም ትተካለህ እንጂ አታርፍም።

12ኛ ክፍል ፈተና የወደቀች ልጅ ራሷን አጠፍች❗ ዛሬ በሲዳማ ክልል በምስራቃዊ ሲዳማ ዞን በንሳ ዳዬ አንድት ሴት ልጅ ከ12ኛ (entrance) ተፈታኝ ባለማለፏ ምክንያት ተበሳጭታ #ቦኖራ ተብሎ በሚ
12ኛ ክፍል ፈተና የወደቀች ልጅ ራሷን አጠፍች❗ ዛሬ በሲዳማ ክልል በምስራቃዊ ሲዳማ ዞን በንሳ ዳዬ አንድት ሴት ልጅ ከ12ኛ (entrance) ተፈታኝ ባለማለፏ ምክንያት ተበሳጭታ #ቦኖራ ተብሎ በሚጠራው ጥልቅ ወንዝ ውስጥ እራሷን አጥፍታለች። ነፍስ ይማር❗ #አዩዘሀበሻ አለማለፍ የውድቀት ጥግ አልነበረም! ሁሌም ምርጫ ሁሌም መንገድ አለ እኛም በጊዜአችን ወድቀናል ግን ደግሞ መውደቅ እድሜ መጨረስ አይደለም! እድሜ ጥይት ነው ጥይትህ እስካላለቅ ኢላማህን ለመምታት የመሞከሩ እድል አለሕ።

ለድሃ ጌታው እምነቱ ፤ እምነቱም ጌታው ነው።

ገንዘብ ሰጥተውህ ድፍረትን ከሚነጥኩህ ድፍረት ኖሮህ ገንዘብ ባይኖርህ ይሻላል።      ካወክበት ድፍረትም ገንዘብ ነው።

ጠላታችሁን ውደዱ ! ሲለን ፤ እሱ ጠላቱን በገሃነም እየቀቀለ ያለ አይመስልም°°°😁🤭

በብዛት ፍላጎትህ ላይ እንጂ የሚሆነው ላይ መብት የለህም!

ሁሉ ከአዲስ አይጀመርም ሁሉ አይተውም ሁሉ አይረሳም በሁሉ አይጨከንም ከሁሉ ወዳጅነት እንደሌለ ከሁሉ ጥልም የለም አዲስ ስለተገኘ የነበረ ሁሉ አይጣልም አንዳንዴ የነበረን ጠግኖ አጥቦ አቃንቶ አድሶ ማስቀጠል ነው ልክነት..

አንዳንዶች እድሉን ስላገኙት እንጂ ከኛ ተሽለው አይደለም የበለጠ ቦታ ላይ የተቀመጡት።         ይድረስ ከነጮች ጋር በ english ቋንቋ ሲንተባተብ ለሰማውት ለ top manager አለቃዬ😁

መገረምን ማለፍ ነው ለመፍጠር ሚያበቃ።

ሰው አብዝቶ የሚያወራው የሚያስበው ስለራሱ ነው።በሰው ምን አለኝ አትጨነቅ!

. ሰው እየለመደው ሲሄድ ስለመልካምነት ብቻ ያደረከውን እንደግዴታህ ያየው ይጀምራል። ሳት ያለህ እለት.......አያድርስ ነው .

#አንዳንዶች ጉዳይ ማጣታቸው እንጂ እንዲፈልጉህ ያደረገው ጉዳይ ሆነህባቸው አይደለም።

ማፈስን እንደመብት ከቆጠረ አካል ሀቅህን እንደ ደሞዝ አጠብቅ እሱ እንደጽድቅ ስራ ስለሚያየው።